ሰይጣንም ለቄሱ እንዲህ አለ
"እኔ ከሞትኩ በችጋር እንደሚሞቱ አይገነዘቡምን? ዛሬ እኔን እንድሞት ጥለውኝ ቢሄዱ ነገ ምን ሰርተው ይኖራሉ? ስሜ ከምድረ ገፅ ድራሹ ቢጠፋ እርስዎ በምን አይነት ሙያ ህይወትዎን ይገፋሉ? ለአስርታት ዓመታት በነዚህ መንደሮች እየተዘወዘወሩ ሰዎችን በወጥመዴ ውስጥ እንዳይወድቁ ሲያስጠነቅቁ ኖረዋል፡፡ እነሱም ለምክሮዎት እና ለአስተምህሮትዎት ውለታ ለመክፈል ሲሉ ደክመው ለፍተው ከሚያገኙት ገንዘብ እና ጥሪት ሲለግሱዎት ቆይተዋል፡፡
ነገ እኔ ክፉ ጠላታቸው መሞቴንና ከዚህ ወዲያ እንደማልኖር ካወቁ ከእርስዎ ዘንድ ምን የሚገዙት ምክርና አስተምህሮ ይኖራቸዋል? ሰዎቹ ከኃጢያት በአስተማማኝ ሁኔታ ስለሚድኑ የዕለት ጉርስዎትን የሚያገኙበት ሥራዎትም ከእኔ ጋር ይሞታል፡፡ እንደ አንድ ቄስነትዎ የሰይጣን መኖር በራሱ የእኔን ጠላት ቤተ-ክርስቲያንን እንደፈጠረ አያውቁምን? ከአማኞች ኪስ ውስጥ የወርቅና የብር ሳንቲሞችን እያወጣ በናንተ በሰባኪዎች እና በወንጌላዊያን ኪስ ውስጥ የሚጨምረው ምስጢራዊ እጅ ይሄ ከጥንት ጀምሮ የነበረው ግጭታችን መሆኑን አያውቁምን?
በርግጠኝነት ክብርዎትን፣ ቤተ-ክርስቲያንዎትን ቤትዎትንና እንጀራዎትን እንደሚያሳጣዎ እያወቁ እንዴት እኔን በዚህ ቦታ እንድሞት ትተውኝ ይሄዳሉ?››
ከድርሰቱ የተቀነጨበ
@zephilosophy
"እኔ ከሞትኩ በችጋር እንደሚሞቱ አይገነዘቡምን? ዛሬ እኔን እንድሞት ጥለውኝ ቢሄዱ ነገ ምን ሰርተው ይኖራሉ? ስሜ ከምድረ ገፅ ድራሹ ቢጠፋ እርስዎ በምን አይነት ሙያ ህይወትዎን ይገፋሉ? ለአስርታት ዓመታት በነዚህ መንደሮች እየተዘወዘወሩ ሰዎችን በወጥመዴ ውስጥ እንዳይወድቁ ሲያስጠነቅቁ ኖረዋል፡፡ እነሱም ለምክሮዎት እና ለአስተምህሮትዎት ውለታ ለመክፈል ሲሉ ደክመው ለፍተው ከሚያገኙት ገንዘብ እና ጥሪት ሲለግሱዎት ቆይተዋል፡፡
ነገ እኔ ክፉ ጠላታቸው መሞቴንና ከዚህ ወዲያ እንደማልኖር ካወቁ ከእርስዎ ዘንድ ምን የሚገዙት ምክርና አስተምህሮ ይኖራቸዋል? ሰዎቹ ከኃጢያት በአስተማማኝ ሁኔታ ስለሚድኑ የዕለት ጉርስዎትን የሚያገኙበት ሥራዎትም ከእኔ ጋር ይሞታል፡፡ እንደ አንድ ቄስነትዎ የሰይጣን መኖር በራሱ የእኔን ጠላት ቤተ-ክርስቲያንን እንደፈጠረ አያውቁምን? ከአማኞች ኪስ ውስጥ የወርቅና የብር ሳንቲሞችን እያወጣ በናንተ በሰባኪዎች እና በወንጌላዊያን ኪስ ውስጥ የሚጨምረው ምስጢራዊ እጅ ይሄ ከጥንት ጀምሮ የነበረው ግጭታችን መሆኑን አያውቁምን?
በርግጠኝነት ክብርዎትን፣ ቤተ-ክርስቲያንዎትን ቤትዎትንና እንጀራዎትን እንደሚያሳጣዎ እያወቁ እንዴት እኔን በዚህ ቦታ እንድሞት ትተውኝ ይሄዳሉ?››
ከድርሰቱ የተቀነጨበ
@zephilosophy