Ethiopian Media Authority


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


This channel is an official channel of Ethiopian Media Authority (EMA).
EMA is an autonomous government organization accountable to the House of Peoples’ Representatives of the FDRE.

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
መገናኛ ብዙኃን እና በማስታወቂያ ይዘቶች ላይ የህግ ጥሰት፣ የሙያ ስነ-ምግባር ግድፈት፣ የጥላቻ ንግግር እና የሐሰተኛ መረጃ ሲመለከቱ በ9192 ነፃ የስልክ መስመር ደውለው ማሳወቅዎን አይርሱ፡፡


እንኳን ለ129ኛው የአድዋ ድል በዓል አደረሳችሁ!


ማንኛውም የብሮድካስት አገልግሎት ባለፈቃድ የህዝብ ጥቅምና የጋራ ሀገራዊ እሴቶች  እንዲጠናከሩ አስተዋፅኦ የሚያደርግ አገልግሎት የመስጠት ግዴታ አለበት፡፡

የህዝብ ጥቅምና የጋራ ሀገራዊ እሴቶችን ማጠናከር ይገባል!


Disseminating hate speech is prohibited!

According to Hate Speech and Dissemination Prevention and Suppression Proclamation No 1185/2020, Article 4: “Any person disseminating hate speech by means of broadcasting, print, or social media using text, image, audio, or video is prohibited.”


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
በህትመት ሥርጭት ላይ የሚገለፁ መረጃዎች

#ብቁ_መገናኛ_ብዙኃን_ለማህበረሰባዊ_ንቃት
#የጥላቻ_ንግግርና_ሐሰተኛ_መረጃን_በጋራ_እንከላከል


የጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃ የቤተሰብን፣የአካባቢን ብሎም  የሀገርን ልማት የሚጎዳ እና ለትዉልድ የማይበጅ አስከፊ ተግባር ነዉ!

በመሆኑም የጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃ የሚያሰራጩትን በማጋለጥ የበኩላችንን እንወጣ!

#የጥላቻ_ንግግርና_ሐሰተኛ_መረጃን_በጋራ_እንከላከል


38ኛው የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔን ላስተባበሩ  ባለሙያዎች  የምስጋና መርሐ-ግብር ተካሄደ

አዲስ አበባ፣ የካቲት 19/2017 ዓ.ም (Ethiopian Media Authority)

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ከአፍሪካ ህብረት ጋር በመተባበር 38ኛውን የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ለመዘገብ የመጡ ጋዜጠኞችን ላስተባበሩ የተቋሙ ባለሙያዎች የምስጋና መርሐ-ግብር አካሂዷል፡፡

በመርሐ-ግብሩ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ሳምሶን መኮንን ዶ/ር፤ የተቋሙ ተልዕኮ እውን ከማድረግ አንፃር ባለሙያዎቹ በአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ ላይ ለመዘገብ ለመጡ ጋዜጠኞችን ከማስተባበርና ምቹ ሁኔታዎችን ከመፍጠር አንጻር ውጤታማ እንደነበር ተናግረዋል፡፡

የተሰራው ስራ ገጽታ ከመገንባት አንጻር ሚናው የላቀ  መሆኑን ገልፀው፤ ለዚህ ውጤታማነት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ላበረከቱ የተቋሙ የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ምስጋና አቅርበዋል፡፡ ቀጣይ እንደ ቷቋምና እንደ ሀገር በሚሰሩ ስራዎች ላይ ይህንን መሰል የስራ ተነሳሽነትን አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባም ዋና ዳይሬክተሩ አያይዘው ተናግረዋል፡፡

በመርሐ-ግብሩ ባለሥልጠኑ የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔን ለመዘገብ ለመጡ የመገናኛ ብዙኃን ባለሙያዎች ባደረገው ተሳትፎ ዙሪያ ሪፖርት የቀረበ ሲሆን፤ ጉባዔውን ሽፋን ለመስጠት ከ አንድ ሺህ በላይ የሀገር ውስጥና የውጭ  የሚዲያ አካላትና ጋዜጠኞች  ሙሉ አገልግሎት እንደተሰጠ ተገልፃል፡፡ 

የ38ኛዉ የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባዔ የሚዲያ አካላትን ላስተባበሩ የተቋሙ ባለሙያዎች የምስጋና የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል፡፡


ማንኛውም ሰው የሐሰት መረጃን በማንኛውም ሁኔታ ማሰራጨት የለበትም!

ማንኛውም ሰው የሐሰት መረጃን በአደባባይ ስብሰባዎች በብሮድካስት፣ በህትመት ወይም በማህበራዊ ሚዲያዎች ወይም በሌላ ተመሳሳይ ዘዴዎች አማካኝነት በፅሁፍ፣ በምስል፣ በድምፅ ወይም በቪዲዮ ማሰራጨት የተከለከለ ተግባር ነው፡፡

#የጥላቻ_ንግግርና_ሐሰተኛ_መረጃን_በጋራ_እንከላከል


ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን  ከዚህ በታች በተመለከቱት የስራ መደቦች ላይ ስራ  ፈላጊዎችን አወዳድሮ  መቅጠር ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች በተባለው ጊዜና ቦታ ተገኝታችሁ እንድታመለክቱ እናሳውቃለን፡፡


ሀሳብን በነፃነት የመግለጽ መብታችንን ስንጠቀም በሌሎች ላይ ጥላቻ ወይም መድልዎ የሚያስፋፋ ንግግር አለመሆኑን እናረጋግጥ!

#የጥላቻ_ንግግርና_ሐሰተኛ_መረጃን_በጋራ_እንከላከል




ለመጀመሪያ ጊዜ የተሰጠ የሬዲዮ ሞገድን በመጠቀም የሚሰራጭ የሬዲዮ ብሮድካስት አገልግሎት ፍቃድ ጸንቶ የሚቆይበት ጊዜ፡-

1. በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚሰራጭ ሲሆን ለ10 ዓመት
2. የሥርጭት ሽፋኑ በክልል ደረጃ የተወሰነ ሲሆን ለ8 ዓመት
3. የሥርጭት ሽፋኑ በአካባቢ ደረጃ የተወሰነ ከሆነ ለ6 ዓመት
4. የማኅበረሰብ ብሮድካስት አገልግሎት ፍቃድ ከሆነ ለ10 ዓመት፤ እና
5. የአጭር ጊዜ የማኅበረሰብ ብሮድካስት አገልግሎት ፍቃድ ከሆነ ለ1 ዓመት ዪሆናል፡፡

#ብቁ_መገናኛ_ብዙኃን_ለማህበረሰባዊ_ንቃት


ማንኛውም ሰው ከባለሥልጣኑ የብሮድካስት ፍቃድ ሳይሰጠው ወይም በታገደ ወይም በተሰረዘ ፍቃድ የብሮድካስት አገልግሎት ማሠራጫ መንገዶችን ተጠቅሞ በብሮድካስት አገልግሎት ሥራ ላይ መሰማራት አይችልም፡፡

#ብቁ_መገናኛ_ብዙኃን_ለማህበረሰባዊ_ንቃት


የመገናኛ ብዙኃን አዋጅ ቁጥር 1238/2013 አንቀፅ 48 ንዑስ (1 ) እንደሚያስረዳው ማንኛውም መገናኛ ብዙኃን ተግባሩን ለመወጣት፡-

• ዜና ወይም መረጃን የመሰብሰብ፣ የመቀበልና የማሰራጨት
• በልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ አስተያየት ወይም ትችት የማቅረብ
• ዘመናዊ የመገናኛ ዘዴዎችን፣ መሣሪያዎችን የመጠቀም እና
• የተለያዩ ሌሎች ዘዴዎችን በመጠቀም የሕዝብን አስተያየት በመቅረፅ ሂደት መሳተፍ አለበት፡፡
 
*በመገናኛ ብዙኃን እና በማስታወቂያ ይዘቶች ላይ የህግ ጥሰት፣ የሙያ ስነ-ምግባር ግድፈት፣ የጥላቻ ንግግር እና የሐሰተኛ መረጃ ሲመለከቱ በ9192 ነፃ የስልክ መስመር ደውለው ማሳወቅዎን አይርሱ፡፡

#ብቁ_መገናኛ_ብዙኃን_ለማህበረሰባዊ_ንቃት


የጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃ የቤተሰብን፣የአካባቢን ብሎም የሀገርን ልማት የሚጎዳ እና ለትዉልድ የማይበጅ አሻራ ነዉ ፡፡

በመሆኑም ማንኛውም የማህበራዊ ሚዲያ አገልግሎት የሚሰጥ ድርጅት የጥላቻ ንግግርና የሐሰተኛ መረጃ ስርጭትን ለመቆጣጠርና ለመግታት ጥረት ማድረግ አለበት።

 በመገናኛ ብዙኃን እና በማስታወቂያ ይዘቶች ላይ የህግ ጥሰት፣ የሙያ ስነ-ምግባር ግድፈት፣ የጥላቻ ንግግር እና የሐሰተኛ መረጃ ሲመለከቱ በ9192 ነፃ የስልክ መስመር ደውለው ማሳወቅዎን አይርሱ፡፡

#የጥላቻ_ንግግርና_ሐሰተኛ_መረጃን_በጋራ_እንከላከል


የመገናኛ ብዙኃን ዘርፉን በብቃት እና በጥራት በማስፋፋት ለሁሉም ዜጎች መረጃን ተደራሽ ለማድረግ የመገናኛ ብዙኃን ፖሊሲ ተዘጋጅቶ በትግበራ ላይ ይገኛል፡፡ ፖሊሲውም የሚከተሉት ዋና ዋና ግቦች አሉት፡፡

•  ሁሉም መገናኛ ብዙኃን በሕገ መንግሥቱ የተሰጣቸውን መብትና ግዴታ በመወጣት የሚጠበቅባቸውን ሚና እንዲጫወቱ ማድረግ
•  አመኔታና እርካታን ማሳደግ
•  ቅንጅታዊ አሰራርን ማጎልበት
•  የሕዝብን ጥቅም ማስቀደም
•  ሀገራዊ ባህልና እሴትን ማጠናከር ናቸው፡፡


የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃ የሚያሰራጩትን በመቃወምና በማጋለጥ ከጥላቻ የጸዳች ሀገር እንገንባ!

የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃ ለሀገራዊ አንድነትና መረጋጋት፣ ለዜጎች ደህንነት እንዲሁም ለዲሞክራሲያዊ ስርዓት ግንባታ ፈተና  ሆነዋል። በመሆኑም የጥላቻ ንግግርና ሐሰተኛ መረጃ የሚያሰራጩትን በማጋለጥና በመቃወም የዜግነት ግዴታችንን ልንወጣ ይገባል፡፡

#ብቁ_መገናኛ_ብዙኃን_ለማህበረሰባዊ_ንቃት
#የጥላቻ_ንግግርና_ሐሰተኛ_መረጃን_በጋራ_እንከላከል


ያለክፍያ ስለሚሰጡ ቅጅዎች

ማንኛውም ሀገር አቀፍ ሥርጭት ያለው በየጊዜው የሚወጣ ህትመት አሳታሚ ህትመቱ ታትሞ ከወጣ ከ5 ቀናት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ የእያንዳንዱን  እትም 2 ቅጂዎች ያለ ክፍያ ለብሔራዊ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መፃህፍት ኤጀንሲ መስጠት አለበት፡፡

በአንድ ክልል ውስጥ ብቻ የሚሰራጭ በየጊዜው የሚወጣ ህትመት አሳታሚ ህትመቱ ታትሞ ከወጣ ከ5 ቀናት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ የእያንዳንዱን እትም 2 ቅጂዎች ያለ ክፍያ ለክልሉ ቤተ-መዛግብት ወይም ለሚመለከተው ቢሮ መስጠት አለበት፡፡

#ብቁመገናኛብዙኃንለማህበረሰባዊንቃት


Haasaan Jibbinsaa fi Odeeffannoon Sobaa babal’achuun, sirna Hawaasummaa, Tasgabbii Siyaasaa, Tokkummaa ummataa, kabaja dhala namaa, Hedduminaafi Walqixxummaaf balaadha. Kanaaf gocha suukaneessaa kana ittisuu fi to’achuuf namni hunduu gahee isaa bahachuu qaba.

Haala kamiinuu haasaa jibbinsaa fi Odeeffannoo Sobaa yeroo argitan lakkoofsa bilbila bilisaa 9192 bilbiltanii gabaasuu hin dagatinaa.



20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.