MADO NEWS


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


. Your go-to source for the latest, most reliable news from Ethiopia and beyond! Get real-time updates, breaking stories, and insightful coverage from trusted sources. Stay ahead, stay informed, and never miss a beat! 📲
📩 @Mado_Inbox

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ፕረዚደንት አቶ ጌታቸው ረዳ ማምሻቸዉን ሶስት የህወሃት የጦር አዛዦችን ከስራ አግደዋቸዋል

ጄኔራሎቹ ከስራ የታገዱት መፈንቅለ መንግሥት ለማድረግ የግጭት እንቅስቃሴ መጀመራቸውን ተከትሎ ነው ተብሏል።
የታገዱት ጄኔራሎች:-
1. ብ/ጄኔራል ምግበይ ሀይሌ
2. ሜ/ጄኔራል ዮሃንስ ወልደጊዮርጊስ
3. ሜ/ጄኔራል ማሾ በየነ ናቸው።
እነዚህ የታገዱት ጄኔራሎች በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ዋና የጦር አዛዥ የነበሩ ናቸው።

[ @MadoNews ]


በሰሜን ባህር ላይ ሁለት መርከቦች ተጋጩ

አንድ ነዳጅ አመላላሽና አንድ የሸቀጥ አመላላሽ መርከብ በሰሜን ባህር ላይ ተጋጭተው 32 ሰዎች መጎዳታቸውንና ወደ ባህር ዳርቻ እንዲወጡ መደረጉን አንድ የእንግሊዝ ወደብ ኅላፊ አስታውቀዋል።

የተጎጂዎቹ ሁኔታን ወዲያውኑ ማወቅ እንዳልተቻለ ያመለከተው የአሶስየትድ ፕረስ ዘገባ፣ የእንግሊዝ የባህር ድንበር ኅይሎች አንድ አውሮፕላንን ጨምሮ በርካታ ነፍስ አድን ጀልባዎችንና አንድ ሄሊኮፕተር ማሰማራታቸውን አስታውቋል።

ከተጋጩት መርከቦች አንደኛው የአሜሪካንን ባንዲራ የሚያውለበልብ ሲኾን ሌላኛው ደግሞ የፖርቹጋልን ባንዲራ የሚያውለበልብ መሆኑም ታውቋል።

የአሜሪካኑን ባንዲራ የሚያውለበልበውና ኬሚካልና ነዳጅ የሚያመላለሰው መርከብ ከግሪክ የተነሳ ሲሆን፣ የፖርቹጋልን ባንዲራ የሚያብለበልበው መርከብ ደግሞ ከስኮትላንድ ተነስቶ ወደ ኔዘርላንድ በማቅናት ላይ ነበር ተብሏል።

[ @MadoNews ]


በውስጥ በደረሰኝ መረጃ መሠረት በምዕራብ ሸዋ ዞን አንድ የሕዝብ ማመላለሻ ተሽከርካሪ ከግንድበረት ወደ ጊንጪ ከ70ሰዎች በላይ ጭኖ ሲጓዝ በፍሬን ምክንያት ጭሊሞ ጫካ ጫፍ ላይ ተገልብጦ ከባድ አደጋ ደርሷል።

ከ10 በላይ ሰዎች ሳይሞቱ እንዳልቀረ እና ከ30 በላይ እንደተጎዱ ነግረውኛል።ያሳዝናል።

[ @MadoNews ]


የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት በጥላቻ ንግግር ግጭት ለመፍጠርየሚንቀሳቀሱ አካላት ተጠያቂ እንዲሆኑ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ በሆነው

ኢትዮጵያ ብዝሃ ሀይማኖት የሆነች ሀገር እንደ መሆኗ የተለያየ እምነት ተከታዬች ለዘመናት ተፈቃቅደውና ተከባብረው ኖረውባታል። እየኖሩባትም ይገኛሉ፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን በተለይም የማህበራዊ መገናኛ ዘዴዎችን በመጠቀም ይህንን በጎ እሴት በመሸርሸር ውዝግብና ግጭት ለመፍጠር የሚሰሩ አካላት እየተበራከቱ መጥተዋል፡፡

በተለይም የእስልምናን መልካም እሴቶች እና የነብዩ ሙሀመድን (ሰ.ዐ.ወ) ክብር በመዳፈር ህዝበ ሙስሊሙን የሚያስቆጡ የጥላቻ ንግግሮች በስፋት እየተሰራጩ መሆናቸውን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ተረድቷል።

ጠቅላይ ም/ቤቱ እነዚህ አካላት ከዛሬ ነገ ህጋዊ እርምጃ ተወስዶባቸው ከጥፋታቸው ይታረማሉ በሚል ቀና እሳቤ ጉዳዩን በትዕግስት ሲከታተል ቆይቷል፡፡ ይሁን እንጂ ጠቅላይ ም/ቤቱ ችግሩን ከዚህ በላይበትዕግስት መመልከት ውጤቱ የከፋ በመሆኑ የኢስላምንና የነብዩ ሙሀመድን (ሰ.ዐ.ወ) ክብር የሚነኩ አካላት በህግ ተጠያቂ እንዲሆኑ ለማድረግ ከየትኛው አይነት ተግባር ቅድሚያ ሰጥቶ የሚሰራ ይሆናል፡፡ የጥላቻ ንግግር በየትኛውም ወገን ቢሰነዘር ጠቅላይ ም/ቤቱ በጽኑ እንደሚያወግዝና ተጠያቂነት እንዲሰፍን እንደሚሰራም ማወቅ ይገባል፡፡

ሙሉ መግለጫው ከላይ በምስል ተያይዟል

[ @MadoNews ]


የኢትዮጵያ ደምና ህብረ ህዋስ ባንክ በመጋቢት ወር ከ10 ሺ ዩኒት ደም በላይ ለመሰብሰብ ማቀዱን ገለፀ።

የፆም ወቅት መሆኑን ተከትሎ የደም ዕጥረት መከሰቱንም ሰምተናል።

ከጣቢያችን ጋር ቆይታ ያደረጉት በኢትዮጵያ ደምና ህብረ ህዋስ ባንክ አገልግሎት የኮሚኒኬሽን ባለሙያ አቶ አለማየሁ  ታረቀኝ፤ መጋቢት የፃም ወቅት መሆኑን ተከትሎ የደም ዕጥረት ሊከሰት መቻሉን አንስተዋል።

በዚህም ምክንያት መጋቢት ወርን የደም መለገስ ወር ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል።

ከዚህ ቀደም ከበጎ ፈቃደኞች ከሚሰበሰበው የደም አቅርቦት አንጻር እጥረት የሚስተዋልበት ሁኔታ ስለመኖሩ አንስተዋል።

የደም እጥረቱ ከፍ እንዳይል የተለያዩ አማራጮችን በመጠቀም የደም ማሰባሰብ ስራ እየተሰራ እንደሚገኝም ባለሙያው ተናግረዋል፡፡

በትምህርት ቤቶች፣ በእምነት ተቋማት እና በአውራ ገዳናዎች ላይ ድንኳኖችን በመዘርጋት የደም ማሰባሰብ ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል።

የጾም ወቅት መሆኑን ተከትሎም ምሽት ላይ እና በማይጾምበት ቀን የደም ማሰባሰብ ሥራ እየተሰራ እንደሆነም ተናግረዋል፡፡
Ethio FM

[ @MadoNews ]


ሕብረተሰቡ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ጥያቄዎቹን እንዲያቀርብ ጥሪ ቀረበ

ሕብረተሰቡ በትምህርት፣ በጤና፣ በኢኮኖሚ ጉዳዮችና አምራች ዘርፎች ላይ ጥያቄዎቹንና ማብራሪያ የሚሹ ጉዳዮችን እንዲያቀርብ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ጥሪ አቀረበ፡፡

በዚሁ መሠረት ሕብረተሰቡ እስከ ማክሰኞ መጋቢት 2 ድረስ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የማኅበራዊ ትሥሥር ገጾች አማካኝነት ጥያቄዎቹን መላክ እንደሚችል ተገልጿል፡፡

ለሚቀርቡ ጥያቄዎችም የሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ምላሽና ማብራሪያ እንደሚሰጡበት ጽሕፈት ቤቱ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጹ አረጋግጧል፡፡

[ @MadoNews ]


በማይናማር በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 32 #ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው መመለሳቸው ተገለጸ፣ 43 የሚሆኑ ደግሞ ምሽት ላይ ይገባሉ ተብሏል

#በማይናማር በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የነበሩ 32 ኢትዮጵያውያን ወደ አገራቸው እንዲመለሱ ማድረጉን መንግስት አስታወቀ።

#ሕንድ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ በማይናማር በእገታ ሥር ቆይተው ወደ ታይላንድ ከተሻገሩ 133 ኢትዮጵያ መካከል 32ቱ ዛሬ መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ወደ አገራቸው ተመልሰዋል ሲል ገልጿል፤ ሌሎች 43 ኢትዮጵያውያን ደግሞ ዛሬ ምሽት ይገባሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቁሟል።

ቀሪዎቹ በታይላንድ ማቆያ የሚገኙ 58 ኢትዮጵያውያንን ወደ አገራቸው ለመመለስ ኤምባሲው ጥረት እያደረገ ይገኛል ብሏል።

በተጨማሪም #ጃፓን በሚገኘውን የኢትዮጵያ ኤምባሲ በኩል በማይናማር በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ሌሎች ኢትዮጵያውያንን ወደ ታይላንድ በማሻገር ወደ አገራቸው ለመመለስ ጥረት እየተደረገ እንደሚገኝ ከውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃያሳያል።

[ @MadoNews ]


የአዲስ አበባ ባለሀብቶች ያላመኑበትን ግብርና ታክስ በተጨማሪ በሌሎች ችግሮች እየተፈተኑ እንደሚገኙ ተገለፀ

የአዲስ አበባ ባለሀብቶች ፎረም በከተማው ውስጥ የሚገኙ ባለሀብቶች ከባድ ችግሮች እያጋጠሟቸው መሆኑን ገልጿል። ፎረሙ የባለሀብቶችን ቅሬታ በሰነድ የተደገፈ መረጃ ለመቀበል ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታውቋል።

የባለአብቶች ፕሬዝዳንት አቶ አሸናፊ ሙሴ አያሌው ለካፒታል እንደገለጹት፣ ባለሀብቶቹ ያላግባብ ድርጅቶቻቸው መታሸግ፣ መፍረስ፣ መነጠቅ (መቀማት)፣ ሥራ እንዲያቆሙ መደረግ፣ ያላመኑበትን ከፍተኛ ግብርና ታክስ ለማስከፈል ማስገደድ፣ የባንክ አካውንታቸው መታገድ፣ ከሀገር እንዳይወጡ ወይም እንዳይገቡ እየተደረጉ ነው ብለዋል።

ከዚህ በተጨማሪ በስልክ ዛቻና ማስፈራሪያ ማድረስ፣ የማያምኑበትን አሰልቺና ተደጋጋሚ መዋጮዎች መጠየቅ፣ እንዲሁም ተረጋግተው ሥራቸውን እንዳይከውኑ ማዋከብ፣ የብድር አገልግሎት በበቂ ሁኔታ ያለማግኘት እና የመሳሰሉት ችግሮች እየደረሱባቸው መሆኑን ሰምተናል ብለዋል።

ይህን ተከትሎ ፎረሙ ከመጋቢት 01 እስከ 27 ቀን 2024 ዓ.ም ድረስ የከተማውን ባለሀብቶች ቅሬታ በሰነድ የተደገፈ መረጃ ለመቀበል መዘጋጀቱንና ባለሀብቶችም መረጃቸውን በሰነድ በማቅረብ እንዲተባበሩ ጥሪ አቅርቧል።

የባለሀብቶቹ ቅሬታ ከተሰበሰበ በኋላ ለሚመለከተው አካል በማቅረብ ችግሮቹ እንዲፈቱ ፎረሙ እንደሚሰራ አቶ አሸናፊ ሙሴ አያሌው ተናግረዋል።

[ @MadoNews ]


እስራኤል የመላ ጋዛ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እንዲቋረጥ አዘዘች

እስራኤል በመላው ጋዛ ሰርጥ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እንዲቋረጥ ትዕዛዝ ሰጠች።
የአገሪቱ የኃይል ሚኒስትር ሐማስ ቀሪ ታጋቾችን እንዲለቅ ጫና ለመፍጠር በሚል ይህ እርምጃ እንደተወሰደ ገልጸዋል።

ሚኒስትሩ ኤሊ ኮኸን ይህንን ያስተላለፉት እስራኤል ከሁለት ሚሊዮን በላይ ህዝብ በሚኖርባት ጋዛ ማንኛውንም የእርዳታ አቅርቦት ካቋረጠች ከአንድ ሳምንት በኋላ ነው።

"ታጋቾቹን ለማስመለስ እንዲሁም በጦርነቱ ማግስት ሐማስ በጋዛ ውስጥ አለመኖሩን ለማረጋገጥ በእጃችን ያሉ ማንኛውንም መሳሪያዎች እንጠቀማለን" ሲሉ ኮኸን እሁድ ዕለት በቪዲዮ ባስተላለፉት መግለጫ ተናግረዋል።

የኤሌክትሪክ ኃይል መቋረጥ በዋነኝነት ለግዛቲቷ ንጹህ መጠጥ አቅርቦት ወሳኝ በሆነው የጨዋማ ውሃ ማጣሪያ ፋብሪካዎች ስራ ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ እንደሚኖረው ተገልጿል።

የእስራኤል መንግሥት የውሃ አገልግሎት ሊያቋርጥ እንደሚችል ፍንጭ ሰጥቷል።
ሚኒስትሩ በመግለጫቸው "ለጋዛ ሰርጥ የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት በአስቸኳይ እንዲቋረጥ ትዕዛዝ ፈርሜያለሁ" ብለዋል።
እስራኤል በጦርነቱ ወቅት ጋዛን በሙሉ ከበባ አስገብታ ኤሌክትሪክን ጨምሮ መሰረታዊ የሚባሉ አገልግሎቶችን ማቋረጧ ይታወሳል።

የጋዛ የተኩስ አቁም ስምምነት የመጀመሪያው ምዕራፍ ከአስር ቀናት በፊት የተጠናቀቀ ሲሆን ይህንን ያልጸና ስምምነት ለማራዘም የሚደረገው ውይይት በያዝነው ሰኞ በኳታር ይቀጥላል ተብሎ ይጠበቃል።

እስራኤል የመጀመሪያው ምዕራፍ የተኩስ አቁም ስምምነትን መራዘምን ሐማስ እንዲቀበል ትፈልጋለች።
ሐማስ በበኩሉ ሁሉም ታጋቾች እንዲለቀቁ እንዲሁም የእስራኤል ጦር ከጋዛ ሙሉ በሙሉ እንዲወጣ እና ዘላቂ መረጋጋትን ማምጣት ያለመው ሁለተኛው ምዕራፍ ተግባራዊ ይሁን እያለ ነው።

[ @MadoNews ]


የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለመቄዶንያ 30 ሚሊዮን ብር አበረከተ

👉🏼የገቢ ማሰባሰቢያዉ 700 ሚሊዮን ብርን ተሻግሯል

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ እቤ ሳኖ 30ኛ ቀኑን በያዘው የመቄዶንያ የእርዳታ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ላይ በመገኘት የባንኩን ድጋፍ አበርክተዋል።

አቶ አቤ እንዳሉት ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሠራተኞች እና ማኔጅመንት አባላት የተሰበሰበ 18 ሚሊዮን ብር እንዲሁም ባንኩ 12 ሚሊዮን ብር ወጪ በማድረግ በድምሩ 30 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደርጓል።

አቶ አቤ መቄዶንያ እያከናወነ የሚገኘው የበጎ አድራጎት ስራ የሚደነቅ እና የሚበረታታ መሆኑን ገልጸው፣ ባንኩ እንደሁልጊዜው ሁሉ ከማእከሉ ጎን እንደሚቆም ተናግረዋል።
አቶ አቤ ሁሉም ዜጋ እንደየአቅሙ ለማዕከሉ ድጋፍ እንዲያደርግም ጥሪ አቅርበዋል።

የመቄዶንያ መስራች እና የበላይ ጠበቂ የክብር ዶክተር ቢኒያም በለጠ በበኩላቸው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የመቄዶንያ ቋሚ ደጋፊ መሆኑን ገልጸው፣ በየጊዜው ለማዕከሉ ለሚያደርገው ድጋፍ ምስጋና አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የአሁኑን ድጋፍ ሳይጨምር ከዚህ በፊት በተለያዩ ጊዜያት ለማዕከሉ 205 ሚሊዮን ብር በላይ ድጋፍ ማድረጉ ይታወቃል።

በኢትዮጵያ ከሚገኙ ታላላቅ ተቋማት ዉስጥ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ቀዳሚ በመሆን ለመቄዶንያ ድጋፍ ያደረገ ሲሆን ከሰሞኑ ደግሞ ንብ ኢንሹራንስ ድጋፍ አድርጓል። እንደ ማለዳ ፎም ያሉ ተቋማት የቁስ ድጋፍ አድርገዋል።

[ @MadoNews ]


የኢትዮጵያ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ከቢሊ ግራሀም ኢቫንጀልስቲክ አሶሴሽን ጋር በጋራ በመሆን ያዘጋጀው ፤ መለኮታዊ ጉብኝት ለኢትዮጵያ የተሰኘው መረሃ ግብር ተጠናቀቀ

[ @MadoNews ]


መቀሌ እና አዲግራት የጊዜያዊ አስተዳደሩን ቢሮዎች ለመቆጣጠር የእነ ዶክተር ደብረፂዮን ኃይል እንቅስቃሴ ላይ መሆኑ ተሰምቷል።የክልሉን ቀውስ እንዳያባብሰው ተሰግቷል።

[ @MadoNews ]


ሰሌክታ ግሩፕ በፖለቲካ አለመረጋጋት ምክንያት ከኢትዮጵያ ወጣ

በስዊዘርላንድ ዋና መስሪያ ቤቱን ያደረገው ሰሌክታ ግሩፕ በሰሜን ኢትዮጵያ ኩንዚላ የሚገኘውን የምርት ማዕከሉን በፖለቲካ አለመረጋጋት እና በወታደራዊ ሁኔታዎች ምክንያት ወደ ኬንያ እና ኡጋንዳ ማዛወሩን አስታዉቋል።

ኩባንያው የዚህ ውሳኔ ምክንያት በኢትዮጵያ ያለው ሁኔታ ለሰራተኞች ደህንነት ስጋት መፍጠሩ እና የሎጂስቲክስ ችግሮች መከሰታቸው እንደሆነ ገልጿል።

የኩባንያዉ ዋና ስራ አስፈፃሚ አንስጋር ክሌም ይህን ውሳኔ "አሳማሚ እርምጃ" ብለው የገለፁት ሲሆን፣ በኢትዮጵያ ያደረጉትን ከፍተኛ ኢንቨስትመንት እና ጥረት ከንቱ መሆኑን ተናግረዋል።

ይህ ውሳኔ በኩንዚላ አካባቢ ከ1,000 በላይ የስራ እድሎችን የሚያሳጣ ሲሆን፣ በቀጥታና በተዘዋዋሪ ወደ 10,000 የሚሆኑ ሰዎችን ይጎዳል። ኩባንያው ለአካባቢው ማህበረሰብ የኢኮኖሚ ህይወት መስመር እንደነበር እና መውጣቱ ትልቅ ጉዳት እንደሚያስከትል ገልጿል።

ካፒታል ያገኘዉ መረጃ እንደሚያመለክተዉ ሰሌክታ ግሩፕ በኬንያ እና ኡጋንዳ ያሉትን የምርት ማዕከላት በማጠናከር ለደንበኞች የምርት አቅርቦት እንዳይቋረጥ ማረጋገጡን ገልጿል። ወደፊት ሁኔታዎች ሲሻሻሉ ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ ተስፋ እንዳለውም አስታውቋል።

ሰሌክታ ግሩፕ በዓለም አቀፍ ደረጃ ግንባር ቀደም የሆነ የአበባ እና የጌጣጌጥ እፅዋት አምራች ኩባንያ መሆኑ ይታወቃል።

[ @MadoNews ]


መቀሌና አካባቢው ጥሩ ያልሆነ የፀጥታ ድባብ እንዳለው እየተሰማ ነው።

መንግስትን ደግፈው መረጃ የሚያጋሩ ምንጮች እንደሚሉት ጊዜያዊ አስተዳደሩ ላይ ዛሬ ሌሊት መፈንቅለ መንግስት ለመፈፀም መታቀዱ ተደርሶበታል ብለዋል።

እነ ዶክተር ደብረፂዮን የዚህ ሂደት መሪ መሆናቸውን ጠቁመዋል።ይህ ጉዳይ ከወራት በፊትም በተመሳሳይ መልኩ ተነስቶ ነበር።ይሁነ እንጅ ከቃላት ጦርነት የዘለለ የተፈፀመ ነገር የለም።

[ @MadoNews ]


የሪፖርተር መረጃ የተሳሳተ ነው:-ተቋሙ‼️

ምንም አይነት  አዲስ ታሪፍ ጭማሪ አልተደረገም
‼️

ከሚያዝያ ወር ጀምሮ አዲስ የታሪፍ ማሻሻያ ተግባራዊ ሊደረግ እንደሆነ ተደርጎ በአንዳንድ የመገናኛ ብዙሃንና የማህበራዊ ሚዲያ የትስስር ገፆች እየተሰራጨ የሚገኘው መረጃ የተሳሳተ ነው።

ተቋሙ ከመስከረም  2017 ዓ.ም ጀምሮ ለ4 ተከታታይ አመታት  በማኅበረሰቡ ላይ ጫና እንዳይፈጠር በየሩብ አመቱ ተከፍሎ ተግባራዊ እየተደረገ የሚገኘውን የታሪፍ ማስተካከያ  ከማስፈፀም ውጪ አዲስ ተግባራዊ ያደረገው የታሪፍ ማሻሻያ አለመኖሩን እንገልፃለን ብሏል።

[ @MadoNews ]


በእነ ጆን ዳንኤል የክስ መዝገብ በተከሰሱ ተከሳሾች የዋስትና ጥያቄ ጉዳይ ላይ ዉሳኔ ሊሰጥ ነዉ ፡፡

አንደኛዋ ተከሳሺ ነፍሰጡር ስለሆነች እና የመዉለጀዋ ጊዜዋ ስለተቃረበ ፍርድቤቱ በልዩ መዝገብ እንዲመለከተዉ ተጠይቆል ፡፡

[ @MadoNews ]


ዘለንስኪ ከትራምፕ ጋር ከተጋጩ በኋላ ዩክሬን ውስጥ ተቀባይነታቸው መጨመሩ ተገለጸ

ጥናቱ የተካሄደው ኪቭ ቁጥር አንድ ከሆነችው አሜሪካ ጋር ያላት ግንኙነት በዋሽንግተን ኦቫል ኦፊስ በተፈጠረው ግጭት ምክንያት ቀውስ ውስጥ በገባበት ወቅት ነው

የዩክሬኑ ፕሬዝደንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ በኋይትሀውስ ከአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ከተጋጩ ወዲህ በሀገር ውስጥ ያላቸው ተቀባይነት በ10 በመቶ ማደጉን ሮይተርስ የህዝብ አስተያየት በመሰብሰብ ቀዳሚ የሆነውን ተቋም ጠቅሶ ዘግቧል።

የኪቭ አለምአቀፍ የሶሾሎጂ ኢንስቲትዩት ያካሄደው የህዝብ አስተያየት በመጋቢት ወር 67 በመቶ የሚሆኑ ዩክሬናውያን ዘለንስኪን ያምኑታል።ይህ ጥናት የተካሄደው ኪቭ ቁጥር አንድ ከሆነችው አሜሪካ ጋር ያላት ግንኙነት በዋሽንግተን ኦቫል ኦፊስ በተፈጠረው ግጭት ምክንያት ቀውስ ውስጥ በገባበት ወቅት ነው።
የኢንስቲትዩቱ ዋና ስራ አስፈፃሚ አንቶን ህሩሽትስካይ የህዝብ አስተያየቱ ሩሲያ በዩክሬን ላይ ልዩ ያለችውን ወታደራዊ ዘመቻ ከከፈተች ከሶስት አመታት በኋላ የዩክሬናውያን ከፕሬዝደንት ዘለንስኪ ጎን መሰለፋቸውን የሚያሳይ ነው ብለዋል።

"ዩክሬናውያን የአዲሱን የአሜሪካ አስተዳደር አካሄድ በዩክሬንና በዩክሬናውያን ላይ እንደተቃጣ ጥቃት አድርገው ያዩታል" ሲሉ ሁሩሽትስካይ ተናግረዋል። ሁሩሽትስካይ እንዳሉት ዩክሬናውያን ሰላም ይፈልጋሉ፤ በከፍተኛ ዋጋ የሚመጣ ሰላም ግን አይፈልጉም።

"የዩክሬናውያን ሰላም ይፈልጋሉ፤ ነገርግን ውጤታችን የሚያሳየው አብዛኞቹ የዩክሬናውያን ሰላም እንደማይፈልጉ ነው"ብለዋል ኃላፊው።
በ2ዐ19 የተመረጡት የ47ቱ የዩክሬን ፕሬዝደንት ዘለንስኪ ሩሲያ በየካቲት 2022 ልዩ ያለችውን ዘመቻ በዩክሬን ላይ ከከፈተች ወዲህ የጽናት ተምሳሌት ሆነዋል።

[ @MadoNews ]


የኢትዮጵያ ህዝብ ብዛት 109 ሚሊየን ብቻ ነው ተባለ‼️

የኢትዮጵያ ህዝብ ብዛት እስከ 135 ሚሊየን ይደርሳል ሲባል የቆየ ቢሆንም ከሳምንታት በፊት የወጣ የመንግስት መረጃ የአገሪቱ ህዝብ ብዛት 109 ሚሊየን ብቻ ነው ሲል መግለፁ እያስገረመ ነው።

የስታስቲክስ አገልግሎት ይፋ ባደረገው መረጃ ባለፈው ሀምሌ 2016 ዓም የኢትዮጵያ ህዝብ ቁጥሩ 109.4 ሚሊየን ደርሷል ሲል ነው የገለፀው።

[ @MadoNews ]


በሶሪያ በተቀሰቀሰው ግጭት  በሁለት ቀናት ውስጥ ከ 1000 ሺ በላይ ሰዎች መሞታቸው ተገለፀ‼️

በአዲሱ የሶሪያ የጸጥታ ሃይሎች እና በቀድሞው የበሽር አልአሳድ መንግስት ታማኝ ተዋጊዎች መካከል በተቀሰቀሰው ግጭት እና የበቀል ግድያ በሁለት ቀናት ውስጥ ከ1,000 በላይ ሰዎች መሞታቸው  ተገልጿል ።

መቀመጫውን በብሪታኒያ ያደረገው የሶሪያ የሰብአዊ መብት ታዛቢ ቡድን እንዳስታወቀው ከማቾቹ መካከል 745 የሚሆኑት ንፁሀን ዜጎች ሲሆኑ ፣125 የሶሪያ የጸጥታ ሃይሎች እና 148 የአሳድ ታማኝ ተዋጊዎች ተገድለዋል ሲል አስታውቋል።

ይህ የበርካታ ሰዎችን ህይወት የቀጠፈው ግጭት በታህሳስ ወር የሶሪያ መንግስት ሀይሎች  የአሳድ አማፂያን ካስወገዱ ወዲህ  አስከፊው ግጭት መሆኑን የሰብአዊ መብት ታዛቢ ቡድኑ ገልጿል ።

ባሳለፍነው ሀሙስ የበሽር አል አሳድ ታማኝ ሃይሎች፣ በሀገሪቱ የባህር ጠረፍ አካባቢ ላታኪያ በተባለችው ከተማ የመንግስት ጸጥታ ሀይሎች ለደህንነት ስራ እየተንቀሳቀሱ ባሉበት ድንገት በከፈቱት ጥቃት ግጭቱ  መቀስቀሱ ይታወሳል።

[ @MadoNews ]


ኢትዮጵያ ድሮን ለውጭ ገበያ ማቅረብ የሚያስችል አቅም ገንብቻለሁ አለች!

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ለሲቪልና ወታደራዊ አገልግሎት የሚውሉ ሰው አልባ አውሮፕላኖችን (ድሮን) የሚያመርተውን የስካይ ዊን ኢንዱስትሪን መርቀው በከፈቱበት እንዳስታወቁት ኢንዱስትሪው የሚያመርታቸው ድሮኖች ኢትዮጵያ ሉዓላዊነቷን የመጠበቅ አቅሟን ይበልጥ ያሳድጋል ፡፡

ኢንዱስትሪው የሚያመርታቸው ድሮኖች ኢትዮጵያ ሉዓላዊነቷን የመጠበቅ አቅሟን ይበልጥ የሚያሳድጉ ናቸው ተብሏል፡፡ድሮኖቹ በከፍተኛ መልካዓ-ምድር ላይ በብቃት አገልግሎት የሚሰጡና ጸረ-ድሮን ጭምር የታጠቁ መሆናቸውንም አረጋግጠዋል፡፡ኢንዱስትሪው ድሮኖችን ከኢትዮጵያ ባሻገር ለውጭ ገበያ ማቅረብ የሚያስችል አቅም አለው ብለዋል ፡

[ @MadoNews ]

Показано 20 последних публикаций.