ትምህርት ቤቴ “ቀልዶብኛል” ያለችው ተማሪ ክስ መሰረተች
የ19 ዓመቷ ወጣት የቀድሞ ትምህርት ቤቷ ላይ “አጥፍቶኛል” ስትል ክስ መስርታለች።
የፖርቶ ሪኮ ተወላጇ አሌሻ ኦርቲዝ በአሜሪካ ኮኔክቲከት ሃርትፎርድ የህዝብ ትምህርት ቤት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቷን ተከታትላ ተመርቃለች።
ወጣቷ ትምህርት ቤቱ ምንም እውቀት ሳይኖረኝና ማንበብና በትክክል መጻፍ ሳልችል “በማዕረግ” አስመርቆ ሸኝቶኛል ስትል ነው ክስ ያቀረበችው።
በአምሥት ዓመቷ ወደ አሜሪካ የመጣችው ኦርቲዝ ትምህርት ቤቱ በቸልተኝነት የሞራል ስብራት እንዲደርስብኝ አድርጎኛል ስትልም ነው ክስ የከፈተችው።
“ቋንቋውን በአግባቡና በትክክል መጻፍና ማንበብ ሳልችል የከፍተኛ ትምህርት ተቋም የነፃ ትምህርት እድል ሰጥቶኛል ይህ መሆኑ ደግሞ የስሜትና የመንፈስ መረበሽ ብሎም የሥነ ልቦና ጫና አሳድሮብኛል” ነው የምትለው።
በወቅቱ ትምህርቴን አጠናቀሻል ከተባልኩ በኋላ በወሰድኩት ፈተና አቅሜን አውቄዋለሁ የምትለው ኦርቲዝ፥ ለቀለዱብኝ ጊዜ እኔም እነሱን ተጠያቂ ማድረግ እፈልጋለሁ ብላለች።
አሁን የኮሌጅ ትምህርት እየተከታተለች ያለችው ወጣት በአብዛኛው በዘመናዊ ስልኮች ላይ በሚጫኑ ቋንቋ አስተማሪ መተግበሪያዎችን እንደምትተጠቀም ትናገራለች።
ዘመናዊ ስልኮችን በመጠቀም ንግግሮችን ወደ ፅሁፍ እንዲሁም ፅሁፎቹን ወደ ንግግር እንደምትቀይርም ነው የምታስረዳው።
ሌላው ቀርቶ የኮሌጅ ማመልከቻ ደብዳቤዋን እና የወረቀት ፅሁፏን በዚህ መልኩ ተጠቅማ በመጻፍ ማስገባቷን ጠቅሳ አሁን ላይ ሁሉም ነገር አስቸጋሪ በመሆኑ ለጊዜው አቁሜዋለሁ ብላለች።
ለጊዜው የአዕምሮ ጤና ክትትል አድርጌ በተሻለ ሁኔታ እመለሳለሁም ነው ያለችው ከሲ ኤን ኤን ጋር በነበራት ቆይታ።(አራዳ FM)
@Ethionews433 @Ethionews433
የ19 ዓመቷ ወጣት የቀድሞ ትምህርት ቤቷ ላይ “አጥፍቶኛል” ስትል ክስ መስርታለች።
የፖርቶ ሪኮ ተወላጇ አሌሻ ኦርቲዝ በአሜሪካ ኮኔክቲከት ሃርትፎርድ የህዝብ ትምህርት ቤት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቷን ተከታትላ ተመርቃለች።
ወጣቷ ትምህርት ቤቱ ምንም እውቀት ሳይኖረኝና ማንበብና በትክክል መጻፍ ሳልችል “በማዕረግ” አስመርቆ ሸኝቶኛል ስትል ነው ክስ ያቀረበችው።
በአምሥት ዓመቷ ወደ አሜሪካ የመጣችው ኦርቲዝ ትምህርት ቤቱ በቸልተኝነት የሞራል ስብራት እንዲደርስብኝ አድርጎኛል ስትልም ነው ክስ የከፈተችው።
“ቋንቋውን በአግባቡና በትክክል መጻፍና ማንበብ ሳልችል የከፍተኛ ትምህርት ተቋም የነፃ ትምህርት እድል ሰጥቶኛል ይህ መሆኑ ደግሞ የስሜትና የመንፈስ መረበሽ ብሎም የሥነ ልቦና ጫና አሳድሮብኛል” ነው የምትለው።
በወቅቱ ትምህርቴን አጠናቀሻል ከተባልኩ በኋላ በወሰድኩት ፈተና አቅሜን አውቄዋለሁ የምትለው ኦርቲዝ፥ ለቀለዱብኝ ጊዜ እኔም እነሱን ተጠያቂ ማድረግ እፈልጋለሁ ብላለች።
አሁን የኮሌጅ ትምህርት እየተከታተለች ያለችው ወጣት በአብዛኛው በዘመናዊ ስልኮች ላይ በሚጫኑ ቋንቋ አስተማሪ መተግበሪያዎችን እንደምትተጠቀም ትናገራለች።
ዘመናዊ ስልኮችን በመጠቀም ንግግሮችን ወደ ፅሁፍ እንዲሁም ፅሁፎቹን ወደ ንግግር እንደምትቀይርም ነው የምታስረዳው።
ሌላው ቀርቶ የኮሌጅ ማመልከቻ ደብዳቤዋን እና የወረቀት ፅሁፏን በዚህ መልኩ ተጠቅማ በመጻፍ ማስገባቷን ጠቅሳ አሁን ላይ ሁሉም ነገር አስቸጋሪ በመሆኑ ለጊዜው አቁሜዋለሁ ብላለች።
ለጊዜው የአዕምሮ ጤና ክትትል አድርጌ በተሻለ ሁኔታ እመለሳለሁም ነው ያለችው ከሲ ኤን ኤን ጋር በነበራት ቆይታ።(አራዳ FM)
@Ethionews433 @Ethionews433