የኢትዮጲያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የብልሹ አሰራር እና የሙስና ጥቆማ መስጫ ዲጂታል የሞባይል መተግበሪያ ስራ ላይ አዋለ።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ በሚፈጠሩ የብልሹ አስራር እና የሙስና ችግሮች ላይ ደንበኞች የሚኖራቸውን ቅሬታ እንዲሁም አስተያየትና ጥቆማ በቀላሉ እንዲያቀርቡ የሚያስችል ዘመናዊ የሞባይል መተግበሪያ አገልግሎት ላይ ማዋሉን አስታውቋል።
ዲጂታል መተግበሪያው ደንበኞች በተቋሙ አገልግሎት አሰጣጥ ሂደት ብልሹ አሰራር እና ተግባር ሲያጋጥማቸው በየትኛውም ቦታ ላይ ሆነው በእጅ ስልካቸው ጥቆማ የሚያቀርቡበት ቴክኖሎጂ ነው ተብሏል።
መተግበሪያው ደንበኞች በሚያመቻቸው አማራጮች ቅሬታቸውን እንዲያቀርቡ የቴሌግራም ቦት እና ድረ ገጽ የተዘጋጀ ሲሆን ሁሉም አማራጮች የደንበኛው ማንነት ሚስጢራዊነቱ ተጠብቆ መገልገል የሚችሉበት መሆኑ ተገልጿል።
ደንበኞች የግል ስልክ ወይም ላፕቶፕ በመጠቀም ጎግል ላይ "eeuethics.et" ብለው በመግባት መተግበሪያውን በመክፈት የሚፈለጉ መረጃዎችን በተዘጋጀው ቅጽ መሰረት በጥንቃቄ ትክክለኛ መረጃዎችን መሙላት እንደሚጠበቅ ተነስቷል።
መተግበሪያው አማርኛ እና እንግሊዝኛ ቋንቋዎችን በመጠቀም ደንበኞች ጥቆማዎችን እንዲያቀርቡ የሚያስችል ሲሆን፣ በቀጣይ ሌሎች ቋንቋዎችን በማካተት አገልግሎቱን ለማስፋት ይሰራል ስለመባሉም ሰምተናል።
[ @MadoNews ]
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ በሚፈጠሩ የብልሹ አስራር እና የሙስና ችግሮች ላይ ደንበኞች የሚኖራቸውን ቅሬታ እንዲሁም አስተያየትና ጥቆማ በቀላሉ እንዲያቀርቡ የሚያስችል ዘመናዊ የሞባይል መተግበሪያ አገልግሎት ላይ ማዋሉን አስታውቋል።
ዲጂታል መተግበሪያው ደንበኞች በተቋሙ አገልግሎት አሰጣጥ ሂደት ብልሹ አሰራር እና ተግባር ሲያጋጥማቸው በየትኛውም ቦታ ላይ ሆነው በእጅ ስልካቸው ጥቆማ የሚያቀርቡበት ቴክኖሎጂ ነው ተብሏል።
መተግበሪያው ደንበኞች በሚያመቻቸው አማራጮች ቅሬታቸውን እንዲያቀርቡ የቴሌግራም ቦት እና ድረ ገጽ የተዘጋጀ ሲሆን ሁሉም አማራጮች የደንበኛው ማንነት ሚስጢራዊነቱ ተጠብቆ መገልገል የሚችሉበት መሆኑ ተገልጿል።
ደንበኞች የግል ስልክ ወይም ላፕቶፕ በመጠቀም ጎግል ላይ "eeuethics.et" ብለው በመግባት መተግበሪያውን በመክፈት የሚፈለጉ መረጃዎችን በተዘጋጀው ቅጽ መሰረት በጥንቃቄ ትክክለኛ መረጃዎችን መሙላት እንደሚጠበቅ ተነስቷል።
መተግበሪያው አማርኛ እና እንግሊዝኛ ቋንቋዎችን በመጠቀም ደንበኞች ጥቆማዎችን እንዲያቀርቡ የሚያስችል ሲሆን፣ በቀጣይ ሌሎች ቋንቋዎችን በማካተት አገልግሎቱን ለማስፋት ይሰራል ስለመባሉም ሰምተናል።
[ @MadoNews ]