የማንም ጓጆ በእውነት ብቻ አልተሰራም ። እውነት በመውደድ ፊት አቅም የለውም ። እውነት ላይ ክችች ያሉ ሰዎች ቤታቸው ሲፈርስ ፣ ከስራ ሲባረሩ ፣ ስራ ሲበላሽባቸው ነው ያየሁት ....
Undeniable truth !!
የሞቀ ቤት ያላቸው ብዙ ቤታቸውን ሊያቀዘቅዘው የሚችል ነገር ታግሰው ነው !! ሳድግ ያየሁት ጥበብ እሱን ነው ። መኖር ያሳየኝ እውነት ይሄ ነው ።
የሚያኖረው መለሳለሳችን ነው !!
ደረቅ እውነት አያሸንፍም። እውነት ብቻውን አያሻግርም ። እሚያኖረን ጥበባችን ነው ። የጎጆ መሰረት እውነት አይደለም መተላለፍ ነው።
ሁሉም የሞቀ ቤት ውስጥ የታለፈ ፣ይቅር የተባለ አደባባይ የማይነገር፣ ያልተነገረ ገበና አለ ።
እየተላለፍን ! ✋ source -
https://t.me/ademeteku Adhanom Mitiku