ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና ጽሑፎች Tsegaye kiflu


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


በዚህ ቻናል ላይ አበው ያስረከቡንን መጻሕፍትን እንዲሁም መንፈሳዊያት ጽሁፎችን ለምዕመናን ተደራሽ ማድረግ ነው።
https://linktw.in/mejQ6H
ሰብስክራይብ ያድርጉ

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter




ት/ቤቶቻችን እና መስተጋብራቸው
***
በቤተ ክርስቲያን የአብነት ት/ቤት ወጥ የሆነ ዘመናትን የተሻገረ ርቱዕ ትምህርት ይሰጣል፤ የቤተ ክርስቲያን መምህራን ይወጡበታል። እነዚህ መምህራን የቤተ ክርስቲያንን ዶግማ፣ ቀኖና እና አዋልድ መጻሕፍትን ሁሉ በዚህ የአብነት መሠረታቸው ይመለከታሉ፤ ያብራራሉ።
ቤተ ክርስቲያን ዘመናዊ ቅርጽ ያላቸው የሥነ መለኮት ት/ቤቶችም አሏት። እነዚህ ት/ቤቶች ሰፋ ያሉ የጥንት ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ፣ ታሪክ፣ የአበው ድርሳናት (ወደ ግእዝ ተተርጉመው የማናገኛቸውን ወይም ቀድሞ ኖረው በኋላ የጠፉትን ጨምሮ)፣ ንጽጽራዊ ሥነ መለኮት እና ነገረ-መለኮትን ለመረዳት የሚጠቅሙ ልዩ ልዩ ጥንታውያን ቋንቋዎች ይሰጡባቸዋል። ምርምር እንደሚያስፈልጋቸው በሚታመንባቸው ጉዳዮች ላይ ጥናቶችም ይሠሩባቸዋል።
ቤተ ክርስቲያን አብነቱን እንደያዘች ሥነ መለኮት ት/ቤቶች እንደሚያስፈልጓት አምና ሁለቱንም ይዛለች። ይህ የሌሎች ኦርቶዶክሳውያን አብያተ ክርስቲያናት እውነታም ነው።
ለወደፊቱ በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ላይ ተግዳሮት ከሚፈጥሩ ነገሮች አንዱ የሁለቱ ት/ቤቶች መስተጋብር ነው። መፈራረጅ እና መቆሳሰል ብዙ ጉዳት አድርሶ የግለሰቦች መጣያ እና መጠላለፊያ ከመሆኑ በፊት በትልቁ ምሥል ላይ በቂ ውይይት ማድረግ ያስፈልጋል። በጉዳዮች ላይ በቂ ውይይት ሳይደረግ ሲቀር ጉዳይ ግለሰባዊ መነቃቀፊያ ወደ መሆን ይወርዳልና።
ጤናማው የአካሄድ መሥመር የቱ ነው? በአብነቱ የማናገኛቸውን ነገር ግን በዘመኑ ለሚነሡ ጥያቄዎች አስፈላጊ የሆኑ የአበው ድርሳናት እና የታሪክ ምንጮች እንዴት እንጠቀም? ተቃርኖ የሚመስሉ ነገሮች ሲገጥሙ እንዴት እንፍታ? የሌሎች ኦርቶዶክስ አብያተ ክርስቲያናት ሊቃውንት መጻሕፍት ስናነብ የሚያስፈልገው ጥንቃቄ ምንድር ነው? የሚሉት እና መሰል ጉዳዮች ሳይረፍድ እና ችግሮች ሳይገነግኑ ለውይይት መቅረብ ይኖርባቸዋል።
የእኔን አጭር እይታ ላስቀምጥ። በሥነ መለኮት ት/ቤቶች የሚማሩ ሰዎች የአብነቱን ትምህርት ትልቅ ዋጋ ሰጥተው ማጥናት ይገባቸዋል፤ የአብነቱን ት/ት ዜማውን ለመማር ቢከብድ እንኳ ይዘቱን (መልእክቱን) አክብሮ ማወቅ እና መረዳት ግዴታ ይመስለኛል። በአብነት ት/ቤት ያሉ ሊቃውንት ደግሞ የሥነ መለኮት ት/ቤት ውስጥ የሚገኙ ተጨማሪ እውቀቶች እና ምንጮች ቢያገኙ የአብነቱን የበለጠ በጥልቀት ለመረዳት እና ለማብራራት ይረዳቸዋል። ነገሮችን ከታሪካዊ ዳራቸው ለመረዳት እና ታሪካዊ ዓውዳቸውን ለመረዳት የሥነ መለኮት ምንጮች ጠቃሚ ናቸው። በመሆኑም ሳይጠራጠሩት በበጎ ኅሊና ሊያዩት፣ እድሉ ከተገኘም ሊማሩት ይገባል። በተለይ ደግሞ የአብነት መሠረት ያላቸው ሊቃውንት የሥነ መለኮት ት/ቤቶች ውስጥ መኖራቸው ሁለቱንም በአግባቡ የመያዝ ሕያው ምስክሮች ስለሚሆኑ በእጅጉ ጠቃሚ ይሆናል። በዚህ መንገድ ለቤተ ክርስቲያን የሠመረ አገልግሎት ትልቅ መመጋገብ ሊኖራቸው ይችላል።

✍️ዲያቆን በረከት አዝመራው


በአርመን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በሊባኖስ የፓኖሲያን ጳጳስ ብፁዕ አቡነ አናንያ ኩጃኒያን ሊባኖስ ውስጥ በተፈጸመ ጥቃት ተገደሉ !ጥር 24 ቀን 2017 ዓ.ም

ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አራም ቀዳማዊ በጳጳሱ ግድያ የተሰማቸውን ሀዘን ገልጸዋል። የሊባኖስ ሪፐሊክ ፕሬዝዳንት ጄኔራል ጆሴፍ አውን በሊባኖስ የአርመን ኦርቶዶክስ ጳጳስ የማኅበረሰብ ጉዳዮችን በመምራት ላይ ሳሉ በተፈፀመው ግድያ የተሰማውን ጥልቅ ሀዘን ገልፀዋል።

ፕሬዝደንቱ ወንጀሉን አጥብቀው እንደሚያወግዙ የገለጹ ሲሆን የፀጥታ አካላት የወንጀል ሁኔታን ለማወቅ ፣ወንጀለኞችን ለመያዝ እና ለሚመለከተው የፍትህ አካል እንዲተላለፉ ለማድረግ ምርመራቸውን እየተከታተሉ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

የደኅንነት ምንጮች እንደገለፁት ጳጳሱ ትናንት ከሰዓት በኋላ መጥፋታቸው ተነግሯል። በምርመራው ወቅት የጸጥታ አካላት አስከሬናቸውን በቤታቸው ውስጥ በማግኘታቸው መገደላቸውን አረጋግጠዋል።

©ተ.ሚ.ማ


file name.PDF
51.2Mb
አልወላእ ወልበራእ




❤️በቤተ ክርስቲያን 5 አይነት አክሊላት አሉ❤️
1 አክሊለ ሰማዕት
ይህ አክሊል ሰማእታት በተጋድሎ የሚያገኙት አክሊል ነው ቅዱስ
ጳውሎስም ስለዚህ አክሊል ሲናገር ሃይማኖቴን ጠብቄለው ሩጫዬን ጨርሻለው ወደፊት የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል ብሎ ጠቅሶታል
2 ጢሞ 4+6-7
በተመሳሳይ ባለራዕዩ ቅዱስ ዮሐንስም እስከሞት ድረስ የታመንክ ሁን የሕይወት አክሊል እሰጥሃለው ብሎ የተናገረው ስለ ሰማእታት አክሊል ነው ራዕ 2+10 ክርስቶስም አክላሎሙ ለሰማእት ተብሏል እመቤታችንም አክሊለ ሰማእት ትባላለች
2 አክሊለ ሶክ (አስኬማ መላእክት)
ይሄ አክሊል የአባ እንጦንዮስ አክሊል ሲሆን መነኮሳት የሚያደርኩት አክሊል ነው ይሄ አክሊል በምንኩስና ዓለምን ከናቁ በኋላ የሚገኝ ነው ክርስቶስ በዕለተ አርብ የተቀበለው አክሊለ ሶክ የሚታሰብበት ሲሆኔ ይሄን አክሊል ያደረጉ መነኮሳት እንደ መላእክት በንጽሕና በቅድስና ስለሚኖሩ አስኬማ መላእክት ተብሏል
3 ተክሊል (የተክሊል አክሊል)
ይህ አክሊል በድንግልና ኑረው ለሚጋቡ ኦርቶዶክሳውያን የሚደረግ የድንግልና ምልክት የሆነ አክሊለ ከብካብ ነው ደናግል ላልሆኑ ፈጽሞ የማይደረግ ነው
4 አክሊለ ነገሥት ይህ አክሊል ለነገሥታት ብቻ የሚደረግ ነው ሰሎሞን ሲነግሥ ሲቀባ የተደረገለት አክሊል ነው አባ ሕርያቆስ በቅዳሴው ወአክሊሉ ለሰሎሞን የሰሎሞን አክሊል ነሽ ብሎ የተናገረው የነገሥታት አክሊል እመቤታችን እንደሆነችና ነገሥታት ሲነግሢ ተቀብተው አክሊል እንደሚያደርጉ ለመግለጽ ነው
5 አክሊለ ካህናት
ይህ አክሊል በክህነት የሚያገለግሉ ካህናትና ዲያቆናት የሚያደርርጉት አክሊል ነው
ክህነት ለሌለው ፈጽሞ የማይደረግ ሲሆን የካህናት አክሊል አሰራሩ ከላይ 4 ማዕዘን ሲሆን የዲያቆናት አክሊለም በአሰራር ከካህናት የተለየ ክብ ነው ዲያቆን የቄሱን አክሊል ፈጽሞ ማድረግ አይችልም አምስቱ አክሊላት እነዚህ ናቸው
አሁን አሁን ግን የካህኑን እና የዲያቆኑን አክሊል ሴቶች ሳይቀር አድርገውት እየታየ ስለሆነ እጅግ የሚያሳዝን ነው
ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን እየተጣሰ ቸል ተብሎ እየታየ ነው ስለዚህ የሊቃውንት ጉባኤ ይሄን ጉዳይ እልባት ሊሰጥበት ይገባል።

መጋቤ ሐዲስ ሄኖክ ፈንቴ




የ"ዝክረ ኒቅያ ዓለም አቀፍ ጉባኤ" ከሚያዚያ 20-24 ቀን 2017 ዓ.ም እንደሚካሔድ ሊቃውንት ጉባኤ አስታወቀ።
+++++++++++++++++++++++++++++
ጥር 23 ቀን 2017 ዓ.ም
****
አዲስአበባ -ኢትዮጵያ
""""""""""""""""""""""

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሊቃውንት ጉባኤ ጥር 23ቀን 2017 ዓ.ም "የዝክረ ኒቅያ ጉባኤን" ዓለም አቀፍ ጉባኤ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ለማካሔድ መርሐ ግብር መያዙ ይታወሳል።

ሆኖም ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ ማካሔድ ይቻል ዘንድ መርሐ ግብሩን ለሌላ ጊዜ ማስተላለፍ በማስፈለጉ ጉባኤው ከሚያዚያ 20-24 ቀን 2017 ዓ.ም እንዲካሔድ መወሰኑን ሊቃውንት ጉባኤ ገልጿል ስለሆነም ጉባኤው በተያዘለት መርሐ ግብር መሰረት የሚካሔድ ይሆናል።

ሊቃውንት ጉባኤ ያስተላለፈው ውሳኔ ደርሶናል እንደሚከተለው ይነበባል፦

ማሳሰቢያ
ጥር 23 ቀን 2017 ዓ.ም.
የዝክረ ኒቅያ ጉባኤ የሚካሄድበት ቀን ማስተካከልን ይመለከታል።

የቅዱስ ሲኖዶስ መጋቢ የሆነው ሊቃውንት ጉባኤ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በተወሰነለት መሠረት፦ በአሁኑ ሰዓት ውይይትና ምክክር በሚያስፈልጋቸው የትውልድ ዐበይት ጥያቄዎች ላይ በመምከር ያለፈውን
ለማጽናት፣ የሚመጣውን ለማቅናት፥ ሃይማኖትና ቀኖናን ጠብቆ ለማስጠበቅ የሊቃውንት መሰባሰብ እጅግ አስፈላጊ ሆኖ በመገኘቱ፤ “ዝክረ ኒቅያ” በሚል
ዓለም ዐቀፍ ጉባኤ ሊቃውንት ከጥር 26-29 ቀን 2017 ዓ.ም. በአዲስ አበባ መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ለማካሄድ ታቅዶ እንቅስቃሴሲደረግ ቆይቷል።

ሆኖም፦
1ኛ) ጉባኤው በመላ ሀገሪቱ የሚገኙ የጉባኤ ቤት መምህራንና ሊቃውንት የሚታደሙበት እንደመሆኑ፥ በተለይ በጠረፉ የሀገራችን ክፍል የሚገኙ
መምህራንን በበቂ ቊጥር ለማካተት እንዲቻል፥ ባለው ተጨባጭ ሁኔታ ተጨማሪ ጊዜ በማስፈለጉ፤

2ኛ) በጥር ወር በርካታ ሀገራዊ ክንውኖችና ሃይማኖታዊ ክብረ በዓላት በየአካባቢው የሚካሄዱ በመሆናቸው የጉባኤው መካሄጃ ጊዜ እንዲስተ ካከል ከአንዳንድ አህጉረ ስብከት በተደጋጋሚ አስተያየት በመሰጠቱ፤

3ኛ) ጉባኤው ከዘመናት ቆይታ በኋላ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚካሄድና በቤተ ክርስቲያኒቱ ጉዳዮች ዙሪያ ጠቃሚ ውይይቶችን በማካሄድ፥

ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ የሚጠቅም የውሳኔ ሐሳብና አስተያየት የሚያቀርብ፥ አልፎም የአቋም መግለጫ የሚያወጣ በመሆኑ፤የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት ከመካሄዱ ጥቂት ቀደም ብሎ ከሚያዝያ 20-24ቀን 2017 ዓ.ም. እንዲካሄድ በሊቃውንት ጉባኤ መወሰኑን በአክብሮትእየገለጸን፤ የአህጉረ ስብከት የሥራ ኀላፊዎች የተሳታፊዎች ልየታ መመሪያ እስከሚደርሳቸው ድረስ ለጉባኤው ይመጥናሉ የሚሏቸውን መምህራን በመለየት ዝግጅት እያደረጉ እንዲቆዩ አደራ እንላለን።

ሊቃውንት ጉባኤ

በማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮች ያግኙን፤ ይወዳጁ ለሌሎችም ያጋሩ።
1. ድረገጽ:- https://eotceth.org
2. ፌስ ቡክ ገጽ:- የ/ኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ/Department of Public Relation
3.https://m.facebook.com/story.php?story_fbid=507787748855477&substory_index=507787748855477&id=61565158745873&mibextid=ZbWKwL
4. በቴሌግራም ቻናላችን#https://t.me/DimtseTewahido1927
5. https://t.me/DimtseTewhido
6. eotcprdepartment@gmail.com




ቀሲስ በላይ መኮንን በ5 ዓመት ጽኑ እስራትና በ10 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ ተቀጡ

የፌደራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ 3ኛ የሙስና ጉዳዮች ወንጀል ችሎት በእነ ቀሲስ በላይ መኮንን መዝገብ ላይ የቀረቡ የግራ ቀኝ ማስረጃዎችን መርምሮ በዛሬው የችሎት ቀጠሮ በጽኑ እስራትና በገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወሰነ።

የፍትህ ሚኒስቴር የሙስና ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዐቃቤ ሕግ በተከሳሾች ቀሲስ በላይ መኮንን፣ በግብርና ኢንቨስትመንት ላይ የተሰማራው እያሱ እንዳለ፣ በኮሚሽን ስራ ላይ የተሰማራው በረከት ሙላቱ እና አለምገና ሳሙኤል እንዲሁም የኒሞና ንግድ ስራ ኃላ/የተ/የግል ማህበር ስራ አስኪያጅ አበራ መርጋ በተባሉ ተከሳሾች ላይ በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ ቁጥር 32 ንዑስ ቁጥር 1 (ሀ) እና የሙስና ወንጀሎች ለመደንገግ የወጣውን አዋጅ ቁጥር 881/2007 አንቀፅ 32 ንዑስ ቁጥር 2 እና ንዑስ ቁጥር 3 ስር የተመለከተውን ድንጋጌ እና በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ ቁጥር 382 ንዑስ ቁጥር 1 ስር የተመለከተውን ድንጋጌ መተላለፋቸውን ጠቅሶ ዝርዝር ክስ አቅርቦባቸው ነበር።

በዚህም ተከሳሾቹ ከአፍሪካ ህብረት ምንም አይነት የክፍያ ትዕዛዝ ባልተሰጠበት ሁኔታ ላይ ተከሳሾች በተለያየ መጠን ክፍያ እንዲፈጸምላቸው የሚል አጠቃላይ የ6 ሚሊየን 50 ሺህ ዶላር ሀሰተኛ የክፍያ ሰነድ በአንደኛ ተከሳሽ አማካኝነት ለባንኩ መቅረቡ ተጠቅሶ በሁሉም ተከሳሾች ላይ ከባድ የማታለል ሙስና ወንጀል ክስ ማቅረቡ ይታወሳል።

በዚህ መልኩ የቀረበውን ዝርዝር ክስ ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱት ተከሳሾች ብቻ ችሎት ቀርበው የክስ ዝርዝሩ እንዲደርሳቸው የተደረገ ሲሆን 4ኛ እና 5ኛ ተከሳሾች በአድራሻቸው ባለመገኘታቸውና በተደጋጋሚ ቀጠሮ ባለመቅረባቸው ለጊዜው ክሳቸው እንዲቋረጥ ተደርጓል።

ከ1ኛ እስከ 3ኛ ተራ ቁጥር የተጠቀሱ ተከሳሾች ክሱ እንዲሻሻልላቸው ያቀረቡት የመጀመሪያ ደረጃ ክስ መቃወሚያ ነጥቦችን ፍርድ ቤቱ መርምሮ ወደፊት በማስረጃ የሚጣራ መሆኑን ገልጾ መቃወሚያቸውን አልተቀበለውም።

ከዚህም በኋላ ተከሳሾቹ በክሱ ላይ የተጠቀሰውን የወንጀል ድርጊት አለመፈጸማቸውን ጠቅሰው የዕምነት ክህደት ቃል መስጠታቸውን ተከትሎ ዐቃቤ ሕግ አጠቃላይ ሶስት ምስክሮችን አቅርቦ ምስክርነታቸውን አሰምቶ ነበር።

ፍርድ ቤቱ የምስክሮችን ቃል መርምሮ በክሱ ዝርዝር የተጠቀሰው የወንጀል ድርጊት መፈጸሙን በዐቃቤ ሕግ በማስረጃ ማረጋገጡን ጠቅሶ በአንደኛው ክስ ብቻ እንዲከላከሉ በሙሉ ድምጽ ብይን ሰጥቶ ነበር።

ሁለተኛውን ክስ በሚመለከት በሐሰተኛ ሰነድ የተፈጸመ ድርጊት መሆኑ በአንደኛውን ክስ ላይ መገለጹን ተከትሎ በሰበር ሰሚ ችሎት ትርጉም የተሰጠባቸው በተደራራቢነት የቀረቡና ተጠቃልለው ሊያስቀጡ የሚችሉ ድንጋጌዎች መኖራቸውን ፍርድ ቤቱ አብራርቶ ሁለተኛውን ክስ ውድቅ በማድረግ በአንደኛው ክስ ብቻ በከባድ አታላይነት ሙስና ወንጀል እንዲከላከሉ ብይን ሰጥቷል።

ሆኖም ተከሳሾቹ እንዲከላከሉ በሰጠው ብይን የዐቃቤ ሕግ ማስረጃን በተገቢው ማስተባበል አለመቻላቸው ተጠቅሷል።

በዚህም 1ኛ ተከሳሽ ቀሲስ በላይ መኮንን በሙሉ ድምጽ የጥፋተኝነት ፍርድ የተሰጠባቸው ሲሆን፤ 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾች በአንድ ዳኛ የሀሳብ ልዩነት በአብላጫ ድምጽ ጥፋተኛ ተብለዋል።

የሀሳብ ልዩነት ያቀረቡት አንደኛው ዳኛ 2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾችን በሚመለከት የባንክ ሂሳባቸው በመገለጹ ብቻ የወንጀል ተግባሩ በስምምነት ተፈጽሟል ለማለት አያስችልም የሚል የሀሳብ ልዩነት እንዳላቸው ጠቅሰው ልዩነታቸውን አሳይተዋል።

ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኝ የቅጣት አስተያየት መርምሮ ዐቃቤ ሕግ ወንጀሉ የተፈጸመው በትብብር መሆኑን ጠቅሶ ያቀረበውን የቅጣት ማክበጃ ይዟል።

በዚህም1ኛ ተከሳሽ ቀሲስ በላይ መኮንን ያቀረቡትን አራት የቅጣት ማቅለያ በመያዝ በዕርከን 21 መሰረት በ5 ዓመት ጽኑ እስራትና በ10 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል።

2ኛ እና 3ኛ ተከሳሾችን በሚመለከት ደግሞ እያንዳንዳቸው አራት፣ አራት የቅጣት ማቅለያ አስተያየት በመያዝ በዕርከን 17 መሰረት በ3 ዓመት ከ3 ወር ጽኑ እስራትና በ3 ሺህ ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ወስኗል።

በፍርድ ቤቱ በተከሳሾች ላይ የተወሰነውን የጽኑ እስራት ውሳኔን የአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት እጃቸው ከተያዘ ጀምሮ ታሳቢ በማድረግ እንዲያስፈጽም ታዟል።
FBC
በታሪክ አዱኛ












Forward from: ቤተ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
"የህይወት እናት ድንግል ማርያም ሆይ ትንሳኤሽ ሳይሆን ሞትሽ ይደንቀኛል፤ እርገትሽ ሳይሆን ወደ መቃብር መውረድሽ ይገርመኛል፤ የብርሃን እናት ድንግል ማርያም ሆይ ትወጂኛለሽን? ብየ አልጠይቅሽም ፍቅርን የወለድሽ አንቺ ለአለሙ ሁሉ ፍቅርሽ የበዛ ነውና፤ አትናፍቂኝምን? ብየም አልጠይቅሽም ዘወትር እኔን ለመጠበቅ ከጎኔ እንደማትለይ አውቃለሁኝና፤ ሆኖም እመቤቴ ሆይ፦ እንደ ቶማስ አይሽ ዘንድ በእጅጉ እጓጓለሁ የቶማስ ንፅህናና ቅድስና ግን የለኝም እንደ ዮሃንስ ከጎንሽ ልሆን እጓጓለሁ የዮሃንስ ፀጋ ግን የለኝም።

እናቴ ሆይ፦ እንደ ኤልሳዕ የልቦናዬ አይን በርቶ ሰማያዊ ክብርሽን ላይ አልተቻለኝምና አዝናለሁ ኤልሳዕ በፀሎት ሃይል የግያዝን አይን እንዳበራ አንቺም አይኔን ታበሪልኝ ዘንድ ሃይልሽን በእኔ ላይ አበርቺ፡፡


ድንግል ሆይ፦ ይህን የምል የእምነት ማረጋገጫ ፈልጌ አይደለም በልጅሽ መሰረትነት የታነፅኩኝ በልጅሽ ስምም የተጠመቅኩኝ ነኝና፤ ነገር ግን ስለምትናፍቂኝ ይህን አልኩኝ ስለዚህም ነይ ነይ እምየ ማርያም እያልኩኝ እንደ እናቶቼም እለምንሻለሁ፡፡ የብርሃን ልብስሽን ለብሰሽ ነይ የክብር አክሊልሽን ደፍተሽ ነይ አንቺ ሱላማጢስ ሆይ ነይ እናይሽ ዘንድ ነይ፡፡"


Forward from: ኦርቶዶክሳዊ ቅዱሳት ሥዕላት: Ethio Icons
+++ሥዕለ እረፍታ ለማርያም+++

በሠዓሊ ኃይለ ማርያም ሽመልስ (በቅዱሳት ሥዕላት ዙርያ አማካሪ፣ ጥናትና ሒስ አድራጊ) 0913 05 2824

++++++++++===+++++++++++
እንኳን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የእረፍት በዓል አደረሳችሁ። ከሥር የእመቤታችን የእረፍትና የግንዘት ታሪክን መሠረት በማድረግ ትውፊቱን ጠብቀው የተሣሉ ጥንታዊያን የብራና፣ የእንጨት ገበታ (ኢቆና)፣ እና የግድግዳ ቤተ መቅደስ ሥዕሎች ቀርበዋል።

የእመቤታችን የእረፍት ሥዕል እንደተሣለበት መደብ እና ያለው የቦታ ስፋት የሚጨመሩ ወይም የሚቀነሱ አካላት አሉበት።

በአጠቃላይ ሲሣል የእመቤታችን ቅዱስ ሥጋ በክብር አልጋ ላይ ሆና (ተቀምጣ / ጋደም እንዳለች)፤
ቅዱስ ነፍሷን ጌታችን በእልፍ አእላፍ መላእክት ተከቦ ሲቀበላት፤
ቅዱሳን ሐዋርያት እያዘኑ ከበዋት መብራት አብርተው፣ መጽሐፍ እያነበቡ እና እያጠኑ፣ ቅዱስ ጷጥሮስ በግርጌ ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በራስጌ ሆነው፣
ቅዱሳን መላእክት እያጠኑ፣
ቅዱሳን ደናግል አዝነው፣
ቅዱስ ዳዊት በገና እየደረደረ፣ ቅዱስ እዝራ በመሰንቆ እያመሰገነ በአጠቃላይ በአስደናቂ መንፈሳዊ ደስታ ይሣላል።

ማስታወሻ፥ የእመቤታችን የእረፍት ሥዕል ላይ ታውፋንያን አስገብቶ መሣል ጸያፍና ተገቢ ያልሆነ ነው። ምክንያቱም ስንክሳር፣ ተአምረ ማርያም ሆነ ሌሎች አዋልድ መጻሕፍት እንደሚነግሩን ታውፋንያ በዚህ በተቀደሰ መንፈሳዊ ስፍራ አስቀድሞ አልነበረም።

የቤተ ክርስቲያን የሆኑት ቅዱሳት ሥዕላት እንወቅ፣ እንመልከት እና እንጸልባቸው። በስጦታ ይሁን  ወይም በስእለት ለቤተ ክርስቲያንም እንስጥ።


ጥንታዊ ቅዱሳት ሥዕላት ለማየት ለማውረድ፣ ለሌሎች ለማጋራት ከፈለጉ @ethioicons ቤተሰብ ይሁኑ።




አስተርዮ ማርያም
የማይታየው የታየበት፣ የራቀው የቀረበበት፣ የረቀቀው መለኮት በገዘፈ ሥጋ ማርያም የተገለጠበት፣ የወልድ ልጅነት በአብና በመንፈስ ቅዱስ የተመሰከረበት፣ በልደቱ፣ በጥምቀቱ አንድነት በሦስትነት እንዲሁም መለኮት በሥጋ ሥጋም በመለኮት በተዋሕዶ ተገልጦ ምሥጢሩ ገሃድ የሆነበት የመገለጥ የመታየት ጊዜ የሆነው ወቅት በቤተ ክርስቲያናችን አስተምህሮ ዘመነ አስተርዮ እየተባለ ይጠራል፡፡
በዚሁ በዘመነ አስተርዮ መካከል የሚገኝ ስለሆነ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም “በዓለ ዕረፍት አስተርዮ ማርያም” እየተባለ ይጠራል፡፡ ይህ አስተርዮ ማርያም የምንለው ታላቅ በዓል እናታችን እመቤታችን ከዚህ ዓለም ድካም ያረፈችበት መታሰቢያ ሲሆን ቀኑም ጥር ፳፩ ነው፡፡ ሰማይና ምድር የማይወስኑትን የወሰነች፣ ሞትን በሞቱ የመሻር ሥልጣን ያለውን፣ ዓለምን በመዳፉ የጨበጠውን የወለደች ክብርት ቅድስት እመቤታችን ከዚህ ዓለም ድካም የምታርፍበት ቀን በደረሰ ጊዜ ይኸውም ጥር ፳፩ ቀን በዕለተ እሑድ በ፷፬ ዓመቷ፣ በ፵፱ ዓ.ም መንፈስ ቅዱስ የዕረፍቷ ጊዜ መድረሱን ነግሯት በልጇ መቃብር ሆና ጸሎት ታድርስ ነበር፡፡ እንዲህም ብላ ጸለየች፤ ‹‹ልጄ ወዳጄ ሆይ ልመናዬን ተቀብለህ ደቀ መዝሙርህን ዮሐንስን በዚህች ሰዓት አምጣው፤ እንዲሁም በሕይወተ ሥጋ ያሉ ሐዋርያትን ሁሉንም፣ ነፍሳቸውንም የለየሃቸውን አምጣቸው፤ አንተ የሕያዋንና የሙታን አምላክ ነህና›› አለች፡፡ (የጥር ፳፩ ስንክሳር)
በዚህ ጊዜ ዮሐንስን ደመና ተሸክማ ከኤፌሶን አመጣችው፤ ምስጋናም አቀረበላት፤ ሁሉም ሐዋርያት የሞቱትም ከመቃብር ተነሥተው ወደ እመቤታችን ደርሰው ሰገዱላት፡፡ እንዲህም ስትል ጠየቀቻቸው፤ ‹‹ትነግሩኝ ዘንድ እሻለሁ፤ ከዚህ ዓለም እንደምለይ ከወዴት ሰማችሁ?›› አለቻቸው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስና ሐዋርያት ሁሉም ‹‹ወደ አንቺ እንድንመጣ መንፈስ ቅዱስ አዘዘን፤ በደመና ላይም በተጫን ጊዜ ወደ አንቺ እንደ ዐይን ጥቅሻ ፈጥነን ደረስን›› አላት፡፡ በዚያን ጊዜ የክብር ባለቤት ልጇ ወዳጇ ኢየሱስ ክርስቶስ እልፍ አእላፍ መላእክቱን አስከትሎ ወደ እርሷ መጣ፡፡ (ጥር ፳፩ ስንክሳር)
እንዲህም አላት ‹‹እናቴ ሆይ ከዚህ ዓለም ድካም ላሳርፍሽ መጥቻለሁ›› አላት፡፡ እርሷ ግን ‹‹ልጄ ሰማይና ምድር የማይወስኑህን ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን በማኅፀኔ ተሸክሜህ፤ በድንግልና ወልጀህ እሞታለሁን?›› አለችው፡፡ በዚህ ጊዜ በሲኦል የነበሩ ነፍሳትን ሁሉ አሳያትና ‹‹እናቴ ሆይ ሞትሽ ለእነዚህ ሁሉ ነፍሳት መዳን ምክንያት (ቤዛ) ይሆናቸዋል›› አላት፡፡ ‹‹እነዚህን ሁሉ ከማርክልኝስ ይሁን›› አለች፡፡ በዚህ ጊዜ ቅድስት ሥጋዋን ከክብርት ነፍሷ ለይቶ በቃለ አቅርንት በይባቤ መላእክት በክብር ነፍሷን ዐሳረጋት፡፡ (መዝገበ ታሪክ ቁጥር አንድ ገጽ ፻፶፭፣ ጥር ፳፩ ስንክሳር)
የእመቤታችን አማላጅነትና ተረዳኢነት አይለየን፤ አሜን



20 last posts shown.