እንማር


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: Quotes


እዚህ Channel ላይ ያስተምራሉ ያዝናናሉ ብለን የምናስባቸውን
🎯 መፅሀፎች
🎯ተከታታይ ልቦለድ
🎯ግጥም
🎯ፍልስፍና
🎯ምክር
የተለያዩ PDF መፅሐፍት እንደፍላጎቶ አሉ
    Ads - @Kiya988
https://youtube.com/channel/UCr7-LDddhyqtFUCH0OHhM2Q
Buy ads: https://telega.io/c/Enmare1988

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
Quotes
Statistics
Posts filter


👣👌ገራሚ የፍልስፍና ቻናል ልጋብዛችሁ ፍልስፍናን ከኛ ጋር ⚱


ልጅ እናቱን ጠየቃት
ልጅ:- "እማዬ ለምን ታለቅሻለሽ?"
እናት:- "ሴት ስለሆንኩ ነው ልጄ።"
ልጅ:- "አልገባኝም እማዬ?"
እናቱ አቀፈችውና :-"በፍፁም አትረዳውም" አለችው።
ከዚያም ልጁ አባቱን ጠየቀ:- "እናቴ ለምን ያለምክንያት ታለቅሳለች?"
አባቱ እንዲህ ሲል መለሰ:- "ልጄ ሁሉም ሴቶች ያለምክንያት ያለቅሳሉ።"

ልጁ ጥያቄው ሳይመለስለት ....

ካደገ በኋላ ያ እናቱ ምታለቅስለት የነበረውን ነገር ለማወቅ አንድ ጠቢብ ጋ ሄዶ ጠየቀ።
"ሴቶች ለምን ያለቅሳሉ?"

ጠቢቡም መለሰለት።
❤ፈጣሪ ሴትን ሲፈጥራት ምድር ላይ ያለውን ሸክም እንድትሸከም ትከሻዋን ጠንካራ አድርጎ ነው የፈጠራት።

❤መዳፎቿንም ለስላሳ እና እረፍት የሚሰጡ አድርጎ ፈጠራት።

❤9ወር ተሸክማ አምጣ ለመውለድም ውስጣዊ ጥንካሬን ሰጣት።

❤ልጆቿ አድገው ሲያስቸግሯትም የማይጨክን አንጀት ሰጣት።

❤የቤተሰቧን ሸክም እንድትሸከም, እንድትንከባከብ, አስቸጋሪ ልጆቿንም እንደየአመላቸው ልትችል, አድገውም ቢሆን ቢያስከፏት ላትጨክንባቸው ሰፊ ልብ ሰጣት።

❤ለልጆቿም የማያልቅና የማይተመን ፍቅር እንዲኖራት አድርጎ ፈጠራት።

❤በመጨረሻ ...
እፎይ ማለት በፈለገች ሰአት እንባ የማፍሰስ አቅሙን ፈጣሪ ሰጣት።

👉ይህ የእሷ ደካማ ጎኗ ነው ያለምክንያት ቢሆንም እንኳን የሴቶችን እንባ ማክበር አለብህ።

👉አንተን ስትወልድህ እትብትህ ከእሷ ጋር ሲቆረጥ የቀረ አካል መኖሩን አትዘንጋ።
በማለት መለሰለት።

ክብር ለሴቶች ክብር ለእናቶች❤❤❤!!


የሆነ ቀን ይመጣል: አንድ የማይቀር ቀን አለ

👇🏾

የሆነ ቀን የእናትህ የስልክ ጥሪ ናፍቆት ብቻ ይሆናል
.
"ምን አለበት ብዙ ጊዜ አብሬያት አሳልፌ በነበረ!" የምትልበት ቀን ይመጣል
.
ቀልዷ ቀርቶ ቁጣዋ የሚናፍቅህ ቀን ይመጣል
.
ትኩስ ቡናዋን እና እንጀራ በሚጥሚጣዋ ከብርንዶ እና ጠጅ በልጦ የሚናፍቅህ ቀን ይመጣል
.
ድምጿ ሁሉ ከአእምሮህ ትውስታ ጠፍቶ ይናፍቅሃል

👇🏾

በል ለእናትህ ደውልላት አሁን: ከቻልክ ሄደህ ዘይራት
.
በህይወት ከሌለች ደግሞ እረፍት ተመኝላት እና በርታ !!

መልካም ቀን !!

❤️🙌🏼

5.3k 0 35 12 249

ናታሊያ - "የእናትነት እና የሃዘን ጥግ" ይሏታል

👇🏾

ለሰባት ወራት ያህል የሞተ ልጇን ይዛ የኖረችው ቺምፓዚ የእናትነት: የሃዘኔታ እና የርህራሄ ምልክት ናት ይሏታል

ቫሌንሲያ ውስጥ ባዮፓርክ የተባለ የእንስሳት መጠበቂያ ውስጥ ናታሊያ የታቀፈችው ልጅ ሞተባት: ሆኖም ግን መልቀቅ አልፈለገችም

የፓርኩ ባለስልጣናት ልጇን ከመቀማት ይልቅ ሃዘኗን እንድትወጣ ፈቀዱላት: የሞተው ልጇን አቅፋ ሰባት ወራትን ቆየች

በስተመጨረሻ የልጇ ስጋ ከአጥንቱ ተላቅቆ ቆዳ እና አፅም የሆነባት ናታሊያ ልጇን ለመጣል ተገደደች: ለሰባት ወራት የቆየው የሃዘን ሂደቷም አለም እንዲህ መዘገበው

🙌🏼❤️

6.9k 0 30 8 249

አባቴ ሁሉ ነገርን መጋፈጥ ይሰብራል ይላል ።

...ጀግና ሁኔታን የሚረዳ ነውም ይላል ።

እኔ የምጋፈጠው ለማሸነፍ ጀግናም ለመሆን አይደለም ሲደርሱብኝ ነበር።

አፈግፍጌ አውቃለሁ።

ያፈገፈኩኝ ግዜ የሚሰማኝ ስሜት መጥፎ ነው።

አባቴ "የማያፈገፍግ ታጋይ በቶሎ ይሞታል" እያለ የውትድርና ገጠመኙን ያጣቅስልኛል።

በሕይወቱ ምድር ላይ እንደኔ የሚጨነቅበት ጉዳይ ያለ አይመስለኝም...

"እሱ ማስረዳት አይችልም... በዛ ላይ ያፈጣል ....ችግር የሚፈታው አንገት ለአንገት በመተናነቅ ይመስለዋል" ይላል ስለ እኔ ሲናገር...

"አንዱ ይገለዋል አጉል ቦታ ይመቱታል የሰው ሰው እጁ ላይ ይጠፋል" ሲል ይሰጋል።

"እኔ በሕይወት የኖርኩት እጅ ሰጥቼ ነው...ይሄው ከዛ በኃላ ያገኘሁት መዓረግ እና ደስታ ይቆጠራል ...?? "

አባቴ ትኩረቱ ስለሆንኩ መሰለኝ...
ልጁ ስለሆንኩ መሰለኝ ...
ስላሳደገኝ መሰለኝ ...
ስለሚያስብልኝ መሰለኝ ...

ከኔ በተሻለ እኔን ያውቀኛል።

ስለእኔ ገምቶ የተሳሳተበት ግዜ አላስታውስም...

"በጠበል አልወጣ ያለ ጂኒ አለበት..." ይላል።

የሆነ ቀን ተሳካልኝ ልጄ ልብ ገዛልኝ ስለቴ ሰመረልኝ ብሎ በመሃበርተኛው ፊት ተናዞ ስለቱን እንዳስገባ የመሃበርተኛው ልጅ አዲሱ ነገረኝ...

ስለት ካስገባበት ቀን ጀምሮ ሳሰላስል ልብ ገዛ እንዳለው አይነት ሰው ሆኛለሁ ።

ደርሰውብኝ ያለፍኳቸው ቀምተውኝ የተውኳቸው ትተውኝ ያለቀስኩበት ሥፍራ ብዙ ነው ።

ምን ብሎ ተስሎ ይሆን ስለቱ የሰመረው...??

ምን አለ አሁን ትልቅ ሕልም እና ሕልሙን መተግበርያ ጥንካሬ ስጠው ብሎ ቢሳልልኝ...

(በአድኃኖም ምትኩ)
(ወግ ብቻ)

7.6k 0 38 4 148

#5


"በመጨረሻም ያመንኩት ሁሉ ውሸት መሆኑን ደረስኩበት"......አልኳቸው...


ከዶርም ልጆች ጋር  "ረጅም ጊዜ እምነታችንን ያገኙ ግን ደሞ ውሸት የነበሩ ነገሮች" በሚል ርዕስ ዙሪያ ያጋጠመንን በየተራ ለመናገር ተስማምተን ንግግሩ ከኔ ተጀምሮ ነው.....



ከሴት ጋር አንድ አልጋ ውስጥ አጊንቼው እህቴ ናት ቢለኝ አምነው ነበር....ቤቲ ደውላ፣ ኮኪ ጠርታኝ፣ ማሂ ፈልጋኝ እያለ የሴት ስም በዝርዝር ሲጠራልኝ በአንዲቷም እንደማይቀይረኝ በሰአቱ ፍቅሩ  አረጋግጦልኛል.....


የhighschool የመጀመሪያ አመት ተማሪ እያለን ነበር ፍቅሩን መግለፅ የጀመረው....ከረጅም የእንቢታ ጊዜ በኋላ በሀሳቡ ተስማማሁ።

የሌላ ፆታ ፍቅርን ሀ ብዬ የተማርኩት በሱ ነው....ወንድሜ፣ ጓደኛዬ፣ ሚስጥረኛዬ እና ወደፊቴን አቃጄ ሆነ....24 ሰአት ልቡ እኔ ጋ ነበር....ታጋሽ፣ ትሁት፣ እኔን ደሞ እንደትልቅ ሰው አክባሪ ለኔ ከሱ በላይ አልነበረም።  እኔም ፀሎቴ ውስጥ ሳይቀር ቅድሚያ ተሰላፊ አደረኩት


የህይወታችን ወሳኙ እድሜ  ፣ አዲስ ነገር ሁሉ ሚፈጠርበት እድሜ ላይ ተገናኘንና አብሮነታችን ላይ ጥገኛ ሆንን....

ለፍቅር ያለኝ ትርጉም በዚ ግንኙነት ተመሰረተ....ማንም ፍቅረኛውን ወዶና መርጦ ካገባ በኋላ ሊከዳት ወይም ልትከዳው አትችልም, መጀመሪያም ያላፈቀረው ጋር ካልተጣመረ በቀር.....

ኮካዬን ጎንጨት ብዬ ወሬዬኔ ቀጠልኩ...

የሆነ ቀን እንደለመድነው ፍቅርሽን ለምን አትገልጪም በሚል ተጣልተን ሁለት ወይም ሶስት ቀን ተኮራረፍን( እውነቱን ነው ፍቅርን በቃል መግለፅ ላይ ጎበዝ አደለሁም😁...ተደጋጋሚ የመጣያ ርዕሳችን ነበር)።

ከዛም በሶስተኛው ቀን  እንደለመድነው ብዙ አመት ተለያይቶ እንደቆየ ሰው ስናወራ ዋልን። በዙሪያ ያሉት ጎደኞቼ ሁሉ በኛ የ24 ሰአት ወሬ እንደተማረሩ ነው...ከልጅነት እስከ እውቀት ምታወሩት አያልቅባችሁም? የሁሉም ጥያቄ ነበር


መጨረሻ ላይም ያስጨነቀው ጉዳይ እንዳለና ልነግርሽ ፈልጋለሁ አለኝ...ህመሙና ጭንቀቱን ሳልሰማው ቢያልፍ ደስታዬ....ብዙጊዜ የሱን ችግር ሰምቼ እኔ እየታመምኩ ለሱም ፈተና ሁኜበታለሁ.....  ምነው አልኩት

እንደቀላል ነገር በተደጋጋሚ ስሟን ይጠራው የነበረችው ልጅ ከሱ አረገዝኩ እንዳለችና እንዴት ልጁን እንደሚያሳድግ እንዳማክረው ጠየቀኝ.....ግራ ገባኝ...ለሱ የሴትነት ልኩ እኔ ነበረኩ....እህቱም፣ እናቱም፣ ፍቅረኛውም.....ምንም አላልኩም "እኔስ" ብቻ ነበር ያወጣሁት ቃል....
እሱም,  በፈለገው ጊዜ በአካል ስለማያገኘኝ እና ፍቅሬን ስለማልገፅ
በፍቅር ቃል ልቡን እንዳሸፈተችና ሁሌም አጠገቡ እንደነበረች ነገረኝ( እኔ የት ሂጄ ማለት ፈልጌ ስላልቻልኩ ዝም አልኩ).....እንደሰው በክብር ተጣልተን ቢሆን ለዚ የበቃነው ደስ ባለኝ ....የሱ እርጋታ ደሞ እኔን እብድ ሊያደርገኝ ደረሰ....

እንደምንም እራሴን አረጋግቼ "መቼ ነው  ኢኼ የሆነው" አልኩት... የሆነ የተለመደው ፀባችን ምሽት ላይ ከቆንጆ ወይን ጋር አጠገቡ ያገኛት እሷን ስለሆነ የኔ ክፍተት እንደሆነ በድጋሜ ነገረኝ....ሶስት ቀን ራሴን ታመምኩ

የቱ ጋር ፍዝዝ ብዬ እንደሆነ አላቅም አንቺ ጋ ነኝ እያለ እሷ ጋር የተገኘው.....

ኢኸው በመጨረሻም እስከዛሬ ያመንኩት ሁሉ ውሸት መሆኑን ደረስኩበት.....በርግጥ የትኛው እምነቴ እንደተሳሳተ አላረጋገጥኩም..... "የእውነት አፍቃሪ ሊክድ አይችልም" ያልኩት ወይስ "እሱን እራሴን ከማምነው በላይ ማመኔ"....

ቶሎ ለመፅናናቴ ትልቁን ቦታ የወሰደው ግን ኢኼ ፅሁፍ ነው "ታምኖ የተገኘ ብቻ ሳይሆን አምኖ የተገኘንም ፈጣሪ ይክሳል" ....ብዬ ታሪኬን ጨረስኩ

ሁሉም አሳዘንኳቸው መሰለኝ ዝም ብለው ቀሩ

✍ሚሚ


https://t.me/justhoughtsss


✅''ማድረግ ያለብህ ሁሉ''እያደረክ በቀኑ መጨረሻ ላይ ባዶነትና የመንፈስ ጭንቀት እየተሰማህ ከሆነ ፣ምን አልባት ሌላ ሰው ለራሱ ደስታ የጻፈውን እየሰራህ እንጂ ማድረግ የምትፈልገውን እያደረክ አይደለም ማለት ነው። ''

✍️ ''Brianna wiest ′′📖

✈️@Enmare1988
✈️@Enmare1988


የኢትዮጵያውያን አንድነት ዳግም የታየበት የካራማራ ድል !

የካቲት 26 ቀን 1970 ዓ/ም የሱማሊያን ዚያድባሬ ጦር ለመመከት በካራማራ ጀግኖች የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች የህይወት መሰዋዕትነት ከፍለው ወራሪውን ጦር ከሀገር ያባረሩበት እና የሀገራቸውን ሰንደቅ ያውለበለቡበት ቀን ነው።

በሶቪየት ህብረት ከፍተኛ የሆነ ድጋፍ የመጣው የዚአድባሪ ጦር የእናት ሀገር ጥሪ እያለ በተሰበሰበው የኢትዮጵያ ጦረኛ " ካራማራ " ላይ ድባቅ ተመትቶ ወደ መጣበት ተመልሷል።

በጦርነቱ መጀመሪያ ሶቪየት ህብረት ሶማሊያን ስትደግፍ ነበር በኃላ ላይ ወደ ኢትዮጵያ አዘንብላ ለኢትዮጵያ ከፍተኛ እገዛ አድርጋለች ፤ ከኢትዮጵያ ጋር ጥሩ ግንኙነት የነበራት አሜሪካ ደግሞ ወደ ሶማሊያ ፊቷን አዙራ ነበር።

በጦርነቱ ኩባ፣ ሰሜን ኮሪያ፣ የመን እና ምሥራቅ ጀርመንን ጨምሮ ሌሎች አገራት አጋርነታቸውን ለኢትዮጵያ አሳይተዋል።

ከ16,000 በላይ የኩባ ወታደሮች በውጊያው እንደተሳተፉ መዛግብት ያሳያሉ። ደቡብ የመንም ጦሯን
#ለኢትዮጵያ አሰልፋ ነበር።

በተለያየ የፖለቲካ የትግል ሁኔታ፣ በተለያየ ቅራኔ ውስጥ የነበሩ የኢትዮጵያ ሀይሎች ሁሉ ስለ ሀገር አንድ ሆነው የዚያድባሬን ጦር የመከቱበት የካራማራ ጦርነት የኢትዮጵያ አንድነት ዳግም በጉልህ የታየበት ስለመሆኑ ይነገርለታል፡፡

በየአመቱ የካቲት 26 ቀን የሚታሰበው የ " ካራማራ ድል " ዘንድሮም ለ47ኛ ጊዜ እየታሰበ ይገኛል
፡፡


#4

"በመጨረሻም ያመንኩት ሁሉ ዉሸት መሆኑን ደረስኩበት "
አለች ከተቀመጠችበት አግዳሚ ወንበር ላይ ፈንጠር ብላ በመነሳት ። አይኖች ሁሉ ወደሷ ሆኑ ። አበደች እንዴ በሚል አይነት አየናት ። ሰንበት ነው አጥቢያችን በሚገኘው ደብር የእለቱን የቤተ-ክርስቲያን ስርአት ካከናወንን ቡሃላ የንስሀ አባታችንን ለማግኘት ልጆቻቸው ሰብሰብ ብለን እየጠበቅናቸው በዚ መሀል ነበር ግቢ ውስጥ ማትጠፋው ፀይም ቆንጅዬ ልጅ ጮክ ብላ ማውራት የጀመረችው (በዝምተኝነቷ ስለምናቃት ደነገጥን)
    "አልደከማችሁም ? ሁሉንም ነገር እርግፍ አድርጎ
     መተው አላማራችሁም ? አለች ሁላችንንም እያየች
ምን እንደሆነች ስለማናቅ ሁላችንም ግራ ተጋባን !
     "እግዜሩም ደሀ ላይ ይበረታል በችግር ላይ ችግር          
      መደራረብ ያውቅበታል " አለች ወደ ሰማይ አንጋጣ
       በትዝበት እያየች
ንሰሀ አባታችን "ደህና አረፈዳችሁ ?" ብለው ወደ አዳራሹ ሲገቡ አንጋጣ ስታነባ አዩዋት
        "ወለተ ጊዮርጊስ ምነው ልጄ ምን ነካሽ ?"
         "አባ ተዉኝ ዛሬ እንኳን ይውጣልኝ "አለች
ወደኛ ዞር ብላ "እብድ መሰልኳቹ አደል ?(በጥልቅ ሀዘን ማውራት ጀመረች) በውሸት አለም ምኖር ሰው አደለም ፈጣሪ የረሳኝ በሁሉ የተገፋው ነኝ ታዲያ ማበድ ይነሰኝ ? "
         "የሆንሽውን ንገሪን እስኪ ልጄ" አሉ በእድሜ ገፋ ያሉ እናት ። በስስት ና በጉጉት ሄዳ እግራቸው ስር ቁጭ አለች ። "እውነት እማማ ይሰሙኛል ?" አለቻቸው እያነባች ። አሳዘነችኝ ለካ ጆሮም ይናፍቃል....ሴትዮዋ አንገታቸውን ነቀነቁላት ። አደለም እሳችው እኛ ሁላችንም  ለመስማት ጆሮዋችን አሹለን እየጠበቅናት ነው ።
            "እየውሎትማ እማማ...አንድ ጨካኝ ወንድም ነበረኝ በጣም ቁማርተኛ ነበር ቤት ውስጥ ምንም ነገር እስከማይቀር ድረስ እየሸጠ ተጫውቶበታል ። ከሁሉም የከፋው ግን የቤታችን ነበር....የሆነ ጥቁር ጠዋት ሱፍ የለበሱ ሰዎች ብጣሽ ወረቀት ይዘው መተው ቤቱን በቁማር እዳ እንደወሰዱት አረዱን ። እናቴ ላቧን ልጅነቷን ደሟን የጨረሰችበት ቤት ያንቺ አደለም ስትባል ልቧ ቀጥ ብሎ በዛው አሸለበች...ታሳዝናለች አይደል ?! በቃ ከዛ የኔን ነገር ተዉት ህይወቴ ግራ ገባው እዛ ና እዚ መባዘን ተግባሬ ሆነ....ከብዙ መባዘኖቼ መሀል አንድ ሰው ተዋወኩ ችግሬን ነገርኩት አለውልሽ አለኝ ትከሻውን ሰጠኝ ሳላመነታ ተደገፍኩት (የንዴት የበቀል እና የእልህ ፈገግታ ፊቷ ላይ በግልፅ ይታያል) ጥሩ ኑሮ መኖር ጀመርኩ " ብላ ጸጥ አለች ፋታ የመውሰድ አይነት ዝምታ ። ሁላችንም በጉጉት እጠበቅናት ነው ። (እኔ በበኩሌ ስንቱን አሰብኩት)

እንባዋን ጠራርጋ ተረኳን ቀጠለች "ከጊዜያት በኋላ ጸነስኩ ደስታ ምሆነውን አሳጣኝ አለም የኔ መሰለችኝ ፈጣሪዬን በብዙ አመሰገንኩ ። ስወልድ ግን ደስታዬ ተሻረ። የሞተ ነው የወለድሽው ብለው ሬሳ አስታቀፉኝ" (እንባዋ እንደጅረት ይወርዳል) ንግሯሯ በጣም ስለሰቀጠጠኝ አይኖቼን በህመም ጨፈንኳቸው እናትነት ሚገባቸው ሴቶች ፊታቸውን በነጠላ ሸፍነው ያነባሉ ።

"ይሄ ይገርሞታል እማማ....ይባስ ብሎ ባሌ ሸጠኝ ።!"
"ሸጠኝ ?!" አሉ እማማ በድንጋጤ
"አዎ ሸጠኝ " አለች ቃላቱን ረገጥ አርጋ
"ለማን ? "
"ለሴተኛ አዳሪነት " አለች ስብር ብላ
እማማ በስመአብ ብለው አማተቡ !

"ለካ ያገባውት ሰው ወንጀለኛ ቁማርተኛ ከህገ ወጥ ስራ ውስጥ ማይጠፋ ሰይጣን ነበር ። ለብዙ ጊዜ ገላዬን እየቸበቸቡ ተጫወቱብኝ እሱም ልጃችን ሲሞት ብቻዬን ጥላኝ ምንም ሳይጎልባት ሽርሙጥና ገባች እያለ ስሜን አጠፋው።"
"ኧረ በዲማው" አሉ እማማ እኛም ብንሆን ምንሰማው ነገር ክብድ ብሎናል ።

" ደሞ እኮ ልጄ ሞቶ አደለም እሱንም ሽጦት ነው። (ፊቷ ትንሽም ቢሆን ተስፋ ተነበበት) ለነፍሴ ያለች ነርስ ናት አሳዘንሽኝ ብላ የነገረችኝ ። አሳየኝ እያልኩ ብዙ ለምንኩት አስለመንኩት ጭራስ አበደች ለየላት የሞተ ልጅ ከየት ላምጣ የኔንስ ሀዘን ለምን ተቀሰቅሳለች እያለ ራሱን እንደ ፃድቅ አስቆጠረ ። እሱ ምስኪን የተገፋ አባት እኔ ግን ( ሳግ ተናነቃት) እኔ ግን እብድ ሱሰኛ ሴተኛ አዳሪ ብዙ ብዙ ተባልኩ። በጣም ስታምም ገላዬ እንደ ድሮ ተፈላጊነት ሲያጣ አውጥተው ጎዳና ጣሉኝ አባ ናቸው ከምንም አንስተው ለዚ እንኳን ያበቁኝ።" ብላ ተነፈሰች

ሁላችንም ወደ አባ ዞርን አቀርቅረው እንባቸውን ያፈሳሉ።

"በቃ እኔ ማለት እቺ ነኝ አለኝ ምለው ወንድሜ የተደገፍኩት ባሌ የፈጠረኝ አምላኬ ተባብረው ያረገፉኝ ማያቁኝ የገፉኝ ያምንኩት ሁሉ የኖርኩት ሁሉ ውሸት የሆነብኝ ሰሚ እንኳን የሌለኝ ብቸኛ " ብላ ተንሰቀሰቀሰች ። አብረናት አነባን....

ስንቶቻችን ነን የኑሮዋችንን ዉሸት ማመን ሳንፈልግ እዛው በሀሰት ምንቦራጨቅ ብናምንም መውጫው የጠፋን....ለካ አንዳንዴ ኑሮ ሀሰት መሆኑን አምኖ መቀበል እረፍት አለው....

ከቤተ መቅደስ የተከፈተው "ከንቱ ነኝ ከንቱ ከንቱ ነኝ ዋስትና መከታ እግዚአብሔር ካልሆነኝ " ሚለው መዝሙር እንባችንን አገዘው ።

                                   ✍️ ወርቅ_አለማው

https://t.me/justhoughtsss


"...አንድ ሰው የሚያጋጥመው ትልቁ ህመም ረሃብ፣ድህነት አልፎ ተርፎም ሞት ሳይሆን ፍቅሩን በማይቀበል አለም ውስጥ ማፍቀርን ነው -ልብን ሙሉ በሙሉ መስጠት እና በምላሹ ባዶነትን እና ዝምታን ብቻ መቀበል ታላቁ ህመም ነው።

በውስጣችን የሚያስፈራ ተቃርኖን ተሸክመናል፡ ፍቅርን እንፈልጋለን ግን እንፈራዋለን። መቀራረብን እንናፍቃለን ግን መልሰን እንሸሻለን; እነዛን ሰዎች እንወዳቸዋለን ግን እንጠራጠራቸዋለን። ከሄዱት ጋር እንድንጣበቅ የሚያደርገን እና ከጎናችን ያሉትን ችላ እንድንል የሚያደርገን ይህ ምን አይነት እርባና ቢስነት ነው?

እኔ የሚገርመኝ፡ ፍቅር የጥንካሬያችን ፈተና ነው ወይስ የድክመታችን መገለጫ? እና ከምንም ነገር ለማምለጥ የምንገባበት ብቸኝነች የፍቅር ተፈጥሯዊ ውጤት ብቻ ነውን?

"The Brothers Karamazov" ከተሰኘው ልብወለድ የተወሰደ


አንድ ቪዲዮ እያየሁኝ ነበር

👇🏾

አንድ ማየት የተሳነው ወጣት የእግር ኳስ ስቴዲየም ከጏደኛው ጋር ገብቶ ጏደኛው ጨዋታውን እየተከታተለ ይተርክለታል

………………

አንድ የረጅም ጊዜ Best Friend አለኝ: like a Brother to me

እንደ አጋጣሚ ሆኖ አንድ የስራ አጋሩ የመስማት ችግር ያጋጥመዋል

ምን ቢያደርግ አሪፍ ነው?

👇🏾

የምልክት ቋንቋ ትምህርት መማር ጀመረ: ወዳጁን ለመርዳት እና ግንኙነታቸውን ለማስቀጠል ሲል ከስራ ሰአቱ ቀንሶ የምልክት ቋንቋ መማር👏🏼

ፈጣሪ ረድቶት ወዳጁንም ፈጣሪ ማረለት እንጂ🙏

❤️🙌🏼

7.4k 0 10 4 221

የኮርማ ፍልሚያው ሜዳ በደጋፊዎች ጩኸት እየተናጠ ነው

ተወዳዳሪው ደግሞ የምንም ጊዜው ድንቅ የኮርማ ተፋላሚው ማታዶር አልቫሮ ሙኔራ ነው

👇🏾

ኮርማው በቁጣ እየተንደረደረ ተፋላሚውን ገንድሶ ሊጥለው አረፋ እያደፈቀ ሲደነፋ ህዝቡ ማታዶር አልቫሮ ምን ሊያደርግ ይሆን ብለው በጉጉት ይጠብቃሉ

ማታዶር አልቫሮ ግን መፋለሙን አቁሙ ከስታዲየሙ ግድግዳ ጥግ ሄዶ ቁጭ አለ

ሊወጋው የመጣው ኮርማ አጠገቡ ሲደርስ አዋራውን አቡንኖ ቆመ: ስቴድየሙ ፀጥ ረጭ አለ

ማታዶር አልቫሮ ሁኔታውን እንዲህ ሲል ይገልፀዋል

👇🏾

“በዚያች ቅፅበት የኮርማው ቀንድ ላይ ያለውን ገዳይ ሃይል ረሳሁት: አይኖቹን ሳያቸው ከቁጣ ይልቅ ንፁህነቱን ተመለከትኩኝ:: ሊያጠቃኝ አልነበረም የመጣው: የህዝቡ ጩኸት እና የተገራበት መንገድ ለጠብ በመሆኑ ብቻ ነበር ሲደነፋ የነበረው: ኮርማውን ጨካኝ እንዲሆን ያደረግነው ተፋላሚዎቹ እና ህዝብ ነው" አልኩኝ

ማታዶር አልቫዶር ወዲያው ለፍልሚያ የሚጠቀምበትን ሻሞላ ጥሎ ለመጨረሻ ጊዜ የኮርማ ፍልሚያ ሜዳን ተሰናበተ

አለም ያጨበጨበለት እና ዝነኛው የኮርማ ተፋላሚ ቀንዱን አሹሎ እየደነፋ የመጣውን ኮርማ በጥቂት ርህራሄ እና ቁጭ በማለት አበረደው

ህይወቱም ተቀየረ!!

👇🏾

ምናልባትም ሃይለኛ እና ቁጡ የምንላቸው ሰዎች የሚፈልጉት ርህራሄ እና ቁጭ ማለትን ቢሆንስ እላለሁኝ

ሃይለኛ እና ቁጡ የሆኑ ሰዎች አይናቸውን ብናይ ርህራሄ እና ህመም የሞላባቸው ሊሆኑ ይችላሉ: ማየት ብቻ በቂ ነው

❤️🙌🏼

6.9k 0 38 2 158

አንዳድ ጊዜ ብቻችሁን ሁኑ!

በመጀመሪያ ለብቻ በመሆንና በብቸኝነት መካከል ልዩነቱን እንወቅ፡፡

ለብቻ መሆን ማለት አንድ ተግባርና ልምምድ ነው፡፡ በራስ ፈቃድና ሆን ተብሎ ከሰዎች ገለል ያለ ቦታና ጊዜ መርጦ ከራስ ጋር ማሳለፍ ማለት ነው፡፡ ለብቻ ለመሆን የግድ በአካልም ሆነ በማሕበራዊ ሚዲያ ከሰዎች ለየት ማለትን ይጠይቃል፡፡

ብቸኛ መሆን ማለት ተግባር ሳይሆን ስሜት ነው፡፡ ይህ ስሜት የሚመጣው በእኛ ፈቃድ ሳይሆን በውስጣችን ካለው የምልከታና የስነ-ልቦና ቀውስ ነው፡፡ ብቸኝነት ስሜት እንዲሰማን የግድ ከሰው በመለየት ብቻችንን መሆን የለብንም፡፡ በሰዎች መካከል እየኖርን እንኳን ይህ ስሜት ሊያጠቃን ይችላል፡፡

• ከእለት እለት ከሰዎች ጋር የምታሳልፉ ከሆነና አንድም ቀን ለብቻችሁ የምታሳልፉበት ጊዜ ከሌላችሁ . . .

• ሁል ጊዜ ከሰው ጋር ካልሆናችሁ የሚጨንቃችሁ ከሆነ . . .

• በአካል ከሰዎች ጋር ካልሆናችሁ የግድ ሶሻል ሚዲያ ላይ የምታሳልፉ ከሆነ . . .

• ብቻችሁን ስትሆኑ የብቸኝነት ስሜት የሚያጠቃችሁ ከሆነ፡፡

ከላይ የተጠቀሱትና መሰል ስሜቶች እንዳለባችሁ የምታስቡ ከሆነ ብቻችሁን የመሆን ልምምድ እንደሌላችሁና የለብቸኝነት ስሜት ተጋላጭ እንደሆናችሁ አሳባቂ ሁኔታ ነው፡፡

ለብቻችሁ ከራሳችሁ ጋር ጊዜን ማሳለፍ ለብዙ ነገር ይጠቅማችኋል፡፡

• ከሰዎች አመለካከት አጉል ተጽእኖ ነጻ በሆነ መልኩ ውስጠ-ህሊናችሁን እንድታደምጡ፣

• ተረጋግቶ ስለወደፊት ለማቀድ፣

• ከሰዎች ጋር ያላችሁን ግንኙነት ለማመዛዘን፣

• ምቾት የማይሰጡ ስሜቶች የፈጠሩባችሁን ሁኔታዎች ለይቶ በማወቅ ለማስተካከል

እና ለመሳሰሉት ስኬታማ ልምምዶች ይጠቅማችኋል፡፡

ለመጨረሻ ጊዜ ለብቻችሁ ያሳለፋችሁት መቼ ነው?

በየስንት ጊዜው ለብቻችሁ የመሆን ልምምድ አላችሁ?

ይህንን ልምምድ ዛሬውኑ ለመጀመር ብትወስኑ ምን ይመስላችኋል
?

Dreyob

7.1k 0 45 9 113

የሞተ ፈረስ ጽንሰ ሃሳብ ይሉታል: The Dead Horse Theory

👇🏾

ይህ እሳቤ ሰዎች: ድርጅቶች: መንግስታት አንድን ችግር እንዴት እንደሚመለከቱ እና ችግሩን ተረድተው ከመፍታት ይልቅ ችግሩን መቀባባት ላይ ማተኮርን ይተነትናል

የእሳቤው ዋና ሃሳብ - የምትነዳው ፈረስ ከሞተ ማድረግ ያለብህ ከፈረሱ ወርደህ መሄድ ነው

ሆኖም ግን ሰዎች ይህንን ከማድረግ ይልቅ

👇🏾

የፈረሱን ኮርቻ ይቀይራሉ
.
ለፈረሱ የተሻለ ምግብ ያቀርባሉ
.
የፈረሱን ጋላቢ ይቀይራሉ
.
የፈረሱን ተንከባካቡ በአዲስ ይተካሉ
.
ኮሚቴ አቋቁመው ስለ ሞተው ፈረስ ችግር ያወራሉ: ይጽፋል: ድምዳሜው ግን አንድ ነው- ፈረሱ ሞቷል
.
በስተመጨረሻም "ሞቷል" የሚለውን ቃል ራሳቸውን በሚያጽናና ቃል ተክተውት ያርፋሉ

👇🏾

ፈረስህ ከሞተ ሞተ ነው

በማይሆን መፍትሄ የሞተን ፈረስ ህይወት ለመስጠት ከመውተርተር ይልቅ መሞቱን አምነህ የሚያስጉዝህን መፍትሄ መምረጥ

🙌🏼❤️

7.7k 0 36 1 127



✨New Platform! New Opportunities! ✨

🥇 Let's celebrate our members' successful withdrawals!

🔥Join Valero Energy today - your success starts here! 🔥

✅ Making money online is easy!

✅ The best platform in Ethiopia

Why choose Valero Energy?

✔️ Trusted by 300,000+ Ethiopians
✔️ Fortune 500 company, safe new energy investment
✔️ Guaranteed withdrawals for all users
Invitation download line commission: 37%
Registration link: https://www.valerosn.com/?invitation_code=58DC2
Official Telegram link https://t.me/Valero1


ፌቨን ትባላለች ፤ ፍቅረኛዋን ትወደዋለች ። ሁሌ በትንሹም በትልቁም ታነሳዋለች ፤ ከእለታት በአንዱ እለት  ምኑን በደንብ ትወጂለታለሽ ???አልኳት

እ.............የምወድለት

ለኔ ያለውን ግዙፍ ፍቅር ፤ በየስፍራው በየጊዜው ይዳስሰኛል ። ሲፈልገኝ ፤ሲቀና፤ ሲጠረጥረኝ ፤ ለኔ ያለውን የፍቅር አሻራ በነካሁት እና ባየሁት ቁጥር እወድዋለሁ።

የለም

በደንብ የምወደው መልካምነቱን ነው ። በዙርያዎቹ  ያሉቱን ሰዎች ፤ሲቆረቆርላቸው ፤ሲጠቅማቸው፤ሲሞገትላቸው ።ለተጠቃ ድምፅ ሲሆን እንድወደው  አድርጎኛል ።

ኖ ......እሱም አይመስለኝም

ሲወስበኝ ያለውን ጀብደኝነቱ ነው የምወደው ። ወሲብ ላይ ያለው ወኔ ድፍረት እና ብልግናውን ነው የምወድለት ።

እሱም ብቻ አይደለም !?

ለአምላኩ ያለውን ታማኝነት፤ሃቀኝነቱን ለሚያምንበት ነገር የሚሄደውን ርቀት፤ ብቻውን የመቆም አቅሙን ፤ ሁሉም ታዝቦት ላገኘው ሰው ሁሉ ትክክል ነኝ እያለ ሙሾ አለማውረዱን ነው የምውድለት !!

ኖ ሳቁን ነው

ደመቅ ብሎ ለዛ ያለው ሳቁን ነው የምወድለት ። ያቺ ልቤን የምታርደው ሳቁን ነው የምወድለት ። ያቺ ከልቡ ሲስቀው ብቻ የሚስቃትን ሳቁን ነው የምወድለት ።

ኖ .....የለም

ሲያወራ የሚያወናጭፈው አለንጋ ጣቱ ናቸው የሚስቡኝ ። አወራሩ ጀንተል ብሎ በስሜት ቃል አጣጣሉ ነው የሚማርከኝ

እ..... ይሄ ን ብቻ ግን አይለም የምወድለት

ያለውን Commitment ። ከብዙ ሰው ጋር ሆ አለማለቱን ነው !! ከመዘባረቁ በፊት ስለሁኔታው ለመረዳት አጠያየቁን ፤ አነባበቡን ነው የምወድለት
.
.
ግን ምክንያቴ  ነው ብዬ ከዘበዘብኩት በላይ አስሬ የማጣቅሰው ምክንያት ። የመንሰፍሰፌ ምንጭ ምክንያት አንድ ይመስለኛል .........የኔ ስለሆነ( ።)


የኔ ስለሆነ ነው የሚተችበትን ሳይቀር የማቆለባብሰው

ከካደኝ ፤ከተወኝ፤ ከጠላኝ፤ ሀይማኖተኝነቱን አክራሪ እለዋለው፤ ጠያቂነቱን መንቻካ እላለሁ፤  መልካምነቱን ብኩን ማለቴ አይቀርም ።

😐ማስታወሻ
    ከውበት በላይ ፍቅር ያሱባል !!!

7.3k 0 42 1 130

የቢራቢሮዎቹ ትምህርት!

ቢራቢሮዎች በዝናባማ እና በጭጋጋማ ወቅት በፍጹም አይበሩም፣ ይባላል፡፡

የዝናቡ ጠብታ ክንፋቸውን ስለሚጎዳውና ለወደፊቱ ያላቸውን የመብረር ብቃት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ስለሚያበላሸው ምንም ያህ ጊዜ ቢፈጅባቸውም ከባዱን የዝናብ ጊዜ ተጠልለው ያሳልፉታል፡፡

የወቅቱ ከባድ ጊዜ እስከሚያልፍ ድረስ ዝም ማለታችሁን፣ ሰወር ማለታችሁንና መታገሳችሁን አትጥሉት፡፡ ከባዱ ጊዜ ያልፍና እንደገና መብረራችሁ አይቀርም፡፡

ዶክተር እዮብ ማሞ

✈️@Enmare1988
✈️@Enmare1988

7.5k 0 48 5 171

💥💥ዲቦራ💥💥

  ባልኮኒውን እየወለወልኩ አያታለሁ። ፈገግታ ሳይለያት ነው የምትውለው። አንድ ለመጠጣት የመጣውን ሁለት ሶስት ስታስደግም አይቻለሁ። አለቃችን ከሁሉም ሰራተኛ በላይ ለእሷ ስሜት ይጠነቀቃል። ዋነኛ የቤቱ የገቢ ምንጭ መሆኗ የአደባባይ ሚስጥር ነው።

   ገና ከተቀጠረች በሳምንቱ አለቃችን ሰዓት እንድታከብር ሲቆጣት "የምሰራው አምኜበት እስከሆነ ድረስ ያንተ አስታዋሽነት አያስፈልገኝም ህሊና አለኝ እኮ! ግን ገና ሳትቀጥረኝ ነግሬህ ነበረ እኔ አስተናጋጅ የመሆን እቅድ አልነበረኝም፥ ቀን ጥሎኝ ነው አሁንም ትምህርት ስለምማር ነው እንጂ ያለምክንያት ስራ የምበድል ሰነፍ አይደለሁም" ብላ ሽርጧን ወርውራ ስትወጣ

   አለቃችን ራሱ ደንግጦ "እባክህ ንጉስ አንተ አነጋግራት እስኪ" ብሎ ላከኝ። ስሄድ ልብስ መቀየሪያ ውስጥ ተቀምጣ ስታለቅስ አየኋት ቀያይ ጉንጮቿ በርበሬ መስለዋል ልቤን እፍን አደረገኝ ከፊቷ ሄጄ በርከክ አልኩና ፊቷን ቀና አድርጌ "አሁን በሶል ንግግር ተናደሽ ማልቀስሸን ባወራ ማን ያምነኛል?!" አልኳት ፈገግ አለች

   "ፀብ አልችልም ለዛ ነው እንጂ እሱም የተናገረው ትክክል ነው ስራዬ አይደል?!" ፊቷን ለመጥረግ የለበሰችው ሸሚዝ አጥሮ አልደርስ አላት። "ይኸው ሶፍት በቃ ይበቃሻል" ብዬ ሰጠኋት "ሳለቅስ ደበርኩህ እንዴ?!" አለቺኝ ፈገግ ብላ አሁንም አይኗ እንደደፈረሰ ነው። "እንደውም ደስ ነው ያለኝ ሶል እንደዛ የሚናገረው ሰው ያስፈልገው ነበረ በይ አሁን ነይ እንውጣ" ብያት ወጣን

    ተያይዘን ከክፍሉ ስንወጣ ሶል በር ላይ ቆሞ ነበረ "ውጡ ውጡ መሽቷል እንደውም" አለ የባጥ የቆጡን እያወራን ቤቷ አድርሻት ተመለስኩ። ከዛ ምሽት በኋላ ጓደኝነታችን በይፋ ታወጀ። ረጅም ሰዓት ከስራ በኋላ እናወራለን ቤቷ ወይ ክላሷ አድርሻት እመለሳለሁ።

    ፈጣሪ ራሴን በሴት መልክ ቢሰራኝ እሷን የምሆን ይመስለኛል። በፊት የምጫወተውን ጨዋታ ራሴ ላይ ትጫወትብኛለች። የምሳሳለትን ፈገግታዋን ለማንም ጠጪ ታባክነዋለች። ውስጤ ሲጨስ ሌላ ሰው የሚሰማው እስኪመስለኝ እናደዳለሁ "ተረጋጋ ምን እየሆንክ ነው" ብለውም ራሴን ምንም ማድረግ ያቅተኛል።

     ሆን ብላ እንደምትጫወት የገባኝ ፈገግ ብላ ስትስለመለም ወንዱ ሲፍረከረክ ሰረቅ አድርጋ ስታየኝ ነው። ራሴን ስራዬ ላይ የጠመድኩ ልመስል ስሞክር ሁለት ግዜ በሀይል ጨብጬ ብርጭቆ ሰብሬያለሁ። ይሄኔ ያንን የተረገመ ፈገግታዋን ብልጭ አድርጋልኝ ታልፋለች።

     የተወለወለ ባልኮኒዬን እየወለወልኩ ትመጣና ተንጠራርታ ፀጉሬን እየነካካች "ፀጉርህን እንዳትቆረጠው እንደዚህ ሲሆን ነው የምወደው" ብላኝ ትሄዳለች። ልቤ የሚሞቀውን ሙቀት ላስቆመው ይከብደኛል።

      ለሁሉም ፈገግ ስትል እንዲህ እያልኩ ራሴን አፅናናለሁ "ለሁሉም ፈገግ ብትል ለሁሉም በነፃነት ከእኔ ጋር የምታወራውን ታወራለች?! ለሁሉም ፈገግ ብትል ከእኔ ውጪ ማን እንዲሸኛት ፈቅዳለች?! ፈገግታዋን ቢያዩ የህይወት ፍልስፍናዋን ያውቃሉ?! ሶል ዝጉ ብሎ ሲሄድ ወይን ይዘን ቀን ባስተናገድንበት ማታ ራሳችንን እያስተናገድን ስለቤተሰቧ ስታወራ አይተዋት ያውቃሉ?! አያውቁም" እያልኩ ንዴቴን አበርደዋለሁ ኧረ እንደውም አጉል የልብ ልብ ይሰማኛል

    ቀኑን እንደዚህ ስታበግነኝ ስትውል ማታውን እኔን ብለው የሚመጡ ሴቶች ባልኮኒው ጋር ይደረደራሉ። በየተራ ይመጣሉ። ትኩረቴን አንዷ ላይ ካቆየሁት አትችልም ትመጣለች። "የኔ ንጉስ" ትለኛለች "ወዬ ልዕልቴ" ብላት ደስስ ባለኝ ኮስተር ብዬ "ምን ልቅዳ?!" እላታለሁ ያኔ ቁጣ ቁጣ ይላታል የጀመርኩትን ወሬ በደንብ ትረብሸዋለች።ፊት አልሰጣትም ትኩረቴ እነሱ ላይ ይሆናል። እንደማትችል አውቃለሁ ፊቷ ሲቀላ አያለሁ ደስስ ይለኛል የቀኑ ፈገግታዋ ይጠፋል። ቀስ በቀስ ሴቶቹ ይሄዳሉ።

እንደዚህ ያለንግግር ስንናቆር ውለን ስራችንን ጨርሰን ስንወጣ ምንም እንዳልተፈጠረ የባጥ የቆጡን እየቀባጠርን እሸኛታለሁ። አንዳንድ ቀን አስተቃቀፏ ይለያል። ደረቴ ላይ ተጣብቃ ትቆያለች። ፀጉሯን እያሻሸሁ "የኔ ቀበጥ ደግሞ ምን ፈለግሽ?!" እላታለሁ "ምንም የኔ ንጉስ ደህና እደር" ብላኝ ጉንጬን ሳም አድርጋኝ ሳትዞር ትሄዳለች። በእያንዳንዷ እርምጃዋ ልቤ ይከብዳል ምን እየሆንኩ ነው?! እያልኩ ወደቤቴ አዘግማለሁ

አንዷ በቅርብ ትዳሯን የፈታች ሴት በብዛት መምጣት አበዛች። ደግሞ ብቻዋን የምትመጣው እንደተመቸኋት ግልፅ ነው ለማውራት የምትከብድ አይደለችም። አንድ ቀን እንደተለመደው ስራዬን እያሳለጥኩ ሳወራት አምሽቼ እሷም ሄዳ ዘጋግቼ ልወጣ ስል ዲቦራን አጣኋት የታለች ስላቸው ተረባብሻ ነው የወጣችው አሉኝ ብደውል አላነሳ አለች። ነብሴ ተጨንቃ አደርኩ። "ምን እየሆነች ነው?! ቢያንስ የሆነ ነገር ብላኝ አትሄድም?!" እያልኩ ስብሰለሰል አደርኩ

ጠዋት ስገባ አልገባችም አርፍዳ መጣች ፊቷ ልክ አይደለም አይኔን ትሸሻለች ላወራት ስሞክር አለባብሳ ታልፈዋለች። ልንወጣ ስንል ቀድሜ ወጥቼ ጠበኳት "ብቻዬን መሄድ እችል ነበር" አለች እና ራመድ ራመድ ማለት ጀመረች "እሺ ምንም አናወራም አብሬሽ እንድሄድ ፍቀጂልኝ" አልኳት ሳትመልስልኝ መራመድ ቀጠለች

   ቤቷ በር ላይ ስንደርስ "ደህና እደር" አለቺኝ ራቅ ብላ እንደቆመች "እንዳቅፍሽ አትፈቅጂልኝም?!" አልኳት ውስጤ ተሰብሮ አየቺኝ ያጣመርኩትን እጄን ዘረጋሁላት እቅፌ ውስጥ ገባች "ንገሪኝ በምንድነው ያስቀየምኩሽ" አልኳት ፀጉሯን እየደባበስኩ

"ሴትዮህ በጣም ቆንጆ ናት ፈት አትመስልም" አለቺኝ

   ቀና አድርጌያት "ፈት መልክ አለው እንዴ?!"  "እኔንጃ" ብላ ድጋሜ ፊቷን በደረቴ ደበቀችው "የኔ ልዕልት ቀናሽ እንዴ?!" አልኳት "ትንሽ" አለች ቀና ሳትል "እንድትቀኚ ብዬ እኮ ነው ሳወራት የነበረው" አልኳት

ወገቤ ዙርያ ያለውን እጇን አጥብቃ "ይሄ ጨዋታ እያደከመኝ ነው ከዚህ በላይ የምችል አይመስለኝም" አለች ፊቷን ቀና አድርጌ እያየኋት "እኔንም አቅም ካሳጣሺኝ ቆይቷል" አልኳት እጇን ከወገቤ ላይ አንስታ አንገቴ ዙርያ አደረገችውና ተንጠራርታ

"ምኖቹ ሞኞች ነን?! ምን እየጠበቅን ነው ታድያ?!" አለቺኝ በሹክሹክታ "አንቺን እየጠበኩሽ ነበር" አልኳን እኔም በጆሮዋ አንሾካሹኬ

"መጠባበቁ የሚበቃ አይመስልህም" ብላ ሸሚዜን ከደረቴ ላይ ይዛ ተንጠራርታ ሳመቺኝ። 

ሰማችሁ ያልኩትን?! ሳመቺች!!!


✍ናኒ

https://t.me/justhoughtsss

7.8k 0 49 10 196

Forward from: Thoughts

20 last posts shown.