ዳጉ-ጆርናል/Dagu-Journal


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic


The best fiction is far more true than any journalism
📢 ተዓማኒ የመረጃ ምንጭ ፤ ለሙያው ስነምግባር ተገዢ በሆኑ ጋዜጠኞች ብቻ
👉 በፌስቡክ ገፆቻችን https://www.facebook.com/simon.dereje.56
👉 https://www.facebook.com/mik0Man

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Statistics
Posts filter


ቅዳሜን ከእኛ ጋር" ፕሮግራም በተወዳጁ ብስራት ኤፍ.ኤም 101.1 ዛሬ ይመለሳል፤ ስንመለስ...

[ ] በልዩ ፕሮግራም ቅዳሜን ከእኛ ጋር ዛሬ የሬዲዮ ሞገዳችሁን 101.1 ላይ ካደረጋችሁ አብረን እንቆያለን። 

[ ]  ተወዳጁን ደራሲ ፣ አርታኢ እና ጋዜጠኛ ጋሽ ስብሃት ገ/እግዚአብሔር ዛሬ እንዘክራለን። ከስብሃት ንግግሮች የማይረሱት የቱን ይሆን እስቲ ይንገሩን። እርሱ ደራሲ ፣ አርታኢ እና ጋዜጠኛ ብቻ አልነበረም የልብ ወለድ ድርሰር ገፀ ባህሪ ጭምር ነው።

[ ] 150 ዓመታትን ለመኖር እያቀደ በድንገት ሞት የቀደሙውን ማይክል ጃክሰንን ዛሬ እናነሳለን።

[ ] የእንግዳ ሰዓት ዛሬም ይኖረናል።

[ ] የ24ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች ዛሬ ይመለሳሉ። በእለተ ቅዳሜ ባለፉት አስር ውድድሮች ያልተሸነፈው ቫታሊቲ ስታዲየም ላይ የሚነግሰው በርንማውዝ መሪውን ሊቨርፑል ያስተናግዳልም የእለቱ ተጣበቂ ጨዋታ ነው። በምሳ ሰዓት ኖቲምግሃም ከሽንፈት ሀንግኦቨር ለመውጣት በብራይተን ይፈተናል።ኒውካስል ከፉልሃም እና ወልቭስ ከአስቶንቪላ ሌላው ተጠባቂ የእለቱ መርሃ ግብር ናቸው።

[ ] ባለፉት አምስት ጨዋታዎች ተመሳሳይ ነጥብ የሰበሰቡት አርሰናል እና ማንችስተር ሲቲ በኤምሬትስ ላይ ይፋለማሉ። አርሰናል ይህንን ጨዋታ ካሸነፈ ከሲቲ ጋር ያለውን የነጥብ ልዩነት ወደ ዘጠኝ ከፍ በማድረግ በዋንጫ ፉክክር ውስጥ ለመቆየት የሚያደርገውን ጥረት ያጠናክራል። ማንችስተር ዩናይትድ ካለፉት 11 የእርስ በእርስ ግንኙነት በክርስታል ፓላስ አምስት ጊዜ ሲሸነፍ ሶስት ነጥብ ተጋርቶ ማሸነፍ የቻለው ሶስት ጊዜ ብቻ ነው። ፓላስ ላይ ነገ ግብ የማያስቆጥሩ ከሆነ ዩናይትዶች በአራት ጨዋታ ግብ ካላስቆጠሩበት የአርሰናል የ1980ዎቹን መጥፎ ሪከርድ ይጋራሉ። ግምታችሁን ላኩልን

[ ] የቅዳሜ ወሬዎችን እያነሳሳን እንቆያለን ምርጥ ምርጥ ሙዚቃ ትጋበዛላችሁ፤ ተረክም አለ ፣ ስፖርታዊ ጥንቅር ከወቅታዊ መረጃዎች ጋር ተዘጋጅቷል።

ስፖንሰሮቻችን ፦
👉 ዘመን ባንክ
👉 ቨርጂኒያ ፋርማሲውቲካልስ
👉 ጣዕም ዳቦና ኬክ ቤት-ሻወርማን ይቅመሱ
👉 ፖል ፎቶ ቬሎና ሜክአፕ
👉 ማር ህይወት ሆስፒታል
👉 ግሎብ ሊንክ ፕሮፐርቲስ በሸራተን አዲስ
👉 ጃፋር የመፅሃፍት መደብር
👉ዲያፕላንትስ - ፍቱን የባህል ህክምና
👉 አውት ዲተርጀንት -የፅዳት መላ

ሁሌም ቅዳሜያችሁን ከ 5 እስከ 7 በተወዳጁ ጣቢያ ብስራት ኤፍ.ኤም 101.1 ላይ እንጠብቃችኃለን።

#ቅዳሜን ከእኛ ጋር
ለአዳዲስ እና ወቅታዊ መረጃዎች ቴሌግራም ቻናላችንን #ዳጉ_ጆርናል ይቀላቀሉ
ሊንክ :- @zena24now




በፒያሳ አድዋ 00 ፊትለፊት የሱቅ ባለቤት መሆን ይፈልጋሉ?

ቴምር ሪል እስቴት ከ900 ሺህ ብር ቅድመ ክፍያ ጀምሮ የንግድ ሱቆችን እየሸጥን እንገኛለን::

ከዚህ በፊት እዛው ፒያሳ ላይ ሁለት ሳይቶችን ሽጠን የጨረስን ሲሆን ይሄኛዉ በፒያሳ የመጨረሻ ሳይታችን ነዉ::

G+5 ሞል ሲሆን የሚንገነባዉ የማስረከብያ ጊዜ (delivery time)አንድ አመት ከተኩል ነዉ::

ለበለጠ መረጃ: በ 0928831219
                           0995126367 ይደዉሉልን::

                ቴምር ሪል እስቴት!


ገጣሚ እና የጦቢያ ግጥም በጃዝ ፕሮግራም አዘጋጅ ምስራቅ ተረፈ ለእስር ተዳረገች

ገጣሚ እና የጦቢያ ግጥም በጃዝ ፕሮግራም አዘጋጅ ምስራቅ ተረፈ ትናንት ጥር 22 ቀን 2017 ዓ.ም በፖሊስ ለጥያቄ ትፈለጊያለሽ ተብላ ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን እንደተወሰደች ታውቋል።

የመሠረት ሚድያ ምንጮች እንደጠቆሙት ምስራቅ ዛሬ ጥር 23 ቀን 2017 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ ፖሊስ ምርመራ ለማጣራት ጊዜ እንዲሰጠው ፌዴራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት አቅርቧት ፍርድ ቤቱ ፖሊስ ምርመራውን አጣርቶ እንዲያቀርብ 7 ቀን በመስጠት  ለጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም ቀጠሮ ሰቷል፣ ምስራቅ ተረፈ ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ተመልሳለች።

ምስራቅ የኪነጥበብ ምሽቶችን በሀገር ውስጥ እንዲሁም በውጭ ሀገራት በማዘጋጀት እንዲሁም የራሷን ግጥሞች በማቅረብ በብዛት ትታወቃለች።

እንደ ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ እና ገጣሚ ትእግስት ማሞ ያሉ የደመቁባቸውን ዝግጅቶች በማሰናዳት የምትታወቀው ግለሰቧ ግጥም፣ መነባንብ፣ ዲስኩር እንዲሁም ጥበብ እና ጥበብ ነክ ስራዎች ይበልጥ እንዲለመዱ እንደለፋች ብዙዎች ይናገራሉ።

ገጣሚ ምስራቅ አሁን ላይ የታሰረችበት ምክንያት ምን እንደሆነ ግልፅ እንዳልሆነ ታውቋል።

ምንጭ:- ከመሠረት

#ዳጉ_ጆርናል


ዱራን ወደ አል ናስር

የአስቶን ቪላው አጥቂ ጆን ዱራን በአምስት ዓመት ከመንፈቅ ውል በ77ሚሊዮን ዩሮ የውል ስምምነት የ አል-ናስር ተጫዋች ሁኗል 🇸🇦

#ዳጉ_ጆርናል


የብልፅግና ጉባዔ በፓርቲዎች ጉባዔ ታሪክ መላው ብሔር ብሔረሰብ ተወካይ ኖሮት የሚደረግ ብቸኛው ጉባዔ ነው- የብልፅግና ፓርቲ ፕሬዝዳንት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)

#ዳጉ_ጆርናል


«በብልፅግና ባለፉት ስድስት አመታት አንድም ታራሚ ቶርች (torch) አልተፈፀመበትም።» የብልፅግና ፓርቲ ሊቀመንበር አብይ አህመድ

#ዳጉ_ጆርናል


በነፃ እንዲገለገሉበት የተፈቀደውን አገልግሎት 20 ሺህ ብር እንዲከፍሉ ያደረገው ሰራተኛ በቁጥጥር ስር ዋለ

በአዲስ አበባ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፍቃድና ቁጥጥር ሰራተኛ የሆነው አቶ አብረሃም ኃይሉ የተባለው ባለሙያ አገልግሎት ፈልገው ከመጡ ተገልጋዮች ገንዘብ ካልሰጣችሁኝ አገልግሎት አልሰጥም በሚል ማስፈራሪያ 20 ሺህ ብር ሲቀበል በፖሊስ እጅ ከፍንጅ ተይዞ ጉዳዩ እየተጣራ መሆኑ የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ፅ/ቤት ገልጿል።

ህብረተሰቡ የመንግስትን አገልግሎት በነፃ የማግኘት መብት ያለው ሲሆን አንዳንድ ሥነ-ምግባር የጎደላቸው ባለሙያዎች የገቡትን ቃል ወደጎን በመተው አገልግሎትን በገንዘብ ለመሸጥ የመሞከርና ተግባሩን ፈፅመው የመገኘት ሁኔታ እንደሚስተዋል ተገልጿል።

ይህ ድርጊት ከገቡት ቃልና ከሀገራችን እሴትም ያፈነገጠ እንዲሁም ከአሰራርና ህግም አኳያ ፈፅሞ ወንጀል በመሆኑ ሌሎች ባለሙያዎች ከዚህ ግለሰብ ሊማሩ እንደሚገባም ተመላክቷል።

በቀጣይም በነፃ የሚሰጠው አገልግሎት ላይ እንዲህ ዓይነት የወንጀል ድርጊት የሚፈፅሙ አገልጋዮች ላይ ክትትሉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክፍለ ከተማ የክፍለ ከተማው ኮሙኒኬሽን ፅ/ቤት ዘግቧል::

#ዳጉ_ጆርናል


ደቡብ አፍሪካ እና ሩዋንዳ በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ጦርነት የተነሳ ቅራኔ ዉስጥ ገቡ

ፕሬዝዳንት ሲሪል ራማፎሳ በሩዋንዳ የሚደገፈውን ኤም 23 አማፂ ቡድን በምስራቅ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የደቡብ አፍሪካ ሰላም አስከባሪዎችን ገድሏል ሲሉ ከከሰሱ በኋላ የደቡብ አፍሪካ እና የሩዋንዳ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ሻክሯል።አማፂያኑ በጦር ሜዳው ትልቁን ግዛት ከመያዝ ባለፈ  የምስራቅ ኮንጎ  ትልቁን ከተማ ጎማን ተቆጣጥረዋል፡፡ደቡብ አፍሪካ ዲፕሎማሲያዊ ዉዝግብ ዉስጥ ከሩዋንዳ ጋር ከመግባት ባለፈ በወታደሮቿ ላይ ተጨማሪ ጥቃት ከተፈጸመ እንደ "ጦርነት አዋጅ" እንደሚቆጠር አስጠንቅቃለች።

የሩዋንዳው ፕሬዝዳንት ፖል ካጋሜ በበኩላቸዉ የኮንጐን መንግስት "የገዛ ህዝቡን እንዲዋጋ" ለመርዳት የተሳተፈችውን ደቡብ አፍሪካን ከሰዋል ።አማፂያኑ ከሩዋንዳ አዋሳኝ ዋና የንግድ ማዕከል ወደሆነችው ወደ ጎማ በመብረቃዊ ጥቃት ሲዘምቱ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በተደረገው ውጊያ ሰላም በማስከበር ላይ የነበሩ በአጠቃላይ 13 የደቡብ አፍሪካ ወታደሮች ተገድለዋል።ባለፈው ዓመት ሌሎች ሰባት ደቡብ አፍሪካውያን በምስራቅ ዲሞክራቲክ ኮንጎ ተገድለዋል፡፡

ይህም በሀገሪቱ ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በጦርነት ከተከሰቱት አሰቃቂ  የወታደሮች ህልፈት አንዱ ነዉ፡፡ደቡብ አፍሪካ እና ሩዋንዳ ለረጅም ጊዜ የቆየና የሻከረ አስቸጋሪ ግንኙነት ነበራቸው።እ.ኤ.አ. በ 2014 በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ በስደት የሚኖር የሩዋንዳ መንግስት ተቃዋሚ ቤት ላይ በደረሰ ጥቃት ሶስት የሩዋንዳ ዲፕሎማቶችን ማባረሯ ይታወሳል።የካጋሜ መንግስት 6 የደቡብ አፍሪካ ልዑካንን በማባረር ምላሽ ሰጥቷል።

800,000 የሚጠጉ ሰዎች የተገደሉበትን 30ኛ ዓመት የዘር ማጥፋት በዓል ምክንያት በማድረግ ባለፈው ዓመት ራማፎሳ በሩዋንዳ ያደረጉትን ጉብኝት ተከትሎ ውጥረቱ የቀዘቀዘ ይመስልም ነበር፡፡ነገር ግን በደቡባዊ አፍሪካ የልማት ማህበረሰብ (ሳድክ) የላከው የቀጣናው ሰላም አስከባሪ ኃይል አካል ሆነው ወደ ምሥራቃዊ ዲሞክራቲክ ኮንጎ የተሰማሩት ደቡብ አፍሪካውያን በታህሳስ 2023 መገደላቸዉን ተከትሎ ዉዝግባቸዉ አገርሽቷል፡፡

በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል




ቻይና በበሽታ ስጋት ከታንዛኒያ፣ ሶማሊያና ሌሎች በርካታ ሀገራት የሚገቡ የእንስሳት ምርቶችን አገደች

ቻይና በተለይም በጎች ወደ አገር ውስጥ እንዳይገቡ ከልክላለች። ከዚህ በተጨማሪ ቻይና ፍየል፣ዶሮና ሌሎች የእንስሳት ተዋፅኦም ከአፍሪካ፣እስያ እና አውሮፓ ወደ ሀገሯ እንዳይገቡ ከልክላለች።

ክልከላው ሊጣል የቻለዉ ከበግና ከፍየሎች የሚነሳ የእግርና የአፍ በሽታ መታየት መጀመሩን ተከትሎ ነው። እግዱ በህይወት ያሉ እንስሳት ብሎም የተቀነባበረ የስጋ ውጤት የሚያጠቃልል ሲሆን ቻይና እዚህ ውሳኔ ላይ ልትደርስ የቻለችውም የዓለም የእንስሳት ጤና ድርጅት በተለያዩ ሀገራት የእንስሳት በሽታ በወረርሺኝ መልኩ እየታየ ነው ማለቱን ተከትሎ ነው።

ከዓለማችን ግዙፍ የእንስሳት ስጋ ተቀባይ በሆነችዉ ቻይና የተወሰነው ውሳኔ እንደ ጋና፣ ሶማሊያ፣ ኳታር፣ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ናይጄርያ፣ ታንዛንያ፣ ቡልጋርያና ኤርትራ የመሳሰሉ ሀገራት ላይ ተፅእኖ ያሳድራል ተብሏል።

ከነዚህ ሀገራት በተጨማሪ ቻይና ከፍልስጤም፣ አፍጋኒስታን፣ ኔፓልና ባንግላዲሽ የሚመጡ የእንስሳት ተዋፅኦ ላይ እገዳ የጣለች ሲሆን ሙሉ በሙሉ ባይሆንም ከጀርመን ወደ ቻይና የሚላኩ የተወሰኑ የስጋ ምርቶች ላይም እገዳ ጥላለች።

በሚሊዮን ሙሴ
#ዳጉ_ጆርናል


የእስራኤል ምርኮኞች ቤተሰቦች ኔታንያሁ የተኩስ አቁም ስምምነቱን ማበላሸት የለባቸውም ሲሉ ተናገሩ

በጋዛ የታገቱ ቤተሰብ ያላቸው እስራኤላውያን የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ የተኩስ አቁም ስምምነቱን እንዳያበላሹ ጥሪ አቅርበዋል፡፡በ+972 መጽሔት ላይ የእስራኤል መንግስትን የሚተቸዉ ዩዳ ኮሄን የተባለዉ ግለሰብ የእስራኤል ወታደር የሆነዉ ልጁ ናምሩድ በጥቅምት 7 የተማረከ ሲሆን እስራኤል በጋዛ ፍልስጤማውያን ላይ የጦር ወንጀል እየፈፀመች ብቻ አይደለም "በእስራኤል ወታደሮች ላይ ወንጀል እየፈፀመች ነው"ሲል ተደምጧል፡፡

"ሁሉም ታጋቾች እንዲመለሱ እፈልጋለሁ" ሲልም አክሏል፡፡ከፍልስጤማውያን ጋር ይበልጥ የተረጋጋ እና ዘላቂ መፍትሄ ላይ መድረስ ተገቢ ነው። ሌላውን ጎን ማየት አለብን። አንዱ ወገን ሲያድግ ሌላኛው ሲሰቃይ ሊሆን አይችልም ። በሌላ በኩል ሐሙስ ዕለት በጋዛ ደቡባዊ ካን ዮኒስ የእስራኤል ምርኮኞችን በርካታ የፍልስጤም ታጠቂ ቡድኖች አሳልፈዉ ለሃማስ መስጠታቸዉ በአካባቢው ባሉ የተቃውሞ ቡድኖች መካከል ያለውን ትብብር እና ግንኙነት ቀጣይነት ያለው መሆኑን የጦርነት ተቆጣጣሪዎች ተናግረዋል ።

የጦርነት ጥናት ኢንስቲትዩት እና Critical Threats ፕሮጀክት (CTP)፣ መቀመጫቸውን አሜሪካ ያደረጉ ሁለት የመከላከያ ትንታኔ ተቋማት፣ የሃማስ ተዋጊዎች፣ የፍልስጤም ተቃዋሚ ኮሚቴ እና የፍልስጤም ሙጃሂዲን ንቅናቄ ሃይሎችን አብረዋቸው እንደነበሩ ያሳያል ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ ከእስራኤል ጋር ከ 15 ወራት ጦርነት በኋላ "በተዳከመ ተቋማዊ የማስተባበር ዘዴ ምክንያት ተግዳሮቶች" ሊያጋጥሟቸው በሚችሉበት በዚህ ወቅት በታጠቁት ቡድኖች መካከል ያለው አንድነት አስገራሚ መሆኑ ተገልጿል፡፡

የእስራኤል ማአሪቭ ጋዜጣ በበኩሉ በጋዛ ጦርነት ላይ የእስራኤልን የህዝብ አስተያየት የሚገመግም የዳሰሳ ጥናት አውጥቷል።በአላዛር ምርምር በተካሄደው የሕዝብ አስተያየት መሠረት 57 በመቶ የሚሆኑ እስራኤላውያን የሀገሪቱ የጦርነት ዓላማዎች "ሙሉ በሙሉ አልተሳካም" ሲሉ 32 በመቶ የሚሆኑት "ምንም አልተሳካም" ብለው ያምናሉ፡፡ምላሽ ከሰጡት ሰዎች መካከል አራት በመቶው ብቻ የእስራኤል የጦርነት ኢላማዉን በጋዛ "ሙሉ በሙሉ አሳክቷል" ብለዋል።

በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል




በህግ ትፈለጋለህ በማለት አንድን ግለሰብ ያላግባብ የገደሉ ሁለት የቀበሌ አመራሮች በእስራት ተቀጡ

በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን አመያ ወረዳ ውስጥ በህግ ትፈለጋለህ በማለት አንድን ግለሰብ አላግባብ የገደሉ ሁለት ግለሰቦች በእስራት መቀጣታቸውን የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ፖሊስ መምሪያ አስታዉቋል።

የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ፖሊስ መምሪያ የኮሚኒኬሽን ፅህፈት ቤት ሀላፊ ምክትል ኢኒስፔክተር ትግሉ ለገሰ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት አንደኛ ተከሳሽ አሰፋ ሂርፓሳ፣ሁለተኛ ተከሳሽ ደረጄ ምስጋና የተባሉ የአመያ ወረዳ ባሮ ቀበሌ አመራር አካላት ሰኔ 10 ቀን 2016 ዓ.ም ከቀኑ 10 ሰዐት ላይ አቶ አህመድ ሀሰን የተባሉ ግለሰብ መኖሪያ ቤት በመሄድ መሀመድ ኑር ጀማል የተባለው ግለሰብን በህግ ትፈለጋለህ በማለት ከቤት ጎትተው በማውጣት በያዙት በጦር መሣሪያ ተኩሰው እንደገደሉት በማስረጃ ተረጋግጧል።

ሁለቱ የቀበሌ አመራሮች በታጠቁት ክላሽን ኮቭ የጦር መሣሪያ ተጎጂውን በህግ ትፈለጋለህ በማለት ከወሰዱት በኋላ ከህግ ሊያመልጥ ነው ብለው በሁለት ጥይት ጉዳት አድርሰውበት ህይወቱ እንዲያልፍ አድርገዋል።

ሁለቱ የቀበሌ አመራር አካላት የፈፀሙት ያልተገባ ድርጊት ፖሊስ ማስረጃ በማጣራት የምርመራ መዝገቡን ለአቃቤ ህግ የላከ ሲሆን አቃቤ ህግም ከፖሊስ የተላከውን የምርመራ መዝገብ ተመልክቶ በወንጀለኛ መቅጫ ህግ ቁጥር 539 ንዑስ አንቀፅ 1 እና በ 32 ንዑስ አንቀፅ 1 መሠረት በከባድ የሰው መግደል ወንጀል ክስ መስርቷል፡፡ በአቃቤ ህግ የተመሠረተውን ክስ ሲከታተል የነበረው የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አንደኛ ተከሳሽ አሰፋ ሂርፓሳ በ13 ዓመት ፅኑ እስራት ሁለተኛ ተከሳሽ ደረጄ ምስጋናው በ14 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ የተወሰነባቸው መሆኑን ምክትል ኢኒስፔክተር ትግሉ ለገሰ ጨምረው ገልፀዋል።

በሰመኃር አለባቸዉ
#ዳጉ_ጆርናል




የአፍሪካ ህብረት በሱዳን የመጨረሻ የፖለቲካ ውይይት እንዲደረግ ጠየቀ

የአፍሪካ ህብረት የሱዳን የፖለቲካ ቡድኖች በሀገሪቱ ያለውን ችግር ለመፍታት ያለመ ሰፊ የፖለቲካ ውይይት ለመጀመር የመጨረሻ ድርድር እንዲያደርጉ መጋበዙን ምንጮች ገልፀዋል። ምክክሩ የአፍሪካ ህብረት የመሪዎች ጉባኤ እንደተጠናቀቀ በየካቲት ወር አጋማሽ በአዲስ አበባ ይካሄዳል ተብሎ እንደሚጠበቅም ምንጮቹ አክለዋል።

ስብሰባዎቹ ባለፉት ወራት በሱዳን ባለድርሻ አካላት መካከል ሰፊ ውይይት ለማካሄድ ዝግጅት ለማድረግ የተካሄዱ ውይይቶች ውጤትን ለመጨረስ ያለመ ነው። የአፍሪካ ህብረት በተለያዩ የሱዳን ወገኖች መካከል የውይይት መንገድ ለመፍጠር የታለመው ሁሉን አቀፍ የፖለቲካ ሂደት አካል ሆኖ በሐምሌ እና ነሐሴ 2023 ሰፊ ምክክር አድርጓል። የአፍሪካ ህብረት የሱዳን ከፍተኛ የፓናል ቡድን ሃላፊ መሀመድ ኢብን ቻምባስ ግብዣዎች ለተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች መላካቸውን ጉዳዩን የሚያውቁ ምንጮች ለሱዳን ትሪቡን ተናግረዋል።

በነሀሴ ወር በተካሄደው የሁለተኛው ዙር ድርድር ተሳታፊዎች የሲቪል ዲሞክራሲያዊ ኃይሎች ማስተባበሪያ (ታጋዱም)፣ የሱዳን ህዝቦች ነፃ አውጪ ንቅናቄ - ኤስ ፒ ኤልኤም-ኤን በአብደል አዚዝ አል ሂሉ የሚመራው፣ የሱዳን ነፃ አውጪ ንቅናቄ (ኤስኤልኤም) የሚመራው  አብደል ዋሂድ መሀመድ ኑር እና የሱዳኑ ባአት ፓርቲ በሐምሌ ወር የመጀመሪያው ዙር ከ20 በላይ ቡድኖች፣ ፓርቲዎች፣ የሲቪክ ማህበራት እና የወጣት ቡድኖች የተሳተፉ ሲሆን አብዛኛዎቹ የሱዳን ጦር ኃይሎችን (SAF) የሚደግፉ ናቸው። እነዚህም በጃፋር አል ሚርጋኒ የሚመራው የዲሞክራሲያዊ ቡድን፣ በቲጃኒ ሲሲ የሚመራው የብሄራዊ ንቅናቄ ቡድን እና በሙባረክ አል-ፋዲል አል-ማህዲ የሚመራው የብሄራዊ ስምምነት ጥምረት ይገኙበታል።

በሚሊዮን ሙሴ
#ዳጉ_ጆርናል


✍️ጥሎ ማለፍ ለመግባት የሚደረገዉ ጨዋታ ሙሉ ድልድል ይህን ይመስላል።

ማችስተር ሲቲ vs ሪያል ማድሪድ 👀

#ዳጉ_ጆርናል


ሀሰተኛ የብር ኖቶች የሚታተምበት እና የሚባዛበት ማሽን በቁጥጥር ስር ዋለ

በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን በቾ ወረዳ እና ወሊሶ ከተማ በተደረገ ፍተሻ የብር ኖቶች የሚታተምበት እና የሚባዛበት ማሽኖች እንዲሁም ሌሎች ቁሳቁሶች ከሀሰተኛ የገንዘብ ኖት ጋር በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ፖሊስ መምሪያ ገልጿል።

የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ፖሊስ መምሪያ የኮምኒኬሽን ፅህፈት ቤት ኃላፊ ምክትል ኢንስፔክተር ትግሉ ለገሰ ለብስራት ሬዲዮና ቴሌቪዥን እንደተናገሩት በደቡብ ምዕራፍ ሸዋ ዞን በቾ ወረዳ ቱሉቦሎ ከተማ ውስጥ ጥር 17 2017 ዓ/ም ከቀኑ 11:30 ላይ በሁለት ግለሰቦች እጅ 43ሺህ 2መቶ ሀሰተኛ ብር  መያዙን ገልፀው ይህንን ተከትሎ የስርጭት ምንጭ የት እንደሆነ ፖሊስ ባደረገው የክትትል ስራ በርካታ የሀሰተኛ የብር ኖቶች እና የማተሚያ ቁሳቁሶች በቁጥጥር ስር መዋሉን ገልፀዋል።

በዚህ መሰረትም  ፖሊስ ከፍርድ ቤት ባወጣው የፍተሻ ትዕዛዝ መሰረትም በወሊሶ ከተማ ውስጥ አቶ ተስፋዬ አንደቦ በተባሉ ግለሰብ ቤት ውስጥ ሀሰተኛ የብር ኖቶች የሚባዛበት እና የሚታተሙበት የተለያዩ ወረቀቶች እና ቀለሞች በተጨማሪም 75,250 ሀሰተኛ የብር ኖቶች መያዙን ገልፀዋል። በዚ ሀሰተኛ ገንዘብ የማተም እና የማሰራጨት ተግባር ላይ የተሰማሩ አምስት ግለሰቦች በቁጥጥር ስር የዋሉ ሲሆን ከነዚህ ግለሰቦች የተለያዩ ማሽኖች እና ማባዣ ፕሪንተሮች መያዛቸውን ገልፀዋል።

ባለ 2መቶ ሀሰተኛ ኖት ብዛቱ 336 ፣ባለ 1መቶ ሀሰተኛ ኖቶች ብዛቱ 78 እና ባለ 50ብር የብር ኖት ሲሆን በአጠቃላይ 75,250 ሀሰተኛ የብር ኖቶች በቁጥጥር ስር ውለው በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባለሙያዋች ማሽን በተደረገ ማጣራት ሀሰተኛ የብር ኖት መሆናቸው መረጋገጡን ገልፀዋል።

በሰብል አበበ
#ዳጉ_ጆርናል


የፊሊፒንስ ምክትል ፕሬዝደንት ሳራ ዱቴርቴ በስልጣን ላይ ባልገዋል በሚል በሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች አደባባይ በመዉጣት ከስልጣን እንዲነሱ ጠየቁ

የፊሊፒንስ ምክትል ፕሬዝዳንት ሳራ ዱቴርቴ ከስልጣን እንዲነሱ በሺዎች የሚቆጠሩ ተቃዋሚዎች በዋና ከተማዋ በማኒላ ጎዳናዎች ላይ ወጥተዋል።በመዲናዋ የሚገኙ ተቃዋሚዎች ሳራ ዱቴርቴ ከስልጣን እንዲወገዱ የሚጠይቁ ምልክቶችን በመያዝ “አሁኑኑ ሳራን ስልጣን ይልቀቁ!” ብለዋል፡፡ አርብ ጠዋት ላይ አደባባይ የወጡ እና በሰልፉ ላይ የተገኙ ሰዎች ወደ 4,000 የሚጠጉ መሆናቸዉን ፖሊስ ገልጿል፤ ባለስልጣናት 7,400 ሁከት የሚቆጣጠሩ የጸጥታ ኃይሎች መሰማራታቸውን አስታውቋል።

ሳራ ዱተርቴ በፕሬዚዳንት ፈርዲናንድ ማርኮስ ጁኒየር አስተዳደር የትምህርት ፀሐፊ ሆና በማገልገል ላይ በነበረችበት ወቅት የመንግስትን ገንዘብ አላግባብ በመጠቀም እና በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላሮችን በመመዝበር ሶስት ክስ ቀርቦባቸዋል።የተወካዮች ምክር ቤት አባል የሆኑት ፔርሲቫል ሴንዳና፣ ከክስ አቤቱታዎች አንዱን የሚደግፉ ሲሆን፣ ባልደረቦቻቸዉ በፍጥነት እንዲንቀሳቀሱ ግፊት አድርገዋል። በየእለቱ የእንቅስቃሴ-አልባነት መኖሩን በመተቸት " ሳራ ዱተሬት ስልጣን አላግባብ መጠቀም እና ትንኮሳን በቸልታ መቀበላል" አይኖርብንም ሲሉ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል።

ክሱ የሚካሄደው በተወካዮች ምክር ቤት አንድ ሶስተኛው አባላት ድጋፍ ሲያገኝ ብቻ ነው፣ የተከሰሱ ባለስልጣን በሴኔት ሁለት ሶስተኛ ድምጽ ከተሰጠባቸዉ ከስልጣን ሊነሱ ይችላሉ።የፊሊፒንስ ሰዎች እዚህ አሉ፣ ለእውነት እና ለፍትህ ለመቆም ዝግጁ ናቸው። እንዳንሰናከላቸው ፣ ሲሉ ሲንዳና ተናግረዋል፡፡የ 46 ዓመቷ ምክትል ፕሬዝዳንት ፕሬዝዳንት ማርኮስ የስልጣን ተግባራቸውን መወጣት ካልቻሉ በህገ መንግሥታዊ ስርዓት መሰረት የመተካት ሚና ይኖራቸዋል፡፡ ምክትል ፕሬዚዳንቱ የተከሰሱባቸውን ውንጀላዎች ፖለቲካዊ በማለት ውድቅ አድርገዋል።

በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል



20 last posts shown.