ተቅዋ የሱና እና የተውሒድ ቻናል


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Din


ተውሒድና ሱና የአንድነት ምንጭ ሲሆኑ
ሺርክና ቢድዓ ደግሞ የልዩነት ምንጭ ናቸው።
ስለዚህ ተውሒድና ሱና አጥብቀህ ያዝ
ሺርክና ቢድዓ ደግሞ በእጅጉ ራቅ
አላህ ቁርኣንና ሐዲስን በደጋግ ቀደምቶች መንገድ
አረዳድ ተረድተው ከሚጓዙ ምርጥ ባሮቹ ያርገን

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
Din
Statistika
Postlar filtri


ሸይኽ ሰዕዲይ (ረሒመሁሏህ) እንዲህ ይላሉ:-

"የወጣትነቱን ግዜ የተጠቀመና (የስራው) መዝገብ ከመጠቅለሉ በፊት   በተውበትና (ወደጌታው) በመመለስ የተቻኩለን ባሪያ አላህ ይዘንለት"

【አል ፈዋኪሁ ሸሂያህ 217】

ወንድሜ -ወጣትነትም ያልፋል
_ሀይልም ይደክማል
_ገንዘብም ያልቃል
ስለዚህ ኋላ ከመፀፀትና ከመለደም በፊት ወደጌታችን እንመለስ

=https://t.me/tdarna_islam


ተቅዋ የሱና ቻናል dan repost
"የፍቅር  መጀመሪያው  ትዳር  ሲሆን

መጨረሻው  ደግሞ  ጀነት  ነው"

አላህ  ፍቅር  እስከ  ጀነት  ይወፍቀን!!

በችግርም በደስታም ግዜ ሳንነጣጠል
አብረን ተያይዘን  ተሳስበ፣ን ተዛዝነን ፣ተዋደን
ዱኒያን   የምንሾልካት ያድርገን በጀነተል ፊርዶወስም በአንድ ላይ ይሰብስበን አሚን!!

=https://t.me/abuluqmanibnidris


ሚስት ከአጅነቢይ ወንድ በራቀችና ለትዳራ ታመኝ በሆነች ቁጥር ለትዳራ ና ለባሏ ያለት ፍቅርና እንክብካቤ ዞትር እያጨመራ ይሄዳል።

ልክ እንደዛው ከአጂነቢይ ወንድ በምንም አይነት ምክንያት በተቀረበች ቁጥር ለትዳራና ለባሏ ያለት እንክብካቤ ና ፍቅር እያቀነሳ ይሄዳል አልፎም ወደ ፍቺ ይወስዳታል ስላዚህ ሚስት ሆይ ምርጫዉ የረስሽ ነው




ተቅዋ የሱና ቻናል dan repost
ሷሊህ የሆኑ ሰዎች ከወንጀል ነፃ አይምሰሉህ!
ኢብኑል ቀይም እንዲህ ይላሉ:—
"ሷሊህ የሆኑ ሰዎች ከወንጀል የነፁ ይመስሉሃልን!? (አይደሉም) ነገር ግን እነሱ (ወንጀልን ሲፈፅሙ) ገሀድ ከማውጣት ስለደበቁ፣ መሀርታን ሰለለመኑ እና በወንጀል ላይ ስላልዘወተሩ ፣ ወንጀል ስለመስራታቸው ምክንያትን ከመደርደር ጥፋታቸውን ስላመኑና ፀያፍ ነገር ከፈፀሙ በኋላ መልካምን ሰለሚያሰከትሉ እንጂ::"
ከሰለፎች አንዱ:— (አንተ ከዲንህ ጋር እንዴት ነህ?) ተብለው ተጠየቁ:—
እሳቸውም እንዲህ ሲሉ መለሱ:—

(ኢማኔን ወንጀሎቼ እየበጣጠሱት እኔም በኢስቲግፋር እየጠጋገንኩተ አለሁ።) አለ ይባላል።
ውዶቼ:— እኛም ከወንጀል የፀዳን አይደለንም እና ኢስቲግፋር የኢማናችን መጠገኛ ይሁነን።


እህቴ ሆይ ጥብቅ ሁኚ!!

የንጉሱ ሚስት ዩሱፍን በመፈተን
አላገኘችውም። ነገር ግን የሹዐይብ
ልጅ ሐያእ በማድረጓ
ሙሳን ማግኘት
ችላለች!! ሀያእ ይኑርሽ እህቴ!!


➧ታላቁ ዓሊም ዐብዱል ዐዚዝ ኢብኑ ባዝ አላህ ይማራቸውና እዲህ ይላሉ‼️

➺ አንተ እኮ ልትበላና ልትጠጣ አይደለም የተፈጠርከው። ህንፃ ዎችን ልትገነባ ፣ ዛፎችን ልትተክል ፣ ወንዞችን ልትሰነጥቅ ፣ ለወሲባዊ ግንኙነት ወይም ለሌላ አልተፈጠርክም። በፍፁም! አንተ የተፈጠርከው ጌታህን እንድታመልክ ነው ። አንተ የተፈጠርከው በትዛዙ ላይ እንድትፀና እና መልክተኛውን ﷺ እንድትከተል ነው ። የተፈጠርከው ለዚህ ነው ። በምድር ላይ ያለ ነገር ሁሉ አላህን ለመታዘዝ ፣ እሱን ከማመፅም ለመራቅ እንድትታገዝበት ነው የተፈጠረው ። እንጂ ለስሜትህ እንድትታገዝበት አይደለም የተፈጠረው ።[ አል ፈተዋ ፡ 7/98]


☑️ ኢልም (እውቀት) ማለት
🔹የቀልብ ምግብ
🔹የቀልብ መጠጥ
🔹የቀልብ መድሀኒት
🔹የቀልብ ህይወት ሲሆን
🔹በአጠቃላይ የቀልብ መስተካከልም ሆነ መበላሸት በእውቀቱ ልክ
የተመሰረተ ይሆናል።

☑️ ቀልብ ህያው የሚሆነውና የሚለመልመው በእውቀት ሲሆን። የሚደርቀውና የሚሞተው ደግሞ ለእውቀት በመራቁ ይሆናል

http://t.me/Sadik_Ibnu_Heyru


ተቅዋ የሱና ቻናል dan repost
ሸይኽ_ዓብዱረዛቅ_አልበድር ሐፊዞሁሏህ እንዲህ ይላሉ : -

«ሸይጧን ማለት ልክ እንደ መንገድ ቆራጭ (ሽፍታ) አይነት ነው። አንድ ባሪያ ወደ አላህ መጓዝ በፈለገ ጊዜ መንገድ ቆራጭ በመሆን እንዳይሄድ ያደርገዋል። ለዚህም ነው ለከፊል ሰለፎች፦ አይሁዶችና ነሳራዎች እኛ (በሸይጧን) አንወሰወስም ይላሉ ሲባሉ፦ እውነታቸው ነው ሸይጧን ባዶ ቤት ውስጥ ምን ይሰራል? ያሉት።»

📚 ۞ أَحاديثُ إِصلاَحِ القُلوبِ【23】۞


⛔️በትዳራቸው ጉዳይ ላይ በባሏ ላይ የምትጮኽ ሚስት በተመለከተ ሸሪዓው ምን ይላል?

ሸይኽ ኢብኑ ዑሠይሚን ረሂመሁላህይህ ጥያቄ ቀርቦላቸው ቀጣዩን ምላሽ ሰጥተዋል።
መልስ፡ ለዚች ሚስት በባሏ ላይ ድመጿን ከፍ ማድረጓ መጥፎ ስነምግባር ነው እንላለን።
ይህ የሆነበት ምክንያት ባልየው የበላይ ጠባቂዋ(ቀውዋማ) እና ተንከባካቢዋ ነው። ስለዚህ እሱን አክብራ በትህትና መናገር አለባት። ይህን ማድረግ በመካከላቸው የትዳራቸው እድሜ የመራዘም  ዕድሉ ከፍተኛ እንዲሆን ያደርጋል። እናም በሁለት የትዳር አጋሮች ቅርርብ በመካከላቸው እንዲኖር ያደርጋል። ባልየውም ከእርሷ ጋር በመልካም መስተጋብር ሊኗኗር ይገባል። መልካም መስተጋብር ሁለቱም በጋራ ሊያስገኙት የሚገባ ነገር ነው። አላህ አዘወጀለ እንዲህ ይላል፦

وَعَاشِرُوهُنَّ بِٱلۡمَعۡرُوفِۚ فَإِن كَرِهۡتُمُوهُنَّ فَعَسَىٰۤ أَن تَكۡرَهُوا۟ شَیۡـࣰٔا وَیَجۡعَلَ ٱللَّهُ فِیهِ خَیۡرࣰا كَثِیرࣰا
(ሚሰቶቻችሁን) በመልካምም ተኗኗሩዋቸው፡፡ ብትጠሉዋቸውም (ታገሱ)፡፡ አንዳችን ነገር ብትጠሉ አላህም በእርሱ ብዙ ኸይር ነገርን ሊያደርግ ይቻላልና፡፡ (አንኒሳእ:19)
እኔ ለዚች ሚስት የምመክረው ለራሷስትል በባልዋ ጉዳይ አላህን እንድትፈራ እና በእሱ ላይ ድምጿን ከፍ እንዳታደርግ (እንዳትጮህ) ነው። በተለይ ባሏ በእርጋታ  እና ድምፁን እየቀነሰ እያናገራት ከሆነ። ሁሉን ቻይ የሆነውን አምላክ እንድትፈራ እመክራለሁ።”

فتاوى نور على الدرب الشريط رقم [312]


=
t.me/Sadik_Ibnu_Heyru


ባልና ሚስት በፍች በሚለያዩ ጊዜ ህፃናት ልጆችን መበቃቀያ ማድረግ አይገባም። አንዳንድ ወንዶች ጨቅላ ህጻንን ከእናት በመንጠቅ መበቀያ ያደርጋሉ። እንደዚሁም አንዳንድ ሴቶች ልጁን አስታቅፌ ህይወትን ፈተና አደርግበታለሁ በሚል አጉል እሳቤ የአብራካቸውን ክፋይ ልክ እንደማይረባ ቁስ ገፍተው ይሰጣሉ። እዚህ መሀል ላይ ልጆች ብዙ ግፍና መከራ ያስተናግዳሉ።
በመጀመሪያ አብሮ መኖር ያልሆነላቸው ጥንዶች እንደ ጠላት ሊተያዩ አይገባም። በመሀላቸው የማይበጠስ ገመድ አለ፣ ኢስላም። ቢለያዩም እህቱ ነች፤ ወንድሟ ነው። ልጅ ሲኖር ደግሞ የማይቆረጥ ዝምድና ተፈጥሯል። የልጇ አባት ለሴቷ፣ የልጁ እናት ለወንዱ ተራ ሰዎች አይደሉም። ልጆች ለኛ ቅርብ እስከሆኑ ድረስ የነሱ ቅርብ ሰዎች ለኛም ቅርቦች ናቸው። ከዚህም አልፎ አብረው በትዳር የኖሩበትንም ዘመን መርሳት አይገባም። "ምንስ ቢሆን አብረን በአንድ መአድ በልተናል'ኮ!" ይላል ያገራችን ሰው። ልጅ እስከማፈራት የደረሰ ህይወት ሲያሳልፉ ደግሞ ይለያል።
﴿وَلا تَنْسَوُا الْفَضْلَ بَيْنَكُمْ﴾
ወደ ጀመርኩት ነጥብ ስመለስ መለያየት ከገጠመን ፈፅሞ ልጆቻችን መበቃቀያ ልናደርጋቸው አይገባም። እንዲያውም በተቻለ መጠን በወላጆች መለያየት የተነሳ የሚገጥማቸውን ማንኛውንም አይነት ጎዶሎ በመመካከር ለመሙላት መጣር ይገባል።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


በመውሊድ ዙሪያ ለበድሩ ሑሴን አሳሳች ንግግር የተሰጠ እርምት
~
መስከረም 26/2017
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


አንድ አዕራቢይ(ገጠሬ) ከኢማሙ ሻዕቢይ ጋር ይቀማመጣል ነገር ግን ዝምታን ያበዛ ነበር ፤
ሻእቢይ አንድ ቀን እንዲህ አሉት:-"አታወራምን?"
አእራቢዩም እንዲህ ሲል መለሰላቸው "ዝም እላለው ከመጥፎ ነገር እድናለሁ፣ አዳምጣለሁ እውቀት አገኛለሁ፤ የአንድ ሰው ከጆሮው ያለው ድርሻ ለራሱ ሲሆን በምላሱ ያለው ድርሻ ለሌላ ሰው ነው..."

እና ወዳጄ ከመናገርህ በፊት ማድመጥን ልመድ!!

ምንጭ ፦
📙((وفيات الأعيان)) لابن خلكان (3/14)


እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በዐርብ ቀን ለስግደት ጥሪ በተደረገ ጊዜ አላህን ወደ ማውሳት ኺዱ መሸጥንም ተው ይህ የምታውቁ ብትኾኑ ለእናንተ በጣም የተሻለ ነው 
ሶለቲቱም በተፈጸመች ጊዜ በምድር ላይ ተበተኑ ከአላህም ችሮታ ፈልጉ አላህንም በብዙ አውሱ ልትድኑ ይከጀላልና
ንግድን ወይም ዛዛታን ባዩ ጊዜም ቆመህ የተዉህ ሲኾኑ ወደእርሷ ይበተናሉ አላህ ዘንድ ያለው ዋጋ ከዛዛታም ከንግድም በላጭ ነው «አላህም ከሰጪዎቹ ሁሉ ይበልጥ ሲሳይን ሰጭ ነው» በላቸው ፡፡
[📚ሱረቱ አል-ጁሙዓህ 9-11] 
       


▪️ከትዳር አትሽሹ!!

🔻እህቶቼ ሆይ! ሚስቶቻቸውን የሚያሰቃዩ ባሎች እንዳሉ ሁሉ የሚንከባከቡም አሉና ከእናንተ የሚጠበቀው ከትዳር መሸሽ ሳይሆን አሏህ ሆይ! መልካሙን ወፍቀኝ ብሎ ዱዓ በማድረግ ወደትዳር መግባት ነው።
ኢንሻ አላህ አሰብ እያደረጋችሁ ወደ ሀላል ግቡ!!
አላህ በሀላል  ይሰትረን።።


አሳዛኝ እውነታ!!
ወንድሞቼና እህቶቼ ወደ አላህ እንመለስ!!!
ቁርአን አይነበብም! ሓዲስ ተዘንግቷል የዑለሞቻችን መፃህፍት ምልከታ ተነፍጓቸዋል! ሶሓቦች ታቢዒዮች ኢማሞቻችን ተረስተዋል መስጂዶቻችን ወጣቶችን ናፍቀዋል!
አላህን መፍራት ቀረ!!! والله! !!
በተቃራኒው— ምናምንቴ የግጥም መድብሎች ይኮመኮማሉ— ይሸመደዳሉ! የአዝማሪዎች ሰይጣናዊ ጩኸትና ማንቋረር ይደመጣል! የማያውቁንና የማይጠቅሙን ተጫዋቾችና ብልሹ አክተሮች ስማቸው ከነ ታሪካቸው ይሸመደዳል— የመኪኖቻቸቸው ስምና ብዛት ሳይቀር!
አላህ ይመልሰን! !


🍃የነቢዩ ተወዳጅ ልብስ ቀሚስ (ጀለቢያ)

ከዑሙ ሰለማ ) ተይዞ፡ እንዲህ ትላለች፦

﴿كان أحبَّ الثيابِ إلى رسولِ اللهِ ▫️ القميصُ﴾

“ተወዳጅ የረሱል ልብስ ቀሚስ ነበር።”

📚 አቡ ዳውድ ዘግበውታል አልባኒ ሶሂህ ብለውታል፡ 4025


🔖ወሳኝ መልእክት ለሴቶች

ብዙ ሴቶች ካገባሁ በኋላ ኢማኔ ደከመ፣ የኢባዳ ጥፍጥና አጣሁ… ሌላም ይላሉ።

ሚስጥሩ ወዲህ ነው። እሱም የባልሽ ሀቅ ስላልተወጣሽ ነው ሚሆነው። ባልሽ የማታከብሬ ፣ ትእዛዙን የምትጥሺ፣ አዛ ምታደርጊውና አሳንሰሽ ምትመለከቺው ከሆነ እንኳን የኢማን ጥፍጥና ማጣት ሌላም ነገር ይፈራልሻል።

ነብዩ እንዲህ ብለዋል።
(ሴት ልጅ የኢማን ጥፍጥና አታገኝም የባሏን ሀቅ በትክክል እስክታደርስ ድረስ።)


⭕️👉ወደ ሰዎች ፈላጊ አትሁን..!

‏قال الإمام ابن تيمية:

አቡል አባስ አህመድ ኢብኑ ተይሚያህ እንደዚህ  ይላሉ..

ومتى كنت مُحتاجاً إليهم -أي الناس- نقص الحب والإكرام والتعظيم بِحسب ذلك، وإن قضَوا حاجتك.

▪️ወደ ሰዎች ፈላጊ ሆነህ በተገኘህ ቁጥር ላንተ ያላቸው ውዴታ፣ ከበሬታ፣ ማላቅ የወረደ ይሆናል እነሱን በጠየከው ልክ።

ሀጃህን ( ከነሱ የፈለከውን) ቢፈፅሙልህም

📚الفتاوى (٤١/١)


ሰደቃ ከገንዘብ ላይ አታጎድልም!

አላህ ) እንዲህ ይላል፦


قُلْ إِنَّ رَبِّي يَبْسُطُ الرِّزْقَ لِمَن يَشَاءُ مِنْ عِبَادِهِ وَيَقْدِرُ لَهُ ۚ وَمَا أَنفَقْتُم مِّن شَيْءٍ فَهُوَ يُخْلِفُهُ ۖ وَهُوَ خَيْرُ الرَّازِقِينَ

“ጌታዬ ሲሳይን ከባሮቹ ለሚሻው ሰው ያሰፋል፡፡ ለእርሱም ያጠብባል፡፡ ከማንኛውም ነገር የምትለግሱትን እርሱ ይተካዋል፡፡ እርሱም ከሲሳይ ሰጪዎች ሁሉ በላጭ ነው” በላቸው፡፡۝

📖 ምዕራፍ ሰበእ: 39

ረሱል ) እንዲህ ብለዋል፦

﴿ما نقصت صدقةٌ من مالٍ، وما زاد اللهُ عبدًا بعفوٍ إلا عزًّا، وما تواضع عبدٌ إلا رفعه اللهُ﴾

“ሰደቃ (ምፅዋት) ከገንዘብ ላይ አታጎድልም። አንድ ባሪያ ይቅር አይልም አላህ የበላይነትን ቢጨምርለት እንጂ። አንድ ባሪያ ለአላህ ብሎ አይተናነስም አላህ ከፍ የሚያደርገው ቢሆን እንጂ።”

ሙስሊም ዘግበውታል: 2588

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.