ESAT (ኢሳት🇪🇹)®


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


ለማንኛውም አስተያየት እና ጥቆማ 👉 @Esat_tv_comment_bot
🇪🇹ኢሳት የኢትዮጵያ አይን እና ጆሮ🇪🇹

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


በረጅምና ተደጋጋሚ ውይይት የተሻለ መግባባት ላይ ተደርሶ በቀን የተሰራን የመስጂድ አጥር ጨለማን ተገን አድርጎ ማፍረስ ኃላፊነት የጎደለው ተግባር ነው‼️

🗣 የአ/አ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት

በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ተባረክ (ጀርመን) መስጂድ ህጋዊ ካርታ ያለው እና ከ1967 ጀምሮ ሲሰገድበት የቆየ መስጅድ ነዉ።

አካባቢውን በአዲስ መልክ ለማልማት መንግስት የጀመረውን እንቅስቃሴ በመደገፍ እና መስጅዱን በአዲስ መልክ ለመስራት ፕሮጀክት ተዘጋጅቶ ለሚመለከተው የመንግስት ተቋም ገቢ ተደርጎ ክትትል እየተደረገ ባለበት ወቅት አካባቢውን እያለማ የሚገኘው ኢግልስ ሂል የፌደራል የሜጋ ፕሮጀክት ተወካዮች፣ የወረዳ እና ክ/ከተማ የመንግሥት አመራሮች በተገኙበት የመስጅዱን ዙሪያ በማጠር እና በሰላማዊ መንገድ ለአካባቢው ጀመዓ በማስረከብ መስጅዱ እየተሰገደበት ይገኛል።

የአዲስ አበባ ከተማ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት ከከተማ መስተዳድሩ የሰላም እና ጸጥታ ቢሮ አስተዳደር ጋር በጉዳዩ ላይ ሰፊ ውይይት ያደረገ ሲሆን አጥሩ ባለበት ሁኔታ በውይይት ዘላቂ መፍትሄ እንዲሰጥ ከስምምነት ተደርሶ ነበር። ከዚህም በተጨማሪ ረመዳን 28 የአካባቢው ጀመዓ ባዘጋጀው የኢፍጣር ፕሮግራም ላይ የክ/ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር አዲሱ ሻንቆ በአካል በመገኘት የማህበረሰቡን ጥያቄ ለመመለስ እየሰሩ መሆኑን አሳውቀዋል።

ይህ በእንዲህ እያለ በሰላማዊ መንገድ በቀን የተገነባውን የመስጅድ አጥር ጨለማን ተገን አድርጎ ማፍረስ እና በመስጅዱ ውስጥ የሚገኙ የመስጅድ ኻዲሞችን ማሰር በምንም መመዘኛ ህግ ማስከበር ሊሆን አይችልም።

በመሆኑም ከፍተኛ ም/ቤቱ ድርጊቱን አጥብቆ ያወግዛል። በመጨረሻም የፌደራል የሜጋ ፕሮጀክት ተወካዮች እና የመንግስት የስራ ሀላፊዎች ባሉበት የተገነባው የመስጅድ አጥር ወደ ነበረበት እንዲመለስ እና ያለምንም ጥፋት ከመስጅድ የታሰሩት ሰዎች በአስቸኳይ እንዲለቀቁ እናሳስባለን።

@Esat_tv1
@Esat_tv1




Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
900,000 ብር ምን መግዛት ይችላል?

መኪና? ቤት?

በዚህ ጊዜ 900,000 ብር ምንም መግዛት አይችልም ።

እኛ ጋር ግን በ900,000 ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ ሱቅ መግዛት ትችላላችሁ

ያውም እስከ 200,000 ብር መከራየት የሚችል ሱቅ።

ፒያሳ አድዋ ዜሮ ዜሮ አጠገብ 20 ካሬ ሱቅ አየሸጥን ነው።

ከግራውንድ እስከ 5ኛ ፎቅ።

ለሁለት ሳምንት ብቻ የሚቆይ ዋጋ ነው

ፈጥነው ይደውሉ!

ለበለጠ መረጃ ዋናው ቢሮ ይደውሉ
0979440044
0939440044 

በቴሌግራም ያውሩን
@TemerPropertiesM

ወይም በዋትሳፕ ያውሩን
https://wa.me/251979440044?text


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) በተገኙበት የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ እየተካሄደ ነው‼️

ዛሬ በተለያዩ ዘርፎች የተከናወኑ የ2017 ዓ/ም የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መጀመሩን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገልጸዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባስተላለፉት መልዕክት፥ በግምገማችን የሚቀጥሉትን ሶስት ወራት ሥራዎቻችንን እቅድ ለማጠናከር የሚረዱ ውይይቶችን እናካሂዳለን ብለዋል።

እስካሁን ያሳካነው የሥራ ውጤት ሰፊ ቢሆንም ስኬታችን ሳያዘናጋን ለበለጠ ከፍታ የሚያነሳሳን ሊሆን ይገባልም ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር)።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በአማራ ክልል የታጠቁ ኃሎች በዩኒሴፍ ሠራተኞች ላይ ያደረሱት ጥቃት‼️

በአማራ ክልል የሚንቀሳቀሱት የታጠቁ ኃሎች በዩኒሴፍ ሠራተኞች ላይ ጥቃት ማድረሳቸውን የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ለገሰ ቱሉ (ዶ/ር) በማህኅበራዊ ትሥሥር ገጻቸው አስታውቀዋል።

ሚኒስትሩ እንደገለጹት፤ በክልሉ የሚንቀሳቀሱት የታጠቁ ኃሎች የአማራ ሕዝብ በሰላም እጦት እንዲታመስ ከውስጥና ከውጭ የጥፋት ኃይሎች ጋር ተመሳጥረው ያደረሱት ታሪክ የማይዘነጋው ጥፋትና ውድመት ነው።

ይህ ሳያንስ ሕፃናት ላይ ትኩረት አድርጎ በሚሠራው ዓለም አቀፍ ተቋም (ዩኒሴፍ) ሠራተኞች ላይ የጥፋት በትራቸውን አንሥተዋል።

ይህ ኃይል ሕፃናትና ታዳጊዎች ወደ ትምህርት ገበታ እንዲመለሱ ለምን አደረጋችሁ? የገንዘብ ድጋፍ በመለገስ ለህፃናት የተመጣጠነ ምግብ ለማድረስ ለምን ሠራችሁ? በማለት የዩኒሴፍ ሠራተኞችን የማገት እና ባሕር ዳር በሚገኘው ተቋማቸው አቅራቢያ የእጅ ቦንብ መወርወሩን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።

ይህ አረመኔያዊነት እና ዓላማ የሌለው የጥፋት እሳቤ ፈሊጥ የጥፋት ቡድኑን አጀንዳ ይበልጥ ከማጋለጥ ባለፈ ብዙዎችን አሳዝኗል።

የዚህ ኃይል ፍላጎት እና ተግባር፣ የአማራ ሕዝብ እንቅስቃሴ እንዲታወክ በማድረግ ሕዝቡ ራሱን እና አገሩን ለማሳደግ የሚያደርገውን ጥረት በሁሉም መስክ የማዳከም፣ ክልሉን የቀነጨሩ እና ከትምህርት ገበታ የራቁ ሕፃናት ማዕከል የማድረግ እንደሆነ በግልፅ ያሳያል።

የቡድኑን ጥፋት እና ክህደት ሕዝቡ ከበቂ በላይ ተረድቶታል፤ የሚያደርሰውንም እኩይ ተግባር በበቂ መጠን ተገንዝቧል ያሉት ሚኒስትሩ፤ ለዚህም ነው ከሕዝቡ የተውጣጣው ሚሊሻ እና የፀጥታ ኃይል በሽብር ቡድኑ ላይ እርምጃ በመውሰድ ወደ መበታተን እና ተራ ሽፍትነት እንዲወርድ እያደረጉት ያለው ብለዋል።
©Ebc

@Esat_tv1
@Esat_tv1


አቶ ጌታቸው ረዳ የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ‼️

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ከሚያዝያ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ አቶ ጌታቸው ረዳን የምስራቅ አፍሪካ ጉዳዮች አማካሪ ሚኒስትር አድርገው ሾመዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ወጣቱ ሙነሽድ ሙሐመድ ሰዒድ በገጠመው ድንገተኛ ህመም ህይወቱ አለፈ‼️

በበርካታ የኅብረትና የግል ነሺዳዎቹ የሚታወቀው ወጣቱ  ሙንሺድ ሙሐመድ ሰዒድ በገጠመው ድንገተኛ ህመም በህክምና ሲረዳ ቆይቶ ዛሬ አመሻሹን ወደ አኼራ መሻገሩ ተሰምቷል።

በደቡ ወሎ ዞን ደሴ ከተማ ተወልዶ ያደገው  ሙሐመድ ሰዒድ በገጠመው ድንገተኛ ህመም ማለፉ ነው የተነገረው።
©ሀሩን ሚድያ

@Esat_tv1
@Esat_tv1


የአክሱም ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ ለብሰው እንዲማሩ የዞኑ ፍርድ ቤት የወሰነ ቢሆንም ትምህርት ቤቶቹ ፈቃደኛ አለመሆናቸው ተገለፀ‼️

🗣ሀሩን ሚዲያ

በትግራይ ክልል የአክሱም ከተማ ወረዳ ፍርድ ቤት በከተማዋ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ እንዳይለብሱ የሚከለክለውን መመሪያ በማገድ ያስተላለፈውን ውሳኔ የዞኑ ማዕከላዊ ፍርድቤት ፍርድ ቤት በማፅደቅ ተማሪዎች ሂጃብ ለብሰው እንዲማሩ ውሳኔ አሳልፎ ነበር።

በወረዳው እና በዞኑ ፍርድ ቤት የታገደው የትምህርት ቤቶቹ አስተዳደራዊ ውሳኔ እስከዛሬ በትምህርት ቤቶቹ አለመተግበሩ እና ተማሪዎቹ መማር አለመቻላቸውን ከትግራይ የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው እስኪመለሱ ድረስ ክሱን እስከ ከፍተኛ ፍርድ ቤት እንደሚቀጥል ገልጿል።

የአክሱም ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ምንም አይነት እልባት ሳያገኙ የትምህርት ዘመኑ ሊጠናቀቅ መሆኑን ገልፀው አስቸኳይ እልባት ተሰጥቷቸው ወደትምህርት ገበታቸው መመለስ እንደሚፈልጉ ተናግረዋል።
©ሀሩን ሚዲያ

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ኢትዮ-ጂቡቲ ምድር ባቡር ነዳጅን ሙሉ በሙሉ ሊያጓጉዝ ነው‼️

የኢትዮ ጂቡቲ የምድር ባቡር አክሲዮን ማኅበር በመጪው ዓመት ለመጀመሪያ ጊዜ ነዳጅን ሙሉ በሙሉ በባቡር ለማጓጓዝ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል።

በቀን እስከ አስር ጊዜ በመመላለስ በዓመት 4.2 ሚሊዮን ቶን ነዳጅ ከጂቡቲ ወደ ኢትዮጵያ ለማጓጓዝ እቅድ ተይዟል። ይህ የነዳጅ አቅርቦት ችግርን ከመቅረፉም በላይ የነዳጅ ማጓጓዣ ጊዜን በእጅጉ ይቀንሳል ተብሎ ይጠበቃል።

ቀደም ሲል አንድ ቦቴ ነዳጅ ከጂቡቲ ለመምጣት እስከ ስምንት ቀናት ይወስድ የነበረ ሲሆን ይህ አዲሱ ስርዓት የነዳጅ ዋጋን ሊያሳንስ ይችላል ተብሏል። የባቡር መስመሩ ሙሉ በሙሉ ሲጠናቀቅ አገልግሎቱ በስፋት እንደሚጀመር ተገልጿል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ቻይና አሜሪካ ላይ የ84 በመቶ ታሪፍ መጣሏን አስታወቀች‼️

ቻይና በአሜሪካ ላይ ጥላው የነበረውን የ34 በመቶ ታሪፍ ወደ 84 በመቶ ማሳደጓን ገልጻላች።

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይና ወደ አሜሪካ የሚገቡ ምርቶች ላይ የ104 በመቶ ታሪፍ መጣላቸውን ተከትሎ ነው ሀገሪቱ ማሻሻያውን ያደረገችው።

“በኢኮኖሚ ረገድ ለሚደረግ ጦርነት እስከመጨረሻው ለመታገል ዝግጁ ነኝ” ያለችው ቻይና፣ አሁንም ወደ ኋላ እንደማታፈገፍግ ነው ያስረገጠችው።

በሌላ በኩል የአውሮፓ ኅብረት በአንድ አንድ የአሜሪካ ምርቶች ላይ ታሪፍ ለመጨመር ድምፅ መስጠቱ ተጠቁሟል።

የታሪፍ እርምጃው የአውሮፓ እና እስያ ሀገራት አክሲዮን ገበያ እንዲያሽቆለቁል ከማድረጉ ባሻገር የአሜሪካ እና የዓለም አቀፍ ኢኮኖሚ 60 በመቶ እንዲወድቅ ያደርጋል ሲል ቢቢሲ በዘገባው አመላክቷል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ከአራት ኪሎ እስከ ሽሮ ሜዳ የዩኒቨርሲቲ መንደር እንዲሆን ተወሰነ‼️

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ካቢኔ በ4ኛ ዓመት 9ኛ መደበኛ ስብሰባው አራት አጀንዳዎች ላይ ተወያይቶ በዛሬዉ እለት ውሳኔዎችን አስተላልፏል።

በዚህም መሰረት:-

1ኛ.በፕላንና ልማት ቢሮ እና በትምህርት ሚኒስቴር በጋራ ተጠንቶ የቀረበዉን ከአራት ኪሎ እስከ ሽሮ ሜዳ ያለዉ አካባቢ የዩኒቨርሲቲ መንደር በመሆን በአካባቢዉ ያሉትን አገልግሎቶች አካቶ የትምህርት ፣ የምርምር ፣ የእውቀት እና የባህል ልህቀትን በከተማዋ ለማሳደግ በሚያስችል አግባብ የቀረበ በመሆኑ ፤ ካቢኔዉ ተወያይቶ የመንደር ምስረታውን ዉሳኔ አፅድቋል፡፡

2ኛ.የምግብ ስርዓትና ኒዉትሪሽን ምክር ቤት ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይ ተወያይቶ ዉሳኔ አስተላልፏል::

3ኛ.የአደጋ ስጋት አመራር ምክር ቤትና ፤የአደጋ ዝግጁነት ፈንድ ማቋቋሚያ ረቂቅ ደንብ ላይ ካቢኔዉ ተወያይቶ ዉሳኔ አስተላልፏል፡፡

4ኛ.በመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ የቀረበዉን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፋይዳ ያላቸዉ ፕሮጀክቶች፤የመሬት ምደባ ጥያቄዎች አስመልክቶ ካቢኔዉ ተወያይቶ ዉሳኔ አስተላልፏል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ሳዑዲ አረቢያ ኢትዮጵያን ጨምሮ በ14 ሀገራት ላይ የቪዛ ጊዜያዊ እገዳ ጣለች‼️

ሳዑዲ አረቢያ ለኡምራ፣ ቢዝነስ እና ቤተሰብ ጥየቃ የሚሰጡ ቪዛዎች ኢትዮጵያን ጨምሮ ለ14 ሃገራት እንዳይሰጡ በጊዜያዊነት አግዳለች።

እገዳው የሃጂ መገባደጃ እስከሆነው የሰኔ ወር አጋማሽ 2025 ድረስ ውሳኔው የተሰጠው በሃጂ ጊዜ ያለውን መጨናነቅ ለመቀነስ እና ደህንነትን ለማረጋገጥ መሆኑ ተነግሯል።

ቪዛ እስከ ሃጂ ማገባደጃ ወር ድረስ እንዳይሰጣቸው የተከለከሉት ሃገራትም የኡምራ ቪዛ ማግኘት የሚችሉት በቀጣዮቹ 5 ቀናት ውስጥ ብቻ መሆኑ ተገልጿል።

ቪዛ እንዳይሰጣቸው የተከለከሉት ሃገራትም ኢትዮጵያ ፣ አልጄሪያ፣ ባንግላዴሽ ፣ ግብፅ፣ ኢንዶኔዥያ ፣ ህንድ፣ ኢራቅ፣ ጆርዳን፣ ሞሮኮ፣ ናይጄሪያ ፣ ፓኪስታን፣ ሱዳን፣ ቱኒዝያ እና የመን ናቸው።

ቪዛ እንዳይሰጥ የተከለከለባቸው ሃገራት ዜጎች በኡምራ ወይም ጉብኝት ቪዛ ወደ ሳዑዲ አረቢያ ከገቡ በኋላ ያለፈቃድ በዛው በመቆየት ያለ ፈቃድ የሃጂ ፕሮግራም ላይ ሲሳተፉ እንደነበር የተገለፀ ሲሆን ሳዑዲ ይህንን መጨናነቅ ለመቀነስ ቪዛውን መከልከሏ ተዘግቧል።

በ2024 በሃጂ ወቅት በተፈጠረው መጨናነቅ እና ከፍተኛ ሙቀት 1200 ሰዎች መሞታቸው የሚታወስ ሲሆን ሳዑዲ ያለ ፈቃድ ሃጂ ሲፈፅሙ የሚገኙ ሰዎችም ለ5 አመታት ወደ ሳዑዲ አረቢያ እንዳይገቡ እንደሚከለከሉ ተናግረዋል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ሌ/ ጄኔራል ታደሰ ወረደ አቶ ጌታቸው ረዳን በመተካት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንትነትን ተረከቡ‼️

"ባለፈው አንድ ወር ገደማ የኢትዮጵያን ሕገ መንግሥት፣ የፕሪቶሪያን ስምምነት እና የዲፕሎማቲክ ማኅበረሰቡን ምክር በማከል ሰፊ ውይይቶች ሲካሄዱ ቆይተዋል። የአቶ ጌታቸው የሥልጣን ዘመን በሕጉ መሠረት ሲያበቃ የሚቀሩ ቁልፍ ሥራዎችን የሚያከናውን አካል፣ ጊዜያዊ መንግሥቱ መቀጠል አለበት የሚል ድምዳሜ ከተያዘ በኋላ፣ ይሄንን ሽግግር ማን መርቶ ከግብ ሊያደርስ ይችላል? የሚሉ ውይይቶችን ስናደርግ ቆይተናል።

ዛሬ በይፋ እና በሰላማዊ መንገድ በአዲስ ባህል የሥልጣን ሽግግሩን እና ቅብብሎሹን ለማካሄድ የተዘጋጀ ፕሮግራም አከናውነናል። ጄኔራል ታደሰ ባለፋት ሁለት ዓመታት የአቶ ጌታቸው ምክትል ሆነው ያገለገሉ ሰው ናችው። ባለፋት ሁለት ዓመታት የነበሩ ድካሞችን እና ጥንካሬዎችን በግልጽ የሚገነዘቡ ሰው ናቸው። አሁን ትግራይ ውስጥ ያለውን ክፍተት ሞልተው ወደ ፊት ሊወስዱ ይችላሉ የሚል እምነት በብዙ አካላት የታመነ ነው። የትግራይ ሕዝብ የጠማውን ሰላም እና ልማት፣ እንደ ሌሎች ወንድሞቹ ወጥቶ የመግባት መሻት ስናሳካ፣ ለኢትዮጵያም ለአፍሪካም እጅግ ጠቃሚ የሆነ ነገር ሠርቶ ለማለፍ ታሪክ የሰጣቸውን ዕድል እንደሚጠቀሙበት ተስፋ አደርጋለሁ።"

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አቶ ጌታቸው ረዳን አሰናበቱ‼️

ጠቅላይ ሚኒስቴሩ እንዲህ ብለዋል:-

በህገ መንግስቱ 62 (9)፣ በአዋጅ 359/1995 አንቀጽ 15(3) እና ደንብ ቁጥር 533/2015 እና በፕሪቶሪያ የሰላም ፕሮፖዛል ስምምነት መሰረት አቶ ጌታቸው ረዳ ላለፉት ሁለት ዓመታት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ሆነው መቆየታቸው ይታወቃል። በዚህም የፌዴራል መንግስት እና አመራሮች እውቅና ተሰጥቶታል። ስለ ቆይታቸው አመሰግናቸዋለሁ። ወደፊትም ተቀራርበን እንደምንሰራ አረጋግጣለሁ።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በትግርኛ ቋንቋ ያስተላለፉት መልዕክት‼️

ብመሰረት ሕገ መንግስቲ ፌዴሪኢ 62 (9) ፣ ብኣወጅ 359/1995 ኣንቀጽ 15(3) ን ደንቢ ቁጥር 533/2015 ከምኡ ድማ ስምምዕ እማመ ሰላም ፕሪቶርያን፣ ኣይተ ጌታቸው ረዳ ንዝሓለፉ ኽልተ ዓመታት ፕረዚደንት ጊዝያዊ ምምሕዳር ክልል ትግራይ ኮይኖም ንዘበርከትዎ፣ ብፍላይ ድማ ዝተረኽበ ሰላም ክዕቀብ ንዝነበሮም ልዑል ጥንቃቐን ኣመራርሓን መንግስቲ ፌደራል ኣፍልጦ ከምዘለዎን፤ ኣብ ቀፃሊ ስራሕቲ እውን ብሓባር ተቐራሪብና ከምእንስራሕን እናረጋገፅኩ፣ ንዝነበሮም ፃንሒት ኣመስግን።

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በሲስተም ላይ ባጋጠመ ብልሽት ምክንያት አገልግሎት ተቋርጧል‼️

🗣የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት

ሲስተም ላይ ባጋጠም ብልሽት ምክንያት 905 እና 904 ነፃ የጥሪ ማዕከሎች እንዲሁም የዲጂታል የክፍያ አማራጮችን ጨምሮ ከኢንተርኔት አገልግሎት ጋር ተያያዥነት ያላቸው የድህረ ክፍያ አገልግሎቶች አገልግሎት መስጠት ማቆማቸውን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታውቋል፡፡

ችግሩ ተፈትቶ የተቋረጠው አገልግሎት እስኪመለስ ድረስ ደንበኞች በአቅራቢያዎቻቸው በሚገኙ ዲስትሪክቶች ወይም አገልግሎት መስጫ ማዕከሎች በአካል ወይም በቀጥታ ስልክ በመደወል ተገቢውን አገልግሎት ማግኘት የሚችሉ መሆኑን የአገልግሎቱ መረጃ ያመለክታል፡፡

@Esat_tv1
@Esat_tv1


በትናንትናው እለት ከባህር ዳር ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ የነበረ አውቶቡስ ተጓዦች ታገቱ‼️

🗣መሠረት ሚድያ

- በተከፈተ የተኩስ እሩምታ የሞቱ መንገደኞችም እንዳሉም ታውቋል

ከባህር ዳር ከተማ ተነስተው በትናንትናው እለት ወደ አዲስ አበባ ሲጓዙ የነበሩ የአንድ አውቶቡስ ተሳፋሪ መንገደኞች በመንገዳቸው መሀል እንደታገቱ ታውቋል።

ለመሠረት ሚድያ የደረሰው መረጃ እንደሚጠቁመው እገታው የተፈፀመው በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ጎሀፂዮን ከተማ አቅራቢያ ነው። ታጣቂዎቹ የተኩስ እሩምታ አውቶቡሱ ላይ በመክፈታቸው የተገደሉ መንገደኞች እንዳለ የታወቀ ሲሆን የተረፉትን ይዘው ወደ ጫካ መግባታቸው ታውቋል።

"ከእገታው ያመለጡ የተወሰኑ ሰዎች አሉ፣ የፌደራል ፖሊስ ደርሶ ከታጣቂዎች ጋር እየተታኳሱ ነው" በማለት አንድ የአካባቢው ምንጭ ለመሠረት ሚድያ ተናግሯል።

ድርጊቱ መፈፀሙን 'የሹፌሮች አንደበት' የተባለው ገፅ ያረጋገጠ ሲሆን "ከጎሀፂዮን እና ቱሉ ሚሊክ ማዕከል አንድ አውቶብስ ሙሉ ሰው ታፍነው መወሰዳቸውን እና በተተኮሰ ጥይት የተሳፋሪ ህይወት ማለፉ ተሰምቷል" ብሏል።

በተመሳሳይ ከሁለት ሳምንት በፊት በፍቼ እና ጎሀፂዮን ከተሞች መሀል 58 ዜጎች መታገታቸው ይታወሳል። እነዚህን መንገደኞች ለመልቀቅ መንግስት 'ኦነግ ሸኔ' ብሎ የሚጠራቸው የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አባላት ለአንድ ታጋች እስከ 1.5 ሚልዮን ብር እየጠየቁ እንደነበር መዘገባችን ይታወሳል።

መጋቢት 8 ቀን የተፈፀመው ይህ እገታ በመንግስት ሚድያዎችም ሆነ በባለስልጣናት ምንም ቃል ያልተተነፈሰበት መሆኑ እጅጉን እንዳሳዘናቸው የታጋች ቤተሰቦች ገልፀው አሁን ላይ የቻሉትን ለመሰብሰብ የየቤቱ እየዞሩ እየለመኑ እንዲሁም በሶሻል ሚድያ ለህዝብ የእርዳታ ጥሪ እያቀረቡ መሆኑን ጠቁመው ነበር።

በዚህ መስመር ከዚህ በተደጋጋሚ እገታዎች የሚፈፀሙ ሲሆን በአካባቢው የኦሮሞ ነፃነት ሰራዊት አባላት በስፋት እንደሚንቀሳቀሱበት ይታወቃል።

@Esat_tv1
@Esat_tv1




በሰሜን ሸዋ የቀጠለዉ እገታና አንድምታ ዝምታዉ ለምን?

🗣ታዬ ደንደአ ከፃፉት

ሰሜን ሸዋ ኦሮሚያ ክልል... እጅግ አደገኛ የእገታ ወንጀል ለዓመታት ቀጥሏል። የዞኑ ነዋሪዎች በየተራ ከከተማና ከገጠር ይታገታሉ። እገታዉ በተመሳሳይ በመንገደኞች ላይም ሲፈፀም ዛሬ ደርሷል። ለታጋቾች ማስለቀቂያ በሚሊየኖችና በመቶ ሺዎች ይጠየቃል። የቻለ ጥሪቱን ሽጦ ወይም ዘመድ አዝማድ አስቸግሮ በመክፈል ይለቀቃል። ከፍያዉ ደግሞ ከካሽ ባሻገር በባንኮች ጭምር እንደሚፈፀም ኢሰመኮም አረጋግጧል። መክፈል ያልቸለዉ እንደሚገደልም ታዉቋል። በዚህ ምክንያት ብዙዎች ጥሪታቸዉን በመነጠቅ ለከባድ ችጋር ተጋልጧል። በርካቶችም ህይወታቸዉን አጥቷል።

ትላንትም በሰሜን ሸዋ ወረ-ጃርሶ ወረዳ የተለመደዉ አሳዛኝ የእገታ ወንጀል መፈፀሙን ሰምተናል። አንድ የመንገደኞች አዉቶቢስ ላይ ተኩስ ተከፍቶ በርካቶች ሲቆስሉ ከአስር በላይ ንፁኃን ዜጎች መገደላቸዉ ተዘግቧል። ታፍነዉ የተወሰዱ ስለመኖራቸዉም ይነገራል። ዜጎች በዚህ ሁኔታ መንገድ ላይ መቅረታቸዉ እጅግ ያሳዝናል። የዜጎችን ደህንነት የመጠበቅ ኃላፊነት ያለበት አካል ግን  የፓርክና የሪዞርት ግንባታ ላይ አተኩሯል።

ከሁለት ቀን በፊት አንድ የፖሊስ ኢንስፔክተር ሁለት መቶ ብር  ጉቦ መቀበሉ ትልቅ ዜና ነበር። ኢቲቪና ፋናም "ሌብነት ላይ ለተጀመረዉ ትግል አበረታች እርምጃ" ብለዉታል። ከሳምንት በፊትም "ሀሰተኛ መረጃን ለማጋለጥ" ጥረዋል። ጉዳዩ የማይመለከታቸዉ ባለስልጣናት ጭምር በየተራ ወጥተዉ የብርቱካን ድራማ "ኢትዮጵያን ለመግደል የተሸረበ ሴራ ነዉ" ብለዉናል። የበርካታ ዜጎችን ህይወት የቀጠፈዉና አካል ያጎደለዉ የትላንቱ ወንጀል ግን ዝም ተብሏል። የሁለት መቶ ብር ጉቦ ያንበገባቸዉ ኢቲቪና ፋና በሚሊዬኖች እየዘረፈ ብዙ ዜጎችን ለመከራ ያጋለጠዉ ተደጋጋሚ የእገታ ወንጀል ምንም ያልመሰላቸዉ ለምን ይሆን? የኢትዮጵያ ህዝብ በሀሰተኛ መረጃ እንዳይጎዳ በዚያ ልክ የተረባረቡት ሚዲያዎችና ባለስልጣናት ንፁኃን ዜጎች በየግዜዉ በመታገት ሲገደሉና አካላቸዉን ሲያጡ ለምን አያማቸዉም? በድራማዉ የታሰበለት የኢትዮጵያ ህዝብ የትላንቱን ተጎጂዎች አያጠቃልልም እንዴ?

ተጨማሪ ጥያቄዎችም አሉ። መጠኑ ቢለያይም በኦሮሚያ የነዋሪዎች እገታ በየቦታዉ ተለምዷል። በሰላም ወጥቶ መግባት በአብዛኛዉ ቅንጦት ሆኗል። ሰላም ሳይረጋገጥ ስለብልፅግና መስበክም ቀልድ ይሆናል። ይሁንና በዚህ ሁሉም ይመሳሰላል። በመንገደኞች እገታ ላይ ግን ግልፅ ልዩነት ይታያል። ከመንገዶች ሁሉ የጎጃም መስመር በዋናነት ተደጋጋሚ ጥቃቶችን አስተናግዷል። የዚህ መስመር ላይ ብዙዎች ተዘርፈዉ ለመከራ ሲጋለጡ በርካቶች ህይወታቸዉንና አካላቸዉን አጥተዋል። ሚስጢሩ ምንድ ነዉ? አጋቹስ በትክክል ማን ይሆን? ተመሳሳይ ወንጀል በተደጋጋሚ ተመሳሳይ ቦታ ላይ ለምን ይፈፀማል? ኃላፊነት ያለበት አካልስ ለምን ዝም ይላል? ይህ አደገኛ ወንጀል በመንግስት ሚዲያ የማይዘገበዉስ ለምንድነው? በርግጥ የእገታዉ ዓላማ ገንዘብ ማግኘት ብቻ ነዉ ወይስ የፖለቲካ ቁማር አለበት? ምናልባት የፖለቲካ ቁማር ኖሮበት ዓላማዉ ኦሮሞንና አማራን ለማጣላት ከሆነ ውጤቱ ማንን ይጠቅማል? ኢቲቪና ፋና ልክ እንደብርቱካን "ድራማ" ተረባርበዉ ቢያጋልጡትስ?

ለሟች ወገኖቻችን እጅግ አዝኛለሁ! የቆሰሉትም ፈጥነዉ ይድኑ ዘንድ እመኛለሁ! ዋናዉ ጉዳይ ግን የፖለቲካ ቀዉሱንና እንቆቅልሹን መፍታት መሆኑን ልብ እንበል እላለሁ!

@Esat_tv1
@Esat_tv1



20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.