ኢጎ እና አእምሮ
የሰው ልጅ ለደረሰበት ስልጣኔ እና ብዙ ሳይንሳዊ እውቀቶች ምክንያት አእምሮዉን በሚገባ መጠቀሙ መሆኑ ግልፅ ነው። ነገር ግን አእምሮአችን በጣም አስፈላጊ የመሆኑን ያህል አውዳሚም ሊሆን ይችላል። እንዴት?
አእምሮ በውስጡ ወደ 100 ቢሊየን የሚጠጉ ኒውሮኖች ይገኛሉ። በዚህም ምክንያት የሰው ልጅ በቀን (24ሰአታት) ውስጥ ከ 40,000 እስከ 60,000 ሀሳቦችን ያስባል። ከነዚህ ሀሳቦች ውስጥ 75% የሚሆኑት መጥፎና አውዳሚ (negative thoughts) ሲሆኑ 95% ደግሞ ተደጋጋሚ (repetitive thoughts) ናቸው። ስለዚህ ከነዚህ ሁሉ ምናስባቸው ሀሳቦች ውስጥ ቀና እና መልካም (positive thoughts) የሚባሉት 5%ቱ ብቻ ናቸው።
ተመስጦ (meditation) የማድረግ ልምድ ካላችሁ ይህንን መረዳት ትችላላችሁ። አእምሮአችን በአብዛኛው ምንም ለህይወታችን ፋይዳ በሌላቸው ሀሳቦች ሲባክን ይውላል። ነገር ግን ይህን ለመረዳት መጀመሪያ አእምሮአችሁን መታዘብ መጀመር አለባችሁ። ይህንን ካላደረጋችሁ ግን የምታስቡት እናንተ እንጂ አእምሮአችሁ ላይመስላችሁ ይችላል። አብዛኛው ሰዉ የሚያስበው አእምሮ መሆኑን አይረዳም፤ የሚያስበው፣ የሚያስታውሰው፣ የሚያሰላስለው አእምሮአችሁ እንጂ እናንተ አይደላችሁም። ይህንን ለማረጋገጥ ጭንቅላቱ ላይ አደጋ የደረሰበትን ሰው መመልከት በቂ ነው፤ ጭንቅላታቸው የተጎዱ ሰዎች ያለፈ የህይወት ታሪካቸውን እና ያከማቹትን እውቀት የሚረሱበት አጋጣሚ አለ።
አእምሮአችን እንድናስብበት እና እንዲያገለግለን የተሰጠን ድንቅ ገፀ በረከት ቢሆንም በተቃራኒው እኛ እራሳችን የአእምሮአችን ባርያ ነን። ነገር ግን አእምሮን በአግባቡ ከተጠቀምንበት መጥፎ ጌታ ከመሆን ይልቅ ጥሩ ባርያ ማድረግ እንችለላለን። አእምሮአችን ማስላት ይወዳል፤ እራሱን ከሌሎች ያነፃፅራል።
አእምሮ የኢጎ ማእከል ነው። ኢጎ እራስን በሆነ አይነት ማንነት ለሰዎች ለመግለፅ መሞከር እና ከሌሎች የተሻለ መሆኑን ለማሳየት የሚሞክርበት መንገድ ነው። ለምሳሌ ፦ የብሔር ማንነትን፣ የትምህርት ደረጃን፣ የቆዳ ቀለምን፣ ሀይማኖትን፣ ግለሰባዊ አመለካከትን እንደ ራስ ማንነት በመቁጠር ከሌሎች የተሻሉ መሆንን ለማሳየት የሚደረግ ጥረት የኢጎ የተለያየ ገፅታ ነው። አንድ ሐኪም ለሙያው ካለው ፍቅር የተነሳ የሚሰጠው የህክምና አገልግሎት ጤናማ ቢሆንም፤ የህክምና እውቀት መያዙ ከሌሎች ሰዎች የተሻለ እንደሆነ እንዲሰማዉ የሚያደርገው ከሆነ እና በየአጋጣሚው ስለሱ የሚያወራ ከሆነ ግን ይህንን ኢጎ ልንለው እንችላለን።
ኢጎ ራስን ከሁለንተና የመነጠል ውጤት ነው። አእምሮአችሁ ከሁለነተና ጋር አንድ እንድትሆኑ አይፈልግም። ምክንያቱም ከሁለንተና (universe) ጋር አንድ ከሆናችሁ ከአእምሮ በላይ ትሆናላችሁ፤ ማሰብ በምትፈልጉበት ሰአት ታስባላችሁ ካልፈለጋችሁ ደግሞ አእምሮን እንዳያስብ ማድረግ (shutdown) ትችላላችሁ። አሁን ግን እየሆነ ያለው የተገላቢጦሽ ነው፤ አእምሮአችን በያንዳንዷ ሰከንድ ያለኛ ፍላጎት ያስባል። ይህም ማለት እጃችን ያለኛ ፍላጎት ቢንቀሳቀስ ማለት ነው፤ አእምሮአችን ግን ይህንን ያደርጋል። ሰዎችም ይህንን የአእምሮአቸውን ጫጫታ ለመርሳት በተለያዩ የአልኮል እና አደንዛዥ እፆች እራሳቸውን ይጠምዳሉ።
እዉነታው ግን እኛ ከሁለንተና የተለየን አይደለንም። አእምሮአችን ከእውነተኛ ውስጣዊ ተፈጥሮአችን በታች ነው። ይህንን ውስጣዊ ተፈጥሮአችንን ለማግኘት ከኢጎ (አእምሮ) የበላይነት መላቀቅ ይኖርብናል። አእምሮ ማለት ምንም ሳይሆን ያለፈ እና የወደፊት ህይወታችን የሀሳብ ጥርቅም ማለት ነው። ከአእምሮአችን ቁጥጥር ለመላቀቅ አሁንን መኖር ይኖርብናል፤ ምክንያቱም አሁን(now) የጊዜ አካል አይደለም። ሀሳብ እንዲኖር ያለፈ ወይም የወደፊቱ ጊዜ መኖር አለባቸው።
@zephilosophy
@zephilosophy
የሰው ልጅ ለደረሰበት ስልጣኔ እና ብዙ ሳይንሳዊ እውቀቶች ምክንያት አእምሮዉን በሚገባ መጠቀሙ መሆኑ ግልፅ ነው። ነገር ግን አእምሮአችን በጣም አስፈላጊ የመሆኑን ያህል አውዳሚም ሊሆን ይችላል። እንዴት?
አእምሮ በውስጡ ወደ 100 ቢሊየን የሚጠጉ ኒውሮኖች ይገኛሉ። በዚህም ምክንያት የሰው ልጅ በቀን (24ሰአታት) ውስጥ ከ 40,000 እስከ 60,000 ሀሳቦችን ያስባል። ከነዚህ ሀሳቦች ውስጥ 75% የሚሆኑት መጥፎና አውዳሚ (negative thoughts) ሲሆኑ 95% ደግሞ ተደጋጋሚ (repetitive thoughts) ናቸው። ስለዚህ ከነዚህ ሁሉ ምናስባቸው ሀሳቦች ውስጥ ቀና እና መልካም (positive thoughts) የሚባሉት 5%ቱ ብቻ ናቸው።
ተመስጦ (meditation) የማድረግ ልምድ ካላችሁ ይህንን መረዳት ትችላላችሁ። አእምሮአችን በአብዛኛው ምንም ለህይወታችን ፋይዳ በሌላቸው ሀሳቦች ሲባክን ይውላል። ነገር ግን ይህን ለመረዳት መጀመሪያ አእምሮአችሁን መታዘብ መጀመር አለባችሁ። ይህንን ካላደረጋችሁ ግን የምታስቡት እናንተ እንጂ አእምሮአችሁ ላይመስላችሁ ይችላል። አብዛኛው ሰዉ የሚያስበው አእምሮ መሆኑን አይረዳም፤ የሚያስበው፣ የሚያስታውሰው፣ የሚያሰላስለው አእምሮአችሁ እንጂ እናንተ አይደላችሁም። ይህንን ለማረጋገጥ ጭንቅላቱ ላይ አደጋ የደረሰበትን ሰው መመልከት በቂ ነው፤ ጭንቅላታቸው የተጎዱ ሰዎች ያለፈ የህይወት ታሪካቸውን እና ያከማቹትን እውቀት የሚረሱበት አጋጣሚ አለ።
አእምሮአችን እንድናስብበት እና እንዲያገለግለን የተሰጠን ድንቅ ገፀ በረከት ቢሆንም በተቃራኒው እኛ እራሳችን የአእምሮአችን ባርያ ነን። ነገር ግን አእምሮን በአግባቡ ከተጠቀምንበት መጥፎ ጌታ ከመሆን ይልቅ ጥሩ ባርያ ማድረግ እንችለላለን። አእምሮአችን ማስላት ይወዳል፤ እራሱን ከሌሎች ያነፃፅራል።
አእምሮ የኢጎ ማእከል ነው። ኢጎ እራስን በሆነ አይነት ማንነት ለሰዎች ለመግለፅ መሞከር እና ከሌሎች የተሻለ መሆኑን ለማሳየት የሚሞክርበት መንገድ ነው። ለምሳሌ ፦ የብሔር ማንነትን፣ የትምህርት ደረጃን፣ የቆዳ ቀለምን፣ ሀይማኖትን፣ ግለሰባዊ አመለካከትን እንደ ራስ ማንነት በመቁጠር ከሌሎች የተሻሉ መሆንን ለማሳየት የሚደረግ ጥረት የኢጎ የተለያየ ገፅታ ነው። አንድ ሐኪም ለሙያው ካለው ፍቅር የተነሳ የሚሰጠው የህክምና አገልግሎት ጤናማ ቢሆንም፤ የህክምና እውቀት መያዙ ከሌሎች ሰዎች የተሻለ እንደሆነ እንዲሰማዉ የሚያደርገው ከሆነ እና በየአጋጣሚው ስለሱ የሚያወራ ከሆነ ግን ይህንን ኢጎ ልንለው እንችላለን።
ኢጎ ራስን ከሁለንተና የመነጠል ውጤት ነው። አእምሮአችሁ ከሁለነተና ጋር አንድ እንድትሆኑ አይፈልግም። ምክንያቱም ከሁለንተና (universe) ጋር አንድ ከሆናችሁ ከአእምሮ በላይ ትሆናላችሁ፤ ማሰብ በምትፈልጉበት ሰአት ታስባላችሁ ካልፈለጋችሁ ደግሞ አእምሮን እንዳያስብ ማድረግ (shutdown) ትችላላችሁ። አሁን ግን እየሆነ ያለው የተገላቢጦሽ ነው፤ አእምሮአችን በያንዳንዷ ሰከንድ ያለኛ ፍላጎት ያስባል። ይህም ማለት እጃችን ያለኛ ፍላጎት ቢንቀሳቀስ ማለት ነው፤ አእምሮአችን ግን ይህንን ያደርጋል። ሰዎችም ይህንን የአእምሮአቸውን ጫጫታ ለመርሳት በተለያዩ የአልኮል እና አደንዛዥ እፆች እራሳቸውን ይጠምዳሉ።
እዉነታው ግን እኛ ከሁለንተና የተለየን አይደለንም። አእምሮአችን ከእውነተኛ ውስጣዊ ተፈጥሮአችን በታች ነው። ይህንን ውስጣዊ ተፈጥሮአችንን ለማግኘት ከኢጎ (አእምሮ) የበላይነት መላቀቅ ይኖርብናል። አእምሮ ማለት ምንም ሳይሆን ያለፈ እና የወደፊት ህይወታችን የሀሳብ ጥርቅም ማለት ነው። ከአእምሮአችን ቁጥጥር ለመላቀቅ አሁንን መኖር ይኖርብናል፤ ምክንያቱም አሁን(now) የጊዜ አካል አይደለም። ሀሳብ እንዲኖር ያለፈ ወይም የወደፊቱ ጊዜ መኖር አለባቸው።
@zephilosophy
@zephilosophy