👆🏻የዲኔ ጉዳይ ያገባኛል👆🏾


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


በዚህ ቻናል
♦️#ተውሒድና_ሱና በሰለፎች አረዳድ ብቻ ከተለያዩ የሰለፊያ መሻይኾችና ኡስታዞች ትምህርት ይቀርባል።
♦ እንዲሁም ሙስሊሙን የተመለከቱ ወቅታዊ መረጃዎችን እናጋራለን ተቀላቀሉ
ولقد بعثنا في كل أمة رسولاً عن اعبد الله واجتنبوا الطاغوت
https://t.me/yedine_guday

ሀሳብ እስተያየቶን በ👇ያድርሱን
@Yedinegudaybot

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


• የእንቅልፍ መጫጫን ሳይሆን የወንጀል ክብደት ነው ለ ለይል ሶላት መነሳት የሚከለክለው። ወንጀል የሕይወት አደገኛ ትብታብ ነው። በጊዜና አሁኑኑ ካልፈታነው መላቀቀቁ ከባድ ነው።
=t.me/AbuSufiyan_Albenan


الله أكبر
الله أكبر
الله أكبر

ኒቃቢስቷ ዛኪራ ሰዒድ በወርቅ ተመርቃለች!

በወሎ ዩኒቨርሲቲ የሳይኮሎጂ ተማሪ የነበረችው ዛኪራ ሰዒድ 3.99 በማምጣት በሁለት ዋንጫ እና የወርቅ ሜዳልያ ተመርቃለች።
Congratulations 🎉🎉🎉 Our sister!

Once again ኒቃብ ከመማር ከመመረቅ ከመሸለም አያግድም፣ተምራለች፣ተመርቃለች: ተሸልማለች።

ትለብሳለች
ትማራለች!

ሙተነቂብን ከትምህርት ማገድ ሃገርን ማውደም ነው።


እኚህ ሰው ማን ናቸው?

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ፥ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።

15፥95 *"ተሳላቂዎችን ሁሉ እኛ በቅተንልሃል"*፡፡ إِنَّا كَفَيْنَاكَ الْمُسْتَهْزِئِينَ

ከሊቅ እስከ ደቂቅ፣ ከሕፃን እስከ አዋቂ፣ ወጣትም ሆነ አዛውንት ስለ እሳቸው ሲወራ "ጆሮ ዳባ ልበስ" የሚል የለም። ሁሉ ስለ እሳቸው ሲወራ አዳሜ ሆነ ሔዋኔ ጆሮውን አስግጎ ይሰማል፥ ከሁሉም ከሁሉም የሚገርመው ደግሞ የሚጠሏቸው ሳይቀር እንኳን ቢሆን ስለ እሳቸው ለመስማት እና ስለ እሳቸው ለማወቅ ይፈልጋሉ። ዝም ብለህ ሰው የተሰበሰበበት መሀል ገብተህ እና ድምጽክን ከፍ አድርገህ፦ "እከሌ" ብለህ ወይም "እከሊት" ብለህ ብትጣራ ፊቱን እና ትኩረቱን ወደ አንተ የሚያዞረው የጠራከውን ስም ባለቤት ብቻ ነው፥ ከሌለም ደግሞ ማንም ፊት እና ትኩረት የሚሰጥክ አይኖርም። ነገር ግን ሰው የተሰበሰበበት ስፍራ ሄደህ የእሳቸውን ስም ጠርተህ ንግግር ብትጀምር ሁሉም ፊቱን እና ትኩረቱን ወደ አንተ ያደርጋል፥ ትኩረት የማይሰጥህ የለም ቢባል ማጋነን እና ማበል አይሆንም። ስለ እሳቸው ለማወቅ የማይሰለፍ አይኖርም፥ እኚህ ሰው፦
1ኛ. የእልፍ አእላፋት መጻሕፍት ርዕስ በመሆን ብዙ ጸሐፊያን የከተቡላቸው ናቸው፣
2ኛ. በሁሉም ልብ ውስጥ በአሉታዊ ሆነ በአንታዊ በሁለት ወገን እንደተሳለ ሰይፍ ሰርስረው የገቡ ናቸው፣
3ኛ. አስተምህሮታቸው የተሟላ መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ፓለቲካዊ የሕይወት ዘይቤ በመሆኑ የዓለማችን ተግዳሮት ነው የተባለላቸው ናቸው፣
4ኛ. "የዓለማችን ቁጥር አንድ አውንታዊ እና አሉታዊ ተጽዕኖ አሳዳሪ" ተብለዋል፥ ለሕሩያን አውንታ ተጽዕኖ እንዲሁ ለእኵያን አሉታዊ ተጽዕኖ አሳዳሪ ናቸው፣
5ኛ. ስለ እርሳቸው ማንነት የገባው ሰው፦ "ሕይወትህን መስዋዕት አርግ" ቢባል ያለ አንዳች ማቅማማት ሕይወቱን እስከ ሞት የሚያደርግላቸው ናቸው።
6ኛ. በታሪክ ውስጥ እሳቸውን ለማነወር፣ ለማበሻቀጥ፣ ለማብጠልጠል ብዙ ጦማሪያን ጦምረዋል፣ ብዙ ኃያሲያን ኃይሰዋል፤ ብዙ ተቺዎች ተችተዋል፣ ብዙ ተሳላቂዎች ተሳልቀዋል። ቅሉ ግን የጦማሪያን ጦማር፣ የኃያሲያን ኂስ፣ የተቺዎች ትችት፣ የተሳላቂዎች ስላቅ ከሟቾች ጋር ሲያልፍ የእሳቸው ስም እና የሰዎችን ሕይወት የቀየሩበት መጽሐፍ እስካሁን አለ የተባለላቸው ናቸው።
እኚህ ሰው ማን ናቸው? አዎ! የዓለማቱ ጌታ የአሏህ መልእክተኛ እና የነቢያት መደምደሚያ ነቢዩ ሙሐመድ"ﷺ" ናቸው። በእርሳቸው ላይ የወረደው ሐቅ ለሰዎች የሚጠቅም ስለሆነ በምድር 1400 ዓመት ቆይቷል፥ ባጢል ቢሆን ኖሮ በእንጭጩ ኮረፋት ሆኖ ተግበስብሶ ይጠፋ ነበር፦
13፥17 *"እንደዚሁ አላህ ለእውነት እና ለውሸት ምሳሌን ያደርጋል። ኮረፋቱማ ግብስብስ ኾኖ ይጠፋል፥ ለሰዎች የሚጠቅመውማ በምድር ላይ ይቆያል፡፡ እንደዚሁ አላህ ምሳሌዎችን ይገልፃል"*፡፡ كَذَٰلِكَ يَضْرِبُ اللَّهُ الْحَقَّ وَالْبَاطِلَ ۚ فَأَمَّا الزَّبَدُ فَيَذْهَبُ جُفَاءً ۖ وَأَمَّا مَا يَنفَعُ النَّاسَ فَيَمْكُثُ فِي الْأَرْضِ ۚ كَذَٰلِكَ يَضْرِبُ اللَّهُ الْأَمْثَالَ
ሐዋ. ሥራ 5፥38-39 አሁንም እላችኋለሁ፦ ከእነዚህ ሰዎች ተለዩ ተዉአቸውም! *ይህ አሳብ ወይም ይህ ሥራ ከሰው እንደ ሆነ ይጠፋልና፥ ከእግዚአብሔር እንደ ሆነ ግን ታጠፉአቸው ዘንድ አይቻላችሁም። በእርግጥ ከእግዚአብሔር ጋር ስትጣሉ ምናልባት እንዳትገኙ"*።

ገማሊያ እንደተናገረው ይህ የነቢያችን"ﷺ" እሳቦት ከሰው ከሆነ ይጠፋ ነበር፥ ግን የነቢያችን"ﷺ" ግልጠተ-መለኮት ከፈጣሪ ስለሆነ ገና በእንጭጭነቱ የመካህ ቁሬይሾች፣ የመዲና በኑ ቁሬይዛህ፣ የሮሙ ባዛንታይን በዕውቀት መሞገት ሲያቅታቸው በጉልበት ሊጠፉት ሞክረው አልተሳካላቸው። ከርሞም ሆነ ዘንድሮም እሳቸው ላይ ለሚሳለቁን ተሳላቂዎች አሏህ በቅቶላቸዋል፥ በእርሳቸው ላይ የወረደውን የአሏህን ብርሃን በአፎቻቸው ለማጥፋት ቢፈልጉ እና ቢጠሉም አሏህ ብርሃኑን ገላጭ ነው፦
15፥95 *"ተሳላቂዎችን ሁሉ እኛ በቅተንልሃል"*፡፡ إِنَّا كَفَيْنَاكَ الْمُسْتَهْزِئِينَ
61፥8 *"የአላህን ብርሃን በአፎቻቸው ሊያጠፉ ይሻሉ፥ ከሓዲዎቹ ቢጠሉም እንኳ አላህ ብርሃኑን ገላጭ ነው"*፡፡ يُرِيدُونَ لِيُطْفِئُوا نُورَ اللَّهِ بِأَفْوَاهِهِمْ وَاللَّهُ مُتِمُّ نُورِهِ وَلَوْ كَرِهَ الْكَافِرُونَ

ይህንን ብርሃን ለማጥፋት እፍ ባሉ ቁጥር እያነደዱት መሆኑን ይዘነጋሉ፥ ኢሥላም በፍጥነት መጠነ-ሰፊ የእድገት መርሓ-ግብር እየታየበት ያለው በምዕራባውያን መሆኑ እፍ ባሉ ቁጥር የሚያነዱበት ውጤት ነው። አሏህ ሂዳያህ ይስጣቸው! ለእኛም ጽናቱን! አሚን።

“ፊዳከ አቢ ወኡሚ ያ ረሡሉሏህ” فِدَاكَ أَبِي وَأُمِّي يَا رَسُول اللَّه

✍ከወንድም ወሒድ ዑመር
https://t.me/Wahidcom

ወሰላሙ አለይኩም


🤲 ዱዓችን ተቀባትነት የሚያገኝበት ቦታ እና ሰዓት እንድሁም ዱዓ ከማድረጋችን በፊት ማሟላት ያለባቸው ነገሮች ተነስተዋል።

መጨረሻም ላይ ኢብኑል ቀይም መስፈርቶቹን ከጠቀሱ ብኃላ «በዚህ አይነት ሁኔታ የተደረገ ዱዓ በፍፁም ሊመለስ አይችልም!» ይላሉ።

-ከ ሙኽተሶር አዳእ ወደዋእ ኪታብ የተወሰደ-
🎙ወንድም አቡ ሱፍያን
=t.me/AbuSufiyan_Albenan


ከአንዲት ገጽ ታሪክ በርካታ ትምህርት

🤝የተቸገሩ ሰዎችን መርዳት

🤲መልካምን ከሰሩ በኋላ ከመተናነስ ጋር አሏህን ከችሮታው መጠየቅ ምን ያማረ መዳረሻ ስለመሆኑ

👉በተለይ ለሴት ልጅ ሐያእ ምን ያህል ግምት የሚሰጠው እሴት እንደሆነ

🤝ውለታን በሚችሉት መመለስ አስፈላጊ ስለመሆኑ

🤝ውለታንም ስንመልስ ባሳመረልን (በዋለልን) የሚመጥን ደረጃ መመለስ እንደሚገባ

🫶አሏህን የሚፈራ እና መልካም ባለውለታ ሰው ሲገኝ ሴት ልጄን ላጋባህ ማለት ችግር የሌለው ስለመሆኑ “ውሀ ጠጡልኝ ልጄን አግቡልኝ” አይባልም የሚለው አባባል ስሑትነት።


እነሆ የረመዷን ወር ገብቷል።
መልካም የዒባዳ ጊዜ ይሁንልን


.



.




.


የሰው ሐቅ ተሸክመህ ወደ ረመዳን አትግባ። መክፈል እየቻልክ የሰው ሐቅ ይዘህ አታጉላላ። አቅቶህ ከሆነ ጊዜ እንዲሰጡህ በትህትና አስረዳቸው።
* የበደልከውን ይቅርታ ጠይቅ። የበደሉህን ይቅር በል።
* መክፈል የማይችል ሰው ላይ ሐቅ ካለህ ብትችል እለፍ ወይም ቀንስላቸው። ካልሆነ ጊዜ ስጣቸው። "የትም ገብታችሁ አምጡ" አትበል። ወንጀል ላይ ገብተው ቢሰጡህ ሐላል አይሆንልህም።
* ስትሸጥም ስትገዛም ገር እና ቅን ሁን። ገዥም ሻጭም ሆነህ ሶደቃ የምታደርግበት ሁኔታ እንዳለ አስተውል።
* ግብይትህ ላይ ከውሸት፣ መሀላ ከማብዛት፣ ከማታለል፣ ... ተጠንቀቅ። ጊዜ ካለህ ቁርኣን ቅራ። ዚክር አድርግ።
* ቤትህ ውስጥ ሰላም ሁን። ከጭቅጭቅ ራቅ። ሶብር ይኑርህ። ለሚስትህ፣ ለልጆችህ አሳቢ፣ ተቆርቋሪ ሁን። ከአላህ በታች ያላንተ ማን አላቸው? ለባልሽ ምቹ ሁኚ። አንቺ ፈተና ከሆንሽበት ውሎውን ሁሉ ሰላም ያጣል።
=
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor


ኡስታዝ  ኢብኑ  ሙነወር (አቡ ሁዘይፋ)

የተከበረው ኽይሩ የበዛው ወር!

      t.me/NABAWITUBE


ነፍሴ በእጁ በሆነችው ጌታዬ እምላለሁ ረመዷንን ማግኘት አሏህ በእኛ ላይ ከዋላቸው ትልልቅ ኒዕማዎች ነው።
ይህን እድል (የዘንድሮን ረመዷን) ያላገኙ ስንት ወንድም እህቶቻችን አልፈዋል? እስኪ በዙሪያችን እናስተውል።
አምና ከኛ ጋር ፆመው የነበሩ ወንድሞች የዚህችን ረመዷን መገናኘት እየናፈቁ የተለዩ የሉምን? አሁንስ አልገባንም? አሏህ አሁንም ሌላ እድል ሰጥቶናል እንዴት እንጠቀመው ይሆን?
ምናልባት ይህ ረመዷን የመጨረሻ ረመዷናችን አለመሆኑን ምን አሳወቀን? ዘንድሮም ሚዲያ ላይ ባልረባው ተጥደን፣ እንቅልፍና ምግብ አግበስብሰን፣ ዛዛታና ወሬ አብዝተን እንደዋዛ የምናሳልፈው ረመዷን ነው? በውስጣችን የተለየ ኒያ ከሌለ አሁን እንወስን! ይህ የመጨረሻ ረመዷናችን ሊሆን ይችላል እንደሰለፎቻችን ሰፊውን ጊዜ ለቁርአን እንስጥ።
ሰለፎቻችን ሐታ የዒልም ሐለቃቸውን ትተው ፊታቸውን ወደ ቁርአን ያዞሩ ነበር፡ በየቀኑ በቀን ሁለቴም ያኸትሙ ነበር።

ስለ ኢማን፣ ኢስቲቋማ፣ ስለ ኻቲማችን፣ ስለ ቀብር፣ ስለ ሲሯጥ፣ ስለ መሕሸር፣ ስለ ጀሀነም አብዝተን ለራሳችንም ሆነ ለቤተሰቦቻችን ዱዐእ የምናደርግበት፡ ራሳችንን የምንተሳሰብበት፣ በግልጽም በድብቅ ለሰራናቸው ጥፋቶች ምህረት የምንጠይቅበት፣ ጌታችንን አብዝተን የምናመሰግንበት ታላቁ ወር ከፊታችን ነው። አሁንስ ኒያችንን ጠንከር አናደርግምን?

በዚህች ወርኮነው ቁርአን የወረደልን፣ በዚህች ወርኮነው #ለይለቱል_ቀድር (የመወሰኛይቱ ሌሊት) የምትገኘው።

ይህች ሌሊት (ከብጤዋ ሌሊት ውጭ) ከአንድ ሺ ወር በላይ እንጂ አንድ ሺ ወርን የምትመጥን አይደለም የተባለችው፡ ደረጃዋን በውል የሚያውቃት እርሱ ብቻ ነው።
ليلة القدر #خير من ألف شهر
ሱብሀነሏህ! ይህ አሏህ ለዝች ኡማ ካጎናጸፋት ጸጋዎች ነው ። እኛንስ ለዚህ አህል ካደረገን እንዴት ልናሳልፈው አሰብን?

በአዘቦት ሞባይል ላይ የማዘውተር ልምድ ያለን ወንድም እህቶች በረመዷን ሶሻል ሚዲያ nearly ባንጠቀም የግድ የሚመለከተንን ጉዳይ አክሰስ ለማድረግ ቢሆን እንጂ። እናም በቋሚነት ትምህርት የምትከታተሉ ካልሆነ እና አስገዳጅ ሁኔታ ከሌለ ውድዱን ጊዜ እዚህ ሰፈር ኢንቨስት ባናደርገው።

አሏህ ረመዷንን አግኝተው አምነውና ተሳስበው ከሚፆሙት ያድርገን።
Nb;
ጽሁፉ የቪዲዮው ትርጉም አይደለም፡ ተያያዥ ማንቂያ ስለሆነ አብሮ የተለጠፈ ነው።
ሸይኽ ዐብዱረሕማን ሱደይስ


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish


ሙሓደራ 221

የተውሒድ አንገብጋቢነት እና በሱ ላይም መፅናት

↪️ በ ቡታጅራ ከተማ የተደረገ ሙሓደራ

🎤 በ ኡስታዝ ኸድር አሕመድ አል ከሚሴ (አቡ ሓቲም)

https://t.me/UstazKedirAhmed/8378


የወርቅ ሜዳለያ ተሸላሚዋ ዛኪራ ተባረክ ••• ኒቃብ ከመማር ከመሸለም ከመምራት አያግድም ብላለች!

ከአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ በሜዲስን 3.87 አምጥታ በዛሬው እለት ተመርቃለች:: መመረቅ ብቻ ሳይሆን ደግሞ በሶስት ዘርፍ ተሸላሚ ሆና ነው የተመረቀችው:: ከሁሉም የህክምና ተማሪዎች አንደኛ ወጥታ ተሸልማለች:: ከሁሉም ሴቶች አንደኛ ወጥታ ተሸልማለች:: ከሁሉም ተማሪዎች አንደኛ ወጥታ የወርቅ ሜዳለያ ተሸልማለች::

እንኳን ደስ አለሽ! እንኳን ደስ አላት! እንኳን ደስ አለንንንን!!

©EHEMSU.


ተሸላሚዋ ራህማ አንሷርም ••• ኒቃብ ከመማር ከመሸለም ከመምራት አያግድም ብላለች::

  እርሷም ከአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ በሜዲስን የተመረቀች ሲሆን ከአጠቃላይ ተማሪዎች 3ተኛ ከሴቶች ሁለተኛ በመውጣት ተሸላሚ ሆናለች::

እንኳን ደስ አለሽ! እንኳን ደስ አላት! እንኳን ደስ አለንንንን!!!

Source: EHEMSU


ነገ ሐሙስ ነው

ወሩም ሻዕባን

ረመዷን is loading ~~~

እርሱ ፆመኛ ሆኖ ስራው አሏህ ዘንድ እንዲቀርብለት የሚፈልግ ነገን ይጹም፡ ይህን ማድረግ ያልቻለ ደግሞ ወንድም/እህቱን ያስታውስ ከሰሪው ላይ ምንም ሳይቀነስ የሰሪውን ያህል ያገኛልና።

ربنا تقبل منا إنك أنت السميع العليم
وتب علينا إنك أنت التواب الرحيم

https://t.me/yedine_guday


መቆሚያ ያጣው የመርከዙ የቁልቁለት ጉዞ!
~
የሸሪዐ ቀዳሚ ግብ ጉዳትን ማስወገድ፣ ካልሆነ መቀነስ እንዲሁም ጥቅምን ማስገኘት ነው። አንዳንዴ የከፋውን ሸር ለማለፍ ወይም ለመቀነስ ሲባል ያነሰውን ሸር እንፈፅም ዘንድ ጫና ሊገጥመን ይችላል። በዚህ የተነሳ ለአጠቃላዩ የደዕዋ መስለሐ ሲባል ውስጣችን የማያምንበት ጉዳይ ላይ ልንነካካ እንችላለን። ይሄ ብስለት አልፎም ድፍረት የሚፈልግ ጉዳይ ነው።

በሌላ በኩል ደግሞ ከእለት ወደ እለት መንሸራተቱን በ "መስለሐ" ወረቀት እየጠቀለለ የሚያቀርብ ብኩን አለ። ማዶ ላይ ያለን "መስለሐ" ሲያስብ ዙሪያውን ስላለው ተጨባጭ አያስብም። "የቆጡን አወርድ ብላ የብብቷን ጣለች" እንደሚባለው ማለት ነው።

የመርከዝ ኢብኑ መስዑድ አካሄድ እዚህ ላይ ነው ያለው። መሪዎቻቸው በዑጅበ ነፍስ የተወጠሩ፣ ቀድራቸውን የማያውቁ፣ "ከኛ ወዲያ መስለሐ እና መፍሰዳ የሚለይ ላሳር" ውስጥ የገቡ ናቸው። ይሄ አዲስ የመጣ ሳይሆን ነባር አመላቸው ነው። በዙሪያቸው ያለው "አገር ለመምራት እድሉ ቢስሰጣቸው መምራት የሚያስችል ብቃት አላቸው" የሚል፣ ቢያጥፉት የሚታጠፍ፣ ቢዘረጉት የሚዘረጋ እንዳሻቸው የሚሰሩት ስብስብ ለራሳቸው የተሳሳተ ግምት እንዲይዙ አድርጓቸዋል። የፈለገ ቢወርዱ "ኧረ አሁንስ በዛ!" የሚል ድፍረት ያለው ከኖረ ከስንት አንድ ነው። እሱውም ከተገኘ። ሰው በዚህ መጠን እንዴት በጋራ ጭፍን ተከታይ ይሆናል? የሚገርም ነው!

ወላሂ! መርከዙን የምታድኑት ኢኽላስን መሰረት ባደረገ እውነተኛ አካሄድ እንጂ በጭፍን ውግንና አይደለም። ሰዎቹንም ሲያጠፉ እጃቸውን በመያዝ እንጂ በጭፍን ብትከላከሉ እነሱንም ላትጠቅሙ ራሳሁንም ትጎዳላችሁ። ይልቁንም ከዚህ "እናንተን የማይታያችሁ ይታየናል" ከሚል አጉል ግብዝነት እንዲወጡ ብታግዟቸው ነው የሚሻለው።
=
የቴሌግራም ቻናል፡-
https://t.me/IbnuMunewor


📖 ሁሌም ምላስህ በዚክር ይርጠብ!

ከአብደላህ ኢብኑ ቡስር ተይዞ፡ ነቢዩ (🤍) ዘንድ አንድ ሰው መጣና፦

﴿إنَّ شرائعَ الإسلامِ قد كثُرَتْ عليَّ فأخبِرْني بشيءٍ أتشَبَّثُ به قال: لا يزالُ لسانُك رطبًا من ذكر اللهِ﴾

“የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! ኢስላማዊ ድንጋጌዎች በርግጥም በዝተውብናል ስለሆነም ጠቅላይ የሆነ የምንጨብጠው ዘርፍ ጠቁሙን አላቸው። እሳቸውም፦ ‘አሸናፊና የላቀውን አላህ በማውሳት ምላስህ ከመርጠብ አይወገድ’ አሉት።”

📚 ሶሂህ አተርጊብ፡ 1491

➖➖➖➖➖➖➖➖

✔️ በነዚህ አድራሻዎች ይከታተሉን፦

✈️፦ https://bit.ly/4ayf0xJ

📞፦ https://bit.ly/486xnrS

👤፦ https://bit.ly/41zEZkk

📸፦ https://bit.ly/4arMbTx

💬፦ https://bit.ly/41tIUPv

🎥፦ https://bit.ly/3UTTSwh


በወንድም ሳሚ የተፃፈ

ለመርከዝ ኢብኑ መስዑድ እና ለነሲሓ ቲቪ አመራሮችና አባሎቻቸው

ምላሹንም የምፈልገው ከጠቀስኳቸው አካላት ነው።

በአደባባይ ያመጣሁትም በአደባባይ የሰሩት ነገር ስለሆነ እና ለዳዕዋው በመቆርቆርም ጭምር ነው።

በተረጋጋ መንፈስ ምላሽ ቢሰጥ መልካም ነው። ከነፍሲያ ወጥተን በመሃል ለታዩ ችግሮች ምላሽ አለመሰጣጠት እንዲሁም በእውቀት እና በስርዓት ምላሽ አለመሰጣጠት በመሃል ያለውን ልዩነት ከማጥበብ ይልቅ ልዩነቱን ወደ ማስፋት ያመራል እና በተረጋጋ መንፈስ መተራረሙ መልካም ነው።

ከነቢያችን ﷺ ወዲህ ከስሕተት የተጠበቀ ሼይኽ፣ ኡስታዝ፣ ጣሊበል-ዒልም እንደሌለ መዘንጋት የለብንም። "ሼይኼ ለምን ተነካ?" ሳይሆን "ምን አድርጎ ነው?" ብለን ማጤን አለብን። ስሕተት ካለ ማረም ከሌለ ደግሞ መመከት።

የመጨረሻው ቅድመ-ጥያቄዬ "ለምን ቀርባችሁ አልተመካከራችሁም?" እንዳይባል ቀርበን ሂደን አውርተናል ግን ከመሻሻል ይልቅ እየባሰ የመጣ ችግር ሁኗል።

-------ጥያቄዬ-------

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በ"መስለሓ" ስም ድሮ ስትኮንኗቸው ከነበሩ ሰዎች ጋር መቀራረብን መመስራታችሁ አደባባይ የወጣ እውነታ ነው፤ በተለይም ከዳዕዋ ቲቪ አባላት (እነ ሼይኽ ሙሓመድ ሓሚዲን እና ባልደረቦቻቸው) ጋር።

አሁን ደግሞ ከአፍሪካ ቲቪ አባላት ጋር ለመስራት እየተቀራረባችሁ እንደሆነም እያየን ነው። "መጥተውባችሁ ነው" እንዳይባል ሄዳችሁባቸው ነው። ማስረጃውንም ኮሜንት ላይ አስፍሬዋለሁ።

ጥያቄዬ:
1- ድሮ ለምን እና በምን ጉዳይ ኮነናችኋቸው?

2- አሁን ላይ ከነሱ ጋር መስራት የጀመራችሁት ድሮ ከነበረባቸው ችግር ተመልሰው ነው ወይስ ድሮ ስትኮንኗቸው የነበረው እናንተው ተሳስታችሁ ነው?

3- ከነበረባቸው ችግሮች ተመልሰው ከሆነ የተመለሱበትን መግለጫ በድምፅም ሆነ በፅሑፍ ያቅርቡ ወይም አቅርቡላቸው።

4- "መጀመሪያም ችግር አልነበረባቸውም" ካላችሁ ለስከዛሬው እናንተው መግለጫ አውጡና ጥፋታችሁን አምናችሁ እኛም እነዚህን መሻኢኾች እንጠቀምባቸው፣ አብረናቸውም እንስራ።

አላህ በሚያውቀው አንድነትን አንጠላም፣ አንድነትን የሚጠላ ልቡ ላይ ችግር ያለበት ሰው ነው፣ አሊያም ስለ አንድነት ያለው ግንዛቤ የተዛባ ነው።

👉 አንድነት ሲባል ግን በዓቂዳም በመንሃጅም አንድ ሲኮን ነው፣ ይሄን ነው ያስተማራችሁን። የሰለፎቻችንን ዓቂዳ ይዞ መንሃጁ ከሰለፎቻችን መንሃጅ ውጪ ከሆነ የአካሄድ ችግር አለበት።

እነዚህ እና መሰል ጥያቄዎች የኔ ብቻ ሳይሆኑ ለናንተ የሚወግኑ ወንድም እህቶች ጥያቄዎች ናቸው።

መልሳችሁን 1- 2- 3- 4- ብላችሁ መልሱልን።

እጠብቃለሁ
Sami Abu Meryem


ነገ ሰኞ ነው
“ሰኞና ሐሙስ ስራዎች ወደ አሏህ ይቀርባሉ። እኔም ፆመኛ ሆኜ ስራዬ እንዲቀርብልኝ እወዳለሁ።“
ረሱሉል አሚን
اللهم صلي على محمد وعلى اله محمد


ከተላመዳቸው ኃጢያቶች በሸዕባን ወር ላይ መቆጠብ ያልቻለ ሙስሊም ረመዳን ሲገባ በአንድ ጊዜ ማቆሙ እንዴት ይቻለዋል?

ሸዕባን የቅድመ ዝግጅትና የመለማመጃ ወር መሆኑን እናስታውስ።
=t.me/Sle_qelbachn1


🔖 በኢሞ ቀጥታ ስርጭት የተደረገ መንሃጃዊ ጥያቄና መልስ

🎙በኡስታዝ ኸዲር አሕመድ [አቡ ሓቲም
-ሐፊዘሁሏህ-

🔗 የካቲት 06/2017 ዓ.ል
የቴሌግራም ቻናል=
https://t.me/UstazKedirAhmed

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.