ዶ/ር ምህረት ደበበ እና ዶ/ር እዮብ ማሞ


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Блоги


👉የዶ/ር ምህረት ደበበ ፣ የዶ/ር እዮብ ማሞ እና የሌሎችም ፦፦፦፦፦፦፦፦
📖አነቃቂና አስተማሪ የሆኑ ወጎች
👉ስለ አመራር
👉አመለካከት(እይታ)
👉mindset
👉ስለ እድገት.......በስፋት እንዳስሳለን
📚 መፅሐፍት pdf
🎙የመፅሐፍ ትረካ
📖 አስተማሪ የሆኑ ፅሁፎች
👉👉👉contact us @Ay_ayche
@Fbg64

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Блоги
Статистика
Фильтр публикаций


ከሰራተኝነት ወደ አምራችነት!

ቀኑን ሙሉ በስራ ሲባክኑ መዋልና ምርታማነት ሁለት የተለያዩ ነገሮች ናቸው፡፡ አንዳንድ ሰዎች ቀኑን ሙሉ ወዲህና ወዲያ ስላሉ ብቻ ስኬታማ የሆኑ ይመስላቸዋል፡፡ ነገር ግን ቀኑን ሙሉ ስራ መስራት ማለት ውጤታማና ምርታማ መሆን ማለት አይደለም፡፡

ለምሳሌ፣ በአንዳንድ መስሪያ ቤቶች ውስጥ ሰራተኞች ብዙ ናቸው፣ አምራቾች ግን ጥቂት ናቸው፡፡ በግል ሕይወታችንም ቢሆን ተመሳሳይ ሁኔታ ሊከሰት ይችላል፡፡ ከጠዋት እስከማታ፣ ሳምንቱን ሙሉ ስነባክንና ስንሯሯጥ ውለንና ከርመን መጨረሻ ላይ ያመረትነው (ያከናወንነው) ነገር ከሌለ ጊዜያችንን በከንቱ አባክነናል፡፡

በጣም እየሰራን ወራትና አመታት አስቆጥረን ብዙም ለውጥ ካላየን ምናልባት ምክንያቱ የምንሰራው ስራ ምርታማ የመሆኑን ጉዳይ ስላላሰብንበት ይሆናል፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ በሚገባ ማሰብ ማለት ሁሉን ነገር ከዋናው ዓላማችንና ከግባችን አንጻር መቃኘት ማለት ነው፡፡

ከሰራተኝነት ወደ አምራችነት ለመዘዋወር አንዱ መንገድ በየቀኑ የምንሰራቸውን ስራዎች ቅደም ተከተል ማውጣት ነው፡፡ ይህንን ተግባር ለምንድን ነው የምተገብረው? ሌላ ሊቀድም የሚገባው ስራ ይኖር ይሆን? እዚህ ቦታ ዛሬ የምሄደው ለምንድነው? ሌላ ቀን ብሄድ ምን ችግር አለበት? ይህ የማደርገው ነገር ማከናወን ከምፈልገው ከዋናው አላማዬ ጋር ምን ግንኙነት አለው? . . .  እና የመሳሰሉትን ጥያቄዎች መጠየቅ እጅግ ወሳኝ ጉዳይ ነው፡፡

ሰራተኝነት ማለት የተገኘውንና ፊታችን የመጣውን ነገር ሁሉ ሲሰሩ መዋል ማለት ነው፣ አምራችነት ማለት ከአላማ አንጻር መስራት ማለት ነው፡፡ ሰራተኝነት ቢዚ ያደርገናል፣ አምራችነት ውጤታማ ያደርገናል፡፡ ሰራተኛ ሆነን አምራች ላንሆን እንችላለን፣ አምራች ሆነን ግን ሰራተኛ ላለመሆን አንችልም፡፡

ብዙ አጠናለሁ (ስራ) ውጤቴ (ምርት) ግን ጥሩ አይደለም . . . ብዙ አይነት ተግባሮች አከናውናለሁ (ስራ)፣ ነገር ግን የገቢዬ ምንጭ (ምርት) ግን አይጨምርም . . . ይኸው ብዙ ስደክም (ስራ) አመታት ሆነኝ፣ ሕይወቴ ግን ምንም ለውጥ የለውም (ምርት) . . . ብዙ ጓደኞች አሉኝ (ስራ)፣ ነገር ግን ከማንም ጋር የጠለቀና ውጤታማ ወዳጅነት እንደለኝ አይሰማኝም (ምርት) . . . ፡፡

ከላይ የተጠቀሱት አይነትና መሰል ስሜቶች ካሉብህ በሁኔታው በሚገባ አስብበት፡፡ ከሰራህ አይቀር ለምርታማነት ስራ፡፡ ከሮጥክ አይቀር ለማሸነፍ ሩጥ፡፡ ከለፋህ አይቀር ውጤት ለማግኘጥት ልፋ፡፡

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


#ትልቅ_ስለ_ማሰብ_ምርጥ_አባባሎች

"ትንሽ ካሰብክ አለምህ ትንሽ ትሆናለች። ትልቅ ካሰብክ አለምህ ትልቅ ትሆናለች።"
#ፓውሎ_ኮሎሆ

“ትንንሽ ግቦችን አስብ እና ትንሽ ውጤት ጠብቅ፤ ትልቅ ግቦችን አስብ እና ትልቅ ስኬትን አሸንፍ።
#ዴቪድ_ጄ_ሽዋርትዝ

“ለጨረቃ አልም፤ ብታጣ እንኳን ከከዋክብት መሀል ታገኛለህ።
#ኖርማን_ቪንሰንት_ፒል

"ነገሮችን እንደ ሁኔታው ሳይሆን ሊሆን እስከሚችለው ድረስ ተመልከት። በዓይነ ሕሊናህ መሳል ሁሉም ነገር ላይ እሴት ይጨምራል። አንድ ትልቅ አሳቢ ሁልጊዜ ወደፊት ሊደረግ የሚችለውን በዓይነ ሕሊናው ይመለከታል እንጂ በአሁን አይዋጥም።
#ዴቪድ_ጄ_ሽዋርትዝ

"ስኬታማ ለመሆን ትልቅ ስራ መስራት፣ ትልቅ ማሰብ እና ትልቅ ማውራት አለብህ።"
#አርስቶትል_ኦናሲስ

“ተራሮችን ማንቀሳቀስ እንደሚችሉ የሚያምኑ፣ ያደርጉታል። እንደማይችሉ የሚያምኑ ሊያደርጉት አይችሉም።
#ዴቪድ_ጄ_ሽዋርትዝ

"ማሰብህ እስካልቀረ ድረስ ትልቅ አስብ።"
#ዶናልድ_ትራምፕ

"የሰው አእምሮ ምንም ይሁን ምን፣ ሊፀነስ እና ሊያምን የሚችለውን፣ ሊያሳካው ይችላል"
#ናፖሊዮን_ሂል

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


#ምን_ላይ_ነህ?

አንድ አስገራሚ እና እውነተኛ ታሪክ ላጫውትህ...

ቫዮሊን ተጫዋቹ፤ ኒውዮርክ በሚገኝ የባቡር ጣብያ ውስጥ ለአርባ አምስት ደቂቃዎች ያህል ቫዮሊን ተጫወተ። ከአጠገቡ ሙዚቃውን የወደዱ ሰዎች ገንዘብ እንዲለግሱት፤ ወደ ላይ አፉን የከፈተ ሳጥን አስቀምጧል።

በነዚያም አርባ አምስት ደቂቃዎች አንድ ሰው ብቻ ቆሞ አጨበጨበለት፤ ሃያ ዶላር ያህልም መሰብሰብ ቻለ።

በነጋታው ምሽት ላይ ይኸው ቫዮሊን ተጫዋች በእጅጉ በታወቀ እና መግቢያው ለአንድ ሰው  መቶ ዶላር በሆነበት... ሺዎች በታደሙበት ግዙፍ  አዳራሽ ውስጥ ተመሳሳይ ሙዚቃ አቀረበ... ቫዮሊኑን ዳግም ተጫወተ። የማያባራ ጭብጨባንም ተቀበለ።

ይህ ታሪክ አንድ እውነታ ያሳየናል - እኛ ማብራት እና መታየት በማንችል ስፍራ ላይ ስንሆን ዋጋችን እናጣለን። በእርያዎች መሃል ያለ እንቁ ከድንጋይነት የተረፈ ዋጋ የለውም።

ብዙ አቅም ያላቸው ሰዎች በማይገባቸው ቦታ ሆነው፤ ክብርን አጥተዋል። ሆኖም ግን ይህንን ሲረዱና ያሉበትን የቆሸሸ ስፍራ ለቀው ሲወጡ፤ ማደግም መፍካትም ይጀምራሉ። ያኔም ልከኛ ዋጋቸውን ያገኛሉ።

በማይገባህ ስፍራ ስትገኝ ሰዎች ረግጠውህ ያልፋሉ፤ አንተ ለእነርሱ ልዩ አይደለህምና።  እናም እባክህን መገኘት ያለብህ ቦታ መገኘትህን እርግጠኛ ሁን!

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


በጣሙን የምናከብራችሁ ተከታታዮቻችን እንኳን ለ2016 ዓ/ም በሰላም አደረሳችሁ!

ባለፈው አመት በነበሩን 365 ቀናት በሕይወታችሁ ላይ መልካምን ዘር እንድንዘራ ስለፈቀዳችሁልን ምስጋናችን ታላቅ ነው፡፡

በዛሬዋ የአመቱ የመጀመሪያ ቀን ከዚህ በታች ያሉትን ሊንኮቼን ለሌሎች (share በማድረግ) እንድታጋሩ ላሳስባችሁ፡፡

@Ab_book
@Ab_book
@Ab_book

መልካም አዲስ አመት!!!


ሰዉ አባቱ የነገረዉ ነገር ሁሉ እዉነት መሆኑን በተረዳበት እድሜ ላይ እዉነት እንደሌለ የሚያስብ ልጅ ይኖረዋል፡፡~ቻርልስ ዋድስዎርዝ~

በማሸነፍና በመሸነፍ መካከል ያለዉ ልዩነት ተስፋ አለመቁረጥ ነዉ፡፡~ዋልት ዲስኒ~

አንድ ሰዉ ተሳካለት የምለዉ አንዴ በወጣዉ ከፍታ ሳይሆን ህይወቱ ሲዘቅጥ እንደገና ተስፈንጥሮ በወጣዉ ርዝመት ልክ ነዉ ~ጀኔራል ጆርጅ ኤስ ፓቶን~

ስኬታማነት ምንም ሚስጥር የለዉም፤ስኬት የዝግጁነት፣ጠንክሮ የመስራትና ከስህተቶችህ ትምህርት የወሰድክበት ዉጤት ነዉ ~ኮሊን ፓዉል~

በቢዝነስ ላይ የተመሰረተ ጓደኝነት በጓደኝነት ላይ ከተመሰረተ ቢዝነስ ይሻላል ~ጆን ዲ ሮክፌለር~

ዉድቀት ማለት በቀላሉ ሲገለፅ አንድን ነገር እንደገና መጀመር ነዉ ግን አሁን በብዙ ብልሀት መጓዝ ያስፈልጋል፡፡ ~ሄነሪ ፎርድ~

ሰዉ ስህተቱን ሊያምን ከስህተቶቹ ሊማርና ስህተቶቹን ለማስተካከል ቆራጥ ሊሆን ይገባዋል፡፡ ~ጆን ሲ.ማክስዌል~

ጨለማዉን እወደዋለሁ፤ባይመሽ ኖሮ ኮከቦቹን መቼም አላያቸዉም ነበር፡፡ ~ስቴፈኒ ሜየር~

የስኬት ቁልፉ ምን እንደሆነ አላዉቅም የዉድቀት ቁልፉ ግን ሁሉንም ሰዉ ለማስደሰት መሞከር ነዉ፡፡ ~ቢል ኮዝቢ~

ዉድቀት የመጨረሻ አይደለም ለመለመጥ አለመቻል ግን የሰዉ መጨረሻ ሊሆን ይችላል ~ጆን ዉድን~

ስኬትን ለማግኘት እሰራለሁ እንጂ አልሜዉ አላዉቅም ~ኢስቴ ላዉደር~

ተስፋ መቁረጥ የዉድቀት ብቸኛዉ መንገድ ነዉ ~ጌና ሾዉአልተር~

ሊሆን በሚችለዉ አደጋ ላይ ካተኮርክ ሃሳብህ ዉስጥ ይባዙና ፓራላይዝ ያረጉሃል..ይልቅስ ማድረግ ስላለብህ ነገር ብቻ አስብ ~ቤሪ ኢስለር~

ለመስራት እየሞከርኩ ያለሁት እንደተለመደዉ አሰራር አይደለም…የኔ ምርጫ ፈፅሞ ባልተሰራበት መንገድ መስራት ነዉ፡፡ ~ሚካኤል ትሬኖር~

ስኬታማ ሰዉ ማለት ሌሎች ሰዎች የወረወሩበትን ድንጋይ አንስቶ ፅኑ መሰረት የሚመሰርት ሰዉ ነዉ፡፡ ~ዴቪድ ብሪንክሌይ~

በዚህ ህይወት የሚያስፈልግህ ነገር ቢኖር የሰዉን ወሬ ንቆ መተዉና በራስ መተማመን ነዉ፤ከዛማ ያለምንም ጥርጥር ስኬት ይከተልሃል ~ማርክ ትዌይን~

እዉነትን የሚናገሩ ተከታዮችና ተከታዩቻቸዉን የሚያዳምጡ መሪዎች ጠንካራና የማይሸነፍ ማንነትን ይፈጥራሉ ~ዋረን ቤኒስ~

ከስኬት አንዱ ገፅታ ዉስጥ ተስፋ ሳይቆርጡ ከዉድቀት ወደ ዉድቀት መራመድ ነዉ፡፡ ~ዊንስተን ቸርችል~

አስር ሺህ አይነት የማያዋጡ መንገዶችን ሞከርኩ እንጂ አልወደቅኩም ~ቶማስ አልቫ ኤዲሰን~

የሰዉ ልጅ ትክክለኛዉ መመዘኛ መልካም ነገር አድርጎለት የማያዉቀዉን ሰዉ የሚይዝበት መንገድ ነዉ ~ሳሙኤል ጆንሰን~

የስኬት ግብህ ለሌላ ጊዜ ተዘዋወረ እንጂ አልወደቅክም ~ዴይሊ ኮትስ~

አንዳንዴ ‹ደህና ነኝ› ስል የሆነ ሰዉ አተኩሮ አይቶኝ ‹ባክህ እዉነቱን ተናገር› እንዲለኝ እፈልጋለሁ፡፡ ~ሳድ ኮትስ~

ሁሉም ሰዉ በመጨረሻ ‹እንደዚህ አይነት ሰዉማ በጭራሽ አልሆንም› ብሎ የተፀየፈበትን ማንነት ይሆናል ~ሳድ ኮትስ~

የስኬት መሰረት ከሆኑት ዉስጥ ያሰብከዉን ያለምንም ማወላወል መፈፀም ነዉ፡፡ ~ፓብሎ ፒካሶ~

በልብህ መርሳት የሌለብህ ነገር ቢኖር ስኬትም ይሁን ዉድቀት የዘላለም አይደሉም ~ሮገር ዋርድ~

ስኬት 99 ፐርሰንቱ ዉድቀት ነዉ ~ሶሂቺሮ ሆንዳ~

ጠላቶችህ ዉድቀትህን ለሰዉ ያዉጃሉ ስኬትህን ግን ይንሾካሾኩታል ~ቲፕስ 21~

ስኬት ለብቻዉ ያቅፍሃል ዉድቀት ግን በህዝብ ፊት ያጨበጭብልሃል ~ፖሊቮር~

ዉድቀት ለስኬት የምትከፍልለት የቤት ኪራይ ነዉ፡፡ ~ዋልተር ብሩኔል~

ስኬት ወደአእምሮህ፤ ዉድቀት ደግሞ ወደልብህ እንዲገቡ አትፍቀድላቸዉ፡፡ ~ዊል ስሚዝ~

እንድወደድ ሳይሆን እንድከበር እፈልጋለሁ፡፡ ~ጃክ ማ~

የዉድቀት መርከብ በይቅርታ ባህር ላይ ትንሳፈፋለች ~ኢሜጅስ በዲ~

ችግሮች እንደሚኖሩ እወቅ..ከዛ ችግሮችህን ቁርስ አድርጋቸዉ ~አልፍሬድ ኤ ሞንታፔርት~

ሰአትህን አትመልከት ይልቅስ ጊዜ የሚሰራዉን ስራ…ጉዞህን ቀጥል! ~ሳም ሌቨንሰን~

ስኬት ይማራል ዉድቀት ግን ያማርራል! ~ዶርቶካርኔይ~

ጨረቃ ላይ አልም..ጨረቃን ብትስት እንኳ ኮከቦቹን ታገኛለህ ~ደብሊዉ ክሌመንት ስቶን~

ህይወትህን ዛሬ ቀይር..ነገ በሚመጣዉ ነገር ቁማር አትጫወት…ያለምንም መዘግየት አሁኑኑ ተንቀሳቀስ! ~ሲሞን ዲ ቢቮዉር~

የስኬት መንገድ አንድ ብቻ ነዉ፤እሱም የህይወትህን አቅጣጫ በራስህ መምራት! ~ክርስቶፈር ሞርሌ~

ችግሮችህን አትፋለማቸዉ ነገር ግን ወስንባቸዉ! ~ጆርጅ ቺ ማርሻል~

‹ጥሩ ሰርተሃል› ከ ‹ጥሩ ተናግረሃል› ይሻላል ~ቤንጃሚን ፍራንክሊን~

ስኬት በተቀረፅክበት ማንነት ልክ የምታገኘዉ ነገር ነዉ ~ጂም ሮን~

የምናስበዉን ነገር እንሆናለን ~አርል ናይትንጌል~

ኮርጀህ ከሚሳካልህ በራስህ ሰርተህ ብትወድቅ ይሻላል ~ኸርማን ሜልቪሌ~

የስኬት ሚስጥሩ ማንም ሰዉ ያላወቀዉን ነገር መገንዘብ ነዉ ~አርስቶትል~

ትግስት ማጣት ስኬትን አዞት አያዉቅም ~ኤድዊን ቻፕሊን~

ወደፊት የሚያስኬድ መንገድ ይሁን እንጂ የትም እሄዳለሁ ~ዴቪድ ሊቪንግስተን~

ቁስሎችህን ወደ ጥበብ ቀይራቸዉ ~ኦፕራ ዊንፍሬይ~

የስኬትን መክፈቻ ቁልፍ ማግኘት ካቃተህ መዝጊያዉን አንሳ፡፡ ~ያልታወቀ ሰዉ~

ዉድቀት የስኬት ተቃራኒ አይደለም፡ዉድቀት የስኬት አካል ነዉ፡፡ ~ዴይሊ ኮትስ~

ህይወት ተፅእኖ የማምጣት ጉዞ እንጂ ገቢ የማስገባት ሩጫ አይደለም ~ኬቨን ክሩስ~

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


የስኬታማዎችና የስኬተ-ቢሶች ልዩነት

በአንድ ዘርፍ አቅጣጫ ስኬታማ ሰዎች ስኬታማ ከሆኑበት ምክንያቶች አንዱ ስኬተ-ቢሶቹ አንዳንድ ጊዜ የሚያደርጉትን ነገር እነሱ ሁልጊዜ በማድረጋቸው ምክንያት ነው፡፡ እኔና አንተ አንዳንድ ጊዜ እንሮጥ ይሆናል፣ ይህ የአንዳንድ ጊዜ ሩጫችን ግን በሩጫ ውድድር ስኬታማ አያደርገንም፡፡ እነዛኞቹ ግን በየቀኑ በመሮጣቸው ምክንያት በሩጫው መስክ ወደስኬታማነት አልፈው ይሄዳሉ፡፡

አንዳንደ ጊዜ በሚያነቡትና ዘወት በሚያነቡት ሰዎች መካከል፣ አንዳንድ ጊዜ በሚሞክሩትና ዘወትር አዳዲስ ነገር ከመሞከር በማያርፉት መካከል፣ አንዳንድ ጊዜ ለጤንነታቸው በሚጠነቀቁትና ዘወትር በሚጠነቀቁት መካከል፣ ከፍቅረኛቸው ጋር አንዳንድ ጊዜ በሚወያዩትና ውይይወትን የዘወትር ልምምዳቸው ባደረጉ ሰዎች መካከል . . . ያለው ልዩነት አንዳንድ ጊዜ ከማድረግ የሚመጣ ደካማ ውጤትና ዘወትር ከማድረግ የሚመጣ ብርቱ ውጤት ነው፡፡

ስኬታማ ለመሆን የመትፈልግበትን የሕይወትህን መስክ በሚገባ አጢነውና ተግባሮችህን ምን ያህል እየደጋገምካቸው እንደምታደርጋቸው አስበው፡፡ ሳትሰለች በምትደጋግማቸው ነገሮች ላይ ስኬታማ ነህ ወይም ስኬታማ መሆንህ አይቀርም፡፡ አንዳንድ ጊዜ በምታደርጋቸው ነገሮች ላይ ደግሞ ስኬተ-ቢስ ሆነህና ዘወትር፣ “ለምን?” እያልክ እንደጠየክ ትኖራህ፡፡ 

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


በራስህ ላይ ያለህ አመለካከት የምትጋፈጠውን ነገር ይወስናል

ድመት እንደሆንክ እያሰብክ አንበሳ የሚጋፈጠውን ትልቅ አውሬ መጋፈጥ አትችልም፡፡ ዶሮ እንደሆንክ እያሰብክ ንስር የሚጋፈጠውን ከፍታ መጋፈጥ አትችልም፡፡ ትንሽ እንደሆንክ እያስብክ ትልቅ መሆናቸውን አምነው የተቀበሉ ሰዎች የሚጋፈጡትን ነገር መጋፈጥ አትችልም፡፡

ምንም ብትማርና ብታጠና እንደማታውቅ እያሰብከ ታላላቅ የእውቀት መስኮችን መጋፈጥ አትችልም፡፡ ምንም ብትሰራ እንደማትበለጽግ እያሰብክ ወደብልጽግና የሚወስዱ ከባባድ መንገዶችን መጋፈጥ አትችልም፡፡ አቅመ-ቢስ እንደሆንከ እያሰብክ አቅም የሚጠይቁ ነገሮችን መጋፈጥ አትችልም፡፡

በራስህ ላይ ያለህን አመለካከት ሚዛናዊ በሆነ መልኩ ስታስተካክልና በሆንከው ልክ ማሰብ ስትጀምር ለአውነተኛ ማንነትህና አቅምህ የሚመጥኑ ነገሮችን መጋፈጥ ትጀምራለህ፡፡

በዚህ ምድር ላይ ንስር ሆኖ ተወልዶ ዶሮ ሆኖ እንደመኖርና እንደማለፍ አሳዛኝ ነገር የለም፡፡

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


የብቃትህና የእድገትህ ግንኙነት

ብቃትህ አሁን ካለህበት ስፍራ ልቆ እስካልተገኘ ድረስ የሚቀጥለው እድገትህ አይመጣም፡፡ ሕይወት በአንድ ቦታ ብዙ ጊዜ ስለከረምክ ብቻ እድገትን የምትሰጥህ ከመሰለህ ተሳስተሃል፡፡ ይህ አይነት አመለካከት ያላቸው ሰዎች በአንድ የስራ መስክ ወይም ቦታ የተወሰኑ አመታት ስለቆዩ ብቻ የሚቀጥለው የስራ እርከን ወይም የገንዘብ ጭማሪ እንዲሰጣቸው ይጠብቃሉ፡፡

ይህ የተዛባ አመለካከት አመታቶቻችንን የሚበላ፣ ሙዳችንን የሚያዛባና ሁኔታችንን እኛ ማድረግ ከሚገባን ሃላፊነታችን አንጻር ሳይሆን ሌሎች ሰዎች አደረጉብን ወይም አደረጉልን ብለን ከምናስበው አንጻር እንድንመለከተው አጋልጦ ይሰጠኛል፡፡

አንድ ቦታ ስለከራረሙ ብቻ እድገትን የሚጠብቁ ሰዎች የጠበቁትን ደረጃ ካላገኙ ለምን ያንን እንዳላገኙ ራሳቸውን በመጠየቅ መልሱን ከማግኘት ይልቅ በመነጫነጭ፣ በማመጽ፣ ስም በማጥፋት፣ የሚወቀስን ሰው በመፈለግ፣ ሌሎቹን ጥሎ ለመነሳት በመሞከር፣ ሌሎችን አስወጥቶ ለመግባት በመጣጣርና በመሳሰሉት አሉታዊ ኃይሎች የፈለጉትን ለማግኘት ይታገላሉ፡፡

እውነታው አጭርና ግልጽ ነው፡- የሚቀጥለውን የኑሮ መሻሻል፣ የእርከን፣ የክፍያና የመሳሰሉትን እድገቶች ከማግኘትህ በፊት በመጀመሪያ ማደግ ያለብህ አንተው ነህ፡፡ የተሰማራህበትን መስክ አልፎ የሄደ ብቃትን እስከምታዳብር ድረስ የሚቀጥለው እድገት አይመጣምና በመጠበቅ ጊዜህን አታባክን፤ ለማግኘት ደግሞ አትታገል፡፡

የብቃትህ ልህቀት ወደላይ ሲወጣ፣ የሕይወት እድገት ደረጃህም ከዚያው ጋር ወደላይ ይወጣል፡፡ ሌሎች ሰዎች የማይገባቸውንና ብቃታቸው የማይፈቅደውን ለማግኘት ሲታገሉ አንተ የሚገባህንና ብቃትህ የሚፈቅደውን ለማግኘት ራስህን በማዘጋጀት አሳድግ፡፡

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


የትኩረት መዛባት
ከእቅድህ ክልል ውጪ በሆነው ነገር ላይ ትኩረትህን በመጣል ዘመንህን አታቃጥል፡፡ በየእለቱ የምታሰላስለው፣ የምታየው፣ የምትመኘውና ስሜትህንና ጊዜህን የምታሳልፈበትን ነገር አስበው፡፡ ይህ ነገር በወደፊት እቅድህና ዓላማህ ውስጥ የተካተተ ነገር ካልሆነ ወይም ከዚያ ጋር ግንኙነት ከሌለው የትኩረት መዛባት ውስጥ ነው ያለኸው፡፡

ወደ አንድ አቅጣጫ ለመድረስ ዓላማን ይዞ ወደፊት የሚሄድ ሰው የትኩረቱ ቅኝትና የስሜቱ ግለት በዚያው አቅጣጫ ሊሆን ይገባዋል፡፡ የሚገሰግሰው ወደፊት፣ የሚያየውና የሚመኘው ግን የጎንዮሽ ወይም ወደኋላ ከሆነ የትኩረት መዛባት አለ፡፡

ከእቅድህና ከዓላማህ ውጪ ስለሆነ የሕይወት ዘይቤ ሲያወጡና ሲያወርዱ መዋል . . . ልታገኛቸው የማትችላቸውንና በሕይወትህ ምንም መዋጮ ሊያደርጉ ስለማይችሉ ሰዎች ሁኔታ ሲደመሙ ውሎ ማደር . . . ካለህ ወቅታዊ እውነታም ሆነ ከወደፊት እቅድ ጋር በፍጹም ሊጣጣምና ሊዋሃድ በማይችል አለም ውስጥ በሃሳብ ሲዋዥቁ መኖር . . . የተዛባ ትኩረት!

ዓላማህን ለይተህ እወቅ . . . እውነታህን ተቀበል . . . ትኩረትህን በዚያ ላይ ሰብስብ . . . ሃሳብህን፣ ምኞትህን፣ ስሜትህንና ያለህን አቅም ሁሉ በዚያ ላይ አውለው! የሆንከውን፣ ያለህን ነገርና ሁለንተናህን አስተባብረህ ወደፊት በመገስገስና እደርስበታለሁ ብለህ በማመን ባላቀደከው ነገር ላይ አይንህንና ሃሳብህን በመትከል ጊዜህን አታባክን፡፡

የትኛው ንስር ነው ከፍታው ላይ መብረሩንና መናጠቁን ትቶ የሜዳ እንስሶችን ሩጫ ሲመኝ የሚውለው? የትኛው አንበሳ ነው ደኑን እየገዛና እያደነ ከመኖር ይልቅ በውሃ ዳር ሆኖ የአሳዎችን ዋና በማየትና በመመኘት ጊዜውን የሚያሳልፈው? . . .  እነዚህ ምሳሌዎቻችን የወደፊታቸው በሌለበት ነገር ላይ ጊዜያቸውን አያባክኑም፡፡ ትኩረትህን ወደ ማንነትህና ወደነገው ዓላማህ መልስ!

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


አንተም ሰው እርሱም ሰው!

• ሰው ከሰበረው፣ አንተ መጠገን ትችላለህ!
• ሰው ከጣለው፣ አንተ ማንሳት ትችላለህ!
• ሰው ከቆለፈው፣ አንተ መክፈት ትችላለህ!
• ሰው ከደበቀው፣ አንተ ማግኘት ትችላለህ!
• ሰው ከተበተበው፣ አንተ መፍታት ትችላለህ!
• ሰው ካበላሸው፣ አንተ ማበጃጀት ትችላለህ!
• ሰው ከበተነው፣ አንተ መሰብሰብ ትችላለህ!
• ሰው ከጻፈው፣ አንተ ማንበብ ትችላለህ!
• ሰው ከደረሰበት፣ አንተም መድረስ ትችላለህ!

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


መሳሪያ የሌለው ፍልሚያ

የየትኛውንም ዘመን የአለም ታሪክ መለስ ብለህ አጥና ፍልሚያና ውጊያ ያልነበረበት ወቅት ለማግኘት ያስቸግርሃል፡፡ በተያያዘ ሁኔታ በአለም ላይ የተደረጉ ፍሚያዎችን አጥና ላለበት ፍልሚያ የሚመጥን መሳሪያ ያልነበረው ሕብረተሰብ ፍልሚያው የተሸነፈ ሕብረተሰብ ነው፡፡ ይህ እውነታ አለማችን ከበሽታ ጋር፣ ከድህነት ጋር፣ ከተፈጥሮ አደጋዎች ጋርም ሆነ ጤና-ቢስ ከሆኑ ሰዎች ጋር ባሳለፈችው ፍልሚያ ተግባራዊነት ያለው እውነታ ነው፡፡

በአሁን ሰዓት በሕይወትህ የምትፋለመው ፍልሚያ ከአቅምህ በላይ ሆነ እያሸነፈህ እንደሆነ ከተሰማህ ምናለባት ተገቢውን መሳሪያ በእጅህ አላስገባህም ብዬ እጠረጥራለሁ፡፡ ፍልሚያህ የስሜት ቀውስ ይሁን፣ የአካል ጤንነት መጉደል ይሁን፣ የኢኮኖሚ ትግል ይሁን፣ የሰዎች አጉል ባህሪይ ይሁን . . . ምንም ይሁን! ትክክለኛው መሳሪያ ካለህ ታሸነፈዋለህ፣ ከሌለህ ደግሞ ትሸነፋለህ፡፡

ፍልሚያህን አስመልክቶ ልትሰራቸው ከምትችላቸው ስህተቶች መካከል ዋና ዋናዎቹ፡- አንደኛው፣ የግልህን ፍልሚያህ ከሰዎች ጋር የማዛመድና ሰዎችን ስላጠቃህ የግል ፍልሚያህን እንደምታሸነፈው የማሰብ ዝንባሌ ሲሆን፣ ሌላኛው ደግሞ ለፍልሚያህ የማይመጥንን (የተሳሳተን) መሳሪያ የመጠቀም ዝንባሌ ናቸው፡፡

መጠየቅ ያለብህ ጥያቄዎች፡-

1) የምፋለመው ፍልሚያ ምንድን ነው?
2) ይህንን ፍልሚያ ለምንድን ነው ማሸነፍ ያቃተኝ?
3) ይህንን ፍልሚያ ለማሸነፍ የሚያስችለኝ ተገቢው የሆነው መሳሪያ ምንድን ነው?
4) ይህንን መሳሪያ እንዴት እጄ ማስገባት እችላለሁ?  

አብዛኛዎቹን ፍልሚያዎችህን የምታሸንፈው ራስህን ለመለወጥ በምታደርገው የተሳካ ትግል መሆኑን ግን አትርሳ፡፡

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


ምንም አይነት የትምህርት ደረጃ እና ልምድ የማያስፈልገው ሲሆን  ማንኛውም የስራ ፍላጎት ያለው ሰው ስለ ስራው አጭር ገለፃ(Presentation) በመውሰድ ወዲያው ሊሰሩ የሚችሉት እጅግ በጣም አዋጭ የፕሮሞሽን ስራ ሲሆን ሂወትን መቀየር የሚፈልግ ማንኛውም ሰው ሊሰራው የሚችል ትርፋማ ስራ ነው።
       -በየትኛውም የትምህርት ደረጃ ላይ ያላችሁ
       -በየትኛውም አከባቢ የምትኖሩ
       -ሌላ ስራ እየሰራችሁ ተጨማሪ ስራ ለምትፈልጉ
       -ከትምህርታችሁ ጋር ማስኬድ ስምትችሉ አብራችሁ መስራት ትችላላቹ።
መረጃውን ባስቀመጥንላቹ ስልክ ማግኘት ትችላላቹ!!

👉@Ay_ayche
👉+251941731143


አርምሞ .pdf
33.8Мб
📚ርዕስ:- አርምሞ
📝ደራሲ:- ዶክተር ኤልያስ ገብሩ አእምሮ
📜ዘውግ:- ልቦለድ 
📅ዓ. ም:- መስከረም 2014
📖የገፅ ብዛ:-250




የሆነልህን እንጂ የሆነብህን አትቁጠር

ሳታሸንፍ በፍጹም እዚህ አልደረስክም፡፡ አንተ የአሸናፊዎች ምሳሌ እንጂ በፍጹም የተሸናፊዎች ምልክት አይደለህም፡፡ የአየሩን መለዋወጥ፣ የኢኮኖሚውን ከፍና ዝቅ ማለት፣ ከሰዎች የሚሰነዘርብህን ደስ የማያሰኙ ሁኔታዎች … አልፈህ እዚህ ደርሰሃል፡፡ ከአሁን ወዲያ ደግሞ ከተሳሳትካቸው ነገሮች ትምህርትን፣ ከተሳኩልህ ጉዳዮች ደግሞ ድፍረትን በመያዝ ወደፊት የመሄድ ሃላፊነት አለብህ፡፡

ማታ እቤት ስትገባ በሰላም መግባትህን አስብ እንጂ ከኪስህ የጠፋውን ገንዘብ ወይም የሞባይል ቀፎ በማሰብ፣ ወይም በመንገድ ላይ ያበሳጨህን ሰው በማሰላሰል አእምሮህን አትሙላው፡፡ ውስጥህን  በይሆናልና በይቻላል መሙላት ከአንተ በፊት ያለፉ ሰዎችን አስደናቂ ፈለግ የመከተል አስገራሚ እርምጃ እንጂ  የቅዠት ምልክት አይደለም፡፡ የሆነልህን መልካም ነገር አእምሮህ ውስጥ ስፍራን ስጠውና በመኮትኮት አሳድገው፡፡ በተቃራኒው ደግሞ ጤና ቢሱን ሃሳብ ስፍራ በመንፈግ አስርበውና እንዲሞት አድርገው፡፡

“ከሃዘኖችህ ይልቅ ሃሴቶችህን፣ ከጠላቶችህ ይልቅ ደግሞ ወዳጆችህን ቁጠር” - Irish Proverb

ስለሚወዱህ ሰዎች ከማሰላሰልና ስለሚጠሉህ ሰዎች ከማሰብ የትኛው ጥሩ ስሜት ይሰጥሃል? የሚወዱህ ሰዎች የነገሩህን የፍቅርና የአክብሮት ቃል ከማሰብና የሚጠሉህ ሰዎች የነገሩህን ስሜትን የሚወጋ ቃል ከማሰላሰል የቱ ይሻልሃል? ምርጫው የአንተ ነው፡፡

ቁጭ ብለህ የማይቀበሉህ ሰዎች ማን ማን እንደሆኑ ከመቁጠር፣ የሚወዱህንና የሚቀበሉህን ሰዎች መቁጠር በስኬትህ ላይ ታላቅ ተጽእኖ አለው፡፡ ጨለማን በብርሃን አሸንፍ እንጂ በጨለማ አትሸነፍ፡፡

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


#ደስታ_የሚመጣው_ችግሮችን_በመፍታት_ነው

በሕይወት ውስጥ ሁልጊዜም ችግሮች አሉ፡፡

አንድ ነገር ለማድረግ ስትሞክር ሌሎች ችግሮች መፈጠራቸው አይቀርም። ለምሳሌ፣ የጤና ችግርህን ስፖርት በመስራት ልትፈታው ስትወስን ጂም በጊዜ ለመድረስ በጊዜ መነሳት፣ በጣም እንዲያልብህ በርትተህ መስራትና ወደ ስራ ስትገባ በመጥፎ ጠረን ቢሮውን እንዳትበክል የግድ መታጠብ ስለሚያስፈልግህ ሌላ አዳዲስ ችግሮች ትፈጥራለህ፡፡

ከሴት ጓደኛህ ጋር በቂ ጊዜ ያለማሳለፍ ችግርህን ለመቅረፍ ማክሰኞ ምሽትን ሁልጊዜ የምትገናኙበት ጊዜ አድርገህ ስትመርጥ ሁለታችሁም እንዳይሰለቻችሁ ለማድረግና አሪፍ ራት መብላት ስላለባችሁ በዚያ ቀን የግድ በቂ ገንዘብ የመፈለግ ችግር ትፈጥራለህ፡፡

ችግሮች ይለዋወጣሉ ወይም ይሻሻላሉ እንጂ አይቆሙም፡፡

ደስታ የሚመጣው ችግሮችን ከመፍታት ነው፡፡

በእዚህ አረፍተ ነገር ውስጥ ቁልፍ የሆነው ቃል “መፍታት” የሚለው ነው፡፡ ችግሮችንህ ችላ ካልክ ወይም ችግሮች እንደሌሉብህ የሚሰማህ ከሆነ፣ ራስህን በጣም አሳዛኝ እያደረግክ ነው፡፡

መፍታት የማትችለው ችግር እንዳለብህ የሚሰማህ ከሆነም አሁንም ራስህን በጣም አሳዛኝ እያደረግክ ነው፡፡ ምክንያቱም የደስታ ሚስጥራዊ ቅመም ያለው ችግሮችን መፍታት ላይ እንጂ ችግሮች የሌሉብህ መሆን ላይ አይደለም፡፡

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


የማንነትህ መለኪያ፡- አንዳንድ ሰዎች የማንነታቸውን ዋጋ ካለፈው ታሪካቸው፣ ከወቅቱ ኑሯቸው፣ ሰዎች በእነሱ ላይ ካላቸው አመለካከትና ከመሳሰሉት ሁኔታዎች በመነሳት ይወስኑታል፡፡ የማንነታችን ዋጋ ግን ሊጨምርም ሆነ ሊቀንስ የማይችል ጉዳይ ነው፡፡ በማንነቴ ዋጋና በተለጠፈብኝ ተመን መካከል ልዩነት ሲኖር የማንነት ቀውስ ያስከትላል፡፡ ይህ መጽሐፍ በጉዳዩ ላይ ጥልቅ ግንዛቤን ያስጨብጣል፡፡

ከመጽሐፉ የተቀነጨበ . . .

አንተንና ሁኔታህን አስመልክቶ ሁለት ጽኑ ምክሮች

በባህሪህ እንጂ በኑሮህ ደረጃ አትፈር

ሰው ሊያፍርበት ወይም ደግሞ ሊኮራበት የሚገባው ዋነኛ ነገር የባህሪው ሁኔታ እንጂ የኑሮው ደረጃ ሊሆን አይገባውም፡፡ የሰዎች የኑሮ ደረጃ የመበላለጡ ሁኔታ ሊካድ የማይቻል እውነታ ነው፡፡

አንዳንዱ ሰው በገንዘብ የበለጸገ ሲሆን ሌላው ደግሞ የገቢው ምንጭ አናሳ ነው፡፡ እንደ እውነቱ ከሆነ ግን፣ ከባለሃብቱም ሆነ ባለሃብት ካልሆነው ሕዝብ መካከል የባህሪይ ድኃም አለ፡፡

በአንጻሩ፣ ከባለሃብቱም ሆነ ባለሃብት ካልሆነው ሕዝብ መካከል የባህሪይ ባለጸጋ ደግሞ ይገኛል፡፡ ስለዚህም ሰው አንገቱን ሊያስደፋውም ሆነ ቀና ብሎ እንዲሄድ ሊያደርገው የሚገባው የባህሪው ጥራት ጉዳይ እንጂ የንብረቱ ብዛት ሊሆን አይገባውም፡፡ የድህነት ሁሉ ድህነት የባህሪይና የስነ-ምግባር ድህነት ነውና፡፡

ምንም ነገር ቋሚ እንዳልሆነ አትዘንጋ

ዛሬ በቁመናው የተመሰከረለት ሰው ብዙም ሳይቆይ የቁመናውን ጊዜአዊነት ወደማወቅ መምጣቱ አይቀርም፡፡ የትናንት ሃብታም የዛሬ ድኃ፣ የትናንት ድኃ ደግሞ የዛሬ ኃብታም ሲሆን እንዳየህ እርግጠኛ ነኝ፡፡ የዛሬ ዝነኛ ወይም ኃይለኛ ነገ ስሙም ላይነሳ ይችላል፡፡ ይህንን የማይለወጥ የሕይወት ሂደት ያልተገነዘበ ሰው አለኝ የሚለውን ነገር ሲያጣ ራሱንም አብሮ ያጣዋል፡፡ የማንነቱን ዋጋ የተመነበት ሁኔታ ሲጎድል፣ ማንነቱም የጎደለ ይመስለዋል፡፡

ሁሉም ነገር ሲለዋወጥ፣ ሲመጣና ሲሄድ፣ አብሮን የሚቆየውና ሁል ጊዜ የምናገኘው ራሳችንን ነው፡፡ ይህንን ማንነታችንን በጥሩ አመለካከትና ብሩህ በሆነ ራእይ በማገዝ ወደ ፊት ካልዘለቅን እንደ ሁኔታው የሚለዋወጥና የትም የማይደርስ ማንነት ይዘን እንቀራለን፡፡

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


#የዴል_ካርኒጌ_13_ምርጥ_አባባሎች   

👉እስካልተገበርከው እውቀትህ ሃይል ሊሆን አይችልም!

👉 ለአንድ ሰአት የሚኖርህ እቅድ ለአስር ሰአታት ከመስራት ድካም ያሳርፍሃል።

👉 ህይወት ማለት ስትወረውረው መልሶ እንደሚመጣ ናት። የሰራኸውን ብቻ ታገኛለህ።

👉 ተግባራዊ አለመሆን በውስጥህ ጥርጣሬ እና ፍርሃትን ይዘራል። ተግባራዊ መሆን ግን በውስጥህ ድፍረት እና በራስ-መተማመን እንዲኖር ያደርጋል።

👉 ለሆነ ሰው ያደረከውን መልካም ነገር መቼም አታስታውሰው። የሆነ ሰው ያደረገልህን መልካም ነገር ግን መቼም አትርሳ!

👉 ከሰዎች ጋር ጥሩ ተግባቦት ያለው መልካም ተናጋሪ መሆን ከፈለግክ፣ በመጀመሪያ ከልብ አዳማጭ ሁን። ተፈላጊ ለመሆን ከፈለግክም በሌሎች ላይ ፍላጎት ይደርብህ።

👉 ትምህርት ተግባራዊ የሚሆን ሂደት ነው። ነገሮችን በማድረግ ተማር። እንዲሁም እውቀት ሁሌም አእምሮህ ውስጥ የሚቀመጥ ስለሆነ፣ ማንም ሊሰርቅህ አይችልም።

👉 ለብልህ ሰው እያንዳንዷ ቀን አዲስ ህይወት ናት።

👉 ክርክርን ለማሸነፍ ብቸኛው መንገድ ከክርክር መራቅ ነው።

👉 እየሰራህ ያለኸውን ስራ የማትወደው ከሆነ መቼም ቢሆን ስኬትህ ላይ አትደርስም!

👉 እንደምታሳካው እመን እንጂ ይሳካልሃል!

👉 ደስታህ እንዲቀጥል ከፈለግክ ለሌሎች ማካፈል ይኖርብሃል።

👉 በዚህ ዘመን ያለው የሰው ልጅ ችግር አለማወቅ ሳይሆን ተግባራዊ ያለመሆን ነው!

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


ስህተትን የማረም ጥበብ 

ስህተትህን እመን
ለራስህ አንድን ቁምነገር እንድትሰራ ልሞግትህ፡፡ ምናልባት ከአንተ ጋር የከረመው የሕይወት ዘይቤ ከዚህ ተቃራኒው ቢሆንም እንኳን፣ ከዚህ በኋላ ግን ስህተት ስትሰራ በቀላሉ ስህተትን አምኖ የመቀበልን “ቀላልነት” ለማዳበር ተጣጣር፡፡

ይህ ቁምነገር የሚጠቅመው ለራስህው ነው፡፡ አንዳንድ ሰዎች ስህተታቸውን አምኖ መቀበል ለሌላው ሰው የሚጠቅም ነው የሚመስላቸው - ሌላ ትልቅ ስህተት! ስህተትህን በቀላሉ አምኖ የመቀበል ዝንባሌ፣ ከሁሉ በፊት ትክክለኛ እንደሆንክ ለማሳየት ከሚመጣ ትግልና ሸክም ነጻ ያወጣሃል፡፡

ሲቀጥልም፣ የእርማት እርምጃ የምትወስድበት ደረጃ ላይ ያስቀምጥሃል፡፡ በመጨረሻም፣ ሰዎች እንዲቀበሉህና እንዲገነዘቡህ መንገድን ይጠርግልሃል፡፡

የመሻሻያ እቅድን አውጣ
ማንኛውም ለውጥ በገጠመኝ አይመጣም፡፡ በተለይም ለውጥ ያስፈለገበት ሁኔታ ከአመለካከት ጋር የተገናኘ ሲሆን ሁኔታው እየከበደና የበለጠ ትኩረት እየፈለገ ይመጣል፡፡ በመነጋገር ላይ ያለነውን ስህተትን የመደጋገም ችግር ለመቅረፍ ልናስብባቸው የሚገቡን ነጥቦች አሉ፡፡

“ይህ ችግር እንዳለብኝ አምኜ ተቀብያለሁ?” “የችግሬ ምንጩ ምንድን ነው?” “ከዚህ ሁኔታ ለመውጣት ምን አይነት እርምጃ መውሰድ እችላለሁ?” “ከየትኛው መጀመር አለብኝ?” “ለውጥ እያመጣሁ መሆኑን ለማወቅ መመዘኛዎቼ ምንድን ናቸው?” እነዚህንና መሰል ጥያቄዎችን በመመለስ እቅድ የተሞላበት እርምጃ ውስጥ መግባት ይቻላል፡፡   

ዲሲፕሊንና ተጠያቂነትን አዳብር
አንድን ልማድ ለማዳበር የምንጀምረው ከዲሲፕሊን ነው፡፡ ፈጽሞ ማድረግ የማንችለውንና የማንፈልገውን ነገር ራሳችንን “በመቆንጠጥ” እና በማስገደድ ስናስጀምረው የዲሲፕሊንን መንገድ ጀምረናል ማለት ነው፡፡ በመቀጠልም ሁኔታው ብዙ ከመደጋገሙ የተነሳ ልማድ ሆኖ መሰረታዊ የባህሪይ ለውጥ ሲያመጣ ዲሲፕሊን ስራውን ሰርቷል ማለት ነው፡፡ በመጨረሻም አሮጌውን ዘይቤ ትተን አዲሱን በመተካት ማቆም እስከማንችል ድረስ ልማድ ሲሆን ዲሲፕሊን ስራውን ጨርሷል ማለት ነው፡፡

ምናልባት ይህንን ጉዞ ሙሉና ስኬታማ የሚያደርግልን አዲሱን ልማድ እስክናዳብር ድረስ በሃላፊነት የሚጠይቀንን ሰው ማግኘትና ለዚያ ሰው ፈቃዱን መስጠት ነው፡፡ 

መልካም ቀን፣ ያገሬ ሰዎች! እወዳችኋለሁ!

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book


የነጋችሁ የሚጀምረው ዛሬ ነው!

ለወጣቶች እና ለጎልማሶች!!!

የዛሬውን ሕይወታችሁን እጅ በእጅ ከምታገኙት ትርፍና ጥቅም አንጻር ብቻ መገምገም አቁሙና ለነገ ከምትዘሩት ዘር አንጻር መገምገም ጀምሩ፡፡ እስከዛሬ ከኖራችኋቸው አመታት ይልቅ በፈታችሁ ያሉት አመታት ብዙ ስለሆኑ ሊያሳስባችሁ የሚገባው ነገር ዛሬ የምታገኙት ነገር ብቻ መሆን አይገባውም፡፡ ከዚያ በተቃራኒ ዛሬ ዘርታችሁ ነገ የሚበቅልላችሁ ነገር ላይ በጥብቅ ማሰብ መጀመር አስፈላጊ ነው፡፡

እስካሁን የኖራችሁት ኑሮ በአብዛኛው ሌሎች ሰዎቸ በዘሩት ዘር ላይ የተመሰረተ ነበር፡፡ ቤተሰብ፣ ሕብረተሰብ፣ መሪዎችና የመሳሰሉት ሰዎች የዘሩትን ስታጭዱ ኖራችሁ ይሆናል፡፡ አሁን ግን ለነገ የምትዘሩበት እድሜ፣ አመለካከትና ብርታት ላይ ነው ያላችሁትና ተጠቀሙበት፡፡

ሌሎች ሰዎች ያደረጉባችሁና ያላደረጉላችሁ ነገር ሰለባ ላለመሆን ወስኑ፡፡

ትናንትና የሆነውን መለወጥ በትችሉም የነጋችሁን ግን መለወጥ እንደምትችሉ አስታውሱ፡፡

ዛሬ ያልዘራችሁት ነገ እንደማይበቅል በመገንዘብ ነቃ በሉ፣ አቅዱ፣ ዘርን ዝሩ፣ ተንቀሳቀሱ፡፡

Join us.....
     @Ab_book
     @Ab_book
     @Ab_book

Показано 20 последних публикаций.

3 249

подписчиков
Статистика канала