Postlar filtri


ከወንጀሉ ክብድትና ቅጣት አንፃር ተከሳሹ ዋስትና መብቱ ቢጠበቅ ተመልሶ የሚመጣ አይመስለኝም በማለት በወ/ሰ/ሰ/ህ/ቁ 67(ሀ) መሰረት የዋስትና ግዴታውን አያከብርም በሚል ጥያቄ ላይ ሰበር በቂና ምክንያታዊ ህጋዊ ማስረጃ ሳይቀርብ ከወንጀሉ ክብደት ብቻ በመነሳት ዋስትናው ሊገደብ አይገባም በማለት አስገዳጅ የህግ ትርጉም
በወ/ስ/ስ/ህ/ቁ 67(ሀ) ሰ/መ/ቁ 269430 በቀን 29/02/2017 ዓም ሰጥቷል
https://t.me/ethiolawtips


የነበረን ቤት ባለበትም ሆነ አፍርሶም ማደስ ከፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 1179 ድንጋጌ አንፃር አንድ ሰው በሌላ ሰው ይዞታ ላይ ባለይዞታው ሳይቃወም ቤት ቢሰራ የተሰራው ቤት ባለቤት እንደሚሆን ከተደነገገው ጋር የሚገናኝ አይደለም።ስለዚህ ቤቱን አፍርሶ ስለሰራ ወይም አድሶ ስለሰራ ባለይዞታ ሳይቃወም አፍርሼ የሰራሁት ወይም ያደስኩት ቤት በመሆኑ የቤቱ ባለቤት ነኝ ለማለት አይቻልም።ሲል የፌ/ሰ/ሰ/ፍ/ቤት በሰ/መ/ቁ 222277 አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሰጥቷል።
👇👇??🔥
https://t.me/ethiolawtips


https://t.me/ethiolawtips
🔥ጋብቻ ሳይፈርስ ንብረትን በፍርድ ቤት ማከፋፈል ስለመቻሉ
  🔥ከተጠየቀው ዳኝነት በተጨማሪ ፍርድ ቤቶች ሊወስኑ ስለሚችሉበት ሁኔታ
🔥በጋብቻ ላይ ጋብቻ ፈጽመው ስለሚኖሩ ተጋቢዎች
🔥 ንብረት አስተዳደርን በተመለከተ እና ድርሻቸውን እንዴት መለየት እንደሚቻል ከንብረት ማፍራት መብት አንፃር  የፌዴሬሽን ምክር ቤት የሕገመንግስት ትርጉም አያሰፈልገውም በማለት የወሰነው ውሳኔ ነው።


አንድ ሰው የወራሽነት የምስክር ወረቀት የያዘ ቢሆንም ንብረቱን ይዞ እስካልተጠቀመ ድረስ የውርስ ንብረቱን በያዘው ሰው ላይ የሚያቀርበው ክስ በፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 1000/1/ መሰረት በ3 ዓመት ይርጋ ቀሪ ነው።
የወራሽነት ጥያቄ የጊዜ ገደብ የለውም በሚል ከዚህ በፊት የተሰጡ የሰበር ውሳኔዎችን በመለወጥ በ7 ዳኞች የተሰጠ አዲስ የህግ ትርጉም። የሰ/መ/ቁ 243973 ጥቅምት 06/ 2017 ዓ.ም

የወራሽነት የምስክር ወረቀት የያዘ ሰው በማንኛውም ጊዜ የውርስ ንብረት ጥያቄ ማንሳት ይችላል በማለት ከአሁን በፊት በሰ/መ/ቁ 205248 44237 ቅፅ(10) 38533 ቅፅ(10) ወዘተ.. የተሰጡ የሰበር ውሳኔዎች በዚህ የሰበር ውሳኔ ተለውጠዋል።
https://t.me/ethiolawtips
ጠበቃ👇
+251911954039

2.6k 0 110 2 31

ክስ ቀርቦብኝ ከዚህ ቀደም ጉዳዩ በእርቅ ስምምነት መዝገቡ ተዘግቶ ነበር የሚለው መከራከሪያ በመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያነት ባይነሳም በፍሬ ነገር ክርክር ላይ በእርቅ ስምምነት መዝገቡ ስለመዘጋቱ መከራከሪያ እስከተነሳ ድረስ ፍ/ቤቱ እንደ መጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ ወስዶ በቅድሚያ እልባት ሊሰጠው የሚገባ እና ፍ/ቤቱ እንደመጀመሪያ ደረጃ መቃወሚያ አስቀድሞ ሊመለከተው የሚገባ ስለመሆኑ የፌደራል ሰበር ሰሚ ፍ/ቤት በሰ/መ/ቁ 222041 ጥቅምት 15 ቀን 2015 የተሰጠ አስገዳጅ የህግ ትርጉም👇
https://t.me/ethiolawtips



6 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.