YeneTube


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


የሰላም ሚኒስትር ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ “ከ18 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ማወያየት ችያለሁ” ሲል ገለጸ

የሰላም ሚኒስትር በበጀት አመቱ “25 ሚሊዮን የህብረተሰብ ክፍሎችን ለማወያየት አቅዶ ከ18 ሚሊዮን የሚልቁትን ማወያየት ችሏል” ሲሉ ሚኒስትሩ አቶ መሐመድ ኢድሪስ መናገራቸው ተገለጸ።

ሚኒስትሩ ይህንን የገለጹት የተቋማቸውን የዘጠኝ ወር የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ለምክር ቤቱ የውጭ ግንኙነት እና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ባቀረቡበት ወቅት መሆኑን ከህዝብ ተዋካዮች ምክር ቤት ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

ሚኒስትሩ “18 ሚሊየን የማህበረሰብ ክፍል” በምን፣ እንዴት እና የት እንዳወያዩ በሪፖርታቸው ስለማካተታቸውም ይሁን አለማካተታቸውን የምክር ቤቱ መረጃ ያለው ነገር የለም።

ሚንስቴር መስሪያ ቤቱ “የፌዴራልና የክልል መንግስታትን እንዲሁም የህዝብ ለህዝብ ግንኙነትን ለማጠናከር በርካታ ስራዎች ሰርቷል” በሚል ከቋሚ ኮሚቴው አድናቆት ተችሮታል ሲል ምክር ቤቱ በይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ፌስቡክ ገጹ ባገራው መረጃ አስታውቋል።

መረጃው በተጨማሪም ቋሚ ኮሚቴው ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ “ለግጭት ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎችን አስቀድሞ በመለየት የግጭት ምንጮችን ከመገናኛ ብዙሃን ጋር በትብብር የማጋለጥ ስራዎች ላይ ትኩረት እንዲደረግ አቅጣጫ እንደተቀመጠለት አመላክቷል።

አቶ መሐመድ፣ “በየአካባቢው የሚከሰቱ ጥቃቅን ግጭቶችን ላይ ላዩን የብሄርና የሃይማኖት መልክ ያለው በማስመሰል በተዛባ ግንዛቤ ግጭቱን ከማስፋፋት ይልቅ፣ የግጭቱን እውነተኛ መንስኤ መፈለግና መፍትሄ መስጠት የተሻለ” ነው ሲሉ ጠቁመዋል ብሏል። ሚኒስቴru ዘላቂ ሰላምን ለማምጣት “ከሃይማኖት ተቋማትና ከሌሎች ተቋማት እንዲሁም የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር በቅንጅት እየሰራ ይገኛል” ሲሉ አቶ መሐመድ አስረድተዋል ብሏል።

@Yenetube


አዲሱ የጌታቸው ረዳ ፓርቲ ስሙ ታወቀ


በጌታቸው ረዳ ካሕሳይ የሚመራው አዲሱ ፓርቲ የትግራይ ሊበራል ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ እንደሚባል ተሰምቷል።

ግንቦት አምስት ቀን 2017 ዓ.ም የፓርቲው ምሥረታ ይፋ ይሆናል ያሉት ምንጮች ምርጫ ቦርድ ህወሃት ከፓርቲነት ለመሰረዝ እስከ ግንቦት አምስት ቀነ ገደብ መስጠቱ ይታወሳል።

"የእነ ጌታቸው" የሚባለው ሕወሓት ትናንት ባወጣው መግለጫ አዲስ ፓርቲ ሊያቋቁም እንደሚችል ፍንጭ መስጠቱ ይታወሳል።

@Yenetube @Fikerassefa


የቀድሞ የስልጤ ዞን ዋና አስተዳደሪ የአሁኑ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ ኃላፊ ክቡር አቶ አሊ ከድር ዛሬ በሞጆ የፍጥነት መንገድ ላይ በደረሰባቸው የመኪና አደጋ ህይወታቸው አልፏል።

@Yenetube @Fikerassefa


ኮሚሽኑ በመጀመሪያ ዙር 75 ሺ የቀድሞ የትግራይ ተዋጊዎችን ወደ ህብረተሰቡ ለመመለስ ቢያቅድም እስከ አሁን የተመለሱት 17 ሺህ ብቻ ናቸው ተባለ!

በአማራ ክልል ከ3ሺህ በላይ ታጣቂዎች የተሃድሶ ስልጠና ተሰጥቷቸው ወደ ማሕበረሰቡ ተቀላቅለዋል ተብሏል

የብሔራዊ ተሃድሶ ኮምሽን በትግራይ ክልል እስከ ሰኔ ወር ድረስ እንደሚጠናቀቅ በተገለጸው በመጀመሪያ ዙር ለ75 ሺህ የቀድሞ ተዋጊዎች የተሃድሶ ስልጠና በመስጠት ወደ ሰላማዊ ሕይወት ለመመለስ ቢያቅድም እስከ አሁን የተመለሱት 17 ሺህ ብቻ መሆናቸውን አስታወቀ።

ባለፈው ኅዳር ወር አጋማሽ 2017 ዓ.ም በብሔራዊ ተሃድሶ ኮምሽን ተጀምሮ የነበረው እንስቅስቃሴ ብዙ ሳይዘልቅ ለወራት ተቋርጦ መቆየቱን የብሔራዊ ተሃድሶ ኮምሽን ኮምሽነር ተመስገን ጥላሁን ተናግረዋል።

"በትግራይ ክልል በወቅቱ የነበረው ፖለቲካዊ አለመረጋጋት ለሥራችን ትልቅ እንቅፋት ሆኖ ነበረ" ያሉት ኮምሽነሩ አክለውም "የቀድሞ ተዋጊዎችን መረጃ ማጥራት፣ ከትጥቅ ርክክብ እና የትጥቅ ሁኔታ ማደራጀት ጋር ተያይዞ ማጥራት ያለብን ጉዳዮች ስለነበሩ በዚሁ ምክንያት ልናቋርጥ ተገደን ነበረ" ብለዋል።

Via AS
@YeneTube @Fikerassefa


የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከዓለም ባንክ ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ ሊቀበል ነው!

መንግስታዊዉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለመጀመሪያ ጊዜ ከአለም ባንክ ከፍተኛ መጠን ያለው የገንዘብ ድጋፍ በሚቀጥለው ሳምንት መጀመሪያ ላይ ለመቀበል በዝግጅት መሆኑ ተጠቆመ።

ከ650 ሚሊዮን ዶላር በላይ ከተመደበው ገንዘብ ውስጥ ከግማሽ በላይ የሚሆነው በዚህ የመጀመሪያ ዙር ዝውውር እንደሚካተት ይጠበቃል።

ይህ በአፈጻጸም ላይ የተመሠረተ የገንዘብ ድጋፍ የአለም ባንክ የፋይናንስ ሴክተርን የማጠናከር ፕሮጀክት አካል ሲሆን፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የፋይናንስ አቅሙን እንዲያሳድግና የኢትዮጵያን ሰፋ ያሉ የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን እንዲደግፍ ያለመ ነው።

ባንኩ ይህንን ድጋፍ ለማግኘት መንግስት ቦንድ ማውጣትንና የቦርድ ስብጥርን ማስተካከልን ጨምሮ የተወሰኑ ቅድመ ሁኔታዎችን አሟልቷል።

ይህን ተከትሎ በሚቀጥለው ሳምንት ቢያንስ 350 ሚሊዮን ዶላር መቀበል እንደሚችል ይጠበቃል። ይህ የገንዘብ ድጋፍ በተለይም ባንኩ ቀደም ሲል ለመንግስት የልማት ድርጅቶች በሰጠው ያልተመለሰ ብድር ምክንያት ያጋጠሙትን የፋይናንስ ተግዳሮቶች ለማቃለል ትልቅ እገዛ ያደርጋል ተብሏል።

የኢትዮጵያ መንግስት የንግድ ባንኩን ካፒታል ለማጠናከር ተጨማሪ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያደርግም ተገልጿል። ባለሙያዎች ይህ የዓለም ባንክ ድጋፍ የሀገሪቱን የፋይናንስ ሴክተር ለማጠናከር ወሳኝ እርምጃ እንደሆነ ይስማማሉ።

Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa


ለአማራ ክልል ዳኞች የተወሰነው የደመወዝ ጭማሪ በመዘግየቱ “ከፍተኛ ቅሬታ” ማስነሳቱ ተገለጸ

የአማራ ክልል ዳኞች ማህበር በክልሉ ለሚገኙ ዳኞች እና የጉባኤ ተሿሚዎች የደመወዝና የጥቅማ ጥቅም ጭማሪ ተፈጻሚ ሳይሆን በመዘግየቱ  “ከፍተኛ ቅሬታ” ማስነሳቱን ገለጸ። ለደመወዝ ጭማሪው የሚያስፈልገውን በጀት የአማራ ክልል መንግስት እንዲመድብ ለማድረግ፤ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት “የቅርብ ክትትል እና ጥረት” እያደረገ መሆኑን ማህበሩ አስታውቋል። 

የዳኞች ማህበሩ ይህን ያስታወቀው ትላንት እሁድ ሚያዝያ 19፤ 2017 ለአባላቱ ባስተላለፈው መልዕክት ነው። ማህበሩ በዚሁ መልዕክቱ፤ ፍርድ ቤቶችን ከማጠናከር እና የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት የጀመረውን የለውጥ ስራ የተሟላ ከማድረግ አኳያ የዳኞችን እና የጉባኤ ተሿሚዎችን ደመወዝ እና ጥቅማ ጥቅም ማሻሻሉ “የማይተካ ሚና ያለው” “መሰረታዊ ነጥብ” እንደሆነ አስገንዝቧል።

የዳኞች ደመወዝ እና ጥቅማ ጥቅም ጥያቄን ለመመለስ፤ የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ኮሚቴ አዋቅሮ ጥናት ካደረገ በኋላ በክልሉ ዳኞች አስተዳደር ዐብይ ጉባኤ አማካኝነት ዝርዝር መመሪያ ማጽደቁን ማህበሩ አስታውሷል።

ዐብይ ጉባኤው ካጸደቀው የደመወዝ እና ጥቅማ ጥቅም በተጨማሪ ሀገር አቀፍ የኑሮ ውድነት ማሻሻያ የደመወዝ ጭማሪ ለሁሉም ሰራተኛ የተደረገ መሆኑን በትላንቱ መልዕክቱ የጠቀሰው ማህበሩ፤ ሁለቱም “እስካሁን ተፈጻሚ ባለመሆናቸው” በዳኞች ዘንድ “ከፍተኛ ቅሬታ” እያስነሳ መሆኑን ገልጿል።

Via Ethiopia Insider
@YeneTube @FikerAssefa


በኢትዮጵያ የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት 71 በመቶ ደርሷል ሲል የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ገለፀ።

የተቀረው ህዝብ ንፅህናው ያልተጠበቀ ውሃ እንደሚጠቀምና ሃገሪቱ ንፅህናው የተጠበቀ ውሃን ለዜጎቿ ለማዳረስ በምታደርገው ጥረት፣ በተለይም በገጠራማው ክፍል መሰናክሎች እንዳሉ ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

ይህ የተገለፀው አክሽን ፎር ዘ ኒዲ የተሰኘው ሃገር በቀል ግብረ ሰናይ ድርጅት ጄኔቫ ከሚገኘዉ አለም አቀፍ የውሃ፣ አካባቢ እና ጤና ኢንስቲትዩት ጋር በውሃና በአካባቢ አያያዝ በጋራ ለመስራት ሚያዝያ 16 ቀን 2017 ዓ.ም በካፒታል ሆቴል በተስማሙበት መድረክ ነው::

በመድረኩ በህክምና መሳሪያዎች አቅርቦት ፤ ተያያዥ ሰብአዊ እና የልማት ድጋፎች ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነትም ተፈርሟል።

የመግባቢያ ስምምነቱ በተፈረመበት ወቅት የውሃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር አስፋው ዲንጋሞ ባደረጉት ንግግር፣ ኢትዮጵያ የንፁህ መጠጥ ውሃ አቅርቦትን ለማዳረስ በምታደርገው ጥረት መሰናክሎች እንዳሉ ገልፀው፣ በተለይም በገጠራማው አካባቢ ችግሩ እንደሚሰፋ ጠቅሰዋል።

መሰረታዊ የንፅህና አጠባበቅን በተመለከተም ከ10 በመቶ በታች ለሆነው የህብረተሰብ ክፍል ብቻ ተደራሽ እንደሚሆን በፈረንጆቹ 2020 የተደረገ ጥናት እንደሚያመላክት የተናገሩት ሚኒስቴር ዴኤታው፣ እንደዚህ ዓይነት ችግሮችን በማቃልለ ረገድ አክሽን ፎር ዘ ኒዲ ግንባር ቀደም ሚና የሚጫወት ግብረ ሰናይ ድርጅት መሆኑን ገልፀዋል።የድርጅቱ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ሳሊሁ ሱልጣን ሂዉማን ብሪጅ ከአሁን ቀደም ለነጌሌ ሆስፒልና ለገጠራማ አካባቢዎች በ40 ሚሊዮን ብር የሚገመቱ የህክምና ቁሳቁሶችን ድጋፍ ማድረጉን ተናግረዋል፡፡

ከዚህ በተጨማሪ ለነጌሌ ሆስፒልና ለገጠራማ አካባቢዎች 80 ሚሊዮን ብር የሚያወጡ ተጨማሪ የህክምና ቁሳቁሶችን ድጋፍ ለማድረግ መስማማቱን ተናግረዋል፡፡ በስምምነቱ መሰረት ለችግር ተጋላጭ የሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለመርዳት በታማኝነትና በቁርጠኝነት መስራት ይጠይቃል ተብሏል፡፡

Via Ethio FM
@YeneTube @FikerAssefa


⭐️ ⭐️ እንኳን ለብርሀነ ትንሳኤዉ በሰላም አደረሳችሁ።  ⭐️ ⭐️

የበዓል ስጦታ በማይታመን ዋጋ!!!

📍 ሳር ቤት ላይ አፖርትመንቶችን

በካሬ 64,200 ብር ብቻ

ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ታላቅ ቅናሽ

ባለ 2 እና ባለ 3 መኝታ አፖርትመንቶችን

ለመኖሪያ ምቹ እንዲሁም ለኢንቨስትመንት አዋጭ!!!

ታድያ ይህ እድል እንዳያመልጥዎ
ፈጥነዉ ይደዉሉ!!!

+251 950 05 56 55

ወይም በቴሌግራም

TG  @Davehomes

What’s up https://wa.me/message/KGIM2YTYQGNYO1


🌏IAT & IAIC INTERNATIONAL STUDENT FAIR🌎

✨Ready to study abroad and change your life?

🎓This is your chance to meet top university representatives from:

USA 🇺🇸 Canada 🇨🇦 Sweden 🇸🇪
Germany 🇩🇪 France 🇫🇷 Finland 🇫🇮 Denmark 🇩🇰 and more!

📆 May 3 & 4
🕐 3:00 - 10:00 (LT)
📍Ghion Hotel

Don’t forget to bring:
🪪Passport or Birth certificate
📚Transcripts or Student copy

✅Entrance Fee: FREE!!

💡Opportunities:
- Study loan options
- Learn about the scholarships offered

🏆Don’t miss this golden opportunity to take your future global!

🆓No entrance fee — just register now!

Click the link below to book your spot: 🔗
https://forms.gle/81ZueGK5d9R9Cg9P6


ሊቨርፑል የፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮናዎች ሆነዋል!  🎉

ዛሬ በአንፊልድ ቶተንሃምን 5-1 ያሸነፉበት ጨዋታ ቀዮቹ የ2024/25 የፕሪሚየር ሊግ ዋንጫን በይፋ አሸንፈዋል።  👏

ከመሀመድ ሳላህ ሪከርድ ሰባሪ ዘመቻ ጀምሮ ፣ አርኔ ስሎት በመጀመሪያዎቹ 12 ወራቶች በአሰልጣኝነት እስከ ማሸንፍ... እንዴት ያለ አስደናቂ የውድድር ዘመን ነበር።  🔥

በመርሲሳይድ ውስጥ PARTY TIME ነው!  🥳


ደብረፂዮን

"በትግራይ ጦርነት ወቅት ለተፈፀመው ወንጀልለ ፍትህ ማግኘት ያስፈልጋል፡፡ ይሁንና በአገር ውስጥ ይህንን ፍትህ ማግኘት አይቻልም፡፡ የተፈፀመው ወንጀል ዓለም አቀፋዊ እንደመሆኑ አጥፊዎች እንዲቀጡና ተጎጂዎች ፍትህ እንዲያገኙ ጉዳዩ በዓለም አቀፍ ደረጃ መዳኘት አለበት። ይህ ካልሆነ ዘላቂ ሰላም ይመጣል የሚል እምነት የለኝም።"

ዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል ለዲደብሊው ከሰጡት ቃለምልልስ የተወሰደ።

@Yenetube @Fikerassefa


💸 አዲስ! የሁሉፔይ ሪፈራል ፕሮግራም አሁን ተጀምሯል!

🤝 ጓደኞችዎን ወደ ሁሉፔይ ሲጋብዙ ከግብይታቸው 10% በብር ያገኛሉ!

💰 ወዳጆችዎ ስታር ወይም ፕሪሚየም ሲገዙ 10% ኮሚሽን ይደርስዎታል

💳 በየቀኑ እስከ 1000 ብር ወደ አካውንትዎ ማውጣት ይችላሉ

📱 የሪፈራል ሊንክዎን ለማግኘት:

1. ህሉፔይ አፕን ይክፈቱ
2. በሾፕ ስክሪኑ ላይ ያለውን 'earn money' ክፍል ይክፈቱ
'3. invite and earn' ቁልፍን ይጫኑ

ሪፈራል ሊንክዎን አጋሩ እና ገቢዎን ይጀምሩ! 🚀

📲 ሁሉፔይን ለመጠቀም ሁሉፔይ ሚኒ አፕን
https://t.me/HuluPayOfficialBot/start?startapp እዚህ ሊንክ ጋር ያገኛሉ 🔗።


ትራምፕ ሩሲያ ነፃ ያወጣቻቸውን አካባቢዎች ተቆጣጥራ መቀጠሏን በተመለከተ የያዙት አቋም "የማይለወጥ" መሆኑን አንድ ዘገባ አመላከተ

ዶናልድ ትራምፕ ዘለንስኪ ግጭቱን ለመፍታት የልዩ መልዕክተኛቸውን ሀሳብ ከመቀበል 'በስተቀር ሌላ ምርጫ የለውም' ብለው እንደሚያምኑ ለስቲቭ ዊትኮፍ ቅርብ የሆኑ ምንጭን ጠቅሶ አንድ የብሪታንያ ጋዜጣ ዘግቧል።

ምንጩ እንዳሉት ዋሽንግተን ኪዬቭ የማትስማማ ከሆነ ግጭቱ ለወራት ወይም ለዓመታት ሊቀጥል እንደሚችል ገልጻለች።

ትራምፕ ግጭቱን ለማቆም በሚደረገው ስምምነት ክራይሚያ የሩሲያ አካል ሆና ትቀጥላለች ሲሉ ቀደም ሲል አስታውቀዋል። የክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ጉዳዩን በተመለከተ በሰጡት አስተያየት 'ከሞስኮ ጋር ሙሉ በሙሉ የሚጣጣም ነው' ብለዋል።

@Yenetube @Fikerassefa


🚀 ቡስትግራም: ተመልካቾች እና ፎሎወሮች ያግኙ።

📣🔥👀📹👍


📹የቲክቶክ : ቪዲዮዎችዎ ብዙ ቪውስ፣ ላይኮች፣ ፎሎወሮች እና ኮመንቶች ያግኙ።

📷የኢንስታግራም: ፎሎወሮች፣ ላይኮች፣ ቪውስ እና ኮመንቶች ያግኙ።

📹የዩቲዩብ: ሰብስክራይበሮች እና ቪዲዮ ቪውስ በፍጥነት ያግኙ።

✈️ቴሌግራም: ቻነል መምበሮች፣ ፖስት ቪውስ፣ ላይኮች እና ሪአክሽኖች ይጨምሩ።

ቡስትግራም - የሶሻል ሚዲያ ገፅታዎን መገንባት አሁን በጣም ቀላል ሆኗል!`

📹 📷 📹 ✈️

LINK - 🔗 👉 https://t.me/boostgramPromoBot/boostgram 🕯📈


አሜሪካ ኤምባሲ ለዜጎቹ በሰጠው የማስጠንቀቂያ መልዕክት ስር በፌደራል ፖሊስ ስም የተሰጠው አስተያየት በተቋሙ ያልተላለፈ መሆኑን ፖሊስ አስተባበለ።

ተቋማችንን አስመልክቶ በአንዳንድ ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ  የሚዘዋወረውን የተዛባ መልዕክት ተመልክተናል። በአዲስ አበባ ከተማ አንዳች የፀጥታ ችግር ያለ ለማስመሰል የተደረገውን ጥረትም አስተውለናል።

ይሁን እንጂ እስከአሁን ባደረግነው ማጣራት መልዕክቱ በተቋማችን እንዳልተላለፈ እና ተቋማችንን የማይወክል መሆኑን እያስታወቅን ፖሊስም ጉዳዩን የበለጠ እያጣራ እንደሚገኝ እንገልፃለን።

የተላለፈው መልዕክትም ፍፁም ከከተማችን ነባራዊ የፀጥታ ሁኔታ ጋር የማይገናኝ ሲሆን አሁን ላይ የከተማችን ሰላምና ደኅንነት ከምን ጊዜውም በላይ በአስተማማኝ ሁኔታ ላይ እንዳለ እንገልፃለን።

Via:- ፌደራል ፖሊስ
@Yenetube @Fikerassefa


Forward from: YeneTube
⭐️ ⭐️ እንኳን ለብርሀነ ትንሳኤዉ በሰላም አደረሳችሁ።  ⭐️ ⭐️

የበዓል ስጦታ በማይታመን ዋጋ!!!

📍 ሳር ቤት ላይ አፖርትመንቶችን

በካሬ 64,200 ብር ብቻ

ለአንድ ሳምንት የሚቆይ ታላቅ ቅናሽ

ባለ 2 እና ባለ 3 መኝታ አፖርትመንቶችን

ለመኖሪያ ምቹ እንዲሁም ለኢንቨስትመንት አዋጭ!!!

ታድያ ይህ እድል እንዳያመልጥዎ
ፈጥነዉ ይደዉሉ!!!

+251 950 05 56 55

ወይም በቴሌግራም

TG  @Davehomes

What’s up https://wa.me/message/KGIM2YTYQGNYO1


Forward from: YeneTube
🌏IAT & IAIC INTERNATIONAL STUDENT FAIR🌎

✨Ready to study abroad and change your life?

🎓This is your chance to meet top university representatives from:

USA 🇺🇸 Canada 🇨🇦 Sweden 🇸🇪
Germany 🇩🇪 France 🇫🇷 Finland 🇫🇮 Denmark 🇩🇰 and more!

📆 May 3 & 4
🕐 3:00 - 10:00 (LT)
📍Ghion Hotel

Don’t forget to bring:
🪪Passport or Birth certificate
📚Transcripts or Student copy

✅Entrance Fee: FREE!!

💡Opportunities:
- Study loan options
- Learn about the scholarships offered

🏆Don’t miss this golden opportunity to take your future global!

🆓No entrance fee — just register now!

Click the link below to book your spot: 🔗
https://forms.gle/81ZueGK5d9R9Cg9P6


አሜሪካ " ነገር አለ ! " ብላለች !

ባልታሰበ ሰዓት የሚከሰት የተቃውሞ እንቅስቃሴ ስላለ። አሜሪካ U.S. Embassy Addis Ababa በአዲስ አበባ ችግሮች ስለሚከሰቱ ራሳችሁን ጠብቁ ብላ ዜጎቿን አስጠንቅቃለች። ወንጀል በየትኛውም ቦታ እና በማንኛውም ጊዜ ሊከሰት ይችላል; ንቃት ተጋላጭነትን ለመቀነስ ቁልፍ ነው። ስለዚህ በኢትዮጵያ ያላችሁ ዜጎቼ ተጠንቀቁ ፤ ነገር አለ ብላለች። ሰልፎችን፣ ስብሰባዎችን እና ሌሎች ትላልቅ የህዝብ ስብስቦች ባሉበት ቦታ እንዳትገኙ ስትል ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ለዜጎቿ ሰታለች። ፖሊሶች እና ሁከትን አጣምራ ችግሮች ቅርብ ናቸው ያለችው አሜሪካ በኢትዮጵያ ውስጥ በቀጣይነት ምን ሊከሰት እንደሚችል የፖለቲካ መልዕክት ያለው እድምታዋን ተንፍሳለች። ሁሉም ሰው እንዲነቃ እናበረታታለን ብላለች።

14.7k 0 135 124 223

የጊዚያዊ አስተዳደሩ ዋነኛ ተልዕኮ “ከቀያቸው ተፈናቅለው በአስከፊ ኑሮ ውስጥ የሚገኙ ነዋሪዎችን መመለስ ነው” - ፕሬዚደንት ታደሰ ወረደ

በትግራይ ክልል ከቀያቸው ተፈናቅለው በከፋ ኑሮ ውስጥ የሚገኙ ተፈናቃዮች ወደ ቀያቸው የመመለስ ጉዳይ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ዋነኛ ተልዕኮ ነው ሲሉ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚደንት ጀነራል ታደሰ ወረደ አስታወቁ።

ፕሬዝዳንቱ ይህንን ያስታወቁት የአፍሪካ ህብረት የፕሪቶርያ የሰላም ስምምነት መከታተል፣ ማረጋገጥና ማክበር ተልእኮ ከፍተኛ ሀላፊ ሆኖው የተመደቡትን ሜጀር ጀነራል ሳማድ አክሶዴ ትላንት ሚያዚያ 16 ቀን 2017 ዓ.ም በፅህፈት ቤታቸው ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት ነው።

ፕሬዚደንቱ አክለውም ተፈናቃዮችን ለመመለስ፣ የትግራይ ሰራዊት ወደ ህብረተሰቡ የማቀላቀልና መልሶ የማቋቋም በአጠቃላይ በፕሪቶርያው ስምምነት አፈፃፀም ዙርያ ከፌደራል መንግስት ጋር በመቀራረብ እንደሚሰራ ገልፀዋል።

ሜጀር ጀነራል ሳማድ አክሶዴ በበኩላቸው በፕሪቶርያው ስምምነት አፈፃፀም፣ ተፈናቃዮች መመለስ በሚቻልበት ሁኔታ እንዲሁም በዲዲአር አፈፃፀም ሂደት ለመወያየት መምጣታቸውን በመጠቆም ለፕሪቶርያው ስምምነት የተሟላ ትግበራ የሚቻላቸውን ሁሉ እንደሚሰሩ መግለፃቸውን የፕሬዝዳንቱ የጽ/ቤት መረጃ ያሳያል።

@YeneTube @FikerAssefa


በአውሮፓ ውስጥ በቱጃሩ ሰው የፖለቲካ አመለካከት የተነሳ የቴስላ ተሽከርካሪ ሽያጭ 28.2 በመቶ ቀንሷል ተባለ

በአውሮፓ ውስጥ አዲስ የመኪና ሽያጭ ከአንድ አመት በፊት በመጋቢት ወር ከነበረው 28.2 በመቶ ቀንሷል ፣ ምንም እንኳን አጠቃላይ የባትሪ ኤሌክትሪክ ተሸከርካሪ ሽያጭ በወር ውስጥ 23.6 በመቶ እንደጨመረ የአውሮፓ አውቶሞቢል አምራቾች ማህበር (ኤሲኤኤ) መረጃ አሳይቷል። በአውሮፓ ውስጥ አጠቃላይ አዲስ የመኪና ሽያጭ በወር ውስጥ 2.8% ከፍ ብሏል ፣ በብሪታንያ እና በስፔን ባለሁለት አሃዝ ዝላይ ጭማሪ አሳይቷል። የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ ትርፍ መጨመር የነዳጅ እና የናፍታ መኪናዎች ውድቀትን እንደሚያካክስ መረጃው አመላክቷል።

በአውሮፓ የቴስላ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪ የሽያጭ ማሽቆልቆል ከቻይና ጋር ያለው ፉክክር እየበረታ እና አንዳንዶች በፖለቲካዊ አመለካከቱ ላይ ተቃውሞ በማሳየታቸው አሽከርካሪዎች የኤሎን ማስክን የኤሌክትሪክ መኪና ከመግዛት እየተቆጠቡ ይገኛል። አውሮፓውያን መኪና ሰሪዎችም ከቻይና ጋር ያለውም ፉክክር እየታገሉ ሲሆን በሀገር ውስጥ ገበያ ከፍተኛ ወጪን ቢኖርም ዋሃውን ለማውረድ እየተዋጉ ይገኜል። አሁን ላይ የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር በአውቶሞቢሎች ላይ የጣሉት የ25 በመቶ ታሪፍ ጋር በመታገል ለኢንዱስትሪው ያለውን ፈተና ይበልጥ አስከፊ አድርጎታል።

በአውሮፓ ህብረት ፣ በብሪታንያ እና በአውሮፓ ነፃ ንግድ ማህበር የመጋቢት ወር ሽያጮች ለሁለት ወራት ከነበረበት መቀዛቀዝ በኋላ ወደ 1.42 ሚሊዮን መኪናዎች ከፍ ብሏል ሲል የአውሮፓ አውቶሞቢል አምራቾች ማህበር (ኤሲኤኤ) መረጃ አሳይቷል በቮልስዋገን እና ሬኖ የተመዘገቡት የተሽከርካሪ ሽያጭ በ10.3 በመቶ እና 13 በመቶ ጭማሪ አሳይቷል። በአውሮፓ የቴስላ ሽያጭ ለሶስት ተከታታይ ወር ቀንሷል። ከዓመት በፊት ከነበረበት 28.2 በመቶ ሲቀንስ የጠቅላላ ገበያ ድርሻው ከአንድ አመት በፊት ከነበረበት 2.9 በመቶ ወደ 2 በመቶ ቀንሷል።

ዳጉ ጆርናል
@Yenetube @Fikerassefa

20 last posts shown.