Postlar filtri


በሕጋዊ ይዞታ ላይ የተፈጠረ የሁከት ድርጊት እንዲወገድ በቀረብ ክስ ላይ ጣልቃገቦች ከሁከቱ ወጭ አዲስ የዳኝነት ክርክር ማቅርብ የማይችሉ እና እራሱን ችለው መክሰሰ የሚገባ ሰለመሆኑ የተወሰነ
====================
በሕጋዊ ይዞታ ላይ የተፈጠረ የሁከት ድርጊት እንዲወገድ ባቀረበው ክስ ላይ መውጫ ተዘግቶብናል በማለት ያቀረቡት የጣልቃገብነት ክርክር አብሮ ተስተናግድ የአመልካችን ክስ ውድቅ መደረጉ ተገቢ አለመሆኑ ።በመሠረቱ በፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1149 መሠረት ሁከት እንዲወገድ እና መውጫ መግቢያ ተከልክለናል በማለት የሚቀርበው ክስ ደግሞ በቀጥታ የሚመለከተው የንብረት አገልግሎት ስለመሆኑ ከፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1221 ድንጋጌ ይዘት መገንዘብ ይቻላል።
👇👇
https://t.me/ethiolawtips


ከወንጀሉ ክብድትና ቅጣት አንፃር ተከሳሹ ዋስትና መብቱ ቢጠበቅ ተመልሶ የሚመጣ አይመስለኝም በማለት በወ/ሰ/ሰ/ህ/ቁ 67(ሀ) መሰረት የዋስትና ግዴታውን አያከብርም በሚል ጥያቄ ላይ ሰበር በቂና ምክንያታዊ ህጋዊ ማስረጃ ሳይቀርብ ከወንጀሉ ክብደት ብቻ በመነሳት ዋስትናው ሊገደብ አይገባም በማለት አስገዳጅ የህግ ትርጉም
በወ/ስ/ስ/ህ/ቁ 67(ሀ) ሰ/መ/ቁ 269430 በቀን 29/02/2017 ዓም ሰጥቷል
https://t.me/ethiolawtips


የነበረን ቤት ባለበትም ሆነ አፍርሶም ማደስ ከፍ/ሥ/ሥ/ሕ/ቁ 1179 ድንጋጌ አንፃር አንድ ሰው በሌላ ሰው ይዞታ ላይ ባለይዞታው ሳይቃወም ቤት ቢሰራ የተሰራው ቤት ባለቤት እንደሚሆን ከተደነገገው ጋር የሚገናኝ አይደለም።ስለዚህ ቤቱን አፍርሶ ስለሰራ ወይም አድሶ ስለሰራ ባለይዞታ ሳይቃወም አፍርሼ የሰራሁት ወይም ያደስኩት ቤት በመሆኑ የቤቱ ባለቤት ነኝ ለማለት አይቻልም።ሲል የፌ/ሰ/ሰ/ፍ/ቤት በሰ/መ/ቁ 222277 አስገዳጅ የህግ ትርጉም ሰጥቷል።
👇👇??🔥
https://t.me/ethiolawtips


https://t.me/ethiolawtips
🔥ጋብቻ ሳይፈርስ ንብረትን በፍርድ ቤት ማከፋፈል ስለመቻሉ
  🔥ከተጠየቀው ዳኝነት በተጨማሪ ፍርድ ቤቶች ሊወስኑ ስለሚችሉበት ሁኔታ
🔥በጋብቻ ላይ ጋብቻ ፈጽመው ስለሚኖሩ ተጋቢዎች
🔥 ንብረት አስተዳደርን በተመለከተ እና ድርሻቸውን እንዴት መለየት እንደሚቻል ከንብረት ማፍራት መብት አንፃር  የፌዴሬሽን ምክር ቤት የሕገመንግስት ትርጉም አያሰፈልገውም በማለት የወሰነው ውሳኔ ነው።


አንድ ሰው የወራሽነት የምስክር ወረቀት የያዘ ቢሆንም ንብረቱን ይዞ እስካልተጠቀመ ድረስ የውርስ ንብረቱን በያዘው ሰው ላይ የሚያቀርበው ክስ በፍ/ብ/ሕ/ቁጥር 1000/1/ መሰረት በ3 ዓመት ይርጋ ቀሪ ነው።
የወራሽነት ጥያቄ የጊዜ ገደብ የለውም በሚል ከዚህ በፊት የተሰጡ የሰበር ውሳኔዎችን በመለወጥ በ7 ዳኞች የተሰጠ አዲስ የህግ ትርጉም። የሰ/መ/ቁ 243973 ጥቅምት 06/ 2017 ዓ.ም

የወራሽነት የምስክር ወረቀት የያዘ ሰው በማንኛውም ጊዜ የውርስ ንብረት ጥያቄ ማንሳት ይችላል በማለት ከአሁን በፊት በሰ/መ/ቁ 205248 44237 ቅፅ(10) 38533 ቅፅ(10) ወዘተ.. የተሰጡ የሰበር ውሳኔዎች በዚህ የሰበር ውሳኔ ተለውጠዋል።
https://t.me/ethiolawtips
ጠበቃ👇
+251911954039

3k 0 122 2 34


6 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.