ደብረ ዘይት ሚዲያ


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Din


ቤተክርስቲያን ሆይ ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ ።

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
Din
Statistika
Postlar filtri




በእርግጥም ዮናስ በሽተኛ አክሞ ስለዳነለት የሚበሳጭ ሐኪም ሆነ፡፡ የነነዌ ሰዎች ግን የሰባኪው ማንነት ፣ የስብከቱ ውበት አልባነት ፣ የአነጋገሩ ለዛ ምክንያት ሳይሆናቸው ተስፋ በማይሰጥ ስብከት ተሰብረው ራሳቸውን አዳኑ፡፡ ብዙ ስብከት አልፈለጉም ፤ ክፋትን ለመተው እና ይቅር በለን ለማለት የተሰበረ ልብ እንጂ በእውቀት መሞላት አያስፈልግም፡፡ ኃጢአታችን ከነነዌ ሰዎች ከበለጠ ቆየ ፤ የጋራ ክፋታችንን በጋራ ንስሓ እንጠበው፡፡

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ጾመ ነነዌ 2011 ዓ.ም
አረንዳል ኖርዌይ

ለተጨነቀች ነፍስ ዕረፍት የሆነው የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ :: እኔም ለእናንተ ከሰበክሁ በኁዋላ የተጣልሁ እንዳልሆን ስለ እኔ ጸልዩ!

የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ ጸልዩ!
ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-
ዩቱብ
https://www.youtube.com/@12Samual

ቴሌግራም
https://t.me/tsidq

ቲክ ቶክ
https://vm.tiktok.com/ZMkpyjd6h


+ ጣዕም የሌለው ስብከት
በዲያቆን ሄኖክ ሐይሌ

ወደ ከተማችን አንድ ሰባኪ ሊሰብክ መጣ ፣ የመጣው ለመስበክ ፈልጎ አልነበረም፡፡ እኛን ለማዳን ጉጉት አድሮበት ፣ የእግዚአብሔርን ቃል ሊያሰማን ጓጉቶ አልነበረም፡፡ በግድ ተገፍትሮ ፣ ተተፍቶ ፣ ተወርውሮ የመጣ ዓይነት ሰው ነበር፡፡ ወደ መሃል ከተማም አልገባም የከተማችን አንድ ሦስተኛውን ብቻ ከተጓዘ በኋላ ስብከቱን ጀመረ፡፡ የሰበከው ስብከት ሰላምታ የለውም ፣ መግቢያ የለውም ፣ መውጫም የለውም ፣ ማጽናኛም የለውም ፣ ‹ንስሓ ግቡ› የሚል አዋጅ የለውም፡፡ በጩኸት የተናገረው አንድ አስደንጋጭ ዐረፍተ ነገር ብቻ ነበር ‹‹በሦስት ቀን ውስጥ ነነዌ ትገለበጣለች!!›› ከነነዌ ነዋሪዎች አንዱ የነነዌን ታሪክ ቢጽፈው የሚጽፈው እንዲህ ነበር፡፡

የነነዌ ሰዎች እግዚአብሔርን የማያውቁ አሕዛብ ናቸው፡፡ ዮናስ ደግሞ እነርሱ የማያውቁትን አምላክ የሚያመልክ ነቢይ ነው፡፡ ዮናስ ወደ እነርሱ የመጣው የማዳን ተልዕኮ ይዞ አልነበረም፡፡ ወደ አሕዛብ መላኩ አላስደሰተውም፡፡ ዮናስ ወደ ነነዌ የመጣው እንደ ሌላ ሰባኪ በየትኛውም ትራንስፖርት ተጉዞ ሳይሆን በዓሣ አንበሪ ወደ ነነዌ ተተፍቶ ነው፡፡ የተተፋ ሰባኪ እንዴት ደስ ብሎት ይሰብካል? እንኳን ስብከት ይቅርና ማንኛውም ሥራ ያለ ፍላጎት እንዴት ሊሳካ ይችላል? ዮናስ የነነዌ ሕዝብ እንዲድን ፍላጎትም አልነበረውም፡፡ እንዲያውም ከመጀመሪያውም ፍርሃቱ ‹ትጠፋላችሁ› ብሎ ተናግሮ ሳይጠፉ ቢቀሩስ የሚል ነበር፡፡

ዮናስ ወደ ከተማይቱ ዘልቆ ሲገባም በፍላጎት አልሰበከም ፤ የሰበከው ስብከት ተስፋ የሚያስቆርጥ ፣ እንደ ሰይፍ የሚቆራርጥ ነበር፡፡ የነነዌ ሰዎች የማያውቁትን አምላክ እንዲያውቁ ዕድል የሚሠጥ ትምህርት አልተሠጣቸውም፡፡ ዮናስም እንደ ኖኅ ‹ይኼንን ያህል ዘመን ተሠጥቷችኋል ተመለሱ› ብሎ አልሰበከም፡፡ መርከብ ሠርቶ ግቡም አላላቸውም፡፡ ‹በሦስት ቀን ውስጥ ነነዌ ትገለበጣለች› ብሎ ጮኸ፡፡

የነነዌ ሰዎች ግን ‹ማን ነው የሚገለብጣት?› ‹ለምን ትገለበጣለች?› ‹ለመሆኑ አንተ ማን ነህ?› ‹ዝም ብሎ ትገለበጣላችሁ ይባላል? መጀመሪያ ትምህርት አይቀድምም?› አላሉም፡፡ራሳቸውን እንጂ ሰባኪውንና ስብከቱን ለመገምገም ጊዜ አልነበራቸውም፡፡ ‹‹እግዚአብሔርን አመኑ ለጾም አዋጅ ነገሩ ከታላቁ ጀምሮ እስከ ታናሹ ድረስ ማቅ ለበሱ››

አንድ ላይ ኃጢአት መሥራት ቀላል ነው ፤ አንድ ላይ ንስሓ መግባት ግን ይከብዳል፡፡ በሀገር ደረጃ ንስሓ መግባት ግን እጅግ ያስደንቃል፡፡ ‹ነነዌ የምትገለበጥ ከሆነ ሀገር እንቀይር› አላሉም ፤ ሀገር ከመቀየር ይልቅ ራሳቸውን መቀየር እንደሚሻል ተረድተው ነበር፡፡ ሁሉም እኩል ልቡ ተሰበረ ፤ ሁሉም ማቅ ለበሰ፡፡

የሰባኪው ስብከት ጣዕም የለውም ብለው አላማረሩም ፣ ‹ተስፋ የሚሠጥ ስብከት መቼ ሰማን› አላሉም፡፡ ሰባኪው እያዋዛ አላስተማራቸውም ፣ ምሳሌ አልነገራቸውም ፣ ቅኔ አልተቀኘላቸውም ፣ ቅዱስ ኤፍሬም እንዲህ ይላል ‹‹የተላከላቸው ጨካኝ ሐኪም ነበር ፤ የያዘው መድኃኒትም የሚያቃጥል ነበር ፤ እንደ ሰይፍ የሚቆራርጥ ቃል ተናገራቸው ፤ እነርሱ ግን አቁስሏቸው ተፈወሱ››

የነነዌ ሰዎች ንስሓ ከላይ እስከታች ነበር፡፡ ነገሥታቱ ሳይቀር ማቅ ለበሱ፡፡ ‹‹ነነዌ ትገለበጣለች› ብሎ ሲናገር ንጉሡ ወታደሮች ልኮ ዮናስን ማሰር ይችል ነበር፡፡ ‹‹ምን በሀገራችን ላይ ታሟርታለህ?›› ብለው አፉን አላፈኑትም፡፡ መፍትሔውን ንገረን ያለውም የለም ፤ ችግሩ እነርሱ ናቸውና መፍትሔውንም ያውቁታል፡፡ ስለዚህ ራሳቸውን መውቀስ ወደዱ፡፡

ሀገሪቱ በአንድ ልብ አለቀሰች፡፡ ንጉሡ ፡- ሰዎችና እንስሶች አንዳች አይቅመሱ! ብሎ አዋጅ አስነገረ፡፡ ከቤተ መንግሥት ጾም የሚታወጅባት ነነዌ እንዴት የታደለች ናት? ‹‹መኳንንቶችሽ ማልደው የሚበሉ አገር ሆይ ወዮልሽ›› ተብሎ ከተጻፈ መኳንንቶችዋ የሚጾሙላት ሀገር እንዴት የታደለች ትሆን? (መክ. 10፡16) መቼም ሕዝብ ብቻ መጾሙ ነገሥታት ቢበሉ የተለመደ ነው፡፡ ነገር ግን እየበሉ የሚጾምን ሕዝብ መምራት እንዴት ይቻላል? ሲጠጡ እያደሩስ ሲጸልይ የሚያድርን ሕዝብ መምራት እንዴት ይቻላል?

ንጉሥሽ ላንቺ ማቅ ለብሶ ያለቀሰልሽ ፣ እንስሳት ሳይቀር የጾሙልሽ ነነዌ ሆይ ምንኛ የታደልሽ ነሽ? ሕዝብሽ ጾም ሲታወጅ የማያላግጡ ፣ ‹እኔ በፈለግሁበት ጊዜ ነው የምጾመው› ብለው የማይመጻደቁ ፣ እንኳን ከቤተ ክህነት ይቅርና ከቤተ መንግሥት የታወጀን ጾም በትሕትና የሚጾሙብሽ ነነዌ ሆይ ምንኛ የታደልሽ ነሽ? የዋሐን ሕጻናትን ጡት ከልክለው የፈጣሪን ርኅሩኅ ልብ የሚያስጨንቁ ፣ እንስሳትን ከውኃ ከልክለው ለምህላ የታጠቁ የነነዌ ሰዎች ምንኛ ድንቅ ናቸው፡፡

ቅዱስ ኤፍሬም ያቺን ከተማ በዓይነ ሕሊናው በጎበኛት ጊዜ እንዲህ ብሏል ፡-
‹‹የንጉሥ ቤት ግብዣ ተቋረጠ ፣ ንጉሥ ማቅ ለበሰ ፤ ንጉሥ ማቅ ከለበሰ ደግሞ የጌጥ ልብስ ይለብሳል፡፡ በዚያን ጊዜ በነነዌ ወርቃችሁን ብትጥሉ ማንም አይሰርቀውም፤ ሀብታችሁ ያለበትን ቤት ክፍት ትታችሁ ብትሔዱ ማንም ዘው ብሎ አይገባም፡፡ ወንዶች ወደ ሴቶች በምኞት አይመለከቱም ፤ ሴቶችም የሚያያቸውን ለመማረክ ጌጦቻቸውን አላደረጉም፡፡ ከልጆቻቸው ጋር አብረው ወደ መቃብር ሊወርዱ ነውና አረጋውያን በላያቸው አመድን ነሰነሱ፡፡ ወላጆች በልጆቻቸው ጥያቄ ተጨነቁ ፤ አብርሃም ልጁ ይስሐቅ ‹የመሥዋዕቱ በግ ወዴት ነው› ሲለው የተጨነቀው ጭንቀት በነነዌ ወላጆች ተደገመ››

ሶርያዊው የበተ መንግሥቱን ሁኔታም እንዲህ ይሥለዋል፡፡

‹‹የነነዌ ንጉሥ ወታደሮቹን ሰብስቦ እንዲህ አላቸውም ፡- ይህ ድል እንደተጎናጸፍንባቸው ውጊያዎቻችን አይደለም ፤ ከባዕድ ሀገር በተሰማው ዜና ኃያላኖቻችን ሳይቀሩ ተብረክርከዋል ፤ አንድ ዕብራዊ መጥቶ በቃሉ አብረከረከን፡፡የጀግኖች እናት ነነዌ አንድን ለብቻው የመጣ ደካማ ሰው ቃል ፈርታለች፡፡
ስለዚህ ወገኖቼ ፤ የማይፈርስ አጥር እንገንባ ፤ ይህች አጥር ንስሓ ናት ፤ ሥውር ጦርነት ታውጆብናልና ራሳችንን ሥውር መሣሪያ እናድርግ!!››

ዮናስ በነነዌ መመለስ ደስ አልተሰኘም ፤ ትንቢቱ ስለማይፈጸምለት ብቻ አይደለም፡፡ ‹‹የእስራኤል ሽማግሌዎች በሚቀማጠሉባት ሰዓት የነነዌ ሽማግሌዎች ሲያለቅሱ አየ ፤ ጽዮን በዝሙት እንደ ሰም ስትቀልጥ ነነዌ ታነባ ነበር›› እስራኤል ከፈጣሪ በራቁበት ሰዓት አሕዛብ የንስሓ ዕንባ ሲታጠቡ ሲያይ ክብር ከእስራኤል መልቀቁን አይቶ ተከፋ፡፡
ዮናስ እስከመጨረሻው ሰዓት የነነዌን መጥፋት ይጠባበቅ ነበር፡፡ ዮናስ ነነዌ የምትገለበጥበትን ቀን ሲቆጥር ነነዌ ደግሞ ኃጢአትዋን ትቆጥር ነበር፡፡

ዮናስ ስለ ነነዌ እንደ ሙሴ ‹እነርሱን ከምታጠፋ እኔን አጥፋኝ› አላለም ፤ በተቃራኒው ‹እነርሱን ካላጠፋህ እኔን አጥፋኝ› እስከማለት ደረሰ፡፡ ቅዱስ ኤፍሬም ነነዌን ወከሎ ነቢዩን እንዲህ ይለዋል ፡-
‹‹አንተ ዕብራዊ ሆይ ሁላችን ብንጠፋ ምን ይጠቅምሃል? አንተ ሰባኪ ሆይ በሁላችን መሞትስ ምን የተሻለ ነገር ይገኛል? የማቴ ልጅ ሆይ ወደ መቃብር በጸጥታ ብንወርድ ምን ታገኛለህ? በቃልህ ፈውሰኸን ልናመሰግንህ ስንመጣ ለምን ታዝናለህ? ዕጣህ ነነዌን ተናግሮ ያጠፋት ከመባል ይልቅ ተናግሮ ያተረፋት መባል ቢሆን አይሻልህም? መላእክት በሰማይ ሲደሰቱ አንተ ለምን ታዝናለህ? ዮናስ ሆይ ከእንግዲህ በስምህ የምትጠራ ናትና ነነዌን አመስግናት››


ሰርፀ ፍሬስብሐት መልካም ልደት ይሁንልህ


ወልደ ገብርኤልና ወለተ ገብርኤል መልካም ጋብቻ ይሁንላችሁ




+ እግዚአብሔር ያልተቀየማቸው ተጠራጣሪዎች +

አባ ጊዮርጊስ እንዲህ አለ ፦ አረጋዊው ስምዖን ‘እነሆ ድንግል ትጸንሳለች’ የሚለውን ትንቢት ተጠራጠረ፡፡ ይህ ጥርጣሬው ግን በደል ሆኖ አልተቆጠረበትም ይልቁንም ስሙ አማኑኤል የተባለውን ሕፃን ለማቀፍ አበቃው እንጂ፡፡ [ወኢተኈልቈ ሎቱ ኑፋቄሁ ኀበ ጌጋይ አላ አብጽሖ ኀበ ሑቃፌ ሕፃን ዘስሙ አማኑኤል]

ቶማስም የጌታን ትንሣኤ ተጠራጠረ፡፡ ትንሣኤውን መጠራጠሩ ግን የጌታን ጎን ለመዳሰስ በችንካሩ እጁን ለማስገባት አበቃው፡፡ [ወአብጽሖ ኑፋቄሁ ኀበ ገሢሠ አጽልእቲሁ ለመድኃኔ ዓለም] በእውነት ‘መተላለፉ የቀረችለት ኃጢአቱም የተከደነችለት ምስጉን ነው’ (መዝ 32፡1) እግዚአብሔር የወደደው ሰው ቍስሉ አይመረቅዝም በደሉም አይታሰብም፡፡

ጌታ ሆይ እኔንም ስለ መጠራጠሬ አትቀየመኝ ልደትህን የተጠራጠረው ስምዖንን እንዲያቅፍህ ፈቀድክለት፡፡ ትንሣኤህን የተጠራጠረውን ቶማስ ጎንህን አስነካኸው፡፡ ያኛው ‘ዓይኖቼ ማዳንህን አዩ’ ብሎ ዘመረልህ ይኼኛው ደግሞ ‘ጌታዬ አምላኬ’ ብሎ መሰከረልህ፡፡

ጌታ ሆይ እኔ እምነተ ቢሱንም መጠራጠሬን አትመልከትብኝ፡፡ የሚዋዥቅ ሕሊናዬን አጽናልኝ፡፡ እንደዚያ የልጅ አባት ‘አለማመኔን እርዳው’ እንደ ጴጥሮስ ‘ወደ አንተ እመጣ ዘንድ እዘዘኝ’ በመጠራጠሬ አትቀየመኝ፡፡

መጠራጠሬን አይተህ አትቀየመኝ፡፡ አንድ ትቢያ ቢጠራጠርህ እንደማይጎድልብህ አውቃለሁ:: ስለዚህ ራርተህ እምነትን አድለኝ:: ምናለ ለእኔም ማዳንህን አይቼ እስካምን እንደ ስምዖን ዕድሜ ብትጨምርልኝ? መቼም ላንተ ዘመን አይቸግርህም፡፡ ሺህ ዓመት ለአንተ አንድ ቀን አይደለች? ቢያንስ አምኜ አሰናብተኝ እስክልህ እስከ ቀትር አቆየኝ፡፡ አንተን በእምነት እንዳቅፍህ እርዳኝ እንጂ ስምዖን አሰናብተኝ እንዳለህ እኔም ደስ ብሎኝ አርፋለሁ፡፡ ማዳንህን ሳልረዳ ፣ አንተን በእምነት መዳፍ ሳላቅፍህ መሞትን ግን እፈራለሁ፡፡

"አምላኬ ጌታዬ" ብዬ ብዘምርም እንደቶማስ ካልዳሰስሁህ ሰውነቴ በእምነት አይኮማተርም፡፡ ተጠራጣሪውን የማትንቀው ሆይ ጥያቄው የማያባራ ልቤን ጥርጣሬው የማያልቅ ከንቱ ሕሊናዬን እንደቶማስ ራራለት፡፡ ለእኔ የቆሰልከውን ቁስል በእምነት መዳፍ ካልነካሁ ፤ እጄን ከችንካርህ ካላገባሁ የፍቅርህ ጥልቀት አይሰማኝምና እባክህን ‘ና ያመንህ እንጂ ያላመንህ አትሁን’ በለኝ፡፡

ሳላውቅህ የኖርኩት ጌታዬ ሆይ እንደዚያ መቶ አለቃ ‘ለካስ የእግዚአብሔር ልጅ ነበረ’ ብዬ ሳልመሰክርልህ አልሙት፡፡ እንደ ሌንጊኖስ ወግቼህ በፈሰሰው በጎንህ ውኃ ዓይኔን አብርተህ ካለማመን ብታወጣኝ ምናለ?
ያላመኑትን የማትንቀው ሆይ ተጠራጣሪዎችን ያልተቀየምከው ሆይ የሚጠራጠርህን ልቤን አትቀየምብኝ፡፡ የሚያስብ የሚጠይቅ አእምሮ ሠጥተህ ለምን ተጠቀምክበት ብለህ አትቀየምምና ስምዖን አቀፈህ ቶማስም ዳሰሰህ!

ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ
ጥቅምት 18 2013 ዓ.ም.

የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ ጸልዩ!
ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-
ዩቱብ
https://www.youtube.com/@12Samual

ቴሌግራም
https://t.me/tsidq

ቲክ ቶክ
https://vm.tiktok.com/ZMkpyjd6h/


እርግጠኛ ነኝ በየትኛውም እምነት ውስጥ ብንሆንም አእምሯችን ይጠይቃል።

መልስ ባለማግኘት የተጨነቃችሁ ወይንም ከጓደኛ ወይ ከቤተሰብ የሚመጣ ጥያቄን ለመመለስ የተቸገራችሁ የማኅበረ ቅዱሳን ትምህርትና ሐዋርያዊ አገልግሎት ሊቃውንትን መድቧል።

“ሃሎ መምህር” እንዲመለስልዎ የሚፈልጉትን ኃይማኖታዊ ጥያቄዎች በስልክ ቁጥር 0111 55 32 32 በተጠቀሱት በመደዎል ይጠይቁ፡፡

ለጥያቄዎ ማብራሪያ እና መልስ ከመምህራን ያገኛሉ፡፡


ካህናት በሚሰሩት ኃጢአት እግዚአብሔር ይቀጣቸዋል እንዲያውም ከራሳቸው በደል አልፎ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ "የሲኦል መሬቱ በካህናት አጥንት ተደምድምድሞ ይገኛል "እስከማለት ደርሶ የሓላፊነቱን ክብደት እንደገለጠው ካህናት በአግባቡ ባልጠበቋቸው
በጎቻቸውንና በምዕምናን በደል ሳይቀር ይጠየቃሉ ሆኖም በካህናቱ ድክመት አሳብበን እነሱን ብናቃልል ደግሞ እነሱ ለጥፋታቸው ሲቀጡ እኛ ደግሞ በእግዚአብሔር ካህናት ላይ ባሳየነውንንቀታችን ምክንያት እንቀጣለን።

አንዳድ ሰዎች የቤተክህነትንና የካህናትን ክፉ ዜና ከመስማት ብዛት ተማርረው "እግዚአብሔር እንዴት ይታረቀን በእነርሱ እጅ ንስሃ ገብተን እውነት ይቅር ልንባል ነው እውነት ፈጣሪ በእገሌ አድሮ ይሠራል? "ብለው ተስፋ ቆርጠው ይጠፋሉ። እንደ መጽሐፍ ቅዱስ ግን
እግዚአብሔር እጅግ የረከሰ ሕይወት በነበራቸው ካህናትአድሮ ሲሠራ ታይቶል።

እግዚአብሔር ቤተመቅደሱን ሲዳፈሩ የነበሩት ልጆቹን እያየ ዝም ባለውና መቅደሱን የምናምንቴዎች መፈንጫ ባደረገው በካህኑ ኤሊ አድሮ ስራ ሰርቷል። ኤሊ ለራሱ መጨረሻው ባያምርም በካህንነቱ ግን ሕዝቡ ተጠቅመው መሥዋዕታቸው አርጓል ሰክረሻል "ብሎ ያስቀየማት መካኒቱ ሐናም ለዘመናት ስታነባ ቆይታ ያልተመለሰላት ጥያቄ መልስ ያገኘው ናት ዕንባናልቅሶዋ ውጤት አምጥቶ ሳሙኤልን የመሰለ ልጅ እናት ለመሆን ያበቃት "በደህና ሂጂ የእስራኤል አምላክ የለመንሽውን ልመና ይስጥሽ "በሚለው በካህኑ ኤሊ ቡራኬ ነበር(1ሳሙኤል1፥17)
ካህን ለራሱ ለልጆቹ የማይጠቅም እንኳ ቢሆን በተሰጠው ስልጣን እግዚአብሔር ስለማይለየው ጸሎት የሚያሳርግና ዕንባን የሚያብስ ለመሆኑ ማሳያ ነው።ጌታችን እንዲሰቀል ነገር ጎንጉነውና በጨለማ ግፍ ሸንጎ የፈረደበትን በማለዳም በጲላጦስ ከፊት ያስፈረደበትን ሊቀ ካህናቱን ቀያፋንስ ማን ይረሳዋል

በነቀዘ የቤተ ዘመድ ሹመት ሊቀ ካህናትነቱን አማትና ምራት እየተፈራረቁ ሲያዙበት በነበረው በዚያብልሹ ወቅት በቤተ መቅደስ በጸሎት ፋንታ የገበያተኞች ጫጫታና የሚሸጡ እንሰሳት ጩኸት እንዲሞላ በተደረገበት ዘመን እግዚአብሔር በክፉው ሊቀ ካህናት አድሮ ይሰራ ነበር።ይህ ክፉ ሰው ክርስቶስ እንዲሞት ነቀሥሲጎነጉን
"ሕዝቡ ሁሉ ከሚጠፋ አንድ ሰው ስለሕዝቡ ይሞት ዘንድ እንዲሻለን አታስቡምን "?ብሎ ነበር ወንጌላዊው ስለዚህ ንግግር ሲያብራራ"ይሕንም የተናገረከራሱ አይደለም ነገር ግን በዚያች ዓመት ሊቀ ካህናት ነበረና ኢየሱስ ስለ ሕዝቡ ሊሞት እንዳለው
ትንቢት ተናገረ"ይላል(ዮሐ11፥50-51)
በሰቃዮቹ ላይ እንኳን አድሮ በሊቀ ክህነታቸው የሚሠራ አምላክ እንደምን ያለ ነው።የካህንን ክፋት ስንሰማ እንደ ዘካርያስ ዘመን ሰዎች ራእይ አይቶ ይህናል የሚል የዋሕ ልብ ይስጠን።

(ዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ)

የእግዚአብሔር ቃል ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ ጸልዩ!
ሌሎች እንዲያነቡትም የሚከተሉት አድራሻዎች Like, Subscribe እና Share ያድርጉ :-
ዩቱብ
https://www.youtube.com/@12Samual

ቴሌግራም
https://t.me/tsidq


@ ራእይ'እንዳየ 'አስተዋሉ።!)

በአንዲት እለት ካህኑ ዘካርያስ በቤተ መቅደስ ለእግዚአብሔር የዕጣን መሰዋዕት በማቅረብ ላይ ነበረ። ለዚህ ጻድቅ ሰው ታዲያ ድንገት በእጣኑ መሰዊያ በስተቀኝ ቅዱስ ገብርኤል ታየው። መላዕኩ ለዚህ አረጋዊ ለብዙ ዘመናት የተመኘውን ጸሎቱን እግዚአብሔር እንደተቀበለውና ሚስቱ ኤልሳ ቤጥ ታላቅ የሚሆን ልጅ እንደምትወልድ ለት ነገረው ዘካርያስ ይኽንን የመላዕኩን ብስራት በሰማ ግዜ
ምንም እንኳን አብርሃም ና ሳራ በስተርጅና ወለዱ የሚለውን ታሪክ ሲያስተምር የኖረ ካህን ቢሆንም ለማመን ተቸግሮ "ይኽ እንደሚሆን በምን አምናለሁ "ብሎ ምልክትን ጠየቀ
ቅዱስ ገብርኤል ለዚህ ጥያቄ "እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ "ብሎ መለሰለት። ይኽ ምላሽ እንደሊቃውንቱ ትርጓሜ "እኔ የእግዚአብሔር አገልጋይ የሆንሁ ለአንተ መገለጤ ምልክት አይደለምን "?
እኔ ኮ "በነበያት መጻሕፍት የምታውቀኝ ገብርኤል ነኝ። በፊትህ የቆምኩት እኮ በእግዚአብሔር ፊት የመቆመው ነኝ
የምነግርህን እንዴት አታምነኝም "?የሚል ትርጉም ያለው ነበረ።
+++++
ቅዱስ ገብርኤል በዚህ አላበቃም "በፊቱ ተጠንቀቁ ቃሉንም አድምጡ ስሜም በእርሱ ስለሆነ ኃጢአት ብትሰሩ ይቅር አይልምና እዳታስመርሩት "ተብሎ ከተነገረላቸው የእግዚአብሔር ሹመኞች
አንዱ ነውና ቃሉን ያላመነውን ዘካርያስን ቀጣው (ዘጸ23፥21)የእምነትን ቃል ሊናገር ሲጠበቅበት የጥርጥር ቃል የተናገረውን አንደበቱን ዘጋው እንዴት የተዘጋ ማህጸን ሊከፍት ይችላል ብሉ ለተጠራጠረው ልቡ አንደበቱ ዘግቶ በመክፈት ማህፀንን የዘጋ አምላክ መልሶ እንደሚከፍት ምልክት አድርጓ ሠጠው።
ዘካርያስ በቤተ መቅደሱውስጥ ከመላዕኩ ጋር ሲነጋገር ህዝቡ በውጪ ቆመው ይጠብቁት ነበር እንደ ኦሪቱ ስርአት ካህኑ "እግዚአብሔር ይባርካችሁ ፊቱንም ያብራላችሁ ሀገር"ብሎ ሳያሰናብታቸው ወደ ቤታቸው አይሄዱም ነበረና ዘካርያስ እስኪወጣ ይጠብቁት ነበረ"ስለዘገየም ይደነቁ ነበረ።" እንጂ እንደ ዘመኑ አስቀዳሽ "እነዚህ ካህናት ከጀመሩ ማብቂያ የላተውም ብለው ተንገሽግሸው የካህኑን ማሰናበቻ ቡራኬ ሳይቀበሉ ወደቤታቸው ጥለው አይሄዱም ነበር።

++++++
ከሁሉም የሚያስደንቀውና በዚች አጭር ስብከት የምናሰላስለው ዘካርያስ ከቤተ መቅደስ ዲዳ ሆኖ ከወጣ ቡዃላ ያለውን የሕዝቡን ምላሽ ነው።ሕዝቡ ዘካርያስን ይጠብቁት ነበር በቤተመቅደስ ምን ስለዘገየ ይደነቁ ነበር
በወጣም ግዜ ሊነግራቸው አልቻለም በቤተመቅደስ ራእይ እንዳየ አስተዋሉ።እርሱም ይጠቅሳቸው ነበረ ዲዳ ሆኖ ኖረ የማገልገሉም ወራት ሲፈጸም ወደ ቤቱ ሄድ።(ሉቃ1፥21-23)
ወዳጄ ሆይ እስኪ ቀና ብለህ ለአፍታ ባለንበት ዘመን ቢህን ብለህ አስበው
አንድ ሰንበት ምዕመናን አስቀድሰው ካህኑ ወተው እስከሚባርኳቸው ሲጠባበቁ ቄሱ በጣም ዘግይተው ሲወጡ ዲዳ ሆነው ቢወጡና ሕዝቡን ማነጋገር ቢያቅታቸው ሕዝቡ ምን የሚህ ይመስልሃል "ራዕይ አይተው ወጡ "ብሎ የሚደነቅ ይመስልሃል ከሆነ ድንቅ ነው።

እውነቱን ለመናገር ግን ይኽ ተከስተው መረጃን ለአለም ለማዳረስ ጥቂት ደቂቃዎች በሚበቁበት በዚህ የኢንተርኔት ዘመን ቢሆን ሕዝቡ ከቤተ ክርስቲያኑ ሳይወጣ ወሬው ለአለም በተሰማ ነበር ካህኑ ዲዳ የሆኑት "ተቀስፈው ነው" ለማለትና እርሳቸውም ድፍረቱን አብዝተውት ነበር ዋጋቸውን ሰጣቸው ብሎ በደላቸውን ለማብዛት ሰውሁሉ ሳይረባረብ አይቀርም። ዘካርያስ "በእግዚአብሔር ፊት ጻድቅ"ሆኖ ሳለ ዲዳ ሆኖ ሲወጣ ሰው እራዕይ አየ ብሎ አሰበለት በዚህ ዘመን ግን ሰውዬው መልካም ሰው ቢሆንም እንኳን ይኽ ክስተት ቢከሰትበት "እንግዲህ ላይ ላዩን ጥሩ መስሎ ውስጡ ችግር ይኖር ይሆናል "እንላለን እንጂ ራእይ አይቶ ይሆናል የሚል ግምት ጨረሶ አይኖረንም።

የዚያ ዘመን ሰዎች ግን ለመንፈሳዊነገር በቅርብ የሆነ አስተሳሰብ ነበራቸው ራእይ አየ ብለው መገመታቸውን ሳይበቃ ዲዳሆኖ የወጣ ሰው ሰሞነኛ ነቱን እስኪፈጽም አገልግልቱን ሲቀጥል
ዲዳ ያደረገው የሆነ ጥፋት ቢያይበት ነው ለምን ያገለግለናል ? ብለው አላጉረመረሙም። ይህ የዚያ ዘመን ሰዎችን መንፈሳዊ ህሊና በዚህ ዘመን ሆነን ስናየው ትልቅ ወቀሳ ያለው ነው።
ምክንያቱም ከፓትርያሪክ እስከ ቀሳውስት አባቶችን ማቃለል የዚህ ዘመን ሙያ ከሆነ ሰንብቷል የፖለቲካ ባለስልጣናትን ሲተቹ እንኳን በጥንቃቄና በፍርሃት የተሸበበባቸው ሰዎች ከመንግስት ስልጣን የሚበልጥ መንፈሳዊ ስልጣን ያላተውን አባቶች መቼም በሰማይ እንጂ በምድር እስር ቤት አይወረውሩንም ብለው ነው። መሰል አንዳንዶች ሲሳደቡ ይታያል ። በዚህ ዘመን ካህናትን ማቃለል ጀግና ለእውነት የቆመ የሚያሰኝ ተግባር እየመሰለ መቷል።
++++++
ይኽንን ስል "ካህናቱም እኮ አልከበር አሉ እንዲህ እያደረጉ ብሎ የሚሞግት አይጠፋም ሆኖም አንድን ካህንነ ጥሩ ስለሆነ ብናከብረው ያስከበረው ጥሩነቱ ነው እንጂ እኛ ክህነቱን አስበን አከበርነው ሊባል አይችልም። እንዲያውም እውነተኛ አክባሪ የሚባለው መጥፎ ምግባር የለውን አባት ስለአባትነቱ የሚያከብር ነው። እውነተኛ አክባሪ የሚባለው እንደኖህ ሰክሮ እርቃኑን የጣለ አባቱን እያየ የሚስቅና ለሌሎች የሚናገር ሳይሆን እንደ ሴምና ያፌት እንኳን ለሌላው ላሳይ ራሴም የአባቴን ውርደት አላይም የሚል ነው።

ቅዱስ ጳውሎስ ያደረገውን እናስታውስ በሸንጎ ቀርቦ ሳለ በዳኛው ትዕዛዝ በጥፊ ተመታ። ይኽን ግዜ ሳይፈረድበት መመታቱ አበሳጭቶት ዳኛውን "አንተ ቀኖራ የተለሰነ ግድግዳ እግዚአብሔር አንተን ይመታ ዘንድ አለው አንተ ልትፈርድብኝ ተቀምጠህ ሳለ ያለ ሕግእመታ ዘንድ ታዘለሕን አለው ጳውሎስ ይህንን ሲናገር ከአጠገቡ የቆሙት "የእግዚአብሔር ን ሊቀ ካህናት ትሳደባለህን አሉት። ጳውሎስ እንዲህ ሲሉት "እንደሊቀካህንነቱ አልከበር ሲል ምን ላርግሽ " አላለም ወይንም በዚያ ዘመን የነበረውን የነቀዘ የፈሪሳውያን ህይወት እንደማስተባበያ አልተጠቀመም
ጳውሎስ ያለው እንዲህ ነበር "ወንድሞቼ ሆይ ሊቀ ካህናት መሆኑን ባላውቅ ነው
በሕዝብ አለቃ ላይ ክፉ አትናገር ተብሎ ተጽፏልና (ሐዋ23፥2-5)

**
ልብአድርጉ የእብራውያንን መልዕክት የጻፈው ጳውሎስ ለምን ሊቀ ካህናት ትሳደባለህ ሲሉት "የሐዲስ ኪዳን ካህናት ኢየሱስ ነው ማለት አቅቶት አይደለም። በጥፊ እያስ መታውም እንኳ ቢሆን
ሊቀ ካህናት መሆኑን ሲረዳ "ሊቀ ካህናት መሆኑን ባላውቅ ነው። "አለ።

በዚህም ካህናትን እንኳን ወሬ ሰምተን ቀርቶ በጥፊ ቢያስመቱን እንኳ
አክብሮታችን እንዳይቀንስና ከተሰደብንም "ካህን መሆናቸውን ባላውቅ ነው ፣ፓትርያሪክ መሆናቸውን ባላውቅ ነው "እያልን እንድንጸጸት አስተማረን።




ዛሬ ጥር 25/5/2017 ዓ/ም
ስራተ ጋብቻችሁን በደብረ ምጥማቅ ቅዱስ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን የፈጸማችሁ
የደብራችን የመሰረተ ተዋህዶ ፍሬ የሆንሽው ቤተልሔም ታፈሰና ዲያቆን አራጋው ገመደ መልካም ጋብቻ ይሁንላችሁ



13 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.