መንሀጅን በተመለከተ ጠንከር ያሉ ምክር አዘል ንግግሮች!* قال ﺍﻟﻌﻼﻣﺔ ﺍﻟﻤﺤﺪِّﺙ ﻣﻘﺒﻞ ﺍﻟﻮﺍﺩﻋﻲ - ﺭﺣﻤﻪ ﺍﻟﻠﻪ تعالى -”ﻓﺎﻟﺪﻋﻮﺓ ﻋﻨﺪﻧﺎ ﺃﻋﺰ ﻣﻦ ﺃﻧﻔﺴﻨﺎ ﻭﻣﻦ ﺃﻫﻠﻴﻨﺎ ﻭﺃﻣﻮﺍﻟﻨﺎ ﻭﻣﺴﺘﻌﺪﻭﻥ ﺃﻥ ﻧﺄﻛﻞ ﻭﻟﻮ ﺍﻟﺘﺮﺍﺏ ﻭﻻ ﻧﺨﻮﻥ ﺩﻳﻨﻨﺎ ﻭﺑﻠﺪﻧﺎ ﻭﻻ ﻧﺘﻠﻮﻥ ﺍﻟﺘﻠﻮﻥ ﻟﻴﺲ ﻣﻦ ﺷﻴﻤﺔ ﺃﻫﻞ ﺍﻟﺴﻨﺔ“اﻫـ .
* የየመኑ ሊቅ ሙቅቢል አል-ዋዲዒይ (ረሒመሁላህ) እንዲህ ይላሉ፦
«ዳዕወቱ-ሰለፊያ እኛ ዘንድ ከነፍሳችን፣ ከቤተሰቦቻችን እና ከንብረቶቻችን በላይ ናት። (ብናጣ) አፈር ለመብላት ዝግጁ ነን። ዲናችንን አንከዳም። ሀገራችንን አንከዳም። አንቀያየርም። መቀየያር ከሱና ሰዎች መገለጪያ አይደለም።»
ﺍﻟﺒﺎﻋﺚ ﻋﻠﻰ ﺷﺮﺡ ﺍﻟﺤﻮﺍﺩﺙ ص ٥٧.* وقال العلامة ابن العطار - رحمه الله:”لا بد من البيان وعدم الكتمان وإظهار الحق وتبيين الكذب من الصدق والله تعالى يعلم المفسد من المصلح والملبس من الموضح“ اﻫـ .
* ኢብኑል ዐጣር የተባሉት እውቁ ሊቅ (ረሒመሁላህ) እንዲህ ይላሉ፦
«(ሀቅን) ግልፅ ማድረግ፤ አለ-መደበቅ ግዴታ ነው። ሀቅን ፍንትው ማድረግ እና ውሸቱን ከእውነቱ ለይቶ ግልፅ ማድረግ (ግዴታ ነው)። አላህ ደግሞ አበላሹን ከአስተካካዩ እንዲሁም የሚያለባብሰውን ከሚገልፀው ለይቶ ያውቃል።»
رسالة السماع له ص - ٤٨.* وقال العلاّمة أحمد النجمي - رحمه الله:”أما الذين سكتوا عن بيان الحق للناس فإنهم ﻻ يعذرون بسكوتهم ولو قالوا نحن لسنا معهم فإنهم ﻻيعذرون“ اﻫـ .
* እውቀተ-ብዙዉ አህመድ ቢን የህያ አን-ነጅሚይ (ረሒመሁላህ) እንዲህ ይላሉ፦
«እንዚያ ሀቅን ለሰዎች ግልፅ ከማድረግ ይልቅ ዝም ያሉትማ ዝምተኛ ናቸው በማለት አይመካኝላቸውም። እኛ (ከባጢል) ሰዎች አይደለንም! ቢሉ እንኳ አይመካኝላቸውም።»
تحذير السلفي من منهج التميع الخلفي ص - ٣١١.*
وقال شيخ الإسلام بن تيمية رحمه الله:"وصاحب الهوى يعميه الهوى ويصمه فلا يستحضر الله ورسوله في ذلك ولا يطلبه ولا يرضى برضا الله ورسوله ولا يغضب لغضب الله ورسوله بل يرضى إذا حصل ما يرضاه بهواه ويغضب إذا حصل ما يغضب له بهواه"
* የኢስላም ባለውለታው ኢብኑ ተይሚያህ (ረሒመሁላህ) እንዲህ ይላል፦
«ስሜትን የሚከተል ሰው ስሜቱ አሳውሮ ያደነቁረዋል። ስሜቱን ሲከተል አላህ እና መልእክተኛው በልቡ አይሰየሙም (አይፈራም)። መፍራትም አይፈልግም። የአላህ እና የመልእከተኛው ውዴታም አያስደስተውም። የአላህ እና የመልእክተኛው መቆጣት አያስቆጣውም። እንደውም እሱ የሚወደው ነገር ሲገኝ ለስሜቱ ሲል ይደሰታል። እሱን የሚያስቆጣው ነገር ሲገኝ ለስሜቱ ሲል ይናደዳል።»
منهاج السنة له ٢٥٦/٥.*
قال الحافظ ابن القَيِّم - رحمه الله: ”ﻭﻣﻌﻠﻮﻡ ﺃﻧﻪ ﺇﺫﺍ ﺍﺯﺩﻭﺝ ﺍﻟﺘﻜﻠﻢ ﺑﺎﻟﺒﺎﻃﻞ ﻭﺍﻟﺴﻜﻮﺕ ﻋﻦ ﺑﻴﺎﻥ ﺍﻟﺤﻖ ﺗﻮﻟﺪ ﺑﻴﻨﻬﻤﺎ ﺟﻬﻞ ﺍﻟﺤﻖ ﻭﺇﺿﻼﻝ ﺍﻟﺨﻠﻖ“ اﻫـ .
* የሳቸው ኮከብ ተማሪ የሆኑት ኢብኑል ቀዪም (ረሒመሁላህ) ደግሞ እንዲህ ይላሉ፦
«እንደሚታወቀው ባጢልን ከማስተማር እና ሀቅን ግልፅ ከማድረግ ዝም ማለት የተቆራኙ ግዜ በመካከላቸው የሀቅ አለ-መታወቅ እና ፍጥረትን ማጥመም ይፈጠራል።»
الصواعق المرسلة ص - ٥٢.*
وقال العلاّمة ابن عثيمين - رحمه الله:”ﺇﻥ ﻛﻨﺖ ﻭﺣﻴﺪﺍ ﻓﻲ ﺑﻠﺪﻙ ﺗﺪﻋﻮﺍ إلى ﺍﻟﺴﻨﺔ ﻭﺍﺗﺒﺎﻉ ﺍﻟﺴﻠﻒ ﻭﻛﺜﺮ ﺍﻷﻋﺪﺍﺀ ﺍﻟﺬﻳﻦ ﻳﺪﻋﻮﻥ ﺇﻟﻰ ﻣﺬﻫﺒﻬﻢ ﺍﻟﺒﺎﻃﻞ ﻓﺎﻟﻮﺍﺟﺐ ﺃﻻ ﺗﻨﻬﺰﻡ لأﻧﻚ ﺇﺫﺍ ﺍﻧﻬﺰﻣﺖ ﻓﻘﺪ ﻫﺰﻣﺖ ﺍﻟﺤﻖ ﺑﻞ ﺍﺛﺒﺖ ﻭﻣﺎ ﺃﺭﻋﺐ أﻋﺪﺍﺀﻙ ﺇﺫﺍ ﺭﺃﻭﻙ ﺛﺎﺑﺘﺎ“ اﻫـ .
* የዘመኑ ሊቅ የነበሩት ኢብኑ ዑሰይሚን (ረሒመሁላህ) እንዲህ ይላሉ፦
«ሀገርህ ውስጥ ቀደምቶችን ወደ-መከተል እና ወደ-ሰለፍያ የምትጣራ ብቸኛ (ዳዒ) ከሆንክ እና ወደ-ጥመታቸው የሚጣሩ ጠላቶችህ ከበዙ ባንተ ላይ ግዴታው አለ-መሸነፍ ነው። ምክንያቱም አንተ እጅ ከሰጠህ (ባንተ ሲመራ የነበረው) ሀቅ ይወድቃል። እንግዲያውስ ፅና። ጠላቶችህ ፀንተህ ሲያዩህ ለነሱ ምንኛ አስፈሪ ነው?! (ፍርሀት ይወድቅባቸዋል።)»
ﺷﺮﺡ ﺍﻟﻜﺎﻓﻴﺔ ﺍﻟﺸﺎﻓﻴﺔ ٢٠١/١.t.me/abuzekeryamuhamedt.me/abuzekeryamuhamed