Zemedkun Bekele (ዘመዴ)


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


"ይህ የቴሌግራም ቻናሌ ግንቦት1/2011ዓም የተከፈተ ነው። የእኔን የስልክ ወጪ ጨምሮ አገልግሎቴን መደገፍ የምትፈቅዱ ጓደኞቼ በ
👉🏿 https://donorbox.org/zemedemedia እና
👉🏿 https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB በኩል ማገዝ ትችላላችሁ። በተረፈ ለቤተ ክርስቲያኔና ለኢትዮጵያ ሀገሬ የሚጠቅመውን ሁሉ አበረክት ዘንድ አብዝታችሁ ጸልዩልኝ።

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


"…የዘመዴ ሚዲያ ጉዳይ ይዞኝ ነው የዘገየሁት። እዚያው ጮቄ ተራራ ላይ ሆኜ የዛሬውን እንደ ኮሶ የሚያሽር መራር እውነት የሆነ ርእሰ አንቀጹን እያዘጋጀሁላችሁ ነው። በትእግስት ጠብቁኝ።

"…ሠራዊተ ጌዴዎን 300 ሺ የዘመዴ ሚዲያ መሥራች ሠራዊቶች ትናንት ማታ በለጠፍኩላችሁ ማስታወቂያ መሠረት ተመዝግባችሁ ሊንኩ ያልደረሳችሁ በሙሉ በኋትስአፕ ቁጥሬ መልእክት አስቀምጡልኝ እና ሊንኩን እልክላችሁና ግሩፑን ትቀላቀላላችሁ። 300 ያለነው በምክንያት ነው። ፍጠኑ ትናንት 197 የነበረው ሰው ዛሬ 237 ሰው ይቀራል። ተመዝግባችሁ ሊንኩ ያልደረሳችሁ እደግመዋለሁ ፍጠኑ። አልያም ለሌሎች ዕድሉን ለመጠት እገደዳለሁ። ፍጠኑ።

"…በተለይ ጎጃም ልሂቃኑ እየጸዳ ነው። የሃይማኖት አባቶች፣ መምህራንና የህክምና ሊቃውንት እየተለቀሙ እየጠፉ ነው። በዐማራ ፋኖ በጎጃም ውስጥ በተሰገሰጉ አገው ሸኔ፣ ቅባቶችና የወያኔም፣ የኦሮሞም ቅጥረኞች አማካኝነት ሊቁ ሁሉ እየጠፋ ነው። የአቢይ ወታደሮች የአረጋውያንን ብልት እየቀሮጡ ሁላ መውሰዳቸው ታይቷል። እነ አስረስ መዓረይም መምህራንን "ጫጫታ ስለበዛ መግደል አቁሙና ደህና አድርጋችሁ ቅጡ" ሲሉ ሰምታችኋል። ለምንድነው በጎጃም ብቻ የዐማራ እና ኦርቶዶክሳዊ የሆኑ ልሂቃን እየተመረጡ የሚረሸኑት? የሚጸዱት? ምልከታዬን ቆይቼ አስቀምጣለሁ።

"…እስከዚያው "መንግሥት የፕሪቶሪያ ውል ስምምነት ያክብር" የሚል መፈክር የሌለውን የአዳነች አበቤንና የበሻሻ አራዳውን የአዲስ አበባ የእነ እትዬ ዘርመጪት፣ እማማ የብርጓልን፣ የአዴ ጫልቱን በትግሬ ስም የተደረገ ሰልፍ እያያችሁ ጠብቁኝ።

• ዘመዴ ነኝ ከጮቄ ተራራ… ቆይቼ እመጣለሁ።

4.3k 1 1 28 189

"…በመልካም ትሮጡ ነበር፤ ለእውነት እንዳትታዘዙ ማን ከለከላችሁ? ገላ 5፥7

• እንደምን አደራችሁ?
• እንደምን አረፈዳችሁ?
• እንደምን ዋላችሁ?
• እንደምን አመሻችሁ?

• መልሱ እግዚአብሔር ይመስገን ብቻ ‼

18.8k 1 3 1.4k 979

ማስታወሻ ፦

"…በቅርቡ የሚመጣውን ዘመዴ ሚዲያ በመደገፍ ሚዲያውን እውን ለማድረግ ከጎኔ የተሰለፋችሁና የተመዘገባችሁ 297 ሠራዊተ ጌዴዎኖች ቀሪዎቹን 3 ሰዎች እየጠበቅን ሁላችሁንም ወደ አዲሱ ቴሌግራም ግሩፕ ለማስገባት ሞክረን ሊንኩ ደርሷችሁ የተቀላቀላችሁት 197 አባላት ብቻ ናችሁ። ቀሪዎቻችሁ በኋትስአፕ ቁጥሬ መልእክት እንዳስቀመጣችሁልኝ ወዲያው ሊንኩን እልክላችሁና ወደ ግሩፑ ተቀላቅለን የተግባር ሥራችንን በፍጥነት እንጀምራለን።

"…እስከዚያው ድረስ የከንቲባ አዳናች አበቤን በነገው ዕለት ለትግራይ ሕዝብ አዝና ሴፍቲኔት ተመዝጋቢ፣ የቀበሌና የወረዳ፣ የከተማው የብልጽግና አባላት በሙሉ በግዳጅ ለማክሰኞ ይወጡ ዘንድ ታዘው ጉዳዩ ለዝግጅት የፈጠነ በመሆኑ ለነገ የተላለፈውን "አዛኝ ቅቤ አንጓች" የኦሮሙማው የጨሰ የበሻሻ አራዳ ጭንቄ ያፈለቀውን የትግሬ ሕዝብ የድጋፍ ሰልፍ ለመሰለፍ ባትችሉ ከዳር ሆናችሁ ለመሳቅ ተዘጋጁ። መከናነብ፣ መሸፋፈን፣ ሂጃብና ማስክ፣ በነጠላም መሸፋፈን ተከልክሏል።

"…ከትግሬ የቀረው ሥላለ አቢይ አህመድ ሊበላው ያሰበውን አሞራ ጅግራ ነው እያለው ነው። አያ ጅቦ ሳታመሃኝ ብላኝ እያሉ ነው አሉላና ስታሊን።

• በሉ ሊንኩ ያልደረሳችሁ አስታውሱኝ። እዚህ ጮቄ መሽቷል እኩሌሊት እየሆነ ነው። ይሄንንም በጨረቃ ብርሃን ነው የጻፍኩላችሁ። 300 ለመሙላት የምትፈለጉት ሦስት ዕድለኛ ሰዎችም ፍጠኑ።

• ሻሎም…!  ሰላም…!


መልካም…

"…ወደ ተማሪ ቤት እየሄድኩ ነው። የአውሮጳን ብርድ ለመሸወድ ተጆባቡኜ፣ የሌለ ተደርቼ ጉርድ በርሜል መስዬ ባቡሬን ተሳፍሬ ጥጌን ይዤ እየሄድኩ ነው። ከክላስ እስክወጣ ድረስ ግን የቤቴን በር ቆልፌባችሁ ከምሄድ በሩነሩን ልክፈትላችሁና እየተወያያችሁ ቆዩኝ። ብዙ ባለጌ ጠፍቷል። ቀንሷልም። ሆኖም ግን አንዳንድ ስድ ባለጌ አይጠፋምና እንደ ድንገት ቤት ተሳስቶ በአፉ ሲጸዳዳ ብታገኙት ክፉ አትናገሩት። ከስሩ ብቻ ዘመዴ BLOCK በማለት ብቻ ጠቁማችሁኝ እለፉ። ከዚያ እኔ ከክላስ ወጥቼ ወደ ቤቴ ስሄድ ባቡሬ ውስጥ ቁጭ ብዬ አስተያየታችሁን እያነበብኩ ለቅሜ እቀስፈዋለሁ። አለቀ።

"…ይሄን ዛሬ 16 ሺ ሰዎች አንብበው 15 ፍሬ ሰዎች ጓ ብው 😡 ያሉበትን ርእሰ አንቀጽ እናንተ ደግሞ ወደመተቸቱ ሂዱ። ተናዳጁ ሁላ እየቀነሰ ነው የመጣው። ይበልጥ ደግሞ ጠንከር እያልኩ በድፍረት ሾተላዩን እየቀጠቀጥኩ ስመጣ ነገሮች እየተገለጡላችሁ ይመጣሉ። ጨከን፣ ደፈር ብላችሁ ስሙኝ እንጂ ገና ምኑን አያችሁና ወገኖቼ። ጥላሁን አበጀ እንኳን ጭንብሉ ተገፍፎ መሳደብ ጀመረ እኮ። 😂😂😂 ገና ምን አይታችሁ። እነ ሰጣርጌና ግርማ አየለም በኮመንት ይሞላለጩ ጀመር። ገና ምን አይተው።

• ዝናቡና ዘመነ ራሳቸውን እንዲጠብቁ ደፍራችሁ ንገሯቸው። በሉ ወደ ክላስ ልገባ ነኝ። መልካም የውይይት ጊዜ ይሁንላችሁ። ጤና እንድታገኙ ተንፍሱ። ተሳዳቢዎችም ቢሆን በእውቀት ለመሞገት ሞክሩ። የሚሻለው ከመሰዳደብ ሓሳብ ማንሸራሸር ነው። እኔ ሲበዛ ዲሞክራት ነኝ። በር ቆልፌ አንጀታችሁን ከማሳርራችሁ በር ከፍቼ ብትተነፍሱ ይሻላል ብዬ ነው።

"…የጎጃም ፋኖ ከተስተካከለ የዐማራ ፋኖ ትግል ይፈወሳል።

37.5k 1 10 156 1.3k

"…አሁን ሁሉ ነገር ሚናውን እየለየ መጥቷል። በስተመጨረሻም አስቀድመው የሚዲያውን ዘርፍ የተቆጣጠሩት ወያኔዎች ከዐማራ የተከራዩአቸውን አፎች ይዘው ወደ አደባባይ ብቅ ማለት ጀምረዋል። ከወሎ አቶ ልደቱ አያሌው፣ ደረጀ ሀብተወልድና ከጎጃም በቃሉ አላምረው፣ አበበ ባዩ፣ ከሸዋ ያየህ ሰው ሽመልስ፣ ከደቡብ መሳይ መኮንን የዐማራ ፋኖ አቀራራቢ፣ አደራደሪና አወያይ ሆነዋል። ለወያኔና ለኦሮሙማው አራጅ ስስ ልብ ያላቸው እነዚህ ጉደኞች በኢትዮጵያ አየር መንገድ በቦሌና በባሌ አውሮጳና ኡጋንዳ ተቀምጠው ለወያኔ አረንጓዴ መብራት፣ ለዐማራ ቀይ መብራት ማብራት ጀምረዋል። አስረስ መዓረይን ለማዳን ኢትዮ ፎረም፣ ኢትዮ ኒውስ፣ አዲስ ድምጽ፣ ሮሐ ሚዲያ፣ ቶፋው ደረጀ ሀብተ ወልድ፣ መሳይ መኮንን፣ ብላ ብላ እዬዬ እያሉ ነው። አስረስ መዓረይ በራሱ ውሳኔ መፍትሔ ብሎ ያቀረበው ሓሳብ ሆን ተብሎ አየር ላይ ውዝግብ ማስነሻ እና ለዐማራው አጀንዳ ለመስጠት ታስቦበት የተበተነ ተንኮል ነው። መዓረይ አንዴ በእስክንድር ምክንያት ብዙ ወገኖች ዋጋ ከፍለዋል ይልና መለስ ብሎ ድርጅቱ ከስሞ በይቅርታ ተሳስተናል ብለው እንደ አዲስ ውይይት መጀመር አለበት ይልላችኋል። ይሄንኑ አነጋገር እኮ ከፋፍሕዴኑ ከጌታ አስራደም አንደበት ሰምተነዋል።

"…የሚገርመው ነገር ደግሞ ከዚህ ጋር በተያያዘ አርበኛ ዘመነ ካሤ ከሻለቃ ዳዊት ጋር የተነጋገሩበት የስልክ  ቅጂ ከዚህ ሁሉ ጊዜ በኋላ ዛሬ እንዴት ሊወጣ ቻለ? በማን በኩል ወጣ? ምን ዓይነት መልእክት ለማስተላለፍ ተፈልጎ? እስቲ ተመራመሩበት። በመጨረሻ መሳይ መኮንን ስለ አብይ አህመድ ሰሞናዊ የብልጽግና ምርጫ ሲጠይቀው አስረስ መዓረይ በሰጠው ገራሚም ጥያቄ የሚጭርም ምላሽ እንሰነባበት። መዓረይ ስለ አቢይ ሲጠየቅ ከመልሱ በጥቂቱ እንዲህ ነበር ያለው። "አብይ አህመድ ትኩረት ይፈልጋል። ለጥቂት ጊዜ አጀንዳ ባናደርገው ጥሩ ነው።" ይልልሃል አንድ የፖለቲካዊ አመራር ነኝ የሚል ግለሰብ በዋናነት የአገሪቱን የመንግሥት ሥልጣን ተቆጣጥሮ ሕዝቡን የሚገድልን ሥርዓት መሪ ትኩረት አትስጡት በማለት። ድጋሚ ትግራይ ላይ ጦርነት ለማስነሳት የኮቱን እጅጌ ሰቅስቆ የተነሣው አቢይ አሕመድ፣ ዐማራን ከአዲስ አበባ ያጸዳው አቢይ አሕመድ፣ በጎጃም ራሱ ምሁራንን፣ ሊቃውንቱን፣ ዶክተሮችን፣ ነጋዴና መምህራንን በተጠና መንገድ እየጨፈጨፈ ያለው አቢይ አሕመድን ትቶ ስለ እስክንድር ነጋ ሲበጠረቅ ይውላል።

"…የትናንቱን የአስረስ መዓረይን እና መሳይ መኮንንን ቃለ መጠይቅ ደጋግሜ ነው የሰማሁት። የጎጄ ሸኔ አስረስ መዓረይን የእኔ ጀግና ብሎ ሊያሻሽጠው ሲሞክር ነው ያየሁት። አልማዝ ባለጭራዋማ እሽኮኮ ሁላ ለማድረግ ስትላላጥ ነበር የዋለችው። ከታዘብኩት መሃል መሳይመኮንን ደግሞ ደጋግሞ ሲጠይቀው ንግግራቸው ውስጥ አስረስ መዓረይ መሳይን "ኧረ በእናትህ መሳይ ክርክር አደረግክብኝ ብሎ በመሳይ ላይ የመናደድ የመበሳጨት ነገርም አይቼበታለሁ" ይሄ የሚያሳየን የእኔ ጎጃም መግባትና በወሬ፣ በፕሮፓጋንዳ ብቻ የቆመ መስሎ በአስረስ ምላስ ሲጨናበር የከረመው የጎጃም ዐማራ ምን ያህል በጎጃም እያደረግኩ ባለሁት ጉብኝት እና ምርመራ አስረስን እንዳስተነፈሰኩት ምልክት ነው። ምክንያቱም ከዚህ ቀደም "አስረስ መዓረይ ከመሳይ ጋር ሲያወራ "መሳይ አንዳንድ ሚዲያዎች እና ግለሰቦች አሉ የምንነጋገርበትን ሚዲያ እንኳን ሊመርጡልን የሚፈልጉ እንደዉም ከመሳይም ጋር አታውሩ ሁላ ይሉናል" እያለ እንደ አስተዳደጉ በየፖለቲካ ድንግልናውን አስረክቦ ሲሳደብ እንዳልነበረ ሁላ አሁን ግን መሳይ ላይ ቀርቦ መሳይ ራሱ በዚህ ፍጥነት ሲቀየርበት ሳይ ምን ያህል ገና ቅድመ ምርመራዬ እንዳራወጠው ነው የታዘብኩት። የዘመኑን ቦለጢቀኞች ንግግር እንደ ፊዚክስ ኳልኩሌሽን ተቀምሮ ለባለቤቶቹ ሌላ መልእክት ለሌላው ለሚሰማው ሌላ መልእክት እንደሚያስተላልፉ ካላወቃችሁ ያው ዕቁባችሁን በጊዜ ትበላላችሁ፣ የፖለቲካ ድንግልናችሁንም ለጠበቃ አስረስ ታስገረስሳላችሁ ማለት ነው። እኔ የምጽፈው ይሄ ሁላ ዝባዝንኬ ለሌላው መዝናኛ መደበሪያ ነው። ለሚመለከታቸው ግን የጋለ ከላይም ከታችም የብረት ምጣድ ነው። የምጽፈው ለሚመለከታቸው ነው። የማይመለከትህ እለፈው። ንካው። አምልጥ።

~ • ይደፈርሳል… ግን ደግሞ ይጠራል…✊

•••

ሻሎም…!  ሰላም…!

ዘመድኩን በቀለ ነኝ።
አሸበርቲው/አስነቀልቲው
ጥር 28/2017 ዓም
ከራየን ወንዝ ማዶ።


ተገዛ እንጂ ሲሉት ሳይ እኔ አዝናለሁ እነ ጥላሁን አበጀ ግን የምናባህ ተቋም ነው እያሉ ነው የሚስቁ፣ የሚሳለቁባቸው።

"…ጥላሁን አበጀ ባለቤቷን የተማመነች በግ ላቷን ደጅ ታሳድራለች እንደሚባለው ነው ከሴራ አጋሩ ከአቶ አስረስ መዓረ የአይዞህ በርታ ግፋበት የሚል የአረንጓዴ መብራት ምልክት ተሰጥቶት በፌስቡክ ገጹ ላይ በግልጽ "የማንኛውም ድርጅት መሪም ሆነ አመራር አይደለሁም። እኔ ግለሰብ ነኝ በማለት በገደምዳሜ ሊገነጥለው ያሰበውን የሦስተኛ አደረጃጀት አንጃውን ሸበልበረንታውን ብርጌድና የ8ተኛ ክፍለጦርን የከራረሙ ፎቶዎች መለጠፉን የተያያዘው። በእርግጥ እቅዱ የቆየ ቢሆንም አሁን ግን ከሹመት ማጣቱ በኋላ ንዴቱን መቆጣጠር አቅቶት በግላጭ ማጉረምረሙን ቀጥሎበታል። ሆን ብሎ ሸበልበረንታን አዳክሞ ወደ ምዐወራብ ጎጃም ለሴራ ሲፈረጥጥ ቦታው የሚሊሻ መሰልጠኛ ሆኖ ብዙ ሀቀኛ ፋኖዎች እና ንጹሐን የጎጃም ዐማሮች ተገድለዋል። ተጨፍጭፈዋል። አስረስ መዓረይ መርጦ ለማርያም አይደርሳትም ቢደርሳት ግን በመርጦ ለማርያም ያሳረዳቸው ዐማሮች መጀመሪያ የሚበቀሉት እርሱ ነው። አሁንም አጅሬ ጥላሁን መጠጊያ ሲያጣ የትም ሲያውደለድልና አንደዜ የወለጋ ዕዝ፣ ሌላ ጊዜ የደቡብ ኢትዮጵያ ፋኖ የሚል የዛገ፣ የሻገተ አጀንዳ ተሸክሞ ሕዝብ ሲያጃጅል ከርሞ የግል ቁርሾውን ለመወጫ ሲያዘጋጃቸው የፋይናንስ ኃላፊነቱን ሲያጣ መጨረሻዬን ከሕዝቤ ጋር ያድርገው እያለ ምስኪን ፋኖዎችን ለማሞኘት ይላላጣል።

"…ተመልከቱ አሁን ላይ ግዮን ብርጌድ ላይ ሰብሳቢው ተፈራ ደመቀ የተባለ የብልፅግና አባልና ርእሰ መምህር የነበረና ሰው ነው። ተፈራ ይሁን እንጂ…

1ኛ፦ አቶ አንሙት አሸንፍ - አደረጃጀት ዘርፍ ሓላፊውም የብልፅግና ርዕሰ መምህር የነበረ

2ኛ፦ አቶ አወቀ የሚባል በሰከላ ወረዳ የአጉት ከተማ የመዘጋጃ ጽሕፈት ቤት ሓላፊ የነበረ እና አሁን የዐማራ ፋኖ የፖለቲካ ዘርፍ ሓላፊ የሆነ

3ኛ፦ ጤናው አቻም የለህ የተባለ ሽፍታና የንፁሐንን ደም ሲጠጣ የከረመ ዘራፊ አሁን የግዮን ብርጌድ ምክትል የጦር አዛዥ የሆኑ ናቸው ግዮን ብርጌድን ተብትበው አንቀው የያዙት። እነዚህን አጥብቆ የሚደግፋቸውም አርበኛ ስለሽ ከበደ የተባለው ወሳኝ ሰው ነው። ስለሺ ከበደ ዘመነ ካሤ አጠገብ ሆኖ ዘመነን እንዲቆጣጠር የተመደበም አደገኛ ነው ይላሉ የመረጃ ምንጮቼ። የጥቅም ትስስርም ስላላቸው አስረስ መዓረይ የዐማራ ፋኖ ዓለምአቀፍ የድጋፍ ሰጪ ቡድን ኮሚቴ ሲቋቋም የስለሺ ከበደን ወንድም ኢንጅነር ግርማ ከበደን በሀገረ እንግሊዝ ወኪል አድርጎ እስከመሾም ሁላ ነው የደረሰው። የለንደን ፋኖን ጀግና ካደረጉት መሃል በዐማራ ፋኖ ስም የተሰበሰበን ገንዘብ ቱርክ ድረስ ሄደው ፀጉር አስተክለውና የዓይን ስር የተሸበሸበ ቆዳቸውን አስወጥረው በመጡ፣ ኮንሠርት በሚያዘጋጁ ሙዚቀኞች ላይ ቀደም ብለው በዐማራ ስም ተቃውሞ ቀስቅሰው ሲያበቁ ከአርቲስቶቹ ጋር በጓዳ በመደራደር ቢዝነስ መሥራት የጀመሩ ሲያልቅ አያምር፣ እንደሠራ አይገድል ከሆኑ ለስንትና ስንት ጉዳይ ሲጠበቁ የነበሩትን ወንድሞችም ጠልፎ እስከመጣል ነው የደረሱት። የዐማራ የደም ገንዘብ ግን እንዲህ ያንቀዠቅዣል ማለት ነው? ብቻ ይሄን ጉዳይ ሌላ ጊዜ እመጣበታለሁ። ሰቀቀናም በፋኖ ተቃውሞ ስም በሚዲያ ስለታየ ታወቂ ሆንኩ ብሎ አዳሜ እንዴት ቅሌታምና ዘማዊ፣ ባለትዳር ሳይቀር ካላማገጥኩ እንደሚል ሲታይ ያሳፍራል። አብዛኞቹ ነቅተው ባያከሽፉት ይሄም ሌላ ኪሣራ ነበር።

"…ሾተላይ ዳግማዊ አቢይ አሕመድ የሆነው አስረስ መዓረይ በእስክንድር ነጋ ማደናገሪያ አጀንዳ ውስጥ ራሱን የማሻሻጥና በቀጣይ የዐማራ ፋኖን ለብቻው፣ የዐማራ ፋኖን በመላው የመበጥበጥ ዕቅድ እና እንዲሁም ለተቀላቀሉት ፋኖዎች የነፍስ አድን ሥራ ለመሥራት በሳምንቱ የንትርክ አጀንዳ ለመስጠት ሲል ከሚዲያ ሚዲያ ሲባዝን ተስተውሏል። አስረስ መዓረይ በተዘዋዋሪ እስክንድር ነጋበትን የተቃወመ መስሎ ድርጅቱን አምነውበት የመሠረቱት ፋኖዎች ምንም እንደማያውቁና እጃቸውን ታስረው የገቡ ይመስል ከመሳይ መኮንን ጋር በነበረው ቃለምልልስ ላይ ሰምታችሁት ከሆነ ለእነሱ ሽፋን ሲሰጥ ይታያል። መሳይ መኮንንም በበኩሉ የጋዜጠኝነት ሚናውን ስቶ የእስክንድርን ሞራል አስጠባቂና አስታራቂና አቀራራቢ ሆኖ ለመተወን ሲላላጥ ይታያል።👇⑤✍✍

👆⑥ ✍✍✍ …የአስረስ ንግግር በአጠቃላይ ሲመዘን አፋህድ ውስጥ የተቀላቀሉት ፋኖዎች ለደረሰባቸው ኪሳራ ሱሬ እንደሚለው safe exit ወይም የማርያም መንገድ የመስጠት አካሄድ ነው እያሳየ የነበረው። ከንግግሩ እንደምትታዘቡት አስረስ አንድነቱን አዘግይቷል የሚለውን የእኔ የዘመዴን ክስ በዚህ ግርግር አሳብቦ አልፎታል። አንድነቱን ያዘገየነው መከታው ከአማራ ፋኖ በሸዋ እንዲወያዩ፣ ደረጄ በላይ ከሀብቴ እንዲነጋገሩ እና ምሬ ወዳጆ ኮሎኔል ፋንታሁን ጋር እንዲነጋገሩ በማሰብ ነው የሚል የውሸት፣ የማምታቻና የቅጥፈት ተግባር ፈጽሟል። አስረስ ጠበቃ ስለነበር ለክህደት ቅርብ የሆነ ሰው ነው። ወንጀለኛን ተከራክሬ ነፃ አደርጋለሁ እያለ ሲሟገት የኖረ ሰው አሁን በፋኖ ትግል ውስጥ ገብቶ ቢቀጥፍ፣ ቢዋሽ ሌሎች ታዝበውት ኧረ ምን አይነት ዋሾ፣ ቀጣፊ ሰው ነው። የፈጣሪ ያለህ ምን ጉድ ነው እያሉ ከመታዘብ በቀር ምንም እንደማያመጡ ስለሚያውቅ ነው እንደ አቡጀዲ፣ እንደ ጣቃ ሲበጠረቅ ስቅቅ የማይለው። ተመልከቱ ሌሎች የፋኖ አደረጃጀቶች ያላመኑበትን ሓሳብ ራሱን ነፃ ለማድረግና ለማሻሻጥ በድፍረት ተጠቅሞበታል። ደግሜ አስረግጬ እናገራለሁ የዐማራ አንድነት እንዳይመጣ ከእነ እስክንድርና ከእነ ስኳድ ፋፍሕዴን ጋር እየተነጋገረ የገደለው አስረስ መዓረይ ነው። 100% እርግጠኛ ሆኜ ነው የምነግራችሁ። ይሄን የሚቃወም ሌላ ሰው ከመጣ እኔ እቀጣለሁ።

"…ልብበሉ በቁጥርም ሆነ በሚያስተዳድሩት ቀጠና ስፋትም ግዙፍ የሆኑ አደረጃጀቶችን አንድነት አፋርሶ፣ ከዚያ ይልቅ በጨበጣ ድርጅት መሥርተን ከመንግሥት ጋር በመናበብ ተወያየን፣ ተደራደርን ከሚሉ አካላት ጋር ትግል ሲጎትቱ፣ ደም ሲያፋስሱ የነበሩትን ግለሰቦችን በመለመን ትግሉን ማጓተት ለምን አስፈለገው? እስክንድርን ነጥሎ ወንጅሎ ሌሎቹን በይቅርታ ስም በመቀላቀል ድጋሚ ትግሉን የማስበጥበጥና የእስክንድርን ሚና የማስቀጠል ዓላማ እንዳለው ነው የአስረስ አካሄድ የሚያሳየው። የእስክንድር ተተኪ ለመሆንም እየጣረ ነው። አይደለም እነ አስረስ ከእነ ባዬ ጋር የተቀላቀሉት እነ ሀብቴ በቶሎ፣ በፍጥነት ወደ አንድነት ካልመጡ የእኔ ድምዳሜ በውድ ሳይሆን ከድርጅቱ ወጥተው እነ ባዬን የተቀላቀሉ፣ በዚያም በአሠራር፣ በምንትስዬ፣ ቅብጥርስዬ ትግሉን የሚጎትቱ ሴረኞች አድርጌ ነው የማየው። በሸዋም እነ መከታውና እነ አቤ ጢሞ ይሄን የእነ ሀብቴን መንገድ ተከትለው የእነ ኢንጂነር ደሳለኝን ተቋም በእርቅ ስም ገብተው እንዲያፈርሱ፣ እንዲያዘገዩ መመሪያ እንደወረደላቸው ነው የሚሰማው። እነ ደሳለኝ ካልተጠነቀቁ ይበሏታል። ሌላው ሰሞኑን ለእስክንድር በልዩ ዘዴ ከሞተበት አፈር ልሶ ተነሥቶ የሌለ የአቅም ግንባታ ሲያደርግ ተስተውሏል። የሚዲያ የበላይነት እና የዲያስፖራ ተቀባይነት እንዳለው ጠቆም አድርጎም አልፏል። በአጠቃላይ እስክንድር የሚመራው ድርጅት እና የዘመነ በስም ብቻ ተቀምጦ አስረስ መዓረይ የሚዘውረው የዐማራ ፋኖ በጎጃም ከጎንደሩ ስኳድ ጋር ከፋፍሕዴንም ጋር በመናበብ አንዱ ሌላኛውን የማዳን ሥራ ላይ ተጠምደው ነበር የከረሙት።


አንድነት ማምጣት ያልፈለጉ የጠላት ቅጥረኛ ሆነው በዐማራ ካባ የሚንቀሳቀሱ ሁሉ የልጅ ልጆቻቸው፣ ዘር ማንዘራቸው በሙሉ የውርደት ካባ፣ የኀዘን ማቅ ይለብሳል። ዘመነ፣ ባዬ፣ ሀብቴ፣ ደረጄ፣ አስረስ፣ ዝናቡ፣ ማንችሎት፣ ምሬ፣ ማስረሻ፣ ሙሀባው፣ እስክንድር፣ መከታው፣ ደሳለኝ በለው ማን ሁሉም በታሪክ ተወቃሽም፣ ተጠያቂም ይሆናሉ። እነርሱ ብቻ አይደሉም እኔንም ጨምሮ አሁን እየደከምኩ ካለሁት ድካም በበለጠ ደክሜ እስከምችለው ጥግ ድረስ ቃል በገባሁት መሠረት ካልተንቀሳቀስኩ፣ ቀራንዮ ሳልደርስ መንገድ ላይ ከፌርማታው ከወረድኩ ዘመድኩን የሚለው ስሜ በይሁዳነት፣ በዲያብሎስነት መጻፉ አይቀርም። ይሄ ደግሞ ጊዜው ደግሞ ሩቅ አይሆንም። በቅዱሱ የዐማራ ትግል ላይ መሳሳት ከባድ ዋጋ ነው የሚያስከፍለው። ፍጻሜዬን እንዲያሳምረው አብዝታችሁም ጸልዩልኝ። አንድነቱን ጎትተው ዐማራን ለጥቃት፣ ለውርደት፣ ለድህነት ምክንያት ሆነው የዳረጉ ሁሉ እገሌ ከእገሌ የለም በነፍስ በሥጋም ይጠየቃሉ። ዛሬ ላይ በሚዲያው ዘርፍ ለከርሳቸው ሲሉ፣ ልጆቻቸውን በዐማራ ሞት ነግደው የሚያሳድጉ፣ ነውረኛ ጋዜጠኞች፣ አክቲቪስቶች፣ ቲክታከሮችም ሆኑ የፖለቲካ ኃይሎችም የሚዋረዱበት ቀን ሩቅ አይደለም። ሰሚ አገኘሁ አላገኘሁ እኔ የህሊና እረፍትና እርካታ ሰላምም በታሪክም በእግዚአብሔርም ፊት የተጠያቂነት ስሜት እንዳይሰማኝ አድርጌ እየደከምኩ ስለሆነ እረፍት ነው የሚሰማኝ። እውነትን ተንፍሼ በሰላም ነው የምተኛው። የማንቀላፋውም።

"…የዐማራ ሕዝብ አሁን ስቃይ ላይ ነው። ግን ይህ ስቃይ ከክብሩና ከማንነቱ እንደማይበልጥ ስለሚረዳ ከገበሬ እስከ ተማርኩ ነኝ ባይ ጥርሱን ነክሶት ችሎ እየኖረ ነው። ስቃዩ ደግሞ በገዢው የኦሮሙማው አገዛዝ ብቻ አይደለም ለአንተ ነው እየታገልኩልህ ያሉት በሚሉትና በስሙ ምለው በሚገዘቱት ከአብራኩ በወጡት ልጆቹ ጭምር ነው። ገበሬው በክረምት ባይኖረው እንኳ በሬውን፣ ፍየሉንና ላሙን ሽጦ እየሸመተ ከልጆቹ እኩል ፋኖን ቀልቧል። አሁንም እየቀለበ ነው። ፋኖዎች ዝናብ ሲመጣባቸው በለሊት ሳይቀር ቤቱን እየከፈተ ኑ ግቡ እያለ እያስጠለለ ኖሯል። በገዢው ኃይል እየተደበደበ በየት በኩል አለፉ ሲባል በቀኝ ከሄዱ በግራ፣ በግራ ከሄዱ በቀኝ እንዲያም ሲል ደግሞ እነሱ ደፈጣ እንዲጥሉ እየተነጋገረ ጠላትን ወስዶ እየማገደም ታግሏል፤ እየታገለም ነው። ይህን የሚያደርገው ሁሉም ነገር ከክብሩ እንዳማይበልጥ ጠንቅቆ ስለሚያውቅ ነው። የእኔ ዘመን የዐማራ ትውልድ ግን ክብርን አያውቀው ይሆናል። ለዚህ ነው ሦስት ሺ

ብር ተቀብሎ የፋኖ የጦር መሪን ለማስገደል ዐማራ ሆኖ በሆዱ የሚወድቀው። እነሱ ግን ከክብር የበለጠ አንዳች ነገር እንደሌለም ያውቃሉ። ኦሮሙማው በብራኑ ጁላ በኩል እንኳን ትጥቁን የዐማራውን ሱሪውን አስፈተዋለሁ ያለ ዕለት ነው በክብሩ እንደተመጣበት የተረደው። አየር መንገድ ፍተሻ ላይ ቀበቶ አውልቁ ሲባል ሞቼ ነው ቆሜ በሕይወት እያለሁማ ቀበቶዬን አላወልቅም የሚል ማኅበረሰብ መሳሪያህን ፍታ ስባል ነው አሁንስ በዛ ብሎ ለክብሩ የተነሣው። ነገር ግን ክብር ምን እንደሆነ በማያውቁ ጎረምሳ፣ ዱርዬ፣ ከየመናሃሪያው ከጫኝና አውራጅነር፣ ከመንደር ፊልም ቤትና መጠጥ ቤት ተግበስብሶ ጫካ የገባው ሆዳም ኃይል ለጊዜው ሚዛን ደፋና ወሳኝ ኃይል እየሆነ ስለመጣ የዐማራን ክብር በሆድ፣ በሥልጣንና በብር ለወጠው። መስተካከሉ ግን አይቀርም።

"…ወደ ቀጣዩ ሰሞነኛ የዐማራ ፋኖ በጎጃም የእነ አስረስ መዓረይ ቲያትር እንምጣ። እኔም በዘመዴ ሚዲያ መወጠሬን ያየው አስረስ መዓረይ ሰሞኑን በተገኘው ሚዲያ ላይ ሁላ እየቀረበ የፖለቲካ ካፒታሉን ለመገንባት ሲላላጥ እያየሁት ነው። በተለይ ቀዌው እስክንድር ነጋ በዐማራ ቦለጢቃ ውስጥ በጊዜ ፈንጂ ረግጦ ብትንትኑ በመውጣቱና እንደማይጠቅም የተረዳው የውጭና የውስጥ ኃይሉ በእስክንድር ነጋ ፖለቲካዊ ሞት እስክንድርን በከሃዲው ፀረ ዐማራ አንድነት በአፍቃሬ ወያኔው የብአዴን ፈረስ የስም ግንባታ ላይ ተጠምደው ከርመዋል። የጎጃም ዐማራ ፋኖ በተፈጠረበት ውስጣዊ መነቃቃት ምክንያት እነ አስረስ መዓረይ ጥያቄ ሲበዛባቸው ጊዜ ከምዕራብ ጎጃም ወደ አባይ ሸለቆአቸው መመለስ ጀምረዋል። በተለይ በአርበኛ ዘመነ ካሤ የፋይናንሱን ክፍል ከማንችሎት ለእኔ ይሰጠኛል ብሎ ይጠብቅ የነበረው የግንቦት ሰባት የብአዴን ቅጥረኛው፣ ዘመነ ካሤን አሳልፎ ሰጥቶ በወኅኒ ያከረመው መሰሪው ጥላሁን አበጀ ምንም ዓይነት ሥልጣን ሥላላገኘ ቆሽቱ እርር ብሎ ወደ ሸበል በረንታው ጥሎት ወደ ሄደው፣ አክስሮት፣፣ አውድሞት ወደሄደው አባይ ሸለቆው ብርጌዱ ዓይኑን በጨው አጥቦ ተመልሷል። ጨዋታው አሁን ነው የሚጀመረው። ግመል ሰርቆ አገንቦሶ አይሆንም እና በሰበር ዜና የማይሸፈን ከባድ ቀውስ አሁን ነው የሚፈጠረው። የምዕራብ ጎጃምና በተለይ የምሥራቅ ጎጃም የተዋሕዶ ልጆች ከአገው የተዋሕዶ ልጆች ጋር ማበርና የምሥራቁን የቅባቴዎቹን መርዘኛ አካሄድ እየተረዱ መጥተው ጓ ማለት መጀመር አስደንግጧቸዋል። አሁን ጮቄ ተራራ ላይ ሆኜ እንደማየው ከሆነ ሠራዊቱ ለእነ አስረስ መዓረይ እንደ ድሮው ጠብ እርግፍ ማለት ሁላ ትቷል። እንዲየውም ለብቻው ትናንሽ አንጇ ሁላ ተፈጥሯል። እነ አስረስ መዓረይን ፀረ ዐማራ አንድነት ኃይል፣ ባንዳ ማድረግ ሁላ ተጀምሯል። ስለዚህ እነ መዓረይ ወደ ቀደመው መሰሪ ሤራቸው መመለስ ጀምረዋል። እዚህ ላይ መዝግቡልኝ። አስረስ መዓረይ፣ እስክንድር ነጋ፣ ማስረሻ ሰጤና ጥላሁን አበጀ አንድም ቀን ተጣልተው አያውቁም። በጥበብ የተጣሉ መስለው ነው እየተናበቡ ሥራቸውን የሚሠሩት። 👇 ④ ✍✍✍

👆⑤ ✍✍✍ "…በቀጣይ በጎጃም በቅርቡ ምንድነው ይሆናል ተብሎ የሚጠበቀው። የእነ አስረስ መዓረይ፣ የማስረሻ ሰጤና  የጥላሁን አበጀ የጋራ ግንባር እንደ አሜባ ሦስት ቦታ ተከፍሎ የጎጃም ዐማራን ቦለጢቃ ያውከዋል። በቀደም ትዊተር ስፔስ ላይ ማስረሻ ሰጤ ሲናገር ልብ ብላችሁ ሰምታችሁት ከሆነ ማስረሻ ፈርጠም ብሎ ጎጃም ውስጥ 3 አደረጃጀት ነው ያለው ነው ያለው። አንደኛው ሕዝባዊ ድርጅት ሲሆን ሁለተኛው በዘመነ ካሴ የሚመራው የዐማራ ፋኖ በጎጃም እንዲሁም ከሁለቱም ያልሆነ ብርጌድና ክፍለጦር አለ ብሎ ነው የተናገረው። የማስረሻ ንግግርም በአጋጣሚ የተነገረ ወይ ደግሞ ለፖለቲካ ፍጆታ ተብሎ የተነገረም አይደለም። በመሰሪዎቹ ፀረ ዐማራ ፋኖ በጎጃሞቹ አስረስ መዓረይና በጥላሁን አበጀ በደንብ ታቅዶበትና ታስቦበት ከማስረሻ ጋር በመናበብ የተነገረ ነው። ለዚህም ማሳያ ከላይ ነካ እንዳደረግኩላችሁ ባለፈው ሳምንት የዐማራ ፋኖ በጎጃም የፋይናንስ ክፍል መሾሙን ተከትሎ ጥላሁን አበጀ በፌስቡክ ገጹ ላይ ንዴቱን፣ ብስጭቱን እሳት እየተፋ ሁላ ጭምር ሲገልጽ ነበር። ምክንያቱም የሕዝብ ግንኙነቱንም ሆነ የፋይናንስ ዘርፉን የአስረስ መዓረይ ቡድን በጅምላ መቆጣጠር በመፈለጉ ምክንያት ያ ባለመሳካቱ ጭምር ነው። አሁን አስረስ መዓረይ ጥላሁን አበጀ እንዲያምፅና ድርጅቱም፣ ተቋሙም መርህ እንደሌለው አድርጎ አዋርዶና የተበሳጨ መስሎ ቀድመው ወደ አዘጋጁት ተጠባቂ የዐማራ ፋኖ በጎጃምን ከፋፍሎ የማዳከሙን ሴራ ወደመጀመር ለመግባት ሰበብ እየፈለገ መሆኑን እያሳየ መሆኑ ነው። በማርሸት ፀሐዩ ተፈርሞ የወጣው የአመራሮች የሚዲያ ላይ ሥነ ምግባር መጣስ እርምጃ እንደሚያስወስድ መመሪያ ቢወጣም በቤተሰብ የተጠረነፈው የዐማራ ፋኖ በጎጃም የጥላሁን አበጀን ጋጠወጥ ጥሰት ለማስቆም አልተቻለውም። በጥላሁን የፌስቡክ ኮመንት ሥር ምስኪን የጎጃም ዐማሮች በንዴት አንተ ሰው ለድርጅቱ፣ ለተቋሙ ሕግና ደንብ


👆③ ✍✍✍ …ለጎጃም ዐማራው ከባድ ጦስ ነው ይዞ እየመጣለት ያለው። የጎጃም ዐማራው ነቅቷል ግን ምንም ማምጣት አልተቻለውም። አገው ሸንጎው በሁለት ካርድ ነው የሚጫወተው። ሲበርደው ዐማራ ሲሞቀው አገው ሸንጎ። ዐማራው ግን ቢበርደውም፣ ቢሞቀውም አንድ ካርድ ብቻ ነው ያለው። ምስኪን ዋሸሁ እንዴ?

"…በቀደም ዕለት አርበኛ ፋኖ የቆየ ሞላ በአገው ፈረሰኞች የፖለቲካ በዓልን አስመልክቶ ባስተላለፈው መልእክት ላይ አማርኛ ቋንቋ ላይና ዐማራ ላይ ያንን መርዝ ሆን ብሎ ነው የረጨው። ያ የቆየ ድንፋታ እንዲሁ ዝም ብሎ በድንገት የመጣም አይደለም። ከዚያ በፊት ብዙ ታስቦበትና የኦሮሞ አክቲቪስቶችና የትግሬ አክቲቪስቶች ሙሁራን ተብዬዎቻቸው ጭምር በቃልም በመጽሐፍም ሲጽፉና ሲናገሩት የከረሙትን ነው ጊዜው ደርሷል ተብሎ በጊዜ የተለቀቀው። የቆየ ሞላ ሴቭ ኦሮሚያ ላይ ሲጻፍ የከረመውን ነው አማርኛን የወታደር ቋንቋ አደርጎ ባለቤቱ አገው ነው ብሎም የተናገረው። ተወደደም ተጠላም የዐማራ ፋኖ በጎጃም አሁን ላይ በአገው ሸንጎው ኃይል ቁጥጥር ስር እየሆነና እየተዋጠ ነው። መሬት ላይ ያለው ኃይል ብቻ አይደለም አየር ላይ ያለው የዐማራ ፋኖ በጎጃም አፈ ቀላጤ ነኝ የሚለው አካል በሙሉ በአገው ሸንጎ ኃይል ነው። እስቲ ጎጃሜ ነኝ የሚሉትን የአየር ላይ ድምጾች ከጥቂቶች በቀር ከአልማዝ ባለጭራዋ ጀምራችሁ ዘራቸውን ቁጠሩ፣ በአብዛኛው ሸንጎና ኦሮሞ ወይ ትግሬ ናቸው። የጎጃም ዐማራ ዶላር ያዋጣል። ዶላሩን የሚሰበስቡትን እናት አባታቸውን ቁጠሩ ብትሏቸው የትግሬና የኦሮሞ፣ እንዲሁም የፖለቲካው ሸንጎ ዲቃሎች ናቸው። እናም ገንዘቡ ተሰብስቦ የሚደርሰው ለጎጃም ዐማራ ፋኖ ታጋዮች አይደለም። ቅማንቴው ፓስተር ምስጋናው እና የትግሬና የአገው ድቅሉ ተስፋዬ ወልደ ሥላሴ የሚሰበስቡት ዶላር ለጎንደር ዐማራና ለጎጃም ዐማራ ሲደርስ አስባችሁታል? አትፍሩ ደፈር ብላችሁ መፍትሄ ፈልጉ።

"…ምን ይሄ ብቻ ወጣቱን እኮ የአገው ሸንጎን ወጣት እነየቆየ ሞላ በፋኖ ስም እስከአፍ ገደፉ እስከ አፍንጫው ድረስ አስታጥቅታል። ዘጭ ነው ያደረጉት። ኢንጂነር ማንችሎት የደቡብ ጎንደር የሰፈሩን ልጆች በጎጃም ዐማራ ስም እስከ አፍንጫው ድረስ እንዳስታጠቀ ሁሉ እነ የቆየም እንዲሁ አስታጥቀዋል። ኮሎኔል ያሬድን አቅፎ አይዞኝ እኛ እጅ ነው ያለው እንለቀዋለን ብሎ የሚናገር ፎቶ ሲነሣ እኮ መጠርጠር ነበረበት የጎጃም ዐማራው። የአገው ሸንጎ ወጣት በዐማራ ፋኖ ስም የጎጃም ዐማራውን ዘርፎ የሌለ ሀብት እንዲያፈራ ተደርጓል። የጎጃም ዐማራ ነጋዴን፣ ባለሀብትን በሙሉ ዘርፈው ባዶ ራቁቱን አስቀርተው አሁን ጠይቁማ እዚያ አካባቢ ያለው ፋኖ ለአዊ ዞን እጁን ሰጠ በሚል ሰበብ ከፋኖ ትግል እያስወጡት ነው። ይህ እንዲሁ ዝም ብሎ በድንገት የተፈጠረ አይደለም። ሁሉም ነገር በዕቅድ በፕላን ነው እየተሠራ ያለው። አሁን እየረፈደ ስላለ ሌላ ተአምር መለኮታዊ ጣልቃገብነት ካልታከለበት በቀር የዐማራ ፋኖ በጎጃም የእነ የቆየን የአገው ሸንጎውን ክንፍ ከነካ ሸንጎው አቅምም ስለፈጠረ በጎጃም ምድር ደስ የማይል በጣም መጥፎ ነገር ሁላ ይፈጠራል። በዚህም አይቆምም አኩራፊ ሆነው ሁላ ይወጣሉ። ከዚያ የአገው ሸንጎው ከብልጽግናው ክንፍ ጋር በመሆን በግልጽ የክልልነት ጥያቄን ያነሣሉ።

"…የብልጽግናው ክንፍ የመጀመሪያ እሳቤው የነበረው ዐማራን 6 ወይም 5 ክልል ለማድረግ ነበር። ለዚህ ብዙ ሥራ ሠርተዋል። ብዙ የሰፈር ጡዘቶችን ፈጥረዋል። ነገር ግን ብዙም አላስኬድ አላቸው። አሁን ትኩረቱን በክልሉ ውስጥ ወዳሉት ልዩ እየተባሉ ወደ ተቀመጡት ዞኖች አድርጓል። በዚህ አያቆምም ሙከራውን ከእነዚህ በመጀመር በመካከል ትልልቅ የቁርሾ ድንበሮችን በመፍጠር ዐማራውና አገው ለዘላለም አብረው እንዳይቆሙና የኦሮሙማው ዳጋፊ እንዲሆኑ የማድረግ ፖለቲካ ነው ለመሥራት እየዳከረ ያለው። ለዚህ ፕሮጀክት ከላይ እንዳልኳችሁ በዋጋኽምራ ውስጥ ውስጡን እየተሠራ ነው። ቤተ ክህነቱ ሁላ ለዚያ ተባባሪ ሆኖ ተገኝቷል። ሰልፍ ሁላ እየተወጣ ነው። ነፃ አውጪ ጦርም በትግሬ እየሰለጠነ ነው። አዊ ዞን በአገው ሸንጎው ከብልጽግናው እስከ ፋኖ መስመር ዘርጎቶ እየተሠራበት ነው። በዚህ ሂደት ውስጥ ትልቅ ጦስ እየመጣበት ያለው ግን የጎጃም ዐማራው ነው። ይህን ፕሮጀክት ያደናቅፋሉ የተባሉ የጎጃም ዐማራ ፋኖዎች ሁላችሁ እንደምታውቁት እየተረሸኑም ዘወር እየተደረጉም ነው። ለምሳሌ የቅርብ ጊዜው አርበኛ ዮሐንስ ከጀርመን ራዲዮው ጋዜጠኛ ጋር ጠንካራ የተባለ ቃለ መጠየቅ ካደረገ በኋላ ስለ አገው ሸንጎ የሰጠው አስተያየት ከባድ ስለነበር በሴራ እንዲወገድ ተደርጓል። ነገርየው ከባድ ነው።

"…እዚህ ላይ ስለ ጎንደሩ ክፍል ስለ ስኳዱ አንድ ሀቅ ልንገራችሁ። ይህ ክንፍ እያንዳንዷን የፖለቲካ ሂደት በጥንቃቄ እየገመገመ ነው የሚንቀሳቀሰው። ወልቃይት ያለው የትግሬ ዲቃላው ስኳድ ጎንደርን እንደ ጋሻ በመጠቀም ራሱ ተቃዋሚውን አብን፣ የገዢ ፓርቲውም ብአዴን ብልፅግና አንድ በመሆን፣ ፋኖም ውስጥ በፋፍዴን በኩል በመወከል የአብይ አህመድን የብልፅግና አካሄደን በሚገባ ገምግሟል። ኡጋንዳና አሜሪካ ያለውም፣ እስራኤልና አዲስ አበባም ያለው የጎንደር አሁን ላይ የደረሱበት የደረሱት ድምዳሜ የጎጃም ዐማራው ራሱን እያዳነ አለመሆኑንም ነው። ይሄን በሚገባ ገምግመው ተረድተውታል። እንበልና አይቀሬው የክልል ጉዳይ ቢመጣ አሁን የጎጃሙ ዐማራ በአገው ሸንጎና በወያኔ ወኪሎች ተጠርንፎ ስለደቀቀ ስኳድ ጣናና ባሕርዳርን ያካተተ ሙሉ የጎንደር ክፍለ ሀገርን መሥርቼ በኃይልም አስከብሬ በመውጣት ክልል መሆን አለብኝ ብሎ ነው እየሠራ የሚገኘው። እነ አያሌው መንበር የአቡነ ሀራ ገዳም የጎንደር ነው። ጣና የደንቢያ ግዛት ነው ብለው ጣና ቲቪ ብለው ለነቆራ የመጡ ከመሰላችሁ ተሳስታችኋል። በጥናት ነው። ስለገባቸው ነው ጎጃሞችም ጎርጎራ ቴቪ ብለው ዊኒጥ ዊኒጥ ለማለት የሚሞክሩት። ለዚህም ቅማንትን፣ እነአብይና የህወሓቱ ክንፍ ጋር ለመነካካት ቢሞክሩም ለጊዜው አልሆነም። በዋናነት አብይ እዚህኛው ላይ አሁን ትኩረት ማድረግ አልፈለገም። እንዲያው እንደ አጋዥ እየተጠቀመባቸው ነው ያለው። በመሃል ትግሬንም ትንሽ ደቁሶ ያቆሰላቸውንም ለቅሞ ገዳድሎ ለመምጣት ስለሚፈልግ ጎንደሬዎቹን ለጊዜው አሞሌ ጨው እያላሰ፣ በሚስቱ በኩል አማቾቹን በረጅም ገመድ አስሮ እንዲፈነጩ እያደረገ ነው። ይሄ ግን ለጊዜው ነው እንጂ አረመኔው አቢይ ዕድሜ ሰጥቶት ከቆየ የሌሎች ሲሳካና በፈለገው መንገድ ሲጠቃለል የጎንደር ዐማራን ልክ እንደ ጎጃም ዐማራ አጣብቂኝ ውስጥ አስገብቶ ይጨፈልቀዋል። ከዚያ ሙሉ ጎንደርን በፖለቲካው ቅማንት ያስወርሩታል። እንዲህ ነው እየተጓዙ ያሉት። አሁን ጎንደር ላይ እድሳት ምናምን እንቶ ፈንቶ የጎንደር ዐማራን ማለዘቢያ ነው። ቅማንቱንም ተው ቆይ ተብሏል። …👇 ③ ✍✍✍

👆④✍✍✍ …

"…በአጠቃላይ የዐማራ ፋኖ አንድ ሁኖ አቅም ካልፈጠረና አሁን ባለበት ከቆየ ምን አልባትም በታሪክ ለሕዝቤ እታገላለሁ ብሎ ሕዝቡን ያስበላና የጠላትን ዓላማ በከፍተኛ ሁኔታ አፍጥኖ ያሳካ ታሪካዊ ኃይል ሁኖ በታሪክ የፋኖነትን ስም፣ ክብር፣ ዓላማና ዝና ጠልሽቶ፣ ተዋርዶ በጥልቅ ጉድጓድ ቀብሮት ያልፋል። ጎንደር እስከ አሁን አንድ አልሆነም። ምክንያቱም ገና ስላልጠራ። እኒህ አሁን ዘመነ እስክንድር እያሉ ለዚህ ሁሉ መከራ ዐማራን የዳረጉት ግለሰቦችም አሟሟታቸው የውሻ ይሆናል። ስማቸውም በዐማራ ሕዝብ ውስጥ እንደ ይሁዳነት ሁኖ ማንም እንዳይጠራበት የክህደት ምልክት ይሆናል። ዛሬ ዐማራን ወደ


👆② ✍✍✍ …ሐሺሽ እየሰጡት፣ ከዓድዋው ትግሬ ከመርዞ ስታሊን ገብረ ሥላሴ ጋር በስልክ እያገናኙት ዘና ፈታ ሲያደርጉት ቆይተው ነው በስተመጨረሻ ከአዲስ ቅዳም ድረስ ሞተር እየነዱ በአዊ ዞን የሚኖሩ የትግሬና የአገው ሸንጎ ዲቃሎች ኮሎኔሉን በሞተር ይዘው እልም ብለው በመውጣት የዐማራ ፋኖ በጎጃምን የተቋም ዝርክርክነት እና አፍቃሬ ወያኔ ትግሬነትን ያሳያት። ኮሎኔሉ አሁንም ጦር እየመራ የጎጃም ዐማራን ይጨፈጭፍ ይሆናል። ከዚያ ሲማረክ እነ ማዕረይ ይለቁታል። ማን ከልካይ አለው?

"…እኔ ጎጃም ከገባሁ በኋላ የዐማራ ፋኖ በጎጃም መሪው አርበኛ ዘመነ ካሴ ሁለት ጊዜ ድምጹ፣ ሦስት ነው አራት ጊዜ ጽሑፉ ከመታየቱ በቀር የት ይግባ የት አይታወቅም። በቃ መንኗል። አርምሞ ላይ ነው ያለው። አሁን በዘመነ ፈንታ አየሩንና ምድሩን እየደበላለቀው፣ እየተንቀዠቀዠም፣ እየተቅበዘበዘም የሚገኘው ራሱን በራሱ የዐማራ ፋኖ በጎጃም ብሬዘዳንት አድርጎ የሾመው አፍቃሬ ትግሬ ወያኔው ብአዴኑ ፀረ ዐማራው መሰሪ ሾተላዩ አስረስ መዓረይ ነው። ሰውየው የሚሆነውን የሚሠራውንም አሳጥቶታል። መንቀዥቀዥ ቢሉ መንቀዥቀዥ አይምሰላችሁ። ልክ እባብ እንደበላች ፍየል ነው እየባዘነ፣ እየተቅበዘበዘ የሚታየው። ዘመነ ካሴ ወይ በረጅም ገመድ ታስሯል አልያም የአመራር ክህሎቱ ጥያቄ ምልክት ውስጥ ወድቋል። ይሄ ሁሉ ሲሆን የርሱ ዝምታ የጤና አይመስለኝም። ወይ ታግቷል ታፍኗል፣ አልያም ደግሞ የሞኝ፣ የየዋህ፣ የምስኪን፣ የአማኝ ገጸ ባሕሪይ ተላብሶ የትወናው አካል ሆኗል ብዬ በደፍረት ብናገር ትክክል እንኳ ባልሆን ስህተት አልሆንም። ወቅቱ ድፍረት ከሌለው መፍትሄ ስለሌለው ነው የምናገረው። አቢይ አቢይ አህመድን መጫወትማ ቀላል እኮ ነው። በፎቶ ቦለጢቃና በሚያማምሩ ቃላት ሕዝብን ማደንዘዝ ለጊዜው እንጂ ለአቢይ አሕመድም አልበጀ። የአርበኛ ዘመነ ካሤን አቋም ብረዳ እጅግ ደስ ባለኝ ነበር። በጊዜው እውነቱ መገለጡ አይቀርም። አሁን ግን ልጁ ያለበትን ሁኔታ ሳላውቅ ብዙ መፍረድም አልፈልግም። ጊዜ ግን ሁሉን መግለጡ አይቀርም።

"…የዐማራ ፋኖ በጎጃም አመራሩ በፓስተሮች፣ በአገው ሸንጎዎች፣ በብአዴኖች፣ በግንቦቴና በኢዜማ፣ በአብን እና በአፍቃሬ ወያኔዎች፣ በጥቂት ስኳዶችም ጭምር የተሞላ እንደሆነም ከላይ በስሱ ተነጋግረናል። ተግባብተናልም። ለዚህ ነው የዐማራ ፋኖ በጎጃም ቁልቁል እየወረደ፣ ሕዝቡም ወደ አዘቅት፣ ወደ መከራ እየሄደ ያለው። የጎጃም ዐማራ እንደ ቆንጆ ልጃገረድ ቁጠሩት። ያቺ ቆንጆ ልጃ ገረድ በአፍቃሬ ብአዴኑ አስረስ መዓረይ አንድ እጇን፣ በአፍቃሬ ብአዴን ግንቦቴው ጥላሁን አበጀ ሌላኛው እጇን፣ በሁለቱ ፓስተሮች ቀኝና ግራ እግሮቿን ተይዛ፣ አፏን ብአዴን፣ አብንና ኢድኅን በጨርቅ፣ በትራስ አፍነው እንዳትጮህም አድርገው ደረቷ ላይ ሸነጎ ተቀምጦ በአረመኔው የኦሮሙማ እያስደፈሯት እንዳለች መስኪን ልጃገረድ ነው የምቆጠርው። የጎጃም ዐማራ የወደቀበትን መከራ ሌላው ዐማራ አልወደቀበትም። አላገኘውምም። የጎጃሙ የተሸፈነው በሃሰተኛ ፀረ ዐማራ፣ ፀረ ጎጃም ዐማራ መሳይ አሞሮች ስለተሞላ ነው። እመኑኝ፣ ዘመዴ ምንአለ በሉኝ ይሄ ነገር ይቀለበሳል። ምልክቶችም እየታዩ ነው፣ እኔን አያድርገኝ ያኔ ዛሬ በሰበር ዜና የዐማራውን ነገድ ሲያጃጅሉ የሚውሉ ፀረ ዐማራ ዐማራ መሳይ አሞሮች በሙሉ ዋጋቸውን ያገኛሉ። እንደቀበጣጠሩ፣ እንደዋሹ መኖርም አይቻልም።

"…ለጎጃም ዐማራ ሌላም የተደገሰ ከፍተኛ የጥፋት ድግስ አለ። ይኸውም አረመኔው አቢይ አሕመድ የትግሬንና የዐማራን ሕዝብ ድምጥማጡን ለማጥፋት በሚያወጣው ዕቅድ መሠረት በሰጠው አቅጣጫም አሁን ላይ በሰሜን ወሎ የሚገኘው የዋግ ኸምራ ዞን ወደ ክልልነት ይደግ ተብሎ በውስጥ እየተሠራ መሆኑ እየተነገረም እየታየም ነው። በወያኔ የሠራዊት ሥልጠናም እየተሰጠው ነው። ባንዲራም ተሰፍቶለታል። ይሄን ተከትሎም የጎጃሙ የአዊ ዞንም የዋግን ፈለግ ለመከተል አቆብቁቧል። የአዊ ዞን ክልል መሆን ግን ለጎጃም ዐማራ የሚያመጣው ከፍተኛ አደጋ አለ። አስቀድማ ወያኔ ሆን ብላ ነው በፕላን የጎጃም ዐማራ አካባቢዎችን በሙሉ ለአገው ሸንጎ የሰጠችው። ለምሳሌ አዊ ዞንም ወደ ክልልነት ይደግ ከተባለ በዳንግላ ወረዳ የይገባኛል ግጭት መፍጠሩ አይቀርም። ይህ ለምሳሌ ያነሣሁት ነው እንጅ ሌሎችም ጊዜ ጠብቀው በጎጃም ምድር ይፈነዱ ዘንድ የተቀበሩ ከባድ አውዳሚ ፈንጂዎችም አሉ። ጃዊ ወረዳ ራሱ የተመሠረተው ከጎንደሩ አለፋ ወረዳ እና ከጎጃም አጎራባች ወረዳዎች ተቆርሶ ነው። ይሄም ሆን ተብሎ የተፈጸመ ነው። ልክ እንደ እንግሊዝ ቅኝ በያዘቻቸው ሀገራት ላይ ጊዜ ጠብቆ የሚፈነዳ የማንነትና የድንበር ጉዳይ እንደምታጠምድ ሁሉ ወያኔም እንደዚያ ነው በዐማራ ላይ ያሰደረገችው። ወያኔ በዐማራ ላይ ብቻ አይደለም በወልቃይት፣ በጠገዴ እና በራያ ከራሷ ከትግሬ ጋር። በአፋርም ከራሷ ከትግሬ ጋር ፈንጂ ቀብራለች። እሳቱ አሁን ላይ ራሷንም እየለበለባት ነው። በባድሜም ከኤርትራ ጋር ሌላኛው ፈንጂ ነው። በኦሮሞና በዐማራ መካከል በሸዋም፣ በወሎም ፈንጂ ቀብራለች። በሶማሌና በኦሮሞ፣ በአፋርና በሱማሌ፣ በአፋርና በኦሮሞ መካከልም ቀብራለች። በሐረሬ እና በኦሮሞ፣ በድሬደዋ በሶማሌና በኦሮሞ፣ በቤኒሻንጉልና በዐማራ፣ ቤኒሻንጉልና በኦሮሞ መካከልም ፈንጂ ቀብራለች። በደቡብ ኦሮሞና ደቡቦች ገና የሚጨፋጨፍበት፣ እንዲሁ የሚፋጅበት የድንበር የማንነት የተቀበሩ ፈንጂዎች አሉ። አዲስ አበባም ገና እሳተ ገሞራን የሚያስንቅ ፈንጂ ነው የተቀበረው። አሁን ላይ ኦሮሙማው በእልህ ዐማራውን ከአዲስ አበባ ማጽዳቱ፣ ዐማራን በምሥራቅ ሸዋ ድንበር አፍርሶ አውራ ጎዳናን አውድሞ ጋዛን ማስመሰሉ የልብ ልብ ስለሰጠው ሰሞኑን ድሬደዋን፣ ሐረርና ጅጅጋን ከሱማሌ ማስመለስ አለብን በማለት አክቲቪስቶቻቸው እያጓሩ ነው። ሞያሌ ላይ በሱማሌ ክልል ስር ያለውንም በጉልበት ሊጠቀልሉት ነው። በጋምቤላ በኩል ከደቡብ ሱዳን በላይ በአሶሳ አቅራቢያም ከሰሜን ሱዳን ተጎራብተዋል። ገና ከኤርትራ ጋር ይጎራበታሉ። ጊዜ ግን ቂጣ ነው። ነገ ደግሞ ይገለበጥና ያላረረውን ዛሬ ላይ ነጭ ለብሶ የሚጨፍረውን ያሳርረዋል። ይሄን መዝግቡልኝ።

"…መተከል ራሱ ኩታ ገጠም ድንበሩ ለአዊ ዞን እንጂ ለጎጃም ዐማራው እንዳይሆን ነው የተደረገው። ልብ በሉ ወያኔ የጎጃም ዐማራን ምድር ቆርሳ፣ ቆራርሳ ነው ክልላ ክልል ያደረገቸው። በዚያ ላይ አዊ የእነ ስማ ጥሩነህ፣ የእነ ኢንጂነር ሀብታሙ፣ የኦሮሞ ብልፅግናም ጠንካራ ድጋፍ አለው። በጎንደር አናሳው የፖለቲካ ቅማንቴው የጎንደር ዐማራው ላይ እንደተሾመ፣ እንደሰለጠነው ሁሉ በጎጃም ዐማራም ላይ አናሳው የፖለቲካው የአገው ሸንጎው በጎጃም ዐማራና አገው ላይ በኢኮኖሚውም፣ በቢሮክራሲውም፣ በፖለቲካውም፣ በጸጥታ ኃይሉም፣ በፍትሕ ተቋማቱም ላይ እንዲሠለጥኑ ተደርጓል። ወደዳችሁም ጠላችሁም፣ አመናችሁም አላመናችሁም በጎጃም ዐማራው ሥልጣኑም ሀብቱም ላይ የለበትም። በአዊ ዞን ኮሽ አይልም። ተማሪው ይማራል፣ ነጋዴው ይነግዳል። በጎጃም ዐማራው ግን ትምህርት ቤት በመከላከያው ይወድማል። መምህራን በአስረስ መዓረይ ፋኖ ይረሸናሉ፣ ይገደላሉ፣ ይሞታሉ። ይታገታሉም። የጎጃም ዐማራ ዱቄት እየተደረገ ነው። የአገው ሸንጎ ባህርዳር ፎቅ እየሠራልህ ነው። ከባድ ነው። ሲነግሩት ለማይሰማ ሕዝብ ሰሚ ባይገኝም ለመፈራረጃ እንዲህ ለታሪክ የሚቀመጥ ሰነድ አስቀምጦ ማለፉም የአባት ነው። ብቻ ለጊዜው ሆይሆይታ እንጅ የአዊ ፖለቲካ…👇② ✍✍✍


"ርእሰ አንቀጽ"

"…ለሚፈለገው ለ300 ሠራዊተ ጌዴዎን 6 ፍሬ ሃባ ሰው ሲቀር 294 ሰዎች በነፍስ ወከፍ ከ1ሺ እስከ 300 ዶላር በማዋጣት በቅርቡ ተቋቁሞ አየር ላይ ሊወጣ በማኮብኮብ ላይ ላለው የዘመዴ ሚዲያን ለመደገፍ ግርር ብለው መጥተው በሰልፍ እየተጋፉ እኔን በደስታ አስክረው እንቅልፍ አሰሳጥተው ጮቤ ያስረገጡኝን ወገኖች መዝግቤ ከጨረስኩ በኋላ ነው ከራየን ወንዝ ማዶ ተነሥቼ ደመና እየጋለብኩ በኤርትራ በኩል በወልቃይትና በትግራይ መሃል አቋርጬ ለጥቂት ደቂቃዎች በሰሜን ተራሮች ላይ አረፍ ብዬ ወደ ተወዳጁ፣ አምሳለ ገነት ደግሞም የምሥራቅ አፍሪካ የውኃ ታንከር ወደሆነችው ወደ ጎጃም ጮቄ ተራራዬ የተመለስኩት። አሁን ደርሻለሁ። በነፋሻማው አየር፣ በፏፏቴው ድምጽ፣ የአእዋፋትን ዝማሬ እያደመጥሁ ርእሰ አንቀጼን መጻፍ እጀምራለሁ። በጥሞና ተከታተሉኝ።

"…በዐማራ ክልል በተለይ በጎጃም ነገሮች ከለቅሶ በኋላ፣ ከሠርግና ከድግስ በኋላ በቤታችሁ ውስጥ እንዳሉ ተዘበራርቀው እንደተቀመጡና ድግሱም፣ ልቅሶና ሠርጉም አልቆ፣ ለቀስተኛው፣ ሠርገኞችም ሄደው ዕቃዎችን ወደነበሩበት ለመመለስ ዝግጅት የሚያደርጉ ቤተሰቦች ቆመው ምን እናድርግ? ዕቃ ማስተካከሉን ከሳሎን እንጀምር ወይስ ከጓዳ፣ ከበረንዳ እንጀምር ወይስ ከኩሽና፣ ከመኝታ ቤት ከየት እንጀምር ብለው እንደሚመክሩ ያሉ ሰዎችን ይመስላል። ዕቃውን ለማስተካከል ራሳችን ብቻ እንበቃለን ወይስ ጎረቤት እንጥራ፣ ወይስ ወዛደር እንቅጠር? የሚሉ ቤተሰቦችን ይመስላል። በጎጃም የነበረው ትርምስምስ በሠርገኞችና በለቀሰኞች ድምጽ ስለተዋጠ ከውጭ ያለ ሰው በውስጥ ያለውን ትርምስ አላየም። አልተረዳውምም። የጎጃም ዝብርቅር አይጣል ነው። መላ ቅጡ ነው የጠፋው። አሁን ከግርግሩ፣ ከስካሩ ከባነኑ በኋላ ጭንቁ እንዴት እናስተካክለው የሚለው ሆኗል። እኔም የታዘብኩት ይሄንኑ ነው።

"…የዐማራ ፋኖ በጎጃም እንደ አጀማመሩ ቢሆን ኖሮ የት በደረሰም ነበር። ሕዝባዊ የነበረውን የዐማራ ፋኖ በጎጃም ትግል እንደ አጀማመሩ የጎንደር፣ የሸዋ፣ የወሎም ርዳታና አጋዥነት ሳያስፈልገው ዓባይን ተሻግሮ አዲስ አበባ ይገባል ተብሎም ነበር በብዙዎች ተገማች የነበረው። ነገር ግን የጎጃም ትግል የግንቦት ሰባት፣ የወያኔ፣ የብአዴን፣ የሻአቢያ፣ የፌክ ኢትዮጵያኒስቱ፣ የግንባሩ፣ የውጭና የውስጥ ኃይሎች ቡዶች በሉት። አፈዘዙት፣ እጅ እግሩን አስረው አላላውስ፣ አላንቀሳቅስ አሉት። ከቤትም አዋሉት። የጎጃም የዐማራ ፋኖ የሆነው እንደዚያ ነው። በሰንሰለት ነው እጅ እግሩ የታሰረው። የተጠረነፈው። ያ ሁላ የጋለ፣ የተንቀለቀለው የነፃነት ጥማት በአንደዜ ነው አፈር ከደቼ የበላው። አሁን ሠራዊቱ አለ፣ መሣሪያው አለ፣ ወንድነቱ አለ፣ ጀግንነቱ አለ፣ ግን ታስሯል። ሽባ ሆኗል። መፈታትን፣ ነፃ መውጣትን ይፈልጋል። ግን እንዴት ወጥመዱ ይሰበር?

"…አሁን የዐማራ ፋኖ በጎጃምን የሚመሩት በ1ኛ ደረጃ የብአዴንና የወያኔ ኤጀንቶች ናቸው። የግንቦት 7 እና የዐብን ኤጀንቶችም የዐማራ ፋኖ በጎጃምን ጠርንፈው እየመሩ ወደ ገደል እየከተቱት ነው። የጎንደር ስኳድ በዐማራ ፋኖ በጎጃም ውስጥ እንደ አገው ሸንጎ ባይሆንም የሆነ ሴል ግን አለው። ኦሮሙማው በብአዴን እና በአገው ሸንጎ በኩል ተወክሎ በጎጃም ዐማራ ፋኖ ውስጥ የራሱን ቦታና ስፍራ ይዞ ተቀምጧል። ወያኔ ትግሬዋና የጴንጤ ፓስተሮችም ጎጃም ከትመዋል። እንደ ስለሺ ከበደ ያለ ወንድሙ ከተማ ከሰው ጋር በግል ሲጣላ ድረስልኝ ብሎ ፋኖ አሳዝዞ የሚያስገድልም ጉደኛ ነው የተፈጠረው በጎጃም። ወያኔ በፋኖ አመራሮች ውክልና አግኝታ በድፍረት የምትንቀሳቀሰው በጎጃም ነው። በሌላም በኩል የወያኔ ሰዎች በጎጃም ከብልፅግና ሠራዊትም ጋር አብረው በመከላከያ ስም ጦር እየመሩ ጎጃም የጎጃምን ወጣት፣ ሽማግሌ፣ ገበሬ፣ ቤቱንና ከብቱን በሕጋዊ መንገድ እያወደሙ ይገኛሉ። "የትግራይ ወጣት ያገኘው መከራ፣ የትግራይ ሕዝብ የወረደበት መዓት ዐማራም ላይ ሊወርድ ይገባል" በሚሉ በመዐማራም ላይ ቂም በቋጠሩ የትግሬ የጦር መኮንኖች የሚመራ የኦሮሙማ ጦር በጎጃም የጅምላ ፍጅት እየፈጸመ ይገኛል። ከብቱ ሳይቀር እየተረሸነ ነው። እርሻ ላይ ያሉ ገበሬዎች እየተረሸኑ ነው። መሪጌቶችና ቄሶች፣ ዲያቆናት እየተረሸኑ ነው። በጎጃም ያለው ሰቆቃ እንዲህ ነው ተብሎ የሚገለፅ አይደለም። ነገር ግን ይሄ ሁሉ ሰቆቃ እንደ ብልፅግና ፓርቲ ኔጌቴቭ ኢነርጂ ያመጣል ተብሎ በሀሰት ፕሮፓጋንዳ፣ በአስረስ መዓረይ ቀጣፊ፣ አለብላቢ፣ ሸውከኛ ምላስ የተሸፈነ ነው። የጎጃም አክቲቪስት ተብለው አየር የያዙት በሙሉ ከሃዲ፣ ይሁዳ፣ ፀረ ዐማራ፣ ድቅል ማንነት ያላቸው፣ ለወያኔ የተገረዱ ይበዙበታል። የጎጃም ዐማራ በእነዚህ ዲቃሎችና ባንዳዎች የሀሰት የፌክ የድል፣ የምርኮ ዜናዎች ተሸፍኖ በጨለማ እየማቀቀ ነው። የጎጃም ዐማራ መራር መድኃኒት ጨክኖ ጠጥቶ መፈወስ እየቻለ በዳተኝነት እንደ ኩርድ ሕዝብ በጎረቤት ሀገራት እየተዋጠ ያለ አሳዛኝ ምስኪን ሕዝብ ነው። የምጽፈው ይመርራል። እውነቱ ግን ይሄው ነው።

"…የኦሮሙማው አገዛዝ ከሌላው የዐማራ ግዛት በተለየ ሁናቴ በአሁኑ ጊዜ ትግሬ ሆነው ከሥራ ውጪ ያደረጋቸውን፣ ከእስር ቤት ከሞት ከርሸና ተርፈው በሕይወት ያሉትን የጦር አመራሮች መልሶ ጠርቶ በመከላከያ ሠራዊት ውስጥ አስገብቶ የላከው ወደ ጎጃም ነው። ምክንያቱ ደግሞ የሚከተለው ነው። አንደኛው የትግሬ የጦር አመራሮች በሰሜኑ የጁንታ ጦርነት ግዜ በዐማራ እንደተመቱ ነው የሚያስቡት፣ ኦሮሞ እሬቻቸውን ቢያበላቸውም እነርሱ ግን እስከ አሁን የሚያስቡት ዐማራ እንደከዳቸው ነው። ሻአቢያ የሱማሌ ሠልጣኝ ተለማማጅ ጦር ይዞ ገብቶ መስቀል ያለበትን ትግሬ ሁሉ አላህ ወአክበር እያለ እንደፈጃቸው እያዩ ዐማራ ፎቢያቸው ግን ፈጥጦ ሲያጓሩ የሚውሉት ዐማራው ላይ ነው። በጦርነቱ ወቅት ጎንደር በከፊል በደቡብ ደብረ ታቦር ድረስ፣ በሰሜኑ ጭና ድረስ፣ ወሎ ሙሉውን፣ ሸዋ ደብረ ሲና ድረስ ወያኔ ገብታ ስላደቀቀችው በዚያን ወቅት ወያኔ ገብታ ምንም ያልሆነው የጎጃም ዐማራ ስለሆነ እሱን ማድቀቅ፣ መስበር ይፈለጋል። ለዚህ ደግሞ በዐማራ ላይ ቂም ከያዙ መርዘኛ የትግሬ የጦር  መኮንኖች የበለጠ አይገኝም። እናም የትግሬ መኮንኖች ጎጃም ገብተው የበቀል ሱሳቸውን እንደጉድ እየተወጡት ነው።

"…እውነተኛው፣ ትክክለኛው የጎጃም ዐማራ እኔ ጎጃም ገብቼ በድፍረት መረጃ እስክነግረው ድረስ ስለ ዐማራ ፋኖ በጎጃም አንዳችም መረጃ አልነበረውም። በፌክ ሰበር ዜና አደንዝዘውት ምንም መረጃ አልነበረውም። ኦሮሙማው የትግሬ የጦር መሪዎችን በብዛት ያሰማራው የጦር መሪዎቹ ጨፍጭፈው፣ ጨፍጭፈው እንኳ በድንገት ቢማረኩ እንደማይገደሉ ስለሚያውቅ ነው። በሸዋ በእነ መከታው እና በጎጃም በእነ አስረስ መዓረይ የሚማረክ የጦር ጀነራል ይሁን ኮሎኔል ተራ ወታደርም ቢሆን የተለየ እንክብካቤ ስለሚያገኝ የኦሮሙማው መከላከያ ጎጃም ገብቶ እንደ መጀመሪያው እነ ዝናቡ ጦሩን ይመሩ በነበረበት ዘመን እንደነበረው ጊዜ አይፈራም። አይሰጋም። የዐማራ ፋኖ በጎጃም ለትግሬና ለኦሮሞ ምርኮኞች የተለየ ፍቅርና እንክብካቤ ስለሚያደርግ አይፈሩም። አይሰጉም። የእነ አርበኛ ዘመነ ካሤ ድርጅት በዚህ በኩል ምስጉን ነው። የትግሬ የጦር መኮንኖች ፈትቶ መቀሌ ድረስ ተንከባክቦ የሚሸኝ ነው። በሰከላ ንጹሐንን ሲጨፈጭፍ የቆየውን ኮሎኔል ያሬድ ኪሮስን የጎጃም ዐማራ ሴት እያቀረቡ ሲያዘሙቱት፣ የሽርሙ*ና አመል ሱሱን ሲያረኩለት፣ ጫትና ቢራ ውስኪም እያቀረቡ፣ ሲጋራና …👇① ✍✍✍


መልካም…

"…ርእሰ አንቀጹ በሚገባ ቀምሜ አዘጋጅቼዋለሁ። አንዳንዶች በመዝገየቴ ጎጃም ገብቼ የታገትኩ መስሏቸው በውስጥ መስመር ሁላ ሲወተውቱኝ እያየሁ ነው። ሱስ ነው የሆንኩት አይደል?

"…ከርእሰ አንቀጹ በፊት እነዚህን ቪዲዮዎች ለ30 ደቂቃ ደግማችሁ እዩአቸው። ለጎጃም ዐማራ የተደገሰ ከፍተኛ የጥፋት ድግስ ለማክሸፍ ስል ስለሆነ የምደክመው ደጋግማችሁ እየተመለከታችሁ ጠብቁኝ።

"…ሸንጎ ሁለት አባት አለው አንዱ ሲሞትበት በአንዱ ነው የሚያለቅስ። ሸንጎ ሁለት ካርድ ነው ያለው ሲቀዘቅዘው፣ ሲበርደው ዐማራ ዐማራነት የሚጨወትበት፣ ሲሞቀው ደግሞ አገው ሸንጎነትን የሚጫወትበት። ዐማራ ግን ምስኪን አንድ ካርታ ብቻ ነው የሚስበው። ሲሞቀውም ዐማራ ነው፣ ሲበርደውም ዐማራ ነው።

"…የምትንጫጩ ሥርዓት ያዙ፣ በድብቅ የምታሰለጥኑትን ፀረ ዐማራ ጦር ይፋ አወጣዋለሁ። የበሰበሰ ዝናብ አይፈራም፣ የጎጃም ዐማራ የተሽኮረመመበትን ጉዳይ እኔ አፍረጠርጠዋለሁ። የጎጃም ዐማራና አገው ከሰማኝ ሰማኝ፣ ካልሰማኝ ለደንታው ነው። እኔ ግን መናገሬን አልተውም።

"…ርእሰ አንቀጹ ከ30 ደቂቃ በኋላ እለጥፈዋለሁ። ከርእሰ አንቀጼ ጋር ስለሚሄድ ዐማራ የተደገሰልህን የጥፋት ድግስ በጊዜ ታከሽፈው ዘንድ እማፀንሃለሁ። ባትሰማኝ እኔ ዕዳ በደል የለብኝም። መሬት ስሚ፣ ሰማይም አድምጪ፣ ቤተ ክርስቲያንም መስክሪ። ውርድ ከራሴ።

• አላችሁ አይደል…?

33.3k 1 15 83 1.3k

መልካም…

"…ጮቄ ተራራ ነው የምገኝ። ሰሞኑን የዘመዴ ሚዲያን 300 የጌዴዎን ሠራዊት በመመዝገብ፣ በማደራጀቱ ጉዳይ ላይ ወደ ራየን ወንዝ ማዶ ተመልሼ አድካሚ ሥራ ላይ ስለነበርኩ የጎጃም ጉብኝትና ምርመራዬን ገታ አድርጌው ነበር። እናም ሁሉንም ተግባር ዕቅዴን በስኬት ስላጠናቀቅኩ አሁን ወደ ምስጢር ገላጯ ጮቄ ተራራ በሰላም ተመልሻለሁ።

• የከረመ፣ ጠንከር መረር፣ ዘለግም ያለ የጎጃም ምርመራዬን አሀጀን ልዘረግፈው ነኝ። ጎጃም የጎጃም ዐማራ ደፈር ብሎ በነገሩ ካልገባበትና በጊዜ መስመር ካላስያዘው ከፊቱ የሚጠብቀው ከባድ አደጋ ነው። መዝግቡልኝ።

"…አለባብሰው ቢያርሱ በዓረም ይመለሱ ነውና አስቡበት። እኔ መመክሬን፣ ሓሳብ መስጠቴን አልተውም። አጠቃላይ የዐማራ ፋኖ ትግል ጎጃም ውስጥ በፅኑ ታሟል። የዓድዋው የአይተ አቦይ ስብሃት ነጋን የመሰለ የጎጃም ዐማራን አንቆ የያዘው ትብታብ በድፍረት በጊዜ ካልተበጣጠሰ የጎጃም ዐማራ ተወደደም ተጠላም ከባድ ዋጋ ይከፍላል።

"…ይሄ ሟርት አይደለም። ዐውቃለሁ የውሸት፣ የፌክ ተደመሰሱ፣ ተማረኩ፣ አለቀለት፣ አበቃለት በሚል የቁጩ የአገው ሸኔ ሰበር ዜና ጆሮውን ሲያጠግብ የኖረ እኔ አሁን የምናገረው ቋቅ ሊለው ይችላል። መድኃኒት ይመርራል፣ ለመዳን መፍትሄው መራሩን መድኃኒት ጨክኖ መዋጥ ነው። ጎጃምን ያህል የምሁራን ሀገር እንዴት በአዝማሪ ይወከላል? ጉድ እኮ ነው።

"…ረዘም ያለ ጦማር ነው። አንብባችሁ አስተያየት ለመስጠት ትችሉ ዘንድ 3 ሰዓት ያህል ለማንበቢያ ጊዜ እሰጣችኋለሁ። ከዚያ እናንተ ደግሞ በጨዋ ደንብ ሓሳባችሁን ትሰጡ ዘንድ የአስተያየት መስጫ ሰንዱቁን እከፍትላችኋለሁ። እሺ በሏኣ…? 😂

"…ዘመዴ ነኝ ከጮቄ ተራራ እስከዚያው እነዚህን ድምጾች እየሰማችሁ፣ ፎቶዎቹን እያያችሁ ለመጠበቅ ዝግጁ ናችሁ…?

37.2k 0 9 206 1.4k

"…ሰውም ጊዜውን አያውቅም፤ በክፉ መረብ እንደ ተጠመዱ ዓሣዎች፥ በወጥመድም እንደ ተያዙ ወፎች፥ እንዲሁ የሰው ልጆች በክፉ ጊዜ በድንገት ሲወድቅባቸው ይጠመዳሉ።” መክ 9፥12

• እንደምን አደራችሁ?
• እንደምን አረፈዳችሁ?
• እንደምን ዋላችሁ?
• እንደምን አመሻችሁ?

• መልሱ እግዚአብሔር ይመስገን ብቻ ‼

42.9k 0 5 1.8k 1.7k

በሰላም ገብቻለሁ…

"…የዘንዶውን ራስ እቀጠቅጥ ዘንድ ቅድም ከራየን ወንዝ ተነሥቼ ኢትዮጵያ ሰሜን ጎንደር በሰላም ገብቻለሁ። ራስ ደጀን አካባቢ ትንሽ ዞር ዞር አረፍም ብዬ ወደ ተቀደሰው ተራራ ወደ አምሳለ ገነቱ ጎጃም ጮቄ ተራራ ከእኩለ ሌሊት በፊት እደርሳለሁ።

"…እስከዚያው 300 ሊሞላ 13 ሰው ብቻ የቀረውን የጌዲዮን ሠራዊት ወደ ለብቻቸው ወዳዘጋጀሁላቸው ወደ ቴሌግራም ግሩፓቸው ማስገባቱን በጨረቃ ብርሃን እያስገባሁ አመሻለሁ። አነጋለሁ። ነገ ከምስጋና በኋላ ነቅነቅ፣ ወዝወዝ የሚያደርገንን ርእሰ አንቀጽ አዘጋጅቼ ጀባ እላችኋለሁ።

• ዘመዴ ነኝ የደመና ጋላቢ ልጅ ከጮቄ ተራራ።

46.5k 1 9 65 1.9k

መልካም

"…ይሄን 18 ሺ ሰው አንብቦት 25 ፍሬ ሰዎች ጓ ብስጭት ያሉበትን የዛሬውን ርእሰ አንቀጽ ወደ ማዳበሩ እንሄዳለን። መቼም ከእኔ ርእሳ አንቀጽ በላይ በእኔ ቤት የሚጻፉ አስተያየቶች የሚናፈቁ ሆነዋል። ባለጌ፣ ባለጌው፣ ስድአደጉ ተጠርጎ ሲወጣ እነ ኢድሪስን የመሰሉ ባለ ለምለም ብዕር ባለቤቶች በቤቱ ናኝተውበታል። ማይም ኮተታም ተሳዳቢውን ወዲያ ጥለን ሓሳባቸውን በተገቢው በጨዋ መንገድ ለሚሸጡ የተመቸ ዘመን ነው የመጣው። ተቃውሞም እኮ ዓይነት አለው። አይደለም እንዴ። አንጀት አርስ ባለ ለምለም ብዕር ባለቤቶችንም አበረታታለሁ።

"…እየመጣ ያለውን ሚዲያ በተመለከተ እየመዘገብኩ ባለሁት የሠራዊተ ጌዴዎን የዘመዴ ሚዲያ የመጀመሪያዎቹ 300 ምርጥ ሠራዊት ውስጥ መስራች አባል ሆኖ ለመመዝገብ እስከ ትናንትናው ዕለት ድረስ አሜሪካ እንደ ኦሎምፒኩ 170 ሰዎች እየመራች ሲሆን፣ ካናዳ በ28፣ እንግሊዝ በ17 ይከተላሉ፣ በአጠቃላይ እስከአሁን ደጋግሜ ቆጠርኩት ስልካቸው የሚታይና የሚሠራ እርግጠኛ የሆንኩባቸው 279 ሰዎች ተመዝግበዋል። የሚቀረው በትክል 21 ሰዎች ብቻ ናቸው ማለት ነው። 18 የተባለው ስቀዠብር ነው።

"…ምሽቱን ደመና እየጋለብኩ አስተያየቶቻችሁን እየኮሞኮምኩ ከራየን ወንዝ ዳርቻ ተነሥቼ ወደ ጮቄ ተራራዬ እመለሳለሁ። እጋግረው ዘንድ ሊጡ ቦክቶ ኩፍ ብሎ እየጠበቀኝ ነው። የነገ ርእሰ አንቀጻችን ከተለመደው ስፍራ ከጮቄ ተራራ ይሆናል ማለት ነው። 

• በሉ ዳይ እግረ መንገዳችሁን ለሠራዊተ ጌዴዎን የዘመዴ ነጭ ነጯን ሚዲያ መሥራች አባልነት እየተመዘገባችሁ የተለመደውን ነጭ ነጯን አስተያየታችሁን በጨዋ ደንብ ማስኮምኮም ጀምሩ።

• 1…2…3… ✍✍✍

48.1k 1 10 171 1.5k

👆⑤✍✍✍ …

~ ሃሎ እገልዬ ዘመዴ ነኝ ደኅና ነህ?

• ዘ መ ዴ እንደ ምን አለህ እግዚአብሔር ይመስገን።

~ ለሆነች ጉዳይ ፈልጌህ ነበር?

• ምን ጉዳይ ዘመዴ?

~ለዘመዴ ሚዲያ ጉዳይ፣ ነጭ ነጯን በአየር ላይ ለመመለስ ለሚዲያው የቦርድ አባል እንድትሆንልኝ ፈልጌ ነበር።

• በደስታ ዘመዴ። ፈቃደኛ ነኝ።

~ ክብረት ይስጥልኝ። ደኅና ይሁኑ።

"…እኔ ያዘጋጀሁት በሓሳቤ 12 ሰው። ሁለት ከእስራኤል፣ አንድ ከእንግሊዝ፣ ከጀርመንም፣ ከካናዳም አዘጋጅቼ ነበር። የተፈለገው 5 ሰው ሆነ። በቃ። አምስቱንም አንድ ምሽት በኋትስአፕ ስልክ ደውዬ አገናኘኋቸው፣ ተዋወቁ፣ ተነጋገሩ። አለቀ። እስከአሁን እነሱ በቴሌግራም ግሩፖቻቸው ላይ የደረሱበትን ሲያወጉ ከማየት በቀር ስብሰባም ድጋሚ አላደረግንም። በመቀጠል ለሚዲያው ቋሚ አባል ብቻ ሳይሆን በመጀመሪያው ለሚዲያው ማስጀመሪያ ደማቸውን የሚሰጡ 300 ሰዎች አስፈለጉኝ። በአብዮት ጠባቂ፣ በደንብ አስከባሪ፣ በፎሊስ ሳይሆን ቀጭን ጥሪ ብቻ ነው በቴሌግራሜ ያስተላለፍኩት። "ነጭ ነጯን ከዘመዴ ጋር ወደ አየር ይመለስ ዘንድ የምትፈልጉ፣ 300 ነፍስ ያላችሁ፣ እስክንድር ተነካብን፣ አስረስ ተገመገመብን፣ ደመቀ ተነቆረብን፣ ሙሃባው፣ ዘመነ፣ ጌታ አስራደ፣ ተተቹብን፣ እነ ሄኖክ ጀንደረባው፣ እነ አክሊል ኮልኮሌውን ኮለኮልብን የማትሉ፣ የእኔን ሰው አትተች፣ ሌላውን ግን ውቀጥ የማትሉ 300 ሰዎች የእውነት አፍቃሪ ወዳጆችም በሰልፍ ኑ ብዬ ጥሪ አቀረብኩ። አሁን እኔ ይሄን እየጻፍኩ ሞልቶም ሊሆን ይችላል 300 ውስጥ ለመግባት አንዳንድ ሺ የአማሪካም የካናዳም ዶላር የያዙ፣ 500፣ 400፣ 300 ም የያዙ ፓውንድ ነሽ፣ ዩሮ የተሸከሙ ሰዎች ተመዝገበው ቁጭ ብለዋል። እነዚህ አስጀማሪዎች ናቸው። ተጠባባቂው ሠራዊት እንዳለ ነው። እንዳለ ተቀምጧል።

"…ሚዲያው ሲከፈት እናት ቤተ ክርስቲያን ያሳደገቻቸው ባለሙያ ጋዜጠኞች፣ በሰንበት ትምህርት ቤት አልፈው ቦታ ዕድል ያጡ ሁሉ፣ የተሸፈኑ፣ የተጋረዱ ዕንቁዎች አዋራቸው ተገልጦ ራሳቸውን ለዓለሙ ሁሉ ያሳዩበታል። በሚዲያው ልክ እንደ መንግሥቱ ኃይለማርያም እንደ ደርጉ ጊዜ መሠረተ ትምህርት ሀ ሁ ሂ ሃ ሄ ህ ሆ ብለን ፊደል ነው የምናስቆጥርበት። ሕፃናት ላይ እንሠራለን። የግዕዝ ትምህርት በሊቃውንቱ፣ ውዳሴ ማርያም ጀምሮ እስከ ዳዊት ድረስ ይቀጸልበታል። ስንክሳር በየዕለቱ ይነበብበታል፣ መሃረነ አብ አይቋረጥም። ጠዋት ጠዋት የኪዳን ጸሎት እንዳለ ነው። ጥንታውያን ገዳማትና አድባራት በጎደለው በኩል እንሞላላቸዋለን፣ በፈረሰው በኩል እንቆምላቸዋለን። በቤቱ ልማት ይሆናል። እንደ ዜጋ ስለ ሀገራችን፣ እንደ አማኝ ስለ ሃይማኖታችን ፕላት ፎርሙን የእውነት፣ የሃቅ መንሸራሸሪያ፣ የኮሶ፣ የመተሬ፣ የእንቆቆ፣ የቃሪያ በበርበሬ መሸጫ እናደርገዋለን፣ በርበሬ እያጠንን፣ በሳማ እየለበለብን ባለተለመደ መንገድ ለኢትዮጵያ የምንገለጠው። ይሄን አስመሳይ፣ አድርባይ፣ ባህል፣ እምነት እንዳይኖረው ተደርጎ ገንፎ ቄጤማ፣ ደንቆሮና ማይም እንዲሆን የተፈረደበትን ቲክቶካም፣ ሱሪውን ዝቅ አድርጎ የመቀመጫውን አንጓ እያሳየ፣ እንደ ፍየል፣ እንደ ገመሬ ዝንጀሮ መቀመጫውን እያሳየ የሚሄድ፣ ዕድሜህ ስንት ነው ሲባል 55 ኪሎ ነኝ የሚል፣ በሴራ የደነቆረን ትውልድ በነፍስ ነው የምንደርስለት። በቤተ መቅደስ፣ በቤተ መስጂድ፣ በቤተ አዳራሽ የተሰገሰጉትን ሃይማኖት አሰዳቢ፣ ፌክ የበግ ለምድ የለበሱትን ተኩላ ቀበሮዎች እንፋለምበታለን። ዘር፣ ቀለም፣ ሃይማኖት ሳንለይ ፀረ ሕዝብ፣ ፀረ ሰው፣ ፀረ ሀገር የሆኑትን በሙሉ ያለ ምህረት፣ ያለ ፍርሃት ያለምንም ዲፕሎማሲ በጨበጣ እንፋለምበታለን።

"…ሠራዊተ ጌዴዎኖች ተከታተሉኝ። 18 ቶቹ ቀሪዎቹም ተመዝገቡ። ግሩፑን ዛሬ አቋቁመዋለሁ። ለብቻ የሚመክር ግሩፕ ነው የማቋቁመው። ይሄ እንዴት ሆነ? ለምን ሆነ? ብለህ የምትበሳጭ ካለህ በረኪና ጠጣበት፣ አዎ ቀዝቀዝ እንዲያረግልህ፣ ከብስጭቱ እንዲያበርድህ እኔ ፔጅ ላይ እየገባህ በኢሞጂ ጓ ብው ከምትል የአይጥ መርዝ ጥሩ ነው እሱን ጎንጨት በልበት። አታስቆመኝ አባው። የኢትዮጵያንም የዐማራንም ትንሣኤ እናበሥራለን። ቃሌ ቃል ነው። የዐማራን ቅዱስ ትግል እንደ መዳኛዬ ቆጥሬ ተቀብዬአለሁ። ሰማይ ዝቅ ምድር ከፍ ቢል ፍንክች ንቅንቅ የሚያደርገኝ የለም። ሃይማኖቴ ሆኗል። እኔ ደግሞ ሐዋርያው። የዐማራን ትግል መናፍቃንን በአፍም በመጣፍም እፋለማቸዋለሁ። አከተመ። የፈለገህን በል አታስቆመኝም። ሾተላዩን በሙሉ እብድ እብድ እየተጫወትኩ ነቃቅዬ እጥለዋለሁ። እንደ ማስቲሽ በዐማራ ትግል ላይ የተጣበቀውን መሰሪ ሁላ ፈቅፍቄ ፈቅፍቄ አራግፈዋለሁ። የቋንጃ እከክ ነው የምሆንበት። እኚኚ ብዬ ነው የምጣበቅበት። ንዝንዝ አድርጌ ነው የምነቅለው። ምንም አባክ አታመጣም። አለቀ።

"…ሓሳብ ያላችሁ ቆይቼ የአስተያየት መስጫ ሰንዱቁን እከፍትላችኋለሁ። ለዚህ ትልቅ ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ የተጠቀምኩት የእግዚአብሔርን ጥበቃ፣ የእመቤታችንን አማላጅነት፣ የቅዱሳኑን ሁሉ ጸሎት ነው። ለሥራው አንድ ሳምሰንግ ስልክ፣ በቤቴ ዋይፋይ፣ አንዲት አመልካች ጣቴን ብቻ ነው። ልሥራ ካልክ፣ እግዚአብሔር ከፈቀደ እንዲህም ይሠራል። ለገተቶች እያስተማርኳችሁ ነው። ሰምተሃል።

…ዘመዴ ሚዲያ እየመጣ ነው።

• ድል ለዐማራ ፋኖ…!
• ድል ለተገፋው ለዐማራ ሕዝብ…!

~ • ይደፈርሳል… ግን ደግሞ ይጠራል…✊

•••

ሻሎም…!  ሰላም…!

ዘመድኩን በቀለ ነኝ።
አሸበርቲው/አስነቀልቲው
ጥር 27/2017 ዓም
ከራየን ወንዝ ማዶ።


👆④ ✍✍✍ …አልሞክርም። ወዳጄ ነው፣ ጓደኛዬ ነው ብሎ ነገር እኔጋር አይሠራም። እውነትን በውለታ አልለውጣትም። አልሸቅጣትም። በማኅበራዊ ሚዲያው እንዲከተለኝ እንጂ የምከተለው ሰው የለም። እንዲሰማኝ እንጂ የምሰማው ሰው የለም። እኔ በሱቄ የራሴን ምርት ነው የምሸጠው። ከከሰርኩ እኔ ልክሰር ማንም አያገባውም። በቶሎ እከብር ብዬ የሰው ጤና በሚጎዳ የሐሰት ንግድ ላይ አልሳተፋትም። እንዲህች ብዬ ሀብታም ሆኜ ለመታየት ለመገኘትም ስል በቅቤ ላይ ሙዝ፣ በበርበሬ ላይ ቀይ የሸክላ አፈር፣ በማር ላይ ስኳር፣ በጤፍ ላይ አሸዋ፣ በከሰል ጆንያ ላይ የኮረት ድንጋይ፣ በእንጀራ ላይ ጂፕሰም፣ የአህያና የውሻ፣ የጅብም ሥጋ የበግ፣ የፍየልና የበሬ ነው ብዬ አልሸጥም። ትርፍ እንደሌለው ባውቅም እውነትን ብቻ። እውነትን አልኩህ። ወይ ንቅንቅ።

"…ዘመዴ የእስክንድር ነጋን መንጋ ስለተጋፈጠ፣ ከግንቦቴ፣ ከባልደራስና ከግንባሩ ሰዎች ከደጋፊዎቻቸውም ጋር ስለተቧቀሰ። ሸዋ ገብቶ ከነመከታው፣ ወሎ ገብቶ ከነ ሙሀባው፣ ጎንደር ገብቶ ከስኳዱ፣ ወልቃይት ገብቶ ከኮሎኔሉ ጋር ስለተዋገረ፣ ከምህረተ አብ ደጋፊዎች፣ ከጃንደረባው ሄኖክ ደቀ መዛሙርቶች፣ ከቲክቶሎጂው ሊቅ ከግብጽ ቅጠረኛው ከአክሊል ወፈፌዎች ጋር ስለተነቋቆረ አይሳካለትም። አይሆንለትም። በተለይ አሁን ደግሞ ገንዘብ፣ አፍ፣ አክቲቪስትና ጋዜጠኛም ሚዲያም ካላቸው ከጎጃሞቹ ሸንጎዎች ጋር እየተፈሳፈሰ ስለሆነ ወፍ የለም ያሉ ነበሩ። አውነት አላቸው። አንድ እኔ ብቻዬን በአንዲት የእጅ ስልኬ ብቻ በሚጻፍ ጦማር የአረመኔው የኦሮሙማ አገዛዝ፣ የወዩና የብአዴን የኦነግም መንጋ ሳይጨመር ሁሉንም ድባቅ ስመታቸው ከመደነቅ፣ በፈጣሪ ሥራ ከመደመም ይልቅ በሰው ሰውኛ እያሰቡ ይሰጋሉ። ስለእኔም ይጨነቃሉ። አዪዪ ሲያልቅ አያምር አሁንስ ዘመዴ እገሌን ነካው፣ እነ እገሌን ተሳፈጠ አለቀለት ብለው ተስፋም ይቆርጣሉ። እኔ ግን የያዝኩት እውነት ዐውቀዋለሁ። አልሰጋም አልፈራምም። አውነት ማለት ቀራንዮ ላይ ተሰቅሎ፣ ወደ መቃብር ወርዶ፣ ድንጋዩን አንከባልሉልኝ፣ መግነዙን ፍቱልኝ ሳይል የታተመ መቃብር ፈንቅሎ ከፍቶ የተገለጠ፣ ሞት ቀብሮ የማያጠፋው እንደሆነ አይረዱም። እውነት ይሰቀላል፣ ይገደላል፣ መቃብር ይወርዳል። ነገር ግን በክብር ይነሣል። እውነት እግዚአብሔር ነው። እውነትን አግቡ፣ ውደዱ፣ አፍቅሩም፣ እንዳትፋቱም።

"…በዚህ መሃል ነው የዘመዴን ሚዲያ አየር ላይ ለማምጣት ወደ አደባባይ የወጣሁት። 32 ሺ መንጋ ይዤ አይደለም ለሰልፍ የወጣሁት። 22 ሺ ፈሪ፣ ድንጉጥ፣ አስመሳይ፣ በትዳሩ፣ በኑሮው አርቴፊሻል የሆነ ሜካፓም ሠልፈኞችን አይደለም ይዤ ለመገለጥ የፈለግኩት። ሰው ሰው ነው። እኔ አንድም ቀን ይለዩኛል ብዬ አስቤ የማላውቃቸው ሰዎች ጥርቅም አድርገውኝ ታዝቤአቸው ዐውቃለሁ። ይሄ የሚገጥም ነው። 10,700 የውሻ ጠባይ ያላቸው፣ የተፉትን የሚልሱ፣ ግብረ ገብ፣ ኤቲክስ የምትሉት ነገር የሌላቸውን ስግብግቦች ይዤ አይደለም ለሰልፍ የወጣሁት። እኔ የእውነት ወዳጆች፣ አፍቃሪዎች፣ ተመሳሳይ ላባና ክንፍ ያለንን ሰዎች ነው በባትሪ የፈለግኩት። ጥሪም ያቀረብኩት በአደባባይ ነው። በኃጢአት፣ በበደል ገንዘብ ያካበቱ ማጅራት መቺዎችን አይደለም የፈለግሁት። በላባቸው፣ በወዛቸው በሃቅ ጎዳና ላይ ላሉቱ ነው ጥሪ ያቀረብኩት። ሚዲያ ላቋቁም ነኝ ተከተሉኝ አልኩ። የምፈልገውንም የሰው ብዛት ተናገርኩ። በቃ የሰሙኝ ጥሪዬንም ሰምተው ወደ እኔ ጎረፉ። 300 ሠራዊተ ጌዴዎን ዘ ኢትዮጵያ አባላትን ምልመላ ጀመርኩ። አሁን 300 ልሞላ 18 ሰው ብቻ ነው የቀረኝ። እሱም ዛሬ ወደ ጎጃም ወደ ጮቄ ተራራዬ ከመመለሴ በፊት የሚሞላ ይመስለኛል።

"…የሚዲያ ፈቃዱን ያወጡት በሥላሴ ስም ሦስት፣ ሚዲያውን በቦርድ አባልነት ይመሩ ዘንድ የተመረጡት አምስት አእማድ የሆኑ ወንድም እህቶች ናቸው። የሳታላይት ቴሌቭዥኑን ከውልደቱ እስከ እድገቱ በገንዘባቸው፣ በእውቀታቸውና በጎልበታቸው የሚያገለግሉት 300 ቋሚ፣ 3000 ሺ አጋር፣ አጋዥ ኢትዮጵያውያን በተጠንቀቅ ላይ ናቸው። 300 ዎቹ ተመራጭ የጌዴዎን ሠራዊቶች ከፍ ሲል አንድ ሺ፣ ከዚያም በላይ፣ ዝቅ ሲል ደግሞ መቶና ሁለት መቶ 300 ም ዶላር ይዘው አዋጥተው የሳታላይት ቴሌቭዥኑን የዓመትና የሁለት ዓመት የአየር ላይ ቆይታውን በመክፈል አረጋግጠው ሥራ የሚያስጀምሩ ናቸው። አሁን የባንክ አካውንት፣ የዜልና የካሽአፕ ቁጥርም እየተዘጋጀ ነው። ሁሉም እንዳለቀ ይለጠፍላችኋል። ከ300 ዎቹ ውጪም ሚልዮኖች ይሳተፉበታል። እንደ እኔ ከእውነት ጋር ሙጭጭ ያሉ ሁሉ አብረውኝ እስከ ቀራኒዮ ድረስ ሽር እልም ነው። ከአውቶቡሱ ላይ ከፌርማታው መውረድ ብሎ ነገር የለም። ከ300 ው የሚያፈነግጥ ሲገኝ ከተጠባባቂው እየተካን ወደፊት ነው አለቀ። አስገድጄ ያመጣሁት፣ ኪሱ ገብቼ የገፈፍኩት የለም። ወዶና ፈቅዶ ነው የመጣው አለቀ።

"…ሌላም ነገር ላንሣ። አንድ ድርጅት ለማቋቋም የምታዩትን መከራ አስታውሱ። ሰው ፍለጋ። ስብሰባ፣ አበል፣ ብድር ፍለጋ፣ የኢንቬስተር፣ የለጋሽ ባለሀብቶችን ቤት ለማንኳኳት መኳተኑ፣ የስልክ ወጪውን፣ የቢሮ ኪራዩንም ሁሉ አስታውሱ። እገሌን እንያዘው፣ እገሌን እናምጣው፣ አምባሳደር እናድርገው፣ ከዚያ ደግሞ ቲክቶከሮችን፣ የማስታወቂያ ሠራተኞችን ፍለጋ፣ በሰበር ዜና በቴሌቭዥን፣ በታዋቂ ጦማርያን "እገሌ ሚዲያ ሊመጣ ነው፣ እየመጣ ነው" ወከባው፣ ግርግሩን ሁሉ አስታውሱ፣ ከዚያ በፌስቡክ፣ በዩቲዩብ፣ በቴሌግራም፣ በኢንስታግራም፣ በቲክቶክ፣ በቴሌቭዥንና ራዲዮ ሁሉ ሞዴላ ሞዴሎች፣ ታዋቂ አርቲስቶች፣ ታዋቂ ሰዎች ምስክርነት ሰጥተውት፣ ዛር ወጥቶ ተንቀጥቅጦ ነው ሚዲያም ተቋም የሚመሰረተው። የዐማራ ማኅበራት፣ የትግሬና ማኅበራት ተለምነው፣ ደጅ ተጠንቶ ነው የሚመሠረተው። ጎፈንድሚው፣ ጨረታውን ሁሉ አስታውሱ። እኔ ጋ ግን ወፍ። ወፍ የለም አልኩህ።👇④ ✍✍✍


👆③✍✍✍ …ስለሌለው ብዙ ነገር የሚያጣም ሰው አለ። ሰው የሚያጣው ደሀ ብቻ አይደለም። በሽተኛ ብቻ አይደለም። ህመምተኛ ብቻ አይደለም። ዲግሪ፣ ዶክትሬት፣ ኢንቨስተር፣ ውብ፣ አትሌት፣ አርቲስት፣ ሚንስተር ሆኖም ሰው የሚታጣበት ጊዜ አለ። ሰው የለኝም አለው ህመምተኛው ለጌታ። መድኃኒት የሆነ ሰው ይስጣችሁ። አሜን በሉ።

"…የ30 ቤቱ ወጣት ውቡ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ ከእርሱም ጋር ያሉት ጎበዛዝቱ ሐዋርያቱ አንጠልጥለው ውኃው ውስጥ እንዲከቱት ጠብቆም ሊሆን ይችላል ህመምተኛው፣ በሽተኛው ሰውዬ። ወይ ደግሞ እንዴዴኤኤ ይሄን ሰው የዛሬ ዓመት፣ ስምንት ዓመት፣ አስራ ዘጠኝ ዓመት፣ ሠላሳ ሁለት ዓመት፣ ሠላሳ ሰባት ዓመት እዚሁ ጋር እዚሁ አልጋው ላይ ተኝቼ አይቼው ነበር እያሉ እንደሚጠይቁት እንደ አንዳንድ ሰዎችም መስሎት ሊሆን ይችላል። የስንቱን የድኅነት፣ የፈውስ ታሪክ እያየ እሱ ሰው ስለሌለው ብቻ መዳን አቅቶት የሚማቅቅ ሰው። አያሳዝንም በማርያም። ዛሬ ግን ከፊቱ የቆመው እግዚአብሔር ወልድ ነው። ወልደ አብ ወልደ ማርያም። ከሦስቱ አካል አንዱ አካል። ዓለማትን በቃሉ የፈጠረ የእግዚአብሔር ቃሉ ወልድ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ከፊቱ የቆመው። እናም ተናገረ ጌታ። "ኢየሱስ፡— ተነሣና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ፡ አለው።" አለቀ። የጠበሉ ጌታ አዘዘ፣ ተናገረ። አስቀድሞ በዘፍጥረት ብርሃን ይሁን ብሎ ቃል አውጥቶ ብርሃናትን፣ ሰማይና ምድርን፣ ፍጥረታትን ሁሉ የፈጠረው ጌታ አሁን ደግሞ 38 ዓመት ሙሉ በሰው እጦት ምክንያት ድህነተ ሥጋ ያጣውን ምስኪን ሰው ራሱ ከዙፋኑ ወርዶ መጥቶ ከፊቱም ቆሞ "ተነሣና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ፡ አለው። 38 ዓመት አልጋ ላይ የተኛን ሰው አልጋህን ተሸከም ሊል የሚችለው እግዚአብሔር ብቻ ነው። ቆይ ወገቡ ይጽና፣ ሙቅና ቅልጥም በልቶ ይጠገን፣ ይጠንክር እንጂ፣ የዲስክ መንሸራተት ቢገጥመውስ ሊል የሚችለው ሰው ብቻ ነው። እግዚአብሔር ግን ሲሠራ ሠራ ነው ትክክል ሆኖ ነው የሚሠራው" በቃ አዘዘው። መጽሐፍ ቅዱስ ምን ይለናል "ወዲያውም ሰውዬው ዳነ አልጋውንም ተሸክሞ ሄደ።" አለቀ።  ፋይሉ ተዘግቷል። ወደ መዝገብ ቤት። ጌታ እኮ ነው።

"…የዛሬ ዓመት አካባቢ ይመስለኛል ዘመዴ ይለኛል አንድ ዲያቆን። አቤት እለዋለሁ። ዲቪ ደረሰኝ። እኔ ገጠር ነው የምኖር። ቤተሰቦቼም፣ ዘመዶቼም ገጠር ነው ያሉት። አማሪካ ዘመድ የለኝም። ድሆች ነነ። ዲቪው ደርሶኝ ሰው ግን አጣሁ። በትምህርቴም ጥሩ ነኝ። ዲቪ እንደደረሰኝ የሰሙ ብዙ ሰዎች አግብተንህ እንሂድ፣ እህቴን አግብተህ ና የሚሉኝ በዙ ይለኛል። ታዲያ እላለሁ በልቤ አግብቶ አይሄድም እኔ ጋር ምን አለፋደደው እላለሁ። ታዲያ ለምን አግብተህ አትሄድም ብዬ ጠየቅኩት። መለሰልኝም። "…አሃ ክህነቴን ማስቀጠል፣ ድንግልዬን መጠበቅ እፈልጋለሁኣ!  ወንድምዓለም አንተ ባታውቀኝም አታውቀኝም እባክህ እርዳኝ። ክህነቴን አስጠብቅልኝ። ካልሆነም ይቀራታል እንጂ ክህኔቴንማ አላቆሽሻትም ይልኛል። የአስረዳኝ የዚህ ዓይነት ሺ ጥያቄዎች በየጊዜው ይቀርቡልኝ ዐውቃለሁ። እኔም ለአንዱም መልሼ አላውቅም። የዚህ ሰው ግን ዲቪ ደርሶት "ክህነቴን አላቆሽሻትም" ማለት ቀልቤን ሳበው። እንዲህ የሚል ወጣት ታዳጊ ልጅ ቀልቤን ገዛው። ደወልኩለት። አወራኝ። ጸልይበት ሰው ልፈልግ አልኩት። ወዲያው ለሱሬ ነገርኩት። ሱሬን ተማጸንኩት። ሱሬ ለቀሲስ ንዋይ ነገረው። ቀሲስ ነዋይ ካሳሁንም ለወንድሙ ለቀሲስ ጌትነት ነገረው። እርሱም ስፖንሰር ሆነው። ያ የማላውቀው ልጅም "የከበረች፣ ቅድስት ክህነቱን" ሳያቆሽሽ ጠብቆ ሁሉ ነገር ተከፍሎለት፣ ወጪም ተችሎት አሜሪካ በሰላም ገባ። አሁን ሁሉ ነገር አልቆለት ቤተ ክርስቲያንን በክብር እያገለገለ ይኖራል። እስከ አሁን የልጁን መልክ አላየሁትም። ቦታውን ከማልጠቅሰው ከአንደኛው ከዐማራ ክልል የመጣ ልጅ ነው። አያችሁ ሰው አንዳንዴ እንዴት መድኃኒት እንደሚሆን። ቀሲስ ነዋይን የቀሲስ ጌትነትን ስልክ ስጠኝ ብዬ ልደውል ከፎከርኩ ይኸው መንፈቅ ሆነ። እባክህ ቀሲስ ጌትነት አንተ ደውልልኝና እኔ ላመስግንህ አባቴ። አያችሁ ጥጋቤን። ጉድ እኮ ነው።

"…ከገንዘብ ይልቅ የሰው ሀብት ያለው ሰው ዕድለኛ ነው። የእግዚአብሔር እውነተኛ ፍቅር የሚገለጠው በሰዎች በኩል ነው። እግዚአብሔር ሲጣላም አርጩሜ አድርጎ ሊቀጣህ ሲፈልግ ሰውን ነው የሚያስነሣው። ዲዮቅልጥያኖስን፣ ፈርኦንን፣ ዮዲት ጉዲትንና ግራኝ አህመድን፣ ደርግንና ወያኔን አቢይ አሕመድን ያስነሣና ዱቄት ያደርገናል። ይዠልጠናል። ሲታረቀንም፣ ከውርደት ሲታደገንም። ከፍ ከፍ ቀና ብለን እንድንሄድ ሲያደርገንም ልክ እንደ እምዬ ምኒልክ ዓይነቶቹን አስነሥቶ ነው የሚያኮራህ የሚያስከብርህ። ሰው ለሰው መድኃኒቱ ነው። ሞቱም መጥፊያውም ነው። ጤና ዕድሜ ሀብት ያለው ሰው ሦስቱም ኑረውት የሰው ሀብት ከሌለው አለቀ። ይሾቃል። ሰው እንዲወድህ ብለህ ጥገኛ አትሁን። ልጥፍ አትሁን። አስመሳይ መስሎ አዳሪ አትሁን። ተለማማጭ፣ ተልመጥማጭም አትሁን፣ አድርባይ፣ እስስትም አትሁን። እንደ ክረምት አየር ፀሐይ ሲሉህ ደመና፣ ዝናብ አትሁን። ሜካፓም አትሁን። አፈ ቅቤ ልበ ጩቤም አትሁን። እወደድ ብለህ ከእውነት አትራቅ፣ አታፈግፍግ። የሚወድህ ሰው ከነ ንፍጥህ፣ ከነ ለሃጭህ ይውደድህ እንጂ አጣጥቦ እንዲስምህ አትፍቀድለት። ፍቅር ንፍጥና ለሃጭን አያይም። ፍቅር ለአፍቃሪው እውር ነው። ካፈቀርክ አፈቀርክ ነው። ያፈቀርከው መልአክ፣ ውብ ጽጌሬዳ፣ ደማቅ ፀሐይ፣ የንጋት ጮራ፣ የሌሊት ጨረቃ መስላ የምትታየው ለአንተ እንጂ ሌላው አይደለም። ምኗን አይቶ ነው የወደዳት? ያፈቀራት? ያገባት? እንዴት ከዚህ መሸጦ ጋር ትኖራለች? መስተፋቅር አስደርጎባት፣ ጠንቋይ ጋር ውሎባት ነው እንጂ፣ ገንዘቡን አይታ ሀብቷን ተመልክቶና ፈልጎ ነው እንጂ ያለ አንዳች ምክንያት እንዲህና እንዲያ አልሆነም እያለ አዳሜ ሲያወራ ይውል ያድር እንጂ ምንም አይፈይድም። ይሄን ግትር፣ ጯሂ፣ ደረቅ እንዴት አገባችው? ይህቺን ክችች ያለች ወይ አትበላ አታስበላ እንዴት አገባት? እያለ አዳሜና ሔዋኔ ከጀርባህ ሲፈተፍት ንቅንቅ የማትለው አንተ በእውነት ያለ ሀሰት ያፈቀርክ፣ እሷም ያፈቀረችህ እንደሆነ ብቻ ነው። ቤተሰብ ተሰብስቦ በቅሎ ናት ፍታት፣ ከዘራችን አይገጥምም ፍቺው ቢል መስሚያችሁ ጥጥ የሚሆነው እናንተ በእውነት ስለ እውነት በሃቅ ከተፋቀራችሁ ብቻ ነው። ሰማይ ዝቅ፣ ምድር ከፍ ቢል በእግዚአብሔር ፍቅር የተባረከ፣ የተጣመረን ሰው ማንም አይለየውም። ፍቅር እስከ መቃብር አለቀ።

"…የእኔም ሀብት ይሄ ይመስለኛል። የሰው ፍቅር ሀብትማ አለኝ። እንደ እኔ በዚህ የከበረ ያለም አይመስለኝ። ብዙዎች በድርቅናዬ ይጠሉኛል፣ በጩኸቴ ይጠየፉኛል፣ በመራር እውነቴ ይቀየሙኛል፣ በግግምናዬ ይበሳጩብኛል። ይሰድቡኛል፣ ይዝቱብኛል፣ ይበሳጩብኛል እያነቡ እስክስታ ነው የምሆንባቸው። ወደድነው ባሉኝ ማግስት፣ ታቦት ይቀረጽለት፣ ብርጌድ ይሰየምለት ባሉኝ ማግስት እሪሪ እንዲሉብኝ ባደርጋቸውም ግን ሲሰድቡኝ ከርመው ስጠፋ ግን እናፍቃቸዋለሁ። እሰይ ጠፋ ተገላገልነው አይሉም። አይናቸውን በጨው ታጥበው መጥተው ይጽፉልኛል። አንተ እኮ ይሄን ይሄን ብታስተካክል በጣም ጥሩ ነበር ብለው መናፈቃቸውን ሳይሰስቱ ይጽፉልኛል። በስድባቸው ከፔጄ የቀስፍኳቸው ሁላ ቆይተው አንተ ልክ ነበርክ ዘመዴ ይሉኛል። ሲሰድቡኝ እንኳ ዘመዴ እያሉ እስከ ዶቃ ማሰሪያዬ የሚያስታጥቁኝ የትየለሌ ናቸው። ከእውነት ሚዛኔ ግን ዝቅ አልላትም። ሰውን ለማስደሰት ብዬ አንዳች የውሸት ቅመም ለማጣፈጫነት ለመጠቀም…👇③ ✍✍✍


👆②✍✍✍ ያስቀምጡሃል። ብዙዎች ገንዘብ በማጣቸው፣ ሰውም ስላጡ እንዴት እንደሚቸገሩ እናያለን። እንመለከታለን።

"…ችሎታው፣ ዕወቀቱ ሳያንሳቸው ገንዘብና ሰው ስለሌላቸው ብቻ ለዓለም ብርሃን የሆነ ዕውቀት ቀብረው በየቤቱ የተቀመጡትን ቤት ይቁጠራቸው። ሰውና ገንዘብ በማጣታቸው ምክንያት ብቻ ህልማቸው የጨነገፈ፣ ክብራቸውንም የሸጡ የትየለሌ ናቸው። በትምህርታቸው ተምረው፣ በሻማ በኩራዝ አጥንተው ፈተና ተፈትነው ስትሬት ኤ የሚያመጡ እህቶችን ካልተኛሁሽ F ነው የማሸክምሽ በሚሉ የሰው ውሻ ዘማዊ ዋልጌ አንዳንድ አረመኔ የመምህራንን ክብርና ዝና በሚያጎድፉ ዋልጌዎች የተሰናከሉ፣ ነጥብ ከሚቀነስብኝ ብለውም ክብራቸውን ያዋረዱ እህቶችን ቤት ይቁጠራቸው። የሥራ ዕድገት ለማግኘት፣ ከሥራ እንዳያባርሯቸው ለልጆቻቸው ሲሉ ከአመዳም፣ ከእከካም የመሥሪያ ቤት አለቃና ሥራ አስኪያጅ ጋር ቋቅ እያላቸው፣ እያስመለሳቸው ክብራቸውን የሚጥሉ እልፍ ናቸው። ባልሠሩት ወንጀል ተከሰው ፍርድቤት ለቀረቡ ባሎቻቸውና ልጆቻቸው ሲሉ "ከተኛሁሽ እለቀዋለሁ፣ እንዲፈታም አደርገዋለሁ" በማለት ስንትና ስንት ንፁሐን፣ ቅዱሳት አንስት ሴቶች ለቤተሰባቸው ሲሉ ከማይፈልጉት ሸታታ፣ ግማታም፣ ቅርናታም፣ ጫማውም፣ አፉም የፈነዳ ሽንትቤት ከመሰለ አረመኔ ቁናሳም ገመድ አፍ ተብታባ ፖሊስ፣ መርማሪ፣ ዐቃቤ ሕግ፣ ዳኛ ወዘተ ጋር ተኝተው ረክሰዋል። በሽታም የሸመቱ ዐውቃለሁ። አዎ አቅም ማጣት እንዲህ ያዋርዳል። የማትፈልገውን አግብታ አስከሬን የመሰለ በድን አግብታ ስሜት ሳይኖራት ለችግሯ ስትል አልጫ የሆነ ትዳር የምትመራ አለች። እንደዚህ የሚኖሩ የትየለሌ ሰዎች አሉ። ይሄን ጦማር የምታነቡም ራሳችሁን እስኪ ጠይቁ። እንዴት ናችሁ…? ሃኣ…?

"…ሰው ለሰው መድኃኒቱም መርዙም ሞቱም ነው። የሚያድን፣ የሚታደግ ሰው አለ። ቀርጥፎ የሚበላህም ሰው አለ። ውለታ ሳይቆጥር፣ በዘር፣ በሃይማኖት፣ በፖለቲካ አመለካከት አንድ ባይሆኑ እንኳ የሰውነት ሚዛኑ ደፍቶ በልጦበት ፍቱን መድኃኒት የሚሆናችሁ ሰው አለ። ቆይ ምን አድርጌለት ነው። ምን አድርጌላት ነው። በዘር፣ በሃይማኖት፣ በሃብት አንገናኝ፣ አንተዋወቅ የምትሉት መድኃኒት የሆነው ሰው የትየለሌ ነው። መድኃኒት የሆነ ሰው ምላሽህን አይጠይቅም። ማነህ ወዴት ነህ አይልም። ችግርህን መፍታቱ ብቻ ያስደስተዋል። እርካታም ይሰጠዋል። አለቀ። የአንተ ችግር ከተፈታ በኋላ ዞር ብሎ አያይህም። ይሄ መድኃኒት የሆነ ሰው ነው። መርዞ፣ ገዳዩን ደግሞ ከላይ አሳይቼአችኋለሁ። አሁን አብዛኛው ሰው የተቸገረው መድኃኒት የሆነ ሰው ማግኘት ላይ ነው። በተለይ በዚህ ዘመን ሰው መድኃኒት የሆነ ሰው ማግኘት ይቸግራል። ከገንዘብ ይልቅ፣ ከመልክ ከውበት ይልቅ፣ ከትምህርት ወረቀት ይልቅ በዚህ ዘመን ሰው ያለው ሰው፣ አምላኩ አብዝቶ የሚወደው ሰው ነው። በተለይ የ4 ተኛ ክፍል ተማሪ ዶክተር ነኝ ብሎ ሀገር በሚመራበት በዚህ ዘመን የተማረ ማግኘት ከባድ ነው። በጣቱ የሚፈርም ነው ዶክተሩን በጥይት የሚገድለው። የማይም፣ የደንቆሮ፣ የአራጆች ዘመን ላይ፣ የከሃዲያን ዘመን ላይ ሰው ማግኘት ከባድ ነው።

"…መጽሐፍ ቅዱስ በዮሐ 5፥7 ላይ "ሰው የለኝም" ብሎ በድፍረት ለራሱ ለጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረን አንድ ሰው ታሪክ ሲተርክ እናያለን። ታሪኩም እንዲህ ነው። "…ከዚህ በኋላ የአይሁድ በዓል ነበረ፥ ኢየሱስም ወደ ኢየሩሳሌም ወጣ። በኢየሩሳሌምም በበጎች በር አጠገብ በዕብራይስጥ ቤተ ሳይዳ የምትባል አንዲት መጠመቂያ ነበረች፤ አምስትም መመላለሻ ነበረባት። በእነዚህ ውስጥ የውኃውን መንቀሳቀስ እየጠበቁ በሽተኞችና ዕውሮች አንካሶችም ሰውነታቸውም የሰለለ ብዙ ሕዝብ ይተኙ ነበር። አንዳንድ ጊዜ የጌታ መልአክ ወደ መጠመቂያይቱ ወርዶ ውኃውን ያናውጥ ነበርና፤ እንግዲህ ከውኃው መናወጥ በኋላ በመጀመሪያ የገባ ከማናቸው ካለበት ደዌ ጤናማ ይሆን ነበር" ይለናል። ወደ ውኃው ወደ መጠመቂያው ቀድሞ የሚገባው ነው የሚድነው። ለመዳን መስፈርቱ ቀድሞ መግባት ነበር። መቼም በሽተኛው አይላወስ፣ አይንቀሳቀስ፣ የሚያንቀሳቅሰው ሰው ነው። ጠንካራ ሰው፣ ብዙ ወዳጅ ያለው ቀድሞ ወደ ውኃው ይገባል ድኖ ይሄዳል። ይሄ ማለት እናንተ ከወር ጀምሮ የደከማችሁበትን፣ ከሌሊት ጀምሮ ውርጭና ብርድ ዝናብም፣ በረዶና ጎርፍ እየወገራችሁ ተራ ይዛችሁ፣ በሰልፍ ነው ብላችሁ ስትጠብቁ፣ ተኝተው፣ ተኳኩለው፣ መኪናቸውን እያሽከረከሩ ወይም በራይድ ተሳፍረው ከኋላችሁ መጥተው እናንተን እዚያው ገትረው ደረማምሰዋችሁ ገብተው ተፈወሰው እንደሚሄዱቱ ማለት ነው። ለሁት ሰው ቅጥር 5 ኪሎ ሜትር ትሰለፋለህ ያልተሰለፈው ቤቱ ሆኖ አንደኛና ሁለተኛ ወጥተው ይቀጠራሉ።

"…እንግዲህ በዚህ ሥፍራ ነው በዚያም ከሠላሳ ስምንት ዓመት ጀምሮ የታመመ አንድ ሰው ነበረ፤ ኢየሱስ ይህን ሰው ተኝቶ ባየ ጊዜ፥ እስከ አሁን ብዙ ዘመን እንዲሁ እንደ ነበረ አውቆ፡— ልትድን ትወዳለህን? አለው የሚለን ወንጌላዊው ዮሐንስ። አስቡት 38 ዓመት እንደ ትኋን መድኃኒቱን እያየ፣ ከጠበሉ ፊትለፊት ተቀምጦ ድኅነት ሲያመልጠው። ማኅበረሰቡ ራስ ወዳድ ስለሆነ እንጂ ሰብሰብ ብለው በኮሚቴም ቢሆን ተነጋግረው እንደው የሚቀጥለው ቅዳሜ ይሄን በሽተኛ፣ ህመምተኛ ወደ ውኃው ወርውረነው ድኖ በሄደ ያለ ሰው አልነበረም። በተኛበት እየተጸዳዳ፣ በተኛበት ትኋን ቅማል እየወረረው፣ ክረምትና በጋ እየተፈራረቀበት እያዩ አንዳቸውም አልረዱትም። እንደ ዘኪ፣ እንደ ቢንያም መቄዶንያው፣ እንደ ሳሌሆሞች፣ እንደ እማማ ዘውዲቱ መሸሻ ከመንገዱ ላይ አንስተው መድኃኒት ለመሆን አልጣሩም። ተመልከቱ 38 ዓመት ሙሉ በሰው ያለመታየት እንዴት እንደሚያበግን? እርስዎ ይሄን ጦማር የሚያነቡ ስንት ዓመት ሆንዎት ሰዎች እያዩዎት ቀላሉን ችግርዎን መፍታት እየተቻላቸው በችግር አልጋ ላይ ከተኙ።

"…ሰውዩም፡—ጌታ ሆይ፥ ውኃው በተናወጠ ጊዜ በመጠመቂያይቱ ውስጥ የሚያኖረኝ ሰው የለኝም ነገር ግን እኔ ስመጣ ሳለሁ ሌላው ቀድሞኝ ይወርዳል፣ ድኖም ወደ ቤቱ ይመለሳል ብሎ የመለሰለት። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። ሰው የለኝም። በዚህ ዘመንም የብዙዎች ጥያቄ ነው። ለአፍታ አይናችሁን ከድናችሁ ሰው ስላልነበራችሁ ብቻ ያመለጣችሁን መልካም ዕድል ሁሉ አስታውሱ። ገንዘብ፣ ሀብት ኖሮት እኮ ሰው…👇②✍✍✍


"ርእሰ አንቀጽ"

"…ቅድምዬ እንደነገርኳችሁ ወደ ጮቄ ተራራዬ ወደ ማረፊያዬ፣ እስከ መስከረም፣ እስከ እንቁጣጣሽ ድረስ ወደ ምቆይበት ወደ ጎዣም ምድር አልተመለስኩም። እዚያው የስደት ሀገሬ በአጎት ሀገር ከራየን ወንዝ ዳር ደክሞኝ እንዳደርኩ ነው ያለሁት። ከባለፈው ቅዳሜ ጀምሮ የዘመዴ ሚዲያን በቅርቡ ዕውን ይሆን ዘንድ እና በአየርም ላይ ይገለጥ ዘንድ ስል ተፍተፍ በትበት ማለት ስለነበረብኝ እዚሁ አውሮጳ ጀረምን ልቆይ ብዬ በመወሰኔ ወደ ጮቄ ተራራ ለመመለስ አልተቻለኝም። ዛሬ ምሽት እመለሳለሁ። ዳመና እየጋለብኩ ነው የምመለሰው። ነገር ግን ከጮቄ ተራራ የቀሩት ወፎቼ ከጎጃም ዐማራ ፋኖ ወፎቼ ጋር እየተናበበ በየሰከንዱ መረጃ መለዋወጣችንን አላቆምንም። ግኑኝነታችንም አልተቋረጠምም። በመንፈስ እዚያው እዚያው ጮቄ ነኝ። ጎጃም ጮቄ ተራራ።

"…ክፉ ጎረቤት ዕቃ ያስገዛል እንዲሉ እኔንም ክፉዎቹ ጠበቃ አስረስ መዓረይና አቶ ግርማ ካሣ በፈጠሩት ያልተቀደሰ ጋብቻ ምክንያት ከምወደውና ስንት ከሆንኩለት ከመረጃ ቴቪ ላይ ነጭ ነጯን ከዘመዴ ጋር የተሰኘውን መርሀ ግብሬን ለጊዜው አቋርጬ በመውጣት በቲክቶክ እና በቴሌግራም ገጼ ብቻ ተወስኜ እቀር መስሏቸው የሸረቡት ሴራ ጭራሽ ሌላ ዕቃ አስገዝቶኝ አረፈው። እኔም በሳታላይት እስክመጣ የዘወትር ተግባሬን ሳላቋርጥ በትጋት በቴሌግራምና በቲክቶክ ቀጥያለሁ። እንዲያውም ከበፊቱ ይልቅ ብሶብኝ ነው ያረፍኩት። ቀላል ጨመርኩኝ እንዴ? ከፍ ብዬም ነው እየበረርኩ ያለሁት። እነ አስረስ እና ግርማ ካሳ ዘመዴ ከሳታላይት እይታ እንደምንም ከወረደ እኛ በምድር ላይ ለምንሸርበው ዐማራን የመቅበር ሴራ እንቅፋት አይሆንብንም። በቲክቶክና በቴሌግራም የሚለፈልፈውና የሚሞነጫጭረውም መሬት ላይ እንደ ሳታላይት ቴቪው ተደራሽ አይሆንም። ስለዚህ እንደምንም ከሳታላይት ቴቪው ይውረድልን ባሉት መሠረት እኔም የቀረበልኝን በሳታላይቱ ላይ የመቆየትና የመውረድ ሁለት ምርጫ "የመውረዱን ምርጫ" አክብቤ ክብሬን እንደጠበቅኩ ክፉ ደጉን ከማንም ሳልነጋገር ሹልክ ብዬ ወርጃለሁ። ለጊዜው ኦሮምቲቲው ግርማ እና አስረስ መዓረይ ጮቤ ቢረግጡም ክፉ ጎረቤት ሆነው የሌለ ዕቃ ነው ያስገዙኝ። እኔ ዘመዴን ያለማወቃቸው ነው የጎዳቸው። የሥላሴ ባርያ የድንግል አሽከር የምለው ለፉገራ፣ ለፉተታ የሚመስለው መንጋ እኮ ለጉድ ነው።

"…ላንቃዬ እስኪሰነጠቅ፣ ጉሮሮዬ እስኪደርቅ፣ ልቤ ዝቅ አስኪል ድረስ ላቤ እንደ ውኃ በጀርባዬ ወርዶ መቀመጫዬን እስኪያርሰው፣ ዋና ገብቼ በውኃ ርሼ፣ ዝናብ እንደወቀጠው ሰው በላቤ በስብሼ የመረጃ ሳታላይት የአየር ሰዓት ክፍያ እንዲፈጸም እና ዐማራ ድምፁ በዓለም እንዲሰማ አኩፋዳዬን ይዤ ምንተ ስሟ ለማርያም፣ ስለ እመ አምላክ ብላችሁ፣ ለዐማራ ሕዝብ ብቸኛው ድምጹ የሚሰማበት ሚዲያ ነውና መረጃ ቴቪን እርዱ፣ አግዙ፣ እያልኩ የመረጃ ቴቪ አየር ላይ እንዲቆይ ከሌሎች በበለጠ መልኩ እንደ ብራቅ እየጮህኩ መክረሜን አስረስ መዓረይና ግርማ ካሣ ለምን እንደሆነ፣ ለምን እንደዚያ እንደማደርግ ግን አልገባቸውም። አልተረዱትምም። የራሴን ወንድሞች፣ አባቶች፣ እህቶችና ቤተሰቦች መረጃ ቴቪ አየር ላይ እንዲቆይ፣ ለዐማራ ድምጽ እንዲሆን እየደወተወትኩ ስለምን እንደነበር አይረዱም፣ ወይም ቢረዱም ለማመን አልፈለጉም። ስለዚህ ግርማ ካሣና አስረስ መዓረይ ሳንካ በመፍጠር እኔን ከመረጃ ቴቪ የምርቅበትን መንገድና ሁናቴ በመፍጠር የተሳካላቸው መስሏቸው ከነ ሰጥ አርጌና ከእነ አልማዝ ባለጭራዋ ጋር ሆነው አሽካኩ፣ አሽኮለኮሉ።

"…አብዛኛው በሚባል መልኩ ብዙ ሰው ለጥቅም፣ ለገንዘብ፣ ለሆዱ ብሎ በሚገረድበት በዚህ በአሁኑ ዓለም እኔም መረጃ ቴቪ ላይ እንደዛ የምጮኸው ለሆዴ፣ ለከርሴ የሚመስለው ነፍ ሰው ነበር። ከዓይንህ ላይ አዋራ እፍ ብሎ ለማውጣት፣ የጠፋህን መንገድ አቅጣጫ ስለጠየቅከው ብር ስጠኝ፣ ገንዘብ ክፈለኝ፣ የላቤን ዋጋ አምጣ ብሎ ግብግብ በሚፈጥርበት በዚህ ዘመን በሳምንት አንድ ቀን በዕለተ እሁድ አራት እና አምስት ሰዓት ሙሉ በላብ ተጠምቄ፣ ጉሮሮዬ እየደረቀ፣ በኩባያ ውኃ እየጠጣሁ እንደዚያ ዋይ ዋይ ስል ለሚያየኝ መንጋ ሚልዮን ዶላር እየተከፈለኝ እንዲህ የማንቋርር እንጂ እንዲህማ በጤናው፣ በብላሽ ያለምንም ክፍያ፣ ያለ ቁጢ በነፃ አይቀውጠውም የሚሉ ቢኖሩም እኔ በበኩሌ አልፈርድባቸውም። በድፍረት የምናገረው ግን እኔ ዘመዴ የዐማራ ድምጹ እንዲሰማ ከመፈለጌ የተነሣ ብቻ እንጂ ሌላ ቤሳቤስቲን ክፍያ የለውም። የምኮራውም ለዚህ ነው። እኔ በዚህ ዘመን ዐማራ ነኝ ከሚሉት አሞሮች የበለጠ በነፃ በብላሽ ለዐማራ ድምፅ በመሆኔ የሌለ ኩራት ነው የሚሰማኝ። ያለ ምንም ምድራዊ ጥቅም በመቆሜ የህሊና እረፍት፣ የውስጥ ሰላም ነው የሚሰማኝ። ሃላስ።

"…እኔ መረጃ ቴቪ ላይ ሆኜ እየለመንኩ እኮ ስኳድ በለጠ ካሣ እዚያው እኔ ለምኜ ባቆምኩት ቤት ላይ ዐማራን የሚያፈርስ፣ ስኳድን የሚያነግሥ ፕሮግራም ይሠራበታል። ሀገር ቤት ካለ ዲኤምሲ ከሚባል ሪል እስቴት ማስታወቂያ ተቀብሎ ዶላሩን እየሞዠለቀ ወደ ኪሱ እያስገባ አሱ ግን የብልፅግና ተቃዋሚ መስሎ በመረጃ ቴቪ ላይ በነፃነት ይገማሸራል። ሌሎችም እንደዚሁ። የመረጃ ቴቪ ፕላት ፎርሙ የማንንም የመናገር ነፃነት ስለማይገድብና ስለሚፈቅድ እኔ ዘመዴ ተቃውሞ የለኝም። ሊኖረኝም አይችልም። ይሄን ግርማ ካሣና አስረስ መዓረይም አሳምረው ያውቁታል። ዘመዴን በቦሌም በባሌም ከመረጃ ቴቪ ማስወረዱ እንጂ የታያቸው የእኔ ዘርፈ ብዙ ጥቅም ለሁለቱ ሾተላዮች በፍጹም አልታያቸውም። ግርማ ካሣ በጀርባ የሚጨቀጭቀኝን ጭቅጨቃ አንድም ቀን ለሌሎቹ የጋራ ወዳጆቻችን ነግሬም አላውቅም። ረጅም ጊዜ አብረው የኖሩ ወዳጆች መሆናቸውን ስለማውቅ ጊዜው ሲደርስ በራሱ መንገድ ይገለጣል በማለት ተንፍሼውም አላውቅ። የተነፈስኩትም ግርማ ካሳና አስረስ መዓረይ የአሸናፊነት ስሜት ተሰምቷቸው በአደባባይ ሲንበጫበጩ ባየሁ ግዜ ነው።

"…ወዲያው ነበር ግርማ ካሣ መረጃ ቴቪ ላይ ወጥቶ ለእኔ በሚገባኝ መልኩ በአሸናፊነት ስሜት የማልደራደርባቸውን "ከእንግዲህ የፋኖ መሪዎችን መንካት፣ መተቸት አይቻልም" የሚል ሕግ አስረስ መዓረይ ሰጥቶት ሲያነብ ሳየው ዳግም ወደ መረጃ ቴቪ የመመለሴ ጉዳይ እንዳከተመለት ሳውቅ ለምን ሌላ መንገድ፣ ሌላ አማራጭ አንመለከትም በማለት ከዚህ በፊት ጀምረነው ወዳቋረጥነው ወደ ዘመዴ ሚዲያ ሓሳብ የተመለስነው። የመጀመሪያው ጸሎት በአባቶች ማስያዝ ነው። ከአባቶች አረንጓዴ መብራት መብራቱ ሲነገረኝ በቀጥታ ወደ ሥራ ነው የገባነው። ጥቂት ወዳጆቼን አማከርኩ። እነርሱም ሰሙኝ ቆሞ የነበረው የዘመዴ ሚዲያ እንዲንቀሳቀስ ተደረገ። ወዲያውም አለቀ። እግዚአብሔር ይመስገን። ደግሞ ደጋግሞ አሁንም ትናንትም፣ ነገ ከነገ ወዲያም እስከ ዘላለሙ ድረስ እግዚአብሔር ይመስገን። የአባቶቻችን አምላክ፣ የአብርሃም፣ የይስሐቅ የያዕቆብ አምላክ ስሙ የተባረከ ይሁን። አሜን።

"…በዚህ ዘመን የትኛውም ተቋም ሲመሠረት ታማኝ የሆኑ ሰዎችና ገንዘብ እጅግ አስፈላጊ ናቸው። ታማኝ የሆኑ ባለሙያ፣ ዐዋቂ ሰዎች አግኝተህ ሥራውን ለመሥራት ግን ገንዘብ ከሌለህ አባዬ ፈቅ ማለት አትችልም። ስለዚህ ብዙዎች ይሄን ችግር ለመፍታት በብዙ ይደክማሉ። አንዳንዴም ገንዘቡን ለማግኘት ሲሉ የማይፈልጉትን ለመፈጸም ይገደዳሉ። ይሄን የምትፈጽምልኝ ከሆነ፣ እገሌን ከአጠገብህ የምታርቀው ከሆነ፣ ስለ እገሌና ስለዚህ ጉዳይ የማትተነፍስ፣ ጭጭ ምጭጭ የምትል ከሆነ ገንዘቡን እሰጥሃለሁ ብለው በሸምቀቆ አስረው፣ በ18 ቁጥር ሚስማር ጠርቅመው ቆለፈው።👇①✍✍✍

Показано 20 последних публикаций.