TIKVAH-ETHIOPIA


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


#ethiotelecom

" በአክስዮን ሽያጩ የተገኘው 3.2 ቢሊየን ብር ገንዘብ እስካሁን ለምንም አይነት ጥቅም ሳይውል በዝግ አካውንት ተቀምጧል " - ኢትዮ ቴሌኮም

➡️ " ከ47 ሺ በላይ ኢትዮጵያውያኖች የኢትዮ ቴሌኮምን አክስዮን ሼር ግዢ አከናውነዋል ! "


ኢትዮ ቴሌኮም በጥቅምት ወር 10 በመቶ ድርሻውን ማለትም እያንዳንዳቸው 300 ብር ዋጋ ያላቸውን 100 ሚሊዮን መደበኛ አክሲዮኖች ለህዝብ በሽያጭ ማቅረቡ ይታወቃል።

ውሳኔው ኢትዮ ቴሌኮም ሙሉ በሙሉ በመንግስት ባለቤትነት ተይዞ ከነበረበት ወደ አክስዮን ማህበርነት ያሻጋገረ ነበር።

ለግዢ የቀረቡት አክስዮኖችን በተመለከተ ተቀባይነት ያገኙ አክስዮን ገዢዎች ከጥር 17/2017 ዓም ጀምሮ እንደሚለዩ ተገልጾ የነበረ ሲሆን ተቀባይነት ያላገኙ አክስዮን ገዢዎች ደግሞ እስከ ሚያዚያ 6/2017 ዓም  ገንዘባቸው ተመላሽ ማድረግ እንደሚጀምር ይፋ አድርጎ ነበር።

ተቀባይነት ያገኙ እና ውድቅ የሆኑ አክሲዮኖችን በተመለከተ በተቀመጠው የጊዜ ገደብ መሰረት ምንም አይነት ይፋ ያደረገው መረጃ ሳይኖር ወራትን ያስቆጠረው ኢትዮ ቴሌኮም በጉዳዩ ላይ በዛሬው ዕለት መግለጫ እየሰጠ ይገኛል።

መግለጫውን የሰጡት የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ምን አሉ ?

- የመጀመሪያው ዙር የአክስዮን ሽያጩ ከተጀመረበት ጥቅምት ዘጠኝ እስከ ታሕሳስ 25/2017 ዓም ድረስ ሲከናወን ቆይቷል።

- የሼሩ ዋጋ ዝቅ የተደረገበት ምክንያት ዝቅተኛውን የማህበረሰብ ክፍል ተጠቃሚ ለማድረግ ነበር።

- ዝቅተኛው 33  ከፍተኛው 3,333 ሺ አክስዮን ሽያጭ ማለትም ከ 9,900 ብር እስከ 99,900 ብር ሲከናወን ነበር።

- አክስዮን ሽያጩ ሪፖርት ተገምግሟል ለካፒታል ገበያ ባለሥልጣንም ስለ አክስዮን ሽያጭ በተመለከተ ሪፖርት አቅርበናል።

- በህዝብ ጥያቄ መሰረት የሽያጭ ቀኑ ካበቃ በኋላም የሽያጭ ጊዜው እንዲራዘም ጥያቄ በመቅረቡ እና ህጉም ይህንን የሚፈቅድ በመሆኑ እስከ የካቲት 7/2017 ዓም ተራዝሞ ቆይቷል።

- የአክስዮን ሽያጩ በአጠቃላይ ለ121 ቀናት ቆይቷል።

- አጠቃላይ 47,377 ኢትዮጵያውያን ኢንቨስተሮች ሼሮችን ገዝተዋል ፤ በአጠቃላይ 10.7 ሚሊየን ሼሮችን ሽያጭ ተከናውኗል በገንዘብ ሲተመን 3.2 ቢሊዮን ብር ይይዛል።

- አክስዮን ግዢውን የፈጸሙት ባለድርሻዎች በመጀመሪያው ዙር 43,848 በሁለተኛው ዙር 3,529 በአጠቃላይ 47,377 ኢትዮጵያውያኖች ናቸው።

- ስቶክ ማርኬት ላይ መገበያየት፣ መሸጥ እና መግዛት የሚችሉ ባለሃብቶች ተፈጥረዋል።

- በቀጣይ ባለ አክስዮኖችን የማነጋገር ስራ ይሰራል ይህንንም ለማድረግ የካፒታል ገበያ ባለሥልጣን መብት ሰጥቷል ህጉም ይፈቅዳል።

- በሂደቱ የሚያስፈልጉት ከባለአክስዮኖች የምንጠይቃቸው ማርጋገጫዎች አሉ በመቀጠል ባለቤትነታቸው እንዲረጋገጥ ወድ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን ይላካል።

- በመቀጠል ሊስት በማደርግ በካፒታል ገበያ መሸጥ እና መግዛት ወደ ሚችሉበት አጋጣሚ ይፈጠራል አላማውም ይሄ ነው።

ቀጣይ የአክስዮኑ ሽያጭ ይቀጥላል ?

የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ፥ ባንኮች እና ትውልደ ኢትዮጵያውያኖች ጥያቄ ማቅረባቸውን ገልጸዋል።

" ይህንን ታሰቢ በማድረግ እና በመጀመሪያው ሂደት ላይ ያጋጠሙ ነገሮችን በመገምገም እና መንግስትን በማማከር በቀጣይ መሳተፍ የፈለጉ ግለሰብ ፣ ተቋማት እና ትውልደ ኢትዮጵያኖች የቀሩ ሼሮችን እንዲገዙ መቼ ለሽያጭ እንደሚቀርቡ የምናሳውቅ ይሆናል " ብለዋል።

አሁን ላይ በአክስዮን ሽያጩ የተገኘው 3.2 ቢሊየን ብር ገንዘብ እስካሁን ለምንም አይነት ጥቅም ሳይውል በዝግ አካውንት ተቀምጦ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

" የባለአክስዮኖች መብት ባስጠበቀ መልኩ ቀጣይ ሂደቶች ይከናወናሉ " ሲሉ አሳውቀዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia


#Update

ኢትዮ ቴሌኮም ስለ አክሲዮን ሽያጩ ምን አለ ?

-  ኢትዮ ቴሌኮም ለ121 ቀናት የ10% ድርሻ አክሲዮን ሲሸጥ ቆይቷል።

- አጠቃላይ 47,377 ኢንቨስተሮች ተሳትፈዋል ፤ ሼሮችን ገዝተዋል።

- አጠቃላይ 10.7 ሚሊዮን ሼር ተሸጧል።

- አጠቃላይ 3.2 ቢሊዮን ብር አሴት/ value ተፈጥሯል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

@tikvahethiopia


" በየቤተ እምነቱ የተመረጡ አካላት የቤታቸውን ግምገማ ያቀርባሉ ማን ማንን ሰደበ ፣ቅዱሳንን አንቋሸሸ የሚለውን የሚከታተሉ ሲሆኑ ውጤታቸውንም ለጉባኤው እና ለህግ አካላት ያቀርባሉ"-የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ

በተለያዩ የማህበራዊ መገናኛ ብዝሃን ዘዴዎች የሚታዩ ሃይማኖታዊ መጓተቶች ጋር በተገናኘ ቤተ እምነቶች እንዲሁም አማኞች ቅሬታቸውም ሲያቀርቡ የሚደመጥ ሲሆን ቤተ እምነቶቹም ክብራችንን ነክቷል ያሉት አካል ላይ ክስ ሲመሰርቱ እና በህግ እንዲጠየቁ ሲያደርጉ ይታያል።

ይህንን ሃይማኖታዊ መጓተቶች ለመቀነስ እና ሌሎች ቤተ እምነቶችን የሚያንቋሽሹ አካላትን ተጠያቂ ለማድረግ ያግዛል የተባለ የህግ ክፍል ማቋቋሙን የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቋል።

የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጠቅላይ ጸሐፊ ሊቀ ትጉሃን ቀሲስ ታጋይ ታደለ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡር ዝርዝር ሃሳብ ምን አሉ ?

" ተቋሙ የቋቋመበትን ባህሪ መገንዘብ ያስፈልጋል የእኛ ሃላፊነት የሰላም ጥሪ ማቅረብ ፣የሚወገዘውን ማውገዝ ፣በህግ መጠየቅ ያለባቸው አካላት በህግ እንዲጠየቁ ጥያቄ ማቅረብ ነው።

አሁን ግን አንዳንድ ግጭቶችን በሚመለከት ራሱን የቻለ ከሁሉም ቤተ እምነት የተወጣጣ ቡድን እንዲኖር እየተሰራ ነው።

የህግ ክፍል አቋቁመናል እንደዚህ አይነት ጉዳዮችን የሚሞግት የህግ ክፍል የለንም ነበር እስካሁን።

በክርስትና ቤት ሆኖ እስልምናን በእስልምና ቤት ሆኖ ክርስትናን የሚያንቋሽሹ አካላትን ከህግ እና የጸጥታ አካላት ጋር እያቀረቡ ፣እያስጠየቁ እና እያስቀጡ የሚኬድበት ሁኔታ እንዲፈጠር በየ ቤተ እምነቱ ቡድን እንዲዋቀር ጥሪ አቅርበን የተመረጡት ሰዎች እንዲላኩልን አድርገናል።

እነዚህ የተመረጡ አካላት ስብሰባ አድርገው የማጥራት ስራ እንዲሰሩ እና የማስጠየቅ ስራ እንዲሰራ እየሄድንበት ነው።

ይህ አሁን በቅርቡ የጀመርነው ነው ከዚህ ቀደም አልነበረም ።

እነዚህ በየ ቤተ እምነቱ የተመረጡ አካላት የቤታቸውን ስራ ግምገማ ያቀርባሉ ማን ማንን ሰደበ ፣ቅዱሳንን አንቋሸሸ የሚለውን የሚከታተሉ ሲሆኑ ውጤታቸውንም ለጉባኤው እና ለህግ አካላት ያቀርባሉ።

የተመረጡት አካላት እና የተዋቀረው ቲም ይህንን ጉዳይ እያጣሩ ለፍትህ እና ለጸጥታ አካላት ግበአት የሚሰጡ ናቸው እንጂ እንደ ጉባኤ ክስ የሚመሰርቱ አይደሉም።

ባለፈው አንድ ወር ውስጥ ለሁሉም ቤተ እምነቶች ደብዳቤ በትነናል ቡድኑም ተዋቅሯል የተወሰኑ ቤተ እምነቶ ተወካዮቻቸውን አላኩም እነሱን እየጠበቅን ነው ሁሉም ከላኩ በኋላ ቡድኑ ወደ ስራ ይገባል " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia


" ሲ3ኤአይ (C3 AI) በተባለና ህጋዊ ንግድ ፈቃድ አለው ብለን ባመነው ተቋም እንደ ግለሰብ ከ200 ሺ ብር በላይ ተጭበርብረናል  " - በኦንላይን ስራ የተጭበረበሩ ግለሰቦች

" ሲ3ኤአይ (C3 AI) በሚል ስም ' በትርፍ ሰዓት ኦላይን ላይ በመስራት ታተርፋላችሁ ' ተብለን ሥራ ብለን በገባንበት ተጭበርብረናል " ያሉ ቅሬታ አቅራቢዎች
- ከጅማ፣
- ከጎንደር፣
- ከአዲስ አበባ፣
- ከባህርዳር፣
- ከባሌሮቤ እና ከበርካታ የሀገሪቱ ክፍሎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታ አስገብተዋል።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ  " ትሰሩታላችሁ " የተባሉት ሥራ በተዘጋጁ ድረ-ገጾች ላይ ይወጣሉ የተባሉ ሰርቨሮችን መከራየት እና የሚገኘውን ኮሚሽን መካፈል እንደነበር ገልፀዋል።

አዳዲስ አባላት በስራቸው ሲያስመዘግቡም ደረጃቸው ከፍ እያለ እንደሚሄድ ተናግረዋል።

በመጀመሪያ ብር እንደሚያስገቡ ለምሳሌ ፦ 1,000 ብር ከሆነ አትርፋችኃል ተብሎ 2,000 ብር ሆኖ እንደሚላክላቸው በዚህም እንዲያምኑ ተደርገው ብዙ ብር እንደሚልኩ ከዛ  ግን ነገሩ የውሃ ሽታ እንደሆነባቸው ጠቁመዋል።

ሥራ ነው ብለው ሲሰሩበት የነበሩበት ሁለት ድረ-ገጾች ካልፈው ሰኞ ሚያዚያ 13 ቀን ከቀኑ 6 ሰዓት በኋላ ዝግትግት ብሎ መጥፋቱን ተናግረዋል።

ለቲክቫህ ኢትዮጵያ " ከ200 ሺህ ብር በላይ ተጭበርብረናል " ያሉ በርካታ ሰዎችን ቃላቸውን የሰጡ ሲሆን
#በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ " ተጨበረበርን " ያሉም አሉ።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ  " ድርጅቱ " በተለያዩ ዋና ዋና የሚባሉ ሚዲያዎች እንደ አሻም ቴሌቪዥን ፣ ናሁ ቴሌቪዥን ፣ ሪፖርተር ጋዜጣ፣ ባላገሩ ቴሌቪዥን እንዲሁም የተለያዩ በርካታ ተከታይ ያላቸው የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች ላይ የዘገባ ሽፋን ማግኘቱ እንድናምነው አድርጎናል ብለዋል።

" ድርጅቱ " ለመቄዶኒያ አረጋዊያን መርጃ ማኅበር ድጋፍ አድርጎ እንደነበር በእነዚህ የሚዲያ ተቋማት የዜና ሽፋን ማግኘቱን ለማወቅ ተችሏል።

በመቄዶኒያ አረጋዊያን መርጃ ማኅበር ላይ ድጋፍ ለማድረግ አስተባባሪ የነበሩትና ማርኬቲንግ ማናጀር የተባሉት አቶ ጌታቸው ጫኔ ናቸው።

አቶ ጌታቸውንም ስለጉዳዩ ጠይቀናቸዋል።

በምላሻቸውም " እኔ ወደ ስራ የገባሁት ከ5 ወር በፊት ነው፣ የገባሁትም እንደማንኛውም ሰው በዋትስአፕ በተላከልኝ መልዕክት የ500 ብር ገዝቸ ነው፣ ድርጅቱን በማመኔ ከግሌ ከ2 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ አድርጊያለሁ፣ በዚህም ከፍተኛ ኪሳራ ደርሶብኛል " ብለዋል።

አያይዘውም " የማወራቸው ሰዎች ሀገር ውስጥ የሌሉ እና በዋትስአፕ ላይ ብቻ ነው፣ በአካል ከሀገር ውስጥ ያገኘሁት ሰው የለም " ሲሉ አስረድተዋል።

የመቄዶንያው ዝግጅት እንዴት ተካሄደ ?

" ድርጅቱ " ቡድን ለሚሰበስቡ ሰዎች የስብሰባ እና የበጎ አድራጎት ሥራ እንዲሰሩ ገንዘብ እንደሚሰጥ ፤ በእሳቸው ቡድን ያሉ ሰዎችን በማስተባበርም እራት ማብላታቸውን ተናግረዋል።

እነዚህን ሰዎች ለማሰባሰብ እንዲሁም ድጋፍ ለማድረግ ገንዘቡ ከየት መጣ ?

አቶ ጌታቸው ለዚህ ሥራ ከውጪ በእሳቸው አካውንት 500 ሺህ ብር እንደገባላቸው በመግለጽ ከዚህ ውስጥ 160 ሺ ብር ወጪ በማድረግ ለአረጋውያኑ ግብዣ እንዳደረጉ፤ ቀሪው ገንዘብ ከቡድናቸው ጋር አዲስ አበባ ላላቸው ስብሰባ የምግብ፤ ትራንስፖርት እና ማደሪያ ወጪ እንደተደረገ ተናግረዋል።

እናንተ የተቋሙ አመራሮች ናችሁ ?

አቶ ጌታቸው ፥ " እኛ ሌሎችን ለማገዝ፤ መረጃ ለመስጠት፤ ለማስተባበር ፊት ለፊት ስለወጣን እንጂ የተለየ ያገኘነው ወይም ሰዎች በእኛ በግል አካውንት ያስገቡት ብር የለም " ሲሉ የእነሱ ሥራ ማስተባበር እንደነበር አስረድተዋል፡፡

ቃላቸውን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የሰጡ በርካታ ቅሬታ አቅራቢዎች  " የተጭበረበርንበት መንገድ ይለያል " ብለው የገለጹ ሲሆን ይህንም እንዴት እንደሆነ አስረድተዋል።

ምን አሉ ?

- ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ሲስሪ ኤአይ ቴክኖሎጂ / SEE THREE AI TECHNOLOGY PLC በሚል ስም እንዲሁም በኢ ትሬድ ማረጋገጫ 0093931744 ቲን ቁጥር መኖሩ።

- በቅርቡ በስካይ ላይት ሆቴል ትልቅ ዝግጅት ለማድረግ ታቅዶ፤ የአዳራሽ ክፍያ ከተስማሙት 1 ሚሊዮን ብር ግማሹን መክፈሉን የባንክ ስቴትመንትና የሆቴሉን ደረሰኝ በግሩፖች ላይ መጋራቱ፤ በዚህም ብዙዎች ተስፋ እንዲያደርጉ መደረጉ።

- ገንዘቡ የሚገባው ሆነ ክፍያ የሚፈጸመው በአንድ ሂሳብ ቁጥር 1000687201888 በሚል መሆኑ።

እንድናምን አድርጎናል ሲሉ ገልጸዋል።

በጉዳዩ ላይ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከሚመለከታቸው አካላት ለማጣራት ጥረት አድርጓል።

➡️ በንግድ ፈቃዱ ላይ በሥራ አስኪያጅነት የተጠቀሰውን ግለሰብ ለማግኘት ቢጥርም አልተሳካም ፤ ስልክ አይሰራም ቴሌግራም ላይም አይመልስም።

➡️ ንግድ ፈቃዱን በተመለከተ በአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ እና ገቢዎች ቢሮ በኩል ለማጣራት ጥረት እያደረግን ነው።

➡️ የባንክ አካውንቱን በተመለከተ ለኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጉዳዩን ያሳወቀ ሲሆን የባንኩን ምላሽ በመጠባበቅ ላይ እንገኛለን።

➡️ ስካይ ላይት ሆቴል ተዘጋጅቷል ለተባለው ዝግጅት በእርግጥም ለሆቴሉ የተከፈለ ነገር መኖሩንና ዝግጅቱ መያዙን ለማጣራት ጥያቄ አቅርበናል።

የብዙዎች ጥያቄ ገንዘብ ሲወጣ ሲገባ የነበረበት አካውንት በአስቸኳይ ይታገድልን የሚል ሲሆን የሚመለከተው የህግ አካልም አስፈላጊውን ማጣራት ያድርግልን ሲሉ ጠይቀዋል።

🔴ቅሬታ አቅራቢዎች ላነሱት ጉዳይ " ምላሽ እሰጣለሁ ፤ አብራራለሁ ፥ አስረዳለሁ " የሚል የትኛውም ወገን ከመጣ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያስተናግዳል።

#እንድታውቁት ፦ C3 AI የአሜሪካ የቴክኖሎጂ ኩባንያ ሲሆን በአርተፊሻል ኢንተለጀንስ ላይ የሚሰራ ነው። ነገር ግን ባደረግነው ማጣራት በተለያዩ የአፍሪካ ሀገራት በዚህ ተቋም ስም ገንዘብ የሚሰበስቡ አሉ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia


🎥

ኢትዮ ቴሌኮም በጥቅምት ወር ይፋ ባደረገው የ10% የአክሲዮን ሽያጭ ላይ አሁን 8:00 ሰዓት ላይ መግለጫ ይሰጣል።

መግለጫውን በቀጥታ በ @tikvahethmagazine መከታተል ትችላላችሁ።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ

Via @Tikvahethmagazine


“ በሙያው ጠቅላላ ሀኪም ነው ቤተሰብ ለመጠየቅ እየሄደ ነው በጥይት ተመትቶ የተገደለው ” - የሟች ጓደኛ

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን መራቢቴ ወረዳ በእናት ሆስፒታል የጠቅላላ ህክምና ሀኪሙ “በተተኮሰበት ጥይት” መገደሉን የቅርብ ሰዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ።

ዶክተር ገብረሚካኤል ወልደ መላክ ተገደለ የተባለው ቤተሰቦቹን ለመጠየቅ በመኪና እየተጓዘ መራቢቴ አካባቢ መሆኑን ገልጸዋል።

ቃላቸውን የሰጡን የሟች ጓደኛ፣ “ ቤተሰብ ለመጠየቅ እየሄደ ባለበት ነው በጥይት ተመትቶ የተገደለው። ትላንት ጠዋት 3 ሰዓት ነው የተገደለው ” ሲሉ ተናግረዋል።

ሌሎች የቅርብ ሰዎቹ በበኩላቸው፣ “ እናት ሆስፒታል ነበር ተቀጥሮ የሚሰራው። መንገድ ላይ መኪና ውስጥ ሆኖ ነው የተተኮሰበት ሰው ሲደርስ ሞቶ ነው ተገኘ ” ብለዋል።

የሙያ አጋሮቹ፣ “ ሕይወት የሚያድን ሀኪም ለዚያውም በጥይት እንዴት ሕይወቱ ባጭር እንዲቀጭ ይፈረድበታል ? እኛም ከፍተኛ ስጋት አለብን ” ሲሉ ሀዘነንና ስጋታቸውን ገልጸዋል።

የገዳዮቹ ማንነት እስካሁን እንዳልታወቀ፣ የቀብር ሥርዓቱ የሚፈጸመው ዛሬ እንደሆነ ተመልክቷል።

ለቲክቫህ ኢትዮጵያ የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው ከሆነ፣ ዶክተር ገብረ ሚካኤል በ2015 ዓ/ም በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ የተመረቀና ገና ወጣት ሀኪም ነው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia


28 ባንኮች 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር መጭበርበራቸው ተነገረ።

28 የኢትዮጵያ ባንኮች 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር መጭበርበራቸውን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ዓመታዊ የገንዘብ ደህንነት ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል፡፡

የባንኩ ሪፖርት እስከ ሰኔ 2024 ድረስ ያሉ የገንዘብ እንቅስቀሴዎች ዙሪያ ትኩረቱን አድርጓል፡፡

ባንኩ በሪፖርቱ ላይ እንደጠቀሰው 28 የኢትዮጵያ ባንኮች 1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር በአጭበርባሪዎች ገንዘባቸውን አጥተዋል ብሏል።

የማጭበርበር ድርጊቶቹ የተፈጸሙት ፦
- በሐሰተኛ የገንዘብ ኖቶች፣
- በተሰረቁ የኤትኤም ማሽኖች፣
- በሐሰተኛ ቼኮች፣
- በሐሰተኛ የስልክ መልዕክት እና ተያያዥ መንገዶች አማካኝነት ነው፡፡

በዚህ ዓመት ባንኮች ያጡት ገንዘብ ከዓምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር በ300 ሚሊዮን ብር ጭማሪ እንዳሳየም በሪፖርቱ ላይ ተጠቅሷል፡፡

በኢትዮጵያ በአጠቃላይ ካሉ 31 ባንኮች ውስጥ 28ቱ ሲጭበረበሩ የቀሪዎቹ ሶስት ባንኮች ማንነት ግን በሪፖርቱ ላይ አልተጠቀሰም፡፡

ባንኮች ከአነስተኛ የብድር እና ቁጠባ ተቋማት ጋር በመቀናጀት ብድሮችን እየሰጡ ነው የተባለ ሲሆን ይህ አገልግሎት እየጨመረ መሄድ እና የበይነ መረብ ማጭበርበሮች መበራከት ባንኮች የሚያጡት ገንዘብ ሊጨምር እንደሚችል ብሔራዊ ባንክ በሪፖርቱ ላይ መጥቀሱን ከፌዴራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን የተገኘው መረጃ ያሳያል።

1 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ተጭበረበሩ የተባሉት ባንኮች ዝርዝር በይፋ አልተገለጸም።

@tikvahethiopia


" በጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ዳግም የመሬት ናዳ እና ጎርፍ ተከስቶ በሰዉና ንብረት ላይ ጉዳት አድርሷል " - የአከባቢው ነዋሪዎች

የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጎፋ ዞን ገዜ ጎፋ ወረዳ ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት ከሰሞኑ በአከባቢያቸዉ ነፋስ ቀላቅሎ እየጣለ ያለዉ ከባድ ዝናብ የመሬት ናዳ እና ጎርፍ በማስከተሉ በሰዉ ሕይወትና ንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን ተናግረዋል።

ከሚያዚያ 9/2017 ዓ/ም  ጀምሮ ለተከታታይ ቀናት በአከባቢዉ እየጣለ ያለዉ ዝናብ በተለይም ፦
- ጎሬ ኦዳ፣
- ጃዉላ ዉጋ ማሽታሌ፣
- ኤላ፣
- አማሮ ሻጌ፣
- ቡልቂ በተባሉ አከባቢዎች ባስከተለዉ ከባድ ነፋስ፣ ከፍተኛ የዉሃ ሙላት እና የመሬት መንሸራተት  የ3 ሰዎች ሕይወት ሲያልፍ ከ4 በላይ ቤቶች በመሬት ናዳዉ መስመጣቸዉንና፤ የእርሻ ማሳዎች እንዲሁም የቤት እንስሳት ጭምር በመሬት መንሸራተቱ መወሰዳቸዉን ነዋሪዎቹ አስረድተዋል።

በወረዳዉ ሰሞኑን በተከሰተዉ ዳግመኛ  የመሬት መንሸራተት አደጋ ምክንያት የተፈናቀሉ ነዋሪዎች በጎዶ አንደኛ ትምህርት ቤት እና በአንድ የሃይማኖት ተቋም ግቢ ተጠልለው እንደሚገኙ የሚናገሩት ነዋሪዎቹ የዝናብ ሁኔታዉ ቀጣይነት ያለዉ ስለሚመስል አሁንም ከፍተኛ ስጋት ዉስጥ መሆናቸዉን ተናግረዋል።

" በወረዳዉ የዛሬ ዓመት በተከሰተዉ የመሬት መንሸራተት አደጋ ምክንያት የተፈናቀሉ ዜጎችን መሉ በሙሉ መልሶ የማደራጀቱ ስራ ባልተጠናቀቀበት ይህ መከሰቱ ስጋታችንን ከፍ ያደርገዋልም " ብለዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገራቸዉ የገዜ ጎፋ ወረዳ አደጋ ስጋት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ማስረሻ ማናዬ በበኩላቸው በአካባቢው እየጣለ ባለዉ ከባድ ዝናብ በወረዳዉ አራት ቀበሌያት በሰዉ፣ በንብረትና በቤት እንስሳት ላይ ጉዳት ማድረሱን አስታዉቀዋል።

ተጨማሪ አደጋዎች እንዳይከሰቱ የወረዳዉ መንግስት በልዩ ተኩረት እየሰራ ነዉ ያሉት አቶ ማስረሻ ጉዳት የደረሰባቸውን ነዋሪዎች የማቋቋም ስራም እንደሚሰራ ገልፀዋል።

ባሳለፍነዉ ዓመት በአከባቢዉ የተከሰተዉ መሰል የመሬት መንሸራተትና ናዳ ምክንያት በርካታ ሰዎች መሞታቸዉ የሚታወስ ሲሆን አሁንም ድረስ በአከባቢው በስጋት የተፈናቀሉ ነዋሪዎችን ሙሉ በሙሉ መልሶ የማቋቋም ስራዉ አለመጠናቀቁን በቅርቡ የአካባቢው ነዋሪዎች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጸው ነበር።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
#TikvahEthiopiaFamilyHW

@tikvahethiopia


#AddisAbaba

" በ3 ወራት ውስጥ 943 ፍቺዎች እንዲሁም 53 ውሳኔ የተሰጠባቸው ጉዲፈቻዎች ምዝገባ ተከናውኗል !! "

የአዲስ አበባ ከተማ የሲቪል ምዝገባና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ ከፌደራል የመጀመርያ ፍርድ ቤት ጋር  የፍቺ እና ጉዲፈቻ ውሳኔዎችን መዝግቦ በአንድ መስኮት አገልግሎት ለመስጠት የጋራ ስምምነት ፈጽመው እየሰሩ ሲሆን ላለፉት 3 ወራት ውስጥ የተሰሩ ስራዎችን አፈፃፀም በጋራ ገምግመዋል።

በዚህም ወቅት በቀረበ ሰነድ 996 ተገልጋዮች በ3 ወራት የኩነት ምዝገባ አገልግሎቱን በፍርድ ቤቶች በአንድ መስኮት ማግኘታቸው ተመላክቷል።

ከዚህም ውስጥ ውሳኔ ያገኙ 943
#ፍቺዎች እንዲሁም 53 ውሳኔ የተሰጠባቸው #ጉዲፈቻዎች በወቅቱ ምዝገባ በማድረግ በአንድ ማዕከል በፍ/ቤቶች አገልግሎት መሰጠቱ ተመላክቷል።

Via
https://t.me/addisvaitalpress/9155

@tikvahethiopia


#DStvEthiopia

🏆 ኤምሬትስ ስታዲየም ከባድ ትንቅንቅ ይጠብቀዋል🔥

⚽️ ከ15 ዓመታት በኃላ አርሰናል ወደ ቻምፒዮንስ ሊግ ግማሽ ፍፃሜ ተመልሷል!

✨ መድፈኞቹ በአርቴታ እየተመሩ የኤንሪኬን በብዙ ሽልማቶች ያጌጠውን ፒኤስጂን ማሸነፍ ይችሉ ይሆን?
⚡️ ዴምቤሌ ፣ ሳካ ፣ ሃኪሚ እና ቲምበር የእንግሊዝና የፈረንሳይን ኮከቦች በሰሜን ለንደን መብራቶች ስር ይጫወታሉ!

🌟 የዋንጫውን አንድ እጅ የሚይዘው ቡድን ማነው?

ዲኤስቲቪ ያስገቡ ፣ ደንበኝነትዎን ያራዝሙ!
#ሁሉምያለውእኛጋርነው #UCL #ARSPSG


#Update

ለፍኖተ ጽድቅ ጠቅላላ ማኅበር ተሰጥቶ የነበረው የዘገባ ፍቃድ ለጊዜው ታገደ።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ከዚህ ቀደም በቤተክርስቲያን መሰረት እምነት፣ ሥርዓተ አምልኮና ትውፊት አክብሮ በቤተክርስቲያን ዙሪያ ዘገባ እንዲያከናውን ለፍኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን ፍቃድ መሰጠቱ ይታወሳል።

ሆኖም ግን በፍኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን በዕለተ ስቅለት " ቅድስት ድንግል ማርያም ቤዛዊተ ዓለም አትባልም " በሚል ርእስ የተላለፈው ትምህርትን ውዝግብ በማሰነሳቱና ቋሚ ሲኖዶስ በጉዳዩ ዙሪያ ተወያይቶ ውሳኔ ለመስጠት ለረቡዕ ሚያዚያ 22 ቀን 2017 ዓ.ም ቀጠሮ የያዘ በመሆኑና ጉዳዩ በሚገባ ተጣርቶ ውሳኔ እስከሚሰጠው ድረስ ከመምሪያው ለፍኖተ ጽድቅ ቴሌቪዥን የተሰጠው የዘገባ ፍቃድ ለጊዜው መታገዱን የቤተክርስቲያኒቱ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ዛሬ አሳውቋል።

@tikvahethiopia


የአዲስ አበባ ከተማ የተርሚናል አገልግሎት አሰራርና ቁጥጥር ደንብ ቁጥር 186/2017 ምን ይላል ?

የአዲስ አበባ ከተማ ካቢኔ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አስፈፃሚ አካላትን ሥልጣንና ተግባር እንደገና ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁጥር 84/2016 አንቀጽ 95 በተሰጠው ሥልጣን መሠረት ደንብ አውጥቷል፡፡

ደንቡ ምን ይላል ?

በተርሚናል አገልግሎት ሥራ ላይ የሚደራጁ ተርሚናል ኢንተርፕራይዞች የሥራ እና ክህሎት ቢሮ በሚያወጣው መስፈርት መሠረት እንደሚደራጁ ይገልጻል።

ቀደም ሲል ተደራጅተው በህጋዊ መንገድ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ የተርሚናል ኢንተርፕራይዞች መስፈርቱን አሟልተው ሲቀርቡ ዳግም እንዲደራጁ እንደሚድረገም ያመለክታል።

የአደረጃጀት መስፈርቱን ያሟሉ ማህበራት ሲደራጁ በተርሚናል ኢንተርፕራይዙ ስም መደበኛና ዝግ የሂሳብ አካውንት መክፈት እንደሚኖርባቸውም ይገልጻል።

በተርሚናል አገልግሎት ሥራ የተደራጁ ኢንተርፕራይዞች የሥራ ውል እንዲገቡ ይደረጋሉ።

የሚገቡት ውል ለ1 ዓመት ነው። የስራ አፈጻጸማቸው እየታየ ለአንድ አመት ለአንድ ጊዜ ብቻ ሊታደስ እንደሚችል ደንቡ ይገልጻል።

የተርሚ ማል ኢንተርፕራዞቹ የውል ዘመናቸው ከመጠናቀቁ በፊት የቁጠባ ካፒታላቸውን ታሳቢ በማድረግ ወደ ሌላ የሥራ ዘርፍ የሚሸጋገሩበር ሥራ በሥራና ክህሎት ቢሮ በኩል ይሰራል።

ኢንተርፕራይዞቹ ከሰበሰቡት ጠቅላላ ገቢ 30% (ሰላሳ በመቶ) የግዴታ ቁጠባ ይቆጠባሉ። 50% (ሃምሳ በመቶ) በመደበኛ ተንቀሳቃሽ የባንክ ሂሳብ ውስጥ ገቢ ይደርጋሉ።

የተርሚናል ኢንተርፕራይዞች ከሚያገኙት ጠቅላላ ገቢ ላይ 20% (ሀያ በመቶ) ለመንግስት ገቢ ያደርጋሉ።

(ሙሉ ደንቡ ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia

12 last posts shown.