የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር፣ በፌደራል መንግሥቱ በኩል የፕሪቶሪያ ግጭት ማቆም ስምምነትን ሙሉ በሙሉ ለመተግበር ያለው ፍላጎት ዝቅተኛ ነው በማለት የስምምነቱን ኹለተኛ ዓመት አስመልክቶ ዛሬ ባወጣው መግለጫ ተችቷል።
ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ በርካታ የደቡብ ትግራይና ጸለምት አካባቢዎች እስካኹን ወደ ትግራይ እንዳልተመለሱና በምሥራቃዊ፣ መካከለኛውና ሰሜን ምዕራብ ትግራይ የሚገኙ በርካታ አካባቢዎች ከኤርትራ ሠራዊት ነጻ እንዳልወጡ ገልጧል።
የሕወሓት አመራር የሕዝቡን ፍላጎት ወደ ጎን በማለት ፖለቲካዊ ንትርክ ውስጥ ገብቷል በማለት የወቀሰው ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ ፌዴራል መንግሥቱ፣ አፍሪካ ኅብረት፣ አውሮፓ ኅብረትና አሜሪካ በስምምነቱ ያልተመለሱ ጉዴዮችን ለመፍታት የሕግና የሞራል ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter
ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ በርካታ የደቡብ ትግራይና ጸለምት አካባቢዎች እስካኹን ወደ ትግራይ እንዳልተመለሱና በምሥራቃዊ፣ መካከለኛውና ሰሜን ምዕራብ ትግራይ የሚገኙ በርካታ አካባቢዎች ከኤርትራ ሠራዊት ነጻ እንዳልወጡ ገልጧል።
የሕወሓት አመራር የሕዝቡን ፍላጎት ወደ ጎን በማለት ፖለቲካዊ ንትርክ ውስጥ ገብቷል በማለት የወቀሰው ጊዜያዊ አስተዳደሩ፣ ፌዴራል መንግሥቱ፣ አፍሪካ ኅብረት፣ አውሮፓ ኅብረትና አሜሪካ በስምምነቱ ያልተመለሱ ጉዴዮችን ለመፍታት የሕግና የሞራል ሃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቋል።
@Addis_Reporter
@Addis_Reporter