አል ኢህሳን ኢሥላሚክ ቻናል


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


በጎ ተግባርን እንያዝ እንማማር ♥♥♥♥ እንዋደድ ነገ በአርሽ ጥላ ስር እንዲያካለን አል ኢህሳን የሙስሊሞች ጀመዐ

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


ARBA MINCH UNIVERSITY dan repost
«በጁምዓ ለሊትና በጁምዓ ቀን ላይ በኔ ላይ ሰላዋት ማውረድ አብዙ፣ በኔ ላይ አንድ ሰላዋት ያወረደ አላህ በእርሱ ላይ አስር ሰላዋት ያወርድለታል።»

[አል ሲልሲለቱ ሰሒሃ: ቁጥር 1407 ]


اللَّهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ، وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ كَمَا صَلَّيْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ، اللَّهُمَّ بَارِكْ عَلَى مُحَمَّدٍ، وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ، كَمَا بَارَكْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ، وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيد
      


TIKVAH-ETHIOPIA dan repost
“ የትራንስፓርትም ዋጋ ጨምሮባቸዋል። መድኃኒትም ከውጭ ነው የሚመጣውና በሁሉም ዋጋ ጨምሮባቸው በጣም በከፍተኛ ሲቃይ ናቸው ህሙማኑ ” - ማህበሩ

“ 400 ሺሕ ሰዎች ዲያሌሲስ ያስፈልጋቸዋል። አብዛኛዎቹ ዲያሊስ ማድረግ ስለማይችሉ ትተው ነው ያሉት ” በማለት የኩላሊት ህክምና እጥበት በጎ አድራጎት ማኅበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።

የማኀበሩ ዋና ሥራ አስኪያጅ ሰለሞን አሰፋ (ዶ/ር) ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ምን አሉ?

“ ብዙ ወጣቶች ናቸው ዲያሌሲስ እያደረጉ ያሉት። ኩላሊት ደግሞ ከዘመድ ካልሆነ ከእኛ ሀገር ከሌላ ቦታ ማገኘት አይቻልም። 

ትልቁ ችግር የኩላሊት ማግኘት ነው። ህሙማኑ የኩላሊት ንቅለ ተከላ ፍላጎት ቢኖራቸውም የሚሰጣቸው ሰው የለም። ቢኖርም እንኳ ቢኖር አንዳንዱ ማች አያደርግም።

አብዛኞቹ ዲያሌሲስ ማድረግ ላይ ነው ትኩረታቸውን የሚያደርጉት ንቅለ ተከላውን እስከሚያደርጉ ድረስ። 

የትራንስፓርትም ዋጋ ጨምሮባቸዋል። መድኃኒትም ከውጭ ነው የሚመጣው በሁሉም ዋጋ ጨምሮባቸው በጣም ከፍተኛ ሲቃይ ላይ ናቸው ህሙማኑ።

ድጋፍ የሚያደርገው ሰውም በጣም እየቀነሰ ስለመጣ ህሙማኑ በጣም ትልቅ ችግር ውስጥ ነው። ዲያሌሲስ ሁለት ጊዜ፣ አንዴ የሚያደርጉ አሉ። አንዳንዶች የሚበሉትን፣ የሚጠጡትን እየቀነሱ ይገኛሉ”
ብለዋል።

በኢትዮጵያ ስንት የኩላሊት ህሙማን አሉ ? ከእነዚህ መካከል ስንቶቹ ህክምና የመከታተል እድል አግኝተዋል ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም ምላሽ ሰጥተዋል።

ዋና ሥራ አስኪያጁ ፦

“ 400 ሺሕ የሚሆኑ ሰዎች ዲያሌሲስ ያስፈልጋቸዋል። አብዛኛዎቹ ዲያሌሲስ ማድረግ ስለማይችሉ ትተው ነው።

ግማሹ ጸበል ይሄዳል። ስለማንሰማ እንጂ ህይወታቸው የሚያልፈው ይበዛሉ። ዲያሌሲስ በማድረግ የሚታገለውን ነው የምናውቀው። ያም ቢሆን ሲቸግረው አንድም ሁለትም ጊዜ ዲያሌሲስ የሚያደርግ አለ በወር ውስጥ።

ይተዛዘናሉ። ሦስት ጊዜ ዲያሌሲስ የሚያደርገው ሰውዬ ‘ሁለት ይበቃኛል’ ብሎ አንዱን ለሌላ ይሰጣል። በእንደዚህ እየታገሉ ነው ያሉት።

የምንችለውን እያደረግን ለተወሰኑ ሰዎች ነው ለመድረስ የቻልነው ለብዙ ሰዎች መድረስ አልቻልንም። ምንክንያቱም ድጋፉ በደንብ ተጠናክሮ እየቀጠለ አይደለም።

ህብረተሰቡም ደግሞ ስለ ጉዳዩ ያገባኛል ብሎ ትኩረት ሰጥቶ ሲረዳ አንመለከትም። የሚያጭበረብረው ሰውም በዝቷል ”
ሲሉ አስረድተዋል።

ማህበሩ ፤ “ ሰው ለመርዳት ችግር የለበትም ይረዳል። ትልቁ ችግር ማስታወስ ላይ ነው ያለው። እናንተም ለህብረተሰቡ በማስታወስ እርዱን ” ሲል አሳስቧል።

“ ትልቅ መፍትሄ ይሆናል ብለን የምናስበው ከሞተ ሰው ኩላሊት እንዲወሰድ የህግ ማዕቀፍ ሲወጣ ነው ” ያለው ማኀበሩ፣ “ ሲጸድቅ ሰዎች ሰላም ያገኛሉ። እስከዚያ ድረስ ዲያሌሲስ እያደረጉ መቆየት ግድ ይላቸዋል ” ብሏል።

#TikvahEthiopiaFamilyAA

@tikvahethiopia




Mujib Amino Z islam dan repost
ሰዎች በምን ሁኔታ ላይ እንዳሉ አታውቅምና ዝም በል!
♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️ ♦️

ዶክተሩ ድንገተኛ የስልክ ጥሪ አንስትቶ በትህትና ጥሪውን አስተናግዶ ሲጨርስ ባስቸኳይ ሮጦ ወደ ሆስፒታል በመግባት የስራ ልብሱን ቀይሮ ወዷ ቀዶ ጥገናው ክፍል እያመራ ሳለ ኮሪኗር ጋር የዶክተሩን መምጣት በጉጉት ይጠብቅ የነበረውን የታማሚ አባት አገኘው፡፡ ሰውየው “ እንቧት ለመምጣት ይህን ያህል ጊዜ ይፈጅብሃል ? የልጇ ህይወት ሊጠፋ አዷጋ ላይ እንዳለች አይታይህም ? ትንሽ ህሊና የለህም ? ' በማለት ዶክተሩ ላይ ጮኸበት፡፡ ዶክተሩም ትንሽ ፈገግ አለና " አዝናለሁ ሆስፒታል ውስጥ አልነበርኩም “ የስልክ ጥሪውን ከተቀበልኩ በኋላ በቻልኩት ፍጥነት እዚህ ለመድረስ ጥሪያለሁ፡፡ አሁን አንተም ብትረጋጋ አኔም ስራየን ብሰራ መልካም ነው " ብሎ አረጋግቶት ሊገባ ሞከረ፡፡ ሰውየው ግን “ ተረጋጋ ነው ያልከው ?! ልጇ ባለችበት ቦታ ያንተ ልጅ ቢሆን አሁን እዚህ ክፍል ውስጥ ትረጋጋ ነበር ? " ልጅህስ ቢሞት ምን ታዟርግ ነበር ? ' ' አለ በንዴትና በቁጣ።

ዶክተሩ አሁንም በትንሹ ፈገግ አለና እንዲህ ሲል ለአእኝኸ አባት መለሰ “ የአምላክ ፈቃድ ይሁን ዶክተር የሰውን ህይወት ሊያሳጥር ፣ ሊያረዝም ፣ ሊያጠፋ፡ሊተካ አይችልም፡፡ ነገር ግን እንደ አምላክ ፈቃድ የቻልነውን ያክል እንጥራለን ፤ ልጅህም ይድንልሃል አይዞህ ፡፡ '' በማለት ወደ ቀዶ ጥገናው ገባ፡፡ ሰውየውም መልሶ እንድህ አለ “ ባልገቡበት ጭንቀት አስተያየትና ምክር መስጠት ቀላል ነው " አለ አያጉረመረመ፡፡ ቀዶ ጥገናው የተወሰኑ ሰዓታትን ወስዶ በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ፡፡

ዶክተሩ በደስታ እየተጣደፈ ከቀዶ ጥገናው ክፍል ወጣ፡፡ ለአባትየውም እንዲህ አለው " ፈጣሪ ይመስገን ቀዶ ጥገናው በተሳካ ሁኔታ ተጠናቆ ልጅህ ተርቧል፡፡ ማንኛውም አይነት ጥያቄ ካለህ ሌሎች ረዳት ዶክተሮችን ስላሉ እነሱን መጠየቅ ትችላለህ " በማለት የሰውየውን መልስ ሳይጠብቅ መንገዱን በሩጫ ቀጠለ፡፡

የልጁም አባት ለረዳት ዶክተሮች እንድህ ሲል አቤቱታ አቀረበ “ ለምንድን ነው ዶክተሩ እንዲህ ስሜታዊና ችኩል የሆነው ? ምናለ አንድ ደቂቃ ወስዶ የልጄን ሁኔታ ቢያስረዳኝ ? " በማለት ጠየቀ ፡፡ ይህንን ሲል የሰማች አንድት ነርስ እንባዋ በጉንጯ እየፈሰሰ “ ትላንት ነበረ የዶክተሩ ልጅ በመኪና አዷጋ የሞተው፡፡ ለልጅህ ህክምና ስንደውልለት የልጁ ለቅሶ ላይ ነበረ ሃዘኑን አቋርጦ መጥቶ ያንተን ልጅ ህይወት ታደገ፡፡ አሁን ቧግሞ የራሱን ልጅ የቀብር ስነ -ስርዓት ሊጨርስ በሩጫ ሄደ " አለች ፡፡ በዚህ ጊዜ የልጅ አባት ከሰዓታት በፊት ዶክተሩ ያሳየው የነበረውን በንግግራቸው መሃል የነበረችን ትንሽ ፈገግታ እያሰበ አለቀሰ፡፡

አንዳንዴ ሰዎች በምን ሁኔታ ላይ እንዳሉ አናውቅም፡፡ ስለዚህ በሰዎች ከመፍረድ ፣ ከመውቀስ ፣ ከማዘንና ከመቆጣት በፊት ነገሩን በቅንነት እንመልከት፡፡ብእስኪ ይህንን ባህሪ እናሳድግ ሰው ሰላም ሳይለን ሲያልፍ ልብ አላለኝም እንበል እንጅ ኮርቶ ነው ፣ ጠግቦ ነው አንበል፡፡ አንድ ሰው ያለምክንያት ሲቆጣን የተናደደበት ነገር ቢኖር ነው እንበል እንጂ ንቆኝ ነው አንበል ፡፡ ያልተመቸን ነገር ካለ ልዩነትን በማክበር በግልፅ ለመነጋገር እንሞክር እንጅ ማንም ላይ አንፍረድ ፡፡
የአዕምሮ ምግብ።


Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር) dan repost
አንዳንድ ቤት ውስጥ ከሚገጥሙ አሳዛኝ ነገሮች ውስጥ አንዱ እናት እና ልጆች ባ'ንድ ላይ በማደም አባትን የሚያገልሉበት በዳይ አካሄድ ነው። ይሄ ህሊና ላለው አካል የኋላ ኋላ እጅግ ከባድ ፀፀት ላይ የሚጥል አላህም የማይወደው ተግባር ነው። ጥፋት ከኖረም ማረሚያው መንገድ ሌላ መልክ ያለው በደል መሆን የለበትም።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor


Murad Tadesse (Official Channel)☪️🇪🇹 dan repost
ጁሙዓ ሙስሊሞች በሳምንት አንድ ጊዜ የሚገናኙበት፣ የሚማማሩበትና አላህን በልዩ ሁኔታ የሚያወድሱበት የተባረከ ቀን ነው። በዚህ ቀን ሊደረጉ ከሚችሉ መልካም ተግባራት መካከል ጥቂቶቹን እነሆ፡-
ጊዜን በአግባቡ መጠቀም: የጁሙዓን ቀን ከሌሎች ቀናት በተለየ መልኩ ለእምነትና ለመንፈሳዊ እድገት ትኩረት በመስጠት ማሳለፍ መልካም ነው።
ጧት ገና መነሳት: ለጁሙዓ ሶላት በጊዜ ለመዘጋጀትና ወደ መስጊድ ለመሄድ ጧት ገና መነሳት ተገቢ ነው።
ራስን ማፅዳትና ጥሩ ልብስ መልበስ: ለጁሙዓ ሶላት ስንሄድ ሰውነታችንንና ልብሳችንን አፅድተን ጥሩና ንጹህ ልብስ መልበስ ሱና ነው።
ሽቶ መቀባት: ሽቶ መቀባትም ከጁሙዓ ሱናዎች አንዱ ነው።
ወደ መስጊድ በእግር መሄድ: የሚቻል ከሆነ ወደ መስጊድ በእግር መሄድ ይመከራል። በእያንዳንዱ እርምጃ ምንዳ አለው ተብሏል።
ሱረቱል ከህፍን መቅራት: በጁሙዓ ቀን ሱረቱል ከህፍን መቅራት ትልቅ ምንዳ እንዳለው ተነግሯል።
በኢማሙ ፊት ለፊት መቀመጥና በጥሞና ማዳመጥ: በጁሙዓ ኹጥባ ወቅት በኢማሙ ፊት ለፊት መቀመጥና ኹጥባውን በጥሞና ማዳመጥ ተገቢ ነው።
ዱዓ ማድረግን ማብዛት: በጁሙዓ ቀን ዱዓ ተቀባይነት የሚያገኝበት ልዩ ሰአት እንዳለ ተነግሯል። ስለዚህ በዚሁ ቀን ዱዓ ማድረግን ማብዛት መልካም ነው።
ሰደቃ መስጠት: በጁሙዓ ቀን ሰደቃ መስጠትም ትልቅ ምንዳ አለው።
ቤተሰብን መንከባከብ: ከቤተሰብ ጋር ጊዜ ማሳለፍና እነሱን መንከባከብም ተገቢ ነው።
ከላይ የተዘረዘሩትንና ሌሎች መልካም ተግባራትን በመፈፀም የጁሙዓችንን ቀን የተባረከና በአላህ ዘንድ ምንዳ የምናገኝበት እንዲሆን ማድረግ እንችላለን። ጁሙዓ ሙባረክ!
ጀሚናይ 2 ፍላሽ


Nejib Reshad (ኢብኑ ረሻድ) dan repost
እርሳቸው ያልተማሩ፣ የማይጽፉ፣ የማያነቡ፣ ትምህርት ለመማር ብለውም ወደየተኛዉም የአለም ክፍል ያልሄዱ ፣ ያለ እናት ያለ አባት ያደጉ ደካማ ድሃ ከመሆናቸው ጋር አላህ ሱ.ወ ይህንን ሁሉ ጸጋ ሰጣቸው ።

اللهم صل وسلم على نبينا وحبيبنا محمد !

~ @Ibnu_Reshad02


አስቾካይ የእርዳታ ጥሪ ለጓደኛችን ኪያር ሽፋ
🥹🥹🥹🥹🥹🥹🥹🥹🥹

ደኛችን ተማሪ ኪየር ሺፋ ሀምዳ
የገርማማ ጋሌ ቀበሌ ተወላጅ እና ነዋሪ ሲሆን
በተጨማሪም የሀይራንዚ ልዩ አደሪ ት/ቤት ተማሪ
የነበረ በመጨረሻም ወራቤ ዩኒቨርስቲ ተቀላቅሎ በህክምና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የ3ተኛ አመት
የ ፋርማሲ ት/ክፍል  ተማሪ ሲሆን ፡፡
በቅርቡ ሴት ልጁ በልብ ህመም  ታማበት  በተለያዩ ሆስፕታሎች  (በወ/ኮ/ስ/ሆስፒታል እና በጡቁር አንበሳ ሆስፒታል ) ስያሳክማት ቆይቶ በመጨረሻም ሊሻላት ስላልቻለ ወደ እስራኤል ሀገር ሄዳ እንድትታከም የጡቁር አንበሰ ሆስፒታል ቦርድ የነገረው ስሆን
ለህክምና የሚያስፈልገውን 2,000,000 ብር የጥቁር አንበሳ በርድ እንደሚሸፍንለት ቃል የተገባለት ስሆን ሆኖም ግን
ለአሰቾካይ ለ ሁለት ሰው Passport አስከ 60,000 ብር  የሚያስፈልግ ሲሆን  እስካሁን 20,000 ብር የደረስን ስሆን ቀሪውን 40,000 ብር
እንድትሸፋኑልን የ እርዳታ እጃችሁን  እንድትዘረጉልን በፈጣሪ ስም አንጠይቃለን ፡፡

እስከ ፊታችን ሰኞ ማለትም እስከ ቀን 12/05/2017 ድረስ ማይጨረስ ከሆነ እድሉን ለሌላ ሰው አሳልፈው እንደሚሰጡበት ተናግረዋሉ

🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
🙏ይህን በማስመልከት  ለ WRU 🙏sudents  በሙሉ የ 100 🙏ቻሌንጅ አዘጋጅተናል 🙏🙏🙏🙏🙏
         
     please ለጓደኞቻችን እና ግሩፖች ለይ Share  እናድር
🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
ኪያር ሽፋ ሀምዳ
CBE= 1000615617842


በፈጣሪ ስም   SHARE  አድርጉት  🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏


قال تعالى:

(إِنَّمَا مَثَلُ الْحَيَاةِ الدُّنْيَا كَمَاءٍ أَنزَلْنَاهُ مِنَ السَّمَاءِ فَاخْتَلَطَ بِهِ نَبَاتُ الْأَرْضِ مِمَّا يَأْكُلُ النَّاسُ وَالْأَنْعَامُ حَتَّىٰ إِذَا أَخَذَتِ الْأَرْضُ زُخْرُفَهَا وَازَّيَّنَتْ وَظَنَّ أَهْلُهَا أَنَّهُمْ قَادِرُونَ عَلَيْهَا أَتَاهَا أَمْرُنَا لَيْلًا أَوْ نَهَارًا فَجَعَلْنَاهَا حَصِيدًا كَأَن لَّمْ تَغْنَ بِالْأَمْسِ ۚ كَذَٰلِكَ نُفَصِّلُ الْآيَاتِ لِقَوْمٍ يَتَفَكَّرُونَ)

«የቅርቢቱ ሕይወት ምሳሌ ከሰማይ እንዳወረድነው ውሃ፣ በእርሱም ሰውና እንስሳዎች ከሚበሉት የምድር በቃይ ተቀላቅሎበት (እንደ ፋፋ) ምድርም ውበትዋን በያዘችና ባጌጠች ጊዜ ባለቤቶችዋም በርሷ ላይ እነርሱ ቻዮች መኾናቸውን ባሰቡ ጊዜ ትእዛዛችን ሌሊት ወይም ቀን መጥቶባት ትላንት እንዳልነበረች የታጨደች እንዳደረግናት ብጤ ነው፡፡ እንደዚሁም ለሚያስተነትኑ ሕዝቦች አንቀጾችን እናብራራለን፡፡»
[ዩኑስ: 24]



فكل ما ترى  أية من آيات الله ....فسبحان الملك !

ጥራት የተገባህ ነህ፣ የአሸናፊዎች አሸናፊ፣ የኃያላኖች ኃያል የሆንከው ጌታችን አላህ‼
||


ዐሊይ ኢብኑል ሀይሠም እንዲህ ይላሉ:–

"አምሳያ ያላየሁለት የዘመን መገለባበጥ፣ የጊዜ መለዋወጥ አይቻለሁ።
★ የአልፈድል ብኑ ረቢዕ ንብረት በአንድ ሺህ ግመል ተጭኖ አይቻለሁ። ሌላ ጊዜ ግን ጠቅላላ ንብረቱ አንዲት ዘንቢል ውስጥ ሆና ተደብቄ አይቻለሁ። በውስጧ መድሃኒቶቹ ተጨምረው።

★ አልሐሰን ብኑ ሰህልን ደግሞ ጠቅላላ ንብረቱ አንዲት ዘንቢል ውስጥ ሆና ተመልክቻለሁ። ከዚያ ግን ንብረቱ በአንድ ሺ ግመል ላይ ተጭኖ አይቼዋለሁ።"

||

ዱንያ እንዲህ ነች። መርጋት የማታውቅ ወላዋይ!!
♣️ ሃያላን ይዋረዳሉ። ደካሞች ይነግሳሉ።
♣️ ሀብታሞች ጎዳና ላይ ይወድቃሉ። ምንዱባን በሰማይ ጠቀስ ህንፃ ይንፈላሰሳሉ።
♣️ ሳር ቅጠሉን የተፀየፈው ጨፍጫፊ አረመኔ አለም ጠባው ከአይጥ ጎሬ ሲያደፍጥ ታየዋለህ። የትላንቱ ተሳዳጅ ተራውን ሲያሳድድ ትመለከታለህ።

® ይሄው ነች ዱንያ!! ብልጭ ብላ ድርግም፣ ቦግ ብላ እልም የምትል። ሁሌ ሳቅ የለም! ሁሌ ድል የለም።
|
♣️ በድር ላይ ለያዥ ለገናዥ ያስቸገሩ፣ ጥጋብ ያስከራቸው ቁረይሾች፣ 70 መኳንንቶቻቸው ትላንት ሲያሳድዷቸው በነበሩ ሶሐቦች ሰይፍ ተበልተው፣ ሌላ 70 ደግሞ በምርኮ አስረክበው የሐዘን ማቅ ለብሰዋል። መካ በዋይታ ተንጣለች።
|
♣️ ኡሑድ ሌላ ቀን ነው። ሌላ ተራ!! አጋሪዎች የፈነደቁበት፣ እነ ሐምዛን፣ እነ ሙስዐብን ጨምሮ ከ70 በላይ ታላላቅ ጀግኖች ወድቀው ሌላ 70 የቆሰሉበት፣ አሳዝኝ ክስተት እውን የሆነበት ቀን። ሶሐቦች አካላቸው በስለት፣ ልባቸው በሐዘን ቢቆስል ጊዜ አላህ እንዲህ ሲል አሳሰባቸው: –

(إِنْ يَمْسَسْكُمْ قَرْحٌ فَقَدْ مَسَّ الْقَوْمَ قَرْحٌ مِثْلُهُ ۚ وَتِلْكَ الْأَيَّامُ نُدَاوِلُهَا بَيْنَ النَّاسَ)
"ቁስል ቢያገኛችሁ ሰዎቹንም መሰሉ ቁስል አግኝቷቸዋል፡፡ እናም እነዚህን ቀናት በሰዎች መካከል (በመልካምና በሌላ) እናቀያይራቸዋለን፡፡" [ኣሉ ዒምራን: 140]

|||

ዱንያ አመሏ ነው። ዛሬም እንዲሁ ናት።
ግን ማነው የሚማረው? ግን ማነው የሚመረምረው? ግን ማነው የዱንያን ከንቱነት ተገንዝቦ ለዘላለም ቤቱ ከልብ የሚጨነቀው?
እስከ መቼ ነው የምናንቀላፋው?
እስከ መቼ ነው የምንዘናጋው?
እስከ መቼ ነው በከንቱ የምንባዝነው?
ኢና ሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂዑን!
ኢላሂ ልብ ስጠን!
=
Ibnu minwor




And you know what? He answered my longed-for dua’.  He did. And in a way and timing which was beyond my wildest hopes and dreams. I know what some of you are thinking–that I’m just special in getting my unanswered prayer. At times this took ten years to come to fruition for me. This is not something only I’ve experienced, it’s a story I hear from others all the time. The answer is always there; it just may not be how you expect.
Don’t give up. Ibn Ataillah made this profound statement, “When God inspires your tongue to ask, know that He wants to give.” Have that fervent certainty that Allah  will answer your dua’ in the best way for your particular circumstances as you continue to ask Him.   
Shifting Our Understanding of How Dua’s are Answered

When it seems like a dua’ I’ve made for so long is not answered, I have to remind myself that our prayers are always being answered, but just not always in exactly the same way we are asking for them. So know that even if you don’t feel it, He is protecting you in what He withholds from you. Know that whenever you pray, He answers. But He answers in His timing, when it’s best for you. And if it turns out that it’s not best for you in this life–then without a doubt, it’ll be waiting for you in the next. 
The fact of the matter is that Allah  is All-Knowing and All-Wise and The Best of Planners, not me. Thus,it may be that I am making a dua’ which is in actuality not in my best interests for my deen, dunya, or akhirah, and He is answering in the way He knows will be best for me in all three. In hindsight I have realized, and I’m sure for many of you have as well, sometimes what I’ve so desperately insisted upon has made me sick: physically, spiritually, or mentally, and I realized that God was protecting me by withholding it. Other times, what I want has come, but delayed to a better time and in a better way than I could have imagined.
As Imam al Ghazali said, “As I look back on my life, I realize that every time I thought I was being rejected from something good; I was actually being re-directed to something better. You must convince your heart that whatever God has decreed is most appropriate and most beneficial for you.” Convince your heart that Allah  is always answering your prayers and always in the best way possible for your very specific, intimate circumstances, even when we don’t see or understand how He is. 


#Islam
Don’t Give Up On That “Unanswered” Prayer
Continuing to ask Allah  for that seemingly unanswered dua’ over and over again may seem impossible or pointless, but it is not.

Published
 January 5, 2022
By
 Ustadha Maryam Amir

I know sometimes you think it’s unfair and you wonder why God isn’t blessing you with the dua’ you’ve been making when you’ve tried so hard and done things right for so long. An unanswered prayer is a part of every human’s life. You want to get married and despite all your efforts and your commitment to doing things right, you’re still so aloneYou’re trying to have a baby, and despite months or years of trying, you have friends who didn’t even want to get pregnant but are conceiving children. You want to get that particular job or get into that particular school and yet…the doors are closed for you, again. And you wonder: what am I doing wrong? Is God mad at me? And you’ve often caught yourself wondering…what’s the point in me still making this dua’ which is not being answered, anyway? 
Sometimes you think it’s unfair that God isn’t blessing you when you’ve tried so hard and done things right for so long. I myself wanted something so badly and I kept praying for it, pouring my heart into begging God to give it to me. But after making dua’ for a while, eventually I would make that dua’ while saying to myself, “God probably wants to test me. He knows how much I want this, so He probably will give me the opposite of it just because I want it so badly.” 
Continuing to ask Allah  for that thing over and over again may seem impossible or pointless, but it is not. With training yourself to hold a positive opinion of Allah  and to recognize His wisdom even when you cannot understand it in the moment, inshaAllah, you will feel the patience to persist by shifting your understanding of a prayer which seems unanswered. Holding these two views in your heart will help you persist in praying for your unanswered prayer, for what you want and never giving up hope in the power of your dua’ and the promise that Allah  will answer it.  
Having a Good Opinion of Allah 
Keep supporting MuslimMatters for the sake of Allah
Alhamdulillah, we're at over 850 supporters. Help us get to 900 supporters this month. All it takes is a small gift from a reader like you to keep us going, for just $2 / month.
The Prophet (SAW) has taught us the best of deeds are those that done consistently, even if they are small. Click here to support MuslimMatters with a monthly donation of $2 per month. Set it and collect blessings from Allah (swt) for the khayr you're supporting without thinking about it.

After praying with so much devotion for something and losing hope in Allah’s  willingness to grant me what I wanted, one day I realized: God says:
أَنَا عِنْدَ ظَنِّ عَبْدِي بِي
“I am as My servant thinks I am.” [Hadith Qudsi;Al Bukahri]
Why would He give me what I want when all I’m thinking is about how much He wouldn’t give it to me? If I don’t even believe He’ll give it to me, if while I’m praying for it I’m thinking He will withhold it–then why would I be blessed with it? The Prophet Muhammad  taught us that we should pray for something while we are certain that God will answer us. It might not come in the same way we want it–but, then again, maybe it will!
Maybe it’ll be better, or maybe we’ll get it in the Hereafter, or perhaps something evil will be prevented and averted from us because of our prayer. In all those scenarios there is one common factor: God will answer. And all the more so, His answer to that dua’ will always be good.
With this newly found positive conviction, I went back to begging God to grant that specific dua’ for me; but this time, I was fervently certain that He would answer me. As the months went by and as one year merged into the next, every time a doubt would enter my heart, I cast it away. I screamed at it! I would say: He has to answer. He will answer. This is Al Mujeeb–The One Who Responds! This is Al Kareem–The Generous! This is Al Wadud–The Loving!


know sometimes you think it’s unfair and you wonder why God isn’t blessing you with the dua’ you’ve been making when you’ve tried so hard and done things right for so long. An unanswered prayer is a part of every human’s life. You want to get married and despite all your efforts and your commitment to doing things right, you’re still so aloneYou’re trying to have a baby, and despite months or years of trying, you have friends who didn’t even want to get pregnant but are conceiving children. You want to get that particular job or get into that particular school and yet…the doors are closed for you, again. And you wonder: what am I doing wrong? Is God mad at me? And you’ve often caught yourself wondering…what’s the point in me still making this dua’ which is not being answered, anyway? 
Sometimes you think it’s unfair that God isn’t blessing you when you’ve tried so hard and done things right for so long. I myself wanted something so badly and I kept praying for it, pouring my heart into begging God to give it to me. But after making dua’ for a while, eventually I would make that dua’ while saying to myself, “God probably wants to test me. He knows how much I want this, so He probably will give me the opposite of it just because I want it so badly.” 
Continuing to ask Allah  for that thing over and over again may seem impossible or pointless, but it is not. With training yourself to hold a positive opinion of Allah  and to recognize His wisdom even when you cannot understand it in the moment, inshaAllah, you will feel the patience to persist by shifting your understanding of a prayer which seems unanswered. Holding these two views in your heart will help you persist in praying for your unanswered prayer, for what you want and never giving up hope in the power of your dua’ and the promise that Allah  will answer it.  
Having a Good Opinion of Allah 


ከ ቀደምቶች ንግግር🔊 dan repost
ነውሯን ሲከታተሉ ከረሙ። ለጀሀነም አጭተዋት ሰርክ ነውሯን በማውሳት ተጠመዱ። የልቧን እናውቃለን ብለው አምላክ ለመሆን ቃጣቸው።በረቀቀ መንገድ በጌታዋ ላይ አሻረኩ። ያ ልቦችን የሚያገለባብጠው አላህ ተውበትን ለባርያው አደላት። በተውበት ቀደመቻቸው። እነሱ ግን አሁንም የሰዎችን ነውር በመከታተል የሚገኝ ቅድስና እንዳለ ነገር ከተግባራቸው አልተቆጠቡም። ይባሱኑ ያወገዙትን ነውር እራሳቸው መፈፀም ጀመሩት።

እርሷ ግን አሁን የምስጋና እንባ እያነባች ነው። እንኳን የሰዎችን ነውር ልትከታተል ቀርቶ ያኔ ነውሯን ሲከታተሉ ለነበሩት እርሷ ያገኘችውን ሰላም ያገኙ ዘንድ ትመኛለች።መገን አላህ ልቦችን ሲያገለባብጥ!
=t.me/AbuSufiyan_Albenan


Abuki Tech በነፃ‼️ dan repost
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته

ነፃ ቂርዓት ፈላጊዎች በሙሉ‼️

👉ቃዒዳ
👉ነዘር
👉ሙራጃዓ

ለመመዝገብ👇

1   ሙለ ስም✅
2   ፆታ✅


ወንዶች በዚህ ብቻ ላኩ 👉@HUZAZI

ሴቶች  በዚህ ብቻ ላኩና  የእህቶች ሊንክ ይሰጣችኃል 👉  @Remm919

☪ቂርዓቱ የሚሆነው በ Online  ነው።
ምዝገባ በሁለት ቀን ያልቃል።
አላማዉ ረመዳንን ቁርዓን ማንበብ ችለን መቀበል ነው።

መቅራት ለሚፈልግ ሼር ያድርጉ🤝

ቻናሉ ለመቀላቀል
👇👇👇👇

https://t.me/abukiweb


Qireat Ders dan repost
ለሽልማቱ እንምረጠው⁉️
=================
(ባለፈ የመረጣችሁም ደጋግማችሁ መምረጥ ትችላላችሁ!)
||
✍ እውነት ለመናገር ሁሉም ተወዳዳሪዎች የሚሸለሙትን ብር ወደ ኪሳቸው የሚያስገቡ ቢሆን ኖሮ፤ ወጣቱን ዒዘድንን ከመምረጥ ውጭ ሌላ አማራጭ የለኝም። ለእናንተ እርሱን ከመምረጥ የተሻለ ሌላ አማራጭ አላገኝላችሁም።

ነገር ግን ካሉት ተወዳዳሪዎች መካከል አንዱ የሆነው የአሚን ጠቅላላ ሆስፒታሉ ዶ/ር ሙሐመድ ሽኩር የ10 ሚሊዮን ሽልማቱን ወደ ኪሱ ሳይሆን የሚያስገባው በኪሱ ካለው ገንዘብ ጋር ጨምሮ እንደተለመደው በኸይር ሥራ ላይ እንደሚያውለው ቃል ገብቷል።

ዶ/ሩ ይህን የ10 ሚሊዮን ብር ምንም ሳይሸራርፍ ለእናቶችና ህፃናታ መታከሚያ እንደሚያውለው፣ በራሱ ገንዘብ የጀመራቸውን የኸይር ሥራዎች ማሳለጫ እንደሚያደርገው ተናግሯል። ስለሆነም ምንም እንኳ እስከዛሬ ከሠራቸው ዘርፈ ብዙ በጎ ሥራዎች አንፃር ሽልማቱ የሚገባውና እንዲያውም የሚያንስበት ቢሆንም፤ ለእናቶችና ህፃናት ከለገሰው ደግሞ ይበልጥ እንዲያሸንፍ ድምፅ ልንሰጠው ይገባል። በአጭሩ እርሱን ለመምረጥ የምንሰጠው ጊዜና መልዕክት ለመላክ በትንሹ የምናወጣት 3 ብር ለእናቶችና ህፃናት መረዳት ሰበብ ናት።



ለናሙና ያክል ዶ/ር ሙሐመድ በቅርቡ ከሠራቸው በጎ ሥራዎች መካከል፦



√ 250,000 ለመሬት መንሸራተት  አደጋ ለተጋረጠው  ለጎፋ ህዝብ፣

√ ከ3,000,000 በላይ ለቃዋቆቶ ኢብኑ ዐባስ መስጅድና መድረሳ፣

√ 300,000 ለሐላባ ወህደቱኒሳእ መድረሳ፣

√ ከ4.3 ሚሊየን ብር በላይ የሚያወጡ የህክምና ቁሳቁሶችን ከኢትዮ አግራ ትሬዲንግ ጋር በመተባበር ለዳሎቻ ከተማ ጤና ጣቢያ፣

√ የ200, 000 ለቅበት ከተማ አስተዳዳር ማህበረሰብ አቀፍ ፋርማሲ፣

√ 2.5 ሚሊዮን ለኬራቴ ጤና ጣብያ፣


√ 250,000 ለጎፍለላ… ወዘተ ከብዙ ጥቂቶቹ ናቸው።




ዶ/ር ሙሐመድን በመምረጥ እናቶችንና ህፃናትን መርዳት እንደምንችል ስላወቅኩ፤ ወደ 9355 SMS ላይ BIW03 ብላችሁ በመላክ ትመርጡት ዘንድ ጋበዝኳችሁ።

ስትመርጡ በፓኬጅ ስለማይቻል ቢያንስ 3 ብር ባላንስ ይኑረው ስልካችሁ።
ከዛ ሚሴጅ ላይ ግቡና 9355 ላይ BIW03 ብላችሁ ጻፉና ላኩት።

ባይሆን BIW በሚለውና 03 በሚለው መካከል ስፔስ (ክፍት ቦታ) መኖር የለበትም። BIW የሚለው በsmall letter biw ሳይሆን ሁሉም ፊደላት በካፒታል ሌተር BIW ናቸው። በትክክል መላካችሁን የምታረጋግጡት፤ BIW03 የሚለውን ወደ 9355 ከላካችሁት በኋላ «You have voted for ( Dr Mohamed shikur ). Thank you for your participation. Abbay TV 'Ethiopia's Best'» የሚል መልዕክት ወዳውኑ ይደርሳችኋል። ከአንድ በላይ ሲም ካላችሁ፣ ወይም መደጋገም ከፈለጋችሁ፣ ወይም ባላችሁ ቤተሰብ ስልክ ሁሉ መላክ ከፈለጋችሁ፣ ካርድ ለሌላቸው እየሞላችሁ … ምረጡት። ድምፃችን እንዳይበታተንና አንድ ቦታ ላይ አድምተን ድምፅ እንድንሰጥ ወጥሩ ቅመሞች።

መልዕክቱን በተለያዩ ገፆችና ግሩፖች አሰራጩት።
መታከሚያ ያጡ ሚስኪን እናቶችና ህፃናት ያሸንፋሉ፤ ኢንሻ አላህ! ያው የኔ ገፅ ቅመሞች በንቃትና በእንዲህ አይነት የኸይር ተሳትፎ አትታሙም። እንኳን በዚህች በቀላሏ ከኪሳችሁም ሚሊዮኖችን አዋጥታችሁ በተደጋጋሚ ለሚስኪኖች ሰድቃችሁ አሳይታችኋል። ሰበብ ሲገኝ ደግሞ እድሉን መጠቀም ነው። አላህ ይቀበላችሁ!



||
t.me/MuradTadesse


#የዓለማችን_አስገራሚ_ሶላት 💔💔

በሲድናያ እስር ቤት ታሳሪ የነበረ የተጅዊድ መምህር ሸይኽ እንዲህ ይተርካል ፦

ሙሉ እርቃን አድርገው አራቆቱኝ። ፀጉሬንም ላጩት ። በአንድ ክፍል ያጎሩን ሁሉ እርቃናችንን ነበርን። ከሴራሚክ ውጭ የምንቀመጥበት ነገር የለም። ልብሳችን ሀዘን፣ ህመም፣ርሃብና ማቃሰት ነበር። ቦታው ጠባብ ስለነበር እድሌ ሆነና ማደሪያዬ ሽንት ቤቱ ጋር ሆነ። የምበላው የምቀመጠውና የምተኛው እርሱ ጋር ነው።

አንድ ሰው ውሃ ሽንት ሲጠቀም ከሽንቱ የተወሰነው ይረጭብኝ ነበር። ደግነቱ ጥቂት ምግብ እንጅ ስለሌለ «ትልቁን ሽንት» በቀን አንድ ጊዜ ወይም በ2 ቀን ወይም በ3 ቀን አንድ ጊዜ ነበር እስረኞች የሚጠቀሙት። በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሆኜ ሶላት የምሰግደው አይኔን በማንቀሳቀስ ብቻ ነበር ።ሙሉ ለሙሉ እርቃን ሆኜ።

ምክንያቱም በእስር ቤቱ ህግ ሶላት የሚሰግድ ሰው ቅጣቱ የሚገለፅ አይደለም! ሞ* ት ከርሱ ይሻላል። የአሰድ የእስርቤት ጠባቂዎች ሲሰግድ ያገኙትን ሰው ወይ ወገቡን ሰብረ* ውት፣ ወይ 5 የጎን አጥንቱን ሰብረ* ውት ፣ ወይ አይኑን አጥ* ፍተ* ውት ወይ አጥንቱን ሰብ*ረው* ት ወይ እጁን ሽ* ባ አድርገውት ወይ እግሩን አንካ* ሳ አድርገውት እንጅ አይገኝም!

ስለሆነም ለሁለት ወር በሽንት ቤት ፣ ሙሉ እርቃን ሆኜ በነጃሳ ቦታ ወደ ቂብላም ሳልዞር አይኔን በማንቀሳቀስ ብቻ ሰገድኩ! አንዳንዴ እየሰገድኩ የአንዱ እስረኛ ሽንት ሲንጠባጠብብኝ ይሰማኝ ነበር! ይላል።

#ላ_ኢላሃ_ኢለላህ!
የዚህ አይነት ሶላት ሰምታችሁ ታውቃላችሁ! ?
የዚህ አይነት ጨ*ካ*ኝ አምባ*ገነ*ን ስርአትስ ሰምታችሁ ታውቃላችሁ?
Via ismaiilnuru


አስሩ የደስታ መሰረቶች

1. ደስታ ያለው በአላህ እጅ ብቻ መሆኑን ማመን፦
- እሱ ነው ልቦችን በተውሒድ፣ በኢማን፣ በሱና፣ በዒልም የሚያሰፋው፣
- ደስታ የአላህ ፍጥረት ነው = ከአላህ እንጂ ከማንም አይጠየቅም።

2. ደስታ ከልብ ውስጥ እንጂ ሌላ ቦታ አይደለም ያለው፦
- ደስታ የሚገኘው በምግብ አይደለም፣
- ደስታ የሚገኘው በመጠጥ አይደለም፣
- ደስታ የሚገኘው በመልበስ አይደለም፣
- ደስታ የሚገኘው በአዱኒያ ጌጦች አይደለም፣
- ደስታ እና እርካታ ከልብ ውስጥ ነው ያለው።

3. ወንጀሎችን ሀጢያቶችን እና ስህተቶችን መቀነስ፣ መተው፦
- ወንጀል በቀነሰ ቁጥር = ደስታ፣ እርካታና እረፍት ይጨምራል።
- ወንጀል ሸክም ነው፣ ጨለማ ነው፣ ጥበት ነው፣ ጭንቀት ነው።

4. በሰዎች መካከል በመልካም መወሳት፦
- የሙእሚን ሰው ፈጣን ብስራት ነው፣
- የሰዎችን መልካም ዱዓ ያስገኛል፣
- የሰው ልጅ ሁለተኛ እድሜ ነው።

5. ከችግር በኋላ ድሎት እንዳለ እርግጠኛ መሆን፦
- አላህ ችግርን ያለ መፍትሄ አልፈጠረውም።
- ሀዘንና ትካዜንም ያለ ግልግል አልሰራውም።
- መከራንም ያለ መፍትሄ አልተወውም።

6.ግልግል ከችግር ጋር እንደሚመጣ ማወቅ፣
- ችግር፣ ሀሳብ፣ ትካዜ በተከሰተ ቁጥር = የአላህ እዝነት እና ግልግል ይመጣል።

7. አላህ አንድን ችግር ሲያመጣ ሁለት መውጫ ያደረገ መሆኑን ማወቅ።

8. ትርፍ ጊዜን በኸይር እና በዒባዳ ላይ ማሳለፍ፦
- ስራ ሲያልቅና ሲጠናቀቅ ወደ ዒባዳ መግባት፣
- ስራ ፈቶ ያለ ምንም ነገር ጊዜን አለማባከን።

9. ዒባዳ ከደስታ ማግኛ ሰበቦች አንዱ ነው።
- አላህን ወደ መታዘዝ መግባት፣
- ዒባዳ በጨመረ ቁጥር = የልብ ደስታና እርጋታ ይጨምራል።
- ሶላት፣ እውቀት፣ ተስቢሕ፣ ተህሊል፣ በመልካም ማዘዝ ከመጥፎ መከልከል፣ ዝምድና መቀጠል ... ኸይር ነገር በጨመረ ቁጥር = የልብ ኢማንና ደስታ ይጨምራል።
- እስከ ሞት ድረስ በዒባዳ ላይ መዘውተር።
- የጭንቀት መድሃኒቱ = ዚክር ነው። ወንጀልን መተው።

10. ስራን ባጠቃላይ ለአላህ ብቻ ማጥራት
- ስራን ለአላህ ማጥራት ፣ ነው ነጃ መውጣት።

ደስታ ከፈለክ እነዚህን አስሮቹን ነገሮች ተጠባባቅ። ወላሁ ተዓላ አዕለም።
~
የሸይኽ ሙሐመድ ብኑ ዐብዲላህ ባሙሳ
ኡሰሉ ሰ፞ዓደቲል ዐሸራህ ኪታብ ተመልከት።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/MOhamedAljawi


hikmiyat🌹ྀ࿐ dan repost
በኩላሊት እጥበት ጊዜ ደም ከሰውነታች በቀዩ ቱቦ ይወጣና በ Dialysis Machine አልፎ በሰማያዊ ቱቦ ተመልሶ ወደ ሰውነታች ይገባል።

እንዲህ እያለ ለ 4 ሰዓታት ይቆያል  ይህ Dialysis በሳምንት 3 ጊዜ በወር 12 ጊዜ ይደረጋል። በአጠቃላይ በወር ለ 48 ሰዓታት ታማሚው ሳይንቀሳቀስ Dialysis ያደርጋል።
እኔ እና እናንተ ግን በቀን 36 ጊዜ ኩላሊታችን ራሱን ያጥባል ያውም ያለ ምንም ህመም እና ስቃይ።
አላህ የዋለልንን ፀጋ እናስታውስ🙏
አልሀምዱሊላህ እንበል 🙏🙏
በዚህ ህመም ለሚሰቃዩ አላህ ጤናቸውን ይመልስላቸው🙏
..........
{ وَإِن تَعُدُّواْ نِعۡمَةَ ٱللَّهِ لَا تُحۡصُوهَآۗ إِنَّ ٱللَّهَ لَغَفُورٞ رَّحِيمٞ }

የአላህንም ጸጋ ብትቆጥሩ አትዘልቋትም፡፡ አላህ በእርግጥ መሓሪ አዛኝ ነውና፡፡

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.