ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


This channel is not operated by Deacon Yaregal Abegaz- ይህ ገጽ የሚንቀሳቀሰው በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ አይደለም
https://youtube.com/@yaregalabegaz?si=1f5NHTaQ2l2LbxWQ
“ዕለት ዕለት የሚከብድብኝ የአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ አሳብ ነው።”
— 2ኛ ቆሮ 11፥28

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ dan repost
“ላገቡት” የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ምክር

ባልና ሚስት አንድ መኾናቸውን ብዙ ጊዜ ስለ ተማራችሁት እርሱን አልደግምላችሁም፡፡ ከዚህ ተነሥቼ ግን ጥያቄ ልጠይቃችሁ፦ ከሰውነታችሁ ውስጥ አንዱ ሕዋስ ቢታመም ቆርጣችሁ ትጥሉታላችሁን? ከሕመሙ ይፈወስ ዘንድ የምትጥሩ አይደላችሁምን? ለትዳር አጋራችሁም እንደዚህ መኾን አለባችሁ፡፡ እንደዉም'ኮ፥ ከሰውነታችሁ ሕዋስ ውስጥ ያለው በሽታ አንዳንዴ ላይድን ይችላል፡፡ የትዳር አጋራችሁ ግን፥ ምንም ክፉ ቢኾንም ሊለወጥ ይችላል፡፡ በሰውነታችን ላይ የሚኖረው አንዳንዱ ችግር ለምሳሌ ልምሾ እጅ ወይም እግር ሥራ መሥራትን ሊከለክለን፣ በሌላዉ የሰውነታችን ክፍል ላይ ጫና ሊያሳድርብን ይችላል፤ ነገር ግን ይበልጥ እንክብካቤ እናደርግለታለን እንጂ ቆርጠን አንጥለዉም፡፡ ታዲያ መዳን ለማይችለው ሰውነታችን ይህን ያህል እንብካቤ እያደረግንለት ሳለ፥ የመዳን (የመለወጥ) ዕድል ያለው አካላችንን (ባለ ትዳራችንን) መቁረጥ (መፍታት) እንደ አማራጭ ማስቀመጣችን እንዴት ብናብድ ነው?








ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ dan repost
አንተ ሰው እስኪ ንገረኝ!

አንድን የሥጋ ቁስል ለመፈወስ ለእያንዳንዱ ሰው ከባድ ነው፤ የነፍስን ቁስል መፈወስ ግን ለኹሉም ቀላል ነው፡፡ የሥጋ ቁስል ለመፈወስ መድኃኒት ብሎም ገንዘብ ያስፈልጋል፤ ነፍስን ለመፈወስ ግን ቀላል ብሎም ወጪን የማይጠይቅ ነው፡፡ ሥጋን ከዚያ ከሚያሰቃይ ቁስሉ ለመፈወስ አድካሚ ነው፡፡ ምክንያቱም በቀዶ ጥገና ምላጭ መቀደድ አለበት፤ መራራ መድኃኒቶችም ሊጨመሩበት ይገባል፡፡ ነፍስን ለመፈወስ ግን እንዲህ ዓይነት ነገር አያስፈልግም፡፡ ፈቃደኛ መኾን ብቻ በቂ ነው፤ ፍላጎቱ ካለ ኹሉንም ነገር ለማድረግ ቀላል ነው፡፡ የእግዚአብሔር መግቦቱም እስከ አሁን ድረስ ይህ ነው፡፡ ሥጋ ቢቆስል ያን ያህል ከባድ ጉዳትን አያመጣብንም፤ ምክንያቱም ምንም ባንታመምም እንኳን ሞት መጥቶ ይህን ሥጋችን ያፈርሰዋል፤ ያበሰብሰዋልምና፡፡ ነፍሳችን ብትታመም ግን ጉዳቱ ብዙ ነው፡፡ እግዚአብሔር የነፍስን ሕመም ለመፈወስ መድኃኒቱ ቀላል፣ ምንም ወጪና ስቃይ የሌለበት ያደረገውም ስለዚሁ ነው፡፡ ታዲያ ምንም እንኳን በሕመሙ ምክንያት የሚያገኘን ጉዳት ያን ያህል ብዙ ባይኾንም የገንዘብ ወጪን የሚጠይቀው፣ ሐኪም የሚያስፈልገው፣ ብዙ ስቃይ ያለበት ሥጋችን ሲታመም እርሱን ለማከም እጅግ የምንደክም ኾነን ሳለ፥ እጅግ ብዙ ጉዳት የሚያመጣውን፣ እርሱን ለመፈወስ ወጪ የማይጠይቀውን፣ ለማስታመም ሌሎች ሰዎች የማያስቸግረውን፣ እንደ ምላጩና እንደ መራራ መድኃኒቱ ስቃይ የሌለበትን ይልቁንም ከእነዚህ አንዱስ እንኳን ሳይፈልግ በእኛ ኃይል ባሉ ምርጫና ፈቃድ ብቻ መዳን የሚችለውን፣ ይህን ማድረግ ሳንችል ስንቀርም ከባድ ፍርድና ቅጣት ስቃይም እንደሚያገኘን በእርግጥ እያወቅን የነፍሳችንን ቁስል ችላ የምንል ከኾነ ሊደረግልን የሚችል ምሕረት እንደ ምን ያለ ምሕረት ነው? እኮ የምናገኘው ይቅርታ እንደ ምን ያለ ይቅርታ ነው?

(ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ - ትምህርት በእንተ ሐውልታት መጽሐፍ #በገብረ_እግዚአብሔር_ኪደ የተተረጎመ)


ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ dan repost
አበው ስለ #እመቤታችን_ዕረፍት እንዲህ አሉ፦

"ሌሎች በድንግልና የኖሩ ሴቶች "ለሞት የሚሆኑ ልጆችን አንሰጥህም" በማለት ሞትን ተቃወሙት፡፡ ድንግል ማርያም ግን አንድ ልጅ በመውለድ በልጅዋ ሞት ራሱ እንዲሞት አደረገችው፡፡ ከዐለት ጋር እንደተጋጨ የተፈረካከሰው በማሕፀንዋ ፍሬ ነውና ሞት ወደ እርስዋ ሲቀርብ ተብረከረከ።"
#ቅዱስ_ጎርጎርዮስ_ዘኑሲስ

"ልጃቸው ተሰብስበው ወዳሉበት መጥታለችና አዳምና ሔዋን ዛሬ ደስ አላቸው። በዚህች ቀን ታላቁ ዳዊት በራሱ ላይ የተዋበ አክሊል የደፋችለትን ሴት ልጁን አይቶ ደስ አለው። በዚህች ቀን ነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት የተናገረላት ድንግል ወደ ሙታን ሥፍራ ልትጎበኘው መጥታለችና ደስ አለው። በዚህች ቀን ብርሃን ሲበራባቸው አይተዋልና ነቢያት ሁሉ ከመቃብራቸው ራሳቸውን ቀና አደረጉ። አርያም በጣፋጭ የመላእክት ዝማሬ ተሞላ፣ ምድር ደግሞ ኀዘንን በተሞሉ በሐዋርያት ለቅሶ ተሞላች፡፡ ሙታንም ሕያዋንም ትርጉሙን ሊገልጹት በማይችሉት [የተለያየ] ዜማ ሰውና መላእክት በዚያች ዕለት አብረው ጮኹ።"
#ቅዱስ_ያዕቆብ_ዘሥሩግ

"የቃሉ አገልጋዮችና ምስክሮች የነበሩት ሐዋርያት በሥጋ የወለደችውን የእናቱን ዕረፍትና እርስዋን የሚመለከቱ የመጨረሻዎቹን ምሥጢራትም ማየት ነበረባቸው፡፡ ይህም የሆነው የክርስቶስ የዕርገቱ የዓይን ምስክሮች እንደሆኑ ሁሉ የወለደችውም እናቱ ወደዚያኛው ዓለም ለሸጋገርዋ ምስክሮች መሆን ስላለባቸው ነው።"
#ቅዱስ_ዮሐንስ_ዘደማስቆ

(በ Deacon Henok Haile የተሰበሰበ)


አስተርዮ ማርያም

በዘመነ አስተርዮ የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መገለጥ የሆነበትና የአምላካችን አንድነትና ሦስትነት የተገለጠበት ብቻም ሳይሆን በጥር ፳፩ የከበረች እናቱ ቅድስት ድንግል ማርያም የዕረፍት ቀን በመሆኑ “አስተርዮ ማርያም” በማለት በዓልን አናደርጋለን፡፡

የአምላክ እናት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህ ምድር ላይ ፷፬ ዓመታትን ከኖረች በኋላ መንፈስ ቅዱስ ባስገነዘባት መሠረት በክብር ዐርፋለች፡፡ የዚህን ዓለም መከራና ሥቃይ ለሰዎች ድኅነት የተቀበለችው ክብርት እናታችን በሥጋ ብትሞትም እንደ ልጇ ደግሞ በትንሣኤዋ ተነሥታለች፤ ይህም የሆነው በተቀደሰች ዕለት ነሐሴ ፲፮ ነው፡፡

እመ ብርሃን ከእናትና ከአባቷ ጋር ሦስት ዓመት፣ በቤተ መቅደስ ፲፪ ዓመት፣ ከተወዳጁ ልጅዋ ጋር ፴፫ ዓመት ከሦስት ወር፣ ከጌታችን ዕርገት በኋላ ከወንጌላዊው ቅዱስ ዮሐንስ ጋር ፲፭ ዓመት፣ በድምሩ ፷፬ ዓመት በዚህ በኃላፊው ዓለም ኖራ ጥር ፳፩ ቀን በ፵፱ ዓመተ ምሕረት በክብር ዐርፋለች፡፡

ክርስቲያኖች በሙሉ ይህንን በዓል ልናከብር ይገባልና ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሥርዓትን ሠርታልናለች፡፡ “አስተርዮ ማርያም” በሕዝበ ክርስቲያን ዘንድ የሚከበር በዓል በመሆኑ በሀገራችን ኢትዮጵያ እና በመላው የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ማኅበረሰብ ዘንድ በድምቀት ይከበራል፡፡ በዓሉን የምናከብረውም የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን ከዚህ ዓለም ድካም ማረፍ በማዘከር ብቻ ሳይሆን አማላጅነቷና ተረዳኢነቷን በማሰብና ተስፋ በማድረግ ነው፡፡

ስለዚህም እመ ብዙኃን እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዐሥራት ሀገሯን ኢትዮጵያን እንድታስባት፣ ለእኛም ለሕዝቦቿ ሰላምን፣ ፍቅርንና አንድነትን ታሰጠን እንዲሁም ለነፍሳችን ድኅነትን ትለምልን ዘንድ ዕረፍቷን መዘከር ይገባል፡፡

የአምላካችን እግዚአብሔር ቸርነት፣ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም አማላጅነትና ተረዳኢነት አይለየን፤ አሜን!!!

#ማህበረ_ቅዱሳን


ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል dan repost
''ቦሩ ሜዳ'' የፊት ለፊት የጥያቄና መልስ መድረክ

''ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለምን የአዋልድ መጻሕፍትን ትጠቀማለች ?''

“ቦሩ ሜዳ” በማኅበረ ቅዱሳን ወርኃዊ የስብከተ ወንጌል ጉባኤ ላይ

ቀን፡- ጥር 25/2017 ዓ/ም
ከቀኑ 7፡30 ጀምሮ

በጠቅላይ ቤተ ክህነት አዳራሽ

እርስዎም ከወዳጅ ዘመድዎ ጋር በመገኘት ከአዋልድ ማጻሕፍት ጋር ተያይዞ ያለዎትን ጥያቄ በማንሳት ምላሽ ያገኙ ዘንድ ተጋብዘዋል፡፡


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
ፕሮቴስታንትች የገድል መጽሀፍ ይጽፋሉ፣ ይጠቀማሉ

#ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ




ንሥር መጻሕፍትና የጽሕፈት መሣሪያ (Eagle Books and Stationery) dan repost
ዜና ድጋሚ ኅትመት !

ሳይንስ እና ሃይማኖት

..✍ሳይንስ የሰው ልጅ ከእግዚአብሔር የተሰጠውን አዕምሮ ተጠቅሞ ያስገኘውና በዚህ ዓለም ያለውን የኑሮ ድካም ማቅለያው የዕውቀት ዘርፍ ሲሆን ሃይማኖት ደግሞ ከአምላኩ ከእግዚአብሔር ጋር የሚያገናኘው መንገድ ነው። ነገር ግን የሳይንስን ውሱንነት ያልተረዱ ሰዎች ሃይማኖትን በሳይንሳዊ ዕውቀት ለመተንተን ሲሞክሩና ወደ ተሳሳተ ግንዛቤ ሲያመሩ ይስተዋላል። በሌላ መልኩ ደግሞ ሳይንስ ለመንፈሳዊ ሰዎች እርባና የሌለው ነው ብለው የሚያምኑም አሉ።
ይህንን በተመለከተ ለሚነሱ ጥያቄዎችና ፍልስፍናዊ አስተያየቶች፣ ጸሐፊው መምህር ያረጋል አበጋዝ፣ በዚህ መጽሐፉ ከሳይንስና ከሃይማኖት ጋር በተገናኙ ፍልስፍናዊ አስተሳሰቦች ዙሪያ ሰፊ ጥናት በማድረግ ከጥልቅ ትንታኔ ጋር አቅርቦልናል። ስለሆነም መጽሐፉን አንብበን የተሻለ ግንዛቤ እንድናገኝና እንድንጠቀምበት እየጠየቅኩ፣ ለመምህር ያረጋል ዕድሜና ጤናን ለእናንተ ለአንባብያን ደግሞ መልካም ንባብ እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ።

ቀሲስ ሰሙ ምትኩ (ፕሮፌሰር)
ቦትስዋና የሳይንስና ቴክኖሎጂ ኢንተርናሽናል ዩኒቨርሲቲ




  ይህ መንፈሳዊ እና ሳይንሳዊ እሳቤዎችን የተነተነ በግሩማን ሐሳቦች የታጨቀው [የተሞላው]  በመምህረ ቤተክርስትያን ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የቀረበ ጥዑም ማዕድ[መጽሐፍ ]  ለ ሁለተኛ ጊዜ የታተመ ሲሆን በግዮን መጻሕፍት  ያገኙታል።# ግዮን መጽሐፍት ለመላው ከሀገር ውጪ እና ሀገር ውስጥ ለምትገኙ አንባብያን  በDHL እና በEMS እንዲሁም የ Delivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን ።

ይደውሉልን !📞፦0913083816
                      ፦0912198891
   https://t.me/GhionBookStore1623


ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል dan repost
ስለሆነም በተደጋጋሚ እየተፈጸሙባት የሚገኙትን እነዚህን እኩይ ተግባራት ከዚህ በላይ በዝምታና በትዕግስት ማለፍ መንፈሳዊ ተልዕኮዋን በአግባቡ እንዳትወጣ የሚያደርጋት ከመሆኑም በላይ መብቷን በእጅጉ የሚጋፋ፣ጥንታዊያን አባቶች ለሥርዓተ አምልኮ መፈጸሚያ ሲጠቀሙባቸው የነበሩና በትውልድ ቅብብሎሽ አሁን ያለው ትውልድ የተረከባቸው ንዋያተ ቅድሳቶቿን አደጋ ላይ የሚጥል ሁኔታ ከመፈጠሩም በላይ በሥርዓተ አምልኮዋ ላይ በማላገጥ በምዕመናን ዘንድ ቁጣ እንዲቀሰቀስ የሚያደርጉ በርካታ ተግባራት እየተፈጸሙ በመምጣታቸው ምክንያት እነዚህ እኩይና ጸብ አጫሪ ተግባራት ሕጋዊ እልባት እንዲያገኙ ማድረግ የግድ የሚልበት ደረጃ ላይ ደርሳለች።

ስለሆነም ቅድስት ቤተክርስቲያናችን ጉዳዩን በልዩ ሁኔታ ማጥናት፣መከታተልና ሕግን መሰረት ያደረገ መፍትሔ እንዲያገኙ ማድግ አስፈላጊ ሆኖ ስላገኘችው ወቅታዊ ሁኔታውን በዝርዝር በማጥናት ተቋማዊ እልባት የሚያገኝበትን መንገድ የሚያጠና ኮሚቴ ተቋቁሞ ወደ ሥራ እንዲገባ ያደረገች ሲሆን የቤተ ክርስቲያናችን የሕግ አገልግሎት መምሪያም በሕግ አግባብ ተጠያቂነትን በማረጋገጥ ፍትሕ ማግኘት የሚቻልበትን ሁኔታ ለመፍጠር አስፈላጊውን መረጃ በማሰባሰብና በማደራጀት ክስ መመስረት የሚያስችለውን ሁኔታ በማመቻቸት ወደ ተግባር ለመለወጥ በዝግጅት ላይ ይገኛል።

ከዚህ ጎን ለጎንም ከፍ ሲል እንደተገለጸው በጠቅላይ ቤተክህነት ከሚገኙ መምሪያዎች መካከል ጉዳዩ በቀጥታ የሚመለከታቸውን መምሪያዎች በማካተት የተቋቋመው ኮሚቴም ዝርዝር ጥናቶችን በሚገባ በማጥናትና ችግሮቹን ለይቶ ከመፍትሔ ሀሳብ ጋር በአጭር ጊዜ ውስጥ በማቅረብ በቤተክርስቲያኒቱ ማዕከላዊ አስተዳደር አማካኝነት ተቋማዊ አቋም የሚወሰድበትና በቅዱስ ሲኖዶስ ደረጃ የማያዳግም መፍትሔ የሚሰጥበትን ሁኔታ ለማመቻቸት የሚያስችል ሥራ በመሥራት ላይ መሆኑን እየገለጸች በሁለቱም ዘርፎች የተገኙ ውጤቶችን በተመለከተ በተከታታይ ለሕዝበ ክርስቲያኑ እንዲገለጽ የምታደርግ መሆኑን ከወዲሁ እያስታወቀች በጉዳዩ ዙሪያ ሙያዊ ድጋፍ ለመስጠት ፈቃደኛ የሆኑ ምዕመናንና ምዕመናት በተቋቋመው ኮሚቴ አማካኝነት የሚደረግላቸውን ጥሪ ተቀብለው ለቤተክርስቲያናችን መብት መከበር የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ እናት ቤተክርስቲያን ጥሪዋን ታቀርባለች።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
ጥር ፲፯ቀን ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም


ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል dan repost
የቤተክርስቲያንን መብትና ጥቅም ለማስከበር እና የሕግ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ በጥብቅ እየተሰራ ነው።

ጥንታዊት፣ታሪካዊትና ዓለም አቀፋዊት የሆነችው የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መንፈሳዊ አገልግሎቷን ለማስፋፋት በምታደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ሁሉ የሌሎችን መብትና ጥቅም ባለመንካት በትዕግሥትና በማስተዋል የምትጓዝ አገራዊ ኃላፊነት የሚሰማት ሰላምን አብዝታ የምትሰብክ መንፈሳዊት ተቋም መሆኗ ይታወቃል።

ቤተክርስቲያናችን ሥርዓተ አምልኮቷን ለማስፋፋት በተጓዘችባቸው አያሌ ዓመታት አገራችን ኢትዮጵያ የራሷ ፊደላትና የራሷ የቀን አቆጣጠር ባለቤት እንድትሆን ያስቻለች፣በሊቃውንቶቿ የመጠቀ እውቀት አማካኝነት የሥነ ጥበብ፣የሥነ ስዕል፣የዕጽዋትና የጠፈር ምርምርና ጥናቶችን በማከናወን ተጨባጭ ውጤቶችን ለዓለም ያበረከተች ጥንታዊት ተቋም ስለመሆኗም አያሌ ማስረጃዎችን ማቅረብ ይቻላል።

ይሁን እንጂ ይህች ለአገረ መንግስት መመስረትና መጽናት፣ለእውቀት መስፋፋት፣ ለአብሮነት መጎልበት፣ ትውልድን በሥነ ምግባር ቀርጻ ፍቅርና አንድነትን በተግባር የሰበከች እናት ቤተክርስቲያን ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በተለያዩ አካላት መብትና ጥቅሟን የሚነኩ፣በአስተምህሮቿ፣በዕምነቷ፣በንዋያተ ቅድሳቶቿ ላይ መሰረታቸውን ያደረጉና ትዕግስቷን የሚፈታተኑ ክብርና ሉአላዊነቷን የሚዳፈሩ እኩይ የትንኮሳ ተግባራት እየተፈጸመባት ይገኛል።




Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
"ብዙ ህዝባችን የሚጠፋው እውቀት ከማጣት ነው!! "

#ዲያቆን_ያረጋል_አበጋዝ


ንሥር መጻሕፍትና የጽሕፈት መሣሪያ (Eagle Books and Stationery) dan repost
ገድለ አቡነ ጸጋ ዘአብ ወእምነ እግዚእኀረያወገድለ አቡነ ታዴዎስ ጽላልሽ
....ገድላት ኹሉን አቀፍ የመረጃ ምንጮች ናቸው። ዘመን፤ በአንድ አካባቢ፤ በአንድ ተመሳሳይ ሁኔታ የሚጓዙ አለመሆናቸው፤ በተለያዩ የዓለም ክፍል በተለያዩ ዘመናትና ጊዜያት የተነሡ የቅዱሳንን ሕይወት የተመለከቱ፤ ከምእመናን እስከ መዐርገ ጵጵስና ድረስ በተራ ዜግነት ከተሰለፉት እስከ ንጉሥነትና ንግሥትነት ደረጃ እስከ ደረሱት ድረስ ምእመናንንና ምእመናትን በእኩልነት የያዘ በመኾኑ ከሃይማኖት ጥቅሙ በተጨማሪም በዓለም አቀፍ ደረጃ የሰዎችን እኩልነት በማሳየቱ የበለጠ አጎልቶ ይሳያል።
  ❞ስለዚኽ ይኸ የካህኑ ጸጋ ዘአብ፣የብፅዕት እግዚእ ኀረያ እና የአቡነ ታዴዎስ ገድል የነፍስና የሥጋ በረከት የምንቀበልበት፤ ኹሉን አቀፍ መረጃ የምናገኝበት በመኾኑ በ፯ቱ ዕለታት በመክፈል በግዕዝና በአማርኛ በመተርጎም ቀርቧል።

❞ይኸም ቅዱሳኑ በሕይወተ ሥጋ እያሉም ኾነ ከዕረፍታቸው በኋላ በዐጸደ ነፍስ ሳሉ ያደረጓቸውን ልዩ ልዩ ድንቅ ተኣምራትን መልክዐቸውንም  አካቶ የያዘ የካህኑ ጸጋ ዘአብን፣ የብፅዕት እግዚእ ኀረያንና አቡነ ታዴዎስን ዝክረ ስም የሚናገር የምስጋናጸሎት ስለኾነ በዚኸ የጸሎት መጽሐፍ ተጠቅመን በረከተ ሥጋ በረከተ ነፍስ እናገኝ ዘንድ ይህን ገድል   ኢቲሳ ደብረ ጽላልሽ አቡነ ተክለ ሃይማኖት አንድነት ገዳም እነሆ  ይለናል ።

ይኽን የቅዱሳን ተጋድሎ እና ምስጋና የያዘ ገድል በግዮን መጻሕፍት የሚያገኙት ሲሆን በሀገር ውስጥ እንዲሁም ከሀገር ውጭ ለምትገኙ አንባብያን በDHLእና በEMS በመላክ የ Delivery አገልግሎት በመስጠት ተደራሽ እናደርጋለን።
https://t.me/GhionBookStore1623




ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል dan repost
ጌታችን መጻጉዕን የፈወሰበትን፣ አልዓዛርን  ከሞት ያስነሣበትን፣ ዓይን ያበራበትን፣ በአጋንንት እስራት የተያዙትን ነጻ ያወጣበትን፣ ዕለት በክብረ በዓል ደረጃ ሳታከብር የቃናው ተአምር ከጌታችን ንዑሳን በዓላት ውስጥ ተደምሮ እንዲከበር ያደረገችበት ጥልቅ ምሥጢርን ስለያዘና ስላዘለ ነው፡፡ ይህ ሰርግ የሚደረገው  ጌታችን  ከአእላፋት  መላእክቱ  ጋር በሚመጣበት  በዕለተ  ምጽአት  ነው፡፡ ዕለተ  ምጽአት  ሙሽራዪቱ  ቅድስት  ቤተ ክርስቲያን በቅዱሳን ምግባር አጊጣ  የምትታይበት፣ የጽድቅ ዘይት ይዘው መገኘት የቻሉ ልባሞች  ከቤተ  ክርስቲያን ጋር ሰርጉን የሚታደሙበት፣ እንደ ቃናው ደስታ በሰማያዊቱም ኢየሩሳሌም፥ በደስታም ወደ ተሰበሰቡት ወደ አእላፋት  መላእከት በሰማያትም ወደ ተጻፉ ወደ  በኵራት ማኅበር፥  የሁሉም  ዳኛ ወደሚሆን ወደ  እግዚአብሔር፥  ፍጹማንም ወደ ሆኑት  ወደ ጻድቃን  መንፈሳት የምንደርስበት ዕለት ነው፡፡ (ዕብ.፲፱፥፳፪)

ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ የቃናን ሰርግ ከሰማያዊው ሰርግ ጋር አሰናስሎ ሲያመስግን እንዲህ ይላል፡፡ “ወደ ሰርግ በዓልዋ ዕለት ደስታን ይዘህላት ስለመጣህ ቃና ታመስግንህ! አክብረኸዋልና ሙሽራው የደፋው ዘውድ አንተን ያከብርሃል።  የሙሽራዋ አክሊልም የአንተን ድንቅ ሥራ ያደንቃል፡፡  ቤተ ክርስቲያንህን በሙሽራዋ መስለሃታልና  በቃና  መስታወትነት  ምሳሌዎች ሁሉ ትርጒማቸውን  አገኙ፡፡ የቃናዎቹ እንግዶች ደግሞ አንተ የመረጥሃቸው (ወደ  ሰማያዊው ራት) የጠራሃቸው  ናቸው::  ምጽአትህንም በሰርግ  ቤቱ ደስታ መሰልከው::”

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን እንደ ሙሽራ አጊጣ፣ ለበጉ ሰርግ ያለ እድፍና ያለ ነውር ውብ ሆና ተዘጋጅታ በምትቀርብበት በዚያ ሰማያዊ ሰርግ ለመገኘትና ወደ በጉ ሰርግ ራት ገብተን፣ ካጌጡ ቅዱሳን ጋር ለመቀመጥና ለመብላት የበቃን ያድርገን!

መልካም በዓል!

ምንጭ፡- ትርጓሜ ወንጌል እና “ቃና ዘገሊላ”
በዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ


ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል dan repost
ቃና ዘገሊላ
እንኳን አደረሳችሁ!

በቤተ ክርስቲያናችን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ካደረጋቸው  እጅግ ብዙ ተአምራት መካከል በዓል አድርጋ የምታከብረው የቃና ዘገሊላውን ተአምር ነው፡፡ በመጽሐፍ ቅዱስም እንዲህ ተመዝግቦ እናገኘዋለን፡፡  “በሦስተኛውም  ቀን  በገሊላ  ቃና ሰርግ  ነበረ፥  የኢየሱስም  እናት በዚያ  ነበረች፤ ኢየሱስም  ደግሞ  ደቀ  መዛሙርቱም ወደ  ሰርጉ ታደሙ። የወይን ጠጅም ባለቀ ጊዜ የኢየሱስ እናት፦ የወይን ጠጅ እኮ የላቸውም” አለችው። ኢየሱስም፦ “አንቺ ሴት፥ ከአንቺ ጋር ምን አለኝ?  ጊዜዬ  ገና  አልደረሰም”  አላት። እናቱም  “ለአገልጋዮቹ፦   የሚላችሁን  ሁሉ አድርጉ” አለቻቸው። አይሁድም  እንደሚያደርጉት የማንጻት  ልማድ   ስድስት  የድንጋይ  ጋኖች   በዚያ  ተቀምጠው  ነበር፥   እያንዳንዳቸውም  ሁለት ወይም  ሦስት   እንስራ   ይይዙ ነበር። ኢየሱስም፦ “ጋኖቹን ውኃ ሙሉአቸው” አላቸው። “እስከ አፋቸውም ሙሉአቸው” አላቸው። እስከ አፋቸውም ሞሉአቸው።  “አሁን ቀድታችሁ  ለአሳዳሪው  ስጡት”  አላቸው፤  ሰጡትም። አሳዳሪውም  የወይን ጠጅ  የሆነውን  ውኃ  በቀመሰ ጊዜ  ከወዴት  እንደ  መጣ አላወቀም፤ ውኃውን የቀዱት አገልጋዮች ግን ያውቁ ነበር፤ አሳዳሪው ሙሽራውን ጠርቶ ፦ሰው  ሁሉ አስቀድሞ መልካሙን  የወይን ጠጅ  ያቀርባል፥  ከሰከሩም  በኋላ  መናኛውን፤ አንተስ  መልካሙን  የወይን  ጠጅ  እስከ  አሁን  አቆይተሃል”  አለው። ኢየሱስ ይህን የምልክቶች መጀመሪያ በገሊላ ቃና አደረገ፤ ክብሩንም ገለጠ፥ ደቀ መዛሙርቱም በእርሱ አመኑ።” (ዮሐ.፪፥፩-፲፩)


ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል dan repost
በዓለ ጥምቀት

እንኳን አደረሳችሁ!

ጥምቀት ሥርዓቱ ከብሉይ ኪዳን ይጀምራል፡፡ አንድ አይሁድነትን ያልተቀበለ አዲስ ሰው ወደ ይሁዲነት ሲመጣ ከማኅበረ አይሁድ ከመቀላቀሉ አስቀድሞ ግዝረትን እና በውኃ  መታጠብን (መጠመቅ) እንዲፈጽም ይደረጋል፡፡ ይህም ለመንጻት ሥርዓት በዘሌዋውያን ካህናት  አማካኝነት  ይፈፀም ነበር፡፡ ውኃ መንጽኢ ነውና ማንም ሰው በተለያየ ምክንያት ቢረክስ  የሚነጻበት  (የኅፅበት) ሥርዓት ለእያንዳንዱ  ምክንያት ነበረው፡፡  (ዘሌ. ፲፬፥፲፭-፳፪) ይህንንም ተዘርዝሮ እናገኘዋለን፡፡ ይህም በእውነት በውኃ ላይ የእግዚአብሔር  መንፈስ እንዳደረበት  ያስረዳል፡፡ (ዘፍ.፫፥፪) ተያይዞ እስከ ዘካርያስ ልጅ ቅዱስ ዮሐንስ ደርሷል፡፡

በመልአኩ  ቅዱስ ገብርኤል  ብሥራት የተወለደው  ጻድቅ፣ ቅዱስ ሐዋርያ ሰማዕት፣ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ የዮሐንስ በረሃ በሚባለው እና ከሕፃናቱ ጀምሮ ባደገበትምድረ በዳ በሚገኝ ዋሻ ውስጥ በብሕትውና ተወስኖ ሲኖር ቆይቶ ለክርስቶስ  መንፈቅ ሲቀረው  በ፴  ዘመኑ የዮርዳኖስ  አውራጃ  በምትሆን በይሁዳ  ‹‹ነስሑ  እስመቀርበት መንግሥተ ሰማያት፤ መንግሥተ ሰማያት በልጅነት፣  ልጅነት  በሃይማኖት ልትሰጥ ቀርባለችና በወንጌል አምናችሁ ንስሐ እያለ ሰበከ፤ በነቢይ ‹‹የጌታን መንገድ አዘጋጁ፤  ጥርጊያውንም አቅኑ  እያለ  በምድረ በዳ  የሚጮህ  ሰው ድምፅ›› እንደ  ተባለለት፡፡ (ኢሳ.፵፥፫፣ማቴ.፫፥፫)

ቃሉን የተቀበሉም ስለ ኃጢአት ስርየት ኃጢአታቸውን እየተናዘዙ በፈለገ ዮርዳኖስ በእደ ዮሐንስ ይጠመቁ ነበር፡፡ ይህም አማኞችን  ለክርስቶስ  ጥምቀት የሚያዘጋጅና በእግዚአብሔር  መንግሥት ውስጥ ለመሆን የሚያበቃ ነበር፡፡ ‹‹እኔስ ለንስሐ በውኃ አጠምቃችኋለሁ፤ ጫማውን እሸክም ዘንድ የማይገባኝ ከእኔ በኋላ የሚመጣው ግን ከእኔ ይበረታል፤  እርሱ በመንፈስ ቅዱስና በእሳት ያጠምቃችኋል›› (ማቴ.፫፥፲፩) ክርስቶስም ናዝራዊ ከተባለበት (ማቴ. ፥፳፫) ከናዝሬት  ወደ ዮርዳኖስ  ጥር ፲፩   ቀን  ወረደ፤  ቅዱስ  ዮሐንስም  ስለ  እርሱ  መሰከረ  ‹‹ነዋ በግዑ ለእግዚአብሔር  ዘያአትት ወያሴስል ኃጢአተ ዓለም፤ እነሆ  የዓለምን ኃጢአት  የሚያስወግድ የእግዚአብሔር  በግ፡፡›› (ዮሐ.፩፥፳፱)

ዮሐንስም ክርስቶስ በእርሱ እንዲጠመቅ መምጣቱን ባየ ጊዜ ወትሮ ባሪያ ወደ ጌታው ይሄዳል  እንጂ እንዴት ይህ ይሆናል?  አለው፤ ትሕትናን ከእናቱ ተምሯልና፤  ‹‹የጌታዬ  እናት ወደ  እኔ ትመጣ ዘንድ  እንዴት  ይሆንልኛል?››  እንዳለች ቅድስት ኤልሳቤጥ፡፡ (ሉቃ.፩፥፵፫)  ደግሞስ ሌላውን ሁሉ በስምህ አጠምቃለሁ፤  አንተን  በማን ስም አጠምቃለሁ?  ቢለው  ‹‹ወልዱ  ለቡሩክ ከሣቴ ብርሃን ተሣሃለነ››፤ ‹‹አንተ  ካህኑ ለዓለም በከመ  ሢመቱ  ለመልከ  ጼዴቅ››  ብለህ  አጥምቀኝ ብሎታል፤  ብርሃንን  የምትገልጥ የቡሩክ  አብ የባሕርይው  ልጅ ይቅር  በለን፤  እንደ  መልከ  ጼዴቅ  የዓለም ሁሉ ካህን  አንተ  ነህ››  እያልክ  አጥምቀኝ ብሎታል፤  ከዚያም ዮሐንስ ሊያጠምቀው ወደ ዮርዳኖስ ገብቷል፡፡

ዮርዳኖስ  የጥምቀቱ ቦታ  እንዲሆን  ጌታ የፈቀደው  አስቀድሞ  ትንቢት  አናግሮ  ምሳሌ መስሎ ‹‹ባሕርኒ ርእየት ወጎየት ወዮርዳኖስኒ ገብአ ድኅሬሁ ርእዩከ ማያት እግዚኦ  ርእዩከ ማያት ወፈርሁ፤ አቤቱ ውኆች አዩህ፤ ውኆችም አይተውህ ፈሩህ፤ ጥልቆችም ተነዋወጡ፤ ውኆችም ጮሁ፡፡›› (መዝ. ፸፮፥፲፮) ‹‹ባሕር  አየች፤  ሸሸችም፤  ዮርዳኖስም  ወደ ኋላ  ተመለሰ፤››  (መዝ.፻፲፫፥፫) ዮርዳኖስ መነሻው ከላይ ነቁ፤ አንድ ነው፤ ዝቅ ብሎ በደሴት ይከፈላል፤  ከታች ወርዶ ይገናኛል፡፡ የሰውም ልጅ አባቱ አንዱ አዳም ሲሆን እስራኤልና  አሕዛብ በግዝረት በቁልፈት  ተለያይተዋልና፡፡ ከታች ወርዶ እንደገና በወደብ እንዲገናኝ ሕዝብ እና አሕዛብ  በክርስቶስ  ጥምቀት አንድ  ሆነዋል፤  ከዚህም  የተነሣ  ጌታ የሁለቱ  ወንዝ  መጋጠሚያ  ላይ  በመጠመቅ አንድነታችንን  መልሶልናል፡፡  ይህንን  ውለታ በማሰብ (ይህን  የነጻነት  በዓል)  እናከብራለን፡፡

ከዚህም በላይ  የሥላሴ  ምሥጢር እኛ በምንረዳው መልኩ ያየንበትን በዓል የዕዳ ደብዳቤያችን የተፋቀበትን ቀን፣ ነጻነታችንን ያወጅንበትን፣ የእግዚአብሔር  ልጆች የሆንበትን  ዕለት  ከበዓልም  የሚበልጥ  ዐቢይ  በዓል  አድርገን  አናከብረዋለን፡፡  ይህንንም  ቀን  ቀድሶ  የሰጠን  ቅዱስ አምላክ ምስጋና ይድረሰው፤ አሜን፡፡
ከበዓሉ በረከት ረድኤት ያሳትፈን!

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.