TIKVAH-ETHIOPIA


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።
@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna
#ኢትዮጵያ

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


🔈 #የሹፌሮችድምጽ

“ የጸጥታ አካላት ጥበቃ ባለማድረጋቸው ለአጃቢ እስከ 2,000 ብር ለመክፈል ተገደናል። በቀናት ብቻ ከ12 በላይ ሹፌሮች ታግተዋል ” - ማኀበሩ

የጸጥታ መደፍረስ በሹፌሮችና ተሳፋሪዎች ግድያና እገታ ማስከተሉን፣ የጸጥታ አካላት ጥበቃ ባለማድረጋቸው አሽከርካሪዎች ለአጃቢ 2,000 ለመክፈል መገደዳቸውን ጣና የአሽከርካሪዎች ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።

“ የጸጥታ አካላት ጥበቃ ባለማድረጋቸው ለአጃቢ እስከ 2,000 ብር ለመክፈል ተገደናል። በቀናት ብቻ ከ12 በላይ ሹፌሮች ታግተዋል ” ሲልም በሁነቱ ተማሯል።

በአማራ ክልል ከገንዳውሃ ወደ ጎንደር ባለው መንገድ ረቡዕ ጥር 28 ቀን 2017 ዓ/ም አንድ ሰው ተገድሎ፣ ሁለቱ ደግሞ መቁሰላቸውን ገልጿል።

“ በአስር ቀናት ደቡብ ጎንደር 3 ሹፌሮች፣ በደባርቅ ዙሪያ 2 ረዳቶችና 6 ሹፌሮች፣ ገንዳውሃ 2 ሹፌሮች፣ አብርሃጀራ አንድ ሹፌር በታጠቁ አካላት ታግተዋል። በአብርሃጅራ ሹፌር ተተኩሶበት አምልጧል፤  ሁለት ቦቴዎችን ወቅንና ገደብዬ መካከል አግተዋቸዋል ” ነው ያለው።

ማኀበሩ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጠው ቃል በዝርዝር  ምን አለ ?

“ ከአሸሬ እስከ ሶረቃ የሚያስፈራ ቦታ አለ። በፈቃድ ለታጠቁ የአካባቢው ሰዎች 2,000 ብር እየከፈልን ነው የምናልፈው። በቅርቡ አንድ አጃቢ አጋች መትቷል ሹፌር ሊያግት ሲል ወርዶ ተኮሰበት።

ጨንቆን ነው እንጂ ይሄ ሂደት ደግሞ መጥፎ ነው። ህግ ባለመከበሩ ምክንያት ለሹፌሮች እለታዊ መፍትሄ ሆኗል። ግን የአጃቢነት ስራ እየሰሩ ያሉ ሰዎች እንዴት ነው የአካባቢ ሰላም እንዲመለስ የሚፈልጉት?

ስለዚህ እገታ ያለባቸው ቦታዎች ይታወቃሉ። በአርማጭሆ በኩል ከከተማው አፍንጫ ስር ከ10 ጊዜ በላይ እገታ ተፈጽሞበት ቦታው ላይ የጸጥታ አካል አይቀመጥም። 

የጸጥታ ዘርፉ ትኩረት ቢሰጥ ችግሩን መቆጣጠር ይችላል። ምክንያቱም በአንድ አጃቢ ከፍለን የምናልፈው አካባቢ ነው። መዝረፊያ በሮች የሚታወቁ ናቸው”
ብሏል።

ለአጃቢ ከመክፈል በተጨማሪ ሹፌሮች ከጸጥታ ስጋት አንጻር በ100ዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮችን ዙሪያ ጥምጥም እንዲጓዙ እየተገደዱ መሆኑም ተገልጿል።

ማኀበሩ በመንገዱ ዙሪያ ምን አለ ?

“ በደባርቅ በኩል ባለው መንገድ ከደብረ ታቦር ጋይንት መንገዱ ችግር ትልቅ አለበት። መንገዱ አማራ ክልል ከጅቡቲ የሚገናኝበት ነው። ማደበሪያ የሚገባው በጋይንት ነው። በሚሌ፣ ጭፍራ፣ ሃራ፣ ወልዲያ አድርጎ በደብረ ታቦር አድርጎ ይመጣል።

ግን ማዳበሪያ የሚጭኑ ተሽከሪካሪዎች በዚህ አመት በጸጥታው ችግር ምክንያት ተጨማሪ መንገድ እየተጓዙ በአዲስ አበባ በኩል ለመምጣት ተገደዋል። ከደጀን በእጀባ ነው የሚመጡት ወደ ጎጃምና ጎንደር ጭምር።

በጸጥታው ችግር ተሽከርካሪዎች ከ500 ኪሎ ሜትር በላይ ተጨማሪ መንገድ ለመሄድ ተገደዋል። ይህ ለአርሶ አደሩም ጉዳት አለው። 1,950 ብር ነው አንድ ኩንታል ማዳበሪያ ከጅቡቲ የሚመጣው። ትራንስፓርት ኮስቱ 1,900 ብር ሲሆን፣ የማዳበሪያው ዋጋ ይንራል።

በጋይንት ቦቴዎች ይሄዳሉ። ጭነው ይመጡና በጸጥታው ችግር መመለሻ ሲያጡ በደባርቅ፣ ዛሪማ፣ በሽሬ፣ ከሽሬ መቀሌ፣ ከመቀሌ አብዓላ አድርገው በአፍዴራ ይወጣሉ። ይሄ ማለት ከ600 በላይ ተጨማሪ ኪሎ ሜትር ይጓዛሉ።

በጎንደር መተማ መንገድ በመተማ በኩል ነው ኢምፖርት ኤክስፖርት የሚገባው። የመተማ ጎንደርን መንገድ የጸጥታ ችግሩን በመፍራት አሽከርካሪዎች በአብርሃጅራ ዙረው እየገቡ ነው። 

180 ኪሎ ሜትር ሲጓዙ የነበሩ አሽከርካሪዎች 140 ኪሎ ሜትር በመጨመር 320 ኪሎ ሜትር ይጓዛሉ ”
ብሏል።

(ስለጉዳዩ ለጸጥታ አካላት ጥያቄ የምናቀርብ ይሆናል)

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia


" ፈጣሪ ምን ይሳነዋል ? የማይገመተው በሱ ፍቃድ ሆኗል። በወጣትነቴ ያጣሁትን የልጅ ጥማት በእርጅና ጊዜ መልሶልኛል ፈጣሪ ይመስገን ! ልጄን የማሳድግበት ጤና ይስጠኝ እድሜ ይጨምርልኝ " - በ76 ዓመታቸው ወንድ ልጅ የወለዱት ወ/ሮ መድህን ሓጎስ

የመቐለ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ መድህን ሓጎስ በ76 ዓመታቸው ወንድ ልጅ የመታቀፋቸው ጉዳይ አነጋጋሪ ሆኗል።

የድምፂ ወያነ ቴሌቪዥን በእናቲቱ መኖሪያ የተዘጋጀውን የክርስትና ድግስ ላይ ተገኝቶ ያጠናቀረውን ፕሮግራም ከትላንት ጀምሮ በሰፊው ህዝብ ጋር ሲዳረስ ነበር።

እናቲቱ በ76 ዓመታቸው መውለዳቸው በዓለም የድንቃድንቅ መዝገብ ላይ እንዲሰፍር ያለመ የ ' X ' ዘመቻም አለ።

የማህበራዊ ትስስር ገፅ ተጠቃሚዎች " እናቲቱ በተለመደው ተፈጥሯዊ መንገድ ነው የውለዱት " ፤ " የለም በህክምና ቴክኖሎጂ በመታገዝ ነው ልጃቸውን የታቀፉት " የሚሉ ክርክሮች በማንሳት ሲፅፉ ታይተዋል።

እናቲቱ በድምፂ ወያነ ቴሌቪዥን እና ሰግለለት ለተባለ ዩቱብ በሰጡት ቃለ-መጠይቅ የተከራካሪዎቹን ጥያቄ ያልመለሰ ድፍን ያለ እንደሆነ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ገልጿል።

የመቐለው አባላችን ፤ እናቲቱ በትግርኛ ቋንቋ ለሚድያዎች የሰጡት ቃለ-መጠይቅ እና የማህበራዊ የትስስር ገፅ ተጠቃሚዎች ያገኘውን መረጃ ከታማኝ የመረጃ ምንጭ ጋር ለማቀናጀት ጥረት አድርጓል።

ወ/ሮ መድህን ሓጎስ ከዚህ በፊት ልጅ  እንዳልወለዱ ፤ የአሁኑ የመጀመሪያ ልጃቸው መሆኑን በልጃቸው ክርስትና ቀን በአንደበታቸው አረጋግጠዋል። 

ወ/ሮ መድህን በሰጡት ቃለ-መጠይቅ ፅንሳቸውን እስከ 8 ወር ድረስ ደብቀውት እንደነበር ከመግለፅ ባለፈ በተለመደው መንገድ ነው የወለዱት ወይስ በህክምና የታገዘ የስነ ተዋልዶ ዘዴ (IVF or In Vitro Fertilization) ጥበብ ያሉት ነገር የለም።

የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ከታማኝ ምንጭ ባገኘው መረጃ እናቲቱ የወለዱት በኢንቪትሮ ፈርትላይዜሽን (IVF) ማለትም የወንዱ ዘር እና የሴቷን እንቁላል አውጥቶ ከማህፀን ውጪ በላብራቶሪ ውስጥ እንዲዋሃዱ የሚደረግበት በህክምና የታገዘ የስነ ተዋልዶ ዘዴ መሆኑን ተረድቷል።

ወ/ሮ መድሂን ህክምናውን ለማግኘት ወደ ታይላንድ ተጉዘዋል።

በዚያው ፅንሱ የ3 ወር ዕድሜ እስኪ ሞላው ድረስ ቆይተዋል።

ከሦስተኛው እስከ ወሊድ ባሉት ጊዜያት የፅንስ ክትትል በመቐለ በሚገኝ አንድ የግል ህክምና ተከታትለው በቀዶ ህክምና ለመውለድ መቻላቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ አረጋግጧል።

በኢትዮጵያ የወሊድ ህክምና በህግ የተፈቀደው IVF / In Vitro Fertilization የህክምና ጥበብ በመቐለ ጨምሮ በአዲስ አበባ እንደሚሰጥ እየታወቀ እናቲቱ ለምን ውጭ ድረስ ለመጓዝ እንደፈለጉ የታወቀ ነገር የለም።

በ76 ዓመታቸው ነው ልጅ ለማቀፍ የቻሉት ወ/ሮ መድህን ሓጎስ እሳቸውም ልጃቸውም በመልካም የጤና ሁኔታ ላይ ይገኛሉ።


" ፈጣሪ ምን ይሳነዋል ? የማይገመተው በሱ ፍቃድ ሆኗል። በወጣትነቴ ያጣሁትን የልጅ ጥማት ፤ በእርጅና ጊዜ መልሶልኛል ፈጣሪ ይመስገን። ልጄን የማሳድግበት ጤና ይስጠኝ እድሜ ይጨምርልኝ " ብለዋል።

ከዚህ ቀደም እ.ኤ.አ. በመስረከም 7/2019 የህንድዋ አንድህራ ፕራደሽ ግዛት ተወላጅ የሆኑት ወ/ሮ ማንጋያማ ያራማቲ በ73 ዓመታቸው በIVF ልጅ በማግኘት በእድሜ ትልቋ ተብለው ነበር።

ባለፈው ዓመት ሳፊና ናሙኩዋያ የተባሉ ኡጋንዳዊ ሴት በIVF ህክምና የመንትያ ልጆች እናት መሆን እንደቻሉ በስፋት ተዘግቦ ነበር።

እንደ አንድ የጤና መረጃ አሜሪካ ውስጥ ከሚወለዱት ህጻናት 2% የሚሆኑት በIVF, or  In Vitro Fertilization የህክምና መንገድ ሲሆን ከ8 ሚሊዮን በላይ ህፃናት በዚህ መንገድ ተወልደዋል።

NB. ኢንቪትሮ ፈርትላይዜሽን (IVF) ማለት የወንዱ ዘር እና የሴቷን እንቁላል አውጥቶ ከማህፀን ውጪ በላብራቶሪ ውስጥ እንዲዋሃዱ የሚደረግበት በህክምና የታገዘ የስነ ተዋልዶ ዘዴ ነው። በላብራቶሪ ውስጥ የተፈጠረው ፅንስ በሚፈለገው ደረጃ እድገቱን ከቀጠለ በኋላ ወደ ሴቷዋ ማህፀን በማስገባት የተፈጥሮ እርግዝና ሂደቱን እንዲቀጥል የሚደረግ ይሆናል፡፡

በዚህ ላይ ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተጨማሪ የጤና ባለሙያ ማብራሪያ ለማቅረብ ጥረት ያደርጋል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia


" ከሞተር ሣይክል ሲቀነስ በነበረ ቤንዚን ምክንያት የተነሳ እሳት አንድ ቤት መሉ በሙሉ ሲያወድም በሁለት ሰዎች ላይ ጉዳት አድርሷል " - የታርጫ ከተማ ፖሊስ

በዳዉሮ ዞን የተርጫ ከተማ ፖሊስ አዛዥ ም/ኢንስፔክተር ሙሉጌታ መንግስቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንዳስታወቁት በትናንትናው ዕለት ምሽት 2 ሰዓት ገደማ በከተማ አስተዳደሩ " ቦዲ ቀበሌ " አንድ ግለሰብ ከማደያ በሞተር ሣይክል የቀዳዉን ቤንዚን ወደ ፕላስትክ ሀይላንዶች እየቀነሰ በነበረበት ወቅት ለብርሃን ተብሎ ከተለኮሰዉ ሻማ ከቤንዚኑ ጋር በመሳሳቡ ምክንያት በተፈጠረ የእሳት አደጋ ከቁጥጥር ዉጪ በመሆኑ ጉዳት ማድረሱን አስታዉቀዋል።

ሰዓቱ አመሻሽና ወቅቱም ነፋሻማ ስለነበር እሳቱን በቀላሉ ለመቆጣጠር አዳጋች አድርጎት እንደነበር ተናግረዋል።

ፖሊስ አዛዡ እሳቱን ለማጥፋት የአካባቢዉ ሕብረተሰብ በነቂስ ባይረባረብ ግለሰቡም ሆነ ባለቤቱ ሕይወታቸዉ ያልፍ እንደነበር ተናግረዋል።

በአደጋዉ አቶ አስናቀ አበራ በተባሉ ግለሰብና ባለቤታቸዉ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ሲሆን የአደጋዉ መንስኤ የነበረዉን ሞተር ሳይክል ጨምሮ ቤታቸውም ሙሉ በሙሉ መዉደሙን ፖሊስ አስታዉቋል።

በአሁኑ ወቅተም ጉዳት የደረሰባቸውን ሁለቱ ግለሰቦች በታርጫ አጠቃላይ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየየተደረገላቸው ነው።

የቤንዚን እጥረት መኖሩን ተከትሎ በየአካባቢው በየቤቱ የሚደረጉ የቤንዚን ማከማቸት ለእሳት አደጋዎች ምክንያት በመሆን በሰዉ ሕይወትና በንብረት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ሊያከትል ስለሚችል ጥንቃቄ ሊደረግ እንደሚገባም ም/ኢንስፔክተር ሙልጌታ መንግስቱ አሳስበዋል።

@tikvahethiopia


🎁 በቅናሽ ላይ ቅናሽ የተደረገባቸው ልዩ ጥቅሎች በቴሌብር ሱፐርአፕ!!

✨ ከመደበኛ ጥቅሎች እስከ 25% ልዩ ቅናሽ የሚያገኙባቸውን የድምጽ እና የኢንተርኔት ጥቅሎች በዕለታዊ፣ ሳምንታዊ እና ወርኃዊ አማራጮች ያገኟቸዋል፡፡

🔗 በቴሌብር ሱፐርአፕ https://onelink.to/uecbbr ብቻ!


ቴሌብር - እጅግ ቀላል፣ ፈጣን፣ ምቹ እና አስተማማኝ!

#Ethiotelecom #telebirr #DigitalAfrica #DigitalEthiopia #RealizingDigitalEthiopia


#ነዳጅ

የነዳጅ ምርቶች ዋጋ በነበረበት ይቀጥላል ተብሏል።

የየካቲት ወር የነዳጅ ምርቶች የችርቻሮ መሸጫ ዋጋ በጥር ወር በነበረበት የሚቀጥል መሆኑን የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታውቋል።


➡ አንድ ሊትር ቤንዚን 101.47 ብር

➡ አንድ ሊትር ናፍጣ 98.98 ብር

➡ አንድ ሊትር ኬሮሲን 98.98 ብር

➡ የአውሮፕላን ነዳጅ 109.56 ብር

➡ አንድ ሊትር ከባድ ጥቁር ናፍጣ 105.97 ብር

➡ አንድ ሊትር ቀላል ጥቁር ናፍጣ 108.30 ብር

#ነዳጅ #ኢትዮጵያ

@tikvahethiopia


“በሌሎች ተብሎ የተገለጸው ቃጠሎ በምርመራው ያልተደረሰባቸው ማለት ነው” - ፌደራል ፓሊስ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ

የኢትዮጵያ ፌደራል ፓሊስ በ2017 ዓ/ም በ6 ወራት በአዲስ አበባና በሌሎች ቦታዎች የተከሰቱ 103 የእሳት ቃጠሎ አደጋዎችን መንስኤ “በፎረንሲክ ምርመራ” ማጣራቱን የሚገልጽ ውጤት ይፋ አድርጓል።

50 ቃጠሎዎች በኤሌክትሪክ ቴክኒክ ችግር ፣ 11 በመካኒካል ችግር ፣ 10 ሆን ተብሎ ፣ 17 በቸልተኝነት፣ 15 በሌሎች ምክያቶች የደረሱ መሆናቸውን ገልጿል።

አጠቃላይ ባለፉት 6  ወራት በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ 96 እና በክልሎች ደግሞ 7 በአጠቃላይ እንደ ሀገር 103 የእሳት ቃጠሎ አደጋዎች ደርሰው የአደጋ መንስኤዎችን ማጣራቱን ጨምሮ ገልጿል።

ከዚሁ ጋር በተያያዘ ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም ምሽት በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ሸማ ተራ ነባር የገበያ ማዕከልና በአካባቢው የደረሰው የእሳት አደጋ መንስኤ በኤሌክትሪክ ቴክኒክ ችግር የተከሰተ አደጋ መሆኑን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ገልጿል።

በግማሽ ዓመቱ በ582 መኖሪያ ቤት፣ በ12 ተሽከርካሪዎች፣ በ1965 ንግድ ቤቶች፣  በ6 ፋብሪካዎችና የተለያዩ ድርጅቶች በቃጠሎ ምክንያት ጉዳት ስለመድረሱ አመልክቷል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ፣ 15 ቃጠሎ በሌሎች ምክንያቶች እንደተከሰቱ ገልጿችኋል፤ ሌሎች ሲባል ምንድን ናቸው? የሚልና ተጨማሪ ጥያቄዎችን ለፌደራል ፓሊስ አቅርቧል።

በፌደራል ፓሊስ የሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ ኃላፊ አቶ ጀይላን አብዲ፣ “በሌሎች ተብሎ የተገለጸው ቃጠሎ ስቲል በምርመራው ያልተደረሰባቸው ማለት ነው” ሲሉ መልሰዋል።

“ለምሳሌ እሳት አደጋ ይደርስና ከዛ ቦታ ላይ ለማስረጃ የሚሆኑ ኢቪደንሶችን፣ ማስረጃዎችን ማጥፋት፣ ቁሳቁሶችን ጠራርጎ ማውጣት እሳቱ ከጠፋ በኋላ። አሁን ይሄ አይነት ቃጠሎ በምን እንደተፈጠረ አይታወቅም” ብለዋል።

“ሆን ተብሎ በሰው” የደረሱ 10 ቃጠሎች በፈጸሙ እርምጃ ተወስዷባቸዋል? ስንል ላቀረብነው ጥያቄ የሰጡን ምላሽ፣ ደግሞ፣ “ተጠያቄ ይሆናሉ ተጣርቶ። ይሄ ፕሮሰስ ላይ ነው። ኢቪደንሱ ተገኝቷል። በዚህ ኢቪደንስ መሰረት ይጠየቃሉ” የሚል ነው።

“ለምሳሌ አንድ ሰው ‘ራሱን አቃጥሎ ነው የሞተው’ ብሎ ሰው ቢገድል ኢቪደንሱ ሲገኝ፣ ግድያው በሰው መሆኑ ሲረጋገጥ ለግድያውም ተጠያቂ ነው የሚሆነው” ሲሉ በምሳሌ አስረድተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን ያክል ሰዎች ናቸው? “ሆን” ብለው በማቃጠል የተጠረጠሩት? ሲል ላቀረበው ጥያቄ ኃላፊው፣ “አሁን ስለእሳቱ ብቻ ነው መግለጽ የፈለግነው። ወደፊት ይገለጻል” ከማለት ውጪ ዝርዝር ማብራሪያ ከመስጠት ተቆጥበዋል።

በቸልተኝነት የደረሰ ቃጠሎ ማለትስ ምን ማለት ነው? ለሚለው ጥያቄም፣ “ለምሳሌ ሻማ አቀጣጥሎ ሳያጠፋ ቢተኛ፣ ተሽከርካሪ ላይ ጌጁ ሙቀት መጨመሩን እያሳዬ አሽከርካሪው እርምጃ ካልወሰደ በቸልተኝነት ይቃጠላል እንደዛ ማለት ነው” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

“በቸልተኝነት ማለት ባልተገባ ሁኔታ ወይም በነግሊጀንስ ማለት ነው” ነው ያሉት አቶ ጀይሉ።

ደረሱ በተባሉት 103 የእሳት ቃጠሎ አደጋዎች ምን ያክል ንብረት እንደወመስ ታውቋል? ስንል ጠይቀናቸው በሰጡን ምላሽ፣ “እሱ ሌላ ነው። አሁን ዋናው ነገር በምን ተቃጠለ የሚለው ነው የተጣራው” ብለዋል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia


#እንድታውቁት

ልዩ መለያ ኮድ (QR Cod) የተካተተበት የደረሰኝ ህትመት ጥያቄ የማቅረቢያ ቀነ ገደብ እስከ የካቲት 30 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ እንዲራዘም ተወሰነ።

ከዚህ ቀደም የደረሰኝ ህትመት ጥያቄ ማቅረብ የሚቻለው እስከ ጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም ብቻ መሆኑ ተገልጾ ነበር።

በዚህ መሰረት ቁጥራቸው 88,717 የሆኑ ግብር ከፋዮች የህትመት ጥያቄ ማቅረብ መቻላቸውን የገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሤ ከክልል እና ከተማ አስተዳደር የገቢ ዘርፍ አመራሮች ጋር በበይነ መረብ ባደረጉት ውይይት ገልጸዋል፡፡

ሆኖም በተለያዩ ምክንያቶች የህትመት ጥያቄያቸውን ያላቀረቡ ግብር ከፋዮች መኖራቸው ታሳቢ በማድረግ የህትመት ጥያቄ ማቅረቢያ ቀነ ገደብ እስከ የካቲት 30 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ እንዲራዘም በውይይቱ ተወስኗል፡፡

እስከ አሁን ድርስ የህትምት ጥያቄ ያላቀረቡ ግብር ከፋዮች በተጠቀሰው የጊዜ ገደብ ውስጥ የህትምት ጥያቄ እንዲያቀርቡ የተባለ ሲሆን የሲስተም መጨናነቅ እንዳይፈጠር የሲስተም ማሻሻያዎችን ማከናውን፣ የህትመት እና ስርጭት ተግባራት በሚፈለገው ደረጃ ለማከናወን ተጨማሪ የህትመት ማሽኖችን ወደ ስራ ማስገባት እና አትሞ በፍጥነት ማሰራጨት እንደሚገባ ስምምነት ላይ መደረሱ ተገልጿል።

@tikvahethiopia


#USA

አሜሪካ በአስገድዶ መድፈር ወንጀል ጥፋተኛ የተባለ ዜጋዋን አፍና ገደለች።

አሜሪካዊው የ52 ዓመቱ ድሜትሪስ ፍሬዘር በአስገድዶ መድፈር እና ግድያ ወንጀሎች ጥፋተኛ ሆኖ ተገኝቷል።

ግለሰቡ በአላባማ በርሚንግሀም ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ፓውሊን ብራውን የተባለች የ2 ልጆች እናትን በመኖሪያ ቤቷ ገብቶ አስገድዶ ከደፈረ በኋላ
#እንደገደላት ተገልጿል።

በሌላ ጊዜ የ14 ታዳጊ የአስገድዶ መድፈር ወንጀል መፈጸሙ መረጋገጡን ተከትሎ በተደራራቢ ወንጀሎች ክስ ተመስርቶበት ነበር።

ይህንንም ተከትሎ ተከሳሽ ድሚትሪስ ፍሬዘር በሞት ፍርድ እንዲቀጣ የተላለፈበት ሲሆን የፍርድ ሂደቱ የተካሄደው የሞት ፍርድ የማይተላለፍበት ሚቺጋን ግዛት ውስጥ በመሆኑ ፍርዱ ወደ እድሜ ልክ እስራት ተቀይሮለት ነበር።

በአላባማ ወንጀል መፈጸሙ በፍርድ ቤት መረጋገጡን ተከትሎ ወደ አላባማ እስር ቤት ተላልፎ ሊሰጥ ችሏል።

አላባማ ግዛት የሞት ፍርድ የተላለፈባቸው ፍርደኞችን አየር አጥሯቸው እንዲሞቱ የሚያደርግ ህግ ስላላት ይህም ወንጀለኛ በናይትሮጅን ጋዝ ታፍኖ ህይወቱ እንዲያልፍ መደረጉን ሮይተርስን ዋቢ በማድረግ አል አይን ኒውስ ዘግቧል።

@tikvahethiopia


➡️ " ቆጣሪው መንገድ ላይ ያለ በመሆኑ ማንም ሰው እየቀጠለ ይጠቀማል ሌሎች በተጠቀሙት እኛ ልንጠየቅ አይገባም " -ነዋሪዎች

🔴 " ከእነዚህ ቆጣሪዎች ሃይል ሲጠቀሙ የነበሩ ሰዎችን መረጃ ከእናንተ እንፈልጋለን " -የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት


በቦሌ አራብሳ ሳይት 3 ብሎክ 534 እና 535 ላይ የሚኖሩ ነዋሪዎች ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር የገቡበትን ውዝግብ በሚመለከት የአገልግሎቱ የምስራቅ አዲስ አበባ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ኦልጅራ በአካባቢው በመገኘት እውነታውን መመልከት እንደሚቻል ማስታወቃቸውን መዘገባችን ይታወሳል።

በዚህም መሰረት ያለውን እውነታ ለመመልከት እና ቅሬታውን ለመፍታት ከቀናት በፊት የአገልግሎቱ የምስራቅ አዲስ አበባ ሪጅን ዳይሬክተር ፣ የሪጅኑ የህግ ክፍል፣ የጸጥታ አካላት እና ነዋሪዎች ጋር በጋራ በመሆን ምልከታ ተደርጓል።

በምልከታው ወቅትም የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብም በቦታው በመገኘት ከአገልግሎቱ ሃላፊዎች እና ነዋሪዎች እውነታውን ለመመልከት ጥረት አድርጓል።

አገልግሎቱ በአራብሳ የጋራ መኖሪያ መንደር ሳይት ሶስት ሃይልን ከቆጣሪ ላይ በህገወጥ መንገድ ቀጥለው ሲጠቀሙ እንደተደረሰባቸው በመግለጽ የቆጣሪውን እዳ እንዲከፍሉ በማሳወቅ ሃይል ያቋረጠባቸው ብሎኮች 534፣ 535፣ 550 እና 551 ናቸው።

የቲክቫህ አባል ቦታው ተገኝቶ እንደተመለከተው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት " በህገ-ወጥ መንገድ ቆጣሪን እንዳይቆጥር በማድረግ ሃይል ሲጠቀሙ እንደነበር ደርሼበታለሁ " በማለት ሃይል ካቋረጠባቸው አራት ብሎኮች ውስጥ ሁለቱ ማለትም ብሎክ 550 እና 551 ሃይል ተቀጥሎላቸው አገልግሎት እያገኙ ነበር።

የእነዚህ ቆጣሪዎች እዳ ባልተከፈለበት እና ከሌሎች ብሎኮች ጋር በጋራ ሃይል በተቋረጠበት ሁኔታ ለእነርሱ በማን እና በምን ሁኔታ ተቀጠለ ? የሚል ጥያቄ ለሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ኦልጅራ ጥያቄ ቀርቦላቸው ነበር።

ዳይሬክተሩም ፤ የቆጣሪዎቹ እዳ ባልተከፈለበት ሁኔታ የእነሱ ሃይል መጠቀም ከእርሳቸው እውቅና ውጪ መሆኑን ገልጸዋል።

ከተቋረጠ በኃላ በራሳቸው ሃይሉን ቀጥለው ይጠቀሙ ወይስ የአገልግሎቱ ሰው ቀጠለላቸው የሚለውን ጉዳይ ማጣራት በማድረግ " አስፈላጊውን ህጋዊ እርምጃ እንወስዳለን " ብለዋል።

በመቀጠለም ምልከታ የተደረገው ብሎክ 534 እና 535 ላይ ሲሆን እነዚህ ብሎኮች " ሃይል በህገ ወጥ መንገድ ቀጥለው ሲጠቀሙ በኢንስፔክሽን ወቅት ተገኝተዋል " በሚል ሃይል ከተቋረጠባቸው ወር እንዳለፋቸው ተናግረዋል።

አገልግሎት በበኩሉ " ሃይሉን ያቋረጥኩት ከጋራ መኖሪያ መንደሩ ነዋሪዎች ለአንድ ዓመት ከአራት ወር በላይ ቀጥዬ ተጠቅሚያለው ያሉ እና የሚጠቀምም ስለመኖሩ በደረሰኝ ጥቆማ መሰረት ነው " ብሏል።

ነዋሪዎች ከእነዚህ ቆጣሪዎች ሃይል ቀጥለው አለመጠቀማቸውን ተከራክረዋል።

የኤሌክትሪክ አገልግሎት ባለሞያዎች ግን የቆጣሪውን ሃይል ባቋረጡበት ወቅት እነዚህ ብሎኮች መጨለማቸውን እንደማስረጃ በመጥቀስ ሃይል በህገወጥ መንገድ እየተጠቀሙ ስለመሆኑ አመላካች ነው ብለዋል።

" ሃይል የተቋረጠብን ለብሎካችን የገባው ስሪ ፌዝ ቆጣሪ በመቆረጡ እንጂ ከተጠቀሰው ቆጣሪ ላይ ሃይል አልቀጠልንም " ሲሉ የተከራከሩት ነዋሪዎች " ቆጣሪው መንገድ ላይ ያለ በመሆኑ ማንም ሰው እየቀጠለ ይጠቀማል ሌሎች በተጠቀሙት እኛ ልንጠየቅ አይገባም " ሲሉ መልሰዋል።

" ከጋራ መኖሪያ ብሎኩም የተጠቀመ ቢኖር ለይቶ እነሱን ተጠያቂ ማድረግ የአገልግሎቱ ሃላፊነት ነው ሁሉም ባላጠፋው ለወር ያህል ነዋሪው ለምን ይቀጣል ? " ሲሉ ጠይቀዋል።

አገልግሎቱም በምላሹ " ከእነዚህ ቆጣሪዎች ሃይል ሲጠቀሙ የነበሩ ሰዎችን መረጃ ከእናንተ እንፈልጋለን " ቢልም ነዋሪዎች ለደህንነታቸው እንደሚሰጉ በመግለጽ ፈቃደኛ አልሆኑም።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የሪጅኑ ዳይሬክተር በቦታው በተገኙበት ወቅት ለነዋሪዎች መፍትሔ ለመስጠት ሃይሉን እንዲቀጠልላቸው ያደረጉ ሲሆን ለህገ ወጥ ድርጊት ምክንያት የተባለውን ቆጣሪም ከቦታው እንዲነሳ አድርገዋል።

ዳይሬክተሩ አቶ ብርሃኑ ሲጠቀሙ የነበሩትን አካላት ማንነት ከነዋሪዎቹ ወይም ኮሚቴዎቹ ማግኘት እንደሚፈልጉ እና በጊዜ ሂደት ማንነታቸውን የማጣራት ስራ እንደሚሰራ ገልጸዋል።

የኤሌክትሪክ ሃይሉ በድጋሚ እንዲቀጠል በተደረገበት ወቅት በብሎኩ ካሉ ሁለት ቆጣሪዎች ለመታዘብ እንደተቻለው 1,500 ብር የተሞላው በ19/02/17 ዓ/ም የነበረ ቢሆንም ሃይል እስከተቋረጠበት 15/04/17 ዓም ድረስ ባለው ሁለት ወር ውስጥ ከካርዱ ጥቃም ላይ የዋለው ከ 10 ብር በታች ሆኖ ተገኝቷል።

" ቆጣሪው ሲገናኝ ያሳየው የብር መጠን 1,492. 5  አና 1,455.32 ብር ነው ይህ ማለት በ2 ወር ጊዜ ውስጥ የተጠቀሙት ከ10 ብር በታች ነው ይህ ሁሉ ህብረተሰብ በ10 ብር 2 ወር ሊጠቀም አይችልም ያማለት ቀጥታ ሲጠቀሙ እንደነበር ተጨባጭ ማስረጃ ነው " ሲሉ አቶ ብርሃኑ ተናግረዋል።

በብሎኮች በመዟዟር በተደረገው ምልከታ በቀጥታ ያለቆጣሪ ከመስመር ላይ በመቀጠል ሃይል የሚጠቀሙ ሰዎች ስለመኖራቸው ለመታዘዘብ ተችሏል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia


" ከግምገማ በኋላ በደረስንበት ውጤት ነዋሪዎቹ መቶ በመቶ ጥፋተኞች ናቸው " - የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን

በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ አራብሳ ኮንዶሚኒየም ለኮንስትራክሽን ሥራ በገቡ እና እንዲነሱ ባልተደረጉ ቆጣሪዎች ምክንያት አንዳንድ ሰዎች ከእነዚህ ቆጣሪዎች በህገወጥ መንገድ ሃይል እንዲጠቀሙ ምክንያት ሆኗል መባሉ ይታወሳል።

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን በተመዘገቡት ቆጣሪዎች አማካኝነት በጋራ መኖሪያ መንደሩ በሚኖሩ ነዋሪዎች በህገወጥ መንገድ አገልግሎት ላይ የዋለ ከ400 ሺህ ብር በላይ እዳ ተመዝግቧል " ይከፈለኝ " ሲል በተደጋጋሚ ኮርፖሬሽኑን በደብዳቤ መጠየቁን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አሳውቆ ነበር።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ በአዲስ አበባ ከተማ በቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የሰሜን ቅርንጫፍ ጽ/ቤትን ምላሽ ጠይቋል።

ኮርፖሬሽኑ ጥፋቱ ያለው ነዋሪዎች ጋር ነው ብሏል።

" በህገ ወጥ መልኩ ቀጥለው ለምን ጸጥ ብለው ይጠቀማሉ ?  " ሲልም ጠይቋል። ' እንዳይቆጥር አድርገው ቀጥለው ሃይል ተጠቅመዋል ለገንዘቡም ተጠያቂ ሊሆኑ የሚችሉት እነርሱ ናቸው " ሲል መልሷል።

ጉዳዩን በተመለከተ ግምገማ መደረጉ የገለጸው ኮርፖሬሽኑ " በደረስንበት ውጤት ነዋሪዎቹ መቶ በመቶ ጥፋተኞች ናቸው በቅርቡ የነዋሪ ኮሚቴን፣ ኮንትራክተሮችን ጠርተን የጠራ ነገር እንይዛለን " ሲል አሳውቋል።

የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን የሰሜን ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ በላይ ሞቱማ (ኢንጂነር) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በዝርዝር ምን ምላሽ ሰጡ ?

ያንብቡ
👇
https://telegra.ph/TikvahEthiopia-02-07

@tikvahethiopia


#USA

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በዓለም አቀፉ የጦር ወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) ላይ ማዕቀብ ጥለዋል።

ትራምፕ " በአሜሪካ እና የቅርብ አጋሯ እስራኤል ላይ ቅቡለነት እና መሠረት የሌለው ተግባር እየፈጸመ ነው " ሲሉ የከሰሱትን የዓለም አቀፉ የጦር የወንጀለኞች ፍርድ ቤት (ICC) ላይ ማዕቀብ የጣሉበት ፕሬዝዳንታዊ ትዕዛዝ ላይ ፈርመዋል።

ትራምፕ ICC ላይ የጣሉት ዕቀባ እና ቪዛን የሚያጠቃልል ነው።

የቪዛ ዕቀባው የአሜሪካ ወይም የአጋሯቿ ዜጎች ላይ ምርመራ የሚያደረጉትንና የሚረዱ ግለሰቦች እና ቤተሰቦቻችን ዒላማ ያደረገ ነው።

ታራምፕ ይህንን ፕሬዝዳንታዊ ትዕዛዝ የፈረሙት የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታኒያሁ ዋሽንግተንን እየጎበኙ ባሉበት ወቅት ነው።

ባለፈው ጥቅምት ዓለም አቀፉ የጦር ወንጀለኞች ፍርድ ኔታኒያሁ በጋዛ ፈጽመውታል ባለው የጦር ወንጀል ምክንያት የእስር ትዕዛዝ አውጥቶባቸው እንደነበር ይታወሳል።

አሜሪካ የዚህ ዓለም አቀፍ ተቋም አባል አይደለችም። በተደጋጋሚም በአሜሪካ ዜጎች ላይ በፍርድ ቤቱ የሚተላለፍ ውሳኔዎችን ውድቅ ማድረጓን ቢቢሲ ዘግቧል።

@tikvahethiopia

11 last posts shown.