Postlar filtri




#የፍርድ ባለመብትና የፍርድ ባለዕዳ በማንኛውም ጊዜ ተስማምተው ጉዳያቸውን #በእርቅ መጨረስ እንደሚችሉ እና በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ.427 የአማርኛ ቅጂው #ገዢ ሰለመሆኑ የተወሰነ አሰተማሪ የአፈጻጸም ውሳኔ


#አፈፃፀም ለአፈፃፀሙ መነሻ የሆነውን መሰረታዊ ፍርድ/ውሳኔ የሚከተል በመሆኑ አፈፃፀሙን የሚመራው ፍርድ ቤት ፍርዱን የሚያስፈፅመው በስነስርዓት ህጉ በተዘረጋው ስርዓት መሰረት እንደ ፍርዱ ይዘትና መንፈስ ውጤት ባለው መልኩ ሊሆን ይገባል፡፡(የፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ.372፤378፤392(1) ድንጋጌዎችን መረዳት ይቻላል

በመሰረቱ የሀራጅ ሽያጭ ስለሚቆምበት ወይም ስለሚቋረጥበት ሁኔታ በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ.427 የተመለከተ ሲሆን የዚህ ድንጋጌ አማርኛ እና እንግሉዘኛ ቅጂ ልዩነት ያለው ሲሆን በአማርኛው ቅጂ መሰረት የሀራጅ ሽያጩ የሚቆመው የሀራጅ ማስታወቂያ ከመውጣቱ በፊት የፍርድ ባለዕዳው የተፈረደበትን ገንዘብ ወጪና ኪሳራውን ጨምሮ ለሀራጅ ሻጩ አልያም ሽያጩን ላዘዘው ፍርድ ያስረከበ መሆኑ ሲረጋገጥ መሆኑን የሚያሳይ ሲሆን እንግሉዘኛው ቅጂ ደግሞ የሀራጁ ሽያጭ የሚቆመው ሀራጅ ባዩ የጨረታውን ከፍተኛ ዋጋ ከመግለፁና ጨረታውን ከማቆሙ በፊት በማናቸውም ጊዜ የፍርድ ባለዕዳው የተፈረደበትን ገንዘብ ወጪና ኪሳራውን ጨምሮ ለሀራጅ ሻጩ አልያም ሽያጩን ላዘዘው ፍርድ ያስረከበ መሆኑ ሲረጋገጥ መሆኑን“…before the lot is knocked down…” የሚለውን ሀረግ በመጠቀም ለፍርድ ባለዕዳው የሰፋ የመክፈያ ጊዜ የሰጠ መሆኑን ከድንጋጌው ይዘት ለመረዳት ይቻላል ከሁለቱ ቅጂዎች የአማርኛ ቅጂው ገዢ በመሆኑ
#ለፍርድ ባለዕዳው የመጨረሻ የእዳው መክፈያ ጊዜ የሀራጅ ማስታወቂያ ከመውጣቱ በፊት ያለው ጊዜ ተደርጎ የሚወሰድ ሲሆን ይህ በሌላ አኳኋን እንዲፈፀም ካልታዘዘ በቀር ማናቸውም ሀብት ወይም ንብረት የሚሸጠው የሽያጭ ስርዓት እንዲያስፈፅም ፍርድ ቤቱ በተለይ ባዘዘው ሰው አማካኝነት ወይም በፍርድ ቤቱ ሰራተኛ አማካኝነት ግልፅ የሀራጅ ሽያጭ በማድረግ መሆኑ በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ.422(2) መመልከቱ
#በተለይም “በሌላ አኳኋን እንዲፈፀም ካታዘዘ በቀር…” በሚል የተከተው የህጉ ሀረግ እንዲሁም በፍርድ አፈፃፀም ምክንያት በሀራጅ እንዲሸጥ የተወሰነውን ንብረት ፍርድ ቤቱ በግል ወይም በስምምነት እንዲሸጥ ትዕዛዝ ለመስጠት የሚችል መሆኑ በፍ/ብ/ስ/ስ/ህቁ.422(2) መመልከቱ የሀራጅ ሽያጭ የአፈጻጸም ሂደት ፍርዱን ለማስፈጸም የተቀመጠ የመጨረሻ አማራጭ መሆኑን የሚያሳዩ በመሆናቸው በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ.427 የተመለከተው ድንጋጌ አፈፃፀምም ከዚሁ ድንጋጌ አግባብነት አንፃር ሊቃኝ የሚገባው መሆኑን ያሳያል፡፡
# የፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ.427 የፍርድ ባለዕዳው የተፈረደበትን ገንዘብ ኪሳራውንና ወጪውን በሙለ መክፈለን ማረጋገጡን የሀራጅ ሽያጩን ለማስቆም መስፈርት አድርጎ ማስቀመጡ ድንጋጌው በአንድ ፍርድ ከንብረት ክፍፍል ጋር በተያያዘ ሁለቱም ወገኖች ባለመብት የሆኑ ወገኖችን የንብረት ክፍፍል ሂደት ለመምራት ከተቀመጠ የአፈፃፀም ድንጋጌ ይልቅ የፍርድ ባመብት በፍርድ ባለዕዳውበፍርድ የተጎናፀፈውን መብት የተለያዩ ምክንያቶችን በመፍጠር አፈፃፀሙን ከሚያደናቅፈው የፍርድ ባለዕዳ ለመጠበቅ የተቀመጠ ጥብቅ ድንጋጌ መሆኑን እያሳየ፤ከንብረት ክፍፍል ጋር በተያያዘ በግልጽ ሀራጅ ሽያጭ ክፍፍለን ማስፈፀም የመጨረሻ አማራጭ መሆኑን ለግራ ቀኙ መብትን ካጎናጸፈው ውሳኔ እና ከፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ.422 ድንጋጌ ለመረዳ ይቻላል👇👇👇
https://t.me/ethiolawtips


በፍ/ብ/ህግ ቁጥር 2472(1/2) ላይ እንደተደነገገዉ #ከብር 500 በላይ የሆነ የገንዘብ ብድር ዉል መኖሩን ማስረዳት የሚቻለዉ #በጽሁፍ ወይም #በፍርድ ቤት በተደረገ የእምነት ቃል ወይም #በመሃላ ካልሆነ በቀር በሌላ ማስረዳት አይቻልም፡፡
#የብድር ገንዘቡ ስለመከፈሉም ማስረዳት የሚቻለዉ በዚሁ አግባብ ብቻ ስለመሆኑ የዚሁ ድንጋጌ ንኡስ ቁጥር ሶስት ይዘት ያሳያል፡፡ሰበር መ/ቁ/205008 ሐምሌ 20 ቀን 2014 ዓ.ም👇
https://t.me/ethiolawtips


የማይንቀሳቀስ ንብረት ይዞታ ማረጋገጫ ካርታ
በማቅረብ ብቻ የሚረጋገጥ አይደለም የሰ/መ/ቁ.
229608

በፍ/ብ/ስ/ስ/ህ/ቁ 33(2) መሰረት ከሳሽ ባቀረበው ክስ ላይ
መብትና ጥቅም የለውም ተብሎ የሚወሰነው ክስ ባቀረበበት
ጉዳይ ላይ መብት ያለው ስለመሆኑ ማስረጃ ሳያቀርብ ሲቀር ነው፡፡አመልካች በስር ፍ/ቤት ክስ ባቀረበበት ንብረት ላይ መብትና ጥቅም ያለው ስለመሆኑ የተለያዩማስረጃዎችን (በሰበር አቤቱታው ላይ የተዘረዘሩ) ከክሱ ጋር አያይዞ አቅርቦ ሳለ የስር ፍ/ቤቱ አመልካች ክሱን ለማቅረብ መብትና ጥቅም የለውም በማለት ክሱን ውድቅ በማድረግ የሰጠው ብይን እና ይግባኝ ሰሚው ፍ/ቤት የሰጠው ትእዛዝ መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ነው፡፡ የስር ፍ/ቤት መብትና ጥቅም የማይንቀሳቀስ ንብረት ይዞታ ማረጋገጫ ካርታ በማቅረብ ብቻ እንደሚረጋገጥ አድርጎ ብይን የሰጠ ሲሆን ይህም የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በሰ.መ.ቁ 36320(ቅጽ 9) በማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ ክስ ለማቅረብ የይዞታ ማረጋገጫ ካርታ ማቅረብ ግዴታ አለመሆኑን እና ባለይዞታነት በሌላ መንገድ ሊረጋገጥ እንደሚችል ከሰጠው አስገዳጅ የህግ ትርጉም ውጪ በመሆኑ መሰረታዊ የሆነ የህግ ስህተት የተፈጸመበት ነው።👇👇.
https://t.me/ethiolawtips


በጋብቻ ውስጥ የተፈራ ንብረት የክፍፍል ጥያቄ ጋብቻው ከፈረሰበት ቀን ጀምሮ በ10 ዓመት ውስጥ ካልቀረበ በይርጋ ይታገዳል የሚል ትርጉም መስጠት የተፋቾችን ሕገ መንግሥታዊ የንብረት መብት የሚጥስ ስለሆነ በሕገ መንግሥቱ አንቀጽ 40(1፣ 7)፣ 50(5)፣ 55፣ 79(1)፣ እና 9(1) መሠረት ተፈጻሚነት የለውም::
ፌደሬሽን ም/ቤት መ/ቁ. 77/12 (ሰኔ 3/2012 ዓ.ም.)👇👇
https://t.me/ethiolawtips

2k 0 72 1 19

ዋስትና ላይ የተሰጠ ትርጉም (1).pdf
615.1Kb
ሰ/መ/ቁ 233903 ጥቅም 08 ቀን 2015 ዓ.ም
በወንጀል ጉዳይ ተከሳሽ የመኖሪያ አድራሻው ሌላ ቦታ መሆኑ እንዲሁም የስራ ሁኔታው ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ የሚያንቀሳቅሰው መሆኑ በሚል የዋስትና መብቱ ሊያጣ አይገባም።
በመዝገቡ ላይ የችሎቱ ሐተታ እንደሚከተለው ይነበባል።
“በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ሕገመንግስት አንቀጽ 32 ለማንኛውም ኢትዮጲያዊ ከተረጋገጠው የመዘዋወር መብት አኳያ አመልካቾች በሐገሪቱ አካባቢ የመዘዋወር እና የመኖሪያ ቦታ የመመስረት መብት አላቸው ፡፡ ስለሆነም አመልካቾች የሌላ ቦታ ነዋሪ መሆናቸው ብቻውን በሕገ መንግስቱ አንቀፅ 19 ንዑስ አንቀፅ 6 የተረጋገጠላቸው በዋስ የመልቀቅ መብት እንዲነፈግ የማድረግ እና በሕገ መንግስቱ አንቀፅ 25 የተደነገገውን በሕግ ፊት እኩል የመሆንና እኩል የሕግ ጥበቃ የማግኘት መብትን የሚጥስ በመሆኑ ተቀባይነት ያለው ምክንያት አይደለም፡፡”
Join👇
https://t.me/ethiolawtips




ክርክር ተደርጎ ዉሳኔ ከተሰጠ በኋላ በፍ/ብ/ስ/ስ ህግ ቁጥር #358 መሰረት ያቀረበችዉ መቃወሚያ #ክርክር መኖሩን #አታዉቅም ነበር ለማለት ጣልቃ ገብታ መከራከር ሲትችል ከቅን ልቦና ዉጪ ዉጤቱን ጠብቃ ያቀረበችዉ አቤቱታ ነዉ የሚለዉን ለመወሰን በእርግጥም የመቃወም አመልካች ቀደም ሲል ክርክር ሲደረግ የነበረ መሆኑን ክርክሩም የእሷን መብት የሚመለከት መሆኑን ታዉቅ እንደነበር መረጋገጥ ያለበት ፍሬነገር ጉዳይ ነዉ

#በክርክሩ ተካፋይ ያልሆነ ወገን ባልተሳተፈበት ክርክር ተድርጎ መብቱን የሚነካ ፍርድ መሰጠቱን ባወቀ ጊዜ ፍርዱን በመቃወም መብቱን ማስከበር እንደሚችል በፍ/ብ/ስ/ስ/ህግ 358 ላይ ተደንግጓል፡፡ይሁንና ይህንን መብት በመጠቀም ረገድ ክርክሩ መኖሩን እያወቀ በቸልተኝነቱ ወይም በእሱ ጉድለት የክርክሩ ተካፋይ ሳይሆን የቀረ ወገን ከቅን ልቦና ዉጪ ጉዳዩን ለማጓተት የሚያቀርበዉ መቃወሚያ ተቀባይነት ሊኖረዉ እንዳማይገባ ሰበር ችሎቱ ገዥ ዉሳኔ የሰጠበት መሆኑ ይታወቃል(ሰበር መ/ቁ/56795፣40229፣93987 እና ሌሎች መሰል መዝገቦችን ይመለከታል)፡፡
#ተከሳሽ ባልና ሚስት ሆነዉ አይነጋገሩም ወይም ክርክሩን አያዉቁም ተብሎ አይገመትም የሚል (መነሻ) ያለማስረጃ ሊገመት አይገባም።



9 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.