የኢትዮጵያ ቼክ የአርብ ሳምንታዊ ዳሰሳ
1. ቲክቶክ በፈረንጆች ሁለተኛ ሩብ ዓመት በኬንያውያን ተጠቃሚዎች የተጫኑ 360,000 ይዘቶችን ማንሳቱን አስታውቋል። በተመሳሳይ 60,000 አካውንቶችንም መሰረዙን ገልጿል። ቲክቶክ ባስነበበው የሩብ ዓመት ሪፖርቱ ከተነሱት ይዘቶች አብዛኞቹ ሀሠተኛ መረጃንና ልቅ ወሲብን ያሰራጩ ናቸው ብሏል። ከተሰረዙት አካውንቶች መካከል ደግሞ 90% ዕድሜያቸው ከ13 ዓመት በታች የሆኑ ልጆች የሚጠቀሙባቸው ሆነው በመገኘታቸው መሆኑን ገልጿል። ኬኒያ ከወራት በፊት ቲክቶክ የየሩብ ዓመቱን ሪፖርት እንዲያቀርብ መጠየቋ ይታወሳል።
2. አንጋፋው የብሪቲሽ ዕለታዊ ጋዜጣ ዘ-ጋርዲያን ኤክስ የተሰኘውን የማህበራዊ ሚዲያ መጠቀም ማቆሙን አስታውቋል። ጋዜጣው በድረገጹ ባስነበበው መግለጫ ኤክስን አሉታዊ ይዘቶች የበረከቱበት “መርዛም” ፕላትፎርም ሲል ገልጾታል። ከጋርዲያን በተጨማሪም የስፔኑ ላ ቫንጋርዲያ ጋዜጣም ኤክስ የሀሠተኛ መረጃ አሰራጮችና የሴራ ተንታኞች የገደል ማሚቶ (echo chamber) ሆኗል የሚል ምክንያት ከሰጠ በኃላ ፕላትፎርሙን መጠቀም እንደሚያቆም ገልጿል።
3. በተመሳሳይ ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች ቡድን (Reporters Without Borders) ኤክስ የተሰኘውን የማህበራዊ ሚዲያ ሀሠተኛ መረጃ በማሰራጨት ወንጀል መክሰሱን አስታውቋል። ቡድኑ በፈረንሳይ ሀገር በሚገኝ ፍርድ ቤት ያቀረበው ክስ ኤክስ ከተቋሙ አንጻር የተሰራጨን ሀሠተኛ መረጃ ተደጋጋሚ ሪፖርት ቢቀርብለትም አለማንሳቱን ያትታል። ቡድኑ ክሱን ያቀረበው የማህበራዊ ሚዲያ አገልግሎት ሰጭ ኩባንያዎች ተጠያቂ መሆን እንዳለባቸው ለማሳየት መሆኑን ባወጣው መግለጫ አስነብቧል።
በሳምንቱ ያቀረብናቸው መረጃዎች የቴሌግራም ሊንኮች፥
-የማህበራዊ ሚዲያ ድርጅቶች በጥላቻ ንግግር እና በሃሰተኛ መረጃ መቆጣጠር ላይ ያላቸው ሚና ምን መምሰል አለበት በሚለው ጉዳይ መልዕክት አስተላልፈናል:
https://t.me/ethiopiacheck/2502
-ከባህር ዳር ከተማ ተነስተው ወደ ጎንደር ያቀኑን ወታደራዊ ኮንቮዮች ያሳያል ተብሎ የተጋራን ፎቶ አጣርተናል:
https://t.me/ethiopiacheck/2503
-‘’የድሮ ፎቶ’’ እንዲመስል በቅንብር የተሰራ ምስልንም ፈትሸናል:
https://t.me/ethiopiacheck/2504
-ቴክኖሎጂን በመጠቀም ‘በሰአታትእ ውስጥ የስኳር በሽታን ማጥፋት ተችሏል በሚል እየተሰራጨ የሚገኝ መረጃንም ተመልክተናል: https://t.me/ethiopiacheck/2505
ኢትዮጵያ ቼክ
@EthiopiaCheck
1. ቲክቶክ በፈረንጆች ሁለተኛ ሩብ ዓመት በኬንያውያን ተጠቃሚዎች የተጫኑ 360,000 ይዘቶችን ማንሳቱን አስታውቋል። በተመሳሳይ 60,000 አካውንቶችንም መሰረዙን ገልጿል። ቲክቶክ ባስነበበው የሩብ ዓመት ሪፖርቱ ከተነሱት ይዘቶች አብዛኞቹ ሀሠተኛ መረጃንና ልቅ ወሲብን ያሰራጩ ናቸው ብሏል። ከተሰረዙት አካውንቶች መካከል ደግሞ 90% ዕድሜያቸው ከ13 ዓመት በታች የሆኑ ልጆች የሚጠቀሙባቸው ሆነው በመገኘታቸው መሆኑን ገልጿል። ኬኒያ ከወራት በፊት ቲክቶክ የየሩብ ዓመቱን ሪፖርት እንዲያቀርብ መጠየቋ ይታወሳል።
2. አንጋፋው የብሪቲሽ ዕለታዊ ጋዜጣ ዘ-ጋርዲያን ኤክስ የተሰኘውን የማህበራዊ ሚዲያ መጠቀም ማቆሙን አስታውቋል። ጋዜጣው በድረገጹ ባስነበበው መግለጫ ኤክስን አሉታዊ ይዘቶች የበረከቱበት “መርዛም” ፕላትፎርም ሲል ገልጾታል። ከጋርዲያን በተጨማሪም የስፔኑ ላ ቫንጋርዲያ ጋዜጣም ኤክስ የሀሠተኛ መረጃ አሰራጮችና የሴራ ተንታኞች የገደል ማሚቶ (echo chamber) ሆኗል የሚል ምክንያት ከሰጠ በኃላ ፕላትፎርሙን መጠቀም እንደሚያቆም ገልጿል።
3. በተመሳሳይ ድንበር የለሽ የጋዜጠኞች ቡድን (Reporters Without Borders) ኤክስ የተሰኘውን የማህበራዊ ሚዲያ ሀሠተኛ መረጃ በማሰራጨት ወንጀል መክሰሱን አስታውቋል። ቡድኑ በፈረንሳይ ሀገር በሚገኝ ፍርድ ቤት ያቀረበው ክስ ኤክስ ከተቋሙ አንጻር የተሰራጨን ሀሠተኛ መረጃ ተደጋጋሚ ሪፖርት ቢቀርብለትም አለማንሳቱን ያትታል። ቡድኑ ክሱን ያቀረበው የማህበራዊ ሚዲያ አገልግሎት ሰጭ ኩባንያዎች ተጠያቂ መሆን እንዳለባቸው ለማሳየት መሆኑን ባወጣው መግለጫ አስነብቧል።
በሳምንቱ ያቀረብናቸው መረጃዎች የቴሌግራም ሊንኮች፥
-የማህበራዊ ሚዲያ ድርጅቶች በጥላቻ ንግግር እና በሃሰተኛ መረጃ መቆጣጠር ላይ ያላቸው ሚና ምን መምሰል አለበት በሚለው ጉዳይ መልዕክት አስተላልፈናል:
https://t.me/ethiopiacheck/2502
-ከባህር ዳር ከተማ ተነስተው ወደ ጎንደር ያቀኑን ወታደራዊ ኮንቮዮች ያሳያል ተብሎ የተጋራን ፎቶ አጣርተናል:
https://t.me/ethiopiacheck/2503
-‘’የድሮ ፎቶ’’ እንዲመስል በቅንብር የተሰራ ምስልንም ፈትሸናል:
https://t.me/ethiopiacheck/2504
-ቴክኖሎጂን በመጠቀም ‘በሰአታትእ ውስጥ የስኳር በሽታን ማጥፋት ተችሏል በሚል እየተሰራጨ የሚገኝ መረጃንም ተመልክተናል: https://t.me/ethiopiacheck/2505
ኢትዮጵያ ቼክ
@EthiopiaCheck