በማሌዥያ የአልጋ ቁራኛ የሆነውን ባለቤቷን ለስድስት ዓመታት ስታስታምም የነበረችው ግለሰብ ከበሽታው ካገገመ በኋላ ሌላ ትዳር መሰረተ
በደረሰበት የተሽከርካሪ አደጋ ለስድስት አመታት የአልጋ ቁራኛ የሆነውን ባሏን የተንከባከበችው ማሌዥያዊት ሴት ባሏ ከበሽታው ካገገመ በኃላ ሌላ ሴት ማግባቷን በቅርቡ አስታውቃለች።
ለዓመታት ኑሩል ስያዝዋኒ የዕለት ተዕለት ህይወቷ የባለቤቷ ጠባቂ በመሆን የምታሳልፈውን ጊዜ በማህበራዊ ድህረ-ገፆች ላይ በማሳየት ስራ የበዛበት ተግባሯን አጋርተች። ይህም ባለቤቷ ምግብ በእጁ ጎርሶ ስለማይወርድለት በናሶጋስቲክ ቱቦ መመገብ፣ ዳይፐር መቀየር እና እንዲታጠብ መርዳት የእርሷ የእለት ከእለት ስራ ነበር። የኑሩል ባል የመኪና አደጋ ከደረሰበት በኃላ እንደገና ለመራመድ ስድስት አመታት መጠበቅ የግድ ብሎት የነበረ ሲሆን በነዚህ ዓመታት ሁሉ ግን እሷ ከጎኑ ነበረች።
ለባሏ ያሳየችው ትጋት እና ታታሪ አገልግሎት በፌስቡክ ላይ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ትኩረት የሳበ ሲሆን ብዙዎቹ የኑሩል ሲያዝዋኒ ባል ካገገመ በኋላ ፈትቷታል፤ ይህም ብቻ ሳይሆን ሌላ ሴት ማግባቱን ሲሰሙ ደንግጠዋል። የእብደት ድርጊት ሲሉ በርካቶች የተደመጡ ሲሆን ኑሩል በፌስቡክ ገጿ የቀድሞ ባለቤቷን እና አዲሲቷን ሙሽሪት እንኳን ደስ አላችሁ ብላለች።ለባለቤቴ እንኳን ደስ አለህ ፤ በመረጥከው ህይወት ደስተኛ እንደሆንክ ተስፋ አደርጋለሁ። አዲሲቱ ሚስቱ አይፋ አይዛም እባካሽ ልክ እንደ እኔ ተንከባከቢው ፤አሁን ተራው የአንቺ ነው ስትል ኑሩል መልዕክቷን አጋርታለች። በጥቅምት 4 መጠናቀቁ የተነገረለት የኑሩል የፍቺ ዜና የማሌዢያን የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎችን ማስደንገጡን ዳጉ ጆርናል ተመልክቷል።
በርካታ ተጠቃሚዎች ደግነቷን ሊከፍላት ይችላል የሚለውን አባባል መቀበል አቅቷቸዋል። በህመሙ ወቅት ከባድ ጊዜን አሳልፌያለሁ በየቀኑ እንዲያገግም እረዳው ነበር፣ ቤተሰቦቼ በየቀኑ ሊረዱኝ ይመጡ ነበር፣ ለልጆቼና ለባለቤቴ የሚያስፈልጉትን ነገሮች ብቻዬን ሳሟላ ቆይቻለሁ ስትል ተደምጣለች።ሆኖም ኑሩል የቀድሞ ባለቤቷ “ኃላፊነቱን በሚገባ እንደተወጣ” እንደሚሰማት ጠቁማ ሰዎች እሱን እና አዲሷን ሚስቱን ማስጨነቅ እንዲያቆሙ ጠይቃለች ። ሆኖም ደጋፊዎቿ በሀሳቧ አልተስማሙም። አንድ ሰው በሰነዘረው አስተያየት “እንዴት እንዲህ ያለው ምስጋና አልባ ሰው ሊኖር ይችላል? ልብ ያለው አይመስለኝም ሲል መደመጡን ዳጉ ጆርናል ዘግቧል።
የቀድሞ ባሏን እና አዲሲቱን ሚስቱን ከብዙሃኑ ትችት ለማዳን ስትል ኑሩል ሲያዝዋኒ በፌስቡክ ላይ የደረሰባትን ያሰፈረችውን ፅሁፏን በማጥፋት ሰዎች ለተፈጠረው ነገር የቀድሞ ባሏን መወንጀል እንዲያቆሙ ደጋፊዎቿን ጠይቃለች።የቀድሞ ባለቤቴን፣ አዲሲቱን ሚስቱን እና ቤተሰቦቻቸውን በፌስ ቡክ ላይ ባጋራሁት መልዕከት ለደረሰባቸው ትችት ይቅርታ መጠየቅ እፈልጋለሁ። የሆነው ሁሉ የእኔ ስህተት ነበር ሲል ኑሩል ጽፋለች።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
በደረሰበት የተሽከርካሪ አደጋ ለስድስት አመታት የአልጋ ቁራኛ የሆነውን ባሏን የተንከባከበችው ማሌዥያዊት ሴት ባሏ ከበሽታው ካገገመ በኃላ ሌላ ሴት ማግባቷን በቅርቡ አስታውቃለች።
ለዓመታት ኑሩል ስያዝዋኒ የዕለት ተዕለት ህይወቷ የባለቤቷ ጠባቂ በመሆን የምታሳልፈውን ጊዜ በማህበራዊ ድህረ-ገፆች ላይ በማሳየት ስራ የበዛበት ተግባሯን አጋርተች። ይህም ባለቤቷ ምግብ በእጁ ጎርሶ ስለማይወርድለት በናሶጋስቲክ ቱቦ መመገብ፣ ዳይፐር መቀየር እና እንዲታጠብ መርዳት የእርሷ የእለት ከእለት ስራ ነበር። የኑሩል ባል የመኪና አደጋ ከደረሰበት በኃላ እንደገና ለመራመድ ስድስት አመታት መጠበቅ የግድ ብሎት የነበረ ሲሆን በነዚህ ዓመታት ሁሉ ግን እሷ ከጎኑ ነበረች።
ለባሏ ያሳየችው ትጋት እና ታታሪ አገልግሎት በፌስቡክ ላይ በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎችን ትኩረት የሳበ ሲሆን ብዙዎቹ የኑሩል ሲያዝዋኒ ባል ካገገመ በኋላ ፈትቷታል፤ ይህም ብቻ ሳይሆን ሌላ ሴት ማግባቱን ሲሰሙ ደንግጠዋል። የእብደት ድርጊት ሲሉ በርካቶች የተደመጡ ሲሆን ኑሩል በፌስቡክ ገጿ የቀድሞ ባለቤቷን እና አዲሲቷን ሙሽሪት እንኳን ደስ አላችሁ ብላለች።ለባለቤቴ እንኳን ደስ አለህ ፤ በመረጥከው ህይወት ደስተኛ እንደሆንክ ተስፋ አደርጋለሁ። አዲሲቱ ሚስቱ አይፋ አይዛም እባካሽ ልክ እንደ እኔ ተንከባከቢው ፤አሁን ተራው የአንቺ ነው ስትል ኑሩል መልዕክቷን አጋርታለች። በጥቅምት 4 መጠናቀቁ የተነገረለት የኑሩል የፍቺ ዜና የማሌዢያን የማህበራዊ ሚዲያ ተጠቃሚዎችን ማስደንገጡን ዳጉ ጆርናል ተመልክቷል።
በርካታ ተጠቃሚዎች ደግነቷን ሊከፍላት ይችላል የሚለውን አባባል መቀበል አቅቷቸዋል። በህመሙ ወቅት ከባድ ጊዜን አሳልፌያለሁ በየቀኑ እንዲያገግም እረዳው ነበር፣ ቤተሰቦቼ በየቀኑ ሊረዱኝ ይመጡ ነበር፣ ለልጆቼና ለባለቤቴ የሚያስፈልጉትን ነገሮች ብቻዬን ሳሟላ ቆይቻለሁ ስትል ተደምጣለች።ሆኖም ኑሩል የቀድሞ ባለቤቷ “ኃላፊነቱን በሚገባ እንደተወጣ” እንደሚሰማት ጠቁማ ሰዎች እሱን እና አዲሷን ሚስቱን ማስጨነቅ እንዲያቆሙ ጠይቃለች ። ሆኖም ደጋፊዎቿ በሀሳቧ አልተስማሙም። አንድ ሰው በሰነዘረው አስተያየት “እንዴት እንዲህ ያለው ምስጋና አልባ ሰው ሊኖር ይችላል? ልብ ያለው አይመስለኝም ሲል መደመጡን ዳጉ ጆርናል ዘግቧል።
የቀድሞ ባሏን እና አዲሲቱን ሚስቱን ከብዙሃኑ ትችት ለማዳን ስትል ኑሩል ሲያዝዋኒ በፌስቡክ ላይ የደረሰባትን ያሰፈረችውን ፅሁፏን በማጥፋት ሰዎች ለተፈጠረው ነገር የቀድሞ ባሏን መወንጀል እንዲያቆሙ ደጋፊዎቿን ጠይቃለች።የቀድሞ ባለቤቴን፣ አዲሲቱን ሚስቱን እና ቤተሰቦቻቸውን በፌስ ቡክ ላይ ባጋራሁት መልዕከት ለደረሰባቸው ትችት ይቅርታ መጠየቅ እፈልጋለሁ። የሆነው ሁሉ የእኔ ስህተት ነበር ሲል ኑሩል ጽፋለች።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter