ሱፍይ (ተሶውፍ)


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


ﺑﺄﺑﻲ ﻭﺃﻣﻲ ﺃﻧﺖ ﻳﺎ ﺧﻴﺮ ﺍﻟﻮﺭﻯ
ﻭﺻﻼﺓُ ﺭﺑﻲ ﻭﺍﻟﺴﻼﻡُ ﻣﻌﻄﺮﺍ ⚘
ﻳﺎ ﺧﺎﺗﻢَ ﺍﻟﺮﺳﻞ ﺍﻟﻜﺮﺍﻡ ﻣﺤﻤﺪٌ
ﺑﺎﻟﻮﺣﻲ ﻭﺍﻟﻘﺮﺁﻥ ﻛﻨﺖَ ﻣﻄﻬﺮﺍ ⚘
ﻟﻚ ﻳﺎ ﺭﺳﻮﻝ ﺍﻟﻠﻪ ﺻﺪﻕُ ﻣﺤﺒﺔٍ
ﻭﺑﻔﻴﻀﻬﺎ ﺷﻬِﺪ ﺍﻟﻠﺴﺎﻥُ ﻭﻋﺒّﺮﺍ ⚘
ለበለጠ መረጃ
@ABDU_RESHID

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


ተሰውፍ በአሏህ ሱ.ወ መመካትን ማረጋገጥ እና የቀልብን ማረፊያ ማሳመሪያ ነው እንዲሁም መጥፎ ከተባሉ ባህሪ ሙሉ በሙሉ ወጥቶ ምስጉን ወደሆኑ ባህሪዎች ውስጥ መግባት ነው ።   ( አኽላቅ  🩵 )
https://t.me/YASIRAJEL_ALEM


#የጂላኒ_ረቡዕ

ሸይኽ ዑመር አብዱል ባዝ (ረዲየላሁ አንህ) እንዲህ ይላሉ፡- “አንድ ጁምዓ ከሰይዲ ሸይኽ አብዱልቃድር ጂላኒ (ረዲየላሁ አንህ) ጋር ወደ መስጂድ ጉዞ ወጣን። ሰዎች ቢያዬቸውም ማንም ሰላምታ የሰጣቸው አልነበረም። በልቤ  አሰብኩ፡- “ዘውትር ጁምዓ ወደ መስጂድ ለመድረስ በሼክ አካባቢ ይሰበሰቡ የነበሩት ሰዎች ዛሬ ምን እየሆኑ ነው?” ወዲያው ሰዎች ሼክን ለመዘየር ሲጣደፉ አየሁ። ሰይዲም በፈገግታ አዩኝና “ዑመር ሆይ፣ የፈለከው ይህንኑ ነው! የሕዝቡ ልብ በእጄ እንዳለ አላስተዋላችሁምን? ከፈለግኩ ከኔ አርቃቸዋለሁ፣ ከፈለግኩ ወደ እኔ እስባቸዋለሁ።

በአንድ ወቅት አብዱልቃድር (ረዲየላሁ አንህ) ንግግር ሲያደርጉ አቡል ሙዓሊ የሚባል ሰው በዚህ ስብሰባ ላይ ተገኝቷል። እሱ በቀጥታ በታላቁ ቅዱሳን ፊት ተቀመጠ። በትምህርቱ ወቅት አቡል ሙዓሊ የሑዙር ጂላኒ (ረዲየላሁ አንህ) መሰባሰብን መልቀቅ ክብር የጎደለው ሆኖ ስላገኘው ይህንን ፍላጎት ለመግታት ሞክሯል። ከዚህ በኋላ አቅቶት ለመሄድ ወሰነ። ይህ ሲሆን አቡል ሙዓሊ በስብሰባ ላይ ሳይሆን ውብ ለምለም ባለው ሸለቆ ውስጥ እንዳለ አወቀ። በወንዙ ውስጥ በሚፈስ ጅረት የበለጠ ተውቧል። ወዲያው የተፈጥሮን ጥሪ ተቀብሎ ዉዱእ አደረገ ከዚያም ሁለት ረከዓ ሰላት ሰገደ። ሶላትን እንደጨረሰ አሁንም በታላቁ ቅዱሳን ስብስብ ውስጥ መመለሱን ተገነዘበ። ነገር ግን ብዙ ቆይቶ አቡል ሙዓሊ የሱ ቁልፎች ከእሱ ጋር እንዳልነበሩ አወቀ። ከዚያም በሁዙር ጋውስ-አእዛም (ረዲየሏሁ ዐንህ) ጋር ወደ ሸለቆው ሲጓጓዝ ከወንዙ አጠገብ ባለው የዛፍ ቅርንጫፍ ላይ የቁልፍ ቀለበቱን ሰቅሎ እንደነበር አስታውሰ። አቡል ሙዓሊ ከዚህ ክስተት በኋላ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ለንግድ ጉዞ የመሄድ እድል አገኘ። በዚህ ጉዞ ውስጥ አንድ ሸለቆ ደረሰ እና እዚያ አረፈ ከዚያም ሸለቆው በትምህርቱ ወቅት የተጓጓዘበት ቦታ መሆኑን አስተዋለ ከዛፉ አጠገብ ሲሄድ ቁልፎቹ አሁንም በዛፉ ቅርንጫፍ ላይ ተንጠልጥለው አገኘው። ሱብሃነላህ!

የሑዙር ጓውስ-አእዛም ተማሪዎች እንደተለመደው ትምህርታቸውን እየተከታተሉ በድንገት የሼኻቸው የተባረከ ፊት ሲቀላ እና ላብ የተባረከውን ፊታቸውን ሸፍኖ እንደነበር ይገልጻሉ። ከዚያም እጃቸውን ካባው ውስጥ አስገብተው ለጥቂት ጊዜ ዝም አሉ። እጃቸውን ከካባው ውስጥ ካወጡ በኋላ፣ ከእጅጌቸው ውስጥ የውሃ ጠብታዎች ይንጠባጠቡ ጀመር። ከመንፈሳዊ ሁኔታቸው ​​የተነሣ ተማሪዎቹ ምንም አይነት ጥያቄ አላቀረቡም ይልቁንም ይህን አስደናቂ ክስተት ቀን፣እና ሰዓቱን መዝግበውታል። ይህ ክስተት ከተፈጸመ ከሁለት ወራት በኋላ በባህር ወደ ባግዳድ የመጡ ነጋዴዎች ደርሰው ለሑዙር የተለያዩ ስጦታዎችን አበርክተዋል። እነዚህን ነጋዴዎች በባግዳድ ከዚህ በፊት ታይተው ስለማያውቁ ተማሪዎቹ በዚህ ግራ ተጋብተው ነበር። ስጦታውን ያመጡበትን ምክንያት ነጋዴዎቹን ሲጠይቋቸው ከሁለት ወራት በፊት ወደ ባግዳድ በመርከብ ላይ እያሉ መርከባቸው በኃይለኛ ማዕበል ተያዘች። የመስጠም አደጋ እንዳለ ሲገባን ወደ ሸይኽ አብዱልቃድር ጂላኒ ተጣራን። ወደርሱም በተጣራን ጊዜ ከሩቅ አንዲት እጅ መርከቦቻችንን ወደ ላይ አነስታ ስጋት ከሌለበት የባህር ክፍል አሳረፈች። ተማሪዎቹ ይህንን ዘገባ በመድረሳ ውስጥ ከተፈጠረው ክስተት ጋር ሲያነፃፅሩ ታላቁ ቅዱሳን እጃቸውን ወደ ካባው ያደረጉበት፣ ቀንና ሰዓት እንደሆነ ተረጋግጧል። ሼክ አብዱልቃድር ጂላኒ  እጃቸውን ወደ ካባው ውስጥ የሚያስገቡ ቢመስልም በተጨባጭ ግን ለእርሳቸው እርዳታ የጠየቁትን ለመርዳት እጃቸውን ወደ ባህር እየዘረጉ ነበር። ሱብሃነላህ!

በሑዙር ዝና በጣም የተደነቀች የባግዳድ እናት ልጇን በእጃቸው ለመተው ወሰነች እና “ይህን ልጅ እንደራስህ ውሰደው፣ እንዳንተ እንዲሆን አሳድገው” አለች። ሼክም ልጁን ተቀብለው አምልኮትን፣ መንፈሳዊነትን ወዘተ ያስተምሩት ጀመር።ከተወሰነ ጊዜ በኋላ እናትየዋ ልጇን ለማየት መጣች እና ቀጥኖ እና ገርጥቶ አንድ ቁራሽ እንጀራ ሲበላ አየችው። ተናደደች እና ሼኩን እንድታይ ጠየቀች። እሷም በመጣች ጊዜ ሁዙር በደንብ ለብሰው፣ ደስ የሚል ክፍል ውስጥ ተቀምጠው ዶሮ ሲበሉ አገኘቻቸው። እሷም “ዶሮህን እየበላህ ላንተ የተውኩት ምስኪን ልጄ ከደረቅ እንጀራ በቀር ምንም የለውም!” ብላ ጮኸች። ሼኩ እጃቸውን በዶሮው አጥንት ላይ አስቀምጠው "አጥንቶችን ከአፈር በሚያነቃቃው በአላህ ስም ተነሳ!" ሲሉ ተናገሩ ዶሮዋ ወዲያው በህይወት ጉብ አለችና “ከአላህ በስተቀር ሌላ አምላክ የለም ሙሐመድም (ሶለላሁ ​​ዐለይሂ ወሰለም) መልእክተኛው ናቸው ሼክ አብዱልቃድር የአላህና የመልእክተኛው ወዳጅ ናቸው!” ብላ በጠረጴዛው ዙሪያ ሮጠች። ሁዙር ጂላኒ ወደ ሴቲቱ ዞር ብለው “ልጅሽ ይህን ማድረግ ሲችል የፈለገውን መብላት ይችላል” አሎት። አላሁአክበር

አንድ ጊዜ ጂላኒ ንግግር ሲያቀርቡ ሸይኽ አሊ ቢን ሄይቲ (ረዲየላሁ አንህ) ከፊታቸው ተቀምጠዋል። በትምህርቱ ወቅት ሸይኽ አሊ ቢን ሄይቲ (ረዲየላሁ አንህ) እንቅልፍ ወሰዳቸው። ሁዙር ጓውስ-አእዛም (ረዲየላሁ አንህ) ይህንን አይተው ከሚንበር ወርደው በእንቅልፍ ላይ ካሉት ሸይኽ አሊ ቢን ሄይቲ ፊት ለፊት ሁለት እጆቻቸውን በአክብሮት አጣጥፈው ቆሙ። ከትንሽ ቆይታ በኋላ ሼክ አሊ ቢን ሄይቲ ከእንቅልፋቸው ሲነቁ ሁዙር ከፊታቸው ቆመው አገኞቸው። ወዲያው በአክብሮት ከተቀመጡበት ተነሱ። ሁዙር ፈገግ ብለው እንዲህ አሉ፡- በአክብሮት ፊትህ የቆምኩበት ምክንያት ረሱል (ሰ.ዐ.ወ ) በሥጋዊ ዓይኖቼ ከአጠገብህ መመልከቴ ነበር።

ሼክ አዲ ኢብኑ ሙሳፈር (ረዲየላሁ አንህ) እንዲህ ይላሉ፡- “በአንድ ወቅት ሁዙር ንግግር ሲያደርጉ ዝናብ ከሰማይ ወረደ። ይህም አንዳንድ ታዳሚዎች እንዲበታተኑ አደረጋቸው ሼኽ አንገታቸውን ወደ ወደ ሰማይ አንሥተው፡- “እነሆ እኔ ለአንተ ስል ሰዎችን እየሰበሰብኩ እንዲህ ከኔ ትበትናቸዋለህ” አሉ። ዝናቡ ወዲያው ትምህርቱ በሚካሄድበት ግቢ ላይ መዝነቡን አቆመ፣ ምንም እንኳን ዝናቡ ሳይቀዘቅዝ ከትምህርት ቤቱ አከባቢ አልፎ ቢቀጥልም በስብሰባው ላይ አንዲት ጠብታ ዝናብ አልዘነበችም። ሱብሃነላህ!

ሸይኽ አህመድ ጃም (ረዲየሏሁ ዐንህ) የሚባሉ ታላቅ ቅዱሳን ነበሩ በየሄዱበት አንበሳ ላይ ይጓዙ ነበር። በጎበኙበት ከተማ ሁሉ የከተማዋን ህዝብ አንድ ላም ለአንበሳው ምግብ እንዲልክላቸው መጠየቅ ልማዳቸው ነበር። ከእለታት አንድ ቀን ወደ ባግዳድ ሄዱ ከደቀ መዛሙርቱ አንደኛውን ወደ ሁዙር ላኩ  ለአንበሳው ማዕድ ላም አንዲላክለት አዘዘ። ታላቁ ጋውስ መምጣቱን አስቀድሞ ያውቁ ነበር ለአንበሳው አስቀድመው ላም አዘጋጅተው ነበር። ደረሳው ላሙን ይዞ ሲሄድ ከሁዙር ቤት አካበቢ ላይ ተቀምጦ የነበረ ያረጀ ውሻ ተከተለው። ለሼኽ አህመድ ጃም ላሙን ሰጣቸው ሼኹም ለአንበሳው ላሟን እንዲበላ ነገሩት። አንበሳው ወደ ላሟ ሲሮጥ ደካማው ውሻ አንበሳውን ወረወረ ጉሮሮውና ሆዱን በመቅደድም ገደለው። እየጎተተም ከሁዙር ፊት አቀረበው። ይህን ሲመለከቱ ሼህ አህመድ በታላቁ ገውስ ፊት ራሳቸውን ዝቅ አድርገው ለትእቢታቸው ይቅርታ ጠየቁ።

*አላሁ ተአላ ለሁዙር እውነተኛ ፍቅር ይስጠን! እንደ ደካማው ውሻ በሱልጣን አውሊያ አብዱልቃድር ጂላኒ አገልግሎት ስር ያድርገን! አሚን!
https://t.me/YASIRAJEL_ALEM


🍂ኢማሙና ጁነይድ ረዲዬሏሁ ዓንሁ
"ተሰውፍ ማለት ምርጫን መተው ነው።" ይላሉ፤ ከአሏህ ውጪ ያለን ነገር ግንዛቤ ውስጥ አትክተት። ይህን ካደረግክማ አማረጥክ ማለት ነው። ከአሏህ ሱ.ወ በስተቀር ምንም አይኑርህ። እርሱን ያገኘ ምን አጣ? እርሱን ያጣ ምን አገኘ? አላህን ያዝ። ዱንያን ፣ ሀብትን ፣ ስልጣንን ፣ ዝናን ፣ ስሜትን ፣ ዘመድን ፣ ፍጡርን ሁሉ ትተህ ወደ ጌታህ ብቻ  ሽሽ .......

https://t.me/YASIRAJEL_ALEM


በኢትዮጵያ ኢስላማዊ ስነፅሁፍ ውስጥ ስሙ ከፍ ብሎ የተሰቀለው የዘመናችን ሉቅማነልሀኪም ኡስታዝ ሀሰን ታጁ ረጅም ዕድሜ ከሙሉ ዓፊያ ጋር አላህ እንዲለግሰው አጥብቀን እንማፀነዋለን !!

በባህሪዉ ፣ በዕዉቀቱ ፣ በሥራዉ ፣ በችሎታዉና በዉጤታማነቱ ታላላቆች ‹አንቱ› ይሉታል ፡፡
(ከ150 በላይ የታተሙ ፤ ከ45 በላይ ያልታተሙ) 196 የሚሆኑ መጽሓፍትን ያዘጋጀ
- ከ30 በላይ መጽሐፍትን አርትኦት የሰራ
- ከ300 በላይ መንፈሳዊና ዓለማዊ መጣጥፎች
- በኢትዮጵያ ለ3ተኛ ጊዜ ቁርዓንን ተርጓሚ
- በኢትዮጵያ የመጀመሪያዉ የቁርዓንን ማብራሪያ አዘጋጅ
- በኢትዮጵያ የመጀመሪያዉ የነብያዊ ትዉፊት ድርሳናትን ተርጓሚና ማብራሪያ አዘጋጅ
- ከ1988 እስከ 2001 የተለያዩ ጋዜጣና መጽሔቶችን በማዘጋጀትና በአምደኝነት ሲሰራ የነበረ
- የህትመት ቤቶችን ሥራ በማረምና በመገምገም ለተነባቢነት ሲያበቃ የኖረ
- አሁንም በጥበብ ወላድነት ላይ የሚገኝ ታላቅ የቀለም ቀንድና የእስልምና ልሂቅ ነዉ #ሐሰን_ታጁ !!
በኢራን-ቴህራን ፣
በቱርክ-ዒስታንቡልና አንካራ ፣
በዱባይ-ኢሚሬትስ ፣
በሱዳን-ካርቱም
እንዲሁም በሌሎች ዓለማቀፍ የሥነ-ፁህፋዊና ሃይማኖታዊ ኮንፈረንሶች ላይ ሀገሩን ኢትዮጵያን በመወከል ተሳትፏል ፡፡

4ለ4 ውይይት ላይ እጅግ የላቀ አስደማሚ ሚና የተጨዋተ ሲሆን ከጎን እና ፊቱ ለተኮለኮሉ የውሀቢያ ሸይኾች ድብቁ ማንነታቸውን ድንገት ሳያስቡት ሲዘረግፍላቸው በሆዳቸው ይሄን ነገር ምነው ባላነሳው በቃ ተጋለጥን በሚል ዓይነት እይታ ዓይናቸውን ቁልጭ ቁልጭ እያደረጉ ሲያደምጡት ማህበራዊ ሚድያ ላይ በሰፊው ሲዘዋወር በትዝብት ተመልክተናል። በሃፍረት ጥፍራቸው ውስጥ መደበቅ ነው ያሰኛቸው። ገዳይነታቸውን አምነው ለተከታዮቻቸው ጭምር በሊሳነልሃል እመኑ ብለው ነው የወጡት።


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
اللهم صلی علی محمد
ملحظ الجمال جمال الجمال
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
https://t.me/YASIRAJEL_ALEM


አፈር መገርገያ
በዱአችሁ
ሺሊላ አበራሙዞ ኧሼ ታዞ
አባና አበራ ሙዞ ትንም ትፈዞ ትፈዞ🥁🥁🥁🥁
https://t.me/YASIRAJEL_ALEM


አምባሳደር ሀሰን ታጁ


ከትላንት ወዲያ በተፈፀመው ዘግናኝ ፍጅት አንባሳደር ሀሰን ታጁ ነገሩን በፌስ ቡክ መንደር ላይ በሰሙትና ባጣሩት መሰረት አጋርተዋል። ‼️

በጉዳዩ ላይ አንባሳደር ሀሰን ታጁ የማንንም ስም ያልጠሩ ሲሆን የትኛውንም በሙስሊሞች መሀከል ግጭትን የሚፈጥር መልክት አላስተላለፉም።



ነገር ግን ስማቸው ባልተጠራበት "ፍስ ያለበት ዝልያ አይችል "እንዲሉ የሞቱ ሰውች ነፍስ  ከቁብ ሳይቆጥሩ የሀዘን መልክእት አንድ ቦታ ላይ ሳይጠቅሱ ኡስታዝ ሀሰን ታጁ በግፍ ለዛውም በሀሪማ ውስጥ ያሉ ኡስታዝና ደረሳን በመርዝ ስለ ገደሉ ሰውች ለኢቲዩጲያን ሙስሊሞች ማጋራተቸው እንደ ሀጢያት መቆጠሩ ገርሞ ገርሞ የሚገርም ነገር ነው።‼️


#ተሶውፍ (ሱፍይነት) ክፍል3
በተሰውፍ ጎዳና ጦሪቃ_(ሱሉክ) አለ። በዚህ መንገድ በጉዞ ላይ ያለ አንድ ሰው "ሳሊክ" (ተጓዥ) ይባላል።
እንደ ሱፍዮች ማንኛውም ሰው በሀይማኖታዊ እውቀት ከፍተኛ ደረጃ መድረስ ይችላል። ነገር ግን በሱፍይ መንገድ ለመራመድ ግን የሸይኽ ( #ሙርሺድ ) ምሪት ያስፈልጋል።
ሳሊኩ ከ ሙርሺዱ ልክ እርሱም ከተዘረጋው ከሸይኽና ሳሊክ ሰንሰለት የጉዞውን ጅማሮ ይቀበላል።
በዚህ ቅብብሎሽ ውስጥ ከነብዩ (ሰ.አ.ወ) የተመዘዘ በረካ አብሮ ይተላለፋል። እንደ ሱፊዮች እምነት ነብዩ ሙሃመድ (ሰ.አ.ወ) ይህን በረካ የሰጡት እጅግ ውስን ለሆኑ ሶሃቦች በተለይም ለ አባበክር (ረ.አ) እና ለአልይ (ረ.አ) ሲሆን እነርሱም በተራቸው ለተከታዮቻቸው አስተላልፈዋል።
በዚህ መንገድ ቅብብሎሹ እስካሁን ጊዜ ደርሷል ለወደፊትም ይቀጥላል። ይህ የቅብብሎሽ መንገድ በአረብኛ ሲልሲላ ሲባል። ከመምህር ወደ ተማሪ የሚተላለፍ ህያው ትውፊት ነው።
ተማሪው ፈላጊ (ጣሊብ)፥ከዚያ ሳሊክ፥በመጨረሻ አሏህ ከተደሰተበት እና ከሻለት አሏህ ዘንድ ተቀባይነት ያገኘ አሪፍ፥የበቃ ይሆናል።
ነገር ግን መንፈሳዊ እውቂያ ያለሸይኽ ወይም መንፈሳዊ መሪ አስጀማሪነት፥ምክር እና ምሪት ሊሳካ አይችልም።
የሱፊ መንገድ ለመከተል የሚሹ ወደ አንድ ሸይክ ይቀርቡና መንፈሳዊ ትስስር ሲልሲላ ይቀበላሉ፡፡ ይህ ትስስር እስከ ነቢዩ ሙሐመድ (ሶ.ዐ.ወ) ድረስ ሳይበጠስ ወደኋላ ይተረተራል፡፡ ፈላጊው መርጦ ሊከተለው የሚችል በርካታ ሲልሲላዎች ሲኖሩ ሁሉም ግን ነቢዩ ራሳቸው ካስጀመሯቸው አንድ ወይም ሌላ ሶሃባ ላይ ያርፋል፡፡ በተሰውፍ የመጀመሪያ ዘመን ውስጥ የነበሩ ብዙ የሱፊ አለቆች ቢኖሩም ተቋማዊ ቅርፅ አልነበረውም፡፡ በአስራ አንደኛው እና አስራ ሁለተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ነበር የመጀመሪያው የቃድሪይ ስርዓት ወይም ጠሪቃ በሸይክ አብዱልቃድር ጀላኒይ (1071-1166) የተመሠረተው።


የሙነወር ልጅ ከቅዠት አይወጣም

በወሎ ታንታ ወረዳ ተዘጋጀቶ በነበረው የመውሊድ ድግስ ወሀብያውች መርዝ ጨምረው ብዙ ሰውች የሞቱ ሲሆን ብዙዎች ደግሞ ወደ ሀኪም ቤት ተወስደዋል።

በጣም የሚገርመው የሙነወር ልጅ ይህን ጉዳይ መቃወም ሲገባው ነገሩን ትክክል እንዳልሆነ የጠቁሙትን ኡስታዝ ሀሰን ታጁን ለመቃወም መሮጡ ነው።‼️ ነብዩ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም ስለ ኻዋሪጅ ሲያወሩ ሚገርም ባህሪ ተናግረዋል እሱም" ትልቁን ቲኒሽ ቲኒሹን ትልቅ ያደርጋሉ"። የሞቱት ሰውችን ትቶ ሀሰን ታጁ ሳያጣሩ ተናገሩ ማለት ምን ማለት እንደሆን እንተው መልሱት?ለካ አንተ የተማርከውንና ምታስተምረውን ነው የተሰራልህ። ስለዚህ እንደጥፍት አትቆጥረውም ከአይሁድ ከነሳራ በፊት ሱፍያውችን ተጋደሉ የሚለው የፈውዛን ንግግር ይህን ቀብር አምላኪ ከስሩ ነቅለህ ጣለው አለፍ ሲል ቋንጃውን በለው የሚለው የአንተ ምክር የስንቱን ንፁሐን ነፍስ ቀጠፈ በሂወት እያለ ከፎቅ ላይ ስንቱ ተወረወረ ነገር ግን አንተ አሁንም ቅዠት ላይ ነህ ቆመህ ትቃዣለህ።‼️
https://t.me/YASIRAJEL_ALEM


إنا لله وإنا اليه راجعون

አሳዛኝ ዜና አሁን ደረሰኝ፤ በወሎ በተንታ ወረዳ ለመውሊድ በተዘጋጀ ምግብ ውስጥ መርዝ ተጨምሮ አምስት ሰዎች ህይወታቸው ወዲያውኑ ያለፈ ሲሆን ሌሎች በርካቶች ሆስፒታል ገብተዋል፡፡

ድርጊቱን የተፈጸመው መዉሊድ እንዳይደረግ ሲከላከሉ በነበሩ ያካባቢው ተወላጅ ጽንፈኞች እንደሆኑ ነዋሪዎች የተናገሩ ሲሆን ሲያሰሙት ከነበረው ዛቻና ለአካባቢው ሙስሊም ነዋሪ ከሚያሳዩት የመረረ ጥላቻ አኳያ እንዲህ አይነት አደጋ ሊያደርሱ እንደሚችሉ ይገመት እንደነበር ነዋሪዎቹ ጠቁመዋል።

✍🏼ambassador ሀሰን ታጁ


#ከሱፍዮች_አለም 1

"አዎ, አዎ; በሺዎች የሚቆጠሩ መጽሃፎችን አንብበሃል ነገር ግን እራስህን ለማንበብ ፈጽሞ አልሞከርክም። ወደ ቤተ መቅደሶቻችሁ፣ ወደ መስጊዶቻችሁ ትሮጣላችሁ፣ ነገር ግን ወደ ልባችሁ ለመግባት ፈጽሞ አትሞከሩም። ከዲያብሎስ ጋር የምታደርጉት ውጊያ ሁሉ ከንቱ ነው ምክንያቱም የራሳችሁን ፍላጎት ለመዋጋት ፈጽሞ አትሞከሩምና


#ተሰውፍ (ሱፍይነት)  #ክፍል_2

ሱፊ የሚለው ቃል ስርወ ፍችውን እና መነሻውን ስናይ ከሶሰት ዐረብኛ ፊደላት- ሰ- ወ- እና ፈ- የመጣ ቢሆንም የዓሊሞች ኺላፍም ልዩነት አላጣውም፡፡ አንደኛው ምልከታ ሱፊ የሚለው ቃል ሰፍ ከሚለው ቃል የመጣ ሲሆን መስመር ወይም ድርድር ማለት ነው፡፡ በነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) ጊዜ መስጊድ ቀድመው የሚመጡና
በሶላት ወቅት የመጀመሪያው ሰልፍ ላይ የሚቆሙትን ያጣቅሳል፡፡
ሌላኛው ዕይታ ቃሉ ሱፋ፣ የነቢዩ ሙሐመድ (ሰ.ዐ.ወ) መስጊድ በረንዳ ማለት ነው፡፡ ሐዲሱ እንደሚለው መኖሪያ ቤት የሌላቸው ቀላል ቁጥር የሌላቸው የነቢዩ ባልደረቦች የሚኖሩበት በረንዳ ነበር፡፡
ጊዜያቸውን በአምልኮ፣ ቅዱስ ቁርአንን በመሸምደድ እና የነቢዩን ቃላት በልባቸው በመያዝ የሚያሳልፉ ነበሩ፡፡ ራሳቸውን ከዓለማዊ
እንቅስቃሴዎች ያናጠቡ በመሆናቸው ነቢዩና ባልደረቦቻቸው ፍላጎታቸውን ያሟሉላቸዋል፡፡ የመስጊዱ በረንዳ መኖሪያቸው ስለነበር አስሀቢ ሱፋ (የበረንዳ ጓዶች) ተብለው ነበር የሚጠሩት፡፡
ሆኖም አብዛኛው ምሁራን ሱፊ የሚለው ቃል የመጣው ሱፍ- ሱፍ ከሚለው ቃል እንደሆነ ያምናሉ፤ ቀደምት ፃድቃኖች ከቅንጦት ህይወት የተናጠቡ በመሆናቸው የሚለብሷቸው ልብሶች ያልቀለሙ ሻካራ በመሆናቸውነበር የሚኮሰኩሰው ልብስ ይችን ዓለም በገዛ ፈቃዳቸው ከነደስታዋ እርግፍ አድርገው እንደተዏት ምልክት ነው፡፡
https://t.me/YASIRAJEL_ALEM




#ሁስነል_ኻቲማ (መልካም-ፍጻሜ)
غليك ربّنا بحسنِ الختامِ
ياربّنا بحسنِ الختامِ
ደጋግ የአሏህﷻ ባሮች አብዝተው እሱን የሚፈሩት
ከልብ አፍቅረው በጀላላው ታጥረው ከውኑን የዘነጉት
እነዛ ምላሳቸው ስሙን ጠርቶ የማይረኩት
የሌላ በመሆን ያልተጠረጠሩት
ኢልምና ተቅዋቸው እጅናጓንት ሁነው ቢሰደቡ ችለው ክብራቸውን ቢያጎድፉት እንኳን ለመቆጣት በቅንጭር ማይመለከቱት
ክብሩ ነው ክብራቸው ያ ታላቁ ጌታቸው አሏህﷻ የእርሱ ድንበር ሲጣስ ችሎ ዝመይልም ጀሰዳቸው፥ሩሃቸው፥ብእራቸው.........
     ፈርዱ ፈርዳቸው ነው ሱናውም ፈርዳቸው ነው ሃራሙ ሃራማቸው ከራሀውም ሃራማቸው እነዛ የአሏህﷻወልዮች ደጋግ ባሮች።

      ታዲያ ምንም እንኳን ኡምራቸውን በሙሉ በኢኽላስ እርሱን ሲገዙት ቢኖሩም የኻቲማቸው ጉዳይ ግን በእጅጉ ያሳስባቸው ነበር።
ባወቁት በእውቀታቸው አይብቃቁም አሏህﷻ ጋር ባላቸው ደረጃ አይመጻደቁም።
ምክንያቱም ቀድሞውኑ በቁርአንም ሆነ በሃዲስ እንዲሁም በታሪክ ተጅሪባት በርካታ አምላካዊ ሚስጥር እንዴት እንደነበር ተረድተዋልና።ለምሳሌ👇
             #በልአም_ኢብኑ_ባኡራ
በበኒ ኢስራኢል ዘመን በልአም ኢብኑ ባኡራ የሚባልን ታላቅ አሊም የአሏህንﷻ ሲፋና ባህሪ በትክክል ማወቅም ብቻ ሳይሆን ከአሏህﷻ መልካም ስሞች ውስጥ ኢስመል አእዞም በመባል የሚታወቀውን የአሏህﷻ  የሚስጥር ስም የተገለጠለት የፈለገውን ነገር ከአሏህﷻ ጠይቆ ማግኘት ይችል የነበር የኢልም መአዱላይ እርሱን የሚከታተሉት ከ20,000 በላይ ሰዎች ነበሩ ብዙ ተምራት(ከራማዎች) እንደነበሩት ተነግሯል በሌላ ዘገባ እንደመጣው ዱአ ሲያደርግ አርሽ ይታየው እንደነበርም ተወስቷል። ታዲያ እንዲህ ያለውን የአሏህ ድንቅ ባሪያ ኻቲማው ይበላሻል ብሎማን ያስባል። በስተመጨረሻ ነፍስያው አሸንፋው እንዲህ ሲል ከጌታው ጋር ያለውን ቀረቤታ በኩፍር ቋጨው لارب فی هذالكون  ለዚህ ሁሉ አለም univers ፈጣሪ የለውም ሲል ኻቲማውን አበላሸ።
አሏህﷻ የዚህን ውለታቢስ ባሪያውን ክህደት በቁርአን ላይ እንዲህ ሲል አስፍሮታል አሏህﷻ እንዲህ ተናገረ👇

وَاتْلُ عَلَيْهِمْ نَبَأَ الَّذِي آتَيْنَاهُ آيَاتِنَا فَانسَلَخَ مِنْهَا فَأَتْبَعَهُ الشَّيْطَانُ فَكَانَ مِنَ الْغَاوِينَ

የዚያንም ተዓምራታችንን የሰጠነውንና ከእርሷ የወጣውን ሰይጣንም ያስከተለውን ከጠማሞቹም የኾነውን ሰው ወሬ በእነርሱ ላይ አንብብላቸው፡፡

وَلَوْ شِئْنَا لَرَفَعْنَاهُ بِهَا وَلَٰكِنَّهُ أَخْلَدَ إِلَى الْأَرْضِ وَاتَّبَعَ هَوَاهُ ۚ فَمَثَلُهُ كَمَثَلِ الْكَلْبِ إِن تَحْمِلْ عَلَيْهِ يَلْهَثْ أَوْ تَتْرُكْهُ يَلْهَث ۚ ذَّٰلِكَ مَثَلُ الْقَوْمِ الَّذِينَ كَذَّبُوا بِآيَاتِنَا ۚ فَاقْصُصِ الْقَصَصَ لَعَلَّهُمْ يَتَفَكَّرُونَ

በሻንም ኖሮ በእርሷ ከፍ ባደረግነው ነበር፡፡ እርሱ ግን ወደ ምድር ተዘነበለ፡፡ ፍላጎቱንም ተከተለ፡፡ ብጤውም ብታባርረው ምላሱን አውጥቶ የሚያለከልክ ወይም ብትተወው ምላሱን አውጥቶ የሚያለከልክ እንደ ኾነ ውሻ ነው፡፡ ይህ የእነዚያ በአንቀጾቻችን ያስተባበሉት ሕዝቦች ምሳሌ ነው፡፡ ያስተነትኑም ዘንድ ታሪኮችን ተርክላቸው፡፡
(ሱራ አል-አእራፍ 175-177 ይመልከቱ)

ተአምራታችንን የሚለው ቃል ብዙቁጥርን ነው የሚያመለክተው። እጥፍ ድርብ የሆኑ ተአምራቶችን እንደሰጠው ቁርአኑ ገልጾታል። ከንቱ ፍላጎቶቹን ተከተለ ብትከለክለውም ባትከለክለውም ምላሱን አውጥቶ በሚያለከልክ ውሻ ይመሰላል ሲል ከሰበዊነት ወደ እንስሳነት አሽቆሎቆለ። ወደታች ወረደ ምጥቀትን አሻፈረኝ ብሎ ዘቀጠ መጥፎ ስሜቱን ተከተለ "አነፍስ ሀይዋንያ" የሚሏት ቀደመችው።
ያስተነትኑ ዘንድ ታሪኩን ተርክላቸው ሲል ገልጾታል።
@Sufizmmm
https://t.me/YASIRAJEL_ALEM


#ተሰውፍ (ሱፍይነት) ክፍል-1
ተሰዉፍ ለዘመናት የእስልምና ትክክለኝነት መለኪያ ሆኖ ቆይቷል፤
አሁንም ነው፡፡ እንደ አንዳንድ ምሁራን የሃይማኖታዊ አስተሳሰቦች
ሰፈፍ ነውም፤ በእስልምና ውስጥ ያሉ ወደ አላህ መሄጃ መንገዶች
የሚገናኙበት ብቻ ሳይሆን ከእስልምናም ውጭ ያሉ፡፡
ጀላሉዲን ሩሚ በታዋቂው ተሰዉፍን በገለፁበት ምሳሌያቸው
ስለአራት የተለያዩ አገራት ተጓዦች ታሪክ ይነግሩናል፡፡ እነዚህ አራት
ተጓዦች ያለቻቸውን አንዲት ሳንቲም ለምግብነት ሊያውሉ ፈለጉና
ክርክር ገጠሙ፡፡ አንድ በአጠገባቸው የሚያልፍ የቋንቋ ሰው
ውዝግባቸውን አድምጦ፣ ሳንቲሙን ከሰጡት ሁሉንም የሚያረካ
ምግብ ይዞላቸው እንደሚያመጣ ይነግራቸዋል፡፡ ሳንቲሙን ሰጡት፣
እርሱም ለአራቱም አራት ዘለላ ወይን ይዞላቸው መጣ፡፡ አራቱም
በመገረም ሁሉም ሲፈልጉት የነበረው ነገር ወይን እንደነበረ ተናዘዙ፡፡
ምንም እንኳ አንድ አይነት ነገር ቢፈልጉም፣ ከቋንቋ ጋ በመጡ
የተለያዩ ቅርፊቶች በእውነተኛው ነገር ላይ እንዳይግባቡ አድርጓቸዋል፡
፡ በእርግጥም ሁላችንም የአላህ ባሪያዎች ነን፤ እርሱን ብቻ ነው
የምንፈልገው፡፡
ሆኖም ይህ ድንቅ ሃይማኖታዊ ቅስቃሴ ከጥቂት ዓመታት ወዲህ
በመጣው ቅርፃዊነት እና ሌሎች የተለያዩ ምክንያቶች እርሱ ራሱ
ምንነቱ እና ማንነቱ ተሸፍኗል፡፡ የእስልምና ሃይማኖት ኩራት ሆኖ
ፍቅርንና እዝነትን የሰብአዊነትን ቀንዲል ይዞ ሃይማኖቱን ለሰዎች
እንዳላዳረሰ አሁን ትክክለኝነቱን ሁሉ ጥያቄ ምልክት ውስጥ የሚከቱትውልዶች መጥተዋል፡፡ ሆኖም ይህ ለተሰዉፍ አዲስ አይደለም፡፡
ታሪኩ እንደሚያሳየው ሁሉ ነገር አልጋ ባልጋ ሆኖለት የደረሰበት ደረጃ
ላይ አልደረሰም፡፡ በርካታ ውጣ ውረዶችን ማሳለፍ ነበረበት፡፡
ተሰዉፍ እንደ ቀድሞው አሁንም ለሰው ዘር፣ ቢያንስ ለእስልምና
ሃይማኖት ተከታዩ አስፈላጊ ነው፡፡ ቅርፃዊነት ያቀረበው ተግዳሮት
ለተሰዉፍ ብቻ አይደለም፣ ለሰው ዘርም ጭምር እንጂ፡፡ ቅርፃዊነት
በምንነቱ ቅርፍታዊ በመሆኑ ለልዩነት የተመቸ ነው፡፡ ሰው ከቅርፁ
በታች ያለውን ማየት ካልቻለ እና በውጭ ከቆየ አንድነትን ከማየት
ይልቅ ልዩነትን ማየቱ አይቀርም፡፡ ነቢዩ ሙሐመድ (ሶ.ዐ.ወ) በታዋቂ
ንግግራቸው ሰዎች በፊጥራ (አምላክን በማወቅ ተፈጥሯዊ ይዞታ
ላይ) ተወልደዋል፤ ነገር ግን አካባቢው ከወላጆቹ ጀምሮ ከባባዊው
ነባራዊ ሁነቶች ይሸፍነዋል እንዳሉት፣ በዚህ ከባቢያዊ ቅርጻዊ ነገሮች
ላይ ብቻ ካተኮርን ልዩነቶቻችንን ማየት ብቻ አይደለም፤
እውነተኛውን ተፈጥሯዊ መቅኔው ያመልጠናል፡፡
ሌላ ምሳሌ ለመስጠት፣ አላህ (ሱ.ወ) በቅዱስ ቁርአኑ የሰውን ልጅ
ከተለያዩ ጎሳዊ፣ ነገዳዊ እና ሃይማኖታዊ ማንነቶች እንደፈጠረ
ይናገርና፤ ለዚህ ደግሞ ምክንያቱ ወተዋወቅ እንደሆነ ያስገነዝባል፡፡
ከሰዎች ሁሉ በላጩ ግን አላህን ተጠንቃቂው እንደሆነ ያሰርጻል፡፡
ቅርጻዊነት ጎሳዊ፣ ነገዳዊ፣ ብሔራዊ፣ ሃይማኖታዊ ልዩነቶች ላይ
አተኩሮ እውነተኛውን ነገር- መተዋወቁን እና አላህን ተጠንቅቆ
ህይወቱን መምራቱንና ለሰው ዘር በጎ መሆኑን ይዘነጋል፡፡
ይቀጥላል..........
https://t.me/YASIRAJEL_ALEM


⇒አሏህ ለአንድ ሰው ከሚሰጠው ፀጋዎች መካከል ራሱን ማወቁ አንዱ ነው። ራሱን ያወቀ ሰው ልኩን ያውቃል፣ ድክመትና ጥንካሬዉን ያውቃል፣ የሚችለዉንና የማይችለዉን ያውቃል፣ የሚያውቀዉንና የማያውቀዉን ያውቃል፣ መቆም ያለበትንና መቆም የሌለበትን ቦታ ያውቃል። ይህን በማድረጉ ራሱንም ሆነ ሌሎችን አይጎዳም።

ራሱን አውቆ መቆም ባለበት ቦታ ላይ ለቆመ ሰው አሏህ ይዘንለት።
https://t.me/YASIRAJEL_ALEM


#አውጅ_ቢን_ኡኑክ

አውጅ የነብዩላህ አደም የልጅ ልጅ ነበር። በጣም ረጅም እና ግዙፍ ቁመቱም 3300 ክንድ ይረዝም ነበር። አውጅ ቢን ኡኑክ እስከ 4,500 አመት እድሜ ያለው ሰው ነው። በነብዩላህ ኑህ عليه سلم ዘመን አላህ መርከብ እንዲሰሩ አዘዛቸው። መርከቡ ለመስራት ግን እንጨት ያስፈልጋቸው ስለነበር እንጨቱ የሚገኘው ኩፋ ውስጥ ነበር እናም ኑህ ካሉበት በጣም ስለሚርቅ ተጨነቁ በዚህ ጊዜ አላህ ራእይ አወረደላቸው አውጅ ቢን ኡኑክን ጠይቅ አላቸው። እሳቸውም አውጅን ጠየቁ እሱም ቅድመ ሁኔታ ጠየቀ ሆዴ መሙላት ስላለበት ምግብ አቅርብልኝ አላቸው። ኑህም ምግብ ሰጡት ሊያጠግበው ግን አልቻለም በመጨረሻ ቢስሚላህ ብሎ እንዲበላ ነገሩት በዚህ ጊዜ ቢስሚላህ ብሎ ሲመገብ ጠገበ። እንጨቱን አመጥቷላቸው መርከቡን ሰሩ። የጥፋቱ ውሀ በመጣና አለምን ሁሉ ባጠፋ ጊዜ ለአውጅ ግን የውሃው ከፍታ ከጉልበቱ መብለጥ አልቻለም ነበር።
   አንዳንዶች በተራሮች ላይ እንደሚኖር ይናገራሉ ረሃብ ሲሰማው አሳ ከባህሩ ስር አውጥቶ በፀሐይ ሙቀት ይጠበስ ነበር። ሰዎችን እንደቆሎ ያፍስ ነበር።
      በነብዩላህ ሙሳ ዘመን ዐውጅ ሙሳንና ህዝቦቹን ሊያጠፋ አሰበ። ከዚያም አውጅ የነብዩላህ ሙሳን ወታደሮች መኖሪያ ቤት ለማየት መጣና ከቦታው ብዙም ሳይርቅ የነብዩ ሙሳ ወታደሮችን መኖሪያ አገኘ። ከዚያም በዙሪያው ያሉትን ተራሮች ነቅሎ በነብዩላህ ሙሳ ወታደሮች ላይ ሊወረውር ተራሮቹን ከጭንቅላቱ አኖራቸው። አውጅ ከጭንቅላቱ በላይ የተያዙትን ተራሮች በነቢዩ ሙሳ ወታደሮች ሊወረውር ጊዜ ከማግኘቱ በፊት አላህ ሁድ(የጀነት) አእዋፍ አማካኝት የአልማዝ ድንጋይ ልኮ አውጅ በያዘው ተራራ ላይ አስቀመጣቸው። አልማዝ በአላህ ሃይል በአውጅ የተያዘውን ተራራ አንገቱ እስኪደርስ ድረስ ዘልቆ ገባው መቋቋም አቃተው። 'አውጅ አልማዙን ለማስወገድ ፈቃደኛ አልነበረም፣ በመጨረሻ ሙሳ መጡ። 
የነብዩላህ ሙሳ ቁመት አርባ ክንድ ሲሆን የበትራቸውም ርዝመት አርባ ክንድ ነበር እና ከቁመታቸው በላይ አርባ ክንድ ዘለው (80 ክንድ) አውጅን በበትራቸው ቁርጭምጭሚቱ ላይ መቱት። በዚያን ጊዜ አውጅ ሙሳ ሆይ ወደ ቀኝ ልውደቅ ወደ ግራ አላቸው ሙሳ ተንኳሉን ስለሚያቁ ወደ ቀኝ አሉት የዚህን ጊዜ ወደ ግራ ወደቀ ግራ ቢሉት ኖሮ ወደ ቀኝ ይወድቅና ሰዎች ላይ ጉዳት ያደርስ ነበር ወደ ቀኝ ሲወድቅ ቀይ ባህርን ለሁለት ከፈለው ለዘመናትም መተላለፊያ ድልድይ ሆነ ሰውነቱንም ጅብ በልቷ እንደጨረሰው ይነገራል። አውጅ በአላህ ሱ.ወ ፈቃድ ወደቀ በመጨረሻ ምንም እንኳን ረጅም እና ከፍተኛ ጥንካሬ ቢኖረውም ከሞት ማምለጥ አልቻለም።

ኢብኑ ከሲር እንዲህ ይላሉ "ስለ አውጅ ዘገባዎች ለመዘገብ ያሳፍራሉ ምክንያቱም 'የአደም ዝርያዎች ተክለ ሰውነት ከዘመን ፍሰት እያነሰ እንደሚመጣ ከሚናገረው ሶሂህ ሀዲስ ጋር ይጋጫል። ምክንያቱም አባታችን አደም ርዝመታቸው 60 ክንድ ነበር" ብለዋል።

*የአደም ልጅ ከሁሉ ፍጥረት የላቀው በግዝፈቱ አይደለም እንደዛ ቢሆንማ ዝሆን ከሰው ይልቅ በከበረች። ሁሌም ይህን በልብህ አኑር: ጥበበኛውን አላህ ማወቅ የልዕቅና ሁሉ ሚስጥር ነው።

https://t.me/YASIRAJEL_ALEM


ተቀዳሚ ሙፍቲ ሃጅ ዑመር ዛሬ በኒ(ኑር) መስጅድ ላይ ከኹጥባ በፊት ካደረጉት ንግግር ከፊሉ እና ጥቂቱ ..

.......የተከበራቹ  አዳማጮች  ኡለማዎች ይናገራሉ አድማጮችም ያዳምጣሉ አላህ ይፈለገውን ይሰራል ይወስናል ።

የሁሉም መለያው መጨረሻው ከሞት ቡኋላ ነው

ከፊሉ የገንዘብ ባሪያ ይሆናል
ከፊሉ በስልጣን ይታለላል
ከፊሉ ይዋሻል
ከፊሉ ያለቅሳል
አላህ ያሻውን ይሰራል

.......
የሰው ልጅ ዛሬ መሪው ገንዘብ ነው ስልጣንም ሚፈልገው ለገንዘብ ነው ።
አሊሙ ለገንዘብ ሲል ፋሲቅ ይሆናል
  አሊሙ እንዲህ ከሆነ ጃሂሉ በምን ይታማል ?

....
መማር ማለት ወረቀት ላይ መፃፍ ብቻ አይደለም ማወቅ ነው ።

ለምክር ሞት በቂ ነው ።
........

ወንዱ ሴት መሆን እየፈለገ ነው ሴቱ ወንድ መሆን እየፈለገ ነው ለመናገርም ተጠይፈነው ቆይተናል አሁን ግን እየገፋ እየባሰ ህጋዊ እየሆነ መጥቷል 😥

ወንጀል እየበረከተ ነው ወጣቶች እንዳትታለሉ እንዳትሞኙ ሞት አለ ሞት አለ ........

የሞትን ቀን የወደቅንለት ስልጣን አይጠቅምም

https://t.me/YASIRAJEL_ALEM


እንኳን ለ1444 አመተ ሂጅሪያ በሰላም አደረጋችሁ
# በነገ ቀን ችግርተኛን እንዳንረሳ
ሁላችንም በየጎረቤታችን በየ ሰፈራችን በየ መንደራችን ስንት የቲሞች አቅመ ደካሞች መከርተኞች ይኖራሉ እና በደግነታችን እንዳንረሳቸው
# ድግነት ውጤቱ ለራስ ነው
https://t.me/YASIRAJEL_ALEM


ለኡስታዝ ሀሰን ታጁ

👉 ለሀበሻ ሙስሊሞች የሀይማኖታዊ እውቀት መስፋት የእርስዎ ሚና አይተኬ ነው ፥ በቅርብ አመታት ደግሞ በአማርኛ ፀሀፊዎች በኩል የቲም የሆነውን የአህለሱናን መስመር ለህዝብ ግልፅ የሚያደርጉ የተወሰኑ መፅሀፍቶችን አበርክተዋል ።

🔰በትክክል ባላወቅናቸው ምክንያቶች እነዚያን ድንቅ መፅሀፎች ለህዝብ ከማድረስ ትንሽ ተቀዛቅዘዋል ፥ በቅርቡ ደግሞ ወደ ሚዲያ ተመልሰው ጥሩ ጥሩ ፅሁፎችን እያካፈሉን ነው ሆኖም ግን እነዚህ ፅሁፎች በሌሎችም የአህለሱና ወንድምና እህቶች  ሊፃፋ የሚችሉና የሀበሻ አህለሱና በዐቂዳዊና በፊቅሀዊ ፅሁፎች  ዙሪያ  የሚታይበትን ክፍተት ሊሸፍኑ አልቻሉም ።

🛑 በተለይ በአህለሱናው የዐቂዳ መንሀጅ ዙሪያ ከምናስበው በላይ በሰፊው ውዥንብሮች እየተሰራጩ ነው ፥ ሰፋ ያሉና ለመረዳት ቀላል የሆኑ ምላሾች ያስፈልጋሉ ፥ ይህን ለማድረግ ደግሞ ከእርሶ የበለጠ ቀለሙ የሰላ ወንድም የሚገኝ አይመስለንም ፥ ብዙ ወንድሞች ጋር ምላሽ የመስጠት አቅሙ አለ ነገር ግን አቂዳ ላይ ያሉ ብዙ ቃላትን ወደ አማርኛ መተርጎም ሲከብዳቸው ተመልክተናል ስለዚህ ሀላፊነቱ እርስዎ ላይ የወደቀ ይመስላልና ከወዲሁ እንድታስቡበት በአሏህ ስም እንጠይቅዎታለን 🙏🙏።
https://t.me/YASIRAJEL_ALEM

Показано 20 последних публикаций.