🙏ሰማያት ክብርህን ይናገራሉ🙏


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


ልቦናዬ መልካም ነገርን አወጣ ፤
እኔም የማርያምን ቅዳሴ እናገራለሁ ።
በማብዛት አይደለም በማሳነስ ነው እንጂ ፤
በማስረዘም አይደለም በማስጠር ነው እንጂ ፤
እኔስ የማርያምን ምስጋናዋን እናገራለሁ።
🌹🌹🌹🌹🌹🌺🌺🌺🌺

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


1⃣7⃣ደቂቃ ቦኃላ ይጠፋል


የ 200 ብር ካርድ የሚያስሸልም ጥያቄ!

በኢትዮጵያ በጣም አስቸጋሪ የነበረዉ  ረሀብ መች አመተምህረት ነበረ


⁉️ጥያቄና መልስ
🌺🌺🌺🌺

'https://t.me/addlist/33Faa1YThXUwMjU0' rel='nofollow'>❤️፩. ኦርቶዶክስ ማለት ምን ማለት ነው?❤️

፪. ጌታ ለምን ድንግል ከሆነች ማርያም 'https://t.me/addlist/33Faa1YThXUwMjU0' rel='nofollow'>ተወለደ? (ለምን በድንግልና ተወለደ?)


🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤 dan repost
"በሰማይ የምትኖር ሆይ፥ ዓይኖቼን ወደ አንተ አነሣሁ፤ እነሆ፥ የባሪያዎች ዓይኖች ወደ ጌታቸው እጅ እንደ ሆኑ፥ የባሪያይቱም ዓይን ወደ እመቤትዋ እጅ እንደ ሆነ፥ እንዲሁ እስኪምረን ድረስ፡ ዓይናችን ወደ አምላካችን ወደ እግዚአብሔር ነው'' መዝ. 122:1-3

#ድምፀ_ተዋህዶ

▫️https://t.me/dmtse_tewaedo




🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤 dan repost
#እንኳን #ለፆመ_ጽጌ በሳላም አደረሳቹህ

✤ወርኃ ጽጌ 40 ቀናት ነው፤ መስከረም 26 ተጀምሮ ኅዳር 5 ያልቃል፤ ጾመ ጽጌ የፈቃድ ጾም ነው (ከሰዓትም ቅዳሴ የሚቀደሰስባቸው አካባቢዎች አሉ (ጎንደር )፡፡
በግዕዝ ጸገየ ማለት   አበበ ፤ አፈራ ፣ በውበት ተንቆጠቆጠ ማለት ነው፡፡ 
በማኀሌቱም ወቅትን እመቤታቸንን 3 ዓመት ከ6 ወር እስከ ግብፅ ከዚያም የአሥራት ሀገሯ  በሆነችው በኢትዮጵያ የተሰደደችበትን ወቅት በማሰብ  በጽጌና በአበባ እመቤታቸንን እና ጌታቸንን በመመሰል ሲያመሰግኗት ፣  ከልጇ ጋር ያየችውን መከራ  እያሰቡ  እና  ምልጃዋን ሲለምኑ ያድራሉ ፡፡

✤እምግብጽ ጸዋዕክዎ ለወልድየ ለክብረ ቅዱሳን፤ ለቅዱሳን ክብር ልጄን ከግብጽ ጠራሁት››
በማለት ነቢዩ ሆሴዕ በምዕራፍ ፲፩ ቍጥር ፩ እና ፪ ላይ አስቀድሞ እንደ ተናገረው ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በልጅነቱ ወደ ምድረ #ግብጽ (ምስር) የተሰደደው የነቢያት ትንቢት ይፈጽም ዘንድ ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ሕፃናትን በመፍጀት ከሚታወቀው ከአረመኔው ንጉሥ ከሄሮድስ ለማምለጥ ነው፡፡ አምላካችን ክርስቶስ ያለጊዜው (ዕለተ ዓርብ) #ደሙ #አይፈስምና፡፡ ስለዚህም ‹‹ሕፃኑንና እናቱን ይዘህ ወደ ምድረ ግብጽ ሽሽ፤ ሄሮድስ ሕፃኑን ለመግደል ይፈልጋልና›› ብሎ መልአኩ ቅዱስ #ገብርኤል ለዮሴፍ በነገረው ቃል መሠረት ሕፃኑንና እናቱን ይዞ በሌሊት ወደ ግብጽ ምድር ተሰደደ፡፡ ይህንን ስደት አስመልክቶ #ሰቆቃወ ድንግል የሚባለውን ቃለ እግዚአብሔር ካህናቱ በሚያሳዝን ዜማ ያደርሳሉ፤ ያቀርባሉ፡፡

#በመቶ ሺሕ የሚቆጠሩ ሕፃናትን ሄሮድስ አስፈጅቷል፡፡ ‹‹ድምፅ በራማ ተሰማ፤ ለቅሶና ብዙ ዋይታ፡፡ ራሔል ስለ ልጆቿ አለቀሰች፡፡ መጽናናትም አልወደደችም፤ የሉምና›› የሚለው ትንቢትም ተፈጸሟል፡፡

#ከሦስት ዓመት ከመንፈቅ የግብጽ ስደት በኋላ ሊቃውንቱ፡- ‹‹ተመየጢ ማርያም ሀገረኪ ናዝሬተ፣ በላዕሌኪ አልቦ ዘያበጽሕ ሁከተ፣ ወኢትጎንድዪ በግብጽ ከመ ዘአልብኪ ቤተ፣ ዘየኀሥሦ ለወልድኪ ይእዜሰ ሞተ፣ በከመ ነገሮ መልአክ ለዮሴፍ ብሥራተ›› እያሉ ከስደት መመለሷን ያበሥራሉ፡፡ ትርጉሙም፡- ‹‹ማርያም ሆይ! ወደ ሀገርሽ ወደ ናዝሬት ተመለሺ፡፡ በአንቺ ላይ ሁከት የሚያመጣ ማንም የለም፡፡ ቤት እንደሌለሽ ሁሉ በግብጽ አትቆይ፡፡ ለዮሴፍ በሕልሙ መልአክ እንደ ነገረው የሕፃኑን ነፍስ የፈለገው (ጠላት ሄሮድስ) ሞቷልና›› ማለት ነው፡፡ የኢትዮጵያ #ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን በዐርባው ቀን (በዘመነ ጽጌ) ወቅት የማርያምን የሽሽትና የመመለስ (የሚጠት) ታሪክ እያነሡ ውዳሴ የሚያቀርቡትና ማኅሌት የሚቆሙት በዚሁ ምክንያት ነው፡፡ በዚህ ወቅት ለእመቤታችን ክብር ሲባል የፈቃድ ጾም የሚጾሙ ምዕመናንና ምዕመናትም ብዙዎች ናቸው በመሃል ኢትዮጵያ  በፈቃድ ጾምነት ሲጾም ; በሰሜኑ አካባቢ ተጹሞ ከሰዓት ይቀደሳል ሌሎች ጋር ግን ጠዋት ያበቃል፡፡

የእመቤታችን ምልጃ ና ጸሎት አይለየን

#ማኅሌተ_ጽጌ
✤የማኅሌተ ጽጌ  የሰቈቃወ ድንግል ደራሲ አባ ጽጌ ድንግል ነው ፡፡
  ገዳሙም ትልቅና ሰፊ የኾነ የፍልፍል ዋሻ ሲኾን ወሎ ወግዲ ወለቃ ወንዝ አጠገብ በረሃ ላይ (ከጋሥጫ ገዳም የ4 ሰዓት የእግር መንገድ) ይገኛል፡፡
✤✤ በየዓመቱ ሳይመረገዱ ያመይታለፉ የማይቀሩ፤ ዚቃቸው የማይለወጥ፤
      እጅጉን በምንወደው የማኅሌተ ጽጌ ቁመት ላይ በየዓመቱ ሳይመረገዱ የማይታለፉ የማይቀሩ፤ ዚቃቸው የማይለወጥ
( ከማኅሌተ ጽጌ፤ ጽጌ አስተርአየ(የመጀመሪያው ሳምንት)፣ በከመ ይቤ መጽሐፍ፣ ትመስል እምኪ ማርያም፣ ዘኒ ስብሐተ ወዘኒ ማኅሌተ፣ ኢየሐፍር ቀዊመ ቅድመ ሥዕልኪ እና ኅብር ሐመልሚል (የመጨረሻው ሳምንት)ናቸው፡፡
✤ ከሰቈቃወ ድንግል፤ በስመ እግዚአብሔር ሥሉስ፣ ብክዩ ኅዙናን፣ እስከ ማዕዜኑ እግዝእትየ እና አብርሂ አብርሂ ናቸው፡፡
✤ከማኅሌተ ጽጌ ውስጥ እንዘ ተሐቅፊዮ ለሕፃንኪ እና ክበበ ጌራ ወርቅ በየሳምንቱ (በኹሉም ዓመታት) ይመረገዳሉ፤ ዚቁ ግን በዓሉን በተመለከተ ይኾናል፡፡
✤ ከላይ ካየናቸው ውጪ የሚገኙት #የማኅሌተ ጽጌና የሰቈቃወ ድንግል ክፍሎች ግን #በየሰባት ዓመት አንዴ ነው የሚመረገዱት፡፡
( የማኅሌቱ ሥርዐት የላይ ቤት (የጎንደር መካነ ነገሥት ግምጃ ቤት ማርያም አብነት) እና የታች ቤት (የጎንደር ደብረ ኀይል በዓታ ለማርያምን አብነት) የሚያደርግ ሲኾን፤

የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤ.ክ የማኅሌት ቁመትም የላይ ቤትን አብነት የተከተለ ሲኾን የዚቁ ወረብ ግን የደብሩን የራሱን (የሸዋን) የተከተለ ነው፤
( የላይ ቤት ቁመት የሚቆሙ አድባራት #ዘግምጃ ቤት የሚለውን እንዲከተሉ፤ የታች ቤትን #ቁመት የሚቆሙ አድባራት ዘበዓታ የሚለውን እንዲከተሉ፡፡ የዚቁ ወረብን ግን የቀጨኔ ደብረ ሰላም
የቤቱን ቀለም አስቀድመን ቀጥሎ ደግሞ ዓዲ (ወይም) በማለት የጎንደርን ስላስቀመጥነው እንደ ደብራችሁ ይትበሃል መርጣችሁ  ተጠቀሙ፡፡

/በቀጨኔ ደ.ሰላም መድኀኔዓለምና ደ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት የተዘጋጀ ::/

    #ድምፀ_ተዋህዶ

https://t.me/dmtse_tewaedo




🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤 dan repost
ይህችን ቅደስት ቤተ ክርስቲያን ካሰባችሁላት ተዋት!

ለልጆቻችሁም ካሰባችሁ ተውን!

ይህ ሕዝብ በጦርነት ዜና፣ በኑሮ ውድነት በሌላም ብዙ ጭንቀት አለበት። እንደአባትነታችሁ ሰላምን ባትሰጡት እንኳ ሌላ ወከባ አትጨምሩበት።

እንደፖለቲከኛ የያዛችሁት ሽኩቻ ሰልችቶናል።

ተናግራችሁና ሠርታችሁ አርአያ መሆን ካልቻላችሁ ዝም በማለት አርአያ ሁኑን!

ይህ ምእመን ቤተ ክርስቲያን ላይ ለደረሰው ሁሉ ዝም ያላችሁ ከላይ እስከታች ስላላጠፋችሁ አልነበረም።

አሳልፈው የሰጡት አባቶች ከመካከል እንደነበሩ ጠፍቶትም አይደለም። ግን ስለማእተቡና ስለቀደሙት አባቶቹ የደም ሰማእትነት ሲል ብዙ እየተደረገ በብዙ ዝም አለ።

እናንተ የተቋም መሪዎቻችን እንጂ ሃይማኖታችን አይደላችሁምና መሠረቱን ክርስቶስን አስቦ ታገሰ!

እናንተ ግን ተጸፅታችሁ ወደ አንድ መጥታችሁ ከውጫዊ ጥቃት ልትጠብቁት ይቅርና እያደረ አዲስ የውስጥ ፈተና ትጠራላችሁ።

ሙስናው፣ መልካም አስተዳደር ችግርና ውጫዊ ፈተናችን ብዙ ነው አይካድም።

የእናንተ የአደባባይ ንተርክ ግን እውነት ለቤተ ክርስቲያን ለውጥ አስባችሁ ነው? ወይስ ለክብራችሁ? ወይስ ስልጣናችሁን ለማጽናት?

ራሳችሁን በጾም በጸሎት የወሰናችሁ ብፁዓን አባቶችስ እስከመቼ ጥግ ይዛችሁ ታያላችሁ? ጸሎት ከሁሉም የበለጠ ኃይል እንደሆነ ብናምንም ተስፋ እንዳንቆርጥ ተግሳጻችሁን እንመኛለን!

እናም ጽሑፉ የሚመለከታችሁ ብፁዓን አባቶች የአደባባይ መዘላለፉን ትታችሁ በውስጥ ተሟገቱ። የውጭ ፈተናችን ይበቃናል። እንደተከታታይ ድራማ እናንተን መከታተል ደክሞናል።

እንዳው በልጅነት የምጠይቃችሁ ድፍረት አይሁንብኝና ከቻላችሁ ወደ ገዳም ገብታችሁ አረፍ በሉ። የጥሞና ጊዜ ጥሩ ነው ብላችሁ አስተምራችሁን የለ?

እስኪ እኛም ካለእናንተ አይነት መሪዎች ቤቱ ምን እንደሚሆን እንየው!

(ከድፍረት ያልሆነ በመድከም የተጻፈ)

✍️ መስከረም

#ድምፀ_ተዋህዶ


|°°ለጀማሪ የግእዝ ቋንቋ ወዳጆች ሁሉ
  🙌 ሰላም ጤና ይስጥልን ክቡራት እና ክቡራን የልሳነ ግእዝ ስልጠና በ @lesangeez128 እየሰጠን እንደሆነ ይታወቃል ሆኖም የጀማሪዎች ስልጠና  በቅርቡ በonline ስለሚጀመር በዚህ #ዙር ላይ 20 ተማሪዎች ብቻ ስለሚካተቱ ከወዲሁዠለጀማሪችሁን እንድታዘጋጁና በፍጥነት እንድትመዘገቡ መልእክታችንን እናስተላልፋለን።
#ለሁለት ወር የመማሪያ ክፍያ #250ብር ብቻ ለበለጠ መረጃ በ @asrategabriel ያነጋግሩን አልያም በ +251970908094 ይደውሉልን።

   🤲ሰብሕዎ የልሳነ ግእዝ ማሰልጠኛ ተቋም🧑‍🎓


🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤 dan repost


🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤 dan repost
#እሬቻ_ላይ_የሚከብረው_እግዚአብሔር_አይደለም_ዲያብሎስ_ነዉ።

🔵 እሬቻ ከክርስትና እምነት ጋር ፈጽሞ ተጻራሪና ጸረ ነፍስ ነው። የእሬቻ የዛር መንፈስ እንጂ ከመንፈስ ቅዱስ አይደለም። ለእግዚአብሔር እንጂ ለዛፍ አትንበርከክ። ለሚያልፍ ፖለቲካ የማያልፍ እግዚአብሔርን አናስቀይም።

"በወደዳችኋት የአድባር ዛፍ ታፍራላችሁና፥ " ኢሳይያስ 1፥29

🔵 እሬቻ ደብረ ዘይት [ቢሾፍቱ] ሆራ አርሰዲ ሓይቅ ዙርያ አርሰዲ የሚባለው መንፈስ እየተወደሰ አንዲት የአድባር ዛፍ ስር ይከበራል። ኢሬቻ የራሱ ካህናት አሉት።

🔵 ተከታዮቹም የሚገብሩት ራሱን የቻለ ግብር አለ። የአድባር ዛፏ ቅቤ ትቀባለች። ሐይቁ ውስጥ አለ ተብሎ ለሚገመተው ቆሪጥም የስለት አረቄ ይጣልለታል። ደስ እንዲለውም ከብት እየታረደለት ደም ይጠጣል። ሞራ ገላጮች "ትንቢት" ይናገራሉ። አማኞችም ተንበርክከው ተረፈ መስዋዕትን ይበላሉ።

🔵 ቪድዮውንና ፎቶውን ይመልከቱ። ቪድዮው ላይ ቁልጭ ብሎ እንደምትመለከቱት ኢሬቻ ሲደርስ አርሰዲ ለሚባለው መንፈስ የደም ግብር ይቀርብለታል። ደም ይጠጣል። የተረፈውን መስዋት ደግሞ ተከታዮቹ ይበሉታል። አርሰዲ የተባለው የኢሬቻ መንፈስ ደም ከጠጣ በኋላ - የኢሬቻ ካህን የሆኑት ወገኖች ላይ አድሮ ያስጓራቸዋል። መንፈሱ አርሰዲም "እኔ ሰው አይደለሁም። መንፈስ ነኝ። አልሞትም ወዘተ" እያለ ይፎክራል። የዛር ፈረስ በመባል የሚታወቁት ካህናቱም ለታመመ "ፈውስ" ይሰጣሉ።

🔵 እነዚህ የኢሬቻ ካህናት ኢሬቻ ሲከበር ሆራ አርሰዲ ያለችው የአድባር ዛፍ ስር እየተገናኙ ድቤ ይመታላቸዋል። ሆራ ቀውጢ ትሆናለች። ያቺ የአድባር ዛፍም ቅቤ ትቀባለች። በግምጃ ታጌጣለች። የሽቶ አይነት ይርከፈከፍላታል። ወዘተ . . . ማንም ሰው የፈለገውን ማምለክ ይችላል። መብቱ ነው። እጁን ወደሚያቃጥለው ወይም ወደ ቀዘቀዘው ውሃ የመክተት ነጻ ሕሊና አለው። መዘዙ ግን በኋላ ነው- የዛሬ ሳቅ የነገ ለቅሶ ስትሆን! ግን ኢሬቻ በሃይማኖት በተለይም በክርስትና አይን ሲታይ ምንድነው? ክርስቲያን የሆነ ሁሉ ኢሬቻን ማክበር ይገባዋልን? መልሱን መፅሐፍ ቅዱስ በማያሻማ ሁኔታ እንዲህ ሲል ይነግረናል።

🔵 "በወደዳችኋት የአድባር ዛፍ ታፍራላችሁና፥ " ኢሳይያስ 1፥29፤ እርግጥ ነው ኢሬቻ የምስጋና ቀን [thanksgiving] ነው። ግን የሚመሰገነውና የሚክብረው ማነው? አርሰዲ የሚባል ደም የሚጠጣ ክርስቲያናዊ አምላክ ወይም ቅዱስ መንፈስ የለም። የኢሬቻን ካህናት የሚያስጓራው ዛር ከክፉው እንጂ ከቅዱስ መንፈስ አይደለም። የክርስቶስም መገኛ ዛፍ ስር ወይም ሐይቅ ውስጥ አይደለም። የራሱ መመለኪያ ቦታ አለው።

🔵 ሳር የሚበተንለት፣ ስለት የሚገባለት፣ ከብት ታርዶ ደም የሚረጭለት፣ የሆራው ቆሪጥ ርኩስ መንፈስ እንጂ ቅዱስ መንፈስ አይደለም።  ዛፍ ምን ስለሆነ ነው ቅቤ የሚቀባው? እንዴት ክርስቲያን ራሱ ተክሎ ላበቀላት ዛፍ ይሰግዳል? እንዴትስ እንደ አምላክ እየታየ ቅቤ ይቀባል። ለምን ህዝብ ይንበረከካል ? ለምንስ ዛፍ ግምጃ ያለብሳል? እኛ ክርስቲያኖች በአምልኮ ልንሰግድለት፣ ልንበረከክለት የሚገባን አንድ አምላክ ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንጂ ዛፍ አይደለም።

🔵 እዚህ በዓል ላይ መገኘትም ሆነ መታደም በክርስትና ዓይን ፈጽሞ የነፍስ ስብራትን የሚያመጣ አምልኮ ባዕድ ነው። ጮክ ብዬ እደግመዋለሁ:- እሬቻን ያከበረ ክርስቲያን በእግዚአብሔር ፊት መጠየቁ አይቀርም። እሬቻ ላይ እግዚአብሔር አይከብርም። እርግጥ ነው:- ዛሬ ፖለቲካው ሃይማኖት ሆኗል። ብዙዎቹንም ፖለቲካ ከሃይማኖት በልጦባቸው "እሬቻ" አይነኬና አይደፈሬ ፖለቲካዊ ሃይማኖት ሆኗል። ትሰሙ እንደሆነ ለራሳችሁ ስትሉ ስሙ መቼም ቢሆን የጅብ ራስ ከመሆን ያንበሳ ጭራ እንሁን! ፖለቲከኞች ተደስተውብን እግዚአብሔር ከሚያዝንብን - መንጋው ጠልቶን እግዚአብሔር አይፈርብን። በነጻነት ስም በአምልኮ ባዕድ አተላ አንጠመድ። ወፍጮ ቤት ገብቶ ብናኝ ዱቄት ሳያገኘው የማይወጣ ሰው የለም። እንዲህ ዓይነት በዓላትም ላይ ተሳትፎ በመንፈሱ የማይወጋ አይኖርም። ወደሽ ከተደፋሽ - ቢረግጡሽ አይክፋሽ ነው ነገሩ። ዛሬ በዓል ያከበርን መስሎን ያደመቅነው የመንፈስ በዓል ነገ spiritual parasite ሆኖ እድሜ ዘመናችን ዋጋ የሚያስከፍለን እንዳንሆን!

🔵 ሞቀ ደመቀ በሚል በይሉኝታ ወይም በአድባርይነት የአምልኮ ባዕድ ሰባኪዎች የሆናችሁም - ነገ በእግዚአብሔር ፊት ዋጋ ትከፍሉበታላችሁ። የማይረባ የዘር ፖለቲካ ሰማይ ቤት ተክትሎህ አይሄድም። ዛሬ የሰበካት ውሸት ነገ ሰማይ ቤት እሳት ሆና ትበላሃለች። ዛሬ ለዛፍ እንዲሰግድ፣ ዛፍ ቅቤ እንዲቀባ ባደረከው ሕዝብ ነፍስ ነገ ለፍርድ ትቀርባለህ።

🔵 የመጨረሻው ዘመን ስለሆነ ሚሊዮኖች ይተማሉ። ርኩሰትም በተቀደሰችው ሀገር ይበዛል። ሌላው ቀርቶ መስቀል ይዞ የክርስቶስን ቀሚስ ለብሶ "እሬቻ ክርስቲያናዊ ነው" ብለው የሚሰብኩ ተረፈ ይሁዳዎች በየሚድያው ይበዛሉ። የመጨረሻው ዘመን ላይ ነን። ትንቢቱ ይደርስ ዘንድ ግድ ነው። ግን አንተ እግዚብሔርን እንጂ ዛፍን አታምልክ። ለቅዱስ መንፈስ እንጂ ለዛር አትገብር። ለክርስቶስ እንጂ ለአርሰዲ አትሸበር። "እሬቻ ኦርቶዶክሳዊ ወይን ኦሪታዊ ነው" የሚሉ በለአሞችን አትስማ። ስለበዙና መንጋ ስለሆኑ የቁጥራቸው ብዛት ያንተን እግዚአብሔርን አያስፈራውም። አንተንም በቁጥር አነስክ ብሎ አይንቅህም። ብቻህን ብትቀር እንኳን ከእውነት ጋር ብቻህን ኑር። አሸናፊው አንተ ነህ። ግን ሁሌም እውነትን እውነት በል።

🔵 እንኳን ለእሬቻ አደረሳችሁ ወይም መልካም እሬቻ ከማለታችን በፊት ደጋግመን ቃሉን እናስበው። ለማን አምልኮ በዓል አደረሳችሁ እያልን እንደሆነ እያስተዋልን።

🔵 እግዚአብሔርንም አመልካለዉ እያላችሁ ነገር ግን [ከእሬቻ፣ ከጨንበላላ፣ ከጊፋታ፣ በመስቀል ስም በሌሎች ባህላዊ አምልኮ ስም] ሰጥታችሁ ከምታመልኩት ጣዖት አምልኮ ባስትመለሱ መጨረሻችሁ ገሃነም እሳት ነው።

“ዳሩ ግን የሚፈሩና የማያምኑ የርኵሳንም የነፍሰ ገዳዮችም የሴሰኛዎችም የአስማተኛዎችም ጣዖትንም የሚያመልኩ የሐሰተኛዎችም ሁሉ ዕድላቸው በዲንና በእሳት በሚቃጠል ባሕር ነው፤ ይኸውም ሁለተኛው ሞት ነው።”
  — ራእይ 21፥8

“የጌታ የኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የእግዚአብሔርም ፍቅር የመንፈስ ቅዱስም ኅብረት ከሁላችሁ ጋር ይሁን። አሜን።”
  — 2ኛ ቆሮ 13፥14

#የእግዚአብሔር_አገልጋይ_ማስረሻ_በላይ
🔵 መልዕክቱን ለሌሎች አድርሱልኝ።


🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤 dan repost
መስቀል ሃይላችን ነው ፣መስቀል መፅናኛችን ነው ፣ መስቀል የነፍሳችን መድሃኒት ነው፣ መስቀል ቤዛችን ነው ።
አይሁድ ይክዱታል እኛ ግን እናምነዋለን ያመነውም እኛ በመስቀሉ እንድናለን ድነንማል።
የተወደዳቹ የቻናላችን ቤተሰቦች
እንኳን ለታላቁ የመስቀል ደመራ በዓል በሰላም አደረሳችሁ አደረሰን!

#ድምፀ_ተዋህዶ

https://t.me/dmtse_tewaedo


🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤 dan repost
መስከረም  ፲፮


በዚች ቀን በኢየሩሳሌም አገር ንግሥት ዕሌኒ የገለጠቻቸው የከበሩ ቦታዎች ሁሉ የተሠሩበትና የከበሩበት ሆነ ።

ቆስጠንጢኖስ ከነገሰ በኋላ እናቱ ቅድስት ዕሌኒ ልጄ ሆይ እኔ ወደ ቅድስት አገር ኢየሩሳሌም በመሔድ የክርስቶስን ዕፀ መስቀል ፈልጌ አወጣ ዘንድ ለእግዚአብሔር ስዕለትን ተስያለሁ አለችው ።

ቆስጠንጢኖስም ሰምቶ ደስ አለው ብዙ ሠራዊትና ገንዘብ ሰጥቶ ላካት። ኢየሩሳሌምም በደረሰች ጊዜ ከከበሩ ቦታዎች ተባረከች ። ከዚህም በኋላ የከበረና አዳኝ  የሆነ የክርስቶስን ዕፀ መስቀል ከብዙ ፍለጋ በኋላ አገኘች እግዚአብሔርንም አመሰገነች።

ከዚህም በኋላ በጎልጎታ፣ በቤተልሔም፣ በጽርሐ ጽዮን፣ በጌቴሴማኔ፣ በደብረ ዘይት እና በከበሩ ቦታዎች ሁሉ በዕንቁ በወርቅና በብር የቤተ መቅደስ መሠዊያዎች እንዲሠሩ አዘዘች።

ጻድቅ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስም በነገሠ በ፴ ዓመቱ የከበሩ ቦታዎች ሕንፃቸው በተፈጸመ ጊዜ ለቁስጥንጥንያ፣ ለአንጾኪያ፣ለእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት ኤጲስቆጶሶቻቸውን በመያዝ ሁሉም በኢየሩሳሌም የታነፁትን አብያተ ክርስቲያናት እንዲያከብሩ አዘዘ። ንጉሡም እንዳዘዘ ሁሉም ተሰበሰቡ የቁርባን ቅዳሴንም ቀድሰው ለምእመናን ሥጋውንና ደሙን አቀበሉ በዚችም ቀን ከቶ እንደርሱ ሆኖ የማያውቅ ታላቅ ደስታ ሆነ።

የቅዱሳን በረከታቸው ይደርብን! አሜን!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር

#ድምፀ_ተዋህዶ
https://t.me/dmtse_tewaedo


🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤 dan repost
# ልዩ የመሰቀል ደመራ ፕሮግራም !!
     ✝️✝️✝️
#የሶዶ_ወረዳ_ቤተክህነት_ልዩ_የደመራ_ዝግጅት
በምሥራቅ ጉራጌ እና ማረቆ ልዩ ወረዳ ሀገረ ስብከት የሶዶ ወረዳ ቤተክህነት አስተባባሪነት በተዘጋጀው የደመራ በዓል የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስና የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ እንዲሁም የሀገረ ስብከቱ የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት ልዩ ፕሮግራም በቡኢ ከተማ በታላቅ ድምቀት ይከበራል።
✝️✝️✝️
እርስዎም የበዓሉ ተሳታፊ እንዲሆኑ እናሳስባለን።
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ!
✝️✝️✝️
የምስራቅ ጉራጌና ማረቆ ልዩ ወረዳ ሀገረ ሰብከት !
መስከረም 11/01/2017 ዓ.ም
             ቡኢ
          ኢትዮጵያ
         ✝️✝️✝️

#ድምፀ_ተዋህዶ

https://t.me/dmtse_tewaedo


🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤 dan repost
ሕይወትን ሊወድ መልካሞችንም ቀኖች ሊያይ የሚፈልግ ሰው፥ምላሱን ከክፉ ከንፈሮቹንም ተንኰልን ከመናገር ይከልክል
፩ኛ ጴጥሮስ ፫÷፲

ይቅርታ አድርጉልኝ !

ትናንት ለበደለን ፡ አምና ላስቀየመን
ቅሬታን አጥፍተን ፡ በደል መቁጠር ትተን
የንስሀን ጊዜ ፡ ጨምሮ ሊሰጠን
ይቅርታ እንድናደርግ፡ ጷጉሜ ተለገሰን ።

ፈንድቆ ለመኖር ፡ እንደ ጨቅላ ህፃን
በሰላም ይፈታ ፡ የቂም ቋጠራችን
ይቅር እንባባል ፡ አንዳችን ለአንዳችን
ለዚህ ነው የተሰጠን ፡ ጷጉሜ ድልድያችን።

እስካሁን ላረኩት ፡ በደል በናንተ ላይ
ይቅርታ አድርጉልኝ ! !

ይቅርታ የሚያደርግ ፡ ነውና አስተዋይ።
ለጥሩም ለመጥፎም ፡ ፍርድ አለ ከሰማይ
ግን እስካለን ድረስ ፡  በጥፉት ምድር ላይ
ለገዛ ጥቅሜ ስል  ፡ ለሰራሁት ጉዳይ
እያወኩኝ ሳላውቅ ፡ እያየሁኝ ሳላይ
ለበደሌ ሁሉ ፡ በሞት ሳንለያይ

ይቅርታ አድርጉልኝ ! !
በአዲሱ አመት ልባችንን ለይቅርታ እናዘጋጂ !

"ወትባርክ አክሊለ ዓመተ ምሕረትከ"
"በቸርነትህ ዓመታትን ታቀዳጃለህ"
                          (መዝ_64:11)

#ድምፀ_ተዋህዶ

https://t.me/dmtse_tewaedo




🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤 dan repost
👉 ያለፈው ዘመን ይበቃናል 👉
    ፩ ጴጥ ም ፬ ቁ ፫
                   4     3

✝ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ✝

🙏 እንኳን ለሊቀ መላዕክት ለቅዱስ ሩፋኤል በዓለ ሢመት አው ለካህኑ መልከጼዴቅ በዓል አደረሳችሁ አደረስን 🙏

👉 ጳጉሜን ፫ (3) በዓለ ሥሉስ ቅዱስ በዓሉ ለቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላዕክት ወመልከጼድቅ ወሰራጵዮን ወዘርያዕቆብ ንጉሥ ኢትዮጵያ 👉

👉 ዘነግህ ምስባክ 👉

መሐለ እግዚአብሔር ወኢይኔስሕ
አንተ ካህኑ ለዓለም በከመ ሢመቱ ለመልከጼድቅ
እግዚአብሔር በየማንከ

✥ ትርጉም ✥

እንደ መልከጼዴቅ ሥርዓት አንተ ዘላለም ካህን ነህ ብሎ
እግዚአብሔር ማለ አይጸጸትም
እግዚአብሔር በቀኝህ
   
   መዝ ፻፱-፬
        109  4

✤ ወንጌል ✤

ሉቃ ም ፲፯ ቁ ፳-፴፩
           17   20  31

✝ የቅዳሴ ምንባባት ✝

ዕብ ም ፯ ቁ ፩-፭
ይሁዳ ም ፩ ቁ ፲፩-፲፯
ግብ.ሐዋ ም ፭ ቁ ፲፯-፳፮

❖ ምስባክ ❖

እግዚአብሔርሰ ገሃደ ይመጽእ
ወአምላክነሂ ኢያረምም
እሳት ይነደድ ቅድሜሁ

🙏 ትርጉም 🙏

እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል
አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም
እሳት በፊቱ ይነዳል
 
    መዝ ፵፱-፪
          49   2

❖ ወንጌል ❖

ማቴ ም ፳፭ ቁ ፴፩-ፍ.ም
            25    31   ፍፃሜው

❖ ቅዳሴ ❖

ያዕቆብ ዘሥሩግ(ተንሥኡ)

" የብርሃናት ፈጣሪ ሆይ ጨለማን የደፋው ጣዖትንም የሻረው በሞቱ ሞት ያጠፋው "
     ቅዳሴ ያዕቆብ ዘሥሩግ
           ም ፩ ቁ ፹፫
                1     83

✝ በዓሉ በዓለ ምህረት በዓለ ድኀነት ያድርግልን ቸሩ መድኃኔዓለም በቸርነቱ ይማረን እመ አምላክ እግዝእትነ ማርያም በምልጇዋ ትጠብቅን ከሊቀ መላዕክት ቅዱስ ሩፋኤል በረድኤቱ ይጠብቅን ካህኑ መልከጼዴቅ በረከቱ ይደርብን ድርሳነ ሩፋኤል ገድለ ቅዱሳን ዕጣነ አሮን መስዋዕት መልከጼዴቅ የተቀበለች የኛም ፆም ፀሎት ጥምቀት ምሕላ በቸርነቱ በብሩህ ገጽ ይቀበልልን ለበዓለ ዓውደ ዓመት በሰላም ያድርሰን ✝

                  ✧ ምስባክ ✧

#ድምፀ_ተዋህዶ

           YouTube chnnl
👇🏽🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘 🔻👇🏽
        
የይቱብ ቻናላችን
             🔔
  🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘🔺‌‌


❤️በናታኒም ቲዩብ❤️
         👇🏽👇🏽
https://youtu.be/MsXeCVCPxX
4
https://youtu.be/MsXeCVCPxX4
htt
ps://youtu.be/MsXeCVCPxX4


🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤 dan repost
➣ አፉየ አስተንፈሰ ወልሳንየ አልኆሰሰ ለክብረ ፍልሰትኪ ድንግል ሶበ አቈርብ ተውዳሰ ማርያም ዘኮንኪ ቅድስተ ቅዱሳን መቅደስ በቅድሜኪ እግዝእትየ እመ ረከብኩ ሞገስ በየማንኪ ባርክኒ ሥልስ ➣

አንደበቴ ተናገረ አፌም ዘመረ ለዕረገትሽ ክብር ዝማሬን በአቀረብኩ ጊዜ ቅድስተ ቅዱሳን መቅደስ የሆንሽ እመቤቴ ማርያም ኾይ በፊትሽስ ባለሟልነትን ባገኝ  በቀኝ እጅሽ ሶስት ጊዜ ባርኪኝ

  መልክአ ፍልሰታ ዘደረሰ አፄ ዘርዓያዕቆብ

ለቅዱሳን የተለመነች ለኛም ትለመነን ቸሪቱ ድንግል ማርያም

               #ድምፀ_ተዋህዶ

YouTube chnnl
👇🏽🔻 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘 🔻👇🏽
         የይቱብ ቻናላችን
             🔔
  🔺 𝒔𝒖𝒃𝒔𝒄𝒓𝒊𝒃𝒆 𝒏𝒐𝒘🔺‌‌


❤️በናታኒም ቲዩብ❤️
         👇🏽👇🏽
https://youtu.be/MsXeCVCPxX4
https://youtu.be/MsXeCVCPxX4
https://youtu.be/MsXeCVCPxX4


🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤 dan repost
Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish


🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤 dan repost
🔴አዲስ አበባ
ይህንን ቤተክርስቲያን ለኮሪደር ልማት በሚል ምክንያት እንደ ሱቅ መንገድ ላይ ቤተመቅደሱን ብቻ ባዶውን ሊያስቀሩት ነው።
በማንኛውም ማሕበራዊ ሚዲያ ድምፅ ሆነን ከመፍረስ እናድነው።
➟ከኪነ-ጥበብ


🎤🌼ድምፀ ተዋህዶ🌼🎤 dan repost
† "በጽዮን መለከትን ንፉ:: ጾምንም ቀድሱ:: ጉባዔውንም አውጁ:: ሕዝቡንም አከማቹ:: ማሕበሩንም ቀድሱ:: ሽማግሌዎችንም ሰብስቡ:: ሕጻናቱንና ጡት የሚጠቡትን አከማቹ:: ሙሽራው ከእልፍኙ: ሙሽራይቱም ከጫጉላዋ ይውጡ::"

         †(ኢዩ. 2:15)

† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †

#አቤቱ ህዝብህን አድን ርስትህንም ባርክ ጌታ ሆይ ማራቸው
ከፍ  ከፍ አድርጋቸው/2/

#ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!

#ድምፀ_ተዋህዶ

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.