[ኢብን ሽፋ - Ibn Shifa]


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


እራስህን ሁል ጊዜ ለቁርኣንና ለሀዲስ ተጎታች አድርግ!
በአንድ ነገር ላይ ከቁርኣንና ከሀዲስ ማስረጃ ሳታገኝ አቋም አትያዝ!
ሁሌም ለሰዎች መልካምን ተመኝ!
ለሀቅ እንጂ ለሰዎች ወጋኝ አትሁን

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


ኢማም ኢብኑ ባዝ (አላህ ይዘንላቸውና) እንዲህ ይላሉ:-

ሱናን አጥብቆ መያዝ ቢድዓን መጠንቀቅ አላህን ከማመስገን ነው! በእርግጥ ብዙ ሰዎች ሌላውን አካል አርዓያ በማድረግና በጭፍን በመከተል በቢድዓ ላይ ይፈተናሉ! መንስዔውም መሃይመነት ነው! ቢድዓ የአላህን ፀጋ ከማስተባበልና ለአላህ سبحانه وتعلى  ምስጋና ካለመኖር ነው!።”
[መጅሙዕ አልፈታዋ 5/175]
#join ⤵️ ቴሌግራም ቻናል
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa


የኮንፈረሱ ግሩፕ ነው ተቀላቀሉ ሼር አድርጉት በረካላሁ ፊኩም
👇👇
https://t.me/+UgqkmJcBqhFjZmY0


በአይነቱ ልዩ የሆነ ታላቅ ኢስላማዊ ኮንፈረንስ

የኮንፈረንሱ መሪ ቃል “ዲናችንን ማወቅ መተግበርና ማስተማር”

🏝 የኢትዮጵያ አህለ ሱና ኢስላማዊ ማህበር ታላቅ ሀገር ቀፍ ኢስላማዊ ኮንፈረንስ ጥቅምት ላይ   በአዲስ አበባ ከተማ ለማካሄድ አስቧል።
ለዚህ ፕሮግራም የአዳራሽ ኪራይ፣ ለተሳታፊዎች ሻይ ቡና ፣ ለዑለማዎች ትራንስፖርትና ማረፊያ ወዘተ የሚያስፈልገውን ወጪ ለመሸፈን እንዲቻል የአንድ ሰው መግቢያ ትኬት 1000 ብር ነው።

🔹 ስለሆነም ትኬት በአካል መግዛት ለምትፈልጉ፦
➡️  አል ኢስላሕ መድረሳ
➡️  ዳሩ ሱና የሸሪዓ እውቀት ማዕከል

🔹በባንክ አካውንት ለምትጠቀሙ
የባንክ አካውንት ቁጥር፦ 1000650550718
          ሙሒዲን ሳሊሕ እና ዩሱፍ ኸድር

   የኢትዮዽያ አህሉ ሱና ኢስላማዊ ማህበር

https://t.me/alateriqilhaq


አላህ ትክክለኛ ወደርሱ የሚጣሩ ዳዒዎችን ያብዛልን!!

:
አቢ ሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) የአላህ መልእክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል አለ:-
:
“ወደ ቀናው መንገድ የተጣራ ሰው የተከተሉትን ሰዎች አይነት ምንዳ አለው፣ እሱም ከተከታዮች ምንዳ አንዳች ሳይቀነስ ነው።
ወደ ጥመት የተጣራ ሰው የተከተሉትን ሰዎች አይነት ወንጀል አለው፣ እሱም ከተከታዮች አንዳች ወንጀል ሳይቀነስ ነው።”
[ሙስሊም ዘግበውታል]
:
አላህ ህዝበ ሙስሊሙን ከጥመትና ከቡድንተኝነት ተጣሪዎች ይጠብቅ!!
✍🏻ኢብን ሽፋ #join ⤵️ ቴሌግራም ቻናል
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa


ሶሪህ አስ-ሱንና

⏯ ክፍል 5

🎙በሸይኽ ዶ/ር ሑሰይን ቢን ሙሀመድ አስ-ሲልጢ (ሀፊዘሁላህ)

በዳር አስ-ሱንና የሸሪዓ እውቀት ማዕከል
⏱ቅዳሜና እሁድ ከመግሪብ እስከ ዒሻእ

ከተዳሰሱ ነጥቦች
- ከሐቅ ጎን መቆም ግዴታ ነው
- ጥቅል ቃላትን የመጠቀም አደጋ
- የባሙሳው ዘገሉ ደዕዋ ኪታብ
- የሙሀመድ አል ኢማም አል ኢባና
- ሪፍቀን አህሉሱንና ቢአህሉሱና ኪታብ
- ኢልያስ አህመድ፣ ኢብኑ ሙነወር፣ ኸድር ከሚሴና ሙሀመድ ሰዒድ
- ከዛም ከዚህም የማይሆኑ ሙዘብዘብ ሰዎች አደገኝነት

የዳር አስ-ሱንና የቴሌግራም 👇👇 ቻናል #join በማድረግ ይቀላቀሉ
https://t.me/DarASSunnah1444
https://t.me/DarASSunnah1444


የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ dan repost
ምክር ከሸይኽ ረቢዕ (1).pdf
866.0Kb
''የ ሙስሊሞች ተጨባጭ ሁኔታ እና ከገቡበት አረንቋ መውጫ መንገዱ - ከሸይኽ ረቢዕ ምክሮች'' በሚል ርዕስ በተከታታይ ስድስት ክፍሎች በቻናላችን ሲለቀቅ የነበረዉ የሸይኽ ረቢዕ ብን ሀዲ አልመድኸሊ ወቅታዊ ምክር የተተረጐመበት ፅሁፍ እነሆ በ PDF ተዘጋጅቶ ለአንባቢያን ቀረበ ።

ሼር በማድረግ የአጅሩ ተካፋይ እንሁን
አላህ አንብበው ከሚጠቀሙት ያድርገን!
የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ

كن على بصيرة

https://t.me/alateriqilhaq


የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ dan repost
የባህር ዳር አህለሱና መሻይኾች ገፅ

https://t.me/alateriqilhaq

كن على بصيرة


Muhammed Mekonn dan repost
#አዲስ_መፅሐፍ
👉 በ ቅ ር ብ ቀን

አንድ ሰው ከሰለፍያህ የሚወጣው መቼ ነው?❞ በሚል ርዕስ የተዘጋጀ በዘመናችን ለተከሰቱ ፊትናዎች መፍትሔ የሚሆን ወሳኝ ኪታብ ነው።

📝 ዝግጅት፦ የተከበሩ ሸይኻችን ሸይኽ አቡ ዘር ሀሰን ኢማም አቡ ጦልሃ አል`ወሎውይ አላህ ይጠብቃቸው!

📨 ለማንኛውም ጥቆማ ➴➷➴
https://t.me/AbuImranAselefybot
                ➚➶➹ ብቅ ይበሉ

🏝 የኪታቡ pdf በሸይኹ ቻናል እና በሌሎችም ቻናሎች በቅርቡ ይለቀቃል።
➷➴➷➴➷➴➷
https://t.me/UstazAbuzarhassenAbutolha


👆👆👆በተለይ ሰለፊይ የሆነ ሰዉ ከእንደዚህ አይነት ባህሪ ሊርቅ ይገባል።

ሀሜትና ወሬ ማመላለስ በአሁን ሰዓት በሰለፊዮች መካከል ሰርፆ የሚገኝ አደገኛ በሽታ ነው።
አብዛኛዉ በማካከላቸዉ የሚመጣዉ ኺላፉ ከእነዚህ ሁለት በሽታዎች ነዉ።
ለአኼራዉ የሚጨነቅ ሰዉ ማንኛዉንም ወሬ ሳያጣራና ከባለቤቱ ሳያረጋግጥ ማውራት ዬለበትም።
አብዛኛዉ ሰዉ እያደረገ ያለዉ ግን በተቃራኒዉ ነዉ፣ የሆነ ሰዉ የሆነ ወሬ ይሰጠዋል እሱ ከባለቤቱ ሳያረጋግጥ ቶሎ ብሎ እርምጃ ይወስዳል።

አገሌ እንዲህ ብሏል ወይም አገሌ እንዲህ አድርጓል ስትባል የነገሩን ምንጭ በደንብ ማጥናት ይኖርብሃል። ይህን ያለዉ ሰዉ ለምንና ከምን አንፃር እንደተናገረዉ ሳታውቅ ወደ አቋም መያዝ አትሂድ።

እንደዉም አብዛኛዉ ሰዉ የመንሃጅና የዱንያን ልዩነት ለይቶ አያውቅም። አንድ ወንድምህ በሆነ ነገር ሲሳሳት ያ የተሳሳተበት ነገር ዱንያዊ ጉዳይ ነው ወይስ መንሃጃዊ ብለህ መለየት ግድ ነው።
ወደድንም ጠላንም ከአንድ ወንድማችን በሆነ ነገር ባንስማማና ያ ነገር መንሃጃዊ እስካልሆነ ድረስ ከሶስት ቀን በላይ መኮራረፍ አይቻልም።
ታዲያ ከማሀላችን ስንቱ ነዉ መንሃጃዊ ባልሆነ ነገር ከሶስት ቀን በላይ የሚኮራራፈዉ?። ከዚህም አልፎ መንሃጃዊ ባልሆነ ነገር ደእዋዉን ለመጉዳት የሚንቀሳቀስ ስንት ኣለ!?።

ከሆኑ ሰዎች ጋር በሆነ ነገር ስላልተስማማህ ብቻ ደዕዋን ለመጉዳት መንቀሳቀስ ወይም ደዕዋዉን ለመጉዳት ማሰብ አላዋቂነት ነዉ።
እንደዚህ የሚያረጉ ሰዎች እንደዉም ደዕዋ ሰለፊያ ካለማወቅ ይመስለኛል። ሰለፊያን ጠንቅቆ የሚያውቅ ሰዉ እያንዳንዱ ንግግሩ፣ እያንዳንዱ አካሄዱ በጥንቃቄ የተሞላ ነዉ።
አንድን ንግግር መቼና ዬት ለምን እንዴት መናገር ወይም መተግበር እንዳለበት ያውቃል።

በአጠቃላይ ሰለፊያን በትክክል የሚያውቅ ሰዉ ስሜቱን ከሰለፊያ ደዕዋ አያስቀድምም።
እያንዳንዱ እንቅስቃሴዉ ወይም ንግግሩ ከሰለፊያ ጥቅምና ጉዳት ጋር ያመዛዝናል። ለግለሰቦች ጥቅም ሳይሆን ለደዕዋዉ ጥቅም ይንቀሳቀሳል።


ምክሩ ለራሴም ጭምር ነው።

t.me/ibnawolllll
t.me/ibnawolllll
t.me/ibnawolllll


ዳር አስ-ሱንና Dar As-sunnah Channel dan repost
👇
ነገ እለተ ቅዳሜ ከ4:00 ጀምሮ ፕሮግራም አለ

التصفية والتربية
አት-ተስፊየህ ወ'ተርቢየህ
ሊሸይኽ ዶ/ር ሑሰይን አስ-ሲልጢ (ሀፊዘሁላህ)
(ተከታታይ ሳምንታዊ የእሁድ ኮርስ) ሲሆን ለቀጣዩ እሁድ ሸይኹ ሌላ ፕሮግራም ስላለባቸው የቀጣዩ እሁድ ለነገ ቅዳሜ ይሰጣል።
ላልደረሰው በፍጥነት በማዳረስ የአጅሩ ተካፋይ ሁኑ

ዳር አስ-ሱንና የሸሪዓ እውቀት ማዕከል

የዳር አስ-ሱንና የቴሌግራም 👇👇 ቻናል #join በማድረግ ይቀላቀሉ
https://t.me/DarASSunnah1444
https://t.me/DarASSunnah1444


ሐሜትና ወሬ አመላላሽነት መልካም ስራን ባዶ ያደርጋል
———
ሰዒድ ኢብን ጁበይር (ረሂመሁላህ) እንዲህ አለ:-
“በእለተ ትንሳዔ ለአንድ ባሪያ የስራው መዝገብ ይመጣና ይከፈትለታል፣ መዝገቡ ላይም የሶላትም ሆነ የፆም ውጤት አይመለከትበትም፣ ወደሰራው መልካም ስራም ቢመለከት የለም፣ ይህን ጊዜ "ጌታዬ ሆይ ይህ እኮ የሌላ ሰው መዝገብ ነው፣ የኔ የስራ መዝገብ አይደለም፣ ምክንያቱም ለኔ መልካም ስራዎች ነበሩኝ እዚህ መዝገብ ላይ ደግሞ የሉም።" ይላል፣ ለእርሱም ምላሹ እንዲህ ይባላል:- ጌታህ አይስትም አይረሳም፣ ስራህ እንዳለ ሰዎችን በማማትህ ጨርሶ ሄዷል። ይባላል፣
አደራ!! ወንድም እህቶቼ ሐሜትንና ወሬ አመላላሽነትን ተጠንቀቁ!! ሁለቱም ዲንን ይጎዳሉ!! የመልካም ሰሪንም ስራ ያበላሻሉ!!። አላህ ይጠብቀንና በሙስሊሞችም መካከል ጥላቻን ያስወርሳሉ።”
[በህር አድ-ዱሙዕ ሊብን አል-ጀውዚ 133]
✍🏻ኢብን ሽፋ
#join ⤵️ ቴሌግራም ቻናል
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa


ኢሬቻ
አለም ቢያከብረው እንኳን ከእስልምና የሚያስወጣ ሺርክ ነው!!
ሺርክ ማለት ደግሞ ዘለአለም በጀሀነም ዘውታሪ የሚያደርግ በአንድ አምላክ አላህ ላይ የማጋራት ተግባር ነው!! ኢሬቻ ሙስሊሞችን የማይወክል በሺርክ የተሞላ ተግባር ነው!!
ሙስሊሞች ተጠንቀቁትም አስጠንቅቁም!!
:
#join ⤵️ ቴሌግራም
https://t.me/IbnShifa


🔷 በቴሌግራም መዘረፍ
      ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯


👉 ነዋይ ያሰ
ከራቸው ሰርቶ መክበር ሳይሆን ዘርፎ መበልፀግ የሚል መርህ ይዘው የሚንቀሳቀሱ በሰዎች ለቅሶ የሚያተርፉ አካላት እየበዙ ነው።
    
👌 እነዚህ አካ
ላት ለዘረፋቸው እንደግብኣት የሚጠቀሙት የተማረ የሰው ሀይልን ነው። ለዘረፋቸው የዘረጉትን መረብ ተቀባይነት እንዲያገኝ መጀመሪያ የሚያሳምኑት የተማሩትን ሰዎች ነው። ከዛ በፒራሚድ አካሄድ እየሰፋ እንዲሄድ ያደርጋሉ። ከታች በመላ ሀገሪቱ የተዘረጋው መረብ ከላይ እንደ ጎጆ ቤት ሙሶሶ ጫፍ ይጠባል። ይህ አሰራር ነው ፒራሚድ የሚባለው። በዚህም ሰፊው ህዝብ ከስሮ ከላይ ያሉት ጥቂቶች ይከብራሉ ማለት ነው።
    
➪ በየደረጃው ላለው ምስኪን ባጭር ጊዜ ትበለፅጋለህ ይባላል። መጀመሪያ ቶሎ ቶሎ የተወሰነ ገንዘብ እየሰጡ ማኖ ያስኩና ዳጎስ ያለ
ገንዘብ አስገብቶ በዛው ልክ ትርፍ ታገኛለህ ይባላል። በመረቡ ወጥመድ ውስጥ የገባው ምስኪን ከራሱም ከዘመድና ከጓደኛ ለቃቅሞ በሰከረ ስሜት ገቢ ያደርጋል። ይህን ሲያደርግ የወሰደውን ወዲያው መልሶ ከድህነት ጋር ላይገናኝ ሲሰናበት እያሰበ ነው። ነገር ግን የሚፈለገው ገንዘብ መጠን ካስገባ ከደቂቃዎች በኋላ ከንቅልፉ እንደነቃ ሰው ምን እንደሰራ በሰመመን ማሰብ ይጀምራል። በብልፅግና መርከብ ሲያንሳፍፉት የነበሩ መስመሮች ሁሉ ዝግ ይሆናሉ። ዙሪያው ይጨልምበታል ኢማን ያለው የአላህ ባሪያ ከሆነ በኢማኑ ተጠብቅ ወደራሱ ይመለሳል። ካልሆነ ዙሪያው ገደል ሆኖበት ወደ ዘላለማዊ ጥፋት ሊያመራ ይችላል።
      
➩ የነዚህ መረብ ባለቤቶች ያሰከሯቸው አንዳንድ ወንድምና እህቶች ሙስሊሙን ነጋዴ በዚህ መረብ አስገብተው እንዲዘረፍ እንዲያደርጉ ተልእኮ የተሰጣቸው መሆኑን ሳያውቁ ረዥም ርቀት ይጓዛሉ። የሚገርመው ዑለሞችን ጭምር በሸሪዓ ይፈቀዳል ስላልገባችሁ ነው እንጂ እያሉ ይሞግታሉ።‼
   
🏝 ለማንኛውም የመሸጥና የመግዛት ስርኣት በኢስላም ሸሪዓ ካለው መስፈርት የተወሰኑትን እንይ፦
▶ በሁለቱ ሰዎች መካ
ከል ስምምነት መኖሩ
▶ የሚሸጠው ነገር በሸሪዓ ለመጠቀሚያነት የተፈቀደ መሆኑ
▶ ሻጩ የሚሸጠው ነገር የራሱ የሆነ ወይም የተወከለ መሆኑ
▶ የሚሸጠው ነገር ለመረከብ የሚቻል ነገር መሆኑ
▶ የሚሸጠው ነገር በማየት የሚታወቅ ወይም አይነቱ በማያሻማ መልኩ የሚታወቅ መሆኑ
▶ የሚሸጥበት ዋጋ ሽያጩ ሲፈፀም (በገዘዢና በሻጭ) መካከል የታወቀ መሆኑ የሚሉት ይገኙበታል።
      
➜ ይህ ሸሪዓዊ የሆ
ነ ግብይት ለማካሄድ ኢስላም ያስቀመጠው መስፈርት ሲሆን በነዋይ የሰከሩ አካላት ለሺያጭ ብለው የሚያቀርቡት ዋጋው የሚታወቅ እቃ የላቸውም። ይልቁንም የሚሸጡት ምኞትን ነው። በወስፍም ይሁን በአይነ
የሚታወቅ ነገር የለም። በተለያየ ጊዜ ስሙንና መልኩን እየቀያየሩ ከሚያመጡዋቸው የግብይት አይነቶች ውስጥ የሚከተሉትን ይገኙበታል፦
➩ ቲያንሺ

➪ ቢትኮይን
➪ ክሪፕቶ ካረንሲና የመሳሰሉት። እነዚህ የግብይት አይነቶች ምንም አይነት ሙንደቢጥ የሆነ የግብይት ስርኣት የሌላቸው የፈጠሩዋቸው አካላት እንደፈለጉ የሚዘርፉባቸው ናቸው።
     
👉 ክሪፕቶ ካረንሲ የተባለው የግብይት አይነት በሀገራችን በቴሌግራም ግሩፕ ተከፍቶ እየተሰራበት ያለ ላም አለኝ በሰማይ ወተትዋንም አላይ አይነት የማጭበርበሪያ መንገድ ነው። ግሩፕ ላይ ተቀላቅለህ ሰው እንዲቀላቀል አድርግ በተቀላቀለው ሰው ልክ ብር ታገኛለህ በሚል የምኞት ማእበል እያናወጡ መጨረሻ ላይ ምትሀት በሚመስል መልኩ አስክረው በመቶ ሺና በሚሊየን ወደ አካውንት እንድታስገባ ይደረጋል። የምታስገባው ገንዘብ ወዲያው ወደ ሌላ አካውንት ትራንስፈር ይደረጋል ። ሀገራችን የዚህ አይነቱን ግብይት የሚከለክል ህግ ስላለ ማንንም መጠየቅ አትችልም ። ምናልባት ባንኮች ቢተባበሩህም የሰዎቹን የረቀቀ ሌብነት ከመንገር ውጪ የሚያደርጉት ነገር የለም ። በቀን ለማመን የሚያስቸግር ትራንዛክሽን (ዝውውር) አላቸው። በየቀኑ በሚሊየኖች ነው እየዘረፉ የሚያዘዋውሩት። ማንነታቸውን ማወቅ አትችልም። አብዛኞቹ ከናይጄሪያ፣ ከኬንያና የተለያዩ ሀገራት ወደ ሀገራችን መጥተው ከኛዎቹ የሰው ጅቦች ጋር ነው አብረው የሚሰሩት። አካውንት የሚከፍቱበት ሁኔታ በጣም የተጠናና የረቀቀ ስለሆነ በምንም መልኩ ወደ ገንዘቡ መድረስ አይቻልም። በተለይ የህግ ክልከላ መኖሩ ለእነርሱ በጣም ተጠቃሚ ያደርጋቸዋል። የሚያዋጣው አላህ በሰጠህ ነገር ተብቃቅተህ ከእንደዚህ አይነት ቁማር መራቁ ነው።

http://t.me/bahruteka


قناة الشيخ الدكتور حسين السلطي dan repost
قال العلامة ابن عثيمين
-رحمه الله-:

"حاول أن تبتعد عن كل شيء يجلب الهم والحزن والغم لتكون دائمًا مستريحًا منشرح الصدر مقبلاً على الله عز وجل وعلى عبادته؛ وإذا جربت هذا استرحت،أما إن أتعبت نفسك بما مضى أو بالاهتمام بالمستقبل على وجهٍ لم يأذن به الشرع فاعلم أنك ستتعب ".

📚شرح بلوغ المرام ٩/١٣٨


ውድ  የሱንና ጓደኛህን ደረጃውን እወቅለት!!
———
"በእጅ ያለ ወርቅ እንደመዳብ ይቆጠራል" እንደሚባለው አታድርገው።

ከታላቆች መንደር ይህቺን ምክር አጥብቀህ ያዝ
👇👇

ሸይኽ ሱለይማን አር-ሩሀይሊ (ሀፊዘሁላህ) እንዲህ ይላሉ:-

“እውነተኛ፣ መካሪና በሱንና (ዲኑ) ላይ ቀጥ ያለ፣ ባለው መልካም ነገርም ላንተ የሚለግስ የሆነን ጓደኛ ካገኘህ፣ በክራንቻ ጥርስህ አጥብቀህ ያዘው። እርሱ ውድ ከሆኑ መዓድኖች ነው፣ ካመለጠ አይመለስም።”

إذا وجدت الصديق الصادق الناصح المستقيم على السنة الباذل ماعنده من خير لك فتمسك به وعض عليه بالنواجذ فإنه من أغلى الكنوز وإذا فات لا يعوض

[ከሸይኽ ሱለይማን አር-ሩሀይሊ የቲዊተር ገፅ ያገኘሁት]
✍🏻ኢብን ሽፋ

#join ⤵️ ቴሌግራም ቻናል
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa


أركان طلب العلم للشيخ محمد بن علي آدم اﻹتيوبي حفظه الله

https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa




🔹ሸይኽ ረቢዕ -  ሀፊዞሁሏህ - የሚከተለውን ተናገሩ:-
"ከዚህ ቦታ ፣ በሙስሊሞች ሶፎች ውስጥ የተሰገሰጉ (ተንኮለኞች)  አልሉ።  ከእነርሱ መካከል የሰለፍያን ካባ ደርቦ  የተሰገሰገውን (ተንኮለኛ) ታያለህ! በውሸት እና በማጨበርበር ሰዎችን ወደእርሷ (ወደ ሰለፍያ) በስሜት ይቀሰቅሳል ፤ (የውጭ) ጠላት ሊፈጽመው የተሳነውን ወጣቶችን የመከፋፈል ፣ የመበታተንን ስራ እርሱ ይሰራል። ለእነዚህ ተጨቃጫቂዎችና ተንኮሎቻቸው መንቃት ይገባል!"

"التوجهات للشباب"  ص/٥٧

https://t.me/alateriqilhaq

كن على بصيرة


قناة الشيخ الدكتور حسين السلطي dan repost
‏صورة من حسين عبد الله


📌በቀዷና በቀደር ማመን
(ከሸህ ሷሊህ ፈውዛን - ሀፊዞሁሏህ - ደርስ በአማርኛ ተተርጉሞ የቀረበ)

(ክፍል አምስት)

ክፍል 1 ⤵️ (ያለፉ ክፍሎች)
https://t.me/alateriqilhaq/5054
ክፍል 2 ⤵️
https://t.me/alateriqilhaq/5057
ክፍል 3 ⤵️
https://t.me/alateriqilhaq/5060
ክፍል 4 ⤵️
https://t.me/alateriqilhaq/5062

በቀዷ በቀደር የማመን ፍሬዎቹ

በቀዷ በቀደር ከማመን ፍሬዎች  ትልቁ ፣ የግለሰቡ እምነት ጤናማ ሆኖ ማእዘኖቹ መሟላታቸው ነው፡፡  ምክንያቱም ቁርዓን እና ሱና እንደሚጠቁመው ፣ በዚህ ማመን በእርሱ እንጅ እምነት የማይረጋገጥበት ከሆኑት ከስድስቱ ኢማን መሰረቶች አንዱ በመሆኑ ነው፡፡

በቀዷ በቀደር በማመን ከሚገኙ ፍሬዎች መካከል የልብ መረጋጋት እና እረፍት ይገኛል፡፡ በዚህ አለም በሰው ልጅ ሂዎት ላይ ችግሮች ሲጋረጡ መጨናነቅ አይኖርም፡፡ ምክንያቱም የሰው ልጅ የአላህ መልክተኛ እንደተናገሩት የሚደርስበት ነገር ሁሉ በአላሀ ውሳኔ መሆኑን ካወቀ ፣ ““እወቅ የሚደርስብህ ነገር የሚስትህ አይደለም ፤ የሚስትህ ደግ የሚደርስብህ አይደለም” የሚለውን የአላህ መልክተኛ ንግግር ከተገነዘበ እንዲሁም የሚደርስበት ነገር የማይቀር ፣ ምንም አይነት መላሽ የሌለው መሆኑን ከተገነዘበ  ነፍሱ ትረጋጋለች ፣ ልቡ የተደላደለ ይሆናል፡፡ 

በዚህ ተቀራኒ በቀዷ በቀደር የማያምን ፣ ሀሳብ እና ሐዘን ትይዘዋለች፡፡ ጭንቀት ይረብሸዋል፡፡ በሂዎት ተጨናንቆ ከእርሷ ለመገላገል  ራሱን እስከማጥፋት ይደርሳል፡፡  ከደረሰባቸው ችግር  ለመሸሽ እና የወደፊት ተስፋቸው በመጨለሙ ከዚህ ነገር ይገላግለናል ብለው ራሳቸውን የሚያጠፉ ሰዎች ቁጥር መብዛቱ የሚስተዋል ነው - ምክንያቱም እነርሱ በቀዷ በቀደር አያምኑምና፡፡ ይህ እንቅስቃሴያቸው የአቂዳቸው መጥፎነት ውጤት ነው፡፡

አላህ የሚከተለውን ተናግሯል

“በምድርም በነፍሶቻችሁም መከራ (ማንንም) አትነካም ፣ ሳንፈጥራት በፊት በመጽሐፍ የተመዘገበች ብትሆን እንጅ፡፡ ይህ በአላህ ላይ ገር ነው፤ (ይህ ማሳወቃችን) ባመለጣችሁ ጸጋ ላይ እንዳታዝኑ ፣ አላህም በሰጣችሁ ነገር (በትዕቢት) እንዳትደሰቱ ነው፡፡ አላህም ኩራተኛን ጉረኛን ሁሉ አይወድም፡፡”

(ሀዲድ ፡22-23)

አላህ በምድርም ይሁን  በነፍሶች ውስጥ የሚከሰቱ መከራዎች የተወሰኑ መሆናቸውን ተናገረ፡፡ የፈለግነውን መከላከል ብንሞክር እርሱ ተወስኗል ፣ ተጽፏል ፣ ከመከሰት የማይቀር ጉዳይ ነው፡፡  ከዚያም  ይህን ያደረገበት  ጥበቡ የመከራ ጊዜ  እንድንረጋጋ ፣ እንዳንበሳጭ ፣ እንዳንቆጭ ፤  ጸጋ ስናገኝ ደግሞ ቅጣትን የሚያስረሳ ደስታ እንዳንደሰት መሆኑን አላህ ግልጽ አደረገ፡፡  ይልቁንም የመከራ ጊዜ ትግስት ማድረግ ፣  ከአላህ ረህመት ተስፋ አለመቁረጥ በእኛ ላይ ግዴታ ነው፡፡ የምቾት ጊዜ ማመስገን ፣ አላህ  አዘናግቶ እኛን አይዘንም ብለን አለመተማመን፡፡  አላህ በሁለቱም ባህሪዎች ከእርሱ ጋር ቁርኝት እንዲኖረን ይፈለጋል፡፡

ኢክሪማ የሚከተለውን ተናገረ“አንድም አካል አይኖርም ፣ የሚደሰት ወይም የሚያዝን ቢሆን እንጅ፡፡  ነገር ግን ደስታን አድርጉት ምስጋና ፣  ሀዘንን አድርጉት ትግስት፡፡”

ይህ ማለት ግለሰቡን  ከመጥፎ የሚጠብቁ ፣ መልካም የሚያመጡ ሰበብ ነገሮችን አይጠቀም ማለት አይደለም፡፡ አንዳንድ ጃሂሎች እንደሚገምቱት በቀዷ በቀደር ይመካ ማለት አይደለም፡፡   ይህ ትልቅ የሆነ ስህተት እና ማህይምነት ነው፡፡ አላህ  ሰበብ ነገሮችን እንድንጠቀም አዞናል ፣ ከስንፍና እና ከቸልተኝነት ከልክሎናል፡፡ ነገር ግን ሰበብ ነገሮችን ተጠቅመን  በምንፈልገው ተቃራኒ ከተከሰተ መናደድ የለብንም - ምክንያቱም ይህ ቀዷ ቀደር ነውና፡፡ ሌላ ቢወሰን ኖሮ ፣ ይሆን ነበር፡፡ በዚህ ምክንያት ነብዩ የሚከተለውን ተናግረዋል ፡ 

“በሚጠቅምህ ነገር ላይ ፍላጎት ይኑርህ፡፡ በአላህ ታገዝ፡፡ አትቆጭ፡፡ አንድ ነገር ቢገጥምህ ፣  ይህን ብሰራው ኖሮ ፣ እንዲህ እንዲህ ይሆን ነበር አትበል፡፡ ነገር ግን አላህ ወሰነው የፈለገውን ሰራ በል፡፡ “ለው” ያለችው ቃል የሰይጣንን ተግባር ትከፍታለች፡፡” ሙስሊም ዘግቦታል፡፡

ይህ ከመሆኑ ጋር ግለሰቡ ነፍሱን ሂሳብ ያድርግ፡፡  ስህተቶቹን ያርም፡፡  አንድም ነገር አይደርስበትም ፣  በወንጀሎቹ ሰበብ እንጅ፡፡

አላህ የሚከተለውን ተናግሯል

“ከመከራም ማንኛውም ያገኛችሁ ነገር እጆቻችሁ በሰሩት (ሐጢአት) ምክንያት ነው፡፡” (ሹራ ፡ 30)

https://t.me/alateriqilhaq

كن على بصيرة

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.