ምስለ አድባራት ወገዳማት


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን" "ስለ ቅዱሳን እንድናገር ፍቅር ያስገድደኛል" ሊቁ ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri




አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አሜን
መጋቢት 2-የኒቅዮስ ኤጲስቆጶስ አባ መከራዊ በሰማዕትነት ዐረፉ፡፡
+ ከሮሀ አገር የተገኘውና የተሠወረውን ሁሉ የሚያይ የጻድቃንን ማደሪያና የኃጥአንንም ኩኔን በገሃድ የተመለከተ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዕረፍቱ ነው፡፡

ሰማዕቱ አባ መከራዊ፡- ይኽም ቅዱስ ከደቡባዊ ግብጽ ከእስሙናይን የተገኘ ነው፡፡ የኒቅዮስ አገር ኤጲስቆጶስ ሆኖ በተሾመ ጊዜ በክርስቲያኖች ላይ ታለቅ ስደትና መከራ ሆነ፡፡ አረማዊ መኮንን ወደዚያች አገር ገብቶ ብዙዎቸን በሰማዕትነት ገደለ፡፡ አባ መከራዊንም ጭፍሮቹን ልኮ ካስመጣቸው በኋላ እምነቱን እንዲክድ አስገደደው፡፡ አባ መከራዊ ግን በእምነቱ ስለጸና በጽኑ ግርፋት አስገረፈው፡፡ ዳግመኛም ብርና እርሳሰ አቅልጠው በአፉ ውስጥ እንዲጨምሩበት አዘዘ፡፡ እንደታዘዘውም ባደረጉ ጊዜ ጌታችን አባ መከራዊን አጸናውና ምንም ጉዳት እንዳላገኘው ሆነ፡፡ 

ከዚህም በኋላ ይህ ከሃዲ መኮንን አባ መከራዊን ወደ እስክንድርያው ገዥ ወደ ኄርሜኔዎስ ላከው፡፡ እርሱም አሠረው፡፡ አባ መከራዊም በእሥር ላይ እንዳለ ብዙ ተአምራትን አደረገ፡፡ የአቅፋስ ከተማ ሹም የሆነውን ልጅ እጅና እግሩ ሽባ ነበርና አባ መከራዊ በጸሎቱ ፈወሰው፡፡ እስክንድርያው ገዥ ወደ ኄርሜኔዎስም ይህንን ሲሰማ በአባ መከራዊ ላይ ሥቃይ አበዛበት፡፡ ሕዋሳቶቹ ሁሉ እስኪቆራረጡ ድረስ በመንኮራኩር ውስጥ ጨምሮ አሠቃየው፡፡ ዳግመኛም ለተራቡ አንበሶች ሰጡት፣ በባሕር ውስጥ አሰጠሙት፣ በእሳት ምድጃ ወስጥ ጨመሩት ነገር ግን በእነዚህ መከራዎች ሁሉ ጌታችን ፈጽሞ ያድነው ነበር፡፡

በመጨረሻም መኮንኑ ማሠቃየት በሰለቸው ጊዜ አንገቱን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ፡፡ አባ መከራዊም በዛሬዋ ዕለት አንገታቸውን ተሰይፈው ሰማዕትነታቸው በድል ፈጸሙ፡፡ ቅዱስ ሥጋቸውንም በመርከብ አድርገው ወደ አገራቸው ሲወስዱ እግዚአብሔር ያርፍ ዘንድ የወደደበት አገር ላይ ሲደርስ መርከቧ አልንቀሳቀስ አለች፡፡ ከአባ መከራዊም ሥጋ ‹‹ሥጋዬ በውስጡ እንዲኖር እግዚአብሔር የፈቀደው ቦታ ይህ ነው›› የሚል ቃል ወጣ፡፡ ይህንንም ለዚያች አገር ሰዎች በነገሯቸው ጊዜ በዝማሬ በእልልታ ቅዱስ ሥጋቸውን ተቀብለው ወስደው በመልካም ቦታ አስቀመጡት፡፡ የአባ መከራዊ መላ ዘመናቸው 131 ዓመት ነው፡፡ 

ረድኤት በረከታቸው ይደርብን፣ በጸሎታቸው ይማረን!!!    
+ + +     

አቡነ ጎርጎርዮስ ረዓዬ ኅቡዓት፡- ይኽም ቅዱስ በሌላኛው ስሙ ጎርጎርዮስ ዘሀገረ ሮሐ እየተባለ ይጠራል፡፡ ረዓዬ ኅቡዓት ማለት ምስጢራትን የተመለከተ ማለት ነው፡፡ ይህም ጻድቅና ሊቅ በቅዳሴው፣ በሃይማኖተ አበው፣ በስንክሳር፣ በገድለ ሰማዕታትና በገድለ ቅዱሳን ስሙ ተደጋግሞ ተጠቅሷል፡፡ በመጀመሪያ የክርስቲያኖች ጠላት የነበረ ሲሆን ዐመጸኛና ኃጥእ ነበረ፡፡

ክርስቲያኖችንም እየፈለገ ያሠቃይና ይገድል ነበር፡፡ አንድ ቀን ድንገት ሳያስበው መልአክ መጥቶ ነጥቆ ወስዶ የኃጥአንንም የመከራ ቦታዎችንና ሲኦልን አሳይቶ መልሶ አምጥቶ መሬት ላይ ሲጥለው እጅግ ደንግጦ በፍጹም ንስሓ ተመልሶ ሐዲሳትንና ብሉያትን ጠንቅቆ በመማር በብዙ ተጋድሎ መኖር ጀመረ፡፡ 
በሌላ ጊዜ አሁንም መልአኩ በረድኤት ተገልጦለት ነጥቆ ወስዶ ገነትን፣ ብሔረ ሕያዋንን፣ ብሔረ ብዑዓንን፣ መንግሥተ ሰማያን ሁሉ አሳየው፡፡ ከዚህም በኋላ ከአመፁ ወደ እግዚአብሔር በንስሓ ተመልሶ መነኮሰ፡፡ በምንኩስናም ሆኖ በብዙ ተጋድሎ ኖረ፡፡ ከዚህም በኋላ የተሰወረውን ሁሉ የሚያይ ቅዱስ አባት ሆነ፡፡ በሊቀ ጳጳስነት ተሾሞ በማገልገል ብዙ ጣዖታትን አፈራርሶ አብያተ ክርስቲያናትን ሠራ፡፡ በመጨረሻም ሹመቱን በመተው በዓቱን አጽንቶ ብዙ ከተጋደለ በኋላ መጋቢት 2 ቀን በክብር ዐርፏል፡፡

የአቡነ ጎርጎርዮስ ረድኤት በረከቱ ይደርብን፣ በጸሎቱ ይማረን!!!


ጠያቂው ተጠየቅ እንጂ…!

"…ክርስቶስ ማነው…? በሚል 303 ጥያቄዎች አሉኝ ብሎ እሱ በማያምንበት ለእኔ ግን ጌታዬ አምላኬና መድኃኒቴ በሆነው በኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ጥያቄ አቅርቧል። በመጽሐፍ መልክም አሳትሟል። መልካም መብቱ ነው። አሕመዲን ጀበል በጌታ ላይ ተሳልቋል፣ በምስጢረ ሥላሴ ላይ አሹፏል፣ ቀልዷል ብለን ሰልፍ አልወጣንም። ይገደልም አላልንም።

"…አሕመዲን ጀበል በኢየሱስ ክርስቶስ ስለማያምን የፈለገውን የመጻፍ መብት አለው ከተባለ እፎይም ሆነ እኔ ስለማላምንበት ስለ መሀመድ ብጽፍ ለምን ትናደዳለህ? አንተ የእኔን በመናቅህ ዝም እንዳልኩህ እኔም የአንተን ስንቅ ዝም ማለት ነው እኮ ያለብህ። አንተ የእኔን ድንበር አልፈህ ለማዋረድ ስትሞክር እኔ በድንበሬ ላይ ቆሜ የአንተን ባዋርድ ለምንድነው ጎረቤት ሁላ እስኪረበሽ የምትንጫጫው። አንተ "ለነቢይህ" ፍቅር፣ አክብሮት፣ ውዴታ አለኝ ካልክ እኔ ለአምላኬና ለመድኃኒቴ ለኢየሱስ ክርስቶስ ምንም ዓይነት ፍቅር፣ መስዋዕትነት የማልከፍል ይመስልሃል?

"…ንጽጽር ብለህ ያለ አቅምህ መጽሐፍ ቅዱስ ትንተና የጀመርከው አንተው ራስህ ነህ። አንተ የማታውቀውን መጽሐፍ ቅዱስ ገልጠህ ስትዳክር ዝም ብለን ቆይተን፣ መልስም ከዚያው ከመጽሐፍ ቅዱስ ስንሰጥህ ከርመን፣ አይ ቆይ እስኪ ለምን ደግሞ ከቁርዓኑና ከሐዲሱ መልስ አንጠይቃቸውም ብለን ስንነሣ ቆንጨራ ይዞ መፎከር ምን የሚሉት ነው? ወይ አስቀድሞ አለመፎከር፣ አቅምን ዐውቆ መኖርም ጥሩ ነው። ግጠመኝ ካልክ በኋላ አንተ በእኔ መጽሐፍ ቅዱስ ልትሞግተኝ ስትመጣ፣ እኔ ደግሞ በአንተው ቁርዓን ልሞግትህ ስነሣ የምን መነጫነጭ ነው?

"…በመስታወት ቤት የሚኖር ሰው የድንጋይ ውርወራ ጠብ ውስጥ ፈጽሞ አይገባም። ባለጊዜ ነን ተብሎ እንደ ሕጻን በልቅሶ፣ በጩኸት ፍላጎትን ለማሳካት መሯሯጥ ያስገምታል።

• እፎይ…!




ስግር፣ ስበላ፣ ስጠጣ፣ ስቀማ፣ ስሰርቅ ነበርሁ እንጂ፣ ሃይማኖት አልተማርሁ፣ ምግባር አልሠራሁ፣ ሰንበትን አላከበርሁ›› ብላ ትመልስለታለች፡፡ ከዚህም በኋላ መላእክተ ብርሃንን ጠርቶ ‹‹ይህቺ ነፍስ አሕዛብ (ያላመነች ያልተጠመቀች) ናትና ኩነኔ እንጂ መንግሥተ ሰማያት አይገባትም፤ ከሥጋዋ ጋር አዋሕጄ ፍጹም ገሃነመ እሳት እስካገባት ድረስ 4 ቀን መንግሥተ ሰማያትን፣ 3 ቀን ገሃነመ እሳትን አዙራችሁ አሳይታችሁ ከኃጥአን ጋራ በሲኦል በርባሮስ አኑሯት›› ይላቸዋል፡፡ መላእክተ ብርሃንም ይዘዋት ወጥተው 4 ቀን መንግሥተ ሰማያትን የባለ ሕጎችን፣ የደናግሎችን ሀገር፣ የመነኮሳቱን ሀገር፣ ማርና ወተት የምታፈስ የተባለችውን አዙረው አሳይው ሽታዋን ጣዕሟን በልቧ አስርፀው፣ አቅምሰው ‹‹አንቺ ነፍስ ሃይማኖት ብትማሪ፣ ምግባር ብትሠሪ ቦታሽ ይህ ነበር…›› ብለው ይዘዋት ወርደው ገሃነመ እሳትን 3 ቀን የእሳቱን ሰንሰለት፣ የእሳቱን አክሊል፣ የእሳቱን ጨለማ፣ የእሳቱን ቁርበት፣ የእሳቱን ዘንዶ፣ የእሳቱን ዝናር፣ የእሳቱን ጫማ፣ ክርፋቱን ግማቱን፣ አዙረው አሳይተው ‹‹አንቺ ነፍስ በእንዲህ ያለ ቦታ ትሉ ከማያንቀላፋ፣ እሳቱ ከማይጠፋ ለዘላለም በዚህ ያኖርሻል›› ብለው ወደ በርባሮስ ይዘዋት ይሔዳሉ፡፡ ከዚህም በኋላ ከሰኦል ደጅ አድርሰው ለአጋንንት ያስረክቧታል፡፡ አጋንንትም ከጨለማው አግብተው በእሳት ጦር እየወጉ፣ በእሳት አለንጋ እየገረፉ፣ በእሳት መንዶ እየቀጠቀጡ ይወስዷታል፡፡ እርሷም መከራው ሲጸናባት ‹‹ወየው! ወየው!…የእግዝእትነ ማርያም ያለህ!›› ትላለች፡፡ ትማፀናለች፡፡ እመቤታችንም ለሁሉ አማላጅ ናትና መጥታ ‹‹ልጄ ወዳጄ ሆይ! ማርልኝ›› ትለዋለች፡፡ ጌታም ‹‹ይህች ነፍስ እኔንም አንቺንም የበደለች ከሃዲ ናትና አልራራላትም›› ይላታል፡፡ እመቤታችንም ‹‹ምሕረት ልማድህ ነውና ማርልኝ›› ብላ ትሰግዳለች፡፡ ጌታም ‹‹ስለ እናቴ ጥቂት አሳርፏት›› ይላቸዋል፡፡
ዛሬ በዚህ ዓለም አንድ ሰው በቆላ ሲሔድ ከላይ ፀሐዩ፣ ከታች ረመጫቱ (የመሬቱ ግለት) ሲፈጀው ላብ ላብ ሲለው ጥቂት ጥላ ያገኘ እንደሆነ እርፍ ብሎ እንደሚነሣ ሁሉ አጋንንትም ያችን ነፍስ ጥቂት አሳርፈው እንደገና መከራዋን ሲያሳዩአት ይኖራሉ፡፡ እርሷም ከመንግሥተ ሰማያት መውጧን ገሃነመ እሳት መውረዷን እያሰበች ፀፀት እንደ እሳት ሲፈጃት ሲያቃጥላት እስከ ዕለተ ምጽዓት ድረስ በሲኦል ትቀመጣለች፡፡ የኃጥእ ሰው ነፍስ ሥቃይዋ ይህን የመሰለ ነው፡፡ እግዚአብሔር ከዚህ መከራ ሁላችንንም ያድነን! አሜን!!!
ማጠቃለያ፡- በዓለም ላይ ያለ ማንም ኃጥእ ሰው ንጉሥ ይሁን ሎሌ፣ የተማረ ምሑር ይሁን ያልተማረ ጨዋ፣ ሀብታም ይሁን ድሀ ማንኛውም ሰው በእውነተኛዋ ሃይማኖት ያላመነ ምግባር የሌለው ከሆነ በስተመጨረሻ በሞት አፋፍ ላይ ሳለ እጅግ እፈሪውን መልአከ ሞትን በገሃድ በተመለከተ ጊዜ እንደንጉሥ አጋግ ‹‹ከመዝኑ ሞት መሪር-በውኑ ሞት እንደዚህ መራራ ነውን?›› ማለቱ አይቀርም፡፡ ሃይማኖት ላልተማሩ ምግባር ላልሠሩ ለኃጥአንና ለክፉዎች ሞት እጅጉን መራራ ነው፡፡ ይልቁንም ሁለተኛው ሞት በገሃነም ያለው ነው፡፡ በእግዚአብሔር ዳኝነት ወደ እሳት ባሕር ይጣላሉ፣ ሥቃያቸውም አያልቅም፡፡ ራእ 14፡11፣ 20፡13፡፡ ጌታችንም በቅዱስ ቃሉ ‹‹ትሉ ወደማያንቀላፋበት እሳቱ ወደማይጠፋበት›› የሚገቡ እንዳሉ አስተምሯል፡፡ ማር 9፡44-48፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም ‹‹እግዚአብሔርን የማያውቁትን፣ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስንም ወንጌል የማይሰሙትን ይበቀላቸዋል፤ ከጌታችን ፊት ከኃይሉም ክብር ርቀው በዘለዓለም ጥፋት ፍዳቸውን ያገኛሉ›› ብሏል፡፡ 1ኛ ተሰ 1፡9፡፡ ከነቢያትም ነቢዩ ኤርምያስ ‹‹እግዚአብሔር ግን እንደ ኃያል ተዋጊ ከእኔ ጋር ነው፣ ስለዚህ አሳዶቼ ይሰናከላሉ፣ ለዘለዓለምም የማይረሳ ጉስቍልናቸውን አላወቁምና ፈጽመው አፈሩ›› በማለት ተናግሯል፡፡ ኤር 20፡11፡፡ ነቢዩ ዳንኤልም ‹‹በምድርም ትቢያ ውስጥ ከአንቀላፉት ብዙዎች እኵሌቶቹ ለዘለዓለም ሕይወት፣ እኵሌቶቹም ለእፍረትና ለዘለዓለም ጉስቍልና ይነሣሉ›› ብሏል፡፡ ዳን 12፡2፡፡
እንግዲህ የነፍስና የሥጋ መለያየት እንደ አጋግ የመረረን ወይም የሚመርረን ሰዎች ሁለተኛው ሞት ሲመጣ ‹‹እንዴት ልንሆን ነው?›› ማለት ይገባል፡፡ ከዚህም ተነሥተን የመጀመሪያውንም የሁለተኛውንም ሞት መራራ የሚያደርገው ሃይማኖትን ከምግባር አስተባብረን አለመያዛችንና ክፋታችን መሆኑን አውቀን ሃይማኖት ተምረን ምግባር ሠርተን ከክፋት ወደ በጎነት መመለስ ይኖርብናል፡፡ ያን ጊዜ ሞታችን እንቅልፍ ወይም እረፍት ይሆንልናል፡፡ 1ኛ ነገ 2፡10፣ ሐዋ 7፡60፣ ራእ 14፡13፡፡
በክርስቶስ ሞት የተሻረ ሞት በእኛ በእውነተኞቹ በክርስቶስ ተከታዮቹ ላይ ሥልጣን አይኖረውም፡፡ 1ኛ ቆሮ 15፡53-57፣ 2ኛጢሞ 1፡10፣ ዕብ 2፡9፣ 14፡15፣ ራእ 18፡፡ ሞት ከክርስቶስ ጋር ለዘለዓለም የሚያኖረን መንገድ ይሆንልናል፡፡ ኢሳ 35፡10፣ 45፡17፣ ዳን 7፡14፣ 12፡2፣ ሉቃ 23፡43፣ ዮሐ 5፡24፣ 1ኛ ተሰ 4፡13፡፡ እንደ ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹እኔስ ከዚህ ዓለም ልለይ በክርስቶስም ዘንድ ልኖር እወዳለሁ፤ ይልቁንም ለእኔ ይህ ይሻለኛል፣ ይበልጥብኛልም›› እንላለን፡፡ ፊል 1፡23፡፡ እንደ ቅዱስ ጴጥሮስም ‹‹እግዚአብሔር የሚመጣበትን፣ ሰማያትም ቀልጠው የሚጠፉበትን፣ ፍጥረትም ሁሉ ተቃጥሎ የሚጠፋባትን ዕለት በተስፋ እየጠበቃችሁ ፍጠኑ፤ እኛ ግን ጽድቅ የሚኖርባቸውን አዲሶቹን ሰማያትና አዲሲቱን ምድር ተስፋ እናደርጋለን›› እያልን በተስፋ መንግሥተ ሰማያት እንኖራለን፡፡ 2ኛ ጴጥ 3፡12፡፡ እንደ ቅዱስ ዮሐንስ ‹‹ዓለሙንና በዓለም ያለውን አትውደዱ፤ ዓለሙን የሚወድ ግን የአብ ፍቅር በእርሱ የለም፡፡ በዓለም ያለው ሁሉ እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት፣ ስለ ገንዘብም መመካት ከዓለም እንጂ ከአብ አይደለም፡፡ ዓለሙ ያልፋል፣ ምኞቱም ያልፈል፣ የእግዚአብሔርን ፈቃድ የሚያደርግ ሰው ግን ለዘለዓለም ይኖራል›› በማለት በሕይወት እንተረጉመዋለን፡፡ 1ኛ ዮሐ 2፡15-17፡፡
የእግዚአብሔር ቸርነት የድንግል ማርያም አማላጅነት አይለየን! አሜን!!!


ወጥታ በአስክሬኑ ላይ ትቀመጣለች፡፡ በዚህ ጊዜ መልአከ ሞት በጥፍሩ ወግቶ ቆንጥሮ በጥርሱ ቆርጥሞ አላምጦ 3 ጊዜ ይተፋታል፡፡ 3 ጊዜ መትፋቱ ስለምን ነው? ቢሉ ‹‹አንቺ ነፍስ በአርአያ ሥላሴ የተፈጠርሽው የሥላሴን አንድነት ሦስትነት አውቀሽ፣ ሃይማኖት ተምረሽ፣ ምግባር ሠርተሽ፣ ሰንበት አክብረሽ፣ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን በንጽሕና ተቀብለሽ፣ በሕግ በሥርዓት ሆነሽ ልትኖሪ ነበር፡፡ ይህን አላወቅሽም፣ አላደረግሽም ዐመፀኛ ነሽ…›› ሲል 3 ጊዜ እየቆረጣጠመ ይተፋታል፡፡ ‹‹ከመዝኑ ሞት መሪር-በውኑ ሞት እንደዚህ መራራ ነውን?›› እንዳለ ንጉሥ አጋግ፡፡ 1ኛ ሳሙ 15፡32፡፡
ዳግመኛም እኩሉ አጋንንት በሰማይ እኩሉ በምድር ሆነው 13 ጊዜ ወደ ሰማይ፣ 13 ጊዜ ደግሞ ወደ ምድር እያንቀረቀቡ ከምድር ላይ ያፈርጧታል፡፡ ስለምን 13 ጊዜ ወደ ሰማይ እያጓኑ ይጫወቱባታል? ቢሉ ‹‹አንቺ ነፍስ ጌታሽ አምላክሽ በዕለተ ዐርብ 13ቱን ሕማማተ መስቀል የተቀበለልሽ ለአንቺ መድኃኒት፣ ለአርአያ፣ ለቤዛ ነበር፡፡ አንቺ ግን ይህን አውቀሽ ሃይማኖት ተምረሽ፣ ምግባር ሠርተሽ፣ ሰንበትን አክብረሽ አልኖርሽም፤ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን በንጽሕና አልተቀበልሽም፤ ሕጉን ትእዛዙን አልጠበቅሽም፤ ዐመፀኛ ነሽ›› ብለው ስለዚህ 13 ጊዜ ወደ ሰማይ እያጓኑ፣ ከምድር ላይ እያፈረጡ ይጫወቱባታል፡፡ ዳግመኛም የፊጥኝ የግርግሪት የኋሊት አሥረው፣ በእሳት ልጓም ለጉመው፣ በእሳት ሰንሰለት አሥረው፣ አንቀው ይዘው በእሳት በሎታ ራስ ራሷን እየቀጠቀጡ ያስለፈልፏታል፤ ያስጨንቋታል፡፡ እርሷም በዚህ ታላቅ ጭንቅና መከራ ውስጥ ሆና ‹‹…ወዮ የሥላሴ ያለህ!›› ትላለች፤ ታማፅናለች፡፡ መላእክተ ጽልመትም ‹‹ከእኛ ዘንድ ስትመጪ ነው ሥላሴን የምታውቂያቸው? ከዚያ ሳለሽ ስለሥላሴ ብለሽ ሃይማኖት በተማርሽ፣ ምግባር በሠራሽ፣ ሰንበትን ባከበርሽ፣ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን በንጽሕና በተቀበልሽ፣ በሕግ በሥርዓት ሆነሽ በኖርሽ ነበር እንጂ…›› እያሉ ‹‹..በሏት ጨርሷት ቀጥቅጧት›› እየተባባሉ ያሠቃዩአታል፡፡ ዳግመኛም ‹‹…ወዮ ወዮ የመድኃኔዓለም ያለህ!›› እያለች ታማፅናለች፡፡ መላእክተ ጽልመትም ‹‹ከእኛ ዘንድ ስትመጪ ነው መድኃኔዓለምን የምታውቂው? ከዚያ ሳለሽ ስለመድኃኔዓለም ብለሽ ሃይማኖት በተማርሽ፣ ምግባር በሠራሽ፣ የታረዘ ባለበስሽ፣ በመጸውትሽ፣ ቤተ ክርስቲያን ስመሽ በኖርሽ፣ ሰንበትን ባከበርሽ፣ ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን በንጽሕና በተቀበልሽ፣ በሕግ በሥርዓት ሆነሽ በኖርሽ ነበር፡፡ መድኃኔዓለምማ በመስቀል ተሰቅሎ፣ ሥጋውን ቆርሶ ደሙነ አፍስሶ የሰጠሸ ለአንቺ መድኃኒት አልነበረምን? ቅዱስ ሥጋውን ክቡር ደሙን በንጽሕና አልቀበልም ብለሽ፣ ሰንበትን አላከብርም ብለሽ፣ ዐርብና ረቡዕን አልጾምም ብለሽ፣ ንስሓ አልገባም ብለሽ ነው እንጂ፡፡ ደግሞ በምድር ላይ ሳለሽ ነው እንጂ መጠንቀቅ…›› እያሉ ‹‹..በሏት ጨርሷት ቀጥቅጧት›› እየተባባሉ ስቃዩአን ያበዙታል፡፡
ያቺ ጉስቋላ ነፍስ ዳግመኛም ‹‹…ወዮ ወዮ የእግዝእትነ ማርያም ያለህ!›› እያለች ታማፅናለች፡፡ መላእክተ ጽልመትም ‹‹ከእኛ ዘንድ ስትመጪ ነው እግዝእትነ ማርያምን ያወቅሻት? ከዚያው ሳለሽ ነበር እንጂ ዝክሯን ማዘከር፣ በዓሏን ማክበር፣ ለተራበ ማብላት፣ ሕጉን ትእዛዙን አጽንቶ መኖር…›› እያሉ ‹‹..በሏት ጨምሩላት›› እየተባባሉ ስቃዩአን ያበዙታል፡፡ ከዚኽም በኋላ የፊተኞቹ እየጎተቱ የኋለኞቹ እያስጨነቁ ይዘዋት ይሔዳሉ፡፡
ከዚኽም በኋላ መላእክተ ብርሃን የጌታን ቃል ሳይሰሙ አይለቋትምና ራስ ራሷን እያዩ ይከታተሏታል፤ እንዲህ ሲከታተሉ ከባሕረ እሳት ይደርሳሉ፡፡ ከዚያም መላእክተ ጽልመት 3 ጊዜ ራሷን ቀጥቅጠው ባሕረ እሳቱን ‹‹ሂጂ ግቢ ተሻገሪው›› ይሏታል፡፡ እርሷም ‹‹ምን ጨብጬ፣ በምንስ ላይ ቆሜ ልሻገረው? ቀኙ እሳት፣ ግራው ውኃ፣ ውስጡ ገደል ነው፣ መንገዱም እንደጭራ የቀጠነ ነውና ምን ረግጬ በምን ላይ ቆሜ ልሻገረው?›› ትላለች፡፡ መላእክተ ጽልመትም ‹‹ለዚህማ መሻገሪያው ታንኳው ለተራበ ማብላት፣ ለተጠማ ማጠጣት፣ ለተቸገረ መርዳት፣ ሰንበትን ማክበር፣ አሥራት በኩራት ማውጣት፣ አንድ በዓል መዘከር፣ ጾም፣ ጸሎት፣ ትሕትና፣ ፍቅር፣ ትዕግሥት፣ ቁጡ አለመሆን፣ ቂም አለመያዝ ነበር፡፡ ዛሬ ከዚህ ደርሰሽ ‹ምን ጨብጬ በምን ላይ ቆሜ ብትይ› ይሆናልን?›› ይሏታል፡፡ እርሷም መልሳ ‹‹ይህስ እንዳለ ባውቅ ኖሮ ስንኳን ሃይማኖት መማር፣ ሰንበትን ማክበር፣ ሀብትን መስጠት ይቅርና እጄን እግሬን ቆርጬ በሰጠሁ ነበር! ብሰማም ዋዛ ፈዛዛ ይመስለኝ ነበር እንጂ›› ትላቸዋለች፡፡ መላእክተ ጽልመትም ‹‹ከእንግዲህ ወዲህ ተመልሰሽ ትሔጃለሽን? ሂጂ ግቢ አሁን ላይ ፀፀት አይረባሽም›› ብለው እነዚያ ክፉውን ሁሉ ሲያስተምሯት የነበሩት ወርውረው ከባሕረ እሳቱ ውስጥ ይጨምሯታል፡፡ እርሷም ከእሳቱ ወጥታ ከባሕሩ፣ ከባሕሩ ወጥታ ከእሳቱ…እያለች አርራ ከስላ ከእሳት እንደገባ ጅማት ተኮማትራ ትሻገራለች፡፡
ዳግመኛም ወዲያ ማዶ ያሉት ‹‹አንቺ ክፉ ምን ያባክንሻል? መንገዱ ይህ አይደለምን!? ፀጥ ብለሽ በመንገዱ አትሻገሪምን!?›› ብለው እየዘበቱባት መልሰው ከባሕረ እሳቱ ውስጥ ይደፏታል፡፡ እርሷም ከእሳቱ ወጥታ ከባሕሩ እያለች አርራ ከስላ እንደቁራ ጠቁራ ትሻገራለች፡፡
ሦስተኛም ወዲህ ማዶ ያሉት ‹‹አንቺ ክፉ ምን ያባክንሻል? መንገዱ ይህ አይደለምን!? ፀጥ ብለሽ በመንገዱ አትሻገሪም!?›› ብለው እየዘበቱባት ወርውረው ይደፏታል፡፡ እርሷም ከእሳቱ ገብታ ከባሕሩ እያለች አርራ ከስላ ትሻገረዋለች፡፡ ዳግመኛም ‹‹ይህንን ሁሉ ሲነግሩኝ ሐሰት ይመስለኝ ነበር›› ብላ እየተጨነቀች ትሻገረዋለች፡፡ ከዚህም በኋላ መከራዋን ስትፈጅ መላእክተ ብርሃን ተቀብለው ይዘዋት ይሔዳሉ፡፡ እርሷም ‹‹ወየው! ከጌታዬ ስደርስ እንዴት እሆን ይሆን…!?›› እያለች ትሔዳለች፡፡ ትሔድም ዛሬ በዚህ ዓለም ያለ ሰው ከንጉሥ አምፆ ተጣልቶ፣ ነፍስ ገድሎ፣ ተይዞ ሊገረፍ፣ ሊቆረጥ፣ ሊፈለጥ፣ ሊሞት እየተጨነቀ እያለቀሰ እንዲሔድ ያችም ጎስቋላ ነፍስ እንደዚያ እየተጨነቀች ትሔዳለች፡፡ ዳግመኛም በዚህ ዓለም ያለ ንጉሥ የሚፈልጥ የሚቆርጥ ሆኖ አስፍቶ ተቆጥቶ እንዲቆይ ሁሉ ፈጣሪዋም ተቆጥቶ ተገርሞ ይቆያታል፡፡ እርሷም በምድር ሳለች ያልተማረች ናትና ደርሳ ሰንግጣ ፈዛ ትቆማለች፡፡ ከዚህም በኋላ መልእክተ ብርሃን ‹‹አንቺ ክፉ፣ ኩሩ፣ ትዕቢተኛ፣ የወትሮው ኩራት አለ መስሎሻል? ፈጣሪሽኮ ነው! ስገጂ እንጂ!...›› ብለው ይገፏታል፡፡ እርሷም ሰግዳ ትቆማለች፡፡ ዕዝ 6፡9፡፡ ከዚህም በኋላ ጌታ ይጠይቃታል፡፡ ምን ብሎ ይጠይቃታል? ቢሉ የወንድ ነፍስ እንደሆነች ‹‹አንቺ ነፍስ እንጨት መቁረጥ፣ መፍለጥ፣ ቤት መሥራት፣ ፈረስ መጋለብ ውኃ ዋና፣ ሰንጠረዥ፣ እርሻ፣ ቁፋሮ፣ በገና፣ ጸናጽል፣ ከበሮ፣ ጽሕፈት፣ ድጉሰት ታውቂያለሽን?›› ብሎ አይጠይቃትም፡፡ የሴትም ነፍስ ብትሆን ‹‹አንቺ ነፍስ አልሞ መደቆስ፣ አለስልሶ መፍተል፣ መፍጨት፣ ወጥ መሥራት፣ እንጀራ መጋገር፣ ጠጅና ጠላ መጥመቅ ታውቂያለሽን?›› ብሎ አይጠይቃትም፡፡ እንግዲያስ ምን ብሎ ይጠይቃታል? ቢሉ ‹‹አንቺ ነፍስ በማን ታመልኪያለሽ? አንድነቴን ሦስትነቴን፣ ምልዐት ስፋቴን፣ ርቀቴን፣ ከሰማየ ሰማያት መውረዴን፣ ከድንግል ማርያም መወለዴን፣ ወልደ አብ በመለኮት፣ ወልደ ማርያም በትስብእት በተዋሕዶ የከበርኩ መሆኔን፣ መገፈፍ መገረፌን፣ መሰቀል መሞቴን፣ መነሣት ማረጌን ታውቂያለችን? ብሎ ይጠይቃታል፡፡ እርሷም ያልተማረች ናትና ‹‹አምላኬ ሆይ! አላውቅም›› ትላለች፡፡ ‹‹ለሥጋዬ ስጥር


ክርስቲያን አልሄድሁ፣ ሃይማኖት አልተማርሁ፣ ምግባርም አልሠራሁ፣ ሰንበትንም አላከበርሁ፣ የተራበ አላበላሁ፣ ለሥጋዬ ስጥር ስግር ስላፋ ስማስን ነበርሁ እንጂ፡፡ እንደ እናንተ ያለም መኖሩን አይቼ ሰምቼም አላውቅም›› ትላቸዋለች፡፡ ከዚህ በኋላ መላእክተ ብርሃን ‹‹ወይ ነፍስ! እንዴት ለደገኛው መንግሥተ ሰማያት ተፈጥረሽ ለገሃነመ እሳት ሆንሽ? በሥላሴ አምሳል ተፈጥረሽ የዲያብሎስ መረገጫ የሰይጣናት መራወጫ ሆንሽ!?›› ብለው አዝነው አልቅሰው ይሔዳሉ፡፡
(እዚህ ጋር አባታችን አባ ኪሮስ የጻድቅ ሰውና የኃጥእ ሰው ነፍስ ከሥጋ ስትለይ በጌታችን ፈቃድ በግልጽ እንደተመለከተ ከገድሉ አውጥተን እንነግራችሁ ዘንድ እንወዳለን፡- ‹‹ጌታችን ለአባ ኪሮስ ‹የነፍስን ከሥጋ መለየት ታይ ዘንድ ወደ አንዲት አገር ትሔድ ዘንድ አዝሃለሁ፣ ካየህም በኋላ ወደ በዓትህ ተመለስ› ብሎት ከእርሱ ተሰወረ፡፡ አባ ኪሮስም በአንደኛው ቀን ተነሥቶ ሲሔድ ከአንዲት ሀገር ደረሰ፡፡ በዚያም ፈጽማ የታመመች አንዲት ሴት አገኘና እርሷ ወዳለችበት ቤት ገባ፡፡ መላእክትን በአጠገቧ ሲመላለሱ ተመለከተ፡፡ በእጃቸው መሰንቆ የያዙ አሉ፣ የገነት አበባ የያዙም አሉ፣ ልብሰ መንግሥትም የያዙ አሉ፣ የጽድቅ ድባብም የያዙ አሉ፡፡ ሁሉም በአንድነት ‹ፈጽሞ ደስ ይበልሽ፣ ከመከራ ወደ እረፍት፣ ከችግር ወደ ብልጽግና ነይ!› ይሏታል፡፡ እንደግድግዳ ከበው ይህን ሲነጋገሩ ከመላእክት አንዱ ስሙ ገብርኤል የሚባል ወደእነርሱ መጣ፡፡ ‹በግድ እንለያት ዘንድ አላዘዘንምና ስለ እርሷ ምን ትላላችሁ! የገነትን አበባ አሽቷት እንጂ› አላቸው፡፡ እንዳዘዛቸውም አፈረጉ፡፡ ነፍስዋም በመዓዛ ገነት በተመስጦ ከሥጋዋ ተለየች፡፡ አባታችን አባ ኪሮስም መላእክትን ‹ነፍስ ከሥጋ ስትለይ እንዲህ ነውን?› አላቸው፡፡ መላእክትም ‹ኪሮስ ሆይ! እንዲህ አትበል፣ ይህ የምታየው ክብር ለጻድቃን ብቻ ነው፡፡ ለኃጥእ ሰው ግን መልአከ ሞት ከሠራዊቱ ጋር በሚያስፈራ ግርማ ይመጣባቸዋል፡፡ የእርሱንም ሥራ በዐይንህ ታይ በጆሮህም ትሰማ ዘንድ አግባብ አይደለም› አሉት፡፡ ይህንንም ነገር ነግረውት መላእክት ወደ ሰማይ ዐረጉ፡፡ አባ ኪሮስም የእግዚአብሔርን ድንቅ ሥራ እያደነቀ ወደ በዓቱ ተመለሰ፡፡ ከዚህም በኋላ አባ ኪሮስ ሦስት ቀን ቆይቶ ወደ ሀገር ወጥቶ ሔደ፡፡ መላእክተ ጽልመት የእሳት በትሮችን ይዘው ሲሽቀዳደሙ አየ፡፡ አባ ኪሮስም ደንግጦ የሚሆነውን ይረዳ ዘንድ ወደ እነርሱ ሔደ፡፡ በዚያም በጽኑ ደዌ የተያዘ አንድ ሰው ነበር፡፡ መላእክተ ጽልመት እንደግድግዳ ከበው በእሳት በትር ይደበድቡታል፡፡ ነፍሱንም ‹አንቺ ጎስቋላ ነፍስ ነይ ውጭ፣ እንደሥራሽም ዋጋሽን ተቀበይ…› እያሉ ይሰድቧታል፡፡ በዚህም ጊዜ ቅዱስ ገብርኤል መጥቶ አባ ኪሮስን በእጁ ያዘው፡፡ ከድንጋጤም የተነሣ ነፍሱ ከሥጋው እንዳትለይ ከእራሱ እስከ እግሩ ጥፍር ድረስ በገነት አበባ አሸውና ‹…መጨረሻውን ታይ ዘንድ ጽና› አለው፡፡ ያንጊዜም መልአከ ሞት መጥቶ በዚያች ነፍስ ላይ መርዙን ተነፈሰባት፣ በአፉም ጎርሶ ውጦ አኝኮ መልሶ ተፋት፡፡ ሦስት ጊዜም መላልሶ እንዲህ አደረጋትና ለመላእክተ ጽልመት ሰጥቷቸው ሔደ፡፡ መላእክተ ጽልመትም ከእነርሱ ለአንዱ በጥፍሩ አሲዘው እስከ ሦስተኛ ሰማይ አውጥተው ወደ ምድር ጣሏት፡፡ ሦስት ጊዜም መላልሰው እንዲሁ አደረጉ፡፡ ከዚህም በኋላ እንደሥራዋ ታገኝ ዘንድ ወደላይ አሳርገው ከእግዚአብሔር ፊት አደረሷት፡፡ ቅዱስ ገብርኤልም አባታችን አባ ኪሮስን ‹የጻድቃንንና የኃጥአንን ሞት አይተሃልና ይህን አስተውል› አለው፡፡ አባ ኪሮስ ግን ከድንጋጤው የተነሣ ታመመ፣ ማናገርም ተሳነው፡፡ ቅዱስ ገብርኤልም ‹አባ ኪሮስ ሆይ! አንተም እንዲህ ትሆናለህን?› አለው፡፡ ይህንንም ብሎ በፊቱና በሁለቱ ጆሮው እፍ አለበት፡፡ ልቡንም በዳሰሰው ጊዜ ፍርሃትና ድንጋጤ ከእርሱ ተወገደለት፡፡ ወዲያም ቅዱስ ገብርኤል ወደላከው ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ አባ ኪሮስም ፈጽሞ እያዘነ ወደ ‹…ወዮልኝ ወዮታ አለብኝ፣ የማዝነው ለዚያ ሰው ብቻ አይደለም ለራሴም ነው እንጂ…› እያለ ወደ በዓቱ ተመለሰ፡፡ በበዓቱም ሆኖ በዕለቱ ዘጠኝ እልፍ ይደግድ ጀመር፣ እንባውም እንደውኃ ይፈስ ጀመር፡፡ ጌታችንም ወደ እርሱ መጥቶ እስካረጋጋውና እስካጽናናው ቃልኪዳንም እስከሰጠው ድረስ እንዲሁ በታላቅ ተጋድሎ ኖረ፡፡)
መላእክተ ብርሃን ‹‹ወይ ነፍስ! እንዴት ለደገኛው መንግሥተ ሰማያት ተፈጥረሽ ለገሃነመ እሳት ሆንሽ? በሥላሴ አምሳል ተፈጥረሽ የዲያብሎስ መረገጫ የሰይጣናት መራወጫ ሆንሽ!?›› ብለው አዝነው አልቅሰው ይሔዳሉ ወዳልነው ነገር እንመለስ-ከዚህ በኋላ መላእክተ ጽልመት የእሳቱን መንዶ፣ የእሳቱን መጋዝ ይዘው መጥተው እንደ ግድግዳ ቆመው አስጨንቀው አስጠብበው ይጠይቋታል፡፡ ምን ብለው ይጠይቋታል? ቢሉ ‹‹አንቺ ነፍስ በማን ታመልኪ ነበር? የሥላሴን አንድነት ሦስትነት፣ ምልዐት፣ ስፋት፣ ርቀት፣ የጌታን ከሰማይ መውረዱን፣ መወለዱን፣ ወልደ አብ ወልደ ማርያም መሆኑን፣ መገፈፍ፣ መገረፉን፣ መሰቀል፣ መሞቱን፣ መቀበሩን፣ መነሣቱን ማረጉን፣ ዳግም ለፍርድ መምጣቱን ታምኛለሽን?›› ብለው ይጠይቋታል፡፡ እርሷም ያልተማረች ከሆዷ በቀር ሌላ የማታውቅ ናትና ‹‹እኔስ የሥላሴን አንድነት ሦስትነት፣ ምልዐት፣ ስፋት፣ ርቀት፣ የጌታን ከሰማይ መውረዱን፣ መወለዱን፣ ወልደ አብ ወልደ ማርያም መሆኑን፣ መገፈፍ፣ መገረፉን፣ መሰቀል፣ መሞቱን፣ መቀበሩን፣ መነሣቱን ማረጉን፣ ዳግም ለፍርድ መምጣቱን አላውቅም፡፡ ለሥጋዬ ስጥር ስግር ስላፋ ስማስን ነበርሁ እንጂ፣ ሃይማኖት አልተማርሁ፣ ምግባር አልሠራሁ፡ እናንተማ ወዳጆቼ ዘመዶቼ አይደላችሁምን? የመከራችሁኝን ሰምቼ ያዘዛችሁኝን ሠርቼ እኖር ነበር እንጂ›› ትላቸዋለች፡፡
የክፉ የኃጥእ ሰው ነፍስ መላእክተ ጽልመትን የት ታውቃቸዋለችና እንዲህ ትላቸዋለች? ቢሉ የክፉ ሰው ነፍስ እንደሆነች ገና በቁመናዋ ሳለች በህልምም በራእይም ከመላእክተ ጽልመት ጋር ገሃነመ እሳት እየወረደች ታይ ነበረችና ስለዚህ ‹‹አውቃችኋለሁ›› ትላቸዋለች፡፡ ቀድሞም አጋንንት ለእርሷ ያዘኑ መስለው ‹‹አንቺ ነፍስ ሰንበትን ብታከብሪ፣ ምጽዋት ብትመጸውቺ፣ ዓሥራት በኩራት ብታወጪ ቦታሽ ይህ ስለሆነ ምን ያደክምሻል? ይልቅስ ቅጠፊ፣ ስረቂ፣ ነፍስ ግደይ፣ ሰንበትን ሻሪ፣ ጾም ግደፊ፣ ጸሎት አቁሚ፣ ዋርሳ ውረሽ፣ ዝሙት ፈጽሚ… ይህንና የመሳሰለውን አድርጊ እያሉ ሲመክሯት ነበርና ስለዚህ ‹‹አውቃችኋለሁ›› ትላቸዋለች፡፡
ከዚኽም በኋላ መላእክተ ጽልመት ‹‹ለራስሽ አንቺ እገዛ እነዳ፣ እበላ እጠጣ፣ እለብስ፣ እደላደል፣ እቀማጠል ብለሽ እንጂ አንቺ ለእኛ ምን ውለታ ውለሽልናል? ቆርሰሽ አላጎረስሽን ጠልቀሽ አላጠጣሽን! አንቺ ኩሩ ትዕቢተኛ እንግዲህ ነይ ውጪ! በቁመናሽ የሠራሽውን የምግባርሽን ዋጋ ብድራቱን ክፈይ…›› እያሉ ራስ ራሷን እየቀጠቀጡ ያስጨንቋታል፡፡ ያስጠብቧታል፡፡ ‹‹ንዒ ፃኢ ከመ ትትፈደዪ ፍዳ አበሳኪ›› እንዳለ ድርሳነ ሰንበት፡፡ ከዚኽ በኋላ መልአከ ሞት ከአድማስ እስከ አድማስ ተስተካክሎ ቁሞ፣ ጥርሱን አግጦ ዐይኑን አፍጦ ይታያታል፡፡ ጥርሱም በመልአኩ ክንድ 88 ነው፡፡ የመልአኩ ክንድ አንዱ በሰው ክንድ 44 ነው፡፡ የአንድ ዐይኑ መቃድ ስፋት 3 ዓመት ከመንፈቅ ያስኬዳል፡፡ የ2ኛው ዐይኑ መቃድ ስፋት 3 ዓመት ከመንፈቅ ያስኬዳል፡፡ በጠቅላላው የሁለት ዐይኑ መቃድ 7 ዓመት ያስኬዳል፡፡ ቁመቱ ደግሞ ከምድር እስከ ሰማይ ነው፡፡ ከዚኽም በኃላ 3 ጊዜ ተራምዶ መጥቶ ከፊቷ ይቆማል፡፡ ያችም ኃጥእ ነፍስ በዚህ ደንግጣ ስትጨነቅ ተንፈንጥራ


እንዲህም ማለቱ በእግረ ነፍስ ነው እንጂ በእግረ ሥጋስ አታስቆምም፡፡ እንዲህማ ከሆነ ምን አድርጋ ትሻገረዋለች ቢሉ በዚህ ዓለም ያሉ አዕዋፍ ዳሩን ገደሉን ባሕሩን እሳቱን ላይ ላዩን በክንፍ እየበረሩ ተሻግረው እንዲሔዱ የእርሷም ሃይማኖቷና ግብሯ ክንፍ ሆኗት መላእክተ ብርሃን ላይ ላዩን ይዘዋት ይሻገራሉ፡፡ እርሷም ከመካከል ስትደርስ አቈልቁላ አይታ መላእክተ ብርሃንን ‹‹…ይህ እሳቱ፣ ባሕሩ፣ ገደሉ፣ ዱሩ ምንድነው?›› ብላ ትጠይቃቸዋለች፡፡ መላእክተ ብርሃንም ‹‹አንቺ ምግባር ብትሠሪ፣ ሃይማኖት ብትማሪ፣ ሰንበትን ብታከብሪ በዚህ መጣሽ እንጂ ምግባር ያልሠሩ፣ ሃይማኖት ያልተማሩ ዘመዶችሽስ በዚያው አረው ከስለው እንደ ጅማት ተኮማትረው መከራ አይተው ይሻገሩታል›› ይሏታል፡፡ እርሷም በዚህ ጊዜ ‹‹…ወየው! ወየው! በምድራዊው ዓለም ላሉ ሰዎች እንዲህ ያለ ብርቱ መከራ እንዳለባቸው ማን በነገራቸው!?...›› ብላ አዝና ተክዛ አልቅሳ ትሔዳለች፡፡
(የክብር ባለቤት ጌታችን ለድንግል እናቱ ለእመቤታችን በሰኔ 21 ቀን በጎልጎታ ስትጸልይ ሳለ ከገባላት ቃልኪዳን ውስጥ አንዱ ‹‹…በቃልኪዳንሽ የታመነውን ይህችን ጸሎት የያዘውን ሰው በደረቴ አቅፌ ባሕረ እሳትን አሻግረዋለሁ፣ ወደ መንበረ መንግሥቴም አቀርበዋለሁ›› የሚል መሆኑን ያስታውሷል፡፡) ወደ ቀደመው ነገር እንመለስና ያቺም ነፍስ አዝና ተክዛ አልቅሳ ስትሔድ ዛሬ በዚህ ዓለም ያለች ሙሽራ አባት እናቷ መልስ ጠርተዋት በደስታ እንድትሔድ እርሷም ከፈጣሪዋ ለመገናኘት ስትሔድ በፍሥሐ በደስታ ትሔዳለች፡፡ ዳግመኛ ዛሬ በዚህ ዓለም ያሉ እናት አባት ለልጃቸው የሚበላውን የሚጠጣውን አሰናድተው እንዲቆዩ ለእርሷም ፈጣሪዋ የመኖሪያዋን ቦታ መንፈሳዊ ምግብና መጠጥ አዘጋጅቶ በፍሥሐ በደስታ ይቆያታል፡፡ እርሷም ገሃነመ እሳትን አልፋ በመውጣቷ ደስ እያላት ከጌታ ዘንድ ስትደርስ ሰግዳ ትቆማለች፡፡ ሰግዳም ስትቆም ጌታ ይጠይቃታል፡፡ ምን ብሎ ይጠይቃታል? ቢሉ የወንድ ነፍስ እንደሆነች ‹‹አንቺ ነፍስ እንጨት መቁረጥ፣ መፍለጥ፣ ቤት ማነጽ፣ ፈረስ መጋለብ ውኃ ዋና፣ ሰንጠረዥ፣ እርሻ፣ ቁፋሮ፣ በገና፣ ጸናጽል፣ ከበሮ፣ ጽሕፈት፣ ድጉሰት ታውቂያለሽን?›› ብሎ አይጠይቃትም፡፡ የሴትም ነፍስ ብትሆን ‹‹አንቺ ነፍስ አልሞ መደቆስ፣ አለስልሶ መፍተል፣ ወጥ መሥራት፣ እንጀራ መጋገር፣ ጠጅና ጠላ መጥመቅ ታውቂያለሽን?›› ብሎ አይጠይቃትም፡፡
እንግዲያስ ምን ብሎ ይጠይቃታል? ቢሉ ‹‹አንቺ ነፍስ በማን ታምኛለሽ? አንድነቴን ሦስትነቴን፣ ምልዐት ስፋቴን፣ ርቀቴን፣ ከሰማየ ሰማያት መውረዴን፣ ከድንግል ማርያም መወለዴን፣ ወልደ አብ በመለኮት፣ ወልደ ማርያም በትስብእት በተዋሕዶ የከበርኩ መሆኔን፣ መገፈፍ መገረፌን፣ መሰቀል መሞቴን፣ መነሣት ማረጌን ታውቂያለችን? ብሎ ይጠይቃታል፡፡ እርሷም የተማረች ናትና ቃሏም እውነተኛ ነውና ‹‹አዎን አምላኬ ሆይ! አንድነትህን ሦስትነትህን፣ ምልዓት ስፋትህን፣ ርቀትህን፣ መውረድ መወለድህን፣ ወልደ አብ ወልደ ማርያም በተዋሕዶ የከበርህ መሆንህን፣ መገፈፍ መገረፍህን፣ መሰቀል መሞትህን፣ መነሣት ማረግህን ዐውቃለሁ›› ብላ ትመልሳለች፡፡ ከዚያም የጌታ በእውነተኛ ቃሉ መላእክተ ብርሃንን ጠርቶ ‹‹ይህቺ ነፍስ ምእመን (ታማኝ) ናትና መንግሥተ ሰማያት እንጂ ገሃነመ እሳት አይገባትም፣ ከሥጋዋ ጋር አዋሕጄ ፍጹም መንግሥተ ሰማያትን እስካወርሳት ድረስ 4 ቀን ገሃነመ እሳትን፣ 3 ቀን መንግሥተ ሰማያትን አዙራችሁ አሳይታችሁ ከጻድቃን ጋራ በገነት አኑሯት›› ብሎ ያዛል፡፡
ከዚህ በኋላ መላእክተ ብርሃን ይዘዋት ወጥተው መንግሥተ ሰማያትን፣ የባለ ሕጎች አገር የደናግልን፣ የጻድቃንን አገር 3 ቀን አዙረው አሳይተው ሽታዋን ጣዕሟን በልቡናዋ አሥርፀው፤ ‹‹አንቺ ነፍስ ሃይማኖት ስላለሽ በጎ ምግባር ስለሠራሽ በእንዲህ ያለ በደስታ ቦታ ያኖርሻል›› ብለው ወደ ገሃነመ እሳት ይዘዋት ይወርዳሉ፡፡ ከገሃነመ እሳት ውስጥ ያለውን የእሳቱን አክሊል፣ የእሳቱን ዘውድ፣ የእሳቱን ዘንዶ፣ የእሳቱን እባብ፣ የእሳቱን አንበሳ፣ የእሳቱን መጋዝ፣ የእሳቱን ሰይፍ፣ የእሳቱን ጦር፣ የእሳቱን ዝናር፣ የእሳቱን ጫማ ይህንንና የመሳሰለውን ሁሉ ካፋቱን ክርፋቱን፣ ግማቱን ሁሉ 4 ቀን አዙረው አሳይተው ‹‹አንቺ ነፍስ ሃይማኖት ባይኖርሽ በጎ ምግባር ባትሠሪ ኖሮ በእንዲህ ያለ መከራ ያኖርሽ ነበር፡፡ ነገር ግን ሃይማኖት ስላለሽ በጎ ምግባር ስለሠራሽ ጌታ በቸርነቱ ከእንዲህ ያለ መከራ አውጥቶ በደስታ ያኖርሻል›› ብለው ወስደው ከጻድቃን ጋር ያኖሯታል፡፡ ሀገረ ሕያዋንን፣ ሀገረ ሰማዕታትን፣ ሀገረ ደናግልን፣ ሀገረ መነኰሳትን፣ ሀገረ ሕጋውያንን እያዞሩ እያሳዩ ‹‹አንቺ ነፍስ ሃይማኖት ብትማሪ ምግባር ብትሠሪ ጌታ በቸርነቱ ከዲያቢሎስ መገዛት ከእንዲህ ያለ መከራ አውጥቶ ከእንዲህ ያለ ተድላ ደስታ አበቃሽ›› ብለው ወስደው ከጻድቃን ጋራ በገነት ያኖሯታል፡፡ ኋላም ከገሃነመ እሳት መውጣቷን፣ መንግሥተ ሰማያት መግባቷን እያሰበች እስከጊዜ ምጽዓት ድረስ በገነት በደስታ ትኖራለች፡፡
ገነት ያለችው በወዴየት ነው? ቢሉ በፀሐይ መውጫ ወይም በስተምሥራቅ በኩል ናት፡፡ በ4ቱ ማዕዛኗ ዐራት ተራሮች አሏት፤ በ4ቱ ተራሮች መካከል 4 አፍላጋት ገብተው ያጠጧታል፡፡
ደገኛይቱ ነፍስ የገሃነመ እሳትን ሥቃይ እያሰበች ከገሃነመ እሳት መውጣቷንና መንግሥተ ሰማያት መግባቷን እያሰበች ፈጣሪዋን እያመሰገነች እስከ ጊዜ ምጽዓት ድረስ በፍሥሐ በደስታ ትኖራለች፡፡ ከምጽአትም በኋላ ከሥጋዋ ጋራ ተዋሕዳ ተድላ ደስታ ካለበት ፍጹም መንግሥተ ሰማያት ትገባለች፡፡ መንግሥተ ሰማያት ያለችው በወዴት ነው? ቢሉ ከኢዮር በላይ ከሰማይ ውዱድ በታች በመካከላቸው ናት፡፡ ሃይማኖት ከምግባር አስተባብሮ የያዘ የመልካም ሰው ነፍስ በዚህ ሁኔታ ዘላለማዊ የክብር ዋጋዋን ተቀብላ ትኖራለች፡፡ ከገቡ መውጣት ካገኙ ማጣት ከሌለባት ከዚህች ፍጹም ተድላ ደስታ ካለባት ርስት መንግሥተ ሰማያት ለመግባት የመድኃኔዓለም ቸርነቱ የድንግል እናቱ የቅዱሳኑ የሰማዕታቱ ሁሉ ምልጃና ጸሎት ይርዳን! አሜን!!!
ሃይማኖት ያልተማረ ከምግባር ጎደለ የኃጥእ ሰው ነፍስስ እንዴት ትሆናለች? ቢሉ የኃጥእ ሰው ነፍስ ገና ከሥጋዋ ሳትለይ በጻዕረ ሞቷ ሳለች መላእክተ ጽልመት በግራ መላእክተ ብርሃን በቀኝ ሆነው ይመጡባታል፡፡ መጥተውም ባዩአት ጊዜ በጨለማ ቁርበት ተጠቅልላ በእሳት ሰንሰለት ታስራ የእሳት አክሊል ደፍታ የእሳት ዝናር ታጥቃ፣ የእሳት ጫማ ተጫምታ፣ ከቁራ 7 እጅ ጠቁራ፣ ከፍታ ከርፍታ ዲያብሎስን መስላ ትታያቸዋለች፡፡ ከዚህ በኋላ መላእክተ ብርሃንን ትገማቸዋለች፣ ትከረፋቸዋለች፤ እነርሱም ይፀየፏታል፡፡ ከእርሷ ርቀው ፈቀቅ ብለው ቆመው ይጠይቋታል፡፡ ምን ብለው ይጠይቋታል? ቢሉ ‹‹አንቺ ነፍስ በማን ታመልኪያለሽ? የሥላሴን አንድነት ሦስትነት፣ ምልዐት፣ ስፋት፣ ርቀት፣ የጌታን ከሰማይ መውረዱን፣ መወለዱን፣ ወልደ አብ ወልደ ማርያም መሆኑን፣ መገፈፍ፣ መገረፉን፣ መሰቀል፣ መሞቱን፣ መቀበሩን፣ መነሣቱን ማረጉን፣ ዳግም ለፍርድ መምጣቱን ታምኛለሽን? የእግዚአብሔርን እንግዳ ተቀብለሻል? ሰንበትን አክብረሻልን?›› ብለው ይጠይቋታል፡፡ እርሷም ያልተማረች ናትና ‹‹እኔስ የሥላሴን አንድነት ሦስትነት፣ ምልዐት፣ ስፋት፣ ርቀት፣ የጌታን ከሰማይ መውረዱን፣ መወለዱን፣ ወልደ አብ ወልደ ማርያም መሆኑን፣ መገፈፍ፣ መገረፉን፣ መሰቀል፣ መሞቱን፣ መቀበሩን፣ መነሣቱን ማረጉን፣ ዳግም ለፍርድ መምጣቱን አላውቅም፡፡ በምንሰ አውቃለሁ? መምህራንን አልጠየቅሁ፣ መጻሕፍትን አላነበብሁ፣ ቤተ


‹‹በውኑ ሞት እንደዚህ መራራ ነውን?›› 1ኛ ሳሙ 15፡32።

(ከዐቢይ ጾሙ ጋር በተገናኘ በብዙዎቻችሁ ጥያቄ መሠረት በድጋሚ የቀረበ)

ይኽ ጽሑፍ ነፍስ ከሥጋ ስትለይ በፍጹም ደስታ አሊያም በእንዴት ያለ አስጨናቂ መከራ ውስጥ እንደምትገኝ የሚያስረዳ ግሩም ምሥጢርን የተመላ ነውና በጥሞና አንብበነው ለነፍሳችን የሚሆን ስንቅ እንሰንቅ ዘንድ ለኹላችን ተዘጋጀልን! (የጽሑፉ ምንጭ ደብረ ሊባኖስ አንድነት ገዳም ‹‹ሕማማተ መስቀል›› በሚል ርዕስ ካሳተመው ድርሳን ላይ ‹‹ሕይወተ ምእመናን›› የሚለው ንዑስ ርዕስ ነው፡፡)
በርዕሱ ላይ ያለውን ኃይለ ቃል ‹‹በውኑ ሞት እንደዚህ መራራ ነውን?›› (1ኛ ሳሙ 15፡32) ሲል የተናገረው በሞት ጣዕር ላይ የነበረው የአማሌቃውያን ንጉሥ አጋግ ነው፡፡ ንጉሥ አጋግ ሃይማኖት የሌለው፣ የብዙ ንጹሐንን ደም በግፍ ሲያፈስ የኖረ ኃጥእ ሰው ነበር፡፡ እርሱም በተራው በሞት አፋፍ ላይ ሳለ ፈራ፣ ተንቀጠቀጠ፡፡ ከጭንቀት ብዛት ጅማቶቹ እርስ በርሳቸው ተለያዩ፤ አጥንቶች ተላቀቁ፡፡
በዓለም ላይ ያለ ማንም ኃጥእ ሰው ንጉሥ ይሁን ሎሌ፣ የተማረ ምሑር ይሁን ያልተማረ ጨዋ፣ ሀብታም ይሁን ድሀ ማንኛውም ሰው በእውነተኛዋ ሃይማኖት ያላመነ ምግባር የሌለው ከሆነ በስተመጨረሻ በሞት አፋፍ ላይ ሳለ እጅግ እፈሪውን መልአከ ሞትን በገሃድ በተመለከተ ጊዜ እንደንጉሥ አጋግ ‹‹ከመዝኑ ሞት መሪር-በውኑ ሞት እንደዚህ መራራ ነውን?›› ማለቱ አይቀርም፡፡ ስለዚህ በአጭሩ ምእመናን ስለ ሃይማኖታቸው ጠንቅቀው ሊያውቁ፣ ምግባር፣ ትሩፋት ሊሠሩ ይገባቸዋል፡፡ ይህስ ስለምንድን ነው? ቢሉ ኋላ በዕለተ ሞት በጌታ ቃል መጠየቅ አይቀርምና ነው፡፡ የክብር ባለቤት ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‹‹በዚህች ምድር ሳላችሁ ሃይማኖት ተማሩ፣ ምግባር ሥሩ›› ብሎ አዟልና ነው፡፡
ኋላ በዕለተ ሞት ጊዜ በጌታ ቃል ምን ተብሎ ይጠየቃል? ቢሉ የመልካም ሰው ነፍስ እንደሆነች ከሥጋዋ ሳትለይ ገና በፃዕረ ሞቷ ሳለች መላእክተ ብርሃን በቀኝ፣ መላእከተ ጽልመት በግራ ሆነው ይመጡባታል፡፡ መጥተውም ባዩዋት ጊዜ የብርሃን ቀሚስ ለብሳ፣ የብርሃን መጐናጸፊያ ተጐናጽፋ፣ የብርሃን አክሊል ደፍታ፣ የብርሃን ዝውድ ተቀዳጅታ፣ የብርሃን ዝናር ታጥቃ፣ የብርሃን ጫማ ተጫምታ፣ የመስቀል ምልክት ያለበት የብርሃን ዘንግ ይዛ፣ ከፀሐይ 7 እጅ አብርታ፣ ከመብረቅ 7 እጅ አስፈርታ፣ አምራና ሠምራ ጌታዋን ክርስቶስን መስላ ትቆያቸዋለች፡፡
ከዚህም በኋላ መላእክተ ጽልመትን እንደ እሳት ትፈጃቸዋለች፤ እንደ ፀሐይ ታንፀባርቅባቸዋለች፤ እነርሱም ይፈሯታል፡፡ ከፊቷ ርቀው ፈቀቅ ብለው ይቆማሉ፡፡ በዚያው ርቀው በቆሙበት ሆነው ጠርተው ይጠይቋታል፡፡ ምን ብለው ይጠይቋታል? ቢሉ ‹‹አንቺ ነፍስ በማን ታመልኪያለሽ? የሥላሴን አንድነት ሦስትነት፣ ምልዐት፣ ስፋት፣ ርቀት፣ የጌታን ከሰማይ መውረዱን፣ መወለዱን፣ ወልደ አብ ወልደ ማርያም መሆኑን፣ መገፈፍ፣ መገረፉን፣ መሰቀል፣ መሞቱን፣ መቀበሩን፣ መነሣቱን ማረጉን፣ ዳግም ለፍርድ መምጣቱን ታምኛለሽን? የእግዚአብሔርን እንግዳ ተቀብለሻል? ሰንበትን አክብረሻልን?›› ብለው ይጠይቋታል፡፡ እርሷም እውነተኛ የተማረች ሃይማኖተኛ ናትና ‹‹አዎን የሥላሴን አንድነት ሦስትነት፣ ምልዐት፣ ስፋት፣ ርቀት፣ የጌታን ከሰማይ መውረዱን፣ መወለዱን፣ ወልደ አብ ወልደ ማርያም መሆኑን፣ መገፈፍ፣ መገረፉን፣ መሰቀል፣ መሞቱን፣ መቀበሩን፣ መነሣቱን ማረጉን፣ ዳግም ለፍርድ መምጣቱን አምናለሁ…ነገር ግን እንደ እናንተ ያለ የከፋ የከረፋ አይቼም ሰምቼም አላውቅም›› ብላ ትመልስላቸዋለች፡፡
መላእክተ ጽልመትም መርምረው የእርነሱ ድርሻ አለመሆኗን ካረጋገጡ በኋላ አፍረው ተዋርደው ‹‹አንቺ ነፍስ እኛ ያጣናትን መንግሥተ ሰማያት አንቺ አገኘሻት!...›› እያሉ እያዘኑ እየተከዙ ትተዋት ይሔዳሉ፡፡
ከዚህም በኋላ መላእክተ ብርሃን ከገነት መልካም መዓዛ ያለው የሽቱ አበባ ቆርጠው ይዘው መጥተው ካጠገቧ ከበዋት ይቆማሉ፡፡ ቆመውም ይጠይቋታል፡፡ ምን ብለው ይጠይቋታል? ቢሉ ‹‹አንቺ ነፍስ በማን ታመልኪያለሽ? የሥላሴን አንድነት ሦስትነት፣ ምልዐት፣ ስፋት፣ ርቀት፣ የጌታን ከሰማይ መውረዱን፣ መወለዱን፣ ወልደ አብ ወልደ ማርያም መሆኑን፣ መገፈፍ፣ መገረፉን፣ መሰቀል፣ መሞቱን፣ መቀበሩን፣ መነሣቱን ማረጉን፣ ዳግም ለፍርድ መምጣቱን ታምኛለሽን? የእግዚአብሔርን እንግዳ ተቀብለሻል? ሰንበትን አክብረሻልን?›› ብለው ይጠይቋታል፡፡ እርሷም ቃሏ እውነት ነውና ‹‹አዎን የሥላሴን አንድነት ሦስትነት፣ ምልዐት፣ ስፋት፣ ርቀት፣ የጌታን ከሰማይ መውረዱን፣ መወለዱን፣ ወልደ አብ ወልደ ማርያም መሆኑን፣ መገፈፍ፣ መገረፉን፣ መሰቀል፣ መሞቱን፣ መቀበሩን፣ መነሣቱን ማረጉን፣ ዳግም ለፍርድ መምጣቱን አምናለሁ›› ብላ ትመልስላቸዋለች፡፡ ዳግመኛም ‹‹5ቱን አዕማደ ምሥጢር 13ቱን ሕማማተ መስቀል ተምረሻል? ሰንበትን አክብረሻል? የእግዚአብሔር እንግዳ ተቀብለሻልን?›› ብለው ይጠይቋታል፡፡ እርሷም ‹‹አዎን አውቃለሁ እናንተማ ወዳጆቼ ዘመዶቼ አይደላችሁምን? የመከራችሁንኝ ሰምቼ፣ ያዘዛችሁኝን ሠርቼ እኖር የለምን? ብላ ትመልስላቸዋለች፡፡ የጻድቅ ነፍስ መላእክተ የት ታውቃቸዋለችና ነው? ቢሉ የመልካም ሰው ነፍስ የሆነች እንደሆነ ገና በቁመናዋ በዓለመ ሥጋ ሳለች በአካለ ነፍስ ከመላእክተ ብርሃን ጋራ ከሰማየ ሰማያት የእወጣች እየወረደች ጌታዋን ፈጣሪዋን ስታመሰግን ትኖር ነበርና ስለዚህ ‹‹አውቃችኋለሁ›› ትላቸዋለች፡፡ መላእክተ ብርሃንም ያችን ነፍስ መርምረው የእነሱ ወገን መሆኗን ካረጋገጡ በኋላ ‹‹ከቃልሽ እናግኘው ብለን ነው እንጂ አዎን እኛማ እናውቅሻለን›› ብለው ይመሰክሩላታል፡፡
ከዚኽም በኋላ ነቢዩ ዳዊት በገናውን፣ ዕዝራ መሰንቆውን ይዘው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እልፍ አዕላፍ መላእክትን፣ ጻድቃን፣ ሰማዕታትን፣ ደናግል መነኰሳትን አስከትሎ ወርዶ በቁመናዋ የሠራችውን የምግባሯን ዋጋ ቃልኪዳን ሰጥቷት ተመልሶ ያርጋል፡፡ መውጣት መውረዱ ለእኛ ክብር ሲል በለበሰው ሥጋ ነው እንጂ በመለሎትነቱስ በሁሉ የመላ ስለሆነ መውጣት መውረድ የለበትም፡፡
ከዚኽም በኋላ መልአከ ሞት አምሮ ሠምሮ መልአከ ብርሃን መስሎ ይታያታል፡፡ ስለምን መልአከ ሞት መልአከ ሣህል መልአከ ብርሃን መስሎ ይታያታል ቢሉ? እንዳትባባ እንዳትፈራ ነው፡፡ ከዚኽም በኋላ መላእክተ ብርሃን ያንን ከገነት ቆርጠው ያመጡትን የሽቱ አበባ ከአፍንጫዋ ላይ ጣል አድርገው ሲያነሡት በመልካሙ የሽታ መዓዛ ተመስጣ ነፍስ ከሥጋዋ ትለያለች፡፡
ከዚኽም በኋላ መላእክተ ብርሃን በፊት በኋላ፣ በቀኝ በግራ ሆነው ዕዝራ መሰንቆውን፣ ዳዊት መገናውን እየደረደሩ እያመሰገኑ ዳዊት ‹‹የጻድቅ ሰው ሞት በእግዚአብሔር ዘንድ ክቡር ነው›› (መዝ 115፡6) እያለ፣ ዕዝራም ‹‹የጻድቃን ሞታቸው ሕይወታቸው ነው…›› እያሉ በዝማሬ በይባቤ ይዘዋት ይሔዳሉ፡፡
ከዚኽም በኋላ መላእክተ ጽልመት ከጌታ ቃል ሳይሰሙ ትእዛዝ ሳይቀበሉ አይመለሱምና ራስ ራሷን እየተመለከቱ ሲከታተሏት ከባሕረ እሳት ይደርሳሉ፡፡ የባሕረ እሳት ቦታዋ ስፍራዋ ወዴት ነው? መጠኗስ ምን ያህል ነው? ቢሉ ቦታዋ ከጠፈር በላይ ከሐኖስ በታች ከመካከል በምጽንዓተ ሰማይ ነው፡፡ ልኳም ይህችን ሰው የሠፈረባት ዓለም ታህላለች፤ ቀኝዋ እሳት ግራዋ ባሕር ነው፣ ውስጧ ገደል መንገዷም ከጭራ የቀጠነ ጠባብ ነው፡፡ ዕዝ 5፡8፡፡




«ክርስቶስ ከዚች ገዳም አለ»
⛪️እመ ምዑዝ ፍቅርተ ክርስቶስ ገዳም⛪️
★ለጌታችን ለአምላካችን ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በ4ቱም አቅጣጫ የሰገደች ቤተ መቅደስ
★ በልዩ ሁኔታ መካን የሚፈታ ጨጓራን የሚያድን ደዌን የሚያርቅ ድንቅ ቦታ
★እስከ ዕለተ ምፅአት ድረስ የማይፈርስ ቤተ መቅደስ
★የጣልያን ጦር አዛዥ የመሰከረለት
★★★★★★ፃድቋ፣ ሰማእቷ፣ ታአምረኛዋ፣ ደጓ፣ ሀዋርያዊቷ፣ ከፋሌ ባህሯ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ትውልዷ ደ/ጎንደር ደራ ፎገራ አንበሳሜ ከእናቷ ከወንጌላዊት ከአባቷ ከላባ በጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ትውልድ ቀን ታህሳስ 29 በታዘዘ መልአክ አብሳሪነት ተወለደች። ልደታቸው ከጌታችን ጋር ከገጠመላቸው ከአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፣ ቅዱስ ላሊበላ፣ ቅዱስ ነአኩተለአብ፣ ከአብረሃ ወአፅብሀ፣ አቡነ አካለ ክርስቶስ፣ አቡነ መዝራእተ ክርስቶስ፣ መስፍን ኢያሱ፣ የገርኣልታው አቡነ ዳንኤል፣ አቡነ አብሳዲ፣ አቡነ ፄዋለፅድቅ፣ ዳግማዊ ቂርቆስ ዘቡልጋ የሷም ልደት ገጥሟል። ስትወለድም በእግሯ ቆማ «በማኅያዊ ቸርነትህ ከጨለማ ወደ ብርሃን ላወጣኸኝ ለአብ ምስጋና ለወልድ ምስጋና ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይገባል» ብላ አመስግናለች። በስእለት ስለተገኘች ስሟን ማርያም ጸዳለ አሏት።
★★★ እናታችን ፍቅርተ ክርስቶስ በነበረችበት ዘመን አፄ ሱስንዮስ ሁለት ባህሪይ የሚለውን የረከሰ የካቶሊኮች አስተምህሮ የሀገራችን ህዝብ እንዲያምን አውጆ በሀገሪቱ ትልቅ ቀውስ ተከስቶ ከ8 ሺህ በላይ ክርስቲያኖች በግፍ ተጨፍጭፈው ሲያልቁ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ከነ አቡነ ስምዖንና ከሌሎች ቅዱሳንና ቅዱሳት ጋር ተሰልፋ ሰማእትነት ተቀብላ ለሀይማኖቷ ምስክር ሆናለች።
★★★ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስን የሃይማኖቷን ፅናት ስላየ ስጋዋ እየተቆረሰ መሬት ላይ እስኪወድቅ ድረስ በብረት በትር አጥብቆ ያስገርፋት ጀመር። በመጨረሻም ምድር እየሰወረቻት ለመግረፍ የማይመቻቸው ቢሆን ከሌሎች ሰማእታት ጋር አንገቷን በሰይፍ አስቆርጦታል። በዚህ ጊዜ ፍፁም ጨለማ ሆኖ ምድርም ተነዋወጠች።
ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስን አንገቷን በሰይፍ ቢቆርጧትና በሞት ብታርፍም ነገርግን ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ገነትና ሲኦልን አሳይቶ 14 ቀን በሰማያዊት ኢየሩሳሌም ከተቀመጠች በኋላ እንደገና እንደተኛ ወይም ከእንቅልፉ እንደሚነቃ ሰው ከሞት አስነስቶ ወደ ቦታዋ መለሳት።
ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሚካኤል ከሞት ካስነሳት በኋላ በየገዳማቱና በየአድባራቱ እየዞረች ያቀናቻቸው ብዙ ገዳማት አሉ።
ለአብነትም በተሰአቱ ቅዱሳን አንዱ በሆኑት አባ ጉባ ተመስርቶ የነበረውንና በግራኝ ጠፍቶ የነበረውን ታላቁን የራማ ኪዳነምህረት ገዳምን ያቀናችው ያቋቋመችው እንዲሁም የወንድ የሴት ብላ ስርአት የሰራችው እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ናት።
★★★ እናታችን ከተከታዮቿ ጋር ወደ ኢየሩሳሌም እየሄደች ሳለ መንገድ ላይ በላአይተ ሰብ (ሰውን ወይም የሰው ስጋ የሚበሉ)  ይዘዋቸው 60 የሚደርሱ አገልጋዮቿን ለመብላት አይናቸውን በጉጠት አውጥተው 4 ወራት  በጨለማ ቤት ውስጥ ዘጉባቸው። ሰይጣንንም ያመልኩ ስለነበር ከ 4 ወራት በኃላ በአል አድርገው ለመብላት ከእሳት ውስጥ ጨመሯቸው ነገር ግን ጌታችን በቸርነቱ ጠብቋቸዋልና እነ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ምንም አልሆኑም። ያንጊዜም ሰው በላዎቹ «እናንተ ሰዎች ምንድን ናችሁ?» ብለው ጠየቋቸው። ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስም ክርስቲያን መሆናቸውንና የሥላሴ ህንፃ የሆነውን የሰውን ልጅ መብላት እንደሌለባቸው ብታስተምራቸው «ምን እንበላለን» አሏት። እርሷም ከራማ ኪዳነ ምህረት ይዛው የመጣችውን ስንዴ ዘርታ በአንድ ቀን አድጎ ታጭዶ ተወቅቶ ተፈጭቶ ተጋግሮ ለምግብነት ደርሷል ቅድስት እናታችንም ቀምሳ ብታቀምሳቸው እንደ ማር እንደወተት የጣፈጠ ሆነላቸው ከዚያም እንዲያ እያደረጉ እንዲበሉ አድርጋ አስተምራም አስጠመቀቻቸው ስድስት አብያተ ቤተ ክርስቲያናትን አሰርታላቸው ወንጌልን፣ ስንክሳርን፣ ሃይማኖተ አበውን፣ ግንዘትን፣ መዝሙር ዳዊት፣ አርጋኖንን ሁሉ በእጇ ፅፋ አስቀመጠችላቸው።እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ የከበረች ሀዋርያዊት መሆኗን ከዚህ እንረዳለን።
★★★በእውነት ፍቅሯ ይደርብንና አምላክን የወለደች በድንጋሌ ስጋ በድንጋሌ የፀናች ክብርት እመቤታችን ድንግል ማርያም ተገልጣላት በልጇ ምክንያት የደረሰባትን ሀዘኖች አውላታላታለች። የፈለገችውን እንድታደርግበት በእጇ ያለውን መስቀል ለቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ሰጥታታለች። በዚህም መስቀል እናታችን ፍቅርተ ክርስቶስ ባህር ከፍላ ደቀ መዛሙርቶቿን አሻግራለች። የአባታችን የአቡነ ኤዎስጣጤዎስ ገድል በማንበብና በመልአኩ ቅዱስ ሚካኤል እርዳታ ባህሩን በአፅፏ ተሻግራ ወደ ሀገረ ናግራን  ሄዳለች። እንዲሁም በበትረ መስቀሏ እንደ አቡነ ዘርአብሩክ ባህር ውስጥ የሰጠሙ የደቀ መዛሙርቶቿን መፅሀፍት ምንም ሳይሆኑ ማውጣት ችላለች። የእናታችንን ገድል ዘርዝረን እንጨርስ ብንል ጊዜ አይበቃንም ስለዚህ ★★★ስለገዳሙ ጥቂት ልበላችሁ
በአንድ ወቅት ጣልያን ሀገራችንን እንደወረረ ብዙ አብያተ ክርስቲያናትና ገዳማትን እያወደመ መነኮሳትን እየገደለ እናታችን ገዳም ይደርሳል መነኮሳትም ሰማእት ለመሆንተዘጋጅተው ሲጠብቁ የጦር አዛዡና ሰራዊቱ የገዳሙን ክልል አልፈው መግባት አልቻሉም የገዳሙ ክልል ላይ ሲደርሱ በተአምር እግራቸው ተሳሰረ መቆምም መቀመጥም ሳይችሉ ቀሩ የጦር አዛዡም «ክርስቶስ በዚህ ገዳም አለ» ብሎ ሃምሳ ጠገራ ብር ሰጥቶ ተመልሷል
★★★ስለገዳሙ ስናወራ እናታችን ቦታው ላይ የብርሃን አምድ ተተክሎ ስላየች ምንታምር ብላ ጠርታታለች። በተጨማሪም ለጌታችን በአራቱም አቅጣጫ እንደሰው የሰገደው ቤተ መቅደስ በአንድ ቀን የተሰራ ሲሆን የተሰራውም በስሚዛ (በሰንሰል) እንጨት፣ በአይጥ ሀረግ፣ በነጠላ ማገር አድርጋ ሰርታ በአንድ ቀን ታህሳስ 16 በእለተ እሁድ ቅዳሴ ቤቱን አክብራለች ይህ ቦታ እስከ እለተ ምፅአት ድረስ እነደማይፈርስ ጌታችን ቃል ኪዳን ገብቶላታል።
★★★በገዳሙ እናታችን ድንጋይ ፈልፍላ የሰራችው ውሃ ማጠራቀሚያ አለ። በእናታችን የፈለቀ ፀበል ሲኖር እጅግ እጅግ ፈዋሽ የነፍስ የስጋ መድኃኒት ነው።
★ይህ ብቻ አይደለም ከስሩ በእናታችን የተተከለው ቄጤማ መሰል ተክል የስንቱን #መካን (መሀን) ማህፀን ፈትቶ ልጅ በልጅ አድርጓል
★በገዳሙ ውስጥ ያለው ሎሚ ደግሞ #የጨጓራ በሽታን ምንም ያህል የከፋ ቢሆን ለመጨረሻ ጊዜ ደህና ሰንብት ያስብላል።
★እናታችን ደጇ ለሄደ ብቻ ሳይሆን የገድሏን መፅሀፍ አዝሎ አምልክን ለተማፀነ ገድሏን አውርዳ ልጅ ታሳዝላለች።
★በገዳሟ ያለው ሌላኛው ሸንኮራ አገዳ ነው ይህ ታአምረኛ አገዳ ቢበሉት ደዌ ይፈውሳል አድርቀው ቢያጨሱት ቁራኛ መናፍስት ከቤት ያርቃል የመተት መናፍስትን ያስወግዳል።
★ገድሏ ካለበት አጋንንት አይደርስም፣ ደጇን የረገጠ አስራ ሁለት ትውልድ ይማርለታል፣ የገድሏን መፅሀፍ የፃፈ፣ ያፃፈ፣ የተረጎመ፣ በእምነት ሆኖ የሰማ ሀጢያቱ ይቅር ይባልለታል። ላይማር ደጇን አይረግጥም።
★★★በእውነት እጅግ የከበረች ፃድቅ ፅድቋ ለአለም የተረፈ፣ ሰማእት ስለ ክርስቶስ አንገቷን የሰጠች፣ ሀዋርያዊት መፅሀፍትን የፃፈች ያስተማረች ፣ ተአምረኛ ባህር የከፈለች በአንድ ቀን ዘርታ አጭዳ ጋግራ የመገበች ፣ መኖክሲት የመነኮሳት እናት የሆነች የእናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ፀሎቷ በረከቷ ረድኤቷ ይደርብን አሜን።★★★
የገዳሙ አድራሻ :— አማራ ክልል ሰሜን ወሎ (ፍላቂት) ገረገራ ከዛ ትንሽ የእግር መንገድ አለው።
@adbaratwegedamat




በዚኽች ዕለት የካቲት 29 ቀን በዓመታዊ የዕረፍት በዓሏ ታስባ የምትውለው እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ማኅበርተኞቿ የሆኑ ደናግል መነኮሳት ልጆቿ በእባብ መርዝ ምክንያት ሞቱ፡፡ እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስም የልጆቿን መሞት ባየች ጊዜ ወደ ልዑል እግዚአብሔር በዕንባ ጸለየች፡፡ ከዚህም በኃላ እነዚያ በእባብ መርዝ የሞቱ ልጆቿ በጸሎቷ ከሞቱ ተነሡ፡፡ እነርሱም በሰማይ ያዩትን የእናታቸውን የቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስን ክብርና የተዘጋጀላትን ርስት አይተው እንዳደነቁ ነገሯት፡፡ ሁላቸውም እራት አብረው ተመገቡ፡፡ በዚህም ጊዜ እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ እነዚያን በጸሎቷ ከሞት ያስነሣቻቸውን ልጆቿን "....ውዳሴ ከንቱ እንዳይሆንብኝ ይህንን ለሰው አትንገሩ" አለቻቸው፡፡ "ነገር ግን ከዕረፍቴ በኃላ ተናገሩ" አለቻቸው።"
+ + +

ዳግመኛም ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ይኽን ተአምር አደረገች፡- ኃጢአቷ የበዛ አንዲት ሴት ነበረች፤ ለበደሏም ወሰን የለውም፡፡ እርሷም ወደ እናታችን ወደ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ሔዳ በጸሎቷና በልመናዋ ተማጸነች፡፡ የሠራችው ኃጢአት ሕፃናትን በስራይ እንዳስወረደች 10 ጊዜም የተለያዩ ባሎቿን እንደገደለች ነገረቻት፡፡

በዚኽም ጊዜ እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ "... ኃጢአትሽን ለቀሲስ እከሌ ተናዘዥ" አለቻትና ስለ እርሷ ጸለየችላት፡፡ ኃጥእዋ ሴትም እናታችን እንዳዘዘቻት ሄዳ ኃጢአቷን ለካህን ተናዘዘች፡፡ በፍጹም ልቧም ንስሓ ገብታ በጾሞ በጸሎት ጸናች፡፡ እግዚአብሔርም ንስሓዋን ተቀብሎ ጸሎቷን ሰምቶ አንቺ ሴት ከዚህ በኃላ ኃጢአት አትስሪ ብሎ ተናገራት፡፡ ያቺም ሴት እግዚአብሔር ኃጢአቷን ይቅር እንዳላት ባየች ጊዜ ዕድሜ ዘመኗን በቀኖና አሳልፋ በሰላም ዐረፈች፡፡ አስማንድዮስ የተባለ ጋኔን በወለተ ራጉኤል ጭን ላይ አድሮ ባሎቿን እየገደለ ሲያሠቃያት ቅዱስ ሩፋኤል ጋኔኑን አስጨንቆ እንዳስወጣላት ሁሉ (ጦቢት 3፡8-17) ልዑል እግዚአብሔርም በቸርነቱና በምሕረቱ በቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስም ምልጃና ጸሎት ይቅር ብሏታልና መንግሥተ ሰማያትን አወረሳት፡፡
+ + +

ከዕለታት በአንደኛው ቀን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ በገዳማትና በተራራዎች መካከል ስትሄድ ከአንድ ሰው ቤት አደሩ፡፡ የዚያም ሰው አንዲት ሴት ልጅ ነበረችው፡፡ እርሷም በጠና ደዌ የታመመች ነበረች፡፡ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስም በልጅቷ ላይ በጸለየችላት ጊዜ ወዲያው ከደዌዋ ዳነች፡፡ የሀገሩ ሰዎችም ይህንን ተአምር ሲሰሙ ተሰበሰቡ፡፡ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ወንድ መስላቸው ነበርና ሰው ሁሉ ሥራዋን እንዳያውቁ ጃንደረባ መስላ ትኖር ዘንድ ወደ እግዚአብሔር እንደለመነች አላወቁምና፡፡

ከዚኽም በኋላ የሀገሩ ሰዎች ‹‹አባታችን እባክህ ከዚህ ተቀመጥ፣ ከዚህ ቦታ ተቀምጠህ ትጸልይልን ዘንድ ሕመምተኞችን ትፈውስልን ዘንድ…›› ብለው ተማጸኑ፡፡ በቤተ ክርስቲያንም አጠገብ ማረፊያ ሠሩ፡፡ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስም በዚያ ሆና ስትጸልይ ስፍር ቁጥር የሌላቸው የሌላቸው ብዙ ሕሙማንን በተአምራት በጸሎቷ ፈወሰች፡፡ ከሰው ብዛትና መጨናነቅ የተነሣ ቦታዋ በሰው ተሞልታ ነበር፡፡ የአገረ ገዥውም ሚስት መጥታ ‹‹አባቴ በጸሎትዎ አስቡኝ፣ አይርሱኝ…›› ብላ ብዙ ምሥጢር ነገረቻት፡፡ ከዚህም በኋላ አንዲትን ሴት ከእናታችን ወጥታ ስትሄድ አንድ ሰው በመንገድ አገኛትና በኃጢአት እንቅፋት ወደቁ፡፡ በዚህም ጊዜ ፀነሰች፤ ባሏም ፅንሷን አወቀና ከማን እንደፀነሰች አስጨንቆ ጠየቃት፡፡ ሴቲቱም ‹‹ይህ መነኩሴ ወደ እርሱ ዘንድ ኔድኩ ጊዜ አስገድዶ ደፈረኝና ፀነስኩ›› ብላ በእናታችን ላይ በሐሰት መሰከረች፡፡ በዚህም ጊዜ ባሏ በጣም ተናዶ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስን አሠራት፡፡ በግርፋትም ያሰቃያት ነበር፡፡ የሀገሩ ሰዎች ግን ይፈታት ዘንድ ይጠይቁት ነበር፡፡ በመጨረሻም ‹‹በቃ ልጁን ይዞ ይሂድ…›› ብለው ስለመከሩት ሰውየው ለቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ሕፃኗን ሰጥቶ አሰናበታት፡፡

እናታችንም ሕፃኗን በጥበብ ወተት አሳደገቻት፡፡ መዝሙረ ዳዊትንም እያስተማረቻት በጸሎት በጾም አሳገቻት፡፡ ልጅቱም ስታድግ መነኮሰች፡፡ ከዚህም በኋላ ያች ክፉ ሴት ማለት እናቷ በጸና ታመመች፡፡ እርሷም በታመመች ጊዜ እናታችንን ወንድ መስላት ስለነበር ‹‹..እርሱ ንጹሕ ነው ከእርሱ አይደለም ያረገዝኩት›› ብላ ተናገረች፡፡ ያ የደፈራት ሰው ግን በመብረቅ ሞተ፡፡ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስም ያሰሯትና የገረፏት ሰዎች በኋላ ላይ ሴት እንደሆነች ባወቁ ጊዜ እጅግ ተጸጽተው አለቀሱ፡፡ ከእግሯም ሥር ወድቀው ‹‹..ሳናውቅ አስቀይመንሻል ይቅር በይን›› ብለው ለመኗት፡፡ እናታችንም ይቅር አለቻቸው፡፡

በእናታችን ፍቅርተ ክርስቶስ ገዳም ውስጥ ዱባ በብዛት ይበቅል ነበር፡፡ ከፍሬውም ብዛት የተነሣ እርሷንና ሌሎቹንም ቅዱሳን ሁሉ ሌሊት ወደ ጸሎት ሲሄዱ የበሰበሰው ዱባ እንደ ጭቃ እያዳለጠ ይጥላቸው ነበር፡፡ እግራቸውንም ይውጣቸው ነበር፡፡ ያልበሰለውም ዱባ እንቅፋት እየሆነ ያሰነካክላቸው ነበር፡፡ ከዚህም በኋላ እናታችን ፍቅርተ ክርስቶስ ያን ዱባ ‹በዚህ ገዳም ውስጥ ብትበቅል እንጂ ፍሬ አትስጥ› ብላ አዘዘችው፡፡ ዱባውም ቃሏን አክብሮ እስካሁን ድረስ ቅጠሉ ቢዘረፈፍም፣ አበባው ቢያሳሳም፣ ሐረጉ ቢጎተትም፣ ዱባው ግን በገዳሙ ውስጥ ፈጽሞ ፍሬን አያፈራም፡፡ ከገዳሙ ውጭ ያሉ ሰዎች ግን ዱባውን እየተከሉ ፍሬም እያፈራላቸው ይጠቀሙበታል፡፡ በገዳሙ ክልል ውስጥ ፈጽሞ ፍሬን አያፈራም፡፡ ይኽም አባታችን አዳም እናታችን ሔዋን በንጽሕናና በቅድስና ሳሉ እንስሳትና ዕፅዋት ይታዘዙላቸው እንደነበር ሁሉ መድኀኔዓለም ክርስቶስ በሞቱ የአዳምንና የሔዋንን የቀድሞ ጸጋቸውን እንደመላቸው ያሳያል፡፡ የክብር ባለቤት ጌታችን ዓለምን በደሙ ካዳነ በኃላ ለቅዱሳኑ ዕፅዋትና እንስሳት መታዘዛቸው ለዚህ ነው፡፡
የእመ ምኡዟ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ባሕርን በአጽፏ ተሻግራ ወደ ሀገረ ናግራን አገር ሄዳ ወንጌልን የሰበከች ታላቅ ሐዋርያዊት እናታችን ናት፡፡ ለእርሷም እመቤታችን ተገልጣላት በጌታችን መከራ ሞት ምክንያት ስለደረሱባት ሀዘናት የነገረቻት፣ የፈለገችውንም ታደርግበት ዘንድ የእጇን መስቀል የሰጠቻት ሰሆን ሰውን ወደሚበሉ ሰዎች አገር ሄዳ ስንዴን በአንድ ቀን ብቻ ዘርታ፣ አብቅላ፣ አጭዳ፣ ፈጭታ ለምግብነት አብቅታ ከመገበቻቸው በኋላ እንደዚህ እያደረጉ እየሠሩ እንዲበሉ አስተምራ አስጠምቃቸው ስድስት አብያተ ክርስቲያናትን የሠራችላቸውና ቅዱስ ወንጌልን፣ ስንክሳርን፣ ሃይማኖተ አበውን፣ ግንዘትን፣ መዝሙረ ዳዊትን፣ አርጋኖንን ሁሉ በእጇ ጽፋ ያስቀመጠችላቸው ሐዋርያዊት እናታችን ስትሆን በሌላም በኩል ሙታንን እያስነሣች ለዐፄ ሱስንዮስ ስለእውነት እንዲመሰክሩለት ታደርግ የነበረችና እርሷም ራሷ አንገቷን ተሰይፋ ሰማዕትነትን የተቀበለችና ጌታችን ከሞት ያስነሣት ቅድስት ናት፡፡
ረድኤት በረከቷ ይደርብን በጸሎቷ ይማረን!
(ገድለ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ)

(ለ3ኛ ጊዜ በተከፈተው አዲስ ቻናል በኩልም በጽሑፍና በድምፅ ይከታተሉ።)
https://t.me/kegedilatandebet27217


መንፈሳዊ የርቀት ትምህርት የምዝገባ ገፅ በዓምደሃይማኖት ሰ/ት/ቤት ግቢ ገብርኤል ቤ/ክ dan repost
ምዝገባ የሚጠናቀቅበት ቀን እየደረሰ ነው !!!

እዚህ ላይ ስምና ስልክ ቁጥር ያስቀመጣቹ ሁሌም ከሰኞ -ቅዳሜ ከጠዋት 2:30 -ማታ 1:00 እንዲሁም እሁድ ጠዋት ከ 3:00- 6:00 ቢሮ ክፍት ስለሆነ አንድ ጉርድ ፎቶ ግራፍ እና ሁለት መፃህፍት የምትወስዱበት 400 ብር ይዛቹ በመምጣት ወይም ሰው በመላክ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን።

ኑ ስለ ሃይማኖታችን እንወቅ
ኑ በሃይማኖታችን እንፅና
ኑ ከራሳችን አልፈን ለሌሎቹ እንትረፍ !!!

ምዝገባ ተጠናቆ ትምህርቱ የሚጀምረው መጋቢት 7/07/17 ዓ.ም ነው ።

👉አሁን ላይ ርቀት ት/ርት ማዕከሉ ከአንድ ሺ በላይ ተማሪዎች ተቀብሎ እያስተማረ የሚገኝ ቢሆንም የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ተደራሽ ከማድረግና ምእመናንን ከማፅናት አንፃር ገና ብዙ ስለሚቀረን ለመማር ፍላጎት ያላቹ ቶሎ መጥታቹ እንድትመዘገቡ እንዲሁም ተመዝግባቹ እየተማራቹ ያላቹ እናንተ ያገኛቹትን ጥቅም ለሌሎቹ እንዲደርስ በመጋበዝ መንፈሳዊ ግዴታቹን እንድትወጡ በቅዱስ ገብርኤል ስም መልዕክታችን እያስተላለፍን ወቅቱ ደግሞ ለዚህ ምቹ ስለሆነ ተጠቀሙበት ።

ቦታ አራት ኪሎ ግቢ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም

ለበለጠ መረጃ 0953191919 /0921599344



👉ከሀገር ውጪ እና ክፍለ ሀገር ያላቹ (ከአዲስ አበባ ውጪ ያላቹ) በኦን ላይን መማር የምትፈልጉ በ 0937206240 ቴሌግራም ላይ በኦንላይ መማር እፈልጋለሁ የሚል አጭር መልዕክት አስቀምጡልን ስለ አመዘጋገቡ ሙሉ ማብራሪያ እንልክላቹሀለን።


🙏ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬ🙏 dan repost
    ዘላለም  ሥላሴ   

📣✝️  እንኩዋን ለአጋእዝተ ዓለም ሥላሴ  ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ  ✝️📣


❝ በሥላሴ ገመድ ፍጹም ታስረናል ፤ ከልባችን በማይነቀል በቅንዋተ ፍቅሩ ተቸንክረናል ፣ እርሱ ወዶናል አይጠላንም። እኛም በእምነት ይዘነዋል አንተወውም። ❞

     [  አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ  ]

❝ እምነታችንም እንዲህ በባሕርይ በመለኮት አንድ ፤ በአካል ፤ በገጽ ሦስት ብለን ነው፡፡ እነዚህ በቅድምና የነበሩ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ ናቸው፡፡ አስቀድመን መላልሰን እንደ ተናገርን ቀዳማዊ ወልድ ሰው ስለ መሆኑና ስለ ቅድስት ሥላሴ የምናምነው እምነት ይህ ነው ፤ ከተማሩ ከሚያስተምሩ ተስፋን ከሚያስረዱ ቅዱሳን ሊቃውንት ለምዕመናን ሁሉ ገልጠን የምናስተምረው ፤ እውነተኛ ሃይማኖትን ከሚያስተምሩ የሰማይ አምላክ ከሾማቸው ከሐዋርያትም ሲያያዝ የመጣልን እጅ ያደረግነው እምነት ነው፡፡ በንጹሕ ልቡና በአፋችንም በልባችንም በዚህ ሃይማኖት እንመን ፤ ያለ ጥርጥርም በበጎ ግብር በቅን ሕሊና እናስተውል ፤ በዚህ እንድንድን መንግሥተ ሰማያትንም እንድንወርስ እንረዳለን፡፡ ❞


  
🗓 ሃይማኖተ አበው  🗓


ጥር ፯ [ 7 ]

ሕንጻ ሰናዖርን ማፍረሳቸውና ቅዳሴ ቤታቸው በዓል ይከበራል።

የሰናዖርን ሕንጻ ያፈረሱ ሥላሴ : የኃጢአታችንን ሕንጻም በቸርነታቸው ያፍርሱልን አሜን በእውነት !


✝️ለባለ ማህተቦች✝️ሼር ያድርጉ↗️

✨✨✨✨✨✨✨
✝️#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ✝️
✨✨✨✨✨✨✨


🎤✨ድምፀ ተዋህዶ✨🎤 dan repost
#ድምፅ_መስጠት_ተጀመረ!

#አንቴክስ_ፉድ_ኤይድ_ፕላስ ባዘጋጀው BIWs prize ብፁዕ አቡነ ኤርምያስን የሰላም ዘርፍ እጩ ተሸላሚ አድርጓቸዋል።

ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ በሰላም ዘርፍ ከአምስት እጩዎች ውስጥ ተክትተዋል የዘርፉ አሸናፊ ከሆኑ #10ሚሊየን ብር ይሸለማሉ!!!

ብፁዕነታቸውን BIWን በማስቀደም ኮድ08 (BIW08) በማስገባት በSMS 9355 ላይ አሁኑኑ ይምረጡ!!! 

ድምጽ መስጠቱ እስከ ሐሙስ ታህሳስ 17/2017 ዓም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ ይካሄዳል!

በSMS 9355 ላይ BIW08 በማለት ብፁዕነታቸውን አሁኑኑ  ይምረጡ!!!

#10ሚልዮን #አንቴክስ #ፉድኤይድፕላስ #biwsprize #BTM #ብፁዕአቡነኤርምያስ  #ይምረጡ

Vote Abune Ermias now for the BIWs prize!

#AbuneErmias
#10million #BIWS2024 #Prize  #ANTEXETHIOPIA  #ANTEXTEXTILE  #FOODAIDPLUS #BESHATUTOLEMARIAMMULTIMEDIA


🙏ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬ🙏 dan repost
🗓🌴
ከአንድ የሾላ ዛፍ ሥር ስትቃርም የነበረችን አይጥ ከነነፍሷ ለመያዝ ከወደሰማይ የነበረው አሞራ ቁልቁል ተምዘግዝጎ ይወርዳል። ሙከራው ለጥቂት በሚባል ሁኔታ ተሳክቶ የአይጧን ጭራ ይይዛል።

: አካሏ ግን ከዛፋ ሥር ካለ ጉድጓድ ገብቶ በልቀቀኝ ዐይነት መታገል ጀምራለች ጉልበቷን ያልተማመነችው አይጥ አሞራውን ለማጃጃል ጥበብ የተሟላ ንግግሯን ተጠቀመች።

: በዚህ መሰረት "አያ አሞራ! የእኔን ጭራ የያዝክ መስሎህ ከሾላው ሥር ጋር ስትታገል መንቁርህ እንዳይሰበር። ይልቅስ የሾላውን ሥር ልቀቅ አትልፉ"አለችው።

:  ቂላቂሉ አሞራም የያዛትን የአይጥ ጭራ ለቀቀ ይባላል

🦅🦅🦅🦅🦅🦅🦅🦅🦅🦅🦅
🇺🇿🇺🇿🇺🇿🇺🇿🇺🇿🇺🇿🇺🇿🇺🇿🇺🇿
እኛ ክርስቲያኖች ብልህ ልንሆን ይገባል ጠላት ዲያቢሎስ ሊያጠቃን ሲያደባ የአባቶችን ጥበብ በመጠቀም ልናመልጥ ይገባናል
❤️❤️❤️❤️❤️❤️❤️
የጥበብ አምላክ እግዚአብሔር ማስተዋልና ጥበቡን ያድለን


ለባለ✝️ ማህተቦች ሼር ያድርጉ⁉️
📣📣📣📣📣📣📣
#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ
📣📣📣📣📣📣📣


🙏ኦርቶዶክሳዊ ዝማሬ🙏 dan repost
🗓ዛሬ ማለትም
#ዕለት:- ማክሰኞ
#ቀን:- ታኅሣሥ ፰ ፳፻፲፯ ዓ.ም

በቅድስት ቤተክርስቲያናችን


አርባዕቱ እንሰሳ(ኪሩቢል) ፣ ሊቀ ነቢያት ፣ ሐዋርያዉ ማትያስ ፣ ካህኑ ዘካርያስ ፣ አባ ኪሮስ ፣ ቅድስት አመተ ክርስቶስ

አክብረን እና አስበን እንውላለን።

📣📣📣
✔️ የጻድቅ መታሰቢያ ለበረከት ነው። ምሳ ፲፤፯

✔️  መታሰቢያ ለዘለዓለም ይኖራል መዝ.፻፳፮፥፮


✔️ "ቅዱሳን በዓለም ላይ እንዲፈርዱ አታውቁምን? ፩ኛ ቆሮ ፮:፪
የመላዕክት ፣ የቅዱሳን ፣ የሰማዕታት ተራዳይነት እና በረከት ከሁላችንም ጋር ይሁን

📣📣📣📣📣📣📣
📣#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ📣
📣📣📣📣📣📣📣


🗓#በዙሪያችን_ካሉ

በዙሪያችን ካሉ ድንቅ ምስክሮች
በእምነት በምግባር ከፀኑት እናቶች
ከፍ ብላ ታየች በገድሏ ብዛት
ንዕድ ክብርት ነች አርሴማ ቅድስት/2/


ሀብትና ንብረቷን ውበቷን የናቀች
ንግስት መባልን በእምነት የተወች
የኢየሱስ ክርስቶስ የስሙ ምስክር
የቅድስት አርሴማ ልዩ ነው የሷ ክብር
/2/
#አዝ
እግዚአብሄር ፅናቷን የመሰከረላት
በቤቱ በቅፅሩ መታሰቢያ አላት
የወንጌሉን ብርሀን ለዓለም ያበራች
ሰማዕቷ አርሴማ ለኛ አማላጅ ነች/2/
#አዝ

ይሔው በዚ ዘመን እግዚአብሄር ገለጣት
ለረድኤት በረከት ምክንያት አደረጋት
አክሊል ተጎናጽፋ ታይታለች በክብር
ዛሬም ለልጆቿ በረከቷ ይደር/2
/
#አዝ
እንደተናገረው ጌታችን በቃሉ
በእኔ የሚያምኑ ድንቅን ይሰራሉ
ደዌ እንዲርቅለት ፈውስን የተጠማ
ከደጇ ላይ ይውደቅ ይበላት አርሴማ/2/

           ሊቀ-መዘምራን
     ዲያቆን ቴዎድሮስ ዮሴፍ
📣📣📣📣📣📣📣
📣#ኦርቶዶክሳዊ_ዝማሬ📣
📣📣📣📣📣📣📣



20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.