የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 22 የተቋሙ አመራርና ሰራተኞች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ ወሰደ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2017 የመጀመሪያው ሰባት ወራት የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ እና ብልሹ አስራርን ለመቀረፍ ባከናወናቸው ተግባራት በ22 አመራርና ሰራተኞች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ ወስዷል፡፡
እርምጃው የተወሰደው ከደንበኞች በቀረቡ የብልሹ አሰራርና ሙስና ጥቆማዎችን መሰረት በማድረግ ሲሆን፣ አስፈላጊው ማጣሪያ ተደርጎ በ22ቱም አመራር እና ሰራተኞች የተለያዩ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወሰድ ተደርጓል።እርምጃ ከተወሰደባቸው አመራር እና ሰራተኞች መካከል ሶስቱ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ እና 19ኙ ደመወዝ እንደተቀጡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኮሙዮኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ አቶ መላኩ ታዬ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።
በሌላ በኩል በሰባቱ ወራት ውስጥ ከ 50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የንብረት ስርቆት እና ውድመት ተቋሙ ላይ ተፈፅሟል፡፡የተፈፀመው ስርቆትና ውድመት የኃይል ሰርቆት፣ የትራንስፎርመር ስርቆት፣ ቆጣሪ መነካካት፣ የኤሌክትሪክ መስመር ጉዳት፣ የመሰረተ ልማት ሰርቆት፣ የተቋሙ ሰራተኞችን ስራ እንዳይሰሩ ማወክ እና የኬብል ሰርቆትን የሚያጠቃልል ሲሆን፤ በአጠቃላይ 163 ወንጀሎች ተፈጽመው ክትትል እየተደረገባቸው ይገኛል፡፡
ከእነዚህ መካከል ውሳኔ ያገኙ የወንጀል ጉዳዮች 11 ሲሆኑ፤ በዚህም 13 ተከሳሾች ከሁለት ወር ቀላል እስራት እስከ 10 ዓመት ፅኑ እስራት እና እስከ 50 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ተቀጥተዋል፡፡በተጨማሪም በሰባቱ ወራት ውስጥ የፍጆታ ክፍያ ለማይከፍሉ ለ368 ደንበኞች ማሰጠንቀቂያ በመሰጠት ከ127 ሚሊዮን ብር በላይ ለድርጅቱ ገቢ ማድረግ መቻሉን አቶ መላኩ ታዬ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።
[ @MadoNews ]
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በ2017 የመጀመሪያው ሰባት ወራት የህግ የበላይነትን ለማረጋገጥ እና ብልሹ አስራርን ለመቀረፍ ባከናወናቸው ተግባራት በ22 አመራርና ሰራተኞች ላይ አስተዳደራዊ እርምጃ ወስዷል፡፡
እርምጃው የተወሰደው ከደንበኞች በቀረቡ የብልሹ አሰራርና ሙስና ጥቆማዎችን መሰረት በማድረግ ሲሆን፣ አስፈላጊው ማጣሪያ ተደርጎ በ22ቱም አመራር እና ሰራተኞች የተለያዩ አስተዳደራዊ እርምጃ እንዲወሰድ ተደርጓል።እርምጃ ከተወሰደባቸው አመራር እና ሰራተኞች መካከል ሶስቱ የፅሁፍ ማስጠንቀቂያ እና 19ኙ ደመወዝ እንደተቀጡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኮሙዮኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ አቶ መላኩ ታዬ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።
በሌላ በኩል በሰባቱ ወራት ውስጥ ከ 50 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት የንብረት ስርቆት እና ውድመት ተቋሙ ላይ ተፈፅሟል፡፡የተፈፀመው ስርቆትና ውድመት የኃይል ሰርቆት፣ የትራንስፎርመር ስርቆት፣ ቆጣሪ መነካካት፣ የኤሌክትሪክ መስመር ጉዳት፣ የመሰረተ ልማት ሰርቆት፣ የተቋሙ ሰራተኞችን ስራ እንዳይሰሩ ማወክ እና የኬብል ሰርቆትን የሚያጠቃልል ሲሆን፤ በአጠቃላይ 163 ወንጀሎች ተፈጽመው ክትትል እየተደረገባቸው ይገኛል፡፡
ከእነዚህ መካከል ውሳኔ ያገኙ የወንጀል ጉዳዮች 11 ሲሆኑ፤ በዚህም 13 ተከሳሾች ከሁለት ወር ቀላል እስራት እስከ 10 ዓመት ፅኑ እስራት እና እስከ 50 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ተቀጥተዋል፡፡በተጨማሪም በሰባቱ ወራት ውስጥ የፍጆታ ክፍያ ለማይከፍሉ ለ368 ደንበኞች ማሰጠንቀቂያ በመሰጠት ከ127 ሚሊዮን ብር በላይ ለድርጅቱ ገቢ ማድረግ መቻሉን አቶ መላኩ ታዬ ለብስራት ሬዲዮ እና ቴሌቪዥን ተናግረዋል።
[ @MadoNews ]