[ኢብን ሽፋ - Ibn Shifa]


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


እራስህን ሁል ጊዜ ለቁርኣንና ለሀዲስ ተጎታች አድርግ!
በአንድ ነገር ላይ ከቁርኣንና ከሀዲስ ማስረጃ ሳታገኝ አቋም አትያዝ!
ሁሌም ለሰዎች መልካምን ተመኝ!
ለሀቅ እንጂ ለሰዎች ወጋኝ አትሁን

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


Semir Jemal dan repost
"አቤት የሰለፎች ኢኽላስ!"
"""""""

ሙሐመድ ቢን ዋሲዕ (ረሂመሁላህ) የሚከተለውን አለ፦

«...ከሰለፎች አንዱ ሚስቱ (ባለቤቱ) አጠገቡ ሳለች፣እንዲሁም አሷ ምንም ሳታውቅ ለ"20" አመታት ያክል አልቅሷል።»

📚 [ሲየር አዕላሚን ኑበላእ፡ 6/122]
@semirEnglish


Bahiru Teka dan repost
🎤 የማይታመን የሰለፍያ ማእበል

ክፍል አንድ

ሐቅ የተዳፈነ እሳት ነው ንፋስ አግኝቶ የተቀጣጠለ ቀን ባጠለልን ወሬ ነጋሪ እንዳይኖር አድሮጎ ይፈጀዋል ። ባጢል የፈለገ ቢገን ገናናነቱ ሐቅ እስኪደርስበት ነው ። ሲደርስበት የገባበት ይጠፋል አንገቱን ይደፋል የውርደት ካባ ይከናነባል ።
የሱፍይ የኢኽዋንና ሙመዪዓ ጥምር የባጢል ሀይል እያቅራራና እየፎከረ በኢኽዋን መሪነት ሐቅን ለመቅበርና የሐቅ ባልተቤቶችን ለማንበርከክ መንግስት ነን እኛ ያልፈቀድንለት መኖር አይችልም እስከማለት ደርሶ በቀረርቶና ሽለላ እንደ እንቦሳ በማናለብኝነት ሲፈነጥዝ ብዙዎችን አስፈርቶ ነበር ።
በተቃራኒው የሐቅ ሰዎች እንደ ብረት ሙሶሶ ረግጠው ቆሞው ከቁርኣንና ሐዲስ መርህ ያፈነገጡ ሸሪዓ ደንጋጊዎች ነን የሚሉ የመጅሊስ አመራሮች አይወክሉንም ያሉት ሰለፍዮች ዛሬ ተአምር እያዩ ነው ። እናንተ የተቋም መሪ እንጂ የሀገር መሪ አይደላችሁም ። መመሪያችሁም የተቋም መመሪያ እንጂ የሀገሪቱ ዜጎች የሚተዳደሩበት መመሪያ አይደለም ። እንደ ሀገር ሁሉንም የሚመለከት የዜጎችን የእምነት ነፃነት ያወጀ ህገመንግስት አለ በመሆኑም መብታችን ሊከበር ይገባል ። በናንተ የጭቆናና የአምባገነን መመሪያ አንተዳደርም ብለው በመፅናት ከዳር እስከዳር ሲታገሉ የሐቅ ብርሃን አድማሱን እያሰፋ ደቡብ ፣ ምእራብ ፣ ሰሜን ላይ ጮራውን እየፈነጠቀ የነበረው ሰለፍያ ምስራቁን ክፍል በማይታመን ሁኔታ ባጢልን እያናወጠውና እያሳደደው ነው ።
የፌዴራሉ መጅሊስ መሪ ፕሬዝዳንት ሐጂ ኢብራሂም ቱፋ ከወራት በፊት ምስራቅ ሐረርጌ አመራሮቹን አስከትሎ በመሄድ ሁሉም ዑለሞችና ኢማሞች እንዲሁም ኡስታዞች በግድ እንዲገኙ በማድረግ እኛ ያልፈቀድንለት አይኖርም ። ዝም ስንል የተኛን መሰላችሁ እንደ ውሀ ነን ውሀ ዝም ብሎ የተነሳ ቀን ይበላል ። እኛም ዝም ስንል ያላወቅን እንዳይመስላችሁ እናጠፋችኋለን ። ኬት የመጣ ሰለፍይ ነው ? ሰለፍይ አይደለም ሰለኽይ ነው ። እያለ እያላገጠና እያሸማቀቀ ፎክሮ ከተመለሰ ከጥቂት ወራት በኋላ ነገሩ የተገላቢጦሽ ሆኖ የማይታመን ክስተት ተከሰተ ። ዝም ብለው የነበሩት ዑለሞች በቃ አሉ ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ሐቅ መሰከሩ ። ኢኽዋኖቹ የዘመናችን ቡኻሪይ ሲሉዋቸው የነበሩት የእድሜ ባለፀጋው አንጋፋው ሸይኽ አሕመድ ወተሬ ሰለፍያ ሐቅ ነው አሉ ። አላሁ አክበር !!! አላሁ አክበር !!! አላሁ አክበር !!! ሸይኽ አሕመድን የማያውቅ ምስራቅ ሐረርጌያዊ የለም ። በዙህዳቸውና በዒልማቸው የሚታወቁት የእድሜ ባለፀጋው ሸይኽ አሕመድ ኢኽዋኖች ጃኬታቸውን የሚሰቅሉባቸው የኛ የሚሏቸው ነበሩ ።
እኚሁ ታላቅ ዓሊም ከሳቸው ስር የወጡ በርካታ ዑለሞችንና መሻኢኾን ይዘው ኢኽዋንን በቃ አሉት ። እኛ ሰለፍዮች ነን የመጅሊስ አመራሮች አይወክሉንም ዑለሞች አሉን መመሪያችን ቁርኣንና ሐዲስ በሶሓቦች ግንዛቤ ነው ። የናንተን የሰው ሰራሽ መመሪያ አንፈልግም በቃን አሉ ። ኢኽዋንና ግብረ አበሮቹ ምድር ዞረባቸው ። ስልጣንም ገንዘብም ምንም ማድረግ እንደማይችል አምነው ለመቀበል ተገደዱ ። በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍል መንገድ በሚያጨናንቁ የሰለፍዮች ፕሮግራሞች ናላቸው የዞረው የመጅሊስ አመራዞች ምስራቅ ሐረርጌ ላይ በተፈጠረው ነገር እግራቸው ራሳቸውን መሸከም ያቃተው ይመስላል ። በአላህ ፈቃድ የመሻኢኾቹን የአቋም መግለጫ በሚቀጥለው ክፍል የማቀርብላችሁ ይሆናል ። ሁላችሁም ለእነዚህ መሻኢኾች ረዥም እድሜ ከመልካም ፍፃሜ ጋር ለምኑላቸው እላለሁ ።

https://t.me/bahruteka


[ኢብን ሽፋ - Ibn Shifa] dan repost
የእለተ ጁምዓ ሱንናዎችና ስርኣቶች
—————
መታጠብና መቀባባት
ከሰልማነል ፋሪሲይ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል አለ:- “አንድ ሰው በእለተ ጁምዓ ታጥቦ፣ ከመፀዳዳትም የቻለውንም ተፀዳድቶ፣ ከሚቀባባ ነገርም ተቀባብቶ፣ ቤቱ ውስጥ ከሚገኝ ሽቶ ተቀብቶ፣ ከዚያም ከቤቱ ወጥቶ በሁለት ሰዎች መካከል ካልለያየ፣ ከዚያም የተፃፈለትን ከሰገደ፣ ከዚያም ኢማሙ በተናገረ ጊዜ ዝም ካለ፣ በዚያች ጁምዓ እና በቀጣዩዋ ጁምዓ መካከል ያለውን ወንጀል ይቅር ይባላል።” [ቡኻሪ 883 ላይ ዘግበውታል]

ከሌላ ጊዜ የተሻለ ቆንጆ የሆነውን ልብስ መልበስ
ከሙሀመድ ኢብን የህያ ኢብን ሂባን (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል:- “አንዳችሁ ለእለተ ጁምዓ ከሌላ ጊዜ የተሻሉ ሁለት ልብሶችን ብይዝ የተሻለ ነው” [አቡዳውድ 1078 ላይ የተዘገበ ሲሆን አልባኒ ሶሂህ ብለውታል]

በጊዜ ወደ መስጂድ መግባት
ከአቢሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል:- “በእለተ ጁምዓ ለጀናባ የሚታጠብ አይነትን ትጥበት የታጠበ፣ ከዚያም (ወደ መስጂድ) የተጓዘ ሰው ልክ ግመል ለሶደቃ እንዳቀረበ ነው፣ በሁለተኛው ጊዜ ወደ መስጂድ የተጓዘ ሰው ልክ ለሶደቃ ከብት (ላም) እንዳቀረበ ነው፣ በሶስተኛው ጊዜ የተጓዘ ሰው ልክ ቀንዳማ የሆነ ሙክት እንዳቀረበ ነው፣ በአራተኛው ጊዜ ወደ መስጂድ የተጓዘ ሰው ለሶደቃ ዶሮ እንዳቀረበ ነው፣ በአምስተኛው ጊዜ ወደ መስጂድ የተጓዘ ሰው ለሶደቃ እንቁላል እንዳቀረበ ነው፣ ኢማሙ ሚንበር ላይ ከወጣ መላኢካዎች ኹጥባውን ለማዳመጥ ይሳተፋሉ።” [ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል]

መስጂድ ከገቡ በኋላ በሁለት ሰዎች መካከል አለመለያየት (በሁለት ሰዎች ትከሻ ላይ አለመረማመድ)
ጃቢር ኢብን ዐብደላህ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ አለ:- የአላህ መልእክተኛ ﷺ እየኾጠቡ እያለ አንድ ሰው ገባ፣ ሰዎች ላይ እየተረማመደ ነበርና የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ አሉት:- “ቁጭ በል! በእርግጥም አስቸግረሃል አርፍደሃልም።” [ኢብን ማጀህ 923 ላይ የዘገቡት ሲሆን አልባኒ ሀሰን ብለውታል]

ሱረቱል ከህፍን መቅራት (ማንበብ)
ከአቢ ሰዒድ አል-ኹድሪይ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል:- “በእለተ ጁምዓ ሱረቱል ከህፍን ያነበበ ሰው በእርሱና በበይተል ዐቲቅ መካከል ብርሃን ይበራለታል።” [አልባኒ በሶሂሁል ጃሚዕ 6471 ላይ ሶሂህ ነው ብለውታል።]

ዱዓ ማብዛትና በእለተ ጁምዓ ዱዓ ተቀባይ የሚሆንባትን ሰኣት መጠባበቅ
ዐብደላህ ኢብኑ መስዑድ (ረዲየላሁ ዐንሁ) የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል አለ:- “የጁምዓ ቀን አስራ ሁለት ሰኣት ነው፣ ከእርሷ ውስጥ አንዲት ሰኣት አለች ሙስሊም የሆነ ባሪያ በዚያች ሰኣት አላህን ከጠየቀ አላህ የጠየቀውን ይሰጠዋል፣ (ያቺን ሰኣት) በመጨረሻ ሰኣት ከአስር በኋላ አካባቢ ፈልጓት።” [ሶሂሁል ጃሚዕ 8190 ላይ አልባኒ ሶሂህ ነው ብለውታል።]

ከአነስ ኢብን ማሊክ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል:- “የዱዓ ተቀባይነት የሚከጀልባትን ሰኣት ከአስር በኋላ ፀሀይ ወደ መግቢያዋ እስከምትቃረብ ድረስ ባለው ጊዜ ፈልጓት።” [ትርሚዚይ 1237 ላይ የዘገቡት ሲሆን አልባኒ ሀሰን ብለውታል።]

በነቢዩ ﷺ ላይ ሶለዋት ማብዛት
ከሶፍዋን ኢብን ሱለይም (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል:- “የጁምዓ ቀን እና የጁምዓ ሌሊት ከሆነ (ከገባ) በኔ ላይ ሶለዋት አብዙ።” [በሶሂሁል ጃሚዕ 776 ላይ አልባኒ ሶሂህ ብለውታል።]

ማሳሰቢያ:- ይህ ተግባር የሚመለከተው ወንዶችን ነው። በተለይ ሽቶ ተቀብቶ መውጣት ለሴት ልጅ ሙሉ በሙሉ ሀራም ነው። ሴቶች ምንም አይነት ጌጣጌጥ ያለውን እና ወንዶችን ሊፈትን የሚችል ልብስም ሆነ ሽታ ያለው ቅባትና ሽቶ ሳይጠቀሙ ሙሉ በሙሉ የሴቶችን ሸሪዓዊ ስርኣት ያሟላ አለባበስ ለብሰው በአደብ ወደ መስጂድ መሄዱ አይከለከሉም።
✍🏻ኢብን ሽፋ (t.me/ibnshifa)
የተለያዩ ት/ቶችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችን ⤵️ #join በማድረግ ይቀላቀሉ
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa


አቡ አዒሻ العلم نور dan repost
   አስደሳች ሰበር ዜና  ለሰለፍዮች

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته

كيف نستقبل رمضان☪️

🔊ታላቅ የዳዕዋ  ፕሮግራም ድግስ ተደግሷል በአይነቱ ለየት ያለ የምክር ክትባትና እርጭት ፍቱን ለአማኝ መድሀኒት ስለሆነ ድን መመካከር ነውና  ሁላችሁም ታድማችሆል ኑ ደሮ ግብር

📝 የፊታችን ቅዳሜ ማለትም የካቲት ቀን /15/06/2017/ሁላችሁም  ተጋብዛችኋል

🔍ልዩ ስሟ የቀደምት ከተማ ደሮ ግብር እማ የተባለች ከወልድያ ዝቅ ከመገንጠያ ከፍ ብላ  ያለች በጎራና ትላልቅ ተራራ በመታጀብ ረባዳ የቦታ አቀማመጥ ሁኔታላይ ትገኛለችና ኑ ደሮ ግብር ተውሂድ ይነገር

💫ስለሆናም በአቅራቢያው ያላችሁና ይሄን የዳዕዋ  ጥሪ የሰማችሁ ሰለፍዮች  በሙሉ በተባለው ቦታና ወቅት ሰአት በመገኘት የዳዕዋው ተካፋይና ተቋዳሽ ተጠቃሚ  ይሁኑ

🪑ተጋባዥ የክብር እንግዶቻችን እነሆ ብለናል

➢1.ሸይኽ ሁሴን ከረም ሀራ
➢2.ሸይኽ መሀመድ ሀያት ሀራ
➢3.ሸይኽ ሰይድ ሙሀመድ ሀራ
➢4.ሸይኽ ሙሐመድ ሲራጅ ሀሮ
➢5.ኡስታዝ ሙሀመድ ሰልማን ሀራ
➢6.ኡስታዝ አብዱረህማን መርሳ

🕉እነዚህንና ሌሎችም የክብር ታጋባዥ ዳኢ ዎችና ኡስታዞች  የሚገኙ ይሆናል  ከርሶ የሚጠበቀው በቦታው ላይ በመገኘት ጥሪዎትን ማክበር ብቻ ነው።

🌎በውጭ ለምትገኙ የሱና ወንድሞችና እህቶች ከተቻለ በቀጥታ ስርጭት የ0nlien ሂደት ስለሚኖረን በተባለው ቀንና ወቅት ብቅ ዘለቅ ማለታችሁን እንዳትረሱ አስታውሱ

🕒 የሚጀመርበት ሰአትና ወቅት ከጧቱ 2:30/ሲሆን በአላህ ፍቃድ እስከ 10:00 🕥ድረስ ይዘልቃል ይጠናቀቃል

⚙የፕሮግራም ደጋሽና
አስተናባሪ እንደሁም ጠሪ
የደሮ ግብር ሰለፍያ ወጣት በመተባበር

🗓 የካቲት ቀን/15/06/2017/የፊታችን/ ቅዳሜ/
➷➷➷➷
https://t.me/hussenhas
https://t.me/hussenhas


ابو البيان نورأديس بن سراج dan repost
ልዩ የሙሐደራ ፕሮግራም

እነሁ የፊታችን  እሁድ በቀን 16/06/2017 ታላቅ የሙሐደራ ፕሮግራም ለየት ባለና በማረ ሁኔታ እንኳን መቅረት ማርፈድ የሚያስቆጭ ፕሮግራም  አዘገጅተን እንጠብቃቹሃላን።

በዚህ ፕሮግራም በአሏህ ፍቃድ ወሳኝ ርእሶች የሚዳሰሱበት ይሆናል


እንዲሁም በእለተ ቅዳሜ በ-15-06 በኣልቾ ልዩ ፕሮግራም ተሰናድቶ ይጠብቆታል

        ተጋባዥ  እንግዶች:-
1ኛ.ኡስታዝ  ኑራዲስ ስራጅ  ከቡታጅራ

2ኛ.ኡስታዝ አብራር አወል  ከአዲስ አበባ


3ኛ.ኡስታዝ ዶክተር  ሸምሱ ከቡታጅራ


እና ሌሎችም ኡስታዞች በአላህ ፍቃድ ይኖራሉ

አድራሻ:-ኦዶ ከተማ ትንሽ ገባ ብሎ  መስጂደል ወሊደይን/ሸረፈ ሙስጠፈ


ሰዓት:-ልክ 2:30 ይጀምራል።

ለበለጠ መረጀ ስልክ

ጀማል ኑሪ 0916293446 

ኑሪ መሀመድ 0989606180 


መሀመድ የሲን   ጀማል 0982612475 

ሼርርርርርርርር
                ርርርርር
                   ርርርር
እናርግ ከጁሙዓ ቦኋላ  እናሰዉቅ።


https://t.me/+kn_NBJK5YaBkMWZk


"የረመዷን ማስታወሻ!"
  ክፍል-➀

አል-ኢማም ኢብኑል ቀይም (ረሂመሁላሁ ተዓላ) የሚከተለውን ይላሉ፦ “ፆም ግዴታ የሆነው ከሂጅራው ከሁለተኛው አመት በኃላ ነበር። የአላህ መልእክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ዘጠኝ (9) ረመዷኖችን ፆመው ነበር ከዚች ዓለም የተለዩት...” [ዛዱል መዓድ (2/30)]

አል-ኢማም አን-ነወዊ (ረሂመሁላሁ ተዓላ) በተመሳሳይም እንዲህ ይላሉ፦ “የአላህ መልእክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) በሕይወት ሳሉ፣ ዘጠኝ (9) ረመዷኖችን ነበር የፆሙት። ይህ ፆም ግዴታ ሆኖ የተደነገገው ከሒጅራው በሁለተኛው ዓመት በወርሃ «ሸዕባን» ላይ ነበር። የአላህ መልእክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ሕይወታቸው ከዚች ዓለም ያለፈው፣ከሒጅራው በ 11ኛው ዓመት በረቢዑል አውል ላይ ነበር...” [አል-መጅሙዕ (6/250)]

አል-ሃፊዝ ኢብኑ ሐጀር (ረሂመሁላህ) እንዲህ ይላሉ፦ ከሂጅራው ሁለተኛው ዓመት «የበድር ጦርነት» የተካሄደበት ጊዜ ነው...” [ተልኺሱል ሀቢር (4/89)]

አል-ኢማም ኢብኑል ቀይም (ረሃመሁላሁ ተዓላ) የሚከተለውን ይላሉ፦ “የአላህ መልእክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) በዚህ በረመዷን ወር በተለያዩ ዒባዳዎች ያሳልፉ ነበር፤ለምሳሌ ከጂብሪል (ዐለይሂ ሰላም) ጋር ሆነው  ቁርኣንን ይከልሱ ነበር፤ከሌሎች ወራት በተለየ በዚህ ወር ሶደቃን ይለግሱ ነበር፣አንዲሁም ዚክርን ያበዙ ነበር፣ ኢዕቲካፍም ይገቡ ነበር...” [ሙኽተሰር ዛደል መዓድ (135)]

አል-በይሀቂ (ረሂመሁላህ) በሱነናቸው ላይ ከናፊዕ ተይዞ እንደዘገቡት፡ “ዐብዱሏህ  ኢብኑ ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁማ) በረመዷን በቤታቸው ሶላትን ይሰግዱ ነበር...ከዚያ ሰዎች ከመስጂድ ከወጡ በኃላ፣ኢብኑ ዑመር በእቃ ውሃ ይዘው ወደ መስጂድ አን-ነበዊ ይሄዳሉ። ከሄዱበት የንጋት ሶላትን ሳይሰግዱ ከመስጂድ አን-ነበዊ አይወጡም ነበር። [አል-በይሀቂ ሱነኑል ኩብራ (2/494)]

ኢብኑ ረጀብ (ረሂመሁላህ) እንዲህ አሉ፦ “ዐብዱሏህ ኢብኑ ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁማ) ፆማቸውን ከድሆች ጋር እንጂ አያፈጥሩም ነበር። ቤተሰባቸው ከከለከሏቸው ደግሞ ያንን ሌሊት ሳይመገቡ ይውላሉ፤እንዲሁም ኢብኑ ዑመር ምግብን እየተመገቡ፣የቸገረው ችግርተኛ መጥቶ ከጠየቃቸው ከተቀመጡበት ተነስተው ከመዓዱ ያካፍሏቸው ነበር...” [ለጧኢፍ አል-መዓሪፍ (ገፅ: 233)]

📝Authentic & copyright Salafi free PDFs
𝑻𝒓𝒂𝒏𝒔𝒍𝒂𝒕𝒆𝒅 𝒃𝒚: 𝑨𝒃𝒖 𝑯𝒂𝒇𝒔𝒂𝒉
@semirEnglish


قال لي شيخنا: أحمد النجمي رحمه الله

"وقد ثبت لدينا بالتجربة أن هناك أناسٌ يدخلون في السلفية

لامن أجل تكثير سواد السلفيين ونصرة الحق
والتعاون على البر والتقوى

ولكن من أجل إشاعة الفوضى بين السلفيين ،

ونشر بذور الخلافات ، التي لا تنتهي ؛ بل تُزهِّد في اتِّبَاع المنهج السلفي ،

وهذه مكائد يبثها الأعداء من

حدادية

وإخوانية

وسرورية

وقطبية وغيرهم

فاتركوا هؤلاء ، ولا تقبلوا منهم كلاماً ، ولا تعد و هم من السلفيين ؛ ليكون ذلك سبباً في سلامة منهجكم"


قلت:وليحذر العقلاء من نقل السفهاء لهم ما قد يصح وما لا يصح من أجل إغار الصدور وإثارة الفتن فهم كالفيروسات لا ينشطون إلا في الفتن .فتنبه

كتبه شيخنا أبو الفضل محمد الصويعي _ حفظه الله .
منقول


قناة الشيخ الدكتور حسين بن محمد dan repost
الشيخ سليمان الرحيلي يبشرنا بتحسن حالة الشيخ ربيع المدخلي حفظه الله الجميع


ልዩ የሙሐደራ ፕሮግራም

የፊታችን እሁድ በቀን 16/06/2017  ታላቅ የሙሐደራ ፕሮግራም በመድረሳችን አልኢስላሕ ለየት ባለና ባማረ ሁኔታ እንኳን መቅረት በማርፈድ የሚያስቆጭ ፕሮግራም አዘጋጅቶ ይጠብቃችኋል፡፡ 

ተጋባዥ እንግዶች፡-

1ኛ.   አሸይኽ ዐብዱልሐሚድ ኢብኑያሲን አልለተሚ (ሐፊዘሁሏህ)

2ኛ.   አሸይኽ ሐሰን ገላው (ሐፊዘሁሏህ)

3ኛ.   አሸይኽ ዩሱፍ አሕመድ (ሐፊዘሁሏህ)

በተጨማሪ ሎሎችም ኡስታዞች የሚገኙ ይሆናል፡፡

👌 በአሽይኽ ዓብዱልሐሚድ ኢብኑ ያሲን አልለተሚይ የሚሰጠው ወርሀዊ ፕሮግራማችን ከፊታችን ጁሙዓህ ከአስር ሰላት በኋላ ጀምሮ በተለመደው ሰአት የሚቀጥል ይሆናል፡፡

አድራሻ፡-  አልኢስላሕ መድረሳ ፉሪ ኑሪ ሜዳ ባጃጅ  ተራ መጨረሻ

ሰዓት፡- ልክ 2፡30 ይጀምራል፡፡

ለሴቶች በቂ ቦታ ተዘጋጅቷል!!!!!



የአልኢስላሕ መድረሳ👇👇👇   የተለያዩ ደርሶችን በቀጥታ ስርጭት ለመከታተል እና የሚለቀቁ ደርሶች ለማግኘት የመድረሳውን ቻናል #join በማለት ይቀላቀሉ። https://t.me/medresetulislah


📲 በባለፈው በ 1446 አ/ሒ ሻዕባን 15 - 17 ላይ በተካሔደው የሌራ ኢማሙ አህመድ መስጂድ ታላቁ ኮንፈረንስ በውድ እና ብርቅዬ መሻይኾች፣ አስታዞ እና ዱዓቶች የተደረጉ ሙሀደራዎች ፈትዋዎች ምክሮች ኮርሶች አንደሚከተሉት ታገኛላችው ፋይሎቹን ርእሶቻቸውን ጠቅ በማድረግ ታገኛቸዋላችሁ!

1, ሙሀደራ በሸይኽ ዐብዱል ሀሚድ ሀፊዘሁላህ
"ስለ ታማኝነት እና በጎ መዋል ወይም ማሳመር!!"

2, ሙሀደራ በሸይኽ ዐብዱል ሀሚድ ሀፊዘሁላህ
“እንግዳን በክብር ማስተናገድ በኢስላም አስተምሮ!!”

3, ሙሀደራ በኡስታዝ ሙሀመድ ኪርማኒይ ሀፊዘሁላህ
“ስለ ቁርአን!!”

4, ኹጥባ በሸይኽ ዐብዱል ሀሚድ ሀፊዘሁላህ
“የረመዳን ትሩፋቶች!!”

5, ኮርስ በሸይኽ ዐብዱል ሀሚድ ሀፊዘሁላህ
ሹሩጦ ሶላት ወአርካኑሃ ክፍል አንድ

ሹሩጦ ሶላት ወአርካኑሃ ክፍል ሁለት

ሹሩጦ ሶላት ወአርካኑሃ ክፍል ሶስት

6, ሙሀደራ በሸይኽ መህቡብ አስ’ሳንኩሪይ ሀፊዘሁላህ
“ከቢድዓ ባለቤቶች ጋር ከመቀማመጥ ማስጠንቀቅ ከአህሉ ሱና መሰረቶች መካከል አንዱ ነው!!”

7, ሙሀደራ በሸይኽ ሙባረክ አል-ወልቂጢይ ሀፊዘሁላህ
“ስራን ለአላህ መነጠል!!”

8, ሙሀደራ በሸይኽ ዐብዱል ሀሚድ ሀፊዘሁላህ
"ስለ ተውሒድ፣ አስማእ ወሲፋት እና ኢስቲዋእ!!”

9, ሙሀደራ በኡስታዝ ሙሀመድ ኪርማኒይ ሀፊዘሁላህ
“ምክር በስልጥኛ!!”

10, ሙሀደራ በሸይኽ መህቡብ አስ’ሳንኩሪይ ሀፊዘሁላህ
“ሱናን አጥብቆ መያዝ በስልጢኛ!!”

11, ሙሀደራ በኡስታዝ ባህሩ ተካ ሀፊዘሁላህ
"ስለ ተውሒድ ማስተማር ከሺርክ ማስጠንቀቅ ክፍል አንድ!!”

"ስለ ተውሒድ ማስተማር ከሺርክ ማስጠንቀቅ ክፍል ሁለት!!”

12, ሙሀደራ በሸይኽ ኑሪ ሀፊዘሁላህ
“ስለ ኢስቲቃማ!!”

13, ፈትዋ በሸይኽ ዐብዱል ሀሚድ ሀፊዘሁላህ

14, “አጭር ምክር በኡስታዝ ሱልጣን አል-አሰሊይ ሀፊዘሁላህ!!"

15, “አጭር ምክር በኡስታዝ ኸድር አል-ሀላቢይ ሀፊዘሁላህ!!"

16, “አጭር ምክር በሸይኽ ኸድር አል-ሀዋሲይ ሀፊዘሁላህ!!"

17, “አጭር ምክር በኡስታዝ ፈጅሩዲን አል-አዳሚይ ሀፊዘሁላህ!!"

18, “አጭር ምክር በኡስታዝ ሙህዪዲን አል-ሆሳኒይ ሀፊዘሁላህ!!"

19, “አጭር ምክር በኡስታዝ ኑራዲስ አል-ቡታጀሪይ ሀፊዘሁላህ!!"

20, “አጭር ምክር በኡስታዝ ዐብዱል መጂድ አድ’ዳሎቺይ ሀፊዘሁላህ!!"

21, "የተከበሩ አዛውንት ምስክርነት!!"

አላህ እንደዚህ አይነት ኮንፈረንሶችን ያብዛልን።


✅ሰበር ዜና  ሰበር ዜና
 السَّلاَمُ عَلَيْكُمْ وَرَحْمَةُ اللّٰه  وَبَرَكَاتُهُ



ታላቅ የሙሐደራ ድግስ  በቀቤና ልዩ ወረዳ በጀብዱ ቀበሌ እና  በእጉማ መንደር  ተሰናድቶ ይጠብቃችኃል

🔴 መቼ ነው   ካለቹን በአላህ ፍቃድ የፊታችን ሐሙስና ጁምዓ ማለትም ከቀን 13/06/2017 ጀምሩ ለሁለት ቀን ተከታታይ የሚቆይ ሲሆን

✅ የሙሀደራው  ብርቅዬ ተጋባዥ እንግዶቻችን

🔷 ብርቅዬና ተናፋቂ ከሆኑ መሻይኾች ውስጥ

🎙 አሸይኽ ዐብዱልሐሚድ  ያሲን (ከለተሞ)
🎙አሸይኽ   ሙባረክ አልወለቅጢ  (ከቀቤና)

ከኡስታዞች

🎙ኡስታዝ ባህሩ ተካ        (ከአዲስ አበባ)
🎙ኡስታዝ ሸምሱ ጉልታ   ( ከአዲስ አበባ)
🎙ኡስታዝ አብዱልቃድር   (ከአዳማ)
🎙ኡስታዝ አብዱልቃድር   (ከድንድላ)
እናም በአላህ ፍቃድ ሌሎችም ኡስታዞች ይኖራሉ ኢንሻአላህ

ስለዚህ አይደለም መቅረት ማርፈድ ያስቆጫል
ከተማ ያላቹህ ወንድም እና እህቶች ቤተሰቦቻችንን በስልክ በመቀስቀስ ጨለማ ከሆነው ሸርክ ወጥተው ብርሀናማ ወደ ሆነው ተወሂድ እንዲገቡ የበኩላቹን አስተዋጾ እንድታረጉ ባአላህ ስም እንጠይቃቸዋለን

እናም ባ4ቱም አቅጣጫ የምትገኙ ቤተሰቦቻችን ለዚ በጣም አጓጊና  ተናፋቂ ለሆነው ሙሀደራ ስንጋብዛቹ በታላቅ ደስታ ነው

አላህ እኛንም እናተንም ቀጥ ወዳለው መንገድ ከሚያመላክቱ ባሮቹ  ያድርገን


⚫️ ኢብኑ ሙነወር፣ኸድር ከሚሴው፣ ሳዳት ከማል፣ አቡ ሙስሊም፣ ሰዒድ ሙሳ፣አቡ ሙዓዝ እነዚህ አካላት :-  ድሮ ስለሙመይዓዎች ይህን ይሉ ነበር ዛሬ  በዚሁ ባስጠነቀቁት የተመዩዕ አደጋ ውስጥ ገብተዋል።

ከራሳቸው አንደበት አድምጡት⬇️

ከክፍል 1 እስከ ክፍል 15  ድረስ በቀላሉ ለማግኘት👇👇👇
👉 ክፍል አንድ አቡ ሙስሊም👇

https://t.me/YusufAsselafy/4248

ክፍል ሁለት አቡ ሙስሊም👇
https://t.me/YusufAsselafy/4253

ክፍል ሶስት ኸድር ከሚሴ👇
https://t.me/YusufAsselafy/4269

ክፍል አራት ኢብኑ ሙነወር👇
https://t.me/YusufAsselafy/4272?single

ክፍል አምስት ኸድር ከሚሴ👇
https://t.me/YusufAsselafy/4332

ክፍል ስድስት አቡ ሙስሊም👇
https://t.me/YusufAsselafy/4345

ክፍል ሰባት ሰዒድ ሙሳ👇
https://t.me/YusufAsselafy/4355

ክፍል ስምንት አቡ ሙዓዝ ሀሰን👇
https://t.me/YusufAsselafy/4363

ክፍል ዘጠኝ ሳዳት ከማል👇
https://t.me/YusufAsselafy/4366

ክፍል አስር ኸድር ከሚሴ👇
https://t.me/YusufAsselafy/4423

ክፍል አስራ አንድ ኢብኑ ሙነወር👇
https://t.me/YusufAsselafy/4432

ክፍል አስራ ሁለት ኢብኑ ሙነወር👇
https://t.me/YusufAsselafy/4436

ክፍል አስራ ሶስት ሳዳት ከማል👇
https://t.me/YusufAsselafy/4443

ክፍል አስራ አራት ኢብኑ ሙነወር👇
https://t.me/YusufAsselafy/4521

ክፍል አስራ አምስት ኢብኑ ሙነወር👇
https://t.me/YusufAsselafy/4529

⚠️ የነ ኢብኑ ሙነወር የድሮ አቋማቸው ይህ ነበር አሁን ተቀይራዋል ተንሸራተዋል ስንል በምክንያት ነው።

እኛ አሁንም የምንለው ትናንትና አናንተ ሰትሉት ወደነበረው አቋም ተመለሱ ነው የምንለው።

ሁላቹም መሪዎቹም ሙሪዶቹም ሰከን ብላችሁ ወደ ጤናችሁ ብትመለሱ ይበጃል።
الحَقُّ أَقْوَى مِنَ الرِّجَالِ
ሐቅ(እውነት) ከግለሰቦች ይበልጣል ።


وَالسَّلَامُ عَلَىٰ مَنِ اتَّبَعَ الْهُدَىٰ  سورة طه ٤٧
  ➡️ ሰላም ቀጥተኛውን  መንገድ በተከተለ ላይ ይሁን  ሱረቱ ጧሀ 47


         ✍ አቡ ያሲር ኢብን ሙዘይን!
     https://t.me/YusufAsselafy
   
http://t.me/aredualelmumeyia
http://t.me/aredualelmumeyia


ማብራሪያ

የራያ ቆቦ አህሉ ሱና ወልጀማዓ  ግሩፕ  ላይ በመግባት  የቀጥታ ስርጭት(የሊቭ  
የዳዕዋ ፕሮግራም ስለሚኖር ሁላችንም ቀድመን በመገኘት የዳዕዋዉ ተጠቃሚ እንሁን
ዳዕዋዉ  ላይ የሚገኙ ኡስታዞች

1   ሸይኽ ሙሐመድ ሐያት ከሀራ

2   ሸይኽ ሑሴን ከረም ከሀራ

3 ሸይኻችን ሸይኽ ሁሴን አደም


ናቸው ቢኢዝኒላህ በሰአቱ እንገኝ
ወሰላሙ አለይኩም ወረሕመቱሏህ

የጎብየ አህሉል ሱና ወልጀምዓ የኡስታዝ መዋጮ ጉሩፕ
https://t.me/+BMjspM54MysxOTA8

ንግድ ባንክ  1000676050284
ቡና ባንክ      2409591000256


📚ለሱኒይዎች ብቻ 💐💐💐💐 dan repost
♻️ بــــشــــرى ســـارة ♻️

አስላሙ አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱሁ

🔆  ታላቅ የደስታ ብስራት ለመላው ለሳንኩራና በዙሪያዋ ላላችሁ  ሙስሊሞች በሙሉ

🔆 በብላል ኢብን ረባህ መስጅድ  ታላቅ የደዕዋ ፖሮግራም ተዘጋጀ !!!

🛣  ቦታ  🛣

በመእከላዊ ኢትዮጵያ ክሊል በስልጤ ዞን በዓ/ገበያ ከተማ አስተዳደር በገተም ዚኮ  ቀበሌ ሀጂ ሻፊ መንደር  የፊታችን ሀሙስ የካቲት 13/2017 ዓ.ል

🕰 ሰዐት 🕰

ከጧቱ 3፡00 ሰዓት እስከ ቀኑ 10፡00 ሰዓት

🕰 ግዜው የታላቁ ረመዷን መቀበያ ስለሆነ ፖሮግራሙም እንዴት እንቀበለው

✈️ ተጋባዥ ከመሸይኾች 🛬

🎙ሸይኽ መሕቡብ ከ ሳንኩራ አለም ገበያ  አለህ ይጠብቃቸው

🚗 ከኡስታዞች 🚗

🎤 ኡስታዝ ኢዘዲን ሲራጅ ከሁልበራግ አለህ ይጠብቃቸው

🎤 ኡስታዝ ነስረዲን ከጉጣንቾ አለህ ይጠብቃቸው

🎤ኡስታዝ ሙሰፋ ከድር ከሳንኩራ
አላህ ይጠብቃቸው

🎤 ኡስታዝ ሙሐባ ሱራጅ ከሻድገር አለህ ይጠብቃቸው

🎤አቡ ፋሩቅ ጀማል አህመድን ከሳንኩራ አላህ ይጠብቃቸው

🎤 አቡ አብዱረህማን በህረዲን ሻፊ ከሀላባ አለህ ይጠብቃቸው

🏍 ከገጣሚዎች 🏍

🎧 1 ወንድማችን ኢብን ኑሪ አለህ ይጠብቀው
እናም እንሻ አላህ ሌሎችም የሱና ኡስታዞች እና ወንድሞች ይገኛሉ።

ይህን የመሰለ የሰለፍያ ፖሮግራም አይደለም መቅረት ማርፈድ ራሱ ያስቆጫል

📚 የፖሮግራሙ አዘጋጅ የመድረሳው ጀመዓ ከሳንኩራ ሰለፍይ ወጣት ጀመዓ ጋ በመተባበር !!!

ተጨማሪ ትምህርቶችን ለማግኘት ወደ ቻናላችን #ጆይን ይበሉ 👇👇👇
https://t.me/Ibnushaffi
https://t.me/Ibnushaffi
https://t.me/Ibnushaffi


ልዩ ሙሃዶራ

ርእስ:- መርከቡዋ ከመስመጧ በፊት!!

🎙 በዳዒ ሐዊ ሙሀመድ (ረሂመሁላህ)

🔹በሀቅ ላይ እንደፀና የሙመይዐህ ፊታና ሳይደርስበት ሱንና ላይ እንደፀና ወደ አኼራ የሄደ እጅግ ኸይረኛ ቅን የነበረ ወንድማችን፣ ልብ የሚያረጥብ ሙሃዶራ!!

🔸ምን አለ ዛሬ ላይ ወደ ኢኽዋን ሰተት ብለው የገቡ ልባችን የሚያደሙት የመርከዝ ኢብኑ መስዑድ (የነሲሓ ቲቢ) ሰዎች እንደ ወንድማችን ሐዊ በጥሩ አቋም እያሉ ከምድር በታች በሆኑ ብዬ እመኛለሁ!! በእርግጥ አሁንም ሱናን እየተዋጉ ቢድዓን እያስፋፉ ህዝቡን በማጥመም ወንጀላቸው ከሚጨምር ከምድር በታች ቢሆኑ ይሻላቸዋል!!

👉 እስቲ ዛሬ ላይ ትውት ያደረጋችሁትን በመልካም የማዘዝና ከመጥፎ የመከልከል ኢስላማዊ መርሆ ጥቂት እንኳ ከተገሰፃችሁ ወደ አኼራ ከመሄዱ በፊት የመከራችሁን ልብ አርጣቢ ምክር አድምጡት!!

#Join ⤵️ ቴሌግራም ቻናል
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa


🔸 አዲስ ሙሀደራ

🔊 "ስለ ተውሒድ፣ አስማእ ወሲፋት እና ኢስቲዋእ!!”

🎙በሸይኽ አቡ ዐብዲል ሀሊም ዐብዱል ሀሚድ ያሲን አል-ለተሚይ (ሐፊዘሁላህ)

🔹በስልጤ ዞን ሌራ ከተማ ሀገር አቀፍ ፕሮግራም ላይ የተደረገ

t.me/abuzekeryamuhamed

#Join ⤵️ ቴሌግራም ቻናል
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa


ድካ የደረሰች በገንዘብ የማትተመን ግሳፄ!!
———
ሱፍያን አስ-ሰውሪ (ረሂመሁላህ) ወደ ወንድሞች በላኩት ግሳፄ እንዲህ አሉ:-
“እራሴንም አንተንም አላህን በመፍራት እመክራለሁ!!። ካወቅከ በኋላ አላዋቂ ከመሆን እንድትጠነቀቅ፣ ዓይንህን ከፍተህ ሀቁን መመልከት ከቻልክ በኋላ እንዳትጠፋ፣ መንገዱ ግልፅ ከሆነልህ በኋላ እንዳትተወው አስጠነቅቅሃለሁ!!።
የዱኒያ ሰዎችም ዱኒያን በመፈለጋቸው፣ ለእርሷም በመጓጓታቸውና እሷንም በመሰብሰባቸው እንዳትታለል። ይህም በጣም ከባድ የሆነ አስፈሪ፣ አደገኛና በቅርበት የሚከሰት ነገር ነው።
ወደ አኼራ ከመወሰድህ በፊት አንተ ወደ አኼራ ተጓዝ፣ የጌታህን መልክተኛ ተቀበል፣ ውሳኔ ተወስኖብህ ከምትፈልገው ነገር ሳትለያይ በፊት ሽርጥህን ጠበቅ አድርግ።
በእርግጥ እራሴን በገሰፅኩበት ነገር ነው የገሰፅኩህ፣ መግጠም ከአላህ ነው የመገጠም መክፈቻው ደግሞ ዱዓ፣ ወደ አላህ መተናነስና ከወንጀል ተፀፅቶ መመለስ ነው።
ከዚያም ስራህን ከሚያበላሽብህ ነገር እንድትጠነቀቅ እመክርሃለሁ!፣ ስራህን የሚያበላሽብህ ነገር ለይዩልኝ (ሪያእ) መስራት ነው፣ ከይዩልኝ ብትርቅ እንኳን በነፍሲያህ በመደነቅህ ነው፣ ከወንድምህ በላይ እንደሆንክ እስኪያስመስልህ ድረስ በራስህ እንድትደነቅ ያደርግሃል። ምናልባትም በራስህ ስትደነቅ የተሻልከው የመሰለህ ሰው ከአንተ የተሻለ በስራው የገጠመና ምንዳ የሚያገኝበት ከባድ ስራ ይኖረው ይሆናል፣ ከአንተ በበለጠ መልኩ አላህ እርም ካደረገው ነገር የተሻለ ጥንቁቅ ሊሆንና በስራ ጥራትም ከአንተ የተሻለ ሊሆን ይችላል።
በራስህ ባትደነቅ እንኳ አደራ በሰዎች መወደስን ከመውደድ ተጠንቀቅ!፣ መወደስህ በስራህ እንዲያከብሩህ እንድትወድና በልባቸው ልዩ ደረጃ እንዲሰጡህ፣ አለያም በጉዳይህ እንዲቆሙልህ እንድትፈልግ ያደርግሃል። ይልቅ በስራህ የአላህን ፊት እና የመጨረሻይቱን ቀን ፈልገህ እንጂ ሌላን ፈልገህ መሆን የለበትም!።
ሞትን በብዛት በማስታወስ፣ ከዱኒያ ቸልተኛ በመሆን ለአኼራ ተነሳሽነት (ፍላጎት) ይኑርህ! ምኞትህ ረዝሞ ፍርሃትህ በማነሱና ወንጀልን በመዳፈርህ ተጠንቀቅ!፣ እውቀት እንጂ ስራ የሌላቸው የሆኑ ሰዎች በእለተ ትንሳዔ በመቆጨታቸውና በመፀፀታቸው ተመከርበት።” [ሂልየቱ'ል አውሊያእ አል-አስበሃኒ]
✍🏻ኢብን ሽፋ (t.me/ibnshifa)
#Join ⤵️ ቴሌግራም ቻናል
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa


🍁موعظة بليغة لاتقدر بثمن🍁

✍🏼 قال سفيان الثوري - رحمه الله -
في وصيته إلى أحد إخوانه يعظه :

* أوصيك وإياي بتقوى الله, وأحذرك أن تجهل بعد إذ علمت, وتهلك بعد إذ أبصرت, وتدع الطريق بعد إذ وضح لك,

* ولا تغتر بأهل الدنيا بطلبهم إياها وحرصهم عليها وجمعهم لها, فإن الهول شديد, والخطر عظيم, والأمر قريب,

* وارتحل إلى الآخرة قبل أن يرتحل بك, واستقبل رسل ربك, واشدد مئزرك من قبل أن يقضى قضاؤك, ويحال بينك وبين ما تريد,

* فقد وعظتك بما وعظت به نفسي, والتوفيق من الله ومفتاح التوفيق الدعاء والتضرع والاستكانة والندامة على ما فرطت,

* ثم إياك وما يفسد عليك عملك فإنما يفسد عليك عملك الرياء, فإن لم يكن رياء فإعجابك بنفسك حتى يخيل إليك أنك أفضل من أخ لك,

* وعسى أن لا تصيب من العمل مثل الذي يصيب, ولعله أن يكون هو أورع منك عما حرم الله ، وأزكى منك عملا,

* فإن لم تكن معجبا بنفسك فإياك أن تحب محمدة الناس ومحمدتهم أن تحب أن يكرموك بعملك ، ويروا لك به شرفا ومنزلة في صدورهم ، أو حاجة تطلبها إليهم في أمور كثيرة,

* فإنما تريد بعملك وجه الدار الآخرة لا تريد به غيره ، فكفى بكثرة ذكر الموت مزهدا في الدنيا, ومرغبا في الآخرة,

* وكفى بطول الأمل قلة خوف, وجرأة على المعاصي, وكفى بالحسرة والندامة يوم القيامة لمن كان يعلم ولا يعمل.

📚|[حلية الأولياء - الأصبهاني]|


Bahiru Teka dan repost
👉 የሌራን ኮንፈረንስ ልዩ የሚያደርገው ምንድነው ?

የሌራ ሀገር አቀፍ ኮንፈረንስ ከሌሎች ለየት የሚያደርገው ብዙ ነገር ቢኖርም በዋነኝነት 3 ነገሮችን ልጥቀስ : –
1 – አስገራሚ ማኔጅመንት
ፕሮግራሙ በጣም አስገራሚ በሆነ ሁኔታ ማኔጅ ተደርጎ ነበር ። ለዚህ ትልቁን ድርሻ የወሰደው ወንድማች ዐ/ሀዲ ሲሆን አላህ ይጨምርለትና በሚገርም ሁኔታ ፕሮግራሙን ከመጀመሪያ እስከመጨረሻ ማኔጅ አድርጎታል ። እንግዶቹን የተቀበሉበትና ያስተናገዱበት ሁኔታ አስደማሚ ነበር አላህ ይቀበላቸው ።

2 – የአካባቢው ሴቶች ተሳትፎ
በጣም በሚገርም መልኩ የአካባቢው ሴቶች ኮሚቴው ካዘጋጀው መስተንግዶ ውጪ ለእንግዶች መቀበያ እንዲሆን አዋጥተው አንድ ሰንጋ ገዝተው በመስጠት ኮሚቴውን ካስደነገጡ በኋላ ላጠቃላይ በሺዎች ለሚቆጠረው እንግዳ ቁርስ አዘጋጅተው አብልተዋል ። ይህ በጣም የሚገርም የሴቶቹ ተግባር አላህ በመልካም ስራ መዝገባቸው ላይ አስፍሮ ለጭንቁ ቀን ስንቅ ያድርግላቸው የሚል ዱዓእ እንዲደረግላቸው አድርጓል ።

3 – የኻዲሞቹ ቅንጅት
በርግጥ በዚህ ነጥብ ላይ የጉንችሬና የሓራ ኻዲሞች የሚጋሩዋቸው ቢሆንም የእነርሱን ለየት የሚያደርገው አንድ ነገር አለ ። እሱም ሌሎቹን ሳይጨምር የወጥ ቤት ኻዲሞች ብቻ አዋጥተው ለወላኢታ ዩንቨርሲቲ ተማሪዮች ለመድረሳ ኪራይ ድጎማ 11 ሺህ ብር ለግሰዋል ። እነርሱንም አላህ ይቀበላቸው እንላለን ።
ባጠቃላይ ፕሮግራሙ ልዩ ትዝታ በሰለፍዮች አእምሮ ላይ ጥሎ አልፏል ምስጋና ለዓለማቱ ጌታ የተገባ ይሁን ።

http://t.me/bahruteka


ባወቅከው ሸሪዓዊ እውቀት ስራበት!!
———
ሸይኽ ሙሀመድ ቢን ሷሊህ አል-ዑሰይሚን (ረሂመሁላህ) እንዲህ አሉ:- “በአሁን ጊዜ አንዳንድ የዲን ተማሪዎች ከገጠሬ የበለጠ ደረቆች ናቸው፣ የፊት የደስ ደስ (ፈገግታ) የለ፣ ሰላምታ ማስቀደም የለ፣ መተናነስ የለ፣ ይልቅ አንዳንድ ሰዎች (በአላህ እንጠበቃለን!) እውቀታቸው በጨመረ ቁጥር ኩራታቸው ይጨምራል። እውነተኛ አዋቂ ማለት እውቀቱ በጨመረ ቁጥር መተናነሱን የሚጨምር ማለት ነው።”
[ሊቃእ አልባብ አል-መፍቱህ 232]
#join ⤵️ ቴሌግራም ቻናል
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.