የዓለም ሀገራት ትናንት ትራምፕና ዘለንስኪ ያደረጉትን ሀይለ ቃል የተሞላበት ውይይት ተከትሎ አስተያየታቸውን እየሰጡ ይገኛሉ።
ፈረንሳይ፦ ፕሬዝዳንት ማክሮን "ወራሪ አለች ሩሲያ፣ ተጎጂ አለች ዩክሬን" በማለት ለዩክሬን ያላቸውን ድጋፍ አሳይተዋል።
"ከሶስት አመት በፊት ዩክሬንን መርዳታችንና ሩሲያ ላይ ማዕቀብ መጣላችን ልክ ነበር" ያሉት ፕሬዚዳንቱ ይህ እርምጃ ወደ ፊትም ይቀጥላል ብለዋል።
ዩናይትድ ኪንግደም፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታርመር "መከባበር የተሞላበት ዲፕሎማሲ ለሰላም ወሳኝ ነው። የአውሮፓ መከፋፈል የሚጠቅሙ ሩሲያን ነው" ያሉት ስታርመር የትኛውም የሰላም ስምምነት ዩክሬንን ያሳተፈ ሊሆን እንደሚገባ አብራርተዋል።
ኖርዌ፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ጆናስ ስቶሬ፣ "ከነጩ ቤተመንግሥት የተመለከትነው ነገር ልብ የሚሰብር ነው" ብለዋል። ትራምፕ ዘለንስኪን "በሶስተኛው የአለም ጦርነት እየተጫወትክ ነው ያሉት ንግግር ምክንያታዊ አይደለም" በማለት ተችተዋል።
ፖላንድ፦ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶናልድ ተስክ፣ "የተከበሩ ዘለንስኪ፣ የተከበራችሁ የዩክሬን ወዳጆች ብቻችሁን አይደላችሁም" ሲሉ አጋርነታቸውን አሳይተዋል።
ጀርመን፦ አዲሱ ፕሬዝዳንት ሜርዝ፣ "በጥሩውም ሆነ በመጥፎው ጊዜ ከዘለንስኪና ከዩክሬን ህዝብ ጎን እንቆማለን" ብለዋል።
ሩሲያ፦ ምንም እንኳን በመንግሥት በኩል ይፋዊ አስተያየት ባይሰጥም ከፍተኛ ባለሥልጣናት ግን ብዙዎችን ላስቆጣው ውይይት አድናቆት ሰጥተውታል።
የቀድሞው ፕሬዝዳንትና የአሁኑ የሩሲያ ደህንነት ምክርቤት ምክትል ሀላፊ ድሜትሪ ሜድቬዴቭ፣ "ትራምፕ ትክክል ናቸው፤ የኪቭ አገዛዝ በሶስተኛው የአለም ጦርነት እየቀለደ ነው" ሲሉ በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው አስፍረዋል። #foxnews#independent#theglobeandthemail
@ThiqahEth