ሱፊዝም


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана



Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций




ረቢዕ ደርሷል አሽቁ ያ ጀመዓ👏


መልካም ለይለቱል ጁሙዓ /ኸሚስ/👏


ያማረ ለይል ይሁንላችሁ👏


ኢስንይን


جمعة مباركة


በአንድ ወቅት በጣም የሚፋቀሩ ፍቅረኛሞች ነበሩ እሚኖሩት በድህነት ነው። ሲኖሩ እሱ የሚያምር ሰዓት አለው ግና የሰአቱ ዘለበት(ማሰሪያው) ጠፍቶበታል። እሷ እረጅም ጸጉር አላት ግና ማበጠሪያ የላትም አንድ ቀን ምሽት ላይ የእነኚህ የሁለት ፍቅረኛሞች ቤት በለቅሶ ተሞላ ከለቅሷቸው ጀርባ አንድ እውነት ነበር እሱም ባል ሰአቱን ሽጦ ማበጠሪያ ገዝቶላታል። እሷ ደሞ ፀጉሯን ተቆርጣ ሸጣ የሰዓት ዘለበት(ማሰሪያው)ን’ ገዝታለታለች።

👉አስታውሱ! "ፍቅርን የምትፈጥሩት የፈጣሪ መንፈስ አብሯችሁ ሲሆን ነው።"
#ጀላሉዲን አል ሩሚ


ሊንኩን ነክታቹ Start በሉት!




ልዩ የዒድ አል-አድሓ ዓረፋ በዓል ቆይታ በሸይኽ ዑመር ኢማም ቤት
ዛሬ ከቀኑ 8፡00 ጀምሮ በአስ-ሱና ቲቪ ይጠብቁን
#ዒድ_ሙባረክ
*****
አስ - ሱናህ TV ''ሚዛናዊ መርህ قناة السنة نهج الاعتدال
As-Sunnah TV ''The Way Of Moderation'' ||


ለሐጅ መንገደኞች !!
እስካሁን 1663 ኢትዮጵያውያን ሁጃጆች መዲና ደርሰዋል ።
በመጅሊስ ታሪክ እጅግ ፈታኙ የሐጅ መስተንግዶ የዚህ ዓመቱ ነው ። አንደኛ ለሳዑዲ ሐጅ ሚኒስቴር ለመንገደኞች የሚከፈለው 30 ሚሊዮን ዶላር አለመገኘቱ ሲሆን ፤ ሁለተኛው የመጅሊሱን ስልጣን በኃይል ለመንጠቅ የሚመኘው ቡድን የሚፈጥረው ውዥንብር ነው ።
ዑለሞችና የመጅሊሱ አመራር በኮቪድ ምክንያት ተቋርጦ የነበረው የሐጅ ፀሎት ከተፈቀደ ካለፉት ሁለት ወራት ጀምሮ ዶላር ለማግኘት የሚቻለውን ሁሉ ሲያደርግ መቆየቱን በተደጋጋሚ ስናሳውቅ መቆየታችን ይታወሳል ።
አሁንም ቢሆን መጅሊሱ ለ3000 ሺ ሁጃጆች ቪዛ ማውረድ እንደሚችልና ለ1000 ሺ ደግሞ በተጠባባቂነት እንዲጠብቁ ደጋግመን ስናሳውቅ ሰንብተናል ። ከ4000 ሺ በላይ የተመዘገቡ ደግሞ ብራቸው በአስገቡበት ባንክ ተመላሽ እንዲደረግ ዑለማ ምክር ቤቱ ወስኗል ። ደጋግሞም መግለጫ መስጠቱ ይታወሳል ፤ እንደ ተቋም እውነቱ ይሄ ነው ።
ነገር ግን የሐጅ እድል በጉዞ ወኪሎች የመገኘት እድሉ ካለ በሚል ተስፋ መጅሊሱ የሚሰጠውን ድጋፍ አድርጎ ሰው ሐጅ እንዲያደርግ እና እንዳይቀር በማሰብ እንዲመዘግቡ ለድርጅቶቹ ይሁንታ ሰጥቷቸዋል ።
ስራቸውንም ግቢ ውስጥ ቢሮ ሰጥቶ በቅርብ ርቀት ሆኖ እየተከታተላቸው እና እየደገፋቸው ይገኛል ። ሆኖም እስካሁን አንዳቸውም ለሳዑዲ ሐጅ ሚኒስቴር የሚላከውን ዶላር አላስገቡም ። ዛሬ ማታና ነገ ያስገባሉ ብለን ተስፋ እናደርጋለን ። የተወሰነ ሓጃጅም በጉዞ ወኪሎች በኩል ቢሄድ ለተቋሙ ትልቅ ስኬት ነው ። ይሄም ተጀምሯል ፤ ከሆነ እሰየው ፤ ካልሆነ ደግሞ የሀጃጁ ገንዘብ ያለው በመጅሊስ አካውንት ስለሆነ ወዲያውኑ ወደ ሀጃጁ አካውንት ተመላሽ ይደረጋል ። የሓጃጁ መሄዱ ነው እንጅ ገንዘብ መመለሱ ለመጅሊሱ አያስቸግረውም ፤ በቀናት ውስጥ ያልሄደው ሀጃጅ ብር በሙሉ መመለስ የሚያስችል አሰራር ባንኮቹ ዘርግተዋል ።
ሌላው ፤ ዛሬ መጅሊስ ግቢ ትላንት የተነሱት አይነት የዶላር ጥያቄና የጉዞ ወኪሎች ምዝገባ ፍጥነት ይኑረው የሚል የሀጃጅ ጥያቄዎች ተነስተው ነበር ።
ይህንን ሰላማዊ ጥያቄ ወደ ረብሻ ለመቀየር ተዘጋጅተው የመጡ እና ሐጅ ለማድረግ ያልተመዘገቡ ግለሰቦች ነበሩ ። ልክ ጥያቄውን ወደ ፉጨትና ጩኸት ከቀየሩ በኋላ ፤ " መጅሊሱ በ24 ሰዓት ውስጥ ስልጣን ይልቀቅ ፤ Dawn Dawn መጅሊስ ፤ Dawn Dawn መጅሊስ ወደሚል ያረጀና ያፈጀ የረብሻ መስመር ሐጃጁን ለማስገባት ሞክረው ነበር ። ህዝቡም አጀንዳው ሌላ መሆኑ ሲገባው መልሶ ፀጥ አለ ። ወዲያው የግቢ ፀጥታ ሃይሎች ሲመጡ ረባሾቹ ፤ ሮጠው ለማምለጥ ሞክረዋል ፤ የተወሰኑት ተይዘዋል ። እውነቱ ይሄው ነው ። እውነትም የአላህ ነው ።

©የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት።




" የታላቁ ህዳሴ ግድብ ቶሎ ተጠናቆ ወደ ሌሎች የልማት ስራዎች ፊታችን ልናዞር ይገባል ሲሉ " ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጅ ዑመር ኢድሪስ አስታወቁ ።
ዛሬ ቅዳሜ ሰኔ 11 የአዲስ አበባ ከተማ ወረዳ ዘጠኝ የግድቡ ገቢ አሰባሳቢ አባላት ዋንጫውን ይዘው የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚደንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ቢሮ በመገኘት ድጋፍና ምርቃት ተቀብለዋል ።
ተቀዳሚ ሙፍቲ የህዳሴ ግድቡ የመሠረት ድንጋይ ከተቀመጠበት ዕለት ጀምሮ አሁን እስካለበት ደረጃ ድረስ በተለያየ መልኩ ትግል ያደረጉ ታላቅ ሰው ናቸው !
ባለፈው ዓመትም የውሃ ሙሌቱን ተከትሎ የግብፁ አህዛር ዩንቨርስቲ ኢማም ከሀሰት ወግነው በአባይ ጉዳይ ለሰጡት ተገቢ ያልሆነ መግለጫ አግባብ ያለውና ዕውነቱን የሚያፀና ምላሽ ለአልጀዚራ ፣ ለቢቢሲ ፣ ለስካይ ኒውስና ለCNN መግለጫ መስጠታቸው ይታወቃል ።
ተቀዳሚ ሙፍቲ ከእውነት ጋር መቆም የዘወትር መርሃቸው ነው ።

©የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት!


ብሔራዊ ባንክ!
==========

የሀጅ ቅድመ ዝግጅት ሊጠናቀቅ በጣት የሚቆጠሩ ቀናት የቀሩት ቢሆንም ይህ በእየ አንድ አንዱ አቅም ባለው ሙስሊም ላይ ግዴታ የሆነ የሀጅ ሀይማኖታዊ ጉዞ እክል ገጥሞታል።

ለችግሩ እንደ ምክኒያት የቀረበው "የዶላር እጥረት" እንደሆነ ቢገለፅም እየተሰሙ ያሉ ጉምጉምታዎች ግን ይህንን ምክኒያት ውድቅ የሚያደርጉ ናቸው!

የዶላር ክልከላው በንግድ ባንኩ ውስጥ በሸሪአ ቦርድ አማካሪነት ተሰግስገው የሚገኙ የወሀብያ/ኢኽዋን አካላት እጅ እንዳለበት የተሰማ ሲሆን፤ የሸሪአ አማካሪዎቹ ከአንድ አንድ ከባንኩ ማኔጅመንት አባላት ጋር ያላቸውን ቅርርብ በመጠቀም አርካኑል ኢስላም በሆነው የሀጅ ጉዞ ላይ ተግዳሮትን እንደፈጠሩ ሹክሹክታዎች አሉ!

የወሀብያ/ኢኽዋን ፀረ እስላማዊ ተግዳሮቶችን በሙስሊሞች ላይ የመጫን ዝንባሌ አዲስ ባይሆንም፤ ብሔራዊ ባንኩ እንዲህ ባለ ተቋማዊ ብልግና ውስጥ እጃቸውን የነከሩ የስራ ሀላፊዎችን አደብ እንዲያስይዝ ግን አፅኑ እናሳስባለን!

እንዲሁም የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ በጉዳዩ ላይ አፋጣኝ መግለጫ እንዲሰጥ በመላው ኢትዮጵያዊ የሀጅ ተጓዥ ስም እንጠይቃለን!

ተቋማዊ ብልግናን ለመዋጋት በፅናት እንቆማለን!


አሁንም ይግባህ

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፕሬዝደንት ክቡር ዶክተር ተቀዳሚ ሙፍቲ ሐጂ ዑመር ከትላንት በስቲያ በፌደራል ቤቶች ኮርፖሬሽን አማካኝነት የተገነቡ ሕንፃዎች ሲመረቁ ከመንግስት በተላለፈላቸው ጥሪ መሰረት በክብር መገኘታቸውና መታደማቸው ይታወሳል።

ዛሬ ደግሞ በአሁኑ ሰዓት ጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አሕመድ ማብራሪያ እየሰጡበት ባለው በተወካዮች ምክር ቤት 13ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ክቡር ተቀዳሚ ሙፍቲ ከመንግስት በተደረገላቸው ጥሪ መሰረት በምታዩት መልኩ በክብር ተጋብዘው ተገኝተዋል።

መንግስት ምን ዓይነት መልዕክት እያስተላለፈልህ እንደሆነ አሁንም ካልገባህ እስኪበቃህ ድረስ ዝለል፣ ተወጠር። መንግስት ሚፈልገው ደረጃ ላይ እክትደርስለት ድረስ ነው እየጠበቀህ ያለው። ትክክለኛው ወቅት ደርሷል ብሎ ሲያምን ግን ያስተነፍስሃል!

በዛሬው የፓርላማ ስብሰባ ላይም ምናልባት የ #ቤርጎው_መጅሊስም ተጋብዞ ከኋላ ተቀምጦ ይሆናል በሚል ተስፋ የቴሌቪዥኑን እስክሪን ከጫፍ እስከ ጫፍ በምሬት እያየ ዓይኑ ሚቀላጥም አይጠፋም እኮ😉


በድጋሚ ለማስታወስ ያህል ለሁሉም ሚድያዎች


የኢትዮጵና እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ይህንን ቅድመ ማሳሰቢያ አውጥቷል:: ላልሰሙት አድርሱላቸው:: ህግን አለማወቅ ከተጠያቂነት አያድንም ይባላል::


ሁሉም ሰዉ ሊያየዉ የሚገባ ድንቅ ፕሮግራም!!!




የዘመናች ፈተና ቀስቃሽ - አእመዲን ጀበል
================
አእመዲን ጀበል በግልፅ ከሸይኽ ዐብዱላህ ሀረሪ የጀመረ ዞሮ ተዟዙሮ በሙፍቲ ዑመር ኢድሪስ አድርጎ ነቢዩ ሙሐመድ ﷺ ጋር ደረሰና ክብራቸውና ክብራችን በሚነካ መልኩ እያልን መወዛገብ ጀመርን:: ይህንን ስጽፍ እንኳ ውርደትና ፍርሃት እየተሰማኝ ነው:: አእመዲን አጥፍቻለሁ እንደማለት ይብስ በሁለት ክፍል አቡካካና የሙፍቲ ዑመርን ጥፋት ወደ መዘርዘር ገባ:: እንደውም ሐሳቡን አጠናከረና > ይለናል:: የሚልም አንቀጽ አምጥቶ የማያውቀውን ተፍሲር ይዘበዝብ ጀመር:: (ሸይኾች ጋር እንደዘመተ ነቢዩ ሙሐመድ ﷺ ጋር ወስዶ ጣለው)::

ነቢዩ ﷺ የደነገጡት እኮ ጂብሪልን ከእነ ሙሉ ተፈጥሮው ለመጀመሪያ ጊዜ ስላዩት ነው:: ከ600 የጂብሪል ክንፎች ውስጥ ሁለቱ ብቻ አድማሱን ይሞላል:: ከእነ600 ክንፉ ሲያዩት ደነገጡ:: ጂብሪልን ከእነሙሉ ተፈጥሮው ቀርቶ የአላህ ቃል ሲመጣ ከክብደቱ ብዛት ብዙ ጊዜ ልባቸው ይመታል:: ያልባቸዋል:: እንደ ቀደምት ነቢያት ሕዝቦች የሳቸውም ሕዝብ እንዳይጠፋ ይፈራሉ:: የአላህ ቁርአን ሲተላለፍ ጂብሪልም ሌሎች መላእክትም እራሳቸውን እንደሚስቱ በሀዲስ ተነግሯል:: የእኛ ልብ የማይመታው እኮ ከድርቀታችን ብዛት ነው:: አንዳንድ በቁርአን የተመሰጥን ቀን ድንገት ሊመታ ይችላል::

ሌላው የሚለው ነቢ አደም, ነቢ ኑህ, ነቢ ኢብራሂም, ነቢ ሙሳ ብለውታል, እኛም ሙስሊሞቹ በየሶላቱ መግቢያ እንለዋለን:: ከዚህም በተጨማሪ ሶላት እየሰገድን ለአላህ ቆመን > እንላለን:: ለምን? ነገ እንዳንጠም እና አሁንም ቢሆን ከነበርንበት ቅናቻ ይበልጥ እንድንቃና ነው::

የመጀመሪያ ሙስሊም እንድንሆን የታዘዝነው ወይም የመጀመሪያ ሙስሊም አድርገኝ የምንለው በእስልምናቸው ውበት ቀዳማይ ወይም እስልምናቸው የተሟላና ጸአዳ ሙስሊሞች ጋር አድርገኝ ማለታችን ነው:: ነቢዩ ሙሐመድ ﷺ የሙስሊሞቹ የመጀመሪያ ናቸው:: በእስልምና የሚቀድማቸው ነብይም ይሁን መላእክት የለም:: ከአፈጣጠርም አኳያ ከአደም ይቀድማሉ:: በእሳቸው ሲታይ አባታችን አደም የትናንት ሕጻን ነው:: ይህንን ትምህርት የምንማረው ውስጥ ነው:: ኢስላም, ኢማንና ኢሕሳን የሚባሉ ትምህርቶች አሉ:: ዝርዝር ውስጥ አልገባም::

ከሚያሳዝነው ሁሉ የሚያሳዝነው አንድን ተራ ግለሰብ ተሳስተሃል ከማለት ይልቅ የነቢያችን ﷺ ክብር ላይ የሚረማመዱና እስልምናቸውን የሚመዝኑና የሚተቹ መንጋዎቹ ሁኔታ ነው:: ነቢዩ ሙሐመድ ﷺ በአካል ቢመጡ ኖሮ መንጋው ብሎ ከእርሱ ጎን መሰለፉና ነቢዩን ﷺ መዋጋቱ አይቀርም ያስብላል:: ይህ የፈተና ሰው በቀጣይ በአላህ ላይ ሳያከራክረን አይቀርም::

ጽሑፉን ሲቋጭ ከፖሊስ ሰልጣኞች ጋር ፎቶ ለጥፎልናል:: ማንም አይነካኝም ማለቱ ይመስላል:: እርሱ በጠራው ፈተና ብዙ ሰው ታሰረ, ተገረፈ, ሞተ:: ሙስሊሙ በዘር ተቧድኖ የሚጋደልበትን ቀን ይጠባበቃል:: ረመዷን, ዒድ እና ጁምዓ ሲደርስ ውሾቹ እንዲያጉዋሩ ጃስ ይላቸዋል:: መስጂድ ሁሉ ይረበሻል:: ረመዷን የመከራ ወር ሆኖ ያልፋል:: እንዲህ ያለ ፈታኝ በጽሑፍ እንጂ በአካል አናውቅም::

©Hasen Injamo

Показано 20 последних публикаций.

1 006

подписчиков
Статистика канала