YeneTube


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


መረጃዎችን ለመላክ @Fikerassefa

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


ዳንጎቴ ግሩፕ በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንቱን ከሲሚንቶ አልፎ ወደ ስኳር ምርት ላይ አመራ!

በቅርቡ በአፍሪካ ውስጥ ካሉት ትላልቅ የኢንዱስትሪ ፕሮጀክቶች አንዱ የሆነውን ግዙፉን የዳንጎቴ ማጣሪያ ፋብሪካን ካስጀመረ በኋላ፣ ዳንጎቴ ግሩፕ በኢትዮጵያ ያለውን የኢንቨስትመንት አይነቱን በከፍተኛ ደረጃ እያሰፋ መሆኑን አስታውቋል።

የግሪፑ ለቀመንበርና ስራ አስፈፃሚ አሊኮ ዳንጎቴ የአገሪቱ እየተሻሻለ የመጣውን የኢንቨስትመንት ምቹ ሁኔታ እና በቅርቡ ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጋር ያደረጓቸውን ውጤታማ ውይይቶች ተከትሎ በአዳዲስ ፕሮጀክቶች ላይ ለመሳተፍ ማቀዱን ገልጿል።

በናይጄሪያ የ 60,000 ሄክታር ስኳር እርሻ በማልማት ያገኘውን ልምድ በመጠቀም ኩባንያው በኦሞ ኩራዝ ስኳር ኩባንያ ውስጥ ኢንቨስት እንደሚያደርግ ጠቁሟል።

ወደፊትም ዳንጎቴ ግሩፕ የአገሪቱ የተፈጥሮ ጋዝ ክምችት ልማት ላይ በመመስረት የእርሻ ምርታማነትን ለማሳደግ ያለመ የማዳበሪያ ማምረቻ ፋብሪካ በኢትዮጵያ ለመመስረት እንቅድ እንዳለው ካፒታል ሰምታለች።

Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa


የጅቡቲ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር መሃሙድ የሱፍ አዲሱ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር ሆነው ተመረጡ!

የ59 ዓመቱ ዲፕሎማት ለሚቀጥሉት አራት ዓመታት ኮሚሽኑን እንዲመሩ የተመረጡት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሔድ በጀመረው የአፍሪካ ኅብረት ዓመታዊ የመሪዎች  ጉባኤ ላይ ነው።

የሱፍ የተመረጡት የኬንያውን የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር ራይላ ኦዲንጋ እንዲሁም የማዳጋስካሩን ሪቻርድ ራንድሪያማንድራቶን በማሸነፍ ነዉ።

55 አባል አገራት ያሉትን ህብረቱን እኤአ ከ 2017 ጀምሮ በሊቀመንበርነት ሲመሩ የነበሩትን ሙሳ ፋኪን በመተካት ያገለግላሉ።

@YeneTube @FikerAssefa


በመተሓራ አቅራቢያ በሬክተር ስኬል 6.0 የተመዘገበ!

-የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ፤ ከፍተኛ ጉዳት መደረሱ አልተገለጸም

በኦሮሚያ ክልል መተሓራ አቅራቢያ በሬክተር ስኬል 6.0 የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ትናንት አርብ የካቲት 7 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 11:28 ላይ መከሰቱን ቮልካኖ ዲስከቨሪ አስታውቋል።የመሬት መንቀጥቀጡ ማዕከል ከከተማዋ 6.5 ኪ.ሜ. ርቀት አካባቢ ላይ እንደነበር እንዲሁም ያደረሰው ጉዳት አለመኖሩን ሪፖርቱ አመላክቷል። የመሬት መንቀጥቀጡ ንዝረት በአካባቢው ባሉ ከተሞች መሰማቱ ተገልጿል።

በአፋር፣ በአማራ እና በኦሮሚያ ክልሎች በተደጋጋሚ እየተከሰተ ባለው የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቶች ምክንያት 90,000 ሰዎች ላይ ተጽዕኖ መፈጠሩንና ሁለት ሰዎችም መጎዳታቸውን የዓለም ጤና ድርጅት ገልጿል።ባለሥልጣናት በአፋር ክልል ከ55 ሺህ በላይ እንዲሁም በኦሮሚያ ክልል ከ20ሺህ በላይ በአጠቃላይ ከ75 ሺህ በላይ ሰዎችን ለአደጋ ተጋላጭ ከሆኑ አካባቢዎች አስወጥተዋል።

ከመስከረም ወር ጀምሮ የዩናይትድ ስቴትስ ጂኦሎጂካል ሰርቬይ 261 የሚሆኑ የመሬት መንቀጥቀጥ ክስተቶችን መዝግቧል። የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋዎቹ በዋናነት የኢትዮጵያ ስምጥ ሸለቆ አካል በሆነው ፋንታሌ አካባቢ ላይ ያተኮሩ ናቸው። ይህም በርካታ ቤቶች እንዲፈርሱ እና በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎች ከቀዬአቸው እንዲፈናቀሉ ምክንያት ሆኗል።

Via AS
@YeneTube @FikerAssefa


ዚምባብዌ ከሁለት አስርት አመታት በፊት በተካሄደው የተዘበራረቀ የመሬት ማሻሻያ መርሃ ግብር የንግድ እርሻዎቻቸው ለተወሰደባቸው ለውጭ አገር ባለቤቶች ካሳ መክፈል ጀምራለች።


በሰሜን ጎጃም ጎንጂ ቆለላ ወረዳ 13 መምህራን በታጣቂዎች ታግተው መወሰዳቸውን ቤተሰቦች ተናገሩ!

በሰሜን ጎጃም ዞን ጎንጂ ቆለላ ወረዳ የኮሬ አንደኛ ደረጃ ትምሕርት ቤት 13 መምህራን ፋኖ ታጣቂዎች ናቸው ባሏቸው ታጣቂዎች ታግተው መወሰዳቸውን ቤተሰቦቻቸው ገለጹ።

ለደኅንነታቸው በመስጋት ስማቸውን በይፋ እንዳንጠቅስ የጠየቁን የታጋች ቤተሰቦች ለአሜሪካ ድምፅ እንደተናገሩት፣ በአካባቢው ትምህርት ከተከፈተ አንድ ወር እንዳለፈው ገልጸው ባለፈው ዕረቡ የካቲት 5 ቀን 2017 ዓ.ም ወደ ትምህርት ቤቱ የሄዱ መምሕራንን ታጣቂዎቹ አግተው ወደ በርሃ ይዘዋቸው እንደሄዱ መስማታቸውን ተናግረዋል።

ታጣቂዎቹ ከዚህ በፊትም ወደ ትምህርት ቤት የሚሄዱ መምህራንን ሥራ እንዳይጀምሩ ማስጠንቀቃቸውን እና ሥራ ለመጀመር ተንቀሳቅሰዋል የተባሉ መምሕራንን በማገት እስከ 50 ሺሕ ብር አስከፍለው እንደሚለቁ ተናግረዋል።በአሁኑ ሰዓት ወረዳው በመንግሥት ቁጥጥር ስር መሆኑን የሚናገሩት የአካባቢው ነዋሪዎች፣ የአካባቢው ባለሥልጣናት “መምህራኑን ሥራ ጀምሩ ጥበቃ ይደረግላችኋል” ብለዋቸው እንደነበርም አክለዋል።

የኮሬ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርዕሰ መምህር አቶ ተረፈ አበጀ በስልክ አግኝተናቸው መምህራኑ መታገታቸውን አምነው ዝርዝር መረጃ ከመስጠት ግን ተቆጥበዋል።ለጎንጂ ቆለላ ወረዳ አስተዳዳሪ ለአቶ ጌታቸው ደገፋው ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም። በአካባቢው ይንቀሳቀሳሉ ከተባሉ የፋኖ ታጣቂዎች ምላሽ ለማግኘትም ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።

Via VoA
@YeneTube @FikerAssefa


በአቃቂ ቃሊቲ ቤቶችን በማኅበር የተቀበሉ ነዋሪዎች ከሕግ አግባብ ውጭ ታግደናል ሲሉ ቅሬታቸውን አቀረቡ!

በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ በሕጋዊ መንገድ በማኅበር ተደራጅተው የመሬት ባለንብረት መሆን የቻሉ ማኅበራት ከ4 ዓመታት ወዲህ በክፍለ ከተማውና በከተማ አስተዳደሩ 'የኦዲት ግኝት ችግር ያሉባቸው ማኅበራት አሉ' በማለት፤ ማንኛውንም አይነት እንቅስቃሴ ማድረግ እንዳይችሉ ያለአግባብ መታገዳቸውን ለአሐዱ ባቀረቡት ቅሬታ ገልጸዋል።

ቅሬታ አቅራቢዎቹ 1997 ዓ.ም ሕጋዊ አሠራሩን በጠበቀ መልኩ በመደራጀት የቤት ባለንብረት መሆን መቻላቸውን ጠቁመው፤ አንድ ማኅበር ውስጥ 12 አባወራ አባላት መኖራቸውን ተናግረዋል።ሁሉም አባላት 94 ካሬ መሬት ይዞታ እንዳላቸውና ሕጋዊ ሰነድ ያሟሉ መሆናቸውን የገለጹም ሲሆን፤ "ነገር ግን በወቅቱ የተለያዩ ግርግሮች በመፈጠራቸው ምክንያት ይህንን አጋጣሚ ተገን በማድረግ 'በሕገወጥ መንገድ ባለንብረት የሆኑ ግለሰቦች አሉ' ተብሎ እግዱ ተጥሎብናል" ብለዋል።

አክለውም ለጉዳያቸው መፍትሔ ፍለጋ ወደሚመለከታቸው ተቋማት ቢሄዱም፤ መፍትሔ ማግኘት እንዳልቻሉ ጠቁመዋል።በዚህም "ቤቶችን መሸጥ መለወጥ እንዳችል እንዲሁም ግብር እንዳንከፍል አሳማኝ ባልሆነ ምክንያት ታግደናል" ብለዋል።ለተጠቀሱት ችግሮች ባለፉት 4 ዓመታት እልባት እንዳልተሰጣቸው የገለጹት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ በዚህም ምክንያት ለአላስፈላጊ ወጪ እና ለእንግልት መዳረጋቸውን አብራርተዋል።

አሐዱ የቅሬታ አቅራቢዎችን አቤቱታ በማድመጥ ምላሽ ለማግኘት በጉዳዩ ዙሪያ የከተማ አስተዳዳሩን አነጋግሯል።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ኮምኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ እናትአለም መለሰ በሰሰጡት ምላሽ ከተማ አስተዳደሩ ከክፍለ ከተማ የሚመጡ ችግሮችን እልባት በመስጠት መልሶ ወደ ክፍለ ከተማ እንደሚልክ አንስተው፤ ጉዳዩን በዋናነት ክፍለ ከተማውን እንደሚመለከት ገልጸዋል፡፡

አሐዱም የአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ዓለማየሁ ሚጀናን አነጋግሯል። ሥራ አስኪያጁም በምላሻቸው ማህበራቱ እንደታገዱ አምነው፤ የኦዲት ችግር ያለባቸው በመኖራቸው የማጣራት ሥራው ብዙ ጊዜ እንደሚፈጅ ተናግረዋል።

አያይዘውም በሕገ-ወጥ መንገድ ሕጋዊነት ያላቸው የሚመስሉ የመሬት ይዞታ ማረጋገጫዎች የሚሰጡ ግለሰቦች በመኖራቸው ምክንያት የማጣራት ሥራው  አጽንኦት ተሰጥቶት እየተሰራበት መሆኑን አብራርተዋል፡፡አክለውም ከ900 በላይ ማህበራት በመኖራቸው ምክንያት የማጣራት ጊዜው መጓተቱን አስረድተው፤ "ምላሹን በቅርቡ ለመስጠት እየተሠራ ይገኛል" ሲሉ ገልጸዋል።

ቅሬታ አቅራቢዎች እንደገለጹት በተለያዩ ጊዜያት ወደ ከተማ አስተዳደሩ እና ክፍለ ከተማ በሚሄዱበት ወቅት የሚሰጣቸው ምላሽ በቅርብ ጊዜያት ውስጥ ለችግሩ እልባት እንደሚሰጥ ነው።ነገር ግን ላለፉት 4 ዓመታት ምላሻ እንዳላገኙ አሳስበዋል።የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በተለያዩ ጊዜያት ከመሬት ይዞታ ጋር በተያያዘ በተደጋጋሚ አቤቱታዎችን ሲያሰሙ ይደመጣል።

Via Ahadu
@YeneTube @FikerAssefa


በዲሞክራቲክ ኮንጎ ኢኳተር ግዛት ምንነቱ ባልታወቀ በሽታ ከ50 በላይ ሰዎች ህይወት አለፈ

በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ምዕራብ ኢኳተር ባንሳኩሱ ግዛት ውስጥ ምንነቱ ባልታወቀ በሽታ ከ50 በላይ ሰዎች ህይወታቸዉን አጥተዋል።

የወረርሽኙ ዋና ማዕከል ከሆነችው ከባሳንኩሱ በ25 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው ቦማቴ ወደ 2,000 የሚጠጉ ሰዎች መሰደዳቸውን ራዲዮ ኦካፒ የኢኳተር ግዛት ሴናተር ዣን ፖል ቦኬትሱ ቦፊሊ የሰጡትን ጋዜጣዊ መግለጫ ጠቅሶ ዘግቧል።

እንደ ቦፊሊ ገለጻ፣ ያልታወቀ በሽታ ምልክቶች የደም መፍሰስ፣ ትኩሳት፣ ራስ ምታት እና የመገጣጠሚያ ወይም የታችኛው ጀርባ ህመም ይገኙበታል።

በባሳንኩሱ ጤና ዞን በአንድ ሳምንት ውስጥ ከ 36 በላይ ሰዎች መሞታቸው የተሰማ ሲሆን ከየካቲት 3 እስከ 9 ባለው ጊዜ ውስጥ ከ 50 በላይ የሚሆኑ ሰዎች መሞታቸው ተሰምቷል፡፡

ህብረተሰቡ የጤና ርምጃዎቹን እንዲከታተል አሳስበዋል።ይህም “ከአካባቢው የአስተዳደር ባለስልጣናት እና ከጤና ስርዓቱ አቅም በላይ የሆነ ከባድ የጤና እና ሰብአዊ አደጋ ነው” በማለት ከአቅማቸው በላይ ሸክም እና የሰው ሃይል እጥረት እንዲገጥማቸው አድርጓል።


Via:- ዳጉ_ጆርናል
@Yenetube @Fikerassefa


🚀  አስደሳች  ዜና ለሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች በሙሉ
ከኢን አፋሪካ ኢንተርናሽናል ኮሌጅ

መገኛውን በፒያሳ ያደረገው ኢንአፍሪካ ኢንተርናሽናል ኮሌጅ ከ እህት ኩባንያው ኢንአፍሪካ ቱጌዘር ጋር በመተባበር የተማሪዎች ምዝገባ እና የገለፃ ፕሮግራም አዘጋጅቷል።🎉

📍ካሌብ ሆቴል
📅የካቲት 9 ከ  ⏰2:00እስከ 10:00

የሪሚዲያል ኮርሳችንን በመመዝገብ ውጭሀገር ሄደው ለመማር ሙሉ እገዛ ከኢንአፋሪካ ቱጌዘር ያግኙ ።
እንዲሁም የኢንግሊዘኛ ቋንቋ ስልጠና🇺🇸 ከአሜሪካ በመጡ መምህራን ያግኙ

📌በሌሎች ኮሌጆች ጋር የሪሚዲያል ኮርስ እየወሰዳችሁ ላላችሁ ተማሪዎች ትልቅ ቅናሽ ያዘጋጀን ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ ወደውጭ ሀገራት ወደሚገኙ ዮኒቨርሲቲዎች እንዴት አፕላይ ማድረግ እንደሚችሉ ስልጠና በነፃ ያገኛሉ።

🎁የተለያዮ አለም አቀፋ አጋሮች እና በሞያውየካበቱ መምህራኖች

ከ ሪሚዲያል በተጨማሪ

✅በ TVET
✅ዲግሪ እና ማስተርስ ፕሮግራም
✅ሲፒዲ ስልጠና

💰ጓደኞቾን በመጋበዝ የ 800 ብር ተሸላሚ ይሁኑ

✍አሁኑኑ ይመዝገቡ

https://forms.gle/R7oZQ9vxNMvaiogp9


Forward from: YeneTube
አቅመ ደካማወችን በነፃ ሀኪም ጥበቡ

እውነታውን ቻናሉን በመቀላቀል የብዙሀኖችን ድምፅ እንስማ

ታምራዊ ፈውስ እና ሰወች ከነበራቸው ህምም በሽታ ሲፈወሱ ሲመሰክሩ እንባቸው ሲታበስ  የምናይበትን ቻናል በመቀላቀል አይተን ተረድተን ለሌሎች ሸር እናድርግ  ኢትዮጵያውይነት ደግነት
    👇
https://vm.tiktok.com/ZMkQ1pTSL/
    ለበለጠ መረጃ
      ሀኪም ጥበቡ
0912718883
0917040506 በቴሌግራም በውስጥ መስመር የሚፈልጉትን ያስቀምጡ
👉አድራሻችን አዲስ አበባ አየር ጤና ካራቆሬ ወደመድኀኒአለም 200ሜትር ገባ ይበሉ
ቁጥር 2ባህርዳር ቀበሌ 11ዲያስፖራ በአሮየው 
አስፓልት መስጊዱ ፊት ለፊት ያገኙናል ይምጡ
ይፈወስ
https://vm.tiktok.com/ZMkQJh8WX/


🚀 Meet DUBAI University Admission Officers – Face to Face!

📅 Date: Saturday, February 15
Time: 3:00 – 7:00 Ethiopian time
📍 Location: Bole Medhalem Road, Selam City Mall, 3rd Floor, Office No. 308, Addis Ababa, Ethiopia

✅ FREE Face-to-Face Consultations with UEA University Admission Officers!

✅ Ask About:

🔹 Application Process 📄
🔹 Visa Guidance 🛂
🔹 Transfer Options to the UK, Europe, and the USA after studying for two years at DUBAI ✈️
✅ More Scholarships & Discount Coupons available for the event!


**ከዱባይ ዩኒቨርስቲ ተወካዮች ጋር በቀጥታ ጥያቄዎች ለመጠየቅ የካቲት 15 በዪኒቨርሳል የትምህርት አማካሪ በሚያዘጋጀው ኘሮግራም ላይ በነፃ ይሳተፉ፤ ይጠይቁ።

📱 Contact Numbers:
0908277979
0920244166
0930652527

📍 Event Location:
ሰላም ሞል, 3ኛ ፎቅ ቢሮ 308 እና 309

🆓 THE EVENT IS FREE!

🆓 Application is Free!


በትግራይ ክልል ጊዝያዊ ምክር ቤት ተቋቋመ

በትግራይን ክልል የዛሬ ሁለት ሳምንት ገደማ የተቋቋመውን ጊዝያዊ አማካሪ ካውንስል የሚተካ ጊዝያዊ ምክር ቤት ነው በዛሬው ዕለት የተቋቋመው።

የትግራይ ጊዝያዊ አስተዳደር አማካሪ ካውንስል የተቋቋመበትን ደምብ ቁጥር 10/2016 የተሻሻለም ሲሆን በዛሬው ዕለት በተደረገ ስብሰባም በ53 የድጋፍ ድምፅ፣ በአንድ ተቃውሞና ሁለት ድምፀ ተአቅቦ አማካሪ ካውንስሉ ፈርሶ ጊዝያዊ ምክርቤት በይፋ ተቋቁሟል።

የአማካሪ ካውንስል ምስራተው የክልሉ መደበኛ ምክር ቤት በፕሪቶርያው ስምምነት መሰረት መፍረሱ ተከትሎ የትግራይ ጊዝያዊ አስተዳደር ማቋቋምያ ሰነድ ጥር 2015 ዓ/ም ሲፀድቅ የተነሳ ሀሳብ መሆነለ ይታወሳል።

@Yenetube @Fikerassefa


ራፐር ካንዬ ዌስት ከሚስቱ ጋር ተፋታ

ራፐር ካንዬ ዌስት እና ከቀናቶች በፊት በግራሚ ሽልማት ላይ እርቃኗን በሚያሳይ ልብስ የታየችው ቢያንካ ሴንሶሪ መፋተታቸው ተሰምቷል።

ለመፍታታቸው ከተጠቀሰው ምክንያት አንዱ ራፐሩ ናዚን የሚደግፍ ፅሁፍ እና የወሲብ ፎቶ በማህበራዊ ሚዲያ በመልቀቁ ነው ተብሏል።


@Yenetube @Fikerassefa

10k 0 10 1 25

Australia work visa
አውስትራሊያ የሥራ ቪዛ
መሥፈርቶች
የታደሰ ፖስፖርት
እድሜ ከ 18_35
የትምህርት ደረጃ: Highschool እና ከዛ በላይ

የስራወቹ አይነት
የኮንስትራክሽን ሥራዎች
የግብርና ሥራዎች

ደሞዝ በሰአት ከ25-35 ዶላር
አኮሜዴሽን ያለው
የጤና ኢንሹራንስ ያለው
ከ 2 አመት በኋላ የመኖሪይ ፍቃድ ማግኘት የምትችሉበት እና ቤተሰባችሁን የምትወስዱብት እድልም ይፈጥራል

ፕሮሰስ ግዜ ከ 2-3 ወር ይፈጃል
የመሳካት እድሉ ከ 95%
   በተጨማሪ

እርሶ ወደ የትኛው ሀገር መሄድ አስበዋል፡፡
ካናዳ፡ አሜሪካ፡ አውስትራሊያ ፡አውሮፓ ወይስ ወደ በሌሎች አለም ሀገራት
ለሁሉም ከሳቢና መልስ አለ
የስራ ቪዛ
የቢዝነስ ቪዛ
የቤተሰብ ቪዛ
የትምህርት ቪዛ
የጉብኝት ቪዛ
የህክምና ቪዛ
የተለያዩ ሁነቶች ላይ ለመታደም የሚያገለግል ቪዛ የማማከር አገልግሎት
እንዲሁም የአየር ቲኬት
ሆቴል ቡኪንግ
የኢንባሲ ቀጠሮዎችን ማመቻቸት
ለተጓዦች ለጉዞ የሚረዱ ስልጠናዎችን እንሰጣለን፡፡
ለሚፈልጉት አገልግሎትና የጉዞ ጉዳዮች ሳቢናን ምርጫዎ ያድርጉ በአጭር ጊዜ ውስጥ ጉዳዮ መፍትሄ ያገኛል፡፡

   👇👇  ለበለጠ መረጃ 👇👇

Contact Us:

@Sabinavisa2

☎️👇

🤳ስልክ  ቁጥራችን 0927555551/2/3/4/7/8

Website

https://sabina.et/

👉 ወደ ቢሮአችን ይምጡ !
👉 ሃያ ሁለት ታውን ስኩዬር ህንፃ 6ኛ ቢሮ ቁጥር 602

እንዲሁም በ ሀዋሳ ቱሩፋት ወርቁ ቡቼ ታወር ፊት ለፊት አዲስ የ ገበያ ማዕከል ሁለተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 201

ከታላቅ አክብሮት ጋር   !!!

https://t.me/sabinaadvisor


ህገወጥ ኬላዎችን የማስነሳት ኃላፊነት የክልል መንግስታት ቢሆንም በአግባቡ ግን ተፈፃሚ መሆን አልቻለም ሲል የጉምሩክ ኮሚሽን አስታወቀ!

ኮሚሽኑ እንዳለው በኢትዮጵያ የንግድ ቁጥጥር ኬላን የማቋቋም እና የማስተዳደር ስልጣን የፌደራል መንግስት ቢሆንም በየአካባቢው ህገ-ወጥ ኬላዎች ተዘርግተው የንግድ እንቅስቃሴን እያወኩ መሆኑን አረጋግጧል።ይህን ተከትሎ በኢትዮጵያ ትላልቅ የንግድ መስመሮች የማላውቃቸው ከ280 በላይ ህገ-ወጥ ኬላዎች ተዘርግተው አግኝቻለው ብሏል።

የጉምሩክ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ደበሌ ቀበታ በየአካበቢው የተዘረጉ እነዚህን ኬላዎች ለማስነሳት የክልል መንግስታት ሀላፊነት የተሰጣቸው ቢሆንም በአግባቡ አልተፈፀመም ሲሉ የአሰራር ሂደቱን ተችተዋል።እነዚህን ኬላዎች ያቋቋሙት አካላት ተገቢ ባልሆነ መልኩ ገንዘብ እየሰበሰቡ መሆኑን የጠቀሱት ኮሚሽነሩ ነጋዴዎች በአንድ መስመር ብቻ ተደጋጋሚ ቀረጥ እንዲከፍሉ እየተገደዱ መሆኑንም ማስረዳታቸውን ካፒታል ከኢትዮጵያ ራዲዮ ያገኘው መረጃ ያመላክታል።

Via Capital
@YeneTube @FikerAssefa


የመውጫ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 540 ያህሉ ተማሪዎች ዳግም ለፈተና ላይቀመጡ ይችላሉ ተባለ።

አገር አቀፉን የመውጫ ፈተና የወሰዱ ተማሪዎች ውጤት መለቀቁን ትምህርት ሚኒስቴርና የኢትዮጵያ ተማሪዎች ኅብረት አስታውቀዋል።ከዚሁ ጋር ተያይዞ ከዲሲፒሊን ጋር በተገናኘ 540 ተማሪዎች ተለይተዋል ብለዋል። በዚህም የዚህኛውን ውጤት እስከ መሰረዝ፣ የሚቀጥለውንም ድጋሚ ያለመፈተን እና ጥፋታቸው ከባድ የሆኑትን ተማሪዎች ደግሞ ዳግም የሚይፈተኑበት ሁኔታ ሊኖር ይችላል ሲል ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።

@YeneTube @FikerAssefa


🚀  አስደሳች  ዜና ለሪሚዲያል ፕሮግራም ተማሪዎች በሙሉ
ከኢን አፋሪካ ኢንተርናሽናል ኮሌጅ

መገኛውን በፒያሳ ያደረገው ኢንአፍሪካ ኢንተርናሽናል ኮሌጅ ከ እህት ኩባንያው ኢንአፍሪካ ቱጌዘር ጋር በመተባበር የተማሪዎች ምዝገባ እና የገለፃ ፕሮግራም አዘጋጅቷል።🎉

📍ካሌብ ሆቴል
📅የካቲት 9 ከ  ⏰2:00እስከ 10:00

የሪሚዲያል ኮርሳችንን በመመዝገብ ውጭሀገር ሄደው ለመማር ሙሉ እገዛ ከኢንአፋሪካ ቱጌዘር ያግኙ ።
እንዲሁም የኢንግሊዘኛ ቋንቋ ስልጠና🇺🇸 ከአሜሪካ በመጡ መምህራን ያግኙ

📌በሌሎች ኮሌጆች ጋር የሪሚዲያል ኮርስ እየወሰዳችሁ ላላችሁ ተማሪዎች ትልቅ ቅናሽ ያዘጋጀን ሲሆን ከዚህም በተጨማሪ ወደውጭ ሀገራት ወደሚገኙ ዮኒቨርሲቲዎች እንዴት አፕላይ ማድረግ እንደሚችሉ ስልጠና በነፃ ያገኛሉ።

🎁የተለያዮ አለም አቀፋ አጋሮች እና በሞያውየካበቱ መምህራኖች

ከ ሪሚዲያል በተጨማሪ

✅በ TVET
✅ዲግሪ እና ማስተርስ ፕሮግራም
✅ሲፒዲ ስልጠና

💰ጓደኞቾን በመጋበዝ የ 800 ብር ተሸላሚ ይሁኑ

✍አሁኑኑ ይመዝገቡ

https://forms.gle/R7oZQ9vxNMvaiogp9


አቅመ ደካማወችን በነፃ ሀኪም ጥበቡ

እውነታውን ቻናሉን በመቀላቀል የብዙሀኖችን ድምፅ እንስማ

ታምራዊ ፈውስ እና ሰወች ከነበራቸው ህምም በሽታ ሲፈወሱ ሲመሰክሩ እንባቸው ሲታበስ  የምናይበትን ቻናል በመቀላቀል አይተን ተረድተን ለሌሎች ሸር እናድርግ  ኢትዮጵያውይነት ደግነት
    👇
https://vm.tiktok.com/ZMkQ1pTSL/
    ለበለጠ መረጃ
      ሀኪም ጥበቡ
0912718883
0917040506 በቴሌግራም በውስጥ መስመር የሚፈልጉትን ያስቀምጡ
👉አድራሻችን አዲስ አበባ አየር ጤና ካራቆሬ ወደመድኀኒአለም 200ሜትር ገባ ይበሉ
ቁጥር 2ባህርዳር ቀበሌ 11ዲያስፖራ በአሮየው 
አስፓልት መስጊዱ ፊት ለፊት ያገኙናል ይምጡ
ይፈወስ
https://vm.tiktok.com/ZMkQJh8WX/


#ቴምር ሪልስቴት
⚠️7ሳይቶችን ስርተን አስረክበናል አሁን ላይ ደግሞ ለሽያጭ ያወጣናቸው ቤቶቾ እና ሱቆች
‼️ፒያሳ (ሊሴ ገ/ማርያም ትምህርት ቤት) ጀርባ
         👉1 መኝታ 66ካሬ=
         10% ቅድመ ክፍያ 693,000ብር
         ሙሉ ክፍያ 6,930,000 ብር
         👉2መኝታ 71ካሬ
        10%ቅድመ ክፍያ 745,000ብር
        ሙሉ ክፍያ 7,455,000ብር
         👉2መኝታ 93ካሬ=
       10% ቅድመ ክፍያ 1,044,000ብር
       ሙሉ ክፍያ 10,044,000ብር
        👉3መኝታ 130ካሬ
      10%ቅድመ ክፍያ 1,365,000ብር
      ሙሉ ክፍያ 13,650,000ብር
        👉ቀሪውን 90% በ17ዙር ከፍለው         የሚጨርሱት
        👉30% እና ከዛ በላይ ለሚከፍል ከከፈሉት ላይ 25% ደረስ የሚደርስ ቅናሽ አዘጋጅተናል
‼️ፒያሳ ሱቅ ሽያጭ 
👉3.9ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ900,000ብር 4ተኛ እና 5ተኛ
👉4.2ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.2ሚሊዮን 3ተኛ
👉4.8ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 1.5ሚሊዮን 2ተኛ
👉5.5ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2ሚሊዮን 1ኛ
👉 7ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 2.8ሚሊዮን ግራውንድ በውስጥ በኩል
👉10ሚሊዮን 20ካሬ ቅድመ ክፍያ 4ሚሊዮን ግራውንድ በውጪ
ለበለጠ መረጃ ይደውሉ
       👇👇👇👇👇👇
     +251939770177
     +251996856273


የቫላንታይን ቀን ምክንያት በማድረግ ፍቅረኛዎን ሰፕራይዝ ያድርጉ።

የተዘጋጁ ፓኬጆች አሉን ያናግሩን።
እንዲሁም እራሶ ያዘጋጁት ካለ እኛ እናደርስሎት።

ከውጪ ሀገርም ሆነው ማዘዝ ይችላሉ።

ከአሁን ሰዓት ጀምሮ Per- Order ማድረግ ትችላላችሁ።

Ordering Line 0926389973

በቴሌግራም ለማዘዝ ኦርደር ለማድረግ በዚህ ያናግሩን @Fikerassefa


ነዳጅ ማደያዎች 24 ሰዓት አገልግሎት እንዲሰጡ ሊደረግ መሆኑ ተገለጸ!

በአዲስ አበባ ከተማ ከ130 በላይ ነዳጅ ማደያዎች ቢኖሩም 24 ሰዓት አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ 35 ብቻ መሆናቸው የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ አስታውቋል፡፡ከ130 በላይ ነዳጅ ማደያዎች ያሉ ሲሆን አብዛኞቹ ምሽት ላይ አገልግሎት እንደማይሰጡ እና በቀጣይ የአገልግሎት አሰጣጣቸው ላይ ማሻሻያ እንደሚደረግ የተናገሩት የከተማዋ ንግድ ቢሮ የገበያ መረጃ ጥናት እና ማስታወቂያ ዳይሬክተር አቶ ሙሰማ ጀማል ናቸው።

"በተሰራው የክትትል ሥራ ላይ የነዳጅ ማደያዎች የአገልግሎት አሰጣጥ ላይ ክፍተት መኖሩን እና አብዛኞቹ 24 ሰዓት አገልግሎት የማይሰጡ መሆናቸውን ተመልክተናል" ነው ዳይሬክተሩ ያሉት፡፡በከተማዋ አገልግሎት የሚሰጡ ነዳጅ ማደያዎች 24 ሰዓት አገልግሎት እዲሰጡ ሊደረግ መሆኑን አንስተው፤ "በአስገዳጅነት የአገልግሎት የሰዓት ለውጥ ከመደረጉ አስቀድሞ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራ ይሰራል" ብለዋል፡፡

ሕገ-ወጥ የነዳጅ ግብይት መፍታት የሚያስችል አዋጅ ለሕዝብ ተወካዎች ቀርቦ መጽደቁንም ተናግረዋል፡፡በመሆኑም በቀጣይ በሕገ-ወጥ ድርጊት ላይ የተገኙ ነዳጅ ማደያዎች ላይ፤ ከ700 ሺሕ ብር ጀምሮ እስከ 5 ዓመት የሚደርስ የእስር ቅጣት እንደሚጣልባቸው አስታውቀዋል፡፡አክለውም ነዳጅ ማደያዎች በቢሮ ፍቃድ እና እውቅና ከተሰጣቸው ውጪ ነዳጅ መሸጥ እንደሌለባቸው አሳስበዋል፡፡

Via Ahadu
@YeneTube @FikerAssefa

20 last posts shown.