👆🏻የዲኔ ጉዳይ ያገባኛል👆🏾


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


በዚህ ቻናል
♦️#ተውሒድና_ሱና በሰለፎች አረዳድ ብቻ ከተለያዩ የሰለፊያ መሻይኾችና ኡስታዞች ትምህርት ይቀርባል።
♦ እንዲሁም ሙስሊሙን የተመለከቱ ወቅታዊ መረጃዎችን እናጋራለን ተቀላቀሉ
ولقد بعثنا في كل أمة رسولاً عن اعبد الله واجتنبوا الطاغوت
https://t.me/yedine_guday

ሀሳብ እስተያየቶን በ👇ያድርሱን
@Yedinegudaybot

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


በወንድም ሳሚ የተፃፈ

ለመርከዝ ኢብኑ መስዑድ እና ለነሲሓ ቲቪ አመራሮችና አባሎቻቸው

ምላሹንም የምፈልገው ከጠቀስኳቸው አካላት ነው።

በአደባባይ ያመጣሁትም በአደባባይ የሰሩት ነገር ስለሆነ እና ለዳዕዋው በመቆርቆርም ጭምር ነው።

በተረጋጋ መንፈስ ምላሽ ቢሰጥ መልካም ነው። ከነፍሲያ ወጥተን በመሃል ለታዩ ችግሮች ምላሽ አለመሰጣጠት እንዲሁም በእውቀት እና በስርዓት ምላሽ አለመሰጣጠት በመሃል ያለውን ልዩነት ከማጥበብ ይልቅ ልዩነቱን ወደ ማስፋት ያመራል እና በተረጋጋ መንፈስ መተራረሙ መልካም ነው።

ከነቢያችን ﷺ ወዲህ ከስሕተት የተጠበቀ ሼይኽ፣ ኡስታዝ፣ ጣሊበል-ዒልም እንደሌለ መዘንጋት የለብንም። "ሼይኼ ለምን ተነካ?" ሳይሆን "ምን አድርጎ ነው?" ብለን ማጤን አለብን። ስሕተት ካለ ማረም ከሌለ ደግሞ መመከት።

የመጨረሻው ቅድመ-ጥያቄዬ "ለምን ቀርባችሁ አልተመካከራችሁም?" እንዳይባል ቀርበን ሂደን አውርተናል ግን ከመሻሻል ይልቅ እየባሰ የመጣ ችግር ሁኗል።

-------ጥያቄዬ-------

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በ"መስለሓ" ስም ድሮ ስትኮንኗቸው ከነበሩ ሰዎች ጋር መቀራረብን መመስራታችሁ አደባባይ የወጣ እውነታ ነው፤ በተለይም ከዳዕዋ ቲቪ አባላት (እነ ሼይኽ ሙሓመድ ሓሚዲን እና ባልደረቦቻቸው) ጋር።

አሁን ደግሞ ከአፍሪካ ቲቪ አባላት ጋር ለመስራት እየተቀራረባችሁ እንደሆነም እያየን ነው። "መጥተውባችሁ ነው" እንዳይባል ሄዳችሁባቸው ነው። ማስረጃውንም ኮሜንት ላይ አስፍሬዋለሁ።

ጥያቄዬ:
1- ድሮ ለምን እና በምን ጉዳይ ኮነናችኋቸው?

2- አሁን ላይ ከነሱ ጋር መስራት የጀመራችሁት ድሮ ከነበረባቸው ችግር ተመልሰው ነው ወይስ ድሮ ስትኮንኗቸው የነበረው እናንተው ተሳስታችሁ ነው?

3- ከነበረባቸው ችግሮች ተመልሰው ከሆነ የተመለሱበትን መግለጫ በድምፅም ሆነ በፅሑፍ ያቅርቡ ወይም አቅርቡላቸው።

4- "መጀመሪያም ችግር አልነበረባቸውም" ካላችሁ ለስከዛሬው እናንተው መግለጫ አውጡና ጥፋታችሁን አምናችሁ እኛም እነዚህን መሻኢኾች እንጠቀምባቸው፣ አብረናቸውም እንስራ።

አላህ በሚያውቀው አንድነትን አንጠላም፣ አንድነትን የሚጠላ ልቡ ላይ ችግር ያለበት ሰው ነው፣ አሊያም ስለ አንድነት ያለው ግንዛቤ የተዛባ ነው።

👉 አንድነት ሲባል ግን በዓቂዳም በመንሃጅም አንድ ሲኮን ነው፣ ይሄን ነው ያስተማራችሁን። የሰለፎቻችንን ዓቂዳ ይዞ መንሃጁ ከሰለፎቻችን መንሃጅ ውጪ ከሆነ የአካሄድ ችግር አለበት።

እነዚህ እና መሰል ጥያቄዎች የኔ ብቻ ሳይሆኑ ለናንተ የሚወግኑ ወንድም እህቶች ጥያቄዎች ናቸው።

መልሳችሁን 1- 2- 3- 4- ብላችሁ መልሱልን።

እጠብቃለሁ
Sami Abu Meryem


ነገ ሰኞ ነው
“ሰኞና ሐሙስ ስራዎች ወደ አሏህ ይቀርባሉ። እኔም ፆመኛ ሆኜ ስራዬ እንዲቀርብልኝ እወዳለሁ።“
ረሱሉል አሚን
اللهم صلي على محمد وعلى اله محمد


ከተላመዳቸው ኃጢያቶች በሸዕባን ወር ላይ መቆጠብ ያልቻለ ሙስሊም ረመዳን ሲገባ በአንድ ጊዜ ማቆሙ እንዴት ይቻለዋል?

ሸዕባን የቅድመ ዝግጅትና የመለማመጃ ወር መሆኑን እናስታውስ።
=t.me/Sle_qelbachn1


🔖 በኢሞ ቀጥታ ስርጭት የተደረገ መንሃጃዊ ጥያቄና መልስ

🎙በኡስታዝ ኸዲር አሕመድ [አቡ ሓቲም
-ሐፊዘሁሏህ-

🔗 የካቲት 06/2017 ዓ.ል
የቴሌግራም ቻናል=
https://t.me/UstazKedirAhmed


በቡድን የመጥጠርነፍ ጣጣ
~
በደዕዋ ላይ የተሰማራ ወይም ወደ ደዕዋ የተጠጋ ሰው ለሌሎች የሚያሳድረው ውግንናም ይሁን ጥላቻው ቡድናዊ ተፅእኖ የተጫነው እንዳይሆን ሊጠነቀቅ ይገባል። በተቋማትና ማህበራት የታቀፉም ይሁኑ በሆነ የጋራ አመለካከት የተሳሰሩ አካላት ጥንቃቄ ካላደረጉ ስብስባቸውን ያማከለ ቡድናዊ ዝንባሌ (ተሐዙብ) የሚይዙበት ሁኔታ ሰፊ ነው። ስብስቡን ወይም የጭፍራውን ቁንጮዎች በጭፍን የመከተል ጥፋት ሊኖር ስለሚችል መጠንቀቅ ይገባል። ብዙ ጭፍራዎች የፖለቲካ ፓርቲዎች አይነት ጥርነፋ አላቸው። በፖለቲካ ፓርቲዎች ውስጥ በአብዛኛው አባላት ባያምኑበት እንኳ የፓርቲውን እንጂ የግላቸውን አቋም ባደባባይ አያንፀባርቁም። በኢስላም ስም የሚደራጁ ስብስቦችም ይሄ ባህሪ የሚታይባቸው በብዛት ይገጥማሉ። ማዶና ማዶ ከሚኖሩ አሰላለፎች ሁለት ምሳሌ ልጥቀስ።

1ኛ፦ መፅነፍ፦

የፀነፈ አቋም ለደዕዋ እንደማያዛልቅ፣ የትም እንደማያደርስ፣ በመጨረሻም እርስ በርስ መበላላትን እንደሚያስከትል የታወቀ ነው። ይሄ ከጥንት እስከ ዛሬ ያሉ ፖለቲካዊም ይሁን ሃይማኖታዊ አደረጃጀቶችን ያየ ሁሉ የሚያስተውለው ነው። በዚያ ላይ በተመሳሳይ አጀንዳ አንዱን መውጋት፣ ሌላውን ማለፍ አይነት መርህ የለሽነት ላይ ይጥላል።

ነጥቤ ምንድነው? በዚህ አይነት ስብስብ ታቅፈው ግን ውስጥ ላይ ችግሮች መኖራቸውን እያወቁ "ለምን?" ለማለት በመንጋው እንዳይወገሩ ፈርተው በዝምታ የሚጓዙ አካላት አሉ። "ለምን?" ያሉ ለታ የሚወሰድባቸው እርምጃ ማዶ ላይ ካሉት የከፋ ስለሚሆን በቡድን ተጠርንፈው፣ በፍርሃት ተሸብበው፣ ውስጣቸው ያለውን እምነት መኖር አቅቷቸው ካቦዎቹ በቀደዱላቸው ቦይ ይፈስሳሉ። ይሄ በብዙ ፅንፈኛ ቡድኖች ውስጥ ያለ ተጨባጭ ነው።

2ኛ፦ መላሸቅ፦

በዚህም ላይ አንዳንዶች የተጨመላለቀ አካሄድ በጭፍራቸው ሲፈፀም ሲያዩ ከመሸማቀቅ ውጭ "አልበዛም ወይ?" ለማለት ቡድናዊ ትስስር ወይም ጥቅም ያሰራቸው ብዙ የውስጥ ቆዛሚዎች አሉ። መላሸቁ በበዛ ቁጥር ቁዘማቸው ይረዝማል። ውስጣቸው ይታመማል። ቢሆንም ራሳቸውን መሆን መወሰን አይችሉም። ራሳቸውን ችለው ቢንቀሳቀሱ ከዚህ ሰቀቀን ነፃ ይሆኑ ነበር። ችግሩ ቀድመው በቡድን ተጠርንፈዋል። የጭፍራው ካቦዎች በተጣጠፉ ቁጥር ያለምርጫቸው ይተጣጠፋሉ። በወረዱበት ቁልቁለት ሁሉ ይወርዳሉ። በማያምኑበት መድረክ ሲያሰማሯቸው ይሰማራሉ። ወይ ራሳቸውን ከጥፋቱ አግልለው ሰላም አያገኙ። ወይ ጭንቅላታቸውን እንደ ካቦዎቻቸው ደፍነው አይገላገሉ። እንዲሁ ከሁለት ያጣ ጎመን።

በየትኛውም ቡድንተኛ ጭፍራ ውስጥ መጥጠርነፍ የህሊና ሰላም፣ የልቦና ረፍት ያሳጣል። ከኢኽላስ ያርቃል። አስመሳይነትን ያላብሳል። መርህ የለሽ ያደርጋል። ስለዚህ ከራስህ ጋር ተጣልተህ የሌሎች አጫፋሪ ከምትሆን ራስህን ነፃ አውጣ። ከአጉል ስብስብ አግልል። መንጋ ጋር አትጓዝ። እንዲህ አይነት ስብስብን በተመለከተ ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
فَاعْتَزِلْ تِلكَ الفِرَقَ كُلَّهَا، ولو أَنْ تَعَضَّ بأَصْلِ شَجَرَةٍ، حتَّى يُدْرِكَكَ المَوْتُ وأَنْتَ علَى ذلكَ!
"ከነዚህ አንጃዎች በሙሉ ራቅ። የዛፍ ስር ነክሰህ መያዝ ቢኖርብህ እንኳ! (ያን አድርገህ ራቅ።) በዚህ ላይ ሆነህ ሞት እስከሚያገኝህ ድረስ።" [አልቡኻሪይ፡ 3606] [ሙስሊም፡ 1847]

የሚገርመው በሁለቱም ጫፎች ተሰልፈው ከነሱ የማይሻሉ አካላት በቀደዱላቸው እየፈሰሱ አበሳቸውን የሚያዩ ክፍሎች መኖራቸው ነው። ወንድሜ ጉዳዩ ከዘላለማዊ ህይወትህ ጋር ይገናኛል። የኣኺራህ ጉዳይ ላይ ሌሎች እንዲወስኑ አትፍቀድ። ከሰመመንህ ውጣ። አይንህን አሸት አሸት አድርግና ከማን ኋላ እንደተሰለፍክ ተመልከት። ልጅ ቢጎትተው፣ ጅል ቤጎትተው ሳያቅማማ የሚከተለው ግመል ነው። ሰው ተደርገህ ተፈጥረሃልና በተግባር ሰው ሁን።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


ታላቅ የዳዕዋና ኮርስ ፕሮግራም      
           በቡታጅራ ከተማ!

=
እነሆ የፊታችን ሐሙስ ቀን 06/06/2017 ከመግሪብ ሰላት በኋላ ጀምሮ እስከ ቅዳሜ ቀን 08/06/2017 ድረስ የሚቆይ የዳዕዋና ኮርስ ፕሮግራም በቡታጅራ ተሰናድቶ ይጠብቅዎታል።

በዕለተ እሁድ ደግሞ ሰፋ ባለ መልኩ በኢንሴኖ ከተማ ደማቅ ፕሮግራም የሚካሄድ ይሆናል። በዚህ ፕሮግራም የተለያዩ ጊዜውን ያማከሉ አርእስቶችና ረሳኢል በኮርስና ዳዕዋ መልክ ይሰጣሉ።

እርሶም የዚህ ታላቅ ፕሮግራም ተሳታፊ ይሆኑ ዘንድ ጥሪ ስናቀርብልዎ በታላቅ ደስታ ነው።

☞ ተጋባዥ እንግዶች፦
     * ሸይኽ አወል አሕመድ አልከሚሴ
     * ኡስታዝ ኸድር አሕመድ አልከሚሴ እና ሌሎችም ኡስታዞችና ዱዓት ይገኛሉ።

«እውቀትን ፍለጋ መንገድን የጀመረ አላህ የጀነትን መንገድ ያገራለታል።» ረሱልﷺ

https://t.me/butajira_Qirat_daewa_group


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ኢማሞች በተከታዮቻችሁ ላይ እዘኑ

ትናትና መጝሪብ የሰገድኩበት አዲስ ኢማም በሁለቱም ረከዓ ከሱረቱል በቀራ አንድ አንድ ሶፍሓ አሰገደን። እውነት ለመናገር ኢማሙ በዛ መልኩ ስላሰገደን በጣም አልተመቸኝም ነበር፡ ሰላት ከጨረስን በኋላ ተንቢህ አደርገዋለሁ ብዬ በኋላ ሌላ የደርስ መልእክት ሲጨመር ሁኔታው ባለመመቻቸቱ ትቼው ወጣሁ። ለዒሻ ስመለስ ከእኔ ውጭ ሁለት የተለያየ ሰው እሮሮ አሰማኝ። አጂብ! እለቱ ሰኞ፣ ወሩ ሸዕባን፣ ሰላቱ መጝሪብ ነው። ብዙ ሰው ሊፆም እንደሚችል ይገመታል፡ ብዙ ፆመኞቹም ሽማግሌዎች ነበሩ። ለምን በዚህ አይነት ወቅት ፈትታን ይኮናል? ኢማሞቻችን ኢንተቢሁ ወላ ተኩኑ ፈታነን ዓላ መእሙሚኩም።

ጢዋለል ሙፈሶል
ወሰጦል ሙፈሶል
ቂሷረል ሙፈሶል
እነማን ናቸው፣ የአሏህ መልእክተኛስ صلى الله عليه وسلم የትኛውን ሙፈሶል በየትኛው ወቅት ያዘወትሩ ነበር ? ሸይኽ ዓብዱስሰላም አሽሹወይዒር ይናገራሉ፡ ፈስተሚዑ ለሁ 👂
https://t.me/yedine_guday


👉ዘመቻ ወደ ቲክቶክ ‼️‼️‼️‼️‼️

♨️በቂ ጊዜ ያላችሁ መሻይኾችና ኡስታዞች ሆይ‼️

ከየመስጂዱ እየተገለለና እየተፈናቀለ ያለዉ የአህባሽ መንጋ ቲክቶክ ላይ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን እየቆራረጠ፣ መረጃዎችን እየቀላቀለና ያለ አግባብ እየተረጎመ የአህሉሱናዎችን ስም እያጠፋ ወጣቱንም እያሳሳተ የተበከለ አቂዳዉን በሰፊዉ በመርጨት ላይ ስለሆነ በቲክቶኩ አለም መዝመት የግድ ያስፈልጋል።

👉እኛ ቲክቶክን አንጠቀምም ብለን ብንተወዉም ይህ ሀረር ላይ የበቀለዉ የጥፋት ጭፍራ ግን ያለ የሌለ አቅሙን ተጠቅሞ ህዝባችንን በማደናገር ላይ ተሰማርቷል።

♨️አዎ ጉዳዩ ከአሳሳቢነትም በላይ ነዉ‼️

ስለዚህ ጊዜና ብቃቱ ያላችሁ ኡስታዞችና መሻይኾች ይህንን ጥፋት እያየን ዝም ማለታችን
👉1 ኛ ሙንከር ሲስፋፋ እያየን ዝም በማለታችን አላህ ፊት ያስጠይቀናል።

👉2 ኛ አህባሾች ባጢላቸዉን ሲዘሩ እያየን ዝም ስንላቸዉ የዋሁ ህዝባችን እነርሱ የተናገሩት ሀቅ ላይ ስለሆኑ ነዉ። እነዚህ ዝም ያሉት ደግሞ ሀቅን ስላልያዙ ነዉ። የሚል አደገኛ ድምዳሜ ላይ ይደርሳል። እንጂ ሆደሰፊነት ነዉ፣ ወይም ሙስሊሙ ለካፊር መሳለቂያ እንዳይሆን አስበዉ ነዉ ብሎ አይረዳህም።

እናም አማራዉን በአማረኛ፣ ኦሮሞዉን በኦሮሞኛ፣ ስልጤዉን በስልጤኛ፣ ዐረቡን በዐረበኛ አጠቃላይ አጥፊዉ በሚናገረዉና በሚገባዉ ቋንቋ መናገር፣ መርዙን መንቀል፣ ህዝቡን ከጥፋቱ መታደግ፣ ጅህልናዉንና ማምታቻዉን ለህዝብ ማጋለጥ፣ የጥፋት ምላሱን እንድሰበስብና ገዳይ መርዙን እንድዉጥ ማድረግ ኢስላማዊ ግዴታችን ነዉ።

ማሳሰቢያ ‼️

አህባሾችም ላይ ሆነ ሌሎች የተሳሳቱ ወገኖች ላይ መልስ ስንሰጥ መዘንጋት የሌለብን ነገራቶች ይኖራሉ።

ጥቂቶችን ልጥቀስ

① እናስተካክላለን ብለን ሌላ ጥፋት እንዳናስከትል በቂ እዉቀትና መረጃ ላይ ተመርኩዝን መሆን አለበት‼️

② ከቁርአንም ሆነ ከሀዲስ በምናቀርበዉ መረጃ ላይ እርግጠኛ መሆን ግድ ነዉ‼️

③ ለፍዞል ቁርአንንም ሆነ ሌላ ዐረበኛ ቃልን ስናነብ መኻሪጀል ሁሩፍ ላይ እና ዒዕራቡ ላይ ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይኖርብናል‼️

③ ቪድዮዉ አሰልቺ እንዳይሆን በተቻለ መጠን አጠር ያለ ቢሆን ይመረጣል‼️

④ እነርሱ ቢያደርጉትም ትምህርቱ ፍፁም ከዉሸት፣ ከስድብና ከዘለፋ የራቀ መሆን አለበት‼️

⑤ መልስ ከተሰጠባቸዉ ወገኖች በኩል ለሚመጣብን አፀፋዊ መልስና ዘለፋ አለመደናገጥና አስገዳጅ ነገር ካልተፈጠረ በስተቀር ጀምሮ አለማቋረጥ‼️

⑥ ግድ ሁኖብን እንጂ ቲክቶክ አስደሳች አለም ስላልሆነ ከሚጋረጡብን የጎንዮሽ ሙንከራቶች እራሳችንን ማራቅና ነፍስያችንን ማሸነፍ‼️

⑦ በየአቅጣጫዉ ለህዝቡ ተደራሽ ይሆን ዘንድ በቲክቶክ የተለቀቁ ትምህርቶችን እንደ ቴሌግራም፣ ፌስቡክ፣ ዋትስአፕ የመሳሳሉ ሌሎች ማህበራዊ ትስስር ገፆች ላይ በሰፊዉ ማሰራጨት‼️

✍ ሙርሰል ሰይድ ጨፌ 30/5/2017
👉ጆይን https://t.me/murselseid




የጁሙዓን ሶላት በተከታታይ ለማይሰግዱ ወንድሞች....

🎙ኡስታዝ አቡ ሓቲም


⭐️አሁን በምንኖርባት ምድር በሂወት ጉዞህ ሶስት አይነት ሰዎች ያጋጥሙሀል

🛑አንዳንዶቹ እንደ እለት ቀለብህ ምንጊዜም የሚያስፈልጉህ እነዚህም በመልካም ሚያዙህ ከመጥፎ የሚከለክሉህ በጥቅሉ ስለ ዲንህ ጉዳይ የሚያሳስባቸዉ የሚቆሮቆሩ ሰዎች ናቸዉ ።

🛑አንዳንዱ እንደ መድሀኒት በሀጃህ ሰዐት ብቻ የሚያስፈልጉህ ሲሆኑ

🛑ከፊሎቹ ደግሞ እንደ መርዝ ናቸዉ በፍጹም በሂወትህ ዉስጥ አያስፈልጉህም እነዚህም ወደ ወንጀል ሚጠሩህ ለዲንህም ሆነ ለዱንያህ የማይጠቅሙህ ናቸዉ ሰላም ታገኝ ዘንድ ከአንበሳ እንደምትሸሸዉ ሽሻቸዉ

منقول من بداية الهداية بتصرف




የነገው ቀጠሮ

በደመቀው ሳሎን - በተዋበው ማጀት
ብትቀማጠለው ከልጅ እስከ ማርጀት

ያሻህን ብትነዳ በዝቶ ተሽከርካሪ
አለምን ብታስስ በሰማይ በራሪ

ጉድጓድ ነው ማረፊያህ የነገ ቀጠሮ
አፈር ልብስህ ሊሆን ሱፍህን ቀይሮ

ታገል ወንድሜ ሆይ ሰንቅ ለአኺራ
ፀፀት ያኔ አይጠቅምም ዛሬ ካልተሰራ



https://t.me/Muhammedsirage


" ኑ በሙያችሁ 'ሙያዊ ሰደቃን አበርክቱ!' " - የፌደራል መጅሊስ

Kottaa ogummaa keessaniin , sadaqaa ogummaadhaa gumaachaa. ¡¡¡

Majlisa federala


كيف #تحفظ_المتون مثل حفظ الفاتحة..

العلامة محمد علي آدم الإتيوبي -رحمه الله رحمة واسعة-

👈 ويذكر طريقته في الحفظ..


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
☜ تلاوة جميل جدا

ቁርአን የልብ ብርሀን የዱኒያ የአሄራን ህይወት የሚያቀና የማይጠገብ ውብ የአላህ ቃል ነው።


https://t.me/yedine_guday


የደዕዋ ድግስ በደሴ ከተማ ወሎ ባህል አምባ አዳራሽ


ታላቅ የምስራች ለደሴ እና አከባቢዋ ሙስሊም ማህበረሰብ  በሙሉ እነሆ የፊታችን እሁድ በቀን 25/05/2017 ዓ·ል  በአላህ ፍቃድ የወሎ መናገሻ እና እንብርት በሆነችው  ደሴ  ከተማ ወሎ ባህል አምባ አዳራሽ  ከአድስ አበባ ፣ ከአፋር፣ ከኸሚሴ፣ እና  ከሌሎችም ሀገራት በሚመጡ ብርቅዬ መሻይኾችና ኡስታዞች   ከጧቱ 3:00 ጀምሮ  እጅግ በደመቀ እና ባማረ መልኩ  የደዕዋ ድግስ ተዘጋጅቶ ሲጠብቃችሁ በታላቅ ደስታ ነው
 
የዕለቱ ተጋባዥ መሻይኾችና ኡስታዞች


① ሸይኽ አወል አህመድ አል ኸሚሴ
ርዕስ:– ረመዷንን እንዴት እንቀበለው

② ኡስታዝ አብዱረህማን ሰዒድ(አቡ ሒዛም)
ርዕስ:–ሱናን አጥብቆ መያዝና ቢድዓን መራቅ(መጠንቀቅ)

③ ኡስታዝ አቡል አባስ (ናስር)
ርዕስ:– የተውሂድ አሳሳቢነትና የሽርክ አደገኝነት እንድሁም በምን ላይ ነው  አንድ የምንሆነው

④ ኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር (ሙሀመድ አህመድ)
ርዕስ:–ኢልምን በመፈለግ ላይ መበርታት፣የሶሻል ሚዲያ አጠቃቀማችን ምን መምሰል አለበት እና መልካም ስነ ምግባር

ማሳሰቢያ:–ለሴቶችም በቂ ቦታ አለ‼

N·B :– የቻናልና የግሩፕ ባለቤቶች በሙሉ ሼር በማድረግ ተደራሽ አድርጉት 

አዘጋጅ፦ የጀዕፈር ኢብኑ አቢ ጧሊብ የደዕዋና የቂርዓት ማዕከል


URGENT: - የደሴ ከተማና በዙሪያዋ ያላችሁ ሙስሊም ማህበረሰብ በሙሉ ፕሮግራሙ ዘንድ ትታደሙ ዘንድ ጥሪ አድርገንላችኋል።

ጆይን ይበሉ ቻናል

t.me/yedesse_selfyochi_yedewa_channel
ግሩፕ

https://t.me/yedesse_selfyochi_group


አልሀምዱሊላህ

የእህቶቻችን ለጊዜው እፎይታ ማግኘት እረፍት ነው። ይህ ከማህበራዊ ሚዲያ እስከ ተቋማዊ (መጅሊስ) ንቅናቄ በተጽእኖ የተቀለበሰ ውሳኔ ነው።

ይሁን እንጂ ይህ ዘላቂ መፍትሄ አይደለም። እስከወዲያኛው የዚህን ችግር ማዳፈን የሚቻለው እስከጥግ ታግሎ የትምህርት ሚኒስቴር የአለባበስ ኮድ ኦፍ ኮንዳክትን (መመሪያ) ማሻሻል እና ኒቃብን ከግልጽ ክልከላ ወደ ግልጽ ፍቅድነት መቀየር ሲቻል ብቻና ብቻ ነው።

ይህንን ከህግ፣ ከሞራል፣ ከሀይማኖት፣ ከማህበራዊ aspects አንፃር መሞገት፡ ማሳመንም ይቻላል። እስከዛው ሁሉም በየፊናው ይታገል።

ኢንሻ አሏህ አንድ ቀን እህቶቻችን ከነሙሉ ክብራቸው ቀና ብለው እስከኒቃባቸው የሚማሩበት ጊዜ ይመጣል!

እኝህ የትግል ጊዜዎችም ታሪክ ይሆናሉ። ኢንሻ አሏህ!

ታዲያ ያንኔ ከታሪክ ሰሪዎች ሆኖ ለመገኘት እንደ አቅማችን፡ እንደ ሚናችን፡ የበኩላችንን እንወጣ።


የዲላ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ጀማዓህ ያወጣው መግለጫ!


#Ethiopia: Muslim students at #Dilla University allege niqab ban, forcing some to stay in Mosque for days

Forty-four female Muslim students at Dilla University allege they have been barred from entering the campus for wearing the niqab, with some staying in a mosque for over five days. According to the students, the niqab was previously allowed but was recently prohibited due to "security concerns." One student explained, “Initially, it wasn’t strictly enforced,” and later, they were told “we couldn’t wear a black mask while wearing a hijab.”

The Chairperson of the Muslim Students’ Association confirmed that “many Muslim students have been staying in the mosque for the past five days” and are unable to attend exams or complete assignments. The Ethiopian Islamic Affairs Supreme Council has urged the Ministry of Education for a permanent solution, emphasizing, “Muslim female students at Dilla University should be allowed to resume their studies without obstruction.” The university has denied these allegations, stating, “Wearing the hijab has not been prohibited at our university.”

https://addisstandard.com/?p=48150

Показано 20 последних публикаций.