" የብዕር ምርኮኛ "✍


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


«ወደ አላህ ከጠራና መልካምን ከሠራ እኔ ከሙስሊሞች ነኝ» ካለም ሰው ይበልጥ ቃሉ ያማረ ማን ነው?
{ፋሲለት:33}🍁🍁
የእውቀት መዓድ ይቀላቀሉ 👇
https://t.me/joinchat/AAAAAFkQxaW5cGELvPrwRQ

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri




Toleha Ahmed (Official Channel) ☪️ dan repost
ٰ'https://t.me/addlist/9XAD2MeM5485ZTZk' rel='nofollow'>            🌹🌹🌹
         🌹🌹🌹🌹        👈አበባውን
      🌹🌹🌹🌹🌹           በመንካት
   🌹🌹🌹🌹🌹🌹          ብቻ
   🌹🌹🌹🌹🌹🌹      እጀግ ጠቃሚ
   🌹🌹🌹🌹🌹🌹   ቻናሎች ያግኙ      
      🌹🌹🌹🌹🌹            
         🌿🌹🌹🌿      
              🌿🌿            👈
                 🌿                     🌿
                  🌿               🌿🌿
                 🌿           🌿🌿🌿
                🌿      🌿🌿🌿🌿
               🌿    🌿🌿🌿🌿
              🌿 🌿🌿🌿🌿
               🌿 🌿🌿🌿
                 🌿
                  🌿
                   🌿   አበባውን ስትነኩ
                    🌿     ነው የሚያመጣላችሁ
                    🌿
                  🌿       በቀላሉ ይቀላቀላሉ ።
👍👍✅👍👍




🌹ኢስላማዊ እውቀት ለሁሉም🌹 dan repost
              ክፍል አንድ

የዘር ሀረጋቸው
•┈┈•🔺❁🔺•┈┈•

ጦልሐ፣ የኡበይዱላህ ልጅ፣ የኡስማን ልጅ፣ የአምር ልጅ፣ የከእብ ልጅ፣ የተሚም ልጅ፣ የሙራህ ልጅ፣ የከእብ ልጅ፡፡ ከአላህ መልእክተኛ ጋር ሙራህ ቢን ከእብ በተባለ አያታቸው ላይ፤ ከአቡበክር ጋር ደግሞ በከእብ ቢን ሰእድ ዘር ሀረግ ይገናኛሉ፡፡ የጦልሐ እናት ሰህባህ ቢንት ሐድረሚ ትባላለች፡፡

ኢብን ደሐክ እንደዘገቡት ጦልሐ ቢን ዑበይዲላህ እንዲህ ሲል አውግቷል፡-

የኡሁድ ዘመቻ እለት የአላህ መልእክተኛ “በጎው ጦልሐ”፣ በአሺረህ ዘመቻ ላይ ደግሞ፡- “ጦልሐቱል ፈያድ”፣ እንዲሁም በሁነይን ዘመቻ ጊዜ፡- “ጦልሐቱል ጀዋድ” በሚሉ ቅጽሎች ጠርተውታል፡፡ ጦልሐ በጣም ብልህ ነበሩ፡፡ ስለ አሰላለማቸው እንዲህ ሲሉ አውግተዋል፡-

ከበስራ ገበያ ተገኘሁ፡፡ አንድ መነኩሴ ከቤተ አምልኮው ውስጥ ሆኖ፡- ‹‹ከገበያተኞች መሐል ከሐረም (መካ) የመጣ ሰው ካለ ጠይቁ፡፡›› አለ፡፡ “እኔ የመጣሁት ከዚያ ነው” አልኩ፡፡ “አህመድ ተከሰተን?” አለ፡፡ “አህመድ ማን ነው?” ስል ጠየቅኩት፡፡ “ቢን አብደላህ፣ ቢን አብዱል ሙጦሊብ፣ ነብይ በሚሆን ጊዜ መጠሪያ ስሙ ይህ ሲሆን፣ የመጨረሻው ነብይ ነው፡፡ መነሻውም ሐረም መካ ነው፡፡ የተምር ዛፍና ጥቋቁር አለቶች ወዳሉባት ምድረ በዳ መሬትም ይሰደዳል፡፡ ፈጥነህ ተከተለው፡፡” አሉ፡፡ ንግግሩን ከልቦናዬ ውስጥ ገባ፡፡ ፈጥኘም ወደ መካ ተመለስኩ፡፡ አዲስ የተከሰተ ነገር እንዳለ ስጠይቅም፡- “ታማኙ ሙሐመድ ቢን አብደላህ ነብይ ነኝ እያለ ነው፡፡ አቡበክር ተከታዩ ሆኗል፡፡” አሉኝ፡፡ እንዲህ ስል ከራሴ ጋር አወጋሁ፡-

“በአላህ እምላለሁ፣ ሙሐመድና አቡበክር በመጥፎ ነገር ላይ አይሰማሙም፡፡ ሙሐመድ እድሜው አርባ ዓመት ደርሷል፡፡ ከዚህ ቀደም ውሸት ሰምተንበት አናውቅም’ በሰዎች ላይ ለመዋሸት ያልደፈረ በአላህ ላይ ለመዋሻት አይደፍርም፡፡”

ከዚያም ወደ አቡበክር ሄድኩ፡፡ “ይህን ሰው ተከተልከውን?” ስል ጠየቅኩት፡፡ “አዎ፣ አንተም ሂድና አግኘው፡፡ ተከተለውም፡፡ ወደ እውነት ነው የሚጣራው፡፡” አለኝ፡፡ “ጦልሐ ለአቡበክር መነሱኬው የነገረውን አወጋቸው፡፡ ተያይዘው ወደ አላህ መልእክተኛ ሄዱ፡፡ እስልምናንም ተቀበሉ፡፡ በጉዞው ያጋጠመውንም ነገራቸው፡፡

ነውፈል ቢን ኹወይሊድ የአቡበክርንና የጦልሐን መስለም ሲሰማ ሁለቱንም ያዛቸው፡፡ በአንድ ገመድም ጠፈራቸው፡፡ የበኒ ተሚም ጎሳ አልታደጋቸውም፡፡ ነውፈል “የቁረይሽ አንበሳ” በሚል ቅጽል ነበር የሚታወቀው፡፡ ከዚህ ክስተት የተነሳ አቡበክር እና ጦልሐ “ተጣማሪዎች” ተብለው ተጠሩ፡፡ ጦልሐ በዚህ አኳኋን እስልምናን በመቀበል ቀዳሚ ሆነ፡፡ በእርግጥ የሰፊ ንግድና የብዙ ሐብት ባለቤት ነበር፡፡ ግና በበጎ ነገር ሌሎችን ቀደመ፡፡

የኡሁድ ንስር
•┈•🔺❁🔺•┈•

በኡሁድ ዘመቻ ቁረይሾች በከፍተኛ ሁኔታ ተዘጋጅተው በነቢዩና (ሰዐወ) በተከታዮቻቸው ላይ ተመሙባቸው፡፡ በታላቁ የበድር ዘመቻ የደረሰባቸውን ብርቱ ሽንፈትና ውድመት ለመበቀል ቋምጠዋል፡፡ በዚህ ዘመቻ ድል ማግኘት እንዳለባቸውም ወስነዋል፡፡ ለዚህም ሲባል ከሙስሊሞች በተሰነዘረባቸው ብርቱ በትር ተስፋ ያልቆረጡ ጽኑና ጀግና ጦረኛቻቸውን አሰልፈው በሙስሊሞች ላይ ቁጣቸውን አዘነቡ፡፡ ይህም ሆኖ በመጀመሪያ ድል አልቀናቸውም፡፡ የሙስሊሞችን ጠንካራ ጥቃት መቋቋምም ሳይችሉ ቀርተው፣ በድንጋጤ ተውጠው ከጦርነቱ መስክ አፈገፈጉ፡፡ ሙስሊሞች በካህድያን ላይ የደረሰውን ውርደት እና ማፈግፈጋቸውን ሲመለከቱ ተቻኩለው መሣሪያ አስቀመጡ፡፡ ምክንያቱም የጦርነቱ ውሎ አድክሟቸው አካላቸው ዝሏል፡፡ ከጋራው ላይ ሆነው ጠላትን በቀስት እንዲከላከሉ የተመደቡ ቀስተኞችም ከምርኮው የድርሻቸውን ለማግኘት ስፍራቸውን ትተው ወረዱ፡፡

የጥንት ሰዎች እንደሚሉት “ጦርነት ማታለል” ነውና ቁረይሾች በድንገት ከበቧቸው፡፡ የጦርነቱን ልጓምም ተቆጣጠሩት፡፡ በዚህ የጦርነት ረመጥ ውስጥ ከሁለቱም ወገኖች በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎች ተገደሉ፡፡ ሙስሊሞች በተፈጠረው ድንገተኛ ነገር እና በጠላት ፈጣን እና ጠንካራ ጥቃት ግራ ተጋቡ፡፡

በዚህ ፈታኝ ወቅት ጦልሐ የአላህን መልእክተኛ ተመለከተ፡፡ ነቢዩ በአደጋ ተከበዋል፡፡ ሰይፎች ወደርሳቸው ዞረዋል፡፡ የተራቡ ውሾች ሊበሏቸው አሰፍስፈዋል፡፡ በሁሉም አቅጣጫዎች የፈረሶች ድምጽ ያስገመግማል፡፡ ወንጀለኛ እጆች ሊያጠቋቸው ተዘርግተዋል፡፡ ግና አንድ ሐይል ይህን የጠላት ጦር ሰንጥቆ መጣ፡፡ ነብዩንም ከእኩያን ጥቃት ታደገ፡፡ ይህ ሐይል በአንድ ብርቱና ጀግና ሰው የተመሰለ ነው፡፡ ያ ሰው ጦልሐ ቢን ኡበይዲላህ ይባላል፡፡ በግራ እጁ የአላህን መልእክተኛ ያዘ፡፡ ወደ ደረቱም አስጠጋቸው፡፡ የሰይፉን እጀታ በቀኙ ይዞም ከወዲያ ወዲህ ያወናጭፈው ጀመር፡፡ እርሱ ሰይፉን ባንቀሳቀሰ ቁጥር አንገቶች ከአካላቸው እየተነጠሉ ልክ እንደ ዛፍ ቅጠል በዙሪያው ረገፉ፡፡

@Islamic_picture_wallpaper


🌹ኢስላማዊ እውቀት ለሁሉም🌹 dan repost
🍃ሴት ልጅ ሐጅና ዑምራህ ላይ፥🍃

1/ወንዶች ባሉበት አካባቢ ላይ ተልቢያህ (ለብይክ አላሁመ ለበይክ...) እና ተክቢራህ ስትል ድምጿን ጮኽ አታደርግም (ማድረግ የለባትም)።

2/የጠዋፍ የመጀመሪያ 3ዙሮች ላይ እንደ ወንዶች ፈጥና አትራመድም። ሰፋና መርዋ ላይም ወንዶች የሚሮጡበት ስፍራ ላይ አትሮጥም።

3/ የሰፋና መርዋ ከፍታ ላይ አትወጣም (የሁለቱም የታችኛው ጫፍ ላይ ብቻ እየደረሰች ትዞራለች)።

4/ጠዋፈል-ወዳዕ (የመሰናበቻ ጠዋፍ) ሳታደርግ ሐይዷ ቢመጣ ጠዋፉን ትታ መሄድ ይፈቀድላታል፤ ካልቸኮለችና ካልተቸገረች ጠብቃ ብታደርግ ግን የተሻለ ነው።

5/ከኒቃብና ጓንት በስተቀር ሸሪዓህ የማይከለክለውን የፈለገችውን ልብስ መልበስ ትችላለች። ወንድ ያለበት ቦታ ላይ ስትሆን ፊትና እጇን ከኒቃብና ጓንት ውጪ ባለ ጨርቅ መሸፈን አለባት፤ ግዴታዋም ነው! እነ ዓኢሻና ሌሎችም ሰሓባ ሴቶች ይህን ነበር የሚያደርጉት።

6/ሙዝደሊፋህ አድራ ንጋት ላይ ከሰዎች ጋር ወደ ሚና መጓዝ የሚከብዳት ከሆነ ሙዝደሊፋህ ላይ እስከ እኩለ-ለሊት ድረስ ከቆየች በኋላ ወደ ሚና መጓዝና በደረሰችበት ሰዓት (ከፈጅርም በፊት ቢሆን) ጠጠር ወርውራ ወደ ማረፊያዋ መሄድ ትችላለች።

7/በእርግዝና፣ በህመም እና መሰል ምክንያቶች ጠጠሮችን እራሷ እየሄደች መወርወር ከከበዳት ሌላ ሰው ወክላ ማስወርወር ትችላለች።

8/ ለንጽህናው ጥንቃቄ ከማድረግ ጋር በሰፋና መርዋ መሀል ሐይድ ላይ እንኳ ብትሆን መመላለስ (ሰዕይ ማድረግ) ትችላለች።

9/ሐይድ ላይ ሆና ከከዕባህ ዙሪያ ጠዋፍ ማድረግ በመሰረቱ አትችልም፤
👉🏻ነገር ግን የሐጅ መሰረት ለሆነው ጠዋፈል-ኢፋዷ በምንም መልኩ እስክትጠራ መጠበቅ ወይም ወደ ሀገሯ ሄዳ ስትጠራ ተመልሳ መጥታ ማድረግ የማትችል ከሆነ ሙሉ ንጽህናዋን ከመጠበቅ ጋር ጠዋፍ ማድረግ እንደምትችል ኢብኑ ተይሚያን ጨምሮ የተወሰኑ ሊቃውንት ገልጸዋል። ወደ ሀገሯ ተመልሳ ስትጠራ ለጠዋፍ መመለስን ከወሰነችም ባለ ትዳር ከሆነች በዚህ መሀል የግብረ-ስጋ ግንኙነት ማድረግ አይፈቀድላትም!
ነገር ግን ሳይቸገሩ መመለስ ለሚችሉ ሴቶች የሚሻለው ሲጠሩ ተመልሶ ማድረጉ ነው።

✍ኡስታዝ አሕመድ ሼኽ ኣደም
@ዛዱል መዓድ7/12/1439 ዓ.ሂ
                      
🔹🔸🔹🔸🔹🔸🔹
🌐https://telegram.me/ahmedadem






"زاد المعاد" ዛዱልመዓድ- የነገው ስንቅ dan repost
🏷️የዛዱል መዓድ ፈታዋ 🌾
فتاوى زاد المعاد
          ቁ/253

ረቢዕ 14/ 11/1445 ዓ.ሂ

🔊በኡስታዝ አሕመድ ሸይኽ ኣደም

የዳውንሎድ ሊንኩን ይጫኑ
⏬  ⏬   ⏬   ⏬   ⏬  ⏬

🔎https://tinyurl.com/27msfykr

    🔹 🔸 🔹 🔸 🔹 🔸
▪️1/ ቁርአን ሲቀራ ሱጁድ እንደሚወረድ ተምርያለሁ እኔ ግን ምኑም አልገባኝ ኡስታዝ  አላህ ጀዛችሁን አላህ ይክፈላችሁ አብራሩልኝ።

▪️2/ ባለቤቴ አይሰግድም የሆነ ጊዜ ይሰግዳል ከዛ ደሞ ለረጅም ጊዜ ያቆመዋል፤ አህዋሉም ልክ እንደ ካፊር ነው ውሎው ጫት ቤት ኸምር ያለበት ቦታ ከጓደኞቹ ጋር ነው የተለያዩ ዘፈን እና ኸምር እንዲሁም ወንድ እና ሴቶች የተቀላቀሉባቸውን ውሎዎቹን በማህበራዊ ገፆች ላይ ይለቃል እና ፈፅሞ ስምምነተ የለንም ብመክረው ባስመሰከረው መስተካከል አልቻለም ምን ይሻለኛል?

▪️3/ ለጓደኛዬ የዛሬ 3አመት የኢትዮጵያ 13ሺ ብር አበድሪያት ነበር ሁለታችንም በስደት ነው ያለነው በጊዜው እኔ ከሳኡዲ የላኩት 1000ሪያል ነበር አሁን ላይ 1000ሪያል ብቀበል ሀራም ይሆንብኛል? ለእሷስ ይሆንባታል? ያብራሩልኝ።

▪️4/ ኒካህ በስልክ ማሰር ይቻላል ወይ ያኔ ባልየውም በስልክ ሚስትየይቱም በስልክ ምስክሮችም በስልክ ወኪሉም በስልክ ኒካህ ማሰር ይቻላል ወይ?? ከተቻለ ቢያብራሩልኝ።

▪️5/ አንድ ባልና ሚስት በስልክ "ፆታዊ ግንኙነት" ቢያደርጉ "ሀራም" ከመሆኑ ውጭ  "ኒካህ" ያበላሻል?

▪️6/ በሀይድ ላይ እያለን መስጂድ እንገባለን ተማሪ ወይም አስተማሪ ነን አይቻልም ተባልን ረመዳን ላይም ሆነ ከረመዳን ውጪ እንዴት ይታያል?
ሀይድ ላይ ሆነው ቁርኣን በባዶ እጅ መቅራት ይቻላል ብለው ይቀራሉ ይህስ እንዴት ይታያል?

▪️7/ የአንገት ጌጥ በስም ማሰራት እንዴት ይታያል?

▪️8/ ከዚህ በፊት ብሬ የወለድ ባንክ ውስጥ ነበር እና እሱን ትቼ ሌላ ከወለድ ነፃ ከፍቼ ነበር አሁን ወለዱ ወደ አስር ሺህ ብር አለ እና እኔ የማልሰግድበት በኦንላይን ለመስጂድ ግንባታ ለተጠየቀ እርዳታ  መስጠት እችላለሁ? ሰደቃ ሳልነየት??

▪️9/ እኛን በመስጂድ ዉስጥ ቂርኣት የሚያቀራን አንድ ኡስታዝ ነበረን እናም አሁን በክፍያ በኦላይን ማቅራት ጀምሯል እናም እኔን እየከፈለኝ እንዳግዘዉ ጠየቀኝ በክፍያ ማገዙ እንዴት ይታያል?

▪️10/ እኔ ለትምህርት መጥቼ እህቴ ጋር ነው የምኖረው እና እህቴ ደግሞ ካፊር ናት ቤታቸው ውስጥ ፎቶ አለ እና እዚያው ውስጥ እኔ እሰግዳለሁ ፎቶ አለበት ቤት ውስጥ  መስገዴ እንዴት ይታያል?

▪️11/ አንድ ሰዉ ኢንሻ አላህ ብሎ ቢምል ከፋራ ይወጅብበታል?

▪️12/ እንደ እስቲም ወይም ወይባ ለሰውነት የሚደረጉ ነገሮችን ከቤት ውጪ መጠቀም ሰውነትን መታሸት እንዴት ይታያል?

▪️13/ ድምፅን በወንድ ቃሪዕ አስመስሎ መቅራት እንዴት ይታያል?

▪️14/ ከሰላት በኋላ አንዳንድ መስጂዶች ዱዓ ያደርጋሉ ዱዓውን ሚጀምሩት በሰለዋት ስለሆነ እኛም ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ማለት አለብን ወይ? ካልን በቢድዓ ማገዝ አይሆንም ወይ?

▪️15/ የኛ ትምህርት ቤት በፈረቃ ነው የምንማረው እናም የከሰአት ስንሆን ማለትም 6:30 እስከ 11:20 ነው የምንማረው በዚህ መሀል ዙሁር እና አስር ያመልጠኛል እዛ ለመስገድም አይመችም ስለዚህ ምን ላርግ ቀዳውንም እንዴት ላውጣ?

▪️16/ አንዲት ሴት የጀነት ባለቤቷ ማን ነው? በዱንያ የነበረው ባለቤቷ ሞተባት፣የፈታችው፣ያላገባችስ ከሆነ  ቢያብራሩልን።

▪️17/ አስር አመት ራሴን በራስ ማርካት ሀራም መሆኑን አላቅም ነበር አሁን የእርሶን ደርሶች ስሰማ ሀራም መሆኑን አወኩ እናም ተፀፅቼም ቁርአን መትቼ ሁለተኛ እንደዚህ አላደርግም ብየ መልሼ ግን ተሳሳትኩኝ እንደዚህ ካደረኩኝ ከእስልምና አወጣኝ ብዬ ምዬ ነበር አሁን በጣም ፀፅቶኛል ይሄን በማለቴ ከፈራ ምንድን ነው?
     ~
💥 በተጨማሪም የተለያዩ ትምህርቶችን ለማግኜት ከታች ያሉትን ሊንኮች ይጠቀሙ
🔸🔹🔸🔹🔸🔹
🌐https://telegram.me/ahmedadem
~
🌐https://t.me/zad_qirat
~~~~
🔗https://www.facebook.com/yenegew/
~~~~
📶  http://www.youtube.com/c/ZadulMaad

አላህ በተከበረው ቃሉ እንዲህ ይላል:-
🔅وَتَزَوَّدُوا فَإِنَّ خَيْرَ الزَّادِ التَّقْوَىٰ ۚ وَاتَّقُونِ يَا أُولِي الْأَلْبَابِ
"ስንቅ ያዙ፤ ከስንቆች ሁሉ በላጩ አላህን መፍራት ነው፤ የአእምሮ/ የልብ ባለቤቶች ሆይ ፍሩኝ" ሱረቱል በቀራ /197






"زاد المعاد" ዛዱልመዓድ- የነገው ስንቅ dan repost
🌾🏷️የዛዱል መዓድ ፈታዋ 🌾
فتاوى زاد المعاد
ቁ/128

ማክሰኞ 3/3/1442 ዓ.ሂ

🔊በኡስታዝ አሕመድ ሸይኽ ኣደም

የዳውን ሊንኩን ይጫኑ
🔹🔸🔹🔸🔹🔸

🔎https://bit.ly/2Hogn8N
🔹🔸🔹🔸🔹🔸
▪️1/የህፃን ልጅ ሽንት ከስንት ጊዜ ጀምሮ ነው የሚነጅሰው?ልብስ ከነካስ እንዴት ነው ማድረግ ያለብን የነካውን ብቻ ነው ማጠብ ያለብን ወይስ ከነገላችን ሙሉ ነው መታጠብ ያለብን?

▪️2/ ሀገር እያለሁ ያመኝ ነበር እና ቤተሰብ ፀበል ወሰዱኝ ቦታውም ቤተክርስትያን ነው አሁን ላይ ሺርክና ኩፍር መሆኑን አወቅኩ ከእስልምና ወጥቻለሁ? ፣ እንዲሁም አይንናስ አስወጥቼ ነበር ይህስ እንዴት ይታያል?ቢያብረሩልኝ

▪️3/ቁርአንን ከፍቶ ስራ መስራት እና ያ ሰው ከፍቶ እያዳመጠ ሌሎች ቢያወሩ እሱ ወንጀለኛ ይሆናል ወይ?

▪️4/የመቶ ሰባ ስድስት ሺ 372 ብርየሁለት ዓመት ዘካ ስንት ነው የሚወጣለት ለአህባሽ ወገኖቻችንስ መስጠት ይቻላል እንድሁም ሶላት ለማይሰግዱትስ

▪️5/አፍንጫ መበሳት እንዴት ይታያል?የተወላገደ ጥርስንስ እንዲስተካከል ማሳሰር እንዴት ይታያል

▪️6/እኔ ያደጉት ከእናቴ አክስት ልጅ ጋር ነው በልጅነቴ ነው እናቴ የሞተችብኝ ያሳደገችኝ ሴትዮ ህፃን ሆኜ አጥብታኛለች እስከ 2 አመት 6 ወር ድረስ አሁን እኔ ያለሁት ስደት ነው የሷልጆች ለኔ አጅ ነብይ ይሆኑብኛል ?ባሏስ ለኔ አጅ ነብይ ነው እነሱ እኔን ማየት ይችላሉ ወይስ አይችሉም ቢያብራሩልኝ ጀዛ ከላሁ ኸይረን

▪️7/አዳበ ነውም አድርጌ ከተኛሁ በኋላ እንደገና ከእንቅልፍ ብነሳ እንደገና ስተኛ ደግሜ አዳበ ነውም ማድረግ አለብኝ? ወይስ የመጀመሪያው ይበቃል?

▪️8/ባለቤቴ ሁሌም ፎቶ ላኪ እያለ ያስቸግረኛል ይሄ ደግሞ ሀራም እንደሆነ እየተማርኩ ነው እና አልክም አልኩት ይህን ባልኩበት ተጠያቂ ነኝ ? ሀቄን አልተወጣሽም እያለ ይዝትብኛል
በዚህ ጉዳይ ላይ ብዙ ጊዜም እንጣላለን ምን ማድረግ አለብኝ ምክር ይስጡኝ

▪️9/አባቴ ሌላ ሚስት አግብቷል እናም እኛን አይጠይቀንም እኛም ስናናግረው በግድ ነው መልስ የሚሰጠን እቤቱም በተደጋጋሚ ስንሄድ አያናግረን ደስተኛ አይደለም እኔ ቤቱ ሄጄ አድሬ ሳናግረው ደስተኛ አልነበረም እንዲሁም ለትዳር ሲጠየቅ ያለምክኒያት አያገባኝም ይላል እኔ በድርጊቱ በጣም እየተሰማኝ ስለሆነ ግንኙነቴን ለማቋረጥ እያሰብኩ ነው ምን ይመክሩኛል?እንዲሁም ወንድሜ ወኪል ሆኖስ መዳር ይችላል?አባታችን አያገባኝም ስለሚል ያብራሩልኝ

🌐https://telegram.me/ahmedadem
~
🔗https://www.facebook.com/yenegew/~~~~~~~~~~~~~~~
📶  http://www.youtube.com/c/ZadulMaad

አላህ በተከበረው ቃሉ እንዲህ ይላል:-
🔅وَتَزَوَّدُوا فَإِنَّ خَيْرَ الزَّادِ التَّقْوَىٰ ۚ وَاتَّقُونِ يَا أُولِي الْأَلْبَابِ
"ስንቅ ያዙ፤ ከስንቆች ሁሉ በላጩ አላህን መፍራት ነው፤ የአእምሮ/ የልብ ባለቤቶች ሆይ ፍሩኝ" ሱረቱል በቀራ /197


🌹ኢስላማዊ እውቀት ለሁሉም🌹 dan repost
ስኬት #ከልፋት ጋር 

✅:ስኬት በርግጥም #ልፋትን ይጠይቃል፡፡

🐜:#ጉንዳን ካሰበችው ለመድረስ ሺ ጊዜ ከምሰሶው ላይ ትወድቃለች ፤ ትነሳለች •

🐝:#ንብ ጣፋጩን ማር🍯 ለመጋገር ሚሊዮን ጊዜ አበቦች አካባቢ ትመላለሣለች •
 
🕊:#ወፍ መኖርያ ጎጆዋን ለመሥራት ማልዳ ወጥታ አምሽታ ትገባለች፡፡ 

         •-•-•-•⚘•-•-•-•

☄:አዎን - ስኬት ትኩረትንና ትእግስትን ይጠይቃል… ያለ #ጥረትም ከስኬት ጫፍ አይደርሰም፡፡ ልብ በሉ፡-

🐺:#ተኩላ ያለመውን ለማደን ቦታና አቅጣጫ ቀያይሮ ያደባል ৲
 
🐈:#ድመት የተመኘችውን ለማግኘት በትእግስት ትጠባበቃለች ৲

🦁:#አንበሳ ያቀደውን ለመያዝ በአንክሮ ይከታተላል ৲

        ════  •• ════

✅:ስኬትና ውጤት ያለ እንቅስቃሴ አይገኝም፡፡ አስተዉሉ ፦

🐆:ነብር ካልተወረወረ አይዝም ⨳

🏹:ቀስት ካልተስፈነጠረ አያድንም ⨳

🗡:ሰይፍ ካልተሠነዘረ አይገድልም ⨳

💡ተንቀሣቀስ አትተኛ • • •

  🎯:ለረጅም ጊዜ የተኛ ውሃ ይሸታል √

  🎯:በአንድ ቦታ ላይ ለዘመናት የቆየ ድንጋይ አንድ ቀን ይፈለጣል √

✅:እንቅስቃሴ በረከት አለው

✅:በሥራ ዉስጥ ለውጥ አለ

✅:ሥራ ፈት ዋጋ የለዉም #ዜሮ ቁጥር ነው

✅:ሽቶ ጫን ጫን ሲሉት ጥሩ ሸተተ ৲

✅:ሰንደል ሲያቃጥሉት አከባቢውን አወደ

✅¹:የሰው ልጅም #በችግሮች ሲደበደብ ካልሆነ ጥሩ ጠረን አይወጣውም

#ወዳጆቼ ! መከራ፣ ፈተና ችግርን አትጥሉ፡፡

🌀:ዱኒያን የታገላት ነው የሚጥላት ☇

🌀:ዓለምን እልህ የተጋባ ነው የሚያሸንፋት ☇

🌀:ጀነትን በመንገዷን የፀና ነው የሚያሳካት ☇

🌿: ህይወት በየቀኑ ሩጫ ናት፡፡ 
 
🌿: የስኬት ገበያ ሁሉ ከባድ ውድድር አለው፡፡ 

🌿:መጀመሪያ የጨሠ ነው ኋላ ብርሃን የሚወጣው፡፡ 
ዛሬ የደከመ ነው ነገ የሚያርፈው፡፡

@islamic_picture_wallpaper
@islamic_picture_wallpaper


ኢስላሚክ ጥያቄዎች እና ሀዲሶች ❤ dan repost
ሶፊያን አስውሪ (رحمه الله) እንዲህ ይሉ ነበር፦

﴿إذا عرفتَ نفسَك لم يضرَّكَ ما قيلَ لَكَ،﴾

“አንተ ስለራስህ የምታውቅ ከሆነ፤ ስላንተ የሚባለው የሰዎች ንግግር አይጎዳህም።”

[«አልሙኽለሲያት» ሊአቢ ጣኺር አልሙኽለስ (1626)]


@Islamic_picture_wallpaper
@Islamic_picture_wallpaper


🌹ኢስላማዊ እውቀት ለሁሉም🌹 dan repost
ተፈሲር ሱረቱ ኒሳዕ part 5

ሰዎች በገንዘብ ነክ ጉዳዮች እንዳይጋጩ የእያንዳንዱ ድርሻ ምን መሆን እንዳለበት ዲነል ኢስላም አስቀምጧል ፣ ከላይ የምእራፏ መጀመሪያ ላይ ስለ የቲሞች ይናገር ነበር .. ስለ መህርም ተናግሯል ፣ ውርሻ ላይ ወንድም ሴትም ባለድርሻ እንደሆኑ ተናግሯል ፣ ቀጥሎ ድርሻውን ወደ መመጠን ይገባል ..
يُوصِيكُمُ اللّهُ فِي أَوْلَادِكُمْ لِلذَّكَرِ مِثْلُ حَظِّ الاُنثَيَيْنِ
የአንቀፁን መጀመሪያ በጥልቀት ተመልከቱ «ዩሲኩሙሏሁ ፊአውላዲኩም» ይላል «አሏህ በልጆቻችሁ ጉዳይ አደራ ይላችኋል»። እንግዲህ ከወላጆች የበለጠ አሏህ አዛኝ ስለሆነ ወላጆች አደራ አስፈለጋቸው! “የልጆችን ነገር አደራ” ብሎ አርሀሙራሂሚን ጉዳዩን ወደሱ መለሰው።

አንድ ሰው ማግኜት ያለበት ከሚመለከተው ሸክምና ሀላፊነት አንፃር ነው ። በወጭ በኩል ሴቶች እንዳይጨነቁ ነው ያደረገው ሸርዑ ሙሉለሙሉ! ለዚህም አንዳንድ ኡለሞች “ማሉል መርአቲ ናሚን” ይላሉ (የሴት ገንዘብ በባህሪው መልማት ብቻ ነው) ካላባከነችው በስተቀር ፥ የራሷንም ወጭ ባሏ ነው መሸፈን ያለበት ። ስጦታም ብታገኝ ፣ ውርስም ብታገኝ ፣ በምንም መልኩ ብታገኝ የሷን ገንዘብ እሷ በፍቃዷ ካላወጣች በስተቀር ሙሉ ለሙሉ የወጭን ሀላፊነት ወንድ አንዲሸከም ነው አሏህ ያደረገው ። አባት ከዛ ባል ከሌሉም ወንድም እንዲወጣ ነው ያደረገው ። እሷ መከራ ማየት የለባትም .. አንተ አገልጋይ ነህ ኸድም ነው በአጭሩ ። ወንዱ ሲያገባ ግን ከፍሎ ነው ፡ ተከፍሎት አይደለም ። በትዳር ሲኖር ሁሉን ወጭ የሚሸፍነው እሱ ነው ፣ የሚሸፍንለት የለም ። ኢንፋቅ የሚባል ነገር እሱን ነው የሚመለከተው ። ይሄ ጠቅለል ያለ መንዙመተል ኢስላም ነው ።

አንድ ሰው ወራሽ መሆን የሚችለው ከሶስቱ አንዱ ውስጥ ከሆነ ነው ። አንደኛው መወለድ ነው ( ወላጅ ወይም ልጅ መሆን) ፣ ሌላኛው ጋብቻ ነው ፣ ሌላኛው ደግሞ ወላእ ነው ( ከባርነት ነፃ የወጣ ማለት ነው) ። የጀመረው ከልጅ ነው ፥ ብዙ ጊዜ ወላጆች ቀድመው ነው የሚሄዱትና አልፎ አልፎ ተቃራኒም አለ ግን ኖርማል ከሆነው ነገር ጀመረ ።

የዚህ አያ ሰበበ ኑዙል እንዲህ ነው ፦
ሰእድ ኢብኑ ረቢዕ የተባለ ሶሃቢይ ኡሁድ ላይ ሸሂድ ሆነ ፣ ሚስቱ ወደ ረሱል ﷺ መጥታ እነዚህ የሰዕድ 2 ሴት ልጆች ናቸው ፣ አጎታቸው መጥቶ ያለውን ገንዘብ ጥርግርግ አድርጎ ወሰደባቸው (ተመልከቱ የጃሂሊያን ሁኔታ እነዚህን የቲሞች መርዳት ሲገባው የወንድሜ ገንዘብ ነው ብሎ ለሚስቲቱም ሳያስቀር ወሰደ ) እንዴት ይደረግ ብላ ጠየቀች ። ረሱልም በዚህ ጉዳይ የሚፈርደው አሏህ ነው አሉ ፣ ይህ አያ ወረደ .. ፣ የአሏህ መልክተኛ ወደ ልጆቹ አጎት ለሰዕድ ልጆች 2/3ኛውን ስጥ ብለው ላኩበት ።

እንግዲህ ወራሾች ወንድና ሴት ልጆች ብቻ ከሆኑ 2/3 ኛው ለወንዱ 1/3ኛው ለሴት ስጡ ፣ ሁለትና ከሁለት በላይ ሴት ካለ ደግሞ 2/3 ኛው ለሴቶቹ ይሰጣቸዋል ፣ አንድ ሴት ብቻ ከሆነች ደግሞ ግማሽ ይሰጣታል አለና የልጆችን በዚህ ጨረሰ ።
ወላጆችና የጋብቻውን በቀጣይ እናየዋለን..!

https://t.me/+VUDQfAORZa43NDM0


ኢስላሚክ ጥያቄዎች እና ሀዲሶች ❤ dan repost
954246760.tejjwid1_1.pdf
203.4Kb
📘 ተጅዊድ

ቁርአን የጥበቦች ሁሉ መፍለቂያ ድንቅ እና ታላቅ መለኮታዊ መጽሐፍ ሲሆን ዘላለማዊ ተአምር የሆነ ሙሉ የህይወት መመሪያ ነው። ይህን መለኮታዊ መጽሐፍ እያስተነተን ተረድተነው ለማንበብ ደግሞ ከቁርአን ጋር በሚኖረን ትስስር ልንላበሳቸው የሚገቡ ደንቦችና በስርአት ለማንበብ የሚያስችሉን ህጎች አሉ። ይህም የተጅዊድ ህግ ተብሎ ይጠራል። ለዚህም ነው አሏሁ አዘወጀል "وَرَتِّلِ الْقُرْآنَ تَرْتِيلًا" ያለን። እነዚህን ህግጋቶች ለመረዳት እንሆ በተከታዩ መፅሀፍ በአማርኛ ተዘጋጅቶልናል  ዳውንሎድ በማድረግ እንማማር !

@Islamic_picture_wallpaper
@Islamic_picture_wallpaper


🌹ኢስላማዊ እውቀት ለሁሉም🌹 dan repost
ተፍሲር ሱረቱ ኒሳዕ ፥ part 4
ከአንቀፅ 7-10

የሱረቱ ኒሳዕ 7ኛው አያ መውረድ ብዙ ነገርን ቀይሯል ፣ በጃሂሊያው ማህበረሰብ ሴት ምንም አይነት ድርሻ አልነበራትም ..
ምክንያቱም መውረስ የሚገባው ጠላት የሚመክት እንጂ ፈረስ ያልጋለበ ፣ በሰይፍ ያልመታ ፣ ቀስት ያልወረወረ ሰው እንዴት ብሎ ይወርሳል ይሉ ነበር ። እንደውም ሴቶችን እንደ እቃ በመቁጠርም እነሱም ይወረሱ ነበር - በጃሂሊያ ። ይህ በአረቦች ብቻ ሳይሆን በሩሞችም ፣ በፋርሶችም ዘንድ የነበረ ልማድ ነበር። ከዚህ አያ መውረድ በኋላ ግን መጠኑ ይለያይ እንጂ ሴትም ድርሻ አላት ትወርሳለች አለን ።

ባለ ደርሻዎች ሲከፋፈሉ ዙሪያውን የሚታዘቡ ሰዎች ይኖራሉ ። የነሱንም ነገር በ8ኛው አያ ተናገረ ። የሀብታምን ገንዘብ ልጆቹ ፣ እህት ወንድሞቹ ወይም ወላጆቹ ቁጭ ብለው ዳጎስ ያለ ድርሻ ሲያገኙ ጎረቤት ያለ የቲም ቁጭ ብሏል ፣ ሚስኪኖች አይናቸው እየቃበዘ እኛም ቢደርሰን ብለው ይጓጓሉ ። እነዛ ሰዎች እንዳይረሱ ምንም እንኳ መጠኑ ይህን ያህል ነው ባይባልም የተወሰነ ነገር ቀነስ አድርጋችሁ ስጡ «ተገቢ ንግግርም ተናገሯቸውም» አለን ፣ ሁሌም ከአንድ ስራ በኋላ መልካም ንግግርን ጎን ለጎን ነው የሚያስቀምጠው ቁርዐን ልብ በሉ ! ንግግር ተፅኖው ከባድ ነው ፣ ጦር ካቆሰለው ንግግር ያቆሰለው ያስቸግራል አይሽርም ። እንደገና ብዙ ችግሮችን በንግግር መፍታት ይቻላል ።

9ነኛው አያ ደግሞ ውርስ የሚያከፋፍሉ ሰዎች በሆነ ሰበብ ወደ አንድ አካል እንዳያደሉ "ነግ በኔ" ይበሉ አለ። ለልጆቹ ፊውቸር የሚሰጋ ሰው በሌላ ሰው ልጅ ላይ ግፍ መስራት የለበትም። እንዲሁ ወሲያ ላይ ሟች ያልሆነ ኑዛዜ ሲናገር የሰማ እንደሆነ መከልክልም አለበት ፣ አንዳንዴ ወራሾችን መጉዳት የሚፈልግ ሰው ይኖራል ። ለፍቼ ለፍቼ ይሄ መናጢ ልጅ ሊወርሰው ነው አንዴ ገንዘቤን :) "ሰደቃ ነው የማደርገው" ሊል ይችላል፣ ለዛም ነው 1/3 ድረስ እንጂ ከዛ በላይ ሰደቃ መስጠት አይቻልም ። "አሱሉሱ ወሱሉሱ ከሲር" ብለዋል ሀቢባችን ፣ በሌላ ሀዲሳቸው ድግሞ “ወራሾችህን ራሳቸውን የቻሉ አድርገህ ጥለህ መሄድ ድሆች አድርገህ እጃቸውን ወደ ሰው የሚዘረጉ አድርጎ ከመሄድ የተሻለ ነው” ብለዋል ።
10ኛው አያ የየቲም ገንዘብ መብላት እሳት መብላት እንደሆነ ይነግረናል ። ረሱልም “የሁለት ደካማ ሰዎችን (የቲሞች እና ሴቶች) ብር ከመብላት እንድትጠነቀቁ አደራ እላችኋለሁ” ብለዋውናል።

https://t.me/+VUDQfAORZa43NDM0


🌹ኢስላማዊ እውቀት ለሁሉም🌹 dan repost
የሴቶች ምዕራፍ ትንታኔ ክፍል ሶስት፥ አንቀፅ ቁጥር ⑥

ትናንት ለሰፊሆች ብር መስጠት ተገቢነት እንደሌለውና እኛ ልንጠብቅላቸው እንደሚገባ ተነጋግረናል ። ታዲያ እስከመቼ ነው የሰፊኾችን ገንዘብ እኛ እየጠበቅን ፣ እኛ እያለማን ፣ እኛ እየተንከባከብን እኛ ወጭ እየሰጠናቸው የምንኖረው? ቢባል ፤ ነፍሳቸውን አውቀው ገንዘባቸውን ማስተዳደር የሚችሉበት አቅም ላይ እስከሚደርሱ ነው ። ለዚህ ብሎ ምን አለ ፦ «ወብተሉል የታማ/የቲሞችን ፈትኗቸው» ማለት ብቃታቸውን ከዚህ በኋላ ብሩ ቢሰጠው ማስተዳደር ይችላል ወይስ አይችሉም? የሚለውን ማለት ነው።
"ሀታ ኢዛ በለጙ ኒካህ" ጋብቻ እስከሚደርሱ ድረስ» በሸርዕ ደረጃ የተቀመጡ መስፈርቶች አሉ ፣ እነዛ ሲሟሉ ህፃን ከሚለው ወጥቷል ። ነገር ግን አንዳንዴ አካለ መጠን ደርሰውም የአእምሮ ብስለቱ ገና የሆነ ይኖራል ። ስለዚህ ምን አለ፦
"ፈኢን አነስቱም ሚንሁነ ሩሽደን/ ከፈተናው በኋላ ነፍስ ማወቅን ከታዘባችሁ ፣ ከተገነዘባችሁ «ፈድፈዑ ኢለይሂም አምዋለሁም/ገንዘቦቻቸውን ወደነሱ አስጠጉ»። "ሩሽድ" የሚለው በዲናቸው ላይ ጥሩ መሆናቸውንና በገንዘብ ጥበቃም ላይ ጥንቁቅ መሆናቸውን ስታውቁ ለማለት ነው ። አንዳንዴ ጎረምሳ ሆኖ ገንዘብ ሲሰጠው ወዳልሆነ አቅጣጫ የሚሄድ አለ .. ይሄ ሰው አይሰጠውም። ምክንያቱም አካሉ በስሏል አምሮው አልበሰለም።

ቀደም ብሎ ባለው አያ ላይ  “አምዋለኩም/ገንዘባችሁ” እያለ ነበር አሁን ደግሞ “አምዋለሁም/ገንዘባቸው” ይለናል ፣ ያኔ እንደዛ ያለው ከብክነት ለመታደግ ነው ፣ ዛሬ ደግሞ ሰዎቹ ራሳቸውን ስለቻሉ የነሱ ብር ተብሎ ወደ ባለቤቱ ይመለስ በሚል አገላለፅ ገለፀው - የቁርአን አገላለጽ ሁሌም ድንቅ ነው።
ለካ አካለ መጠን ሲደርሱ ገንዘባቸው ወደነሱ ይመለሳል። ያ ቀን ሳይደርስ በፊት ለምን ዛሬ ቀንጨብ ፣ ቀንጨብ አላደርግም የሚል ዟሊም እንዳይኖር ደግሞ "ወላ ተዕኩሉሃ ኢስራፈን" አለ በማባከን መልኩ ገንዘባቸውን እንዳትበሉ።
"ወቢዳረን አን የክበሩ" ነገ አድጎ ከእጄ ከመውጣቱ በፊት ዛሬ አትበሉ ። እናንተ ባለ አደራ እንጅ ባለ ገንዘብ አይደላችሁም ።

እንበልና ገንዘቡን ስንረከብ ልጁ የአንድ አመት ቢሆን አስራ አምሰት አመት በእኔ እጅ ነው ይሄ ገንዘብ ያለው ፣ ብሩን ማልማት አለብኝ ። አሁን ሊነሳ የሚችለው ጥያቄ ፦ በሱ ገንዘብ ላይ ጉልበቴን ፣ ጊዜዬን ..ሳባክን የራሴን ኑሮ ትቼ እንዴት ነው የሚሆነው? የሚል ጥያቄ እንደሚመጣ ስለሚያውቅ ምን አለ « ወመን ካነ ጘኒየን ፈልየስተዕፊፍ» የየቲም ገንዘብ የሚንከባከብ ሰው ከዛ ከየቲሙ ገንዘብ ውጭ የራሱ የሆነ ገቢ ኖሮት የተብቃቃ የሆነ ሰው ለአሏህ ብሎ ይስራ .. ክፍያ ሳይጠይቅ ። ከዚህ ነገር ይጠንቀቅ ወይም ይራቅ ።
ድሃ ከሆነሳ? የየቲሞችን ገንዘብ የሚያለማ ከሆነ የራሱ ስራ ሊቀር ነው ፣ የነሱን ትቶ ወደ ራሱ ስራ ከሄደ የዚህ የየቲም ገንዘብ ሊባክን ነው። እህ ምን ይሁን ታዲያ ? ... ደመወዝ ይመደብለት! «ወመን ካነ ፈቂረን ፈልየእኩል ቢልመዕሩፍ» የሚፈልገውን ያህል ሳይሆን የሚገባውን ያህል ደመወዝ ይመደብለት! ማነው የሚመድብለት? ከተባለ ያው ቤተዘመድ አለ ፣ ፍርድ ቤት ይኖራል ይህን በማስተዳደርህ ይሄ ይገባሀል ብሎ ይመድብለታል ። በዛ መልኩ መጠቀም ይችላል ። አሁንም ሌላ ጥያቄ ፦ ደሃ የሆነ የየቲም አሳዳጊ ይህን የየቲም ብር በደመወዝ መልኩ ከበላ በኋላ ሲያገኝ ይመልሳል ወይስ አይመልስም? በዚህ ላይ ፉቀሃወች ሁለት ቀውል አላቸው።
የመጀመሪያው .. አነስ ያለ መጠን የችግሩን ያህል ይመገብ መመለስ አይጠበቅበትም። የላቡ ስለሆነ ሌላ ቦታ ቢሰራ ሊያገኝ የሚችለውን ነው ያገኘው ችግር የለውም የሚሉ አሉ (ሻፊኢያዎች) ምክንያታቸው ደግሞ አያው «ፈልየእኩል ቢልመዕሩፍ» ሲል "ይመልስ" አላለምና ይላሉ ። ሁለተኛው ቀውል ደግሞ የየቲም ገንዘብ በመሰረቱ ክልክል ነውና ለችግር ቢፈቀድለትም ሲያገኝ የመመለስ ግዴታ አለበት ያሉ ኡለሞችም አሉ ።

ገንዘባቸውን አስረክቡ ካለ በኋላ አሁን ደግሞ ሲያስረክቡ ሞግዚቶች እንዳይበደሉ መስፈርት አስቀመጠ።ምን አለ «ፈኢዛ ደፈዕቱም ኢለይሂም አምዋለሁም» እናንተ አሳዳጊዎች የቲሞቹ አካለ መጠን ደርሰው ገንዘባቸውን ስታስረክቧቸው ዝም ብላችሁ ጠርታችሁ ና ውሰድ ሳይሆን «ፈአሽሂዱ አለይሂም/አስመስክሩባቸው » አለ ..ገንዘብ ያጨቃጭቃል ፣ የሚያናቁረውም የሚያፋቅረውም እሱ ነው ። ሙሲባ ነው ። ደግሞ ከሱ መብቃቃትም አይቻልም ። ስለዚህ የየቲሞቹን ዘመዶች አስቀምጦ ፦ የተረከብኩት ይሄ ይሄ ነበር ፣ ይህን ያህል ወጭ በማሳደግ ሂደት አውጥቻለሁ ፣ ይሄን ያህል ልማት ለምቷል ፣ በጥቅሉ ዛሬ የቀረለት ደግሞ ይሄ ነው ብሎ በምስክር ፊት ያስረክብ ይላል ። 🛑 ምስክር ከሌለ በኋላ የቲሙ ሊከዳ ይችላል ..ገንዘቤን ሲበላ ኖሮ መጨረሻ ላይ የቀረችውን እንኳ ሳያስረክበኝ ቀረ ሊል ይችላል ። አልያም አሳዳጊው ትንሽ ነገር ወርወር አድርጎ ሌላውን ለራሱ ሊያስቀር ይችላል። ሲረከብም ምስክር መኖር እንዳለበት ሁሉ ወጭዎችም በትክክል መመዝገብ አለባቸው ፣ ሲያስረክብም በምስክር ፊት ቆጥሮ ማስረከብ ይጠበቅበታል።ይሄ ህግ ነው ።በዚህ ህግ የሚኖር ማህበረሰብ ሚጨቃጨቅበት ምንም ሰበብ የለም!! ተቋጥሯል፣ ተደንግጎለታል ።
አስመስክረናል ብሎ ደግሞ የሆኑ የሆኑ ነገሮችን ደብቆ ፣ አታሎ የሚሰራ ካለ ደግሞ አብሽር ፣ የሰው ምስክር ባይኖርህ እኔ አለሁ እያለ ነው (ወከፋ ቢሏሂ ሀሲባ /ሂሳብ አድራጊ በአሏህ ይብቃ) ማንኛውንም ነገር አሏህ በመዝገቡ ላይ አስቀምጦታል ስለዚህ ዛሬ አማና ያልተወጣ ሰው ነገ ረቡል አለሚን ይተሳሰበዋል። ከምስክር ሁሉ በላይ ነው አሏህ .. ይሄ ስሜት ልቡ ውስጥ ያለ ሰው ለማጭበርበር ፣ አኼራን ለመሸጥ አይጋለጥም .. ለህጉ ያህል ነገ ላለመጠየቅ ምስክሮችን ያስቀምጣል ፣ ረቡል አለሚን ፊት ደግሞ ላለመጠየቅ የራሱን ጥንቃቄ ያደርጋል ። ተቅዋ ካለ ፣ ህግ ካለ በደል የለም ።

በመሰረቱ የየቲም ገንዘብን ወደማስተዳደር ሰፍ ብሎ መግባት አደጋ ነው ፣ እንደውም አፊያ የፈለገ ሰው ከመጀመሪያው ይሄ ነገር ይቅርብኝ ቢል ይሻላል ። እሱ ካልገባ ይጠፋባቸዋል ብሎ ካልሰጋ በስተቀር ..ረሱል ﷺ ለአቡዘር «ኢኒ አራከ ዶዒፋ/ አቡዘር ሆይ እንደው ሳይህ ደከም ያልክ ሰው ነህ (ገራገር ነበሩ) ፣ እኔ ደግሞ ላንተ ለራሴ የምወደውን እወድልሃለሁ (ለራሴ የምመክረውን እመክርሃለሁ እንደማለት ነው) ፦ በሁለት ሰው መካከል አሚር እንዳትሆን (ስልጣንን ሽሻት ማለት ነው) የየቲም ገንዘብ ላይም እንዳትሾም» ብለውታል ፤ መወጣቱ ከባድ ስለሆነ ማለት ነው ።

https://t.me/+VUDQfAORZa43NDM0




🌹ኢስላማዊ እውቀት ለሁሉም🌹 dan repost
ሱረቱል ኒሳእ ክፍል ሁለት

ይህች ምዕራፍ ወሳኝና አስፈላጊ የሆኑ ገንዘብ ነክ ጉዳዮችን በጥልቀት እና በስፋት ታስቀምጣለች ብለናል። ለዛም ነው በዝርዝር ለማየት የወሰነው
وَلَا تُوْتُواْ السُّفَهَاء أَمْوَالَكُمُ
«ሱፈሃዕ» የሚለው አስተሳሰቡ ደካማ ፣ ነገሮችን በመልካም ማስተባበር የማይችሉ ፣ አዕምሮው ብቁ ያልሆነ ሰውን ብር ከሰጠነው ነገን ስለማያስቡ .. እጃቸው የገባውንም መጠበቅም ሆነ ማልማት ስለማይችሉ ባልሆነ አቅጣጫ ያባክኑትና ..ገንዘቡም ጠፍቶ እነሱም ተመፅዋቾች እና ጥገኞች ይሆናሉ ። ስለዚህ ሊሰጣቸው አይገባም ነው ። "ሱፈሓዕ" ከየቲሞች አካለ መጠን ያልደረሱና ሩሽድ የሌላቸውን ወይንም ደግሞ ትልቅም ሆኖ አቅሉ ደካማ የሆነን ይመለከታል ፣ ፆታ አይለይም ። ታዲያ እነዚህን ሰዎች ከቤተዘመድ መካከል ገንዘቦቻቸውን የሚያስቀምጥላቸው ፣ በሚያስፈልጋቸው ልክ ወጭ የሚያደርግላቸው ሀላፊ ፣ ወኪል፣ ዋቢ ያፈልጋቸዋል ማለት ነው። ይህን ሲገልፅ በሚገርም መልኩ ነው ያስቀመጠው።

አስተውሉ "አምዋለኩም/ገንዘቦቻችሁ" ነው ያለው ፣ ገንዘቡ የነሱ ሆኖ ሳለ ለምን የናንተ አለ ?! ይሄ ዲነል ኢስላም በገንዘብ ላይ ያለውን አጠቃላይ ፍልስፍና የሚገልፅ ነው -በአንድ ተውላጠ ስም "ኩም" በምትለው ዶሚር! ። ገንዘብ የተወሰኑ ሰዎች ንብረት ነው ተብሎ ቢመዘገብም በአጠቃላይ የማህበረሰቡም ጭምር ነው ። የግለሰቦች ብቻ አይደለም ፣ የሚያባክኑትም ከሆነ አጠቃላይ በአካባቢው የሚኖር ሰው ነው የሚጎዳው ። ስለዚህ አባካኞች እንዲያባክኑ ሊፈቀድ አይገባም ማለት ነው ። የኛ ነው ብላችሁ መጠበቅ አለባችሁ እያለን ነው ። ምክንያቱም ገንዘብ ካለ.. ልማት አለ ፣ ስራ አለ ፣ ንግድ አለ ፣ ኪራይ አለ፣ ተቀጥሮ መስራት ይገኛል 
... ቅብብሎሹ ይቀጥላል ። ገንዘብ ደግሞ የሚያድገው ቅብብሎሽ ሲኖር ነው.. አለዛ እየጠፋ ነው የሚሄደው ፣ ለሰፊህ ከሰጠኸው ባልሆነ መልኩ ያውለዋል ። አባካኞች የሰይጣን ወንድሞች ናቸው ይለናል። ቁርዓን ስለ መለገስ ያስተማረውን ያህል ስለ መቆጠብም ያስተምራል ። መቆጠብ ፣ ማልማት፣ መንከባከብ ልዩ ትኩረት ተሰጥቶታልና እነዚህ ሰፊሆች ብሩን ካስረከብካቸው በአጭር ጊዜ ውሥጥ ብክንክን ያደርጉትና ዳግም የዚያው የማህበረሰቡ ሸክም ነው የሚሆኑት ። በባልተቤትነት አይን ማየትና መንከባከብ ይጠበቅባችኋል ማለት ነው።

أَمْوَالَكُمُ الَّتِي جَعَلَ اللّهُ لَكُمْ قِيَاماً
አጠቃላይ ስለ ገንዘብ ሲነግረን መቋቋሚያ አድርጎ የፈጠረላችሁ ይለናል ። በሰዎች መካከል ገንዘብ የሚለው ነገር የተፈጠረው ዱንያ ላይ ቆሞ መኖር እንዲችሉ አሏህ ስለሻ ነው ። ለልብሳቸው ፣ ለቁርሳቸው ፣ ለቤተሰቡ ፣ ለወገኑ እያካፈለ ማህበረሰቡ ቆሞ እንዲቀጥል ነው ። አሶቡል ሀያት ነው / የህይወት የደም ቧንቧ ነው - ገንዘብ ፣ እንደፈለገ መመዝበር የለበትም ። ሲመጣም አግባብነት ባለው መንገድ መከሰብ አለበት ፤ ሲወጣም ጤናማ በሆነ መልኩ ነው መውጣት ያለበት ።
وَارْزُقُوهُمْ فِيهَا
ገንዘቦቻቸውን ተቆጣጠሩላቸው ፣ አትስጧቸው ሲባል እንዳይበሉ ፣ እንዳይጠጡ ማለት አይደለም! ከገንዘባቸው ላይ እናንተ አቅል ያላችሁ ሞግዚቶች ሪዝቃቸውን ስጧቸው «ወክሱሁም» አልብሷቸው ። ይጠቀሙበት ፣ ይብሉ ፣ ይጠጡ ፣ ይልበሱ የሰው ጥገኛ እነዳይሆኑ ይጠበቅላቸው ።

በገዛ ገንዘቤ አንተ ላየ ላይ ተሹመህ እየቆጠርክ ትሰጠኛለህ እንዴ? ብለው እንዳይከፉ ደግሞ ❝« وَقُولُواْ لَهُمْ قَوْلاً مَّعْرُوفًا / ጥሩ የሆነ ቃል ተናገሯቸው❞ አለን ። ግዴለም አንተ ልጅ ነህ ፡ አባትህ የለም የሚጠቅምህን የማውቀው እኔ ነኝ .. ላንተው መስለሃ ነው ቢቀመጥልህ ፣ ቢለማልህ ፣ ቢያድግልህ ነገ ላንተው ነው .. የመሳሰሉ ጥሩ የሆኑ ቃልም ተናገሯቸው ። ሞራልም ይጠበቅ ማለት ነው !! ፣ ገንዘብ ብቻ አይደለም! አያችሁ የኢስላም ተሽሪዕ ጥበቡ ሁሉን ነገር መጥኖ እንደሚሄድ .. ሰው መስጠት ብቻ አያስተካክለውም ። ንግግርም ፣ አቀራረብም የራሱ የሆነ ሚና አለው "ከፍትፍቱ ፊቱ" ይባል የለ ። እያበላህ ግን ክፉ የምትናገረው ወይም ክፉ ፊት የምታሳየው ከሆነ "ምነው በቀረብኝ" ይላል ፣ ለሱ ኸይር እየሰራህ ራሱ ማመናጨቅ መኖር አይገባውም ። ጥሩ በሆነ መልኩ አስተናግዱ ይለናል ... !

ለዛሬ አንዲቱን አያ ( 5ኛዋን) በጥልቀት ለማየት ሞክረናል .. በዚህ መልኩ ይቀጥል...

https://t.me/+VUDQfAORZa43NDM0


🌹ኢስላማዊ እውቀት ለሁሉም🌹 dan repost
✓ ተፍሲር ሱረቱ ኒሳዕ ...

ሱረቱ አለ ኢምራን የጨረሰው «ያአዩሃለዚነ አመኑ ኢስቢሩ ወሷቢሩ ወራቢጡ “ወተቁሏህ” » በማለት "አማኞችን" በማናገር ነበር ፣ ሱረቱ ኒሳዕ ደግሞ ሲጀምር ይህንኑ የተቅዋ ትዕዛዝ "ለመላ የሰው ዘሮች" በማስተላለፍ ነው «ያአዩሃናሱ ኢተቁ-ረበኩም..»

ቁጥሩ ይርቃል እንጂ ዞሮ ዞሮ የሰው ልጅ ሁላ ዘመዳም መሆኑን "ከአንዲት ነፍስ የፈጠራችሁ" በማለት ነገረን ፡ በመቀጠል "ዝምድናን ጠብቁ" ይለንና ዘመድ የሌለው እንዳይረሳ ደግሞ ስለ የቲሞች ይነግረናል። ዘመድ ነኝ በሚል የየቲም ብር እንዳይበዘበዝ "ኢነሁ ካነ ሁበን ከቢራ" በማለት የየቲም ገንዘብ መብላት ከሰባቱ ትላልቅ ሀጢአት አንዱ መሆኑን ያስታውሰናል።

وَإِنْ خِفْتُمْ أَلاَّ تُقْسِطُواْ فِي الْيَتَامَى
ይህን አያ ለመረዳት ለምሳሌ የሚያሳድጋት የቲም ልጅ ለጋብቻ ሀላል የሆነች የአጎትን ልጅ ምናምን ሊያሳድግ ይችላል ፣ መጨረሻ ግን እድሜዋ ሲደርስ ቆንጆ ከሆነች ወይም ለብሯ ብሎ ሌላ ሰው ከሚያገባት እኔ ላግባት ይልና መህሯን ቀነስ አድርጎ ለራሱ ያገባታል ፣ ይሄ አድሎ ነው! ካገባሃት ከሌላ ሚስትህ ጋር እኩል አድርገህ ወይም ደግሞ እሷን የሚመጥን ኑሮ ላይ ማኖር ግዴታ ነው። ይህን ማድረግ አልችልም ካልክ ግን ለገንዘቧ ፣ ለውበቷ ፣ ለዲኗ የሚፈልጋት ይኖራል .. እድሏን ትጠብቅ ፣ ገንዘቧን አስረክብ ! አንተ ማስቀረት አይፈቀድልክም ነው ። "ፈንኪሁ" ሲል ሌላ የተፈቀደላችሁን አግቡ ሁለት ፣ ሶስት ፣ አራት ተፈቅዶላችኋል ። ሺዓዎች "መስና" የሚለውን 2×2 ፡ ሩባዕ የሚለውን 4 ሲባዛ በ4 በማለት ነው የሚፈስሩት ፤ ይህ ግን በቋንቋ ደረጃም ስህተት ነው ። ለምሳሌ ስለ መላኢኮች ክንፍ ሲነግረን "መስና" ሲል እያንዳንዳቸው ሁለት ክንፍ ያላቸው ፣ "ወሱላስ" ሲል አንዱ ሶስት ሌላኛውም ሶስት ያላቸው እንጂ 3 ሲባዛ በ3 ማለት አይደለም ።

እስከ 4 ተፈቅዷል ሲባል ታዲያ ፍትህ ሊኖር ግድ ነው ። ፍትህ ሲባል ...በልብሳቸው፣ በመኖሪያቸው ፣ በቀለባቸው፣ በሚደረገው ነገር ሁሉ እኩል ማድረግ አለበት! እዚች ሁለት ቀን ካደረ እዛች ሁለት ቀን ማደር ግዴታው ነው ። ወደ መንገድ ሲሄድም መጀመሪያ እጣ መጣል አለበት ፣ ሁለተኛው ግን የሌላይቱ ይመጣል በዚህ መልኩ ነው የተደነገገው ። በቁሳዊ ነገር እኩል ማድረግ ግድ ነው በተቻለ መጠን ..

ነገር ግን ፍቅርን እኩል መክፈል አይቻልም ። አንዷ ዘንድ የሚያገኘውን ሌላዋ ዘንድ ካላገኘ (በባህሪዋ ፣ በውበቷ ፣ በኺድማዋ ...በተለያየ ነገር) ወደ አንዷ ልቡ ሊዘነብል ይችላል፤ ይሄ ከአቅም በላይ የሆነው አፍው ይደረጋል ። ይህን ሲያመለክት እዚሁ ሱራ 129 ላይ «በሴቶች መካከል 100% እኩል ልታደርጉ አትችሉም ጉጉት እንኳ ቢኖራችሁ ታዲያ ሙሉ ለሙሉ እንዳታዘንብሉ ተጠንቀቁ» ብሎናል ። ረሱልም ሁሉንም ነገር ያከፋፍሉና «ሀዛ ቀስሚ ፊማአምሊክ፡ፈላቱአሂዝኒ ፊማ ላአምሊክ/እኔ በምችለው ይሄ ነው የኔ አከፋፈል ፤ በማልችለው አትያዘኝ ፣ አትውቀሰኝ ጌታዬ» ይሉ ነበር ። ይህን ያህል ጥንቃቄ ካደረገ ከዛ ውጭ ያለውን አሏህ አፍው ይላል ማለት ነው ።

فَإِنْ خِفْتُمْ أَلاَّ تَعْدِلُواْ فَوَاحِدَةً
❝አለማስተካከልን ብትፈሩ አንዲትን ብቻ አግቡ!❞

ሊኩሊ ሳቂጠቲን ላቂጥ / የወደቀ ሁሉ አንሺ አያጣም እንደሚባለው  ..ሁሉም ሰው ቢጤውን ፈልጎ እራሱን ኢዕፋፍ ማድረግ ያስፈልጋል። መጀመሪያ "መስና " በማለት በሁለት ነው የጀመረው .. ሸሪዓው የሰው ዘር እንዲበዛ ይፈልጋል፣ ነብዩም ﷺ ወላድና ወዳድ አግቡ "ፈኢኒ ኡካሲሩ ቢኩሙል ኡመም" ብለዋል ።

ذَلِكَ أَدْنَى أَلاَّ تَعُولُواْ
የሚለው ሁለት ትርጉም አለው፦ አንደኛው - ግፍ አንዳትሰሩ ፣ አድሎ ውስጥ አንዳትገቡ በአንድ ተብቃቁ እንደማለት ሲሆን ሁለተኛው ፍች ደግሞ እንዳትደኸዩ ማለትም ይሆናል ፥ ቤተሰብ ሲበዛ ከገቢህ ጋር የማይመጣጠን ከሆነ አቅምህን ያንገዳግዳልና በአንድ ተብቃቃ ተብሎም ይፈሰራል።

وَاتُواْ النَّسَاء صَدُقَاتِهِنَّ نِحْلَةً
"ሶዱቃ" የሚለው ቃል ሲድቅ ከሚለው ይመሰሰላል ፡ ትዳሩን ሷዲቅ የሚያደርገው መህሩ ነው በማለትም ይፈስሩታል ፣
“ኒህላ” የሚለው ግዴታ ወይም ካንተ በጎ ፈቃደኝነት ማለት ነው። ደስ እያለክ out of love ስጥ እንጂ ምን ይሄን ሸክም ቶሎ ሰጥቼ ልገላገል¡ በሚል መንፈስ አይሁን! ብዙ ሰው መጀመሪያ ላይ መህር ቃል ሲገባ አይፈራም ። ደግሞ መህርን ሙሉ ለሙሉ ዱቤ አድርገነዋል ማህበራችን ውስጥ :) አላያችሁም ለሰርጉ ብዙ ሺዎችን ያወጣና መህር ላይ ሲመጣ ወደፊት የሚከፈል ይላል፣ ወደፊት ስለሆነ ቀላል ይመስለዋል .. አንድ ቀን አብሮ ካደረ ጀምሮ በእርሱ ላይ ዋጂብ ነው። ቢሞት እንኳ ሰው ዞልሞ ነው የሚሞተው ማለት ነው። ደስ እያለው መስጠት ተገቢ ነው ፣ ሀዲያ አንደሚሰጥ ሰው (romantic gift) ያድርገው ነው ሀሳቡ ። እዳ ነው ፣ ሸክም ነው በሚል መሆን የለበትም ። ህይዎቷን ሰጥታካለች ፤ አንተም ህይወትክን ሰጥተካታል ..ገንዘብ ሊያጨቃጭቅ አይገባም ።

ባይሆን ሴቷም ይቅርብኝ ካለች ወይም ከሰጣት በኋላ ይህችን ለእንዲህ አድርግባት ብላ ከሰጠችው በፍቃደኝነት ከሆነ ችግር የለውም።
فَإِن طِبْنَ لَكُمْ عَن شَيْءٍ مِّنْهُ نَفْسًا فَكُلُوهُ هَنِييًا مَّرِييًا 
በፈቃደኝነቷ ከሰጠችህ እኔው ሰጥቼ እኔው ልጠቀምበት? ብለህ አትሳቀቅ ፥ ተጠቀምበት take it, and enjoy it ! በመሰረቱ የሰዎቹ መፈቃቀር ነው እንጂ የሚፈለገው ገንዘቡ አይደለም .. ገንዘቡ ይመጣል ይሄዳል « አልማሉ ዚሉን ዛኢል» ይላሉ .. ብር እንደ ጥላ ነው አሁን ያንዣብባል አሁን ይጠፋል!

ይቀጥላል ..!
መልካም መስሎ ከታያችሁ ሸር አድርጉት ፣ በጋራ ምንዳ እናግኝ
  خيركم من تعلم القرآن وعلمه 

https://t.me/+VUDQfAORZa43NDM0

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.

780

obunachilar
Kanal statistikasi