Addis መረጃ™


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


@Addis_Mereja ቀዳሚ የመረጃ ምንጭ 🇪🇹 🇪🇹
.
⏬ምርት እና አገልግሎቶን ለማስተዋወቅ ከፈለጉ⏬
⏬ ꜰᴏʀ ᴘᴀɪᴅ ᴘʀᴏᴍᴏᴛɪᴏɴ ⏬

መረጃዎችን ለመላክ @Adis_Merejaa_bot

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


📍አዲስ አበባ

የህዝብ ትራንስፖርት ታሪፍ ላይ ጭማሪ ተደረገ፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ትራንስፖርት ቢሮ ዛሬ አዲስ ታሪፍ ይፋ አድርጓል።

በዚህም በሕዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ላይ በተሰማሩ ሚኒ-ባሶች ፣ ሚዲ-ባስ ታክሲዎችና የከተማ አውቶብሶች ላይ የአገልግሎት ታሪፍ ጭማሪ ተደርጓል።

አዲሱ ታሪፍ ከነገ ጥቅምት 06 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ተብሏል።

ጭማሪ በተደረገበት በአዲሱ ታሪፍ ዝቅተኛው 10 ብር ሲሆን ከፍተኛው 65 ብር ገብቷል።

" ቀድሞ አገልግሎት ሲሰጥበት የነበረው የታሪፍ ተመን ከጥቅምት 20 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ አገልግሎት ላይ የዋለ ነበር ፤ ስሌቱም የነዳጅ ጭማሪ ዋጋን ብቻ ታሳቢ ያደረገ ነበር " ሲል ቢሮው ገልጿል። የአሁን አዲስ ታሪፍ ወቅታዊ የነዳጅ የችርቻሮ ዋጋ እና ሌሎች አስተዳደራዊ ወጪዎችን ያማከለ እንደሆነ አመልክቷል። የህዝብ ትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች አዲስ በተሻሻለው ህጋዊ የታሪፍ ተመን ብቻ አገልግሎት እንዲሰጡ አሳስቧል።

(የአዲሱ ታሪፍ ዝርዝር ከላይ ተያይዟል)

@Addis_Mereja


የኢትዮጵያ አየር መንገድ በ #አፍሪካ የመጀመሪያ የሆነ ግዙፍ አውሮፕለን በተያዘው ጥቅምት ወር እንደሚረከብ ገለጸ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውና ''Ethiopia land of origins'' በሚል መጠሪያ የተሰየመውን ኤ350-1000 የመንገደኞች አውሮፕላን በተያዘው ጥቅምት ወር ከኤርባስ ኩባንያ እንደሚረከብ ገለጸ።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው፤ 400 መቀመጫዎች ያሉት ኤ350- 1000 አውሮፕላኑ በአይነቱ ልዩና ለደንበኞች የላቀ አገልግሎት መስጠት የሚያስችል ዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተገጠመለት መሆኑን ለኢዜአ ተናግረዋል።

አቶ መስፍን፤ አየር መንገዱ በአፍሪካ የአቪዬሽን መስክ ያለውን የቀዳሚነት ድርሻውን ለማስቀጠል በየጊዜው አዳዲስ አውሮፕላኖችን በማስመጣት እንዲሁም ዓለም አቀፍ መዳረሻዎቹን በማስፋት ላይ ይገኛል ብለዋል።

አየር መንገዱ ኤ350-900 አውሮፕላኖችን መጠቀም ከጀመረ ሰባት ዓመታትን ያስቆጠረ መሆኑን ጠቅሰው አሁን ላይ ሃያ የኤ350- 900 አውሮፕላኖች በስራ ላይ መሆናቸውንም አንስተል።አየር መንገዱ በአሁኑ ወቅት ባሉት 147 አውሮፕላኖች 139 ዓለም አቀፍና 22 የሀገር ውስጥ የበረራ መዳረሻዎችን እየሸፈነ ይገኛል ተብሏል።

@Addis_Mereja


በትራምፕ የምርጫ ቅስቀሳ አቅራቢያ ሁለት ሽጉጥና ሐሰተኛ ፓስፖርት ይዞ የተገኘው ግለሰብ ታሰረ!

ዶናልድ ትራምፕ በካሊፎርኒያ የምርጫ ቅስቀሳ እያደረጉ ባሉበት መድረክ አቅራቢያ ሁለት ያልተመዘገቡ ሽጉጦች ይዞ ተገኝቷል የተባለው ግሰለብ በቁጥጥር ሥር መዋሉን ፖሊስ ገለፀ።የ49 ዓመቱ ተጠርጣሪ ቬም ሚለር ጥቁር መኪና እየነዳ ሳለ ነው በፖሊስ እንዲቆም ታዞ ፍተሻ የተደረገበት። ፖሊስ ከመኪናው ውስጥ ሁለት ሽጉጥ እና “ብዙ ጥይቶች ያሉት ካርታ” ማግኘቱን ይፋ አድርጓል።

በቁጥጥር ሥር የዋለው ግለሰብ ምርመራ እየተደረገበት እንደሆነ የአካባቢው ፖሊስ ኃላፊ አሳውቀዋል።የአሜሪካ የደኅንነት መሥሪያ ቤት ሲክሬት ሰርቪስ ግለሰቡ ለትራምፕ “አደጋ የሚሆን አይደለም” ብሎ ምንም ዓይነት ግርግር እንዳልተፈጠረ አስረድቷል።

የአካባቢው ፖሊስ በቁጥጥር ሥር የዋለውን ግለሰብ “ወፈፌ” ሲሉ የገለፁት ሲሆን የትራምፕ ምርጫ ቅስቀሳ ታዳሚዎች ላይ ምንም ዓይነት ጉዳት አልደገነም ብለዋል።

ነገር ግን አሁንም በርካታ ጥያቄዎች ምላሽ አላገኙም።የሪቨርሳይድ ክፍለ ግዛት ፖሊስ ኃላፊ ተጠርጣሪው ምን ዕቅድ እንደነበረው ማወቅ ከባድ ቢሆንም ግለሰቡ ግን ፖሊስ ፕሬዘደንቱን ከሶስተኛ የግድያ ሙከራ እንደታደጋቸው ነው “የሚያምነው” ይላሉ።

ግለሰቡ በቁጥጥር ሥር የዋለው በአካባቢው ሰዓት አቆጣጠር ከሰዓት 11፡00 ሲሆን ትራምፕ የምርጫ ቅስቀሳ ለማድረግ አንድ ሰዓት ቀርቷቸው ነበር።የአሜሪካ ምርጫ ድምፅ መስጫ ቀን ሶስት ሳምንታት ይቀሩታል። በየቦታው እየዞሩ የምረጡኝ ቅስቀሳ እያደረጉ የሚገኙት ዶናልድ ትራምፕ ከባድ የሚባል ጥበቃ እየተደረገላቸው ነው።

[BBC]
@Addis_Mereja


የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር መስመር አዋሽ አካባቢ መጠነኛ ጉዳት አጋጠመው!

የኢትዮ-ጅቡቲ የባቡር መስመር አዋሽ አካባቢ መጠነኛ ጉዳት እንደደረሰበት ተገለጸ፡፡15 ሜትር ርዝመት ያለው የባቡር ሃዲዱ ብረት ወደ መሬት መስጠሙን እና አንዳንድ የሃዲዱ ማሰሪያዎች (ማያያዣዎች) መቆራረጣቸውም ተገልጿል፡፡

የኢትዮ-ጅቡቲ ባቡር አክሲዮን ማኅበር ዋና ሥራ አስፈጻሚ ታከለ ኡማ (ኢ/ር) የጉዳት መንስኤ እየተጣራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡የተፈጠረውን መጠነኛ ጉዳት በፍጥነት በማስተካከል መስመሩን ወደ ሙሉ አገልግሎት ለመመለስ ርብርብ እየተደረገ መሆኑንም አመላክተዋል፡፡

@Addis_Mereja


በሬክተር ስኬል 4.6 አካባቢ የተመዘገበ የመሬት መንቀጥቀጥ ዛሬ ጠዋት 1 ሰዓት ከ37 ደቂቃ ከ50 ሴኮንድ ላይ ባለፈው በተከሰተበት አዋሽ ፈንታሌ አካባቢ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጂኦፊዚክስና ስፔስ ሳይንስ ዳይሬክተር ዶክተር ኤሊያስ ሌዊ ለብሔራዊ ጣቢያ ተናግረዋል።

የመሬት መንቀጥቀጥ ንዝረት አዲስ አበባ ድረስ መሰማቱንም ነው የገለጹት። ለመሬት መንቀጥቀጡ ምክንያት የሆነው ቅልጥ አለት መሬት ውስጥ መምጣቱ መሆኑ የተናገሩት ዶክተር ኤሊያስ ይሄው እንቅስቃሴ ወደላይ አለመወጣቱን ነው የተናገሩት።

ላለፉት 19 ተከታታይ ቀናት ያህል ተመሳሳይ እንቅስቃሴዎች መኖራቸውን እና አሁንም ያለውን ሁኔታ እየተከታተልን ነው ብለዋል።

@Addis_Mereja


በአዋሽ ፈንታሌ ዛሬ ጠዋት ላይ የመሬት መንቀጥቀጥ ተከሰተ!

ዛሬ ከጠዋቱ 1 ሠዓት ከ37 ገደማ በአዋሽ ፈንታሌ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን ሠማራ ዩኒቨርሲቲ አስታውቋል፡፡በዩኒቨርሲቲው የምርምርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዚዳንት አደም አሊ ጉዳዩን አስመልክተው ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት እንደገለጹት÷ ዛሬ ጠዋት በአዋሽ ፈንታሌ በተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ እስከ አሁን የተለየ ጉዳት የለም፡፡

ቀደም ሲል በፈንታሌ ዛሬ ጠዋት ደግሞ በአዋሽ ፈንታሌ የመሬት መንቀጥቀጥ መከሰቱን በመግለጽ÷ የሚመለከታቸው አካላት በነዋሪዎች ላይ ጉዳት እንዳይደርስ አስፈላጊውን ሥራ እንዲያከናውኑ ጠይቀዋል፡፡

በተለይም በአዋሽ ፈንታሌ ግድብ ከመኖሩ ጋር ተያይዞ በመሬት መንቀጥቀጡ ጉዳት  ቢደርስበት የሚያስከትለውን አደጋ በመገንዘብ በአካባቢው ያሉ ነዋሪዎችን ወደ ሌላ ቦታ የማዛወር ሥራን ጨምሮ ሌሎች የቅድመ ጥንቃቄ ተግባራትን ማከናወን እንደሚገባ መክረዋል፡፡

በሌላ በኩል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ጨምሮ ዘርፉ የሚመለከታቸው ድርጅቶች በአካባቢው ስላለው ሁኔታ ጥናት በማካሄድ ጉዳት ከመድረሱ በፊት ሣይንሳዊ ግኝቶችን ማሳወቅ እንደሚጠበቅባቸው ገልጸዋል፡፡

[FBC]
@Addis_Mereja


የጥቅምት 1 ረፈድ ዋና ዋና የአለም ዜናዎች፡-

⚡️የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን በቱርክሜኒስታን በሚካሄደ አለም አቀፍ መድረክ ላይ ለመሳተፍ ቱርክሜኒስታን ገብተዋል። ከጉባኤው ጎን ለጎን የሁለትዮሽ ስብሰባዎች ሊኖሩ ይችላሉ፤ በዚህም ከኢራን ፕሬዚዳንት ጋር ይወያያሉ።

⚡️10 የዩክሬን ሰው አልባ አውሮፕላኖችን በአንድ ሌሊት ማውደሙን የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አስታውቋል።

⚡️የእስራኤል መከላከያ ሰራዊት በዌስት ባንክ ቱልካርም ከተማ አክራሪ የፍልስጤም "አስላማዊ ጅሃድ " ቡድን መሪን መገደሉን አስታወቀ።

⚡️የአሜሪካ ፕሬዝዳንታዊ እጩ ዶናልድ ትራምፕ ካማላ ሃሪስን በ2 በመቶ እየመሩ መሆኑን የራስሙስሰን ተቋም በጥቅምት ወር መጀመሪያ ላይ ባደረገው የሕዝብ አስተያየት መሰብሰቡን ገለፀ

⚡️አሜሪካዊው ቢሊየነር እና ሥራ ፈጣሪ ኤሎን ማስክ በቴስላ ሾፌር አልባ ሮቦታክሲን አስተዋወቀ።

⚡️ሩሲያ እና ቻይና በፓስፊክ ውቅያኖስ ሰሜናዊ ክፍል የባህር ዳርቻ ጠባቂ መርከቦችን ለመጀመሪያ ጊዜ በጋራ ሲቆጣጠሩ መቆየታቸውን የሩሲያ የፌደራል ደህንነት አገልግሎት አስታወቀ።

@Addis_Mereja


የግብጹ ፕሬዝዳንት ከሶማሊያና ኤርትራ መሪዎች ጋር የሶስትዮሽ ጉባዔ ለማድረግ አስመራ ገቡ

የግብጹ ፕሬዝዳንት አብደል ፈታ አልሲሲ ከሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሃሰን ሼክ ሞሃመድ እና ከኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈውርቂ ጋር የሶስትዮሽ ጉባኤ ለማድረግ አስመራ ገቡ።

በትላንትናው ዕለት የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሃሰን ሼክ ሞሃመድ ኢርትራ መግባታቸው እና ‘በሶማሊያ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት’ ዙርያ ከኢሳያስ ጋር ውይይት ማድረጋቸው ተገልጿል።

የኤርትራ የማስታወቂያ ሚንስትር የማነ ገ/መስቀል የግብጽ እና የኤርትራ መሪዎች የሁለትዮሽ ግንኙነታቸውን በማሻሻል እና ሌሎች የጋራ ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚወያዩ ገልጸዋል። ይህንንም ተከትሎ የግብጹ ፕሬዝዳንት አብደል ፈታ አልሲሲ፣ የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሃሰን ሼክ ሞሃመድ እና ከኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈውርቂ የሶስቱን አገራት ግንኙነትን ለማጠናከር እንዲሁም በቀጠናው ጸጥታ እና መረጋጋት ዙሪያ የሶስትዮች ጉባኤ ያደርጋሉ ተብሏል።

@Addis_Mereja


የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር መሪ "ግብፅ የአየር ጥቃት ፈጽማብኛለች" አሉ!

የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር መሪ መሀመድ ሃምዳን ዳጋሎ (ሄሜቲ) "ግብፅ በወታደሮቻችን ላይ የአየር ድብደባ ትፈጽማለች፣ ለሱዳን ጦርም ሥልጠናና ሰው አልባ አውሮፕላኖችን ትሰጣለች" ሲሉ ከሰዋል፡፡

የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ትላንት ባወጣው መግለጫ ሄሚቲ ትላንት ረቡዕ ባሰሙት ንግግር ያሰሙትን ክስ በማስተባበል “ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በሄሜቲ የቀረበው ክስ የእውነት ስለመሆኑ ማስረጃ መኖሩን እንዲያጣራም” አሳስቧል፡፡

ሄሚቲ “ግብጽ ለሱዳን ጦር ድጋፍ እየሰጠች ነው” በማለት የከሰሱት፣ ለ18 ወራት ያህል በዘለቀው ጦርነት የሱዳን ጦር ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የበላይነት እያገኘ መጥቷል በተባለበት በዚህ ወቅት መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

ግብፅ የሱዳኑ ጦር መሪ ጀኔራል አብደል ፋታህ አል ቡርሃን የቅርብ ወዳጅ ተደርጋ ብትታይም ግጭቱን ለመሸምገል ጥረት ከሚያደርጉት ከዩናይትድ ስቴትስ እና ሳኡዲ አረብያ ጋር አብራ ሰርታለች፡፡ ካይሮ የተቀናቃኞቹን ወገኖች ውይይት በዚህ ዓመት መጀመሪያ ላይ አስተናግዳለች፡፡

ሄሚቲ በቪዲዮ በተቀረጸ መልዕክታቸው “በዚህ ግጭት ግብፅ በፈጸመችው የአየር ጥቃት የአሜሪካ ቦምቦችን ተጠቅማለች” ብለዋል፡፡“አሜሪካውያኑ ባይስማሙ እነዚህ ቦምቦች ሱዳን አይደርሱም ነበር” ሲሉም ሄሚቲ አክለዋል፡፡

“ሀገሪቱ ውስጥ የትግራይ፣ የኤርትራ፣ የአዘርባይጃን እና ዩክሬን ቅጥር ነፍሰ ገዳዮች ታይተዋል” ያሉት ሄሚቲ “ኢራናውያን ከሱዳን ጦር ጎን በመሆን በጦርነቱ ተሳትፈዋል” የሚለውን ክስ በድጋሚ አሰምተዋል፡፡

የሱዳን ጦር በቅርቡ በሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም እና በደቡብ ምስራቅ ግዛት ጀብል ሞያ አካባቢ ድል ቀንቶታል፡፡ ጀብል ሞያ ሄሚቲ ወታደሮቻቸው ከስትራቴጂያዊ አካባቢ ተገፍተው እንዲወጡ ግብጽ የአየር ጥቃት ፈጽማለች ያሉበት አካባቢ ነው፡፡

ቀደም ሲል የታየውን የሰላም ፍላጎት ድምጸት በሚለወጥ መልኩ የፈጥኖ ደራሹ ጦር መሪ ባሰሙት ንግግር “ ይህ ጦርነት በአንድ ወይም በሁለት ሶስት እና አራት ዓመታት ውስጥ አያልቅም፡፡ አንዳንዶች ስለ አንድ ሚሊዮን ወታደር ያወራሉ በቅርቡ አንድ ሚሊዮን እንገባለን” ብለዋል፡፡

እኤአ በመጋቢት 2023 የጀመረው የሱዳን ጦርነት ወደ 10 ሚሊዮን የሚደርሱ ሰዎችን ከቤት ንብረታቸው አፈናቅሏል፣ ረሀብን በከፍተኛ ደረጃ አስፋፍቷል፥ በአብዛኛው ፈጥኖ ደራሹ ጦር ተጠያቂ ነው የሚባልበትን ብሄር ተኮር የሆኑ ጥቃቶች እንዳስነሳ የሮይተርስ ዘገባ አመልክቷል፡፡

@YeneTube @FikerAssefa


ኢትዮጵያ በታሪኳ በቡና ምርት ከፍተኛውን ገቢ ማግኘቷ ተገለፀ!

በኢትዮጵያ ታሪክ ከፍተኛ ነው የተባለለት 1.43 ቢሊየን ዶላር የቡና የውጭ ምንዛሬ መገኘቱን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታውቋል።

ባለፈው ዓመት 3 መቶ ሺህ ቶን የሚጠጋ ቡና ለዓለም ገበያ ቀርቦ ከ1.4 ቢሊየን ዶላር በላይ መገኘቱን የተጠቆመ ሲሆን በቡና ምርት ከብራዚል እና ቬትናም ቀጥላ በዓለም 3ኛ የሆነችውን ኢትዮጵያን ከቬትናም ጋር እኩል ለማድረግ ምርት ማሳደግ ላይ በትኩረት እንደሚሰራም ተጠቁሟል፡፡ ኢትዮጵያ በዓለም ገበያ 1 ኪሎ ግራም ቡናን በ103 ሺህ ብር መሸጥ መቻሉ ይታወሳል፡፡

@Addis_Mereja


መንጃ ፍቃድ❗️

ከአዲስ መንጃ ፈቃድ ውጭ ያሉ ሁሉም መንጃ ፈቃዶች ከነገ ጀምሮ በየአራት ዓመቱ እንደሚታደሱ ተገለፀ!

ከአዲስ መንጃ ፈቃድ እና ዕድሜያቸው ከ55 በላይ ከሆኑ ግለሰቦች ውጭ ያሉ ሁሉም መንጃ ፈቃዶች ከነገ ጀምሮ በየአራት ዓመቱ እንደሚታደሱ የአዲስ አበባ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፍቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን አስታውቋል፡፡

ባለሥልጣኑ ባለፉት 6 ዓመታት የመልካም አስተዳደር እና የፍትኃዊነት ጥያቄን ሲያስነሳ የነበረው የሁለት ዓመት እና የአራት ዓመት የመንጃ ፈቃድ ዕድሳት ጥያቄ ምላሽ ማግኘቱን ገልጿል።

በዚህም ከአዲስ መንጃ ፈቃድ እና ዕድሜያቸው ከ55 በላይ ከሆኑ ግለሰቦች ውጭ ያሉ ሁሉም መንጃ ፈቃዶች ከነገ መስከረም 30 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ በየአራት ዓመቱ እንደሚታደስ አስታውቋል፡፡

አዲስ መንጃ ፈቃድም ከሁለት ዓመት ሙከራ በኋላ፣ ባለው አሰራር መሠረት በየአራት ዓመቱ እንደሚታደስ ከባለስልጣኑ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ ዕድሜያቸው ከ55 ዓመት በላይ ለሆኑ ግለሰቦች በየሁለት ዓመት የሚታደስ ሆኖ ክፍያው የአራት ዓመቱ ክፍያ ግማሽ (50%) እንደሚሆንም ተመላክቷል።

@Addis_Mereja


የኢትዮጵያ እና ኤርትራ ዜጎች የስልክ ግንኙነት መቋረጡ ተሰማ!

ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ከሁለት አስርት ዓመታት በኋላ ዶ/ር አብይ አህመድ ወደ ስልጣን ከመጣበት 2010 ዓ.ም ጀምሮ ሁለቱ መሪዎች ባደረጉት መልካም ግንኙነት የስልክ፣ የትራንስፖርት እና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት በእጅጉ ተሻሽሎ እንደነበር ይታወቃል፡፡

የኤርትራ ዜጎች ወደ ኢትዮጵያ ገብተው የመስራት እና የመኖር እንድሁም ኢትዮጵያውያን ኤርትራ የሚኖሩ ዘመዶቻቸው ጋር ለመገናኘት የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና የስልክ አገልግሎት ክፍት ሆነው እስከ ቅርብ ወራቶች አገልግሎት አግኝተዋል፡፡

ይሁንና ከፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት በኋላ የሁለቱ መሪዎች ግንኙነት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ መጥቶ ባሳለፍነው ወር የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ኤርትራ የሚያደርገውን ጉዞ አቋርጧል፡፡

ኤርትራም ከኢትዮጵያ ጥቅም በተቃራኒው ከቆሙ እንደ ግብጽ ያሉ አገሮችን ጋር ግንኙነት በመፍጠር፣ በሶማሊያ ጉዳይ አስተያየቶችን በመስጠት የሁለቱ አገሮች ግንኙነት በእጅጉ እያሽቆለቆለ መጥቷል፡፡

በቅርቡ የመከላከያ ሰራዊት ኢታማጆር ሹም ብረሃኑ ጁላ የኤርትራን ሰራዊት በትግራይ ጦርነት ወቅት ፈጥሞታል ያሉትን ከተናገሩ በኋላ በምላሹ የኤርትራ የማስታወቂያ ሚኒስትር መልስ ሰጥተዋል፡፡

ሰሞኑን ደግሞ የኤርትራ እና የኢትዮጵያ ዜጎችን የሚያገኛኘው የስልክ አገልግሎት ሙሉ በሙሉ መቋረጡን ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ የኤርትራ ስደተኞች ተናግረዋል፡፡ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ እስከ አሁኑ ባለው ወደ ኤርትራ እና ኢትዮጵያ ዜጎች በስልክ ይገኛኙ እንደነበር የተናገሩ ሲሆን ሰሞኑን የስልክ አገልግሎት መቋረጡን ተናግረዋል፡፡

@Addis_Mereja


ሰበር

አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ ኢትዮጵያ አዲሱ ፕሬዝዳንት ሆነዋል

ላለፉት 8 ወራት በውጭ ጉዳይ ሚኒስትርነት ሲያገለግሉ የነበሩት አምባሳደር ታዬ አጽቀስላሴ በፕሬዝዳንትነት ተሾሙ።የተወካዮች እና የፌዴሬሽን ምክር ቤቶች ዛሬ ሰኞ መስከረም 27 ባካሄዱት የጋራ ስብሰባ፤ የአቶ ታዬን ሹመት በ5 ድምጸ ተዐቅቦ አጽድቀዋል

@Addis_Mereja


የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ የመጀመሪያውን ኤርባስ A350-1000 በጥቅምት ወር ሊረከብ መሆኑ ተገለጸ!

የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ አኅጉር የመጀመሪያውንና ከ350 እስከ 410 መንገደኞች ማሳፈር የሚያስችለውን ግዙፍ ኤርባስ A350-1000 አውሮፕላን በጥቅምት ወር እንደሚረከብ ተሰምቷል።

አውሮፕላኑ ET-BAW በሚል የተመዘገበ ሲሆን፤ 46 የቢዝነስ ደረጃ እና 349 የኢኮኖሚ ደረጃ መቀመጫዎች በአጠቃላይ 395 መቀመጫዎች እንዳሉት ተነግሯል፡፡ ከሌሎች አውሮፕላኖች ጋር ሲወዳደርም ከፍተኛ የቢዝነስ ደረጃ መቀመጫዎችን ያሉት ነው።

ኤ350-1000 የመጀመሪያ በረራውን ከአዲስ አበባ ወደ ሄትሮው ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ህዳር 3 ቀን 2024 በማድረግ ሥራ ይጀምራል ተብሎ እንደሚመጠበቅ ተነግሯል።

እነዚህ አውሮፕላኖች ከ777-300ER በመቀጠል ሁለተኛው ከፍተኛ ሰው የመጫን አቅም ያላቸው እንደሚሆኑም ተመላክቷል።

በሐምሌ ወር 2014 የኢትዮጵያ አየር መንገድ በአፍሪካ የመጀመሪያ የሚያደርገውን የኤርባስ A350-1000 ትዕዛዝ ከኤርባስ አውሮፕላን አምራች ኩባንያ ጋር መፈራረሙ ይታወቃል፡፡

አየር መንገዱ ከዚህ በፊት ከኩባንያው 22 ኤርባስ A350-900 አውሮፕላን በማዘዝ 16ቱን ተረክቦ ሥራ ላይ ያዋለ ሲሆን፤ ከተቀሩት የኤርባስ A350-900 አውሮፕላን ትዕዛዞች አራቱ ወደ ኤርባስ A350-1000 እንዲቀየሩ ከኤርባስ አውሮፕላን አምራች ኩባንያ ጋር ስምምነት ማድረጉ ይታወሳል፡፡የኢትዮጵያ አየር መንገድ ኤርባስ A350-1000ን አገልግሎት ላይ ያዋለ የመጀመሪያው የአፍሪካ አየር መንገድ ያደርገዋል፡፡

[Ahadu]
@Addis_Mereja


አዋሽ ፈንታሌ በመሬት መንቀጥቀጥ የተወሰኑ ቤቶችን መፍረሳቸው ተሠምቷል

በአዋሽ ፈንታሌ እና አካባቢው ትናንት ምሽት የተከሰተው የመሬት መንቀጥቀጥ የተወሰኑ መኖሪያ ቤቶችን ማፍረሱን ሰመራ ዩኒቨርሲቲ አስታውቋል፡፡

በመሬት መንቀጥቀጡ መሬት መሰንጠቁንም ዩኒቨርቲው ዛሬ ሰኞ ማለዳ ባወጣው መግለጫ ተናግሯል።

በፈንታሌ ተራራ ላይ ተከስቶ ንዝረቱ አዲስ አበባ ከተማ ድረስ የተሰማው የመሬት መንቀጥቀጥ፣ ከሁለት ሳምንታት በላይ በተለያየ አጋጣሚ መከሰቱን ባለሞያዎች ገልጸዋል።

ትናንት መስከረም 26/2017 ምሽት 2፡10 ገደማ የተከሰተው በሬክተር ስኬል 4 ነጥብ 9 የተመዘገበበት ነበር።

"የሰሞኑ የመሬት መንቀጥቀጥ በአዋሽ ፈንታሌ እና አካባቢው ከፍተኛ ሥጋት ፈጥሯል" ያለው ዩኒቨርሲቲው፤ አደጋው በተከሰተበት ሳቡሬ ቀበሌ ተገኝቶ መረጃ የመሰብሰብ እና ለማህበረሰቡ ጥንቃቄ የግንዛቤ ማስጨበጥ ሥራ መሥራቱን ገልጿል።

የአካባቢው ነዋሪዎች የትናንቱ መንቀጥቀጥ ተወሰኑ ቤቶችን እንዳፈረሰ፣ መሬትን እንደሰነጠቀ እና በተለይ እንስሳት ከፍተኛ መደናገጥ ውስጥ እንደገቡ ገልጸዋል::

የዩኒቨርሲቲው ጂኦሎጂስቶች ነዋሪዎች ከፈንታሌ ኮረብታማ ቦታ እና ከከሰም ግድብ ርቀው እንዲቆዩ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል። ትናንት እሑድ ምሽት የተከሰተውና በአዲስ አበባ በነዋሪዎች ላይ መደናገጥ የፈጠረው የመሬት መንቀጥጠጥ ለ18 ሴኮንድ የቆየ እንደነበረ ባለሞያዎች መናገራቸውን አሐዱ ዘግቧል።

@Addis_Mereja


የ2017 ዓ.ም የሆረ አርሰዲ የኢሬቻ በዓል አከባበር ሥነ-ሥርዓት

[EBC]
@Addis_Mereja

16 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.