Фильтр публикаций


የተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ የቻት ጂፒ.ቲ ፕላስ አገልግሎቶችን ለዜጎቿ በነፃ አቀረበች፡፡

በተባበሩት አረብ ኢሚሬትስ የሚኖሩ ሰዎች የቻት ጂፒ.ቲ ፕላስ አገልግሎቶችን በነጻ መጠቀም እንዲችሉ የሀገሪቱ መንግስት ከኦፕን ኤ.አይ ኩባንያ ጋር ስምምነት አድርጓል፡፡ ስምምነቱ በክፍያ ይቀርቡ የነበሩ የቻት ጂፒ.ቲ ፕላስ አገልግሎቶችን ለመላው ሕዝቧ በነፃ ያቀረበች የመጀመሪያዋ ሀገር ያደርጋታል።


ኦሮሚያ ባንክ “ሚልኪ” የተሰኘ ያለ ዋስትና ብድር መስጠት የሚያስችል መተግበሪያ ይፋ አደረገ

#FastMereja I ኦሮሚያ ባንክ ያለ ምንም የዋስትና ማስያዣ ብድር መስጠት የሚያስችል ሚልኪ የተሰኘ አዲስ ዲጅታል የብድር አገልግሎት መተግበሪያ ስራ ላይ ማዋሉን ዛሬ ግንቦት 20/2017 ዓ.ም በሐያት ሪጀንሲ ሆቴል በተከናወነ የማብሰሪያ ስነ ስርዓት ተገልጿል።

ኦሮሚያ ባንክ ከኳንተም ቴክኖሎጂ አ.ማ ጋር በመሆን ያበለፀገዉን ሚልኪ የተሰኘ ዲጂታል የብድር አገልግሎት መተግበሪያ፤ በቀላል መልኩ ብድርን ለሁሉም ዜጎች ተደራሽ ለማድረግ ያለመ የዲጂታል አገልግሎት መሆኑ ተነግሯል።

ይህ ዲጅታል የብድር አገልግሎት የባንኩን የዲጅታል ባንኪንግ ተደራሽነት ከማስፋቱም በተጨማሪ የፋይናንስ አካታችነትን በተግባር በማረጋገጥ ሀገራችን ኢትዮጵያ ለያዘችዉ የዲጅታይዜሽን እቅድ መሳካት ጉልህ ሚና ይኖረዋል ሲል የባንኩ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ተፈሪ መኮንን ተናግሯል።

ሚልኪ ዲጂታል የብድር አገልግሎት ከሚሰጣቸዉ ዘርፈ ብዙ አገልግሎቶች መካከል በወርሀዊ ደመወዝ ለሚተዳደሩ፣ የደሞዝ መዳረሻ ብድርን ጨምሮ የብድር አቅርቦት አስፈልጓቸው በዋስትና ማስያዢያ ምክንያት አገልግሎቱን ላጡ የተለያዩ የህበረተሰብ ክፍሎች ያለምንም ዋስትና ብድር የሚያገኙበት ሁኔታ አመቻችቷል፡፡

ሚልኪ ዲጅታል የብድር አገልግሎት ከሚሰጣቸዉ ግልጋሎቶች መካከል ሚልኪ ፉርቱ የተሰኘዉ አገልግሎት በዕለት ተዕለት ገቢ የሚተዳደሩና እና ንግዳቸዉን ለማሳደግ የብድር አገልግሎት ለሚፈልጉ ዜጎች እንዲሁም ስራ ፈጣሪዎች የማስያዣ ዋስትና ማቅረብ ሳይጠበቅባቸዉ ብድር ማግኘት የሚያስችል አሰራርም ዘርግቷል፡፡

በተለየ መልኩ ሴቶችን ተጠቃሚ የሚያደርገዉ ሚልኪ ሀርሜ የተሰኘዉ የብደር አገልግሎት ከሌሎች የብድር አቅራቢዎች በተለየ አነስተኛ የአገልግሎት ክፍያ ብቻ በማስከፈል ያለምንም ማስያዣ ብድር በመስጠት ለባርካታ የሀገራችን ሴቶች አማራጭ የፋይናንስ አቅርቦት ሆኖ መጥቷል፡፡

በተጨማሪ የጥቃቅንና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ብድር፤ ለሞባይል ፣ ለኤሌክትሮኒክስ እና የቤት ቁሳቁስ መግዣ ብድርእንዲሁም ሌሎች አጓጊ ጥቅሎችን በዉስጡ አካቷል፡፡

ሚልኪ ዲጅታል የብድር አገልግሎትን ከሌሎች መሰል አገልግሎት ከሚሰጡ መተግበሪያዎች ለየት የሚያደረግዉ የነዳጅ ግብይትን ለማዘመን የተያዘዉን እቅድ ለማሳካት ፤ ነዳጅ ቀጂዎች በሂሳባቸዉ በቂ ገንዘብ ባይኖራቸዉም እንኳ፣ በሚልኪ ፈጣን የብድር አገልግሎት በመጠቀም ነዳጅ መቅዳት የሚያስችል አሰራር አካቷል።

ደንበኞች ወደ ባንኩ በአካል መምጠትም ሆነ የብድር ዋስትና ማስያዣ ማቅረብ ሳይጠበቅባቸው በእጅ ስልካቸዉ ላይ በሚያወርዱት ሚልኪ መተግበሪያ ላይ በመመዝገብ ብቻ በሴኮንዶች ዉስጥ ፈጣን የብድር አግልግሎት ማግኘት ይችላሉ።


ከአውሮፓ ወጥቶ ወደ ኤዥያ ያቀናው ማንችስተር ዩናይትድ በኳላ ላምፑር ከሽንፈት አላመለጠም 1 ለ 0 ተሸንፏል። የመጀመሪያ የቱር ጨዋታችን በሽንፈት ተደምድሟል ሲል ክለቡ ገልጿል።


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ግንቦት 21 ከሐመረ ብርሀን ደብረ ምጥማቅ ማርያም አይቀርም!


በጎንደር ከተማ ቀበሌ 06 የምትገኘው ሐመረ ብርሃን ደብረ ምጥማቅ ማርያም ቤተ ክርስቲያን በህዝበ ክርስቲያኑ ከፍተኛ ርብርብ ግንባታዋ 40 በመቶ ደርሷል።

ቤተ ክርስቲያኗ ከ300 ዓመታት በላይ አስቆጥራለች። አሁን በመሰራት ላይ ያለችው ቤተ ክርስቲያንም 1,700 ካሬ ላይ ያረፈች ሲሆን ስራው ከተጀመረም አንድ አመት ከ5 ወራት አልፎታል።

በዚህ ስራ ላይም እጅግ በርካታ የጎንደር ምዕመናን እየተሳተፈ ይገኛል።

በነገው እለት ማለትም ግንቦት 21 ቀን 2017 ዓ.ም የእመቤታችን የቅድስተ ቅዱሳን ድንግል ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል በደመቀ ሁኔታ ስለሚከበር የጎንደር ከተማ እና አካባቢው ምዕመናን መጥተው እንዲያከብሩ ተጋብዘዋል። አድራሻ፦ ጎንደር ከተማ ቀበሌ 06 ነው።


ጠሪ:- ቤተ ክርስቲያኗ


ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የተሰጠ ማብራሪያ

ግንቦት 19 ቀን 2017 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ሚዲያ አገልግሎት በተሰኘ የዜና ማሰራጫ እንደ ሰበር ዜና የተላለፈ መልእክት “በኢትዮጵያ ንግድ ባንከ የውስጥ አካውንት ውስጥ ተቀምጦ የነበረ ከ7 ቢሊየን ብር በላይ መዘረፉ ተገለፀ” በማለት ባንካችን ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ እንደተዘረፈ፣ ዘራፊዎቹ እንዳልተያዙ እና ባንካችንም ጉዳዩን አድበስብሶ እንዳለፈው የሚገልጽ የሐሰት ዜና ስለተዘገበ በጉዳዩ ላይ አጭር መግለጫ ለመስጠት ተገድደናል።
ከላይ የተጠቀሰው ሚዲያ እና ሌሎችም ይህንኑ ሚዲያ ያጣቀሱ ሚዲያዎች ከባንካችን ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ እንደተዘረፈ የሚገልጽ ዜና ቢዘግቡም፣ እውነታው ግን፡-

➢ በሚዲያዎቹ ከተዘገበው በተቃራኒ ከባንካችን ምንም የተዘረፈ ገንዘብ አለመኖሩን፣ ይልቁንም ከፍተኛ ገንዘብ ለመዝረፍ የተደረገ ሙከራ መሆኑን፣

➢ ባንካችን ሙከራው በተደረገ በጥቂት ደቂቃዎች ዉስጥ በጠንካራው የውስጥ ቁጥጥር ስርአታችን አጠራጣሪ ግብይት መፈፀሙን ስለደረሰበት ምንም ዓይነት ገንዘብ ወጪ ሳይደረግ ሙከራው ወዲያውኑ እንዲከሽፍ መደረጉን፣

➢ ሙከራው በጥቂት ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት ባሰቡ ተጠርጣሪዎች የተፈፀመ እንጂ የባንካችንን ሲስተም ተላልፎ የተፈፀመ ጥቃት አለመሆኑን፣

➢ ባንካችን ሙከራ የተደረገበትን ገንዘብ ባለው ጠንካራ የቁጥጥር ስርዓት አማካኝነት ከጥቃት ከተከላከለ በኋላ ጉዳዩን ለሚመለከተው የሕግ አካል በማሳወቅ ተጠርጣሪዎቹ በፖሊስ ቁጥጥር ስር የዋሉና የምርመራ ስራውም ተጠናክሮ እየተከናወነ የሚገኝ መሆኑን፣

➢ በማጠቃለያም ባንካችን እንደማንኛውም የፋይናንስ ተቋም በተለይም እንደ ግዙፍ የፋይናንስ ተቋምነቱ ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት አስበው ለሚንቀሳቀሱ አካላት ኢላማ መሆኑ እሙን ቢሆንም እንዲህ አይነቱን ሕገ ወጥ ተግባር ለመከላከል የሚያስችል ጠንካራ የቁጥጥር ስርዓትና የዘመነ ሲስተም ያለው ለመሆኑ ይህ የሙከራ ድርጊት መክሸፉ አንዱ ማሳያ ነው፡፡

በአሁኑ ወቅትም ጉዳዩ በሕግ አካላት ተይዞ ጥብቅ ክትትል እየተደረገበት የሚገኝ እና የምርመራ ሂደቱም ያልተጠናቀቀ መሆኑን እያሳወቅን በቀጣይ የሕግ ሂደቱ ሲጠናቀቅ ዝርዝር መረጃውን የምናሳውቅ መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን፡፡




ወጣቱ ኢትዮጵያዊ የዓለም የሰላም አምባሳደሮች ሽልማት በስቶኮልም ተጎናፀፈ

#FastMereja I ወጣቱ ኢትዮጵያዊ የሰላም አምባሳደር ስለሺ ዑመር የዓለም የሰላም አምባሳደር ሽልማት አሸናፊ በመሆን ሀገሩንና ህዝቡን በትልቅ መድረክ አስጠርቷል። ወጣቱ ሽልማቱን ያሸነፈው ሰሞኑን ሲዊድን ስቶኮልም በተካሄደ ትልቅ ስነስርዓት ነው።

ወጣቱ የሰላም አምባሳደር ይህንን ትልቅ የሰላም አምባሳደርነት ሽልማት አሸናፊ የሆነው ፤ በሰላም፣ በዲፕሎማሲ፣በወጣቶች ሁለንተናዊ ተሳትፎና ተጠቃሚነት፣በስብዕና ግንባታና ተያያዥ መስኮች እያከናወነ ባለው ስኬታማ ስራ ሲሆን ሽልማቱም በሰላምና በተያያዥ ጉዳዮች ስኬታማ ስራ ላከናወኑ ግለሰቦችና ተቋማት በስቶኮልም የሚሰጥ ሽልማት መሆኑ ታውቋል።

አምባሳደር ስለሺ ዑመር በዓለም አቀፍ የሰራተኞች ድርጅት (lLO)፣በተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ኮሚሽን ( UNHCR) እና በተባበሩት መንግስታት የሕፃናት መርጃ ድርጅት (UNICEF) የወጣቶች መረብ ሊቀመንበር ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ወጣቶች ምክር ቤት አባልም ነው።
ወጣት አምባሳደር ስለሺ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት (ተ.መ.ድ)፣ በአፍሪካ ሕብረትና በብሪክስ የወጣቶች ካውንስል ለሐገሩ በሰላም፣ በኢኮኖሚና በፖለቲካዊ ተሳትፎው ትልቅ ድልን እየተጎናፀፈ የሚገኝ ወጣት መሪ እንደሆነም ለማወቅ ተችሏል።

የሰላም አምባሳደሩ ወጣት ከዚህም በተጨማሪ ከተመሰረተ ሰባት ዓመታትን ያስቆጠረውና በወጣቶች መሪነት፣ በዲፕሎማሲ፣ በስራ ፈጠራና በተያያዥ ዘርፎች ላይ አተኩሮ የሚሰራው የ “Safe Light Initiatives” ሀገር በቀል ሲቪል ማህበር መስራችና ዳይሬክተርም ነው።

ወጣቱ በስቶኮልም ያሸነፈው የሰላም አምባሳደርነት ሹመት ለኢትዮጵያ ወጣቶች መነቃቃትን የሚፈጥርና ምሳሌ የሚሆን ነው ተብሏል።


በአዲስ አበባ በሚያዝያ ወር ብቻ 9ሺ እግረኞች ተቀጡ!

#FastMereja I በአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ባለስልጣን በአስራ አንዱም ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች ደንብ 557/2016 መነሻ ባደረገ ጥብቅ ቁጥጥር በሚያዚያ ወር ብቻ 9,617 እግረኞች መቅጣቱን አስታወቀ።

ባለፈው ሚያዚያ ወር በአስራአንዱም ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች እግረኞች ትክክለኛውን የመንገድ አጠቃቀም እንዲከተሉ ተከታታይነት ባለው የግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ ግብር በተጓዳኝ በተካሄደ ቁጥጥር የእግረኛ ማቋረጫ /ዜብራ/ ላይ ያልተሻገሩ፣ በተሸከርካሪ መንገድ ላይ የተጓዙ፤ ተሸከርካሪን ከፊት እያዩ ባላተጓዙና በሌሎችም ጥፋት የተገኙ እግረኞች በገንዘብ ተቀጥተዋል፡፡

ከገንዘቡም ውጪ በማህበራዊ አገልግሎት እንዲሰጡ የተደረጉ እግረኞች መኖራቸውንና ይኸው በግንዛቤ የተደገፈ የእግረኛ ቁጥጥር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ታውቋል፡፡


የትምባሆ ምርቶች ማራኪ ሆነው መቅረባቸው ወጣቶችን እያሳሳቱ ነው ተባለ።

#FastMereja I የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለስልጣን ግንቦት 23 ቀን 2017 ዓ.ም የሚከበረውን የዓለም ትምባሆ የማይጨስበት ቀንን ምክንያት በማድረግ ለህብረተሰቡ ግንዛቤ ለማስጨበጥ የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን እያደረገ እንደሚገኝ ተገለጸ።

በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ38ኛ ጊዜ በሀገር አቀፍ ደረጃ ደግሞ ለ33ኛ ጊዜ ዘንድሮ ግንቦት 23/2017 ዓ.ም የሚከበረውን ትምባሆ የማይጨስበት ቀን የዓለም ጤና ድርጅት በትምባሆ እና በኒኮቲን ምርቶች ላይ የትምባሆ እንዱስትሪ አሳሳችና ድብቅ ስልቶችን በማጋለጥ ወጣቶችን እንታደግ በሚል መሪ ቃል እንዲከበር የወሰነ ሲሆን ዘመቻው የትምባሆ እና የኒኮቲን ኢንዱስትሪዎች ጎጂ ምርቶቻቸውን ማራኪ ለማስመስል የሚጠቀሙባቸውን ዘዴዎች በማጋለጥ ላይ እንዲያተኩር ተደርጓል ተብሏል።

የዘንድሮው የዘመቻ ርዕስ የተመረጠበት ዋነኛ ምክንያት በአሁን ወቅት ካሉት ግንባር ቀደም የህብረተሰብ ጤና ችግሮች መካከል በተለይም ለወጣቶች ጤና ተግዳሮቶች ከሆኑት ውስጥ ትምባሆ፣ ኒኮቲን እና ተዛማጅ ምርቶችን ማራኪነት/ሳቢነት ባላቸው መንገድ መቅረባቸው ሲሆን የትምባሆ ኢንዱስትሪው እነዚህን ምርቶች አጓጊ ለማድረግ ሽታቸው ጣዕማቸው ወይም መልካቸውን የሚቀይሩ ቅመሞችን እና ሌሎች ንጥረ ነሮችን በመጨመር ያለማቋረጥ ሙከራዎች በማድረግ የትምባሆ ምርቶች ጉዳት ለመደበቅ ጥረት በማድረግ ላይ በመሆኑ ነው::

በአሁኑ ወቅት ዘመናዊ ምርቶችን ለመጠቀም እንደ ቁጥር አንድ ምክንያት ሆነው ይጠቀሳሉ፡፡ በመሆኑም እነዚህ የትምባሆ ኢንዱስትሪዎች ጎጂ የሆኑ የትምባሆ ምርቶችን እና ሱስ የሚያስይዙ የኒኮቲን ምርቶቻቸውን በመጠቀም በተለይም ለወጣቶች ማራኪ እንዲሆኑ በማድረግ ስውር ስልቶችን ይጠቀማሉ ተብሏል።

ከሚጠቀሙባቸው ስልቶች መካክል ማራኪ ግብይት፣ ቄንጠኛ ዲዛይኖች ማራኪ ቀለሞች እና ማራኪ ጣዕሞች በዲጂታል ሚዲያ ቻናሎችን ጨምሮ ወጣቱን የህብረተሰብ ክፍል ለመሳብ ስልታዊ በሆነ መንገድ ተጠቅመው ገበያ ላይ ያውላሉ። በተጨማሪም አሳሳች ንድፎች፣ ማቀዝቀዣች እና ተጨማሪ ማጣፈጫዎችን እንደሚጠቀሙ ተገልጿል።

ስለሆነም ይህን የትምባሆ ኢንዱስትሪዎች ጣልቃገብነትና ድብቅ ሴራ ለማጋለጥ የዘንድሮ በዓለም ትምባሆ የማይጨስበት ቀን መሪ ሀሳብና ጭብጥ በመጠቀም የህብረተሰቡን ግንዛቤን ማሳደግ ወሳኝ ተግባር ተደርጎ መወሰድ አለበት ተብሏል።


የስፔኑ ክለብ ሲቪያ አትሌት ሰለሞን ባረጋ እና ጄሱስ ናቫስን ፎቶ አያይዘዉ እንኳን ለግንቦት 20 አደረሳችሁ ብሏል።


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
የቀድሞ ፕሬዝዳንት መንግስቱ ኃ/ማርያም ከረጅም አመታት በኋላ በቪዲዮ ያስተላለፉት መልዕክት።
🎥 ገነት አየለ


በ230 መርከቦች እስከ ሰባ ሺ ሰራዊት ይዘው ተጉዘዋል


የኖሩበት ዘመን ከ485 እስከ 515 ዓም ነው። በኢትዮጵያ ክርስትና ከተሰበከ ወዲህ ከነገሱ የአክሱም ነገሥታት ከኢዛና ቀጥሎ ከፍ ያለ ስም ያላቸውና ከፍተኛ ተግባርም ያከናወኑ ናቸው። ታላቁ ጻድቅ ንጉስ አፄ ካሌብ በዘመነ መንግስታቸው ኢትዮጵያ ከፍተኛ የእድገትና የስልጣኔ ደረጃ ላይ የደረሰች ቢሆንም የሰላም ጊዜ ግን አልነበረም። ሀገሪቱ በውስጥም ሆነ በውጭ የተለያዩ ጦርነቶች ነበሩባት።

ስለዘመነ ምንግስታቸው ስልጣኔና ጦርነት በርካታ ማስረጃዎች በድንጋይ ላይ ከተቀረፁ ጽሑፎች ተገኝተዋል። በተለይ በደቡብ አረቢያ የአሁኑ የመን ያደረጉት ዘመቻ በክርስቲያኖች ላይ ይደርስ የነበረውን በደል ለመግታት የዘመቱበት ነው፡፡ ከእርሳቸው በፊት የነበሩት የአክሱም ነገስታት የጦር አበጋዞቻቸውን እየላኩ በደቡብ አረብ ዉጊያ ቢያደርጉም አፄ ካሌብ ግን ራሳቸው የጦርነቱ መሪ በመሆን ከኢትዮጵያ ውጭ ውጊያ ያካሄዱ የመጀመሪያው ንጉሥ ናቸው።


ቅዱሱ ንጉሥ አፄ ካሌብ ሰራዊታቸውንም ይዘው ባህር ተሻግረው ለዘመቻ ከመሄዳቸው በፊት የህዝብን ድጋፍ ጠይቀዋል። በዚያ ዘመን ህዝቡ የሃይማኖት መሪዎችን አጥብቆ ያዳምጥ ስለነበር "የአክሱም ህዝበ ክርስትያን ርቀው እንዳይሄዱ" የሚለዉን ትእዛዝ በማንሳት ወደ ደቡብ አረብ ሄደው ለሚያደርጉት ጦርነት ድጋፍ እንዲሰጧቸው ከዘጠኙ ቅዱሳን አንዱ የነበሩትን አባ ጰንጠልዮንን ጠየቁ። አቡነ ጴንጠልዮንም ሙሉ ድጋፋቸውን ቡራኬያቸውን ሰጥተው ጦርነቱን በአሸናፊነት አጠናቀው በክብር ወደመናገሻ ከተማቸው እንዲመለሱ ጸልየው ሸኛቸው። ከዚህ በኋላ ሰራዊታቸውን የሚያጓጉዙባቸው መርከቦችን አዱሊስ አጠገብ በነበረው ገበዛን የሚባል የመርከብ መስሪያ ቦታቸው ማሰራት ቀጠሉ።


አፄ ካሌብ ወደ ደቡብ አረብ የሚዘምተውን ሠራዊት በ230 መርከቦች እስከ ሰባ ሺ ሰራዊት ይዘው ተጉዘዋል፡፡ የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍትና ሊቃውንት ግን ንጉሡ በጸሎት በተከፈተላቸው የምድር ውስጥ መንገድ ተጉዘው ከሀዲውን የአይሁድ መሪ ፊንሐስ እንዳጠፉት ይገልጻሉ፡፡ በንግሥና ዙፋን ከመቀመጣቸው በፊት የሚገባውን መንፈሳዊ ትምሕርት ጠንቅቀው የተማሩ ሃይማኖታቸው የጠራና እጅግ የሚደነቅ ነበር፡፡

አፄ ካሌብ ለእመቤታችንና ለቸር ልጇ የነበራቸው ጥልቅ ፍቅር የተገለጠና የሚያስቀና ነበር፡፡ ገና በዙፋን ሳሉ ጸሎትን የሚያዘወትሩ ካህን ወንጉስ ነበሩ፡፡ በወቅቱ ዐመፀኛው የአይሁድ መሪ ፊንሐስ በሃገረ ናግራን የአሁኗ የመን ውስጥ የነበሩ ክርስቲያኖችን ክርስቶስን ካዱ በሚል ጨፈጨፋቸው፡፡ ከተማዋንም ለ40 ቀናት በእሳት አነደዳት::


ዜናው በመላው ዓለም ሲሰማ በርካቶቹ ቢያዝኑም የተረፉትን ለመታደግ የሞከረ አልነበረም፡፡ ቅዱስ አፄ ካሌብ ግን የሆነውን ሲሰሙ ሔደው ንጉሱን አጥፍተው ሃይማኖት መልሰው ቤተ ክርስቲያን አንጸው ተመልሰዋል፡፡  እንደተመለሱም  "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ስላደረክልኝ የምሰጥህ ሰውነቴን እንጂ ሐብቴን አይደለም" በማለት መንግስታቸውን ለልጁ ገብረ መስቀል አውርሰው የወርቅ አክሊላቸውን አውልቀው በአባ ዸንጠሌዎን እጅ መንኩሶ መንኩሰው መንነዋል፡፡ ከዚያም በዐታቸወን ዘግተው በጾምና በጸሎት ተወስነው በ70 ዓመታቸው በ529 ዓ.ም ግንቦት 20 ቀን ዐርፈዋል፡፡ ጌታችንም በሰማይ ክብርን አጐናጽፎታል፡፡

የዓለምን ክብር የናቁ፣ ዘለዓለማዊውን ክብር የናፈቁ ቅዱሳን ሁሉን ትተው በገዳማት ይመንናሉ፡፡ ገዳማቸውን ስንደግፍ በዓታቸውን ስናጸና በረከታቸው ያድርብናል፡፡


ድጋፍ ለማድረግ:- ሙትአንሳ  ማር  ቅዱሰ ሚካኤል አንድነት  ገዳም


ኢትዮጲያ ንግድ ባንክ
1000442598391

ወይም

አቢሲኒያ ባንክ
141029444


የገዳሙ ስልክ ቁጥር:-0918077957 ወይም 0938644444




13. የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅ ምርጫን አስመልክቶ በሥራ ላይ የነበሩት ብፁዓን አባቶች የሥራ ዘመናቸውን ያጠናቀቁ በመሆኑ ለቀጣይ ሦስት ዓመታት የሚሠሩ ብፁዓን አባቶችን ለመምረጥ ዕጩዎችን የሚያቀርቡ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን በመሰየም ምልዓተ ጉባኤው ተገቢውን ምርጫ አከናውኗል፡፡

በዚሁም መሠረት ፡-
*. ለቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊነት ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ፣ በደቡባዊ ዞን ማይጨው፣ የደቡባዊ ምሥራቅ ትግራይና የራያ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስን መርጦ ሰይሟል

*. ለመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ሥራ አስኪጅነት ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የደቡብ ምዕራብ ሸዋ፣የሸገር ከተማ እና የምስካዬ ኀዙናን መድኃኔዓለም ገዳም የበላይ ኃላፊ ሊቀጳጳስን መርጦ ሰይሟል፡፡
* ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የሀድያና ስልጤ አህጉረ ሰብከትን እንደያዙ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
* ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም ሊቀ ጳጳስ ሆነው እንዲሠሩ ቅዱስ ሲኖዶስ መርጦ ሰይሟል፡፡
* ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ ሀገረ ሰብከት ሊቀ ጳጳስ
* ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የሜኖሶታና የኮሎራዶ አህጉረ ሰብከት ሊቀ ጳጳስ ሆነው እንዲሠሩ ቅዱስ ሲኖዶስ መድቧል፡፡

14. ብፁዕ አቡነ ገብርኤል የምዕራብ ሸዋ ሀገረ ሰብከት ጳጳስ፣ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ የደቡብ ኦሞና አሪ ዞኖች አህጉረ ሰብከት ሊቀ ጳጳስ፣ብፁዕ አቡነ በርናባስ የደቡብ ካልፎርኒያ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በሚዲያ ያስተላለፏቸው ትምህርቶች ስሕተትና ነቀፋ ያለባቸው መሆናቸውን አምነው ቅዱስ ሲኖዶስንና መላውን ሕዝበ ክርስቲያን ይቅርታ በመጠየቅ ሊቃውንት ጉባኤ ከቅዱሳት መጻሕፍት በማጣቅስ ያቀረበውን አስተምህሮ የተማሩት የሚያምኑትና የሚያስተምሩት መሆኑን በመግለጻቸው ቅዱስ ሲኖዶስ የሦስቱን አባቶች ይቅርታ ተቀብሎ ወደፊት እንዲህ ዐይነት የስሕተት ትምህርት ውስጥ እንዳይገኙና ነቀፋ ያለበትን ትምህርታቸውን በማረምና በማስተካከል ርቱዕ የሆነውን የቤተ ክርስቲያናችንን አስተምህሮ መሠረት በማድረግ በኢትዮጵያ ኦርቶዶስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መገናኛ ብዙኀን ሥርጭት ድርጅት በመቅረብ ትምህርት እንዲሰጡ በማለት ምልዓተ ጉባኤው ወስኗል፡፡

15. በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የሚኖሩ በግልና በቡድን ተደራጅተው ማኅበራዊ ሚዲያዎችን በመክፈት ከሃይማኖት ሥነ ምግባር በወጣ መልኩ የቤተ ክርስቲያናችንን ልዕልና የቅዱስ ሲኖዶስን ክብር የሚጋፋ ፣የአባቶችንና የአገልጋዮችን ተልእኮ የሚያደናቀፍ ያልተገባና መሠረት የሌለው መግለጫ የሚያሰራጩ አካላት እንዲታረሙ ቅዱስ ሲኖዶስ ለአንዴየና ለመጨረሻ ጊዜ በጥብቅ ያሳስባል፡፡

በመጨረሻም በሀገራችን በአንዳንድ ቦታዎች የሚታየው ግጭትና መፈናቀል ተወግዶ፣የሰው ልጅ የመኖርና የመዘዋወር መብት ተከብሮ፣ ሰብዓዊ ክብሩ ተጠብቆ ሁሉም ዜጋ በእኩልነት፣ በሰላምና በፍቅር ተከባብሮ በጋራ እንዲኖር፤ አለመግባባቶች በውይይት እንዲፈቱ ቤተ ክርስቲያን የሰላም ጥሪዋን ታስተላልፋለች፡፡

ግጭት፣ ጥላቻና ደም መፋሰስ፣ አካል ከማጉደልና ንብረት ከማጥፋት በቀር የሚያመጡት ክብርና ዘላቂ ሰላም ስለሌለ ልጆቻችን ችግሮችን በሰላማዊ መንገድ እንድትፈቱ ቅዱስ ሲኖዶስ ደጋግሞ ጥሪውን በማቅረብ በመላው ዓለም ጦርነት ባለባቸው ሀገራት ሁሉ ሰላምና ዕርቅ እንዲሰፍን በመጸለይ ቅዱስ ሲኖዶስ ግንቦት 20 ቀን 2017 ዓ.ም ዓመታዊ ጉባኤውን በጸሎት አጠናቋል፡፡

እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ

አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት

ግንቦት ፳ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ


የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ፡፡
ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

በመንፈስ ቅዱስ የሚመራው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 5 ቁጥር 164 በተደነገገው መሠረት የርክበ ካህናት መደበኛ ስብሰባውን ከግንቦት 6 ቀን 2017 ዓ.ም እስከ ግንቦት 19 ቀን 2017 ዓ.ም. ድረስ አካሂዷል፡፡

የመንበረ ሐዋርያት ወራሽ የሆነው ቅዱስ ሲኖዶስ ለቤተ ክርስቲያናችን አንድነትና እድገት፣ ለሀገር ሰላምና መረጋጋት፣ ለሐዋርያዊ ተልእኮ መስፋፋትና ለመንፈሳዊ ልዕልና ልዩ ትኩረት በመስጠት አስፈላጊ ውሳኔዎችን አሳልፎአል፡፡
በዚሁ መሠረት፡-

1. ለሰላምና ለአንድነት ቅድሚያ መስጠት፣ምትክ ለሌለው የሰው ልጅ ሕይወት ባለአደራ የሆነው ቅዱስ ሲኖዶስ ስለ ሰላም ያለማቋረጥ መጸለይ፣ ጸሎተ ምሕላ ማወጅ፣ የሰላምና የአንድነት ጥሪ ማስተላለፉ እንደተጠበቀ ሆኖ ለሰላምና ለአንድነት ልዩ ትኩረት ሰጥተው ሁሉን አቀፍ ሥራ የሚሠሩ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትን “የሀገራዊ ሰላምና የቤተ ክርስቲያን አንድነት ኮሚቴ” በማድረግ ቅዱስ ሲኖዶስ ሰይሟል፡፡

ኮሚቴውም ዘላቂ ሰላምንና አንድነትን ለማስፈን፣ የዜጎችን ሕይወት እየነጠቀ ያለው ግጭት እንዲቆም ጥረት እንዲያደርግ፣ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላትን ባካተተ መልኩ በየደረጃው የምክክርና የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና፣ ውይይቶችንና የጥናት መድረኮችን እንዲያዘጋጅ፤ አፈጻጸሙንም በየሦስት ወሩ ለቋሚ ሲኖዶስ ሪፖርት እንዲያደርግ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

2. ለሰዋስወ ብርሃን ቅዱስ ጳውሎስ መንፈሳዊ ኮሌጅ የትርጓሜ መጻሕፍትና የሴሚናሪ ደቀ መዛሙርት የሚሰጠው የምስክር ወረቀት ዲግሪ እንዲሆን በተወሰነው መሠረት በመማር ላይ ያሉትና በቀድሞው ሥርዓተ ትምህርት ተምረው በመመረቅ ቤተ ክርስቲያናችንን በማገልገል ላይ የሚገኙት ምሩቃን ተጓዳኝ ትምህርቱን ተምረው ዲግሪያቸውን ማግኘት እንዲችሉ የቀረበው ሥርዓተ ትምህርት ተግባራዊ እንዲደረግ፣በኮሌጁ የተጀመረው ሁለገብ ሕንፃም በተያዘለት የጊዜ ሠሌዳ መሠረት እንዲጠናቀቅ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

3. በገዳማት አስተዳደር መምሪያ አስፈጻሚነት የተደረገው የአንድነት ገዳማት ሀገር አቀፍ የምክክር ጉባኤ በየዓመቱ እንዲካሄድና የአቋም መግለጫው ላይ የቀረቡት ሐሳቦች በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት በኩል እየታዩ በቅደም ተከተል እንዲፈጸሙ ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ አስልፏል፡፡

4. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለሀገራችን እድገትና ሥልጣኔ ፈር ቀዳጅ በመሆን ያበረከተችው አስተዋጽኦ በታሪክ ምዕራፍ ውስጥ ጉልህነት ያለው ሲሆን፣ አሁንም እየተሠራ ባለው የኮሪደር ልማት መርሐ ግብር ላይ ኃላፊነቷን እየተወጣች ትገኛለች፡፡

ይኽን ቋሚ ታሪክ ያልዘነጋው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርና ክብርት ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ የቤተ ክርስቲያንን ይዞታ ለግንባታ በሚያመች ሁኔታ አሰባስቦ በመስጠት ለፈረሱ ቤቶች ካሣ በመክፈል፣ በጽርሐ ምኒልክ ሕንጻ ምትክ በነባሩ ቦታ ላይ B+G+4+ቴራስ በመንግሥት በጀት መልሶ እንዲገነባ በማድረጋቸው ቅዱስ ሲኖዶስ ምስጋናውን ያቀርባል፡፡

በይዞታዎቻችንም ላይ ደረጃውን የጠበቀ ግንባታ ለማካሄድ የገቢ አሰባሳቢ ኮሚቴ ተሰይሞ ገቢ የማሰባሰብ ሥራው በሕጋዊ መንገድ እንዲከናወን ቅዱስ ሲኖዶስ መመሪያ ሰጥቷል፡፡

በመሆኑም በፈረሱት ቤቶች ምትክ የተረከብናቸውን ክፍት ቦታዎች በአጭር ጊዜ ማልማት ግዴታ ስለሆነ በዓለም ዙሪያ ያላችሁ ኦርቶዶክሳውያን የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን እንደ አባቶቻችሁ የታሪክ ባለቤቶች ትሆኑ ዘንድ ልማቱን በገንዘብና በእውቀት እንድታግዙ ቅዱስ ሲኖዶስ ጥሪውን ያቀርባል፡፡

5. በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት የተፈጠረውን የአስተዳደር ችግር አስመልክቶ በብፁዓን አባቶች የሚመራው አጣሪ ልዑክ ባቀረበው ሪፖርት መሠረት ውይይት በማድረግና የሥራ ኃላፊዎቹን በማንሣት ቅዱስ ሲኖዶስ አስተዳደራዊ ውሳኔዎችን አስተላልፏል፡፡
ወደፊትም በየደረጃው ያለውን ችግር ማስተካከል ይቻል ዘንድ ችግሩን እያጠና የሚያቀርብ ኮሚቴ እንዲቋቋም ምልአተ ጉባኤው ወስኗል፡፡

6. ዝክረ ኒቅያ በሚል መሪ ቃል ከመላው ሀገራችን በተወከሉ የምስክር ጉባኤ ቤቶች መምህራን በተካሄደው ጉባኤና የጥናት ውይይት የቀረበው ምክረ ሐሳብ እጅግ የሚጠቅም የሊቃውንት ድምጽ በመሆኑ፣በነገረ ማርያም፣ በነገረ ክርስቶስና በሌሎችም አስተምህሮዎች ዙሪያ የተሰጡት ሐሳቦች የቅዱሳት መጻሕፍት ትርጓሜን መሠረት በማድረግ ተብራርቶና ተስተካክሎ፣ የጎደለው ሞልቶ፣ የጠመመው ተቃንቶ በሊቃውንት ጉባኤ በኩል በመጽሐፍ መልክ እንዲታተም፣በሚዲያ ሊተላለፍ የሚገባው አስተምህሮ ደግሞ በሊቃውንት ጉባኤ ብቻ እንዲተላለፍ፣ የሊቃውንት ጉባኤውም በተሟላ የሰው ኃይልና በጀት ተጠናክሮ እንዲደራጅ፣ሀገር አቀፍ ጉባኤው በዓመት ሁለት ጊዜ እንዲደረግና የጉባኤው መዋቅር በየአህጉረ ስብከቱ እንዲጠናከር ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

7. የመናገሻ አምባ ማርያምና የጋራው ደብረ መድኃኒት መድኃኔዓለም አንድነት ገዳም ጥንታዊ የሆነ ሰፊ ታሪክ ያለው በመሆኑ ሁለቱ ገዳማት በአንድ አበምኔት በአንድነት ገዳም ሥርዓት በጋራ እንዲመሩ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፤

8. በቅድስት ሀገር ኢየሩሳሌም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ገዳማት መነኰሳትን ከመላክ ጀምሮ፣ በአስተዳደራዊና ቀኖናዊ አሠራር ክፍተት ምክንያት የተከሰቱ ችግሮችን በማረምና ሊቀ ጳጳሱን በማዛወር ማእከላዊ መዋቅር እንዲጠበቅ ቅዱስ ሲኖዶስ የወሰነ ሲሆን፣ነባሩ መተዳደሪያ ደንብ ተሻሽሎ እንዲቀርብ በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የሚመራ ኮሚቴ ሰይሟል፤

9. የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሕገ ልቡና፣በሕገ ኦሪትና በሕገ ወንጌል ያገኘቻቸው ዶግማዊ፣ ቀኖናዊና ትውፊታዊ ሀብቶቿ የሕግ ጥበቃና ከለላ አግኝተው ሃይማኖታዊ፣ታሪካዊና ሁለንተናዊ ይዘታቸውን ሳይለቁ ተከብረውና ተጠብቀው ለትውልድ እንዲተላለፉ ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡

10. የ2018 ዓ.ም የመደበኛ እና የካፒታል ዓመታዊ በጀት ብር 5,407,415,607.25/አምስት ቢሊየን አራት መቶ ሰባት ሚሊዮን አራት መቶ ዐሥራ አምስት ሺህ ስድስት መቶ ሰባት ብር ከሃያ አምስት ሣንቲም/እንዲሆንና የበጀት አርዕስቱ ተጠብቆ ሥራ ላይ እንዲውል ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

11. በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲ በመገንባት ላይ የሚገኘውን ሕንጻ በተመለከተ የተፈጠረው የአሠራር ግድፈት እንዲታረም፣ዩኒቨርስቲው ከባንክ ጋር የገባው የብድር ውል እንዲቋረጥና የተጀመረውን ሕንፃ በራሱ አቅም እንዲገነባ ሆኖ፤ የቤተ ክርስቲያናችንን አንጡራ ሀብት ማለትም ሕንጻዎችን፣ መሬቶችንና ሌሎች ቋሚ ንብረቶችን በማስያዝ የሚደረጉ ብድሮች ተፈጻሚ እንዳይሆኑ የሚያደርግ መመሪያ ለሁሉም አህጉረ ስብከት እንዲተላለፍ ቅዱስ ሲኖዶስ ወስኗል፡፡

12. የቤቶችና ሕንፃዎች አስተዳደር ልማት ድርጅትን አስመልክቶ በቀረበው ሪፖርት መሠረት የሥራ ክፍተቱን በማረም በየደረጃው ያሉ ኃላፊዎች እንደየጥፋታቸው እንዲጠየቁና እንዲታረሙ ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ሰጥቷል፡፡




መምህር አብዱላሂ አማን ይባላሉ የአርሲ / አቦምሳ/ ነዋሪ ሲሆኑ በ34ኛው ዙር የአድማስ ዲጂታል ሎተሪ የ1ኛው ዕጣ የ4 ሚሊየን ብር / አራት ሚሊየን ብር / ዕድለኛ ሆነዋል ፡፡

መምህር አብዱላሂ ባለትዳርና የአራት ልጆች አባት ሲሆኑ በደረሳቸውም ገንዘብ ቤት እንደሚሰሩበት ገልፀዋል ፡፡


የቀድሞ ፕሬዝዳንት መንግሥቱ ኃ/ማርያም በሥልጣን ዘመናቸው የመሠረተ ትምህርት ዘመቻን ተግባራዊ ለማድረግ ላበረከቱት አስተዋፅዖ Ethiopian society partnership የተባለ ድርጅት ዕውቅና ሰጥቷቸዋል። ሽልማቱን ሐራሬ ዚምባብዌ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ተገኝቼ አስረክቤያቸዋለሁ።

በዚሁ ጊዜ ባደረጉት ንግግር ''መሃይምነትን ከሃገራችን ለማጥፋት የተደረገው ጥረት እሳቸው ወደ ሥልጣን ከመምጣታቸው በፊት በንጉሡ ዘመን ''የፊደል ሠራዊት''በሚል ለጎልማሶች ትምህር ይሰጥ እንደነበረ አስታውሰው የመሠረተ ትምህርት ዘመቻ በተጀመረ ጊዜ በመላው አገሪቱ በርካታ ሰዎች ተሠማርተው በሠሩት ሥራ አመርቂ ውጤት የተገኘበት መሆኑን ገልፀዋል።

"ሽልማቱ የኔ ብቻ ሳይሆን በወቅቱ የነበሩ አብዮታውያን ጓዶች፣ተማሪዎች፣ አስተማሪዎች፣ በጎ ፈቃደኞችና መላው ኅብረተሰብ በንቃት የተሳተፈበት ስለሆነ የነሱም ነውና ክብርና ምስጋናውን እነሱም ይውሰዱ'' ብለዋል። አያይዘውም ''በዚያን ጊዜ ይህ መሃይምነትን ለማጥፋት የሠራውን መልካም ሥራ አስታውሰው ዕውቅና ለሰጡት ሁሉ ከፍ ያለ ምስጋናዬን አቀርባለሁ ''ብለዋል።

በዚሁ ሥነ ሥርዓት ላይ የተገኘችው ልጃቸው ዶክተር ትዕግሥት መንግሥቱ ''ለትምህርት ያለህ ጥማትና ፍላጎት ያኔ ገና በወጣትነትህ የተገለጠው የመጀመሪያ ልጅህን ''ትምህርት'' ብለህ ስትሰይማት ነው። ''መማር መማር አሁንም መማር'' የሚለው መፈክር የሁላችንም ትዝታ ነው። ትምህርት ለሁሉም እንዲዳረስ ያደግኸውን ጥረት በዚያ ተጠቃሚ የነበሩት ብቻ ሳይሆኑ ከመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር እኛም ቤተሰቦችህ እናደንቃለን ''ብላለች።

ዘገባው የገነት አየለ ነው።


ስለ ግንቦት 20 በዓል

ነሐሴ 2016 ዓ/ም የሕዝብ በዓላት እና የበዓላት አከባበር ለመወሰን በወጣው አዋጅ ቁ. 1334/2016 አንቀጽ 4 እና 5 ግንቦት 20 ታስበውም ሆነ ተከብረው በሚውሉ ብሔራዊ በዓላት ዝርዝር ውስጥ አልተካተተም።

በአዋጁ አንቀጽ 19(2) “ከዚህ አዋጅ ጋር የሚቃረን ማንኛውም አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ ወይም ልማዳዊ አሠራር በዚህ አዋጅ በተሸፈኑ ጉዳዮች ላይ ተፈፃሚነት አይኖረውም” በሚል ተደንግጓል።

ይህም ሲከበር የነበረው ግንቦት 20 እንደሚቀር ያመላክታል።

ስለሆነም ግንቦት 20 ካላንደር አይዘጋም።

ሳሙኤልግርማ
የሕግ አማካሪና ጠበቃ


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ቅዱስ ገብርኤል የልባችሁን መልካም መሻት ይሙላላችሁ!!!

ቪዲዮውን ያድምጡት👇

Показано 20 последних публикаций.