የሶማሊያ ጦር ከአጋሮቹ ጋር በመሆን ባካሄደው ዘመቻ ከ40 በላይ የአልሸባብ ታጣቂዎች ተገደሉ
የሶማሊያ ብሄራዊ የቴሌቪዥን ጣብያ ባሰራጨው ዘገባ ከ40 በላይ የአሸባሪው ቡዱን አልሸባብ ተዋጊዎች ስኬታማ በነበረ ኦፕሬሽን ተገድለዋል ብሏል።
የሶማሊያ ጦር የሰጠው መግለጫ ኦፖሬሽኑ እንደተካሄደ ማረጋገጫ የሰጠ ሲሆን፣ ከዓለም አቀፍ አጋሮቻችን ጋር በመተባበር በሂርሻቤለ ግዛት ቢያ ካዴ አከባቢ የተሳካ ዘመቻ አካሂደናል ብሏል። የሶማልያ ብሄራዊ ጦር ከዓለም አቀፍ አጋሮቹና የአከባቢው ሰዎች ጋር በመሆንም ሌላ ተጨማሪ የአሸባሪው ቡዱን ክንፎችና አባላት ከአከባቢው ለማፅዳት እየሰሩ መሆኑ የሶማሊያ ጦር በኤክስ ላይ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
እኤአ በ2004 በሶማሊያ የተመሰረተው አልሸባብ እኤአ ከ2010 ጀምሮ የተለያዩ የሶማሊያ ግዛቶችን መቆጣጠር የቻለ ሲሆን ከሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃዶሾ ግን እኤአ በ2011 እንዲወጣ ተደርጓል። በዚህም ከዛን ጊዜ ጀምሮ አልሸባብ የሽምቅ ተዋጊ በመሆን በተለያዩ የሶማሊያ አከባቢዎች በሞቃዲሾ መንግስት ጦርና አጋሮች ላይ የአጥፍቶ ጠፊ ጥቃቶችን ሲፈፅም ቆይቷል።
አልሸባብ እኤአ ከ2012 ጀምሮ በይፋ የአልቃይዳ ክንፍ መሆኑንም ያወጀ ሲሆን በዚህም ሶማሊያ መረጋጋት የተሳናት ሰላም የራቃት ሀገር ትሆን ዘንድ የራሱን ከፍተኛ ሚና ሲወጣ ቆያቷል።
[ @MadoNews ]
የሶማሊያ ብሄራዊ የቴሌቪዥን ጣብያ ባሰራጨው ዘገባ ከ40 በላይ የአሸባሪው ቡዱን አልሸባብ ተዋጊዎች ስኬታማ በነበረ ኦፕሬሽን ተገድለዋል ብሏል።
የሶማሊያ ጦር የሰጠው መግለጫ ኦፖሬሽኑ እንደተካሄደ ማረጋገጫ የሰጠ ሲሆን፣ ከዓለም አቀፍ አጋሮቻችን ጋር በመተባበር በሂርሻቤለ ግዛት ቢያ ካዴ አከባቢ የተሳካ ዘመቻ አካሂደናል ብሏል። የሶማልያ ብሄራዊ ጦር ከዓለም አቀፍ አጋሮቹና የአከባቢው ሰዎች ጋር በመሆንም ሌላ ተጨማሪ የአሸባሪው ቡዱን ክንፎችና አባላት ከአከባቢው ለማፅዳት እየሰሩ መሆኑ የሶማሊያ ጦር በኤክስ ላይ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
እኤአ በ2004 በሶማሊያ የተመሰረተው አልሸባብ እኤአ ከ2010 ጀምሮ የተለያዩ የሶማሊያ ግዛቶችን መቆጣጠር የቻለ ሲሆን ከሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃዶሾ ግን እኤአ በ2011 እንዲወጣ ተደርጓል። በዚህም ከዛን ጊዜ ጀምሮ አልሸባብ የሽምቅ ተዋጊ በመሆን በተለያዩ የሶማሊያ አከባቢዎች በሞቃዲሾ መንግስት ጦርና አጋሮች ላይ የአጥፍቶ ጠፊ ጥቃቶችን ሲፈፅም ቆይቷል።
አልሸባብ እኤአ ከ2012 ጀምሮ በይፋ የአልቃይዳ ክንፍ መሆኑንም ያወጀ ሲሆን በዚህም ሶማሊያ መረጋጋት የተሳናት ሰላም የራቃት ሀገር ትሆን ዘንድ የራሱን ከፍተኛ ሚና ሲወጣ ቆያቷል።
[ @MadoNews ]