ሁላችንም የተፈጥሮ አካላቶች ነን - ስፒኖዛ
ምንጭ፦ ፍልስፍና ከዘርአያዕቆብ እስከ ሶቅራጠስ
ዝግጅት፦ ፍሉይ አለም
በአጽናፈ ዓለም ውስጥ ብዙ ኃይላት አሉ፡፡ ምድር ወደ ላይ በረን እንዳንሄድ ስባ ታስቀረናለች፡፡ ጸሐይ ምድርን በክብ ምህዋር ላይ እንድትዞር ታስገድዳታለች... ብንዘረዝራቸው የማያልቁ ብዙ ኃይላትን በሁለንተና ውስጥ እናገኛለን፡፡ በእያንዳንዱ ቁስ አካል ውስጥም ይፈሳሉ፡፡ በዓለም ሁሉ ያለ ነገር በእነዚህ ሃይሎች ተይዟል፡፡ ሰዎች፣ በባህር ውስጥ ያለ አሳ፣ ከወፎች የሚወጣ ድምጽ... ሁሉም የዚህ ኃይል አካል ናቸው፡፡ ሁላችንም በእነዚህ ኃይላት ታስረናል፡፡
ይህ ሁለንተናን በሌላ መንገድ የመመልከቻ ሃሳብ የቀረበው ባሩክ ስፒኖዛ በተባለ ፈላስፋ ነው፡፡ የፍልስፍናውም ሃሳብ ሞኒዝም ተብሎ ይጠራል፡፡ ሞኒዝም ቃሉ “አንድ ብቻ” የሚል ትርጓሜ አለው፡፡ ይህም በሁለንተና ውስጥ ያለ ነገር ሁሉ እንደ “አንድ አካል” ነው የሚል አንድምታ አለው፡፡ እኔም አንተም፣ ጨረቃም ጸሐይም - ሁላችንም በአንድ አካል ውስጥ እንዳሉ ህዋሳቶች ነን፡፡
ስፒኖዛ በአብርሆት ዘመን በፊት የነበረ አውሮፓዊ ፈላስፋ ነው፡፡ ከእርሱ ጋር በአንድ ዘመን የነበረው ዴካርት በሁለንተና ውስጥ ያሉ ነገሮችን በሶስት ይከፍላቸዋል- አእምሯዊ፣ አካላዊ እና አምላክ (ያልተፈጠረ እና ሁለንተናን የፈጠረ)።
ነገር ግን ስፒኖዛ እንዲህ ይላል - ከሁላችንም በላይ የሆነ እና ሁላችንንም የሚያውቅ አምላክ ካለ፣ ይህ አምላክ በሆነ መንገድ ከሁላችንም ጋር ይገናኛል ማለት ነው፡፡
“አቤቱ፣ ፈትነኝ መርምረኝም፤ ኩላሊቴንና ልቤን ፈትን:: እንዳለው መዝሙረኛው ዳዊት፣ ልብ እና ኩላሊትን የሚመረምር አምላክ በልብም፣ በኩላሊትም ውስጥ መገኘት አለበት ይለናል ስፒኖዛ፡፡ የአካላቸው ክፍል የሆኑ ነገሮችን ብቻ ነው ልንመረምር የምንችለው... አምላክም እኛን ሊመረምር የሚችለው እኛ የእርሱ አካል እስከሆንን ድረስ ብቻ ነው፡፡ እግርህ ላይ ያለ ህመም የሚሰማህ እግርህ የአንተ አካል ስለሆነ ነው፡፡ አምላክም የእኛ ህመም የሚሰማው እኛ የእርሱ አካል ስለሆንን ነው፡፡
በተመሳሳይም በሁለንተና ውስጥ ያሉ ሁሉም ነገሮች እንደ አንድ አካል ናቸው፡፡ አእምሮም፣ አካላዊ ቁሶችም የአንድ ግዙፍ ስርዓት አካል ናቸው፡፡ እንደ አንድም ይንቀሳቀሳሉ። ሁሉም ነገር ስረ መሰረቱ አንድ ነው፡፡ ያንተ ህሊናም፣ የጉንዳኖች ጉዞም፣ የአንዲት የብርሃን ቅንጣት፣ አንዲት ጠብታ ውሃም መዳረሻቸው አንድ ነው ... ሞኒዝም፡፡
አንስታይን ስፒኖዛን ይወደው ነበር፡፡ የስፒኖዛ ፍልስፍና ለእርሱ ሒሳባዊ ቀመሮች የሚፈይድለት ነገር ኖሮ አይደለም፤ ነገር ግን ስፔኖዛ ተፈጥሮን እንደ አምላክ አድርጎ ስለሚገልጻት ነው። አንስታይንም ተፈጥሮን አምላክ ብሎ ይጠራት ነበር፡፡
ስፒኖዛ ከጥቃቅን ነገሮች ወይም ተፈጥሮን/አምላክን ለመረዳት መጓዝ አለብን ይለናል፡፡ በተፈጥሮ ሁነቶች ተነስተን ውስጥ ራሳችንን እያስመጥን ስንመጣና ከተፈጥሮ ጋር ፍጹም አንድ ስንሆን፣ መታበያችን ከእኛ ይርቃል። እኔ እንዲህ ነኝ ማለትንም እናቆማለን፡፡ ራሳችንንም ነጥለን የምንኮራበት አልያም የምንወቅስበት ምክንያት አይኖርም... ምክንያቱም “እኔ” የሚባል ማንነት
አይኖረንም...
ስፒኖዛ የሰው ልጆች ሕይወታቸውን አወሳስበው ይኖራሉ ይለናል። ልክ እንደ ህጻናትም በጸደይ አበባ መሃል ከመቦረቅ ይልቅ፣ በብዙ ጥቃቅን ጉዳዮች ራሳችንን አስረነዋል። ይህ የሚገባን ግን እድሜያችን ሲገፋ ብቻ ነው፡፡ በእርጅና ዘመናችን በወጣትነታችን የነበሩ አላስፈላጊ ጭንቀቶቻችን እና ፍርሃቶቻችን ይገለጡልናል። ሕይወታችን ውስጥ ያሉ ነገሮችንም መውደድ እና ማድነቅ እንጀምራለን፡፡
@zephilosophy
@zephilosophy
ምንጭ፦ ፍልስፍና ከዘርአያዕቆብ እስከ ሶቅራጠስ
ዝግጅት፦ ፍሉይ አለም
በአጽናፈ ዓለም ውስጥ ብዙ ኃይላት አሉ፡፡ ምድር ወደ ላይ በረን እንዳንሄድ ስባ ታስቀረናለች፡፡ ጸሐይ ምድርን በክብ ምህዋር ላይ እንድትዞር ታስገድዳታለች... ብንዘረዝራቸው የማያልቁ ብዙ ኃይላትን በሁለንተና ውስጥ እናገኛለን፡፡ በእያንዳንዱ ቁስ አካል ውስጥም ይፈሳሉ፡፡ በዓለም ሁሉ ያለ ነገር በእነዚህ ሃይሎች ተይዟል፡፡ ሰዎች፣ በባህር ውስጥ ያለ አሳ፣ ከወፎች የሚወጣ ድምጽ... ሁሉም የዚህ ኃይል አካል ናቸው፡፡ ሁላችንም በእነዚህ ኃይላት ታስረናል፡፡
ይህ ሁለንተናን በሌላ መንገድ የመመልከቻ ሃሳብ የቀረበው ባሩክ ስፒኖዛ በተባለ ፈላስፋ ነው፡፡ የፍልስፍናውም ሃሳብ ሞኒዝም ተብሎ ይጠራል፡፡ ሞኒዝም ቃሉ “አንድ ብቻ” የሚል ትርጓሜ አለው፡፡ ይህም በሁለንተና ውስጥ ያለ ነገር ሁሉ እንደ “አንድ አካል” ነው የሚል አንድምታ አለው፡፡ እኔም አንተም፣ ጨረቃም ጸሐይም - ሁላችንም በአንድ አካል ውስጥ እንዳሉ ህዋሳቶች ነን፡፡
ስፒኖዛ በአብርሆት ዘመን በፊት የነበረ አውሮፓዊ ፈላስፋ ነው፡፡ ከእርሱ ጋር በአንድ ዘመን የነበረው ዴካርት በሁለንተና ውስጥ ያሉ ነገሮችን በሶስት ይከፍላቸዋል- አእምሯዊ፣ አካላዊ እና አምላክ (ያልተፈጠረ እና ሁለንተናን የፈጠረ)።
ነገር ግን ስፒኖዛ እንዲህ ይላል - ከሁላችንም በላይ የሆነ እና ሁላችንንም የሚያውቅ አምላክ ካለ፣ ይህ አምላክ በሆነ መንገድ ከሁላችንም ጋር ይገናኛል ማለት ነው፡፡
“አቤቱ፣ ፈትነኝ መርምረኝም፤ ኩላሊቴንና ልቤን ፈትን:: እንዳለው መዝሙረኛው ዳዊት፣ ልብ እና ኩላሊትን የሚመረምር አምላክ በልብም፣ በኩላሊትም ውስጥ መገኘት አለበት ይለናል ስፒኖዛ፡፡ የአካላቸው ክፍል የሆኑ ነገሮችን ብቻ ነው ልንመረምር የምንችለው... አምላክም እኛን ሊመረምር የሚችለው እኛ የእርሱ አካል እስከሆንን ድረስ ብቻ ነው፡፡ እግርህ ላይ ያለ ህመም የሚሰማህ እግርህ የአንተ አካል ስለሆነ ነው፡፡ አምላክም የእኛ ህመም የሚሰማው እኛ የእርሱ አካል ስለሆንን ነው፡፡
በተመሳሳይም በሁለንተና ውስጥ ያሉ ሁሉም ነገሮች እንደ አንድ አካል ናቸው፡፡ አእምሮም፣ አካላዊ ቁሶችም የአንድ ግዙፍ ስርዓት አካል ናቸው፡፡ እንደ አንድም ይንቀሳቀሳሉ። ሁሉም ነገር ስረ መሰረቱ አንድ ነው፡፡ ያንተ ህሊናም፣ የጉንዳኖች ጉዞም፣ የአንዲት የብርሃን ቅንጣት፣ አንዲት ጠብታ ውሃም መዳረሻቸው አንድ ነው ... ሞኒዝም፡፡
አንስታይን ስፒኖዛን ይወደው ነበር፡፡ የስፒኖዛ ፍልስፍና ለእርሱ ሒሳባዊ ቀመሮች የሚፈይድለት ነገር ኖሮ አይደለም፤ ነገር ግን ስፔኖዛ ተፈጥሮን እንደ አምላክ አድርጎ ስለሚገልጻት ነው። አንስታይንም ተፈጥሮን አምላክ ብሎ ይጠራት ነበር፡፡
ስፒኖዛ ከጥቃቅን ነገሮች ወይም ተፈጥሮን/አምላክን ለመረዳት መጓዝ አለብን ይለናል፡፡ በተፈጥሮ ሁነቶች ተነስተን ውስጥ ራሳችንን እያስመጥን ስንመጣና ከተፈጥሮ ጋር ፍጹም አንድ ስንሆን፣ መታበያችን ከእኛ ይርቃል። እኔ እንዲህ ነኝ ማለትንም እናቆማለን፡፡ ራሳችንንም ነጥለን የምንኮራበት አልያም የምንወቅስበት ምክንያት አይኖርም... ምክንያቱም “እኔ” የሚባል ማንነት
አይኖረንም...
ስፒኖዛ የሰው ልጆች ሕይወታቸውን አወሳስበው ይኖራሉ ይለናል። ልክ እንደ ህጻናትም በጸደይ አበባ መሃል ከመቦረቅ ይልቅ፣ በብዙ ጥቃቅን ጉዳዮች ራሳችንን አስረነዋል። ይህ የሚገባን ግን እድሜያችን ሲገፋ ብቻ ነው፡፡ በእርጅና ዘመናችን በወጣትነታችን የነበሩ አላስፈላጊ ጭንቀቶቻችን እና ፍርሃቶቻችን ይገለጡልናል። ሕይወታችን ውስጥ ያሉ ነገሮችንም መውደድ እና ማድነቅ እንጀምራለን፡፡
@zephilosophy
@zephilosophy