EBSTV NEWS


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Новости и СМИ


Welcome to EBS TV NEWS Telegram! We have daily news brief, interesting videos and breaking news updates, Sport. Don’t forget to share it with your friends.
https://t.me/ebstvworldwide
Inbox - @EbswhatsnewBot

Связанные каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Новости и СМИ
Статистика
Фильтр публикаций


የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ የመጋቢት 2 / 2017 ዓ.ም የምሽት 1፡00 ሰዓት የሀገር ውስጥ ዋና ዋና ዜናዎች፦

🎯የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ጌታቸው ረዳ በ3 ከፍተኛ የሰራዊት አዛዦች ላይ ጊዚያዊ እግድ ማውጣታቸውን ተከትሎ የህወሃት ፕሬዝዳንት የሆኑት ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል እግዱን አጣጥለዋል።

🎯የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከመጭው ሚያዝያ እስከ ሰኔ ወር ድረስ የፍጆታ የአገልግሎት ታሪፍ ተመን ጭማሪ ሊያደርግ መሆኑ ታወቀ፡፡

🎯የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ከተለያዩ አገራት ተሰደው የሚመጡ ስደተኞች በከተሞች የመኖር ፍላጎት እያስከተለ ያለው የህዝብ ቁጥር መጨመርና የተለያዩ ፍላጎቶች ማሻቀብ እንዳሳሰበው ገልጿል፡፡

🎯በዘመናዊ መንገድ እንጆሪና ለመድሃኒት ግብዓት የሚውል ሳፍሮን የተሰኘ አበባ በማምረት ለውጪ ገበያ የሚያቀርብ አፍሪካን ፋርሚንግ ኢንዱስትሪስ የተሰኘ ኩባንያ በ2 ሚሊዮን ዶላር ኢንቨስትመንት በሀገር ውስጥ ማምረት ሊጀምር ነው ተብሏል፡፡

🎯በአዲስ አበባ የሚገኙ 76 ወንዞች ግለሰቦችና የተለያዩ ድርጅቶች በሚለቋቸው ቆሻሻ ፍሳሽ ምክንያት የተበከሉ በመሆናቸው ለምንም አይነት አገልግሎት መዋል እንደማይችሉ ተገልጿል፡፡

ኢትዮጵያ በአፍሪካ የአውሮፓ ሕብረት ቁልፍ አጋር ሆና መቀጠሏን በኢትዮጵያ የሕብረቱ አምባሳደር ሶፊ ፍሮም ኢመስበርገር ገለጹ።

ዜና አዲስ ነገር ነው! አዲስ ነገርም ዜና ነው!"
የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ


#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


አንጋፋው ድምፃዊ፣ የግጥምና ዜማ ደራሲ፣ መሰንቆና ዋሽንት ተጫዋች፣ ክራርና በገና ደርዳሪ፣ የኢትዮጵያ የባህል ሙዚቃ መምህር የሆኑት አለማየሁ ፋንታ ከ6 ወራት በፊት በድንገት ወድቀው እግራቸው በመሰበሩ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ትላንት መጋቢት 1 ቀን 2017 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

የጥምር ሙያ ባለቤት ስለነበሩት አለማየሁ ፋንታ በወፍ በረረ ይስሩ ስለነበረው ስራ እና የቤተሰብ ሁኔታ የተወሰነ ነገር እንንገራችሁ፡፡

በባህላዊ የሙዚቃ መሳሪያ ተጫዋጭነታቸው የሚታወቁት ሙዚቀኛው አለማየሁ ፋንታ ስራቸውን የጀመሩት ሃገር ፍቅር ቲያትር ቤት በመቀጠር ነው፤ እዚያም ለ10 ዓመታት ሰርተዋል፡፡

ለ40 ዓመታት ያህል በያሬድ የሙዚቃ ትምህርት ቤት በመምህርነት ሲያገለግሉ የቆዩት ሙዚቀኛው፤ በዕድሜአቸው መጨረሻ ጡረታ ከውጡ በኋላ በዚሁ ያሬድ ሙዚቃ ትምህርት ቤት ማገልገላቸውን የሙዚቀኛው የቅርብ ሰው ሆኑት ታዋቂው የበገና መምህር መጋቢ ብሉይ አለሙ አጋ ነግረውናል፡፡

ባህላዊዎቹን የኢትዮጵያ የሙዚቃ መሳሪያዎች በገናን በመደርደር፣ ክራርና መሰንቆን አሳምረው በመጫወት ይታወቁ ነበር፡፡

አንጋፋው ሙዚቀኛ አለማየሁ ፋንታ የቀለም ትምህርትን የተማሩ እንዲሁም የድቁና ትምህርትም የነበራቸው ሲሆን ባለ ትዳርና 6 ልጆች አባት ነበሩ፡፡

ስርዓተ ቀብራቸው በነገው ዕለት ፒያሳ በሚገኘው በገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ከቀኑ በ9 ሰዓት ይፈፀማል።

ጣቢያችን ኢቢኤስ ቴሌቪዥን በአንጋፋው ሙዚቀኛ አለማየሁ ፋንታ ህልፈት የተሰማውን ልባዊ ሀዘን እየገለጸ ለቤተሰቦቻቸውና ለመላው አድናቂዎቻቸው እንዲሁም ለወዳጅ ዘመዶቻቸው ልባዊ መጽናናትን ይመኛል፡፡

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


አንድ ፓኪስታናዊ አባት በሴት ልጁ የራስ ቅል ላይ የደህንነት መቆጣጠሪያ ካሜራ ማድረጉ አጀብ አስብሏል ይለናል ኦዲት ሴንትራል አስገራሚ ብሎ ይዞት በወጣው መረጃ፡፡

ነገሩ እንዲህ ነው ፓኪስታናዊ ዜግነት ያለው አባት የሴት ልጄ የእለት ከእለት የውሎ ደህንነቷ ያሰጋኛል ፣ ያሳስበኛል በማለት ሁሉንም እንቅስቃሴዎቿ በእይታዎቼ ውስጥ አድርጊያለሁ ብሏል፡፡

ይህ ፓኪስታናዊ አባት ድርጊቱን በኤክስ ገጹ ያጋራ ሲሆን ምስሉ በብዙዎች ዘንድ ደርሶ መነጋገሪያ ሆኗል፡፡ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ ምልከታቸውን ያጋሩ ተጠቃሚዎች ድርጊቱን ''የደህንነት ደረጃን ከፍ ያደረገ ሲሉ'' በስላቅም ይሁን በቁም ነገር ባይታወቅም ገልጸውታል፡፡

እቺ ፓኪስታናዊ ሴትም እነዚህ የደህንነት ካሜራዎች ራሷ ላይ ስለመገጠሙ ለተጠየቀችው ጥያቄ “ይህ የአባቴ ሃሳብ ነው እና በፍጹም ልቃወመው አልፈልግም ደህንነቴ ስለሚያስጨንቃቸው ነው'' ማለቷ በብዙዎች ዘንድ አግራሞትን ጭሯል፡፡

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


የመጋቢት 2/2017 የከሰአት ዓበይት የዓለም ዜናዎች።
🎯እስራኤል በፍልስጤሟ ጋዛ ባካሄደችው የአየር ጥቃት በትንሹ 6 ሰዎች መገደላቸው ተነገረ።
🎯የአሜሪካና የዩክሬን ተደራዳሪዎች የዩክሬንን ጦርነት ለማቆም ያስችላል የተባለውን ወሳኝ ድርድር ዛሬ በሳዑዲ አረቢያ መዲና ሪያድ አካሄዱ ።
🎯ምስራቅ አፍሪካዊቷ ኡጋንዳ ወደእርስ በርስ ጦርነት ልትገባ ጫፍ ላይ ነች በተባለችው ደቡብ ሱዳን ልዩ ጦሯን ማሰማራቷ ተነገረ።
🎯ሩሲያ ባለፉት 24 ሰአታት ብቻ በመዲናዋ ሞስኮ ጥቃት የፈፀሙ ከ 300 በላይ የዩክሬን የሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትታ መጣሏን የሀገሪቱ ባለስልጣናት ተናገሩ።
🎯የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ትራምፕ የዩክሬኑ አቻቸው ቮሎድሚር ዘለንስኪ ከስልጣን እንዲለቁ ፍላጎት ያላቸው መሆኑ ተዘገበ።

ዜና አዲስ ነገር ነው! አዲስ ነገርም ዜና ነው!"
የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ


#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


በኢትዮጵያ እግር ኳስ ላይ ሰፊ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ በማድረስ የሚታወቀው ወጣቱ ጋዜጠኛ ኑርሁሴን ዓሊ በድንገተኛ የትራፊክ አደጋ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይቷል።

ጋዜጠኛ ኑርሁሴን ዳጉ ስፖርት የተሰኘ የማህበራዊ ትስስር ገጽ እና የድህረ ገፅ ሚድያን በማቋቋም መረጃዎችን ከማድረስ በተጨማሪ ለእግር ኳሱ እድገት የራሱን ተሳትፎ በማድረግ ላይ የነበረ ታታሪ ወጣት ነበር።

ከከፍተኛ ሊግ እስከ አንደኛ ሊግ ያሉ ውድድሮችን በመዘገብ አንቱታን ያተረፈው ወጣቱ ጋዜጠኛ ኑርሁሴን ዛሬ ረፋድ በድንገተኛ የመኪና አደጋ ሕይወቱ አልፏል፡፡

በወጣቱ ጋዜጠኛ ህልፈት የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለፅን ለቤተሰብ ፣ ለወዳጅ ዘመድ እና ለመላው የኢትዯጵያ እግር ኳስ ቤተሰብ መፅናናትን እንመኛለን

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


⚽️የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ሁለተኛ ዙር ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት ሲከናወኑ ሊቨርፑል ፓሪሴንት ጀርሜይንን ባየር ሊቨርኩሰን ባየር ሙኒክን የሚያስተናግዱባቸው ጨዋታዎች ተጠባቂ ሆነዋል፡፡

⚽️27 ሙከራዎችን ቢያስተናግድም በፓርክ ደፕሪንስ ፓሪሴንት ጀርሜይንን 1-0 አሸንፎ የተመለሰው ሊቨርፑል በአንፊልድ ሮድ የመልሱን ጨዋታ ምሽት 5 ሰዓት ላይ ያደርጋል፡፡

⚽️ሊቨርፑል የመጀመሪያውን ዙር ጨዋታዎች ባሸነፋቸው ያለፉት 14 የሻምፒየንስ ሊግ መርሃ ግብሮች ወደ ተከታዩ ዙር ማለፍ ችሏል፡፡

⚽️ሌላኛው የምሽቱ ጨዋታ ደግሞ ባየር ሊቨርኩሰን እና ባየር ሙኒክን በባይ አሬና ምሽት 5 ሰዓት ያገናኛል፡፡

⚽️በሁለቱ ቡድኖች የመጀመሪያ ጨዋታ ባየር ሙኒክ 3-0 አሸንፏል፡፡ የሻምፒየንስ ሊጉ አድማቂ ባየር ሙኒክ ከዚህ ቀደም ለ34 ያህል ጊዚ በሩብ ፍጻሜው ተገኝቷል፡፡

⚽️ አንድ ተጫዋች በቀይ ካርድ ወጥቶበት በስታዲዮ ዳሉዝ ቤኒፍካን 1-0 አሸንፎ የተመለሰው ባርሴሎና በስታዲዮ ኦሎምፒኮ የመልስ ጨዋታውን ምሽት 2፡45 ላይ ያደርጋል፡፡

⚽️በአውሮፓ የክለቦች ውድድር ታሪክ ባርሴሎና ቤኒፍካን 10 ጊዚ የገጠመ ሲሆን አንድ ሽንፈት ብቻም በፖርቱጋሉ ክለብ አስተናግዷል፡፡

⚽️ሌላኛው ምሽት 5 ሰዓት የሚደረገው ጨዋታ ደግሞ ኢንተር ሚላን እና ፌይኖርድን ያገናኛል፡፡ ኢንተር ሚላን ከሜዳው ውጭ 2-0 አሸንፎ መመለሱን ተከትሎ ወደ ተከታዩ ዙር ለማለፍ እድሉን አስፍቷል፡፡

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


⚽️እንግሊዛዊው የአርሰናል የመስመር ተጫዋች ቡካዮ ሳካ ከሳምንታት መልስ ወደ ሜዳ እንደሚመለስ ተሰማ ።

⚽️በከባድ የእግር ጉዳት ምክንያት ለወራት ከሜዳ የራቀው ጨዋታ አቀጣጣዩ ከሁለት ሳምንታት መልስ ወደ ጨዋታ እንደሚመለስ ተገልጿል።

⚽️መደበኛ ልምምዱን እየከወነ ያለው የ23 አመቱ እንግሊዛዊ በያዝነው አመት 16 የሊግ ጨዋታዎች ላይ የተሰለፈ ሲሆን 5 ግብ አስቆጥሮ 10 ለግብ የሚሆኑ ኳሶችን ደግሞ ለቡድን አጋሮቹ አመቻችቶ መስጠት ችሏል።

⚽️አርሰናል በቀጣይ በፕሪሚየር ሊጉ ወደ ጉዲሰን ፓርክ አቅንቶ ኤቨርተንን በሚገጥምበት ጨዋታ ሳካ ወደ ሜዳ እንደሚመለስ ተነግሯል።

⚽️ከ2018/2019 የውድድር ዘመን አንስቶ ለመድፈኞቹ መጫወት የጀመረው ቡካዮ ሳካ በሁሉም ውድድሮች 250 ጨዋታዎችን ያደረገ ሲሆን 67 ግቦች አስቆጥሯል።

⚽️አማካዩም ከክለቡ ጋር በነበረው ቆይታም የእንግሊዝ ኤፌ ዋንጫ እና የኮምዩንቲ ሺልድ ክብርን ማሸነፍ ችሏል።

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


⚽️የማንችስተር ዩናይትዱ ባለ ድርሻ ሰር ጂም ራት ክሊፍ ሩበን አሞሪም ለረጅም ጊዚ በቲያትር ኦፍ ድሪምስ እንደሚቆይ ገለጹ።

⚽️የክለቡን 25 በመቶ ድርሻ ከግሌዘር ቤተሰቦች ከገዙ በኃላ ስር ነቀል ለውጦች ለማምጣት እየሰሩ የሚገኙት እንግሊዛዊው ባለጸጋ ከውጤት ማጣት ቀውስ ጋር በተያያዘ ሩበን አሞሪምን ለማባረር እንደማይጣደፉ ገልፀዋል።

⚽️ፖርቱጋላዊውን ታክቲሺያን ምርጥ ወጣት አሰልጣኝ ሲሉ ያሞካሹት ራትክሊፍ ሩበን አሞሪም ጥሪ አሰልጣኝ ነው ጊዜም ሊሰጠው ይገባል ያሉ ሲሆን በዩናይትድም ረጅም ጊዚ የሚቆይ ይመስለኛል ሲሉ ተደምጠዋል።

⚽️እርሱ ወጣት እና ተስፈኛ ነው እኛም ቡድን እንዲገነባ እና ቡድኑን እንዲላመድ እድል መስጠት አለብን ሲሉም ተናግረዋል።

⚽️የ40 አመቱ ሩበን አሞሪም ማንችስተር ዩናይትድን ይዞ 26 ጨዋታዎችን የመራ ሲሆን 10 ጨዋታ አሸንፎ በሰባቱ አቻ ወጥቶ በዘጠኙ ተሸንፏል። 38.4 በመቶ ጨዋታዎችን የማሸነፍ ንጻሬም አለው።

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


⚽️የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ2026 የአለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች ይረዳው ዘንድ መጋቢት 4 ይሰባሰባል፡፡

⚽️መጋቢት 12 ግብፅን ካዛ ብላንካ ላይ መጋቢት 15 ጅቡቲን አልጀዲዳ ላይ የሚገጥመው ስብስቡ ከቀናት በኋላ በአዲስ አበባ ከተማ ዝግጅቱን ይጀምራል፡፡

⚽️ለ24 በሀገር ውስጥ እና በውጭ ለሚገኙ ተጫዋች ጥሪ የቀረበ ሲሆን ከረጅም ጊዚ መልስም አቡበከር ናስር ለዋልያዎቹ እንዲጫወት ጥሪ ደርሶታል፡፡

⚽️3 ግብ ጠባቂዎች 10 ተከላካዮች 6 አማካዮች 5 አጥቂዎች በጥሪው ሲካተቱ አህመድ ሁሴን እና መሀመድ አበራ እና አብዱ ሰላም የሱፍ ለመጀመሪያ ጊዚ ለዋልያዎቹ ጥሪ ደርሷቸዋል፡፡

⚽️ብሔራዊ ቡድኑ ከመጋቢት 4 እስከ መጋቢት 9 በመዲናዋ የሚቆይ ሲሆን በቀን ለሁለት ጊዚ በአዲስ አበባ ስቴዲየም እና በጅምናዚየም ውስጥ ልምምዱን የሚያደርግ ይሆናል፡፡

⚽️ዋልያው በሰሜን አፍሪካዊቷ ሀገር ሞሮኮ ጨዋታውን የሚያደርግ ሲሆን ወደ ስፍራውም መጋቢት 10 እንደሚያቀና ተነግሯል፡፡

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ የመጋቢት 2 2017 ዓ.ም የእኩለ ቀን 7፡ 00 ሰዓት የሀገር ውስጥ ዋና ዋና ዜናዎች፦

🎯የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት አንዱ የሌላውን ሃይማኖት ለመስደብና ለማዋረድ ጥቅም ላይ ሊውል አይገባውም አለ፡፡

🎯የአሜሪካ መንግስት ለጉዞ አደገኛ ናቸው ሲል 23 አገራትን ይፋ ያደረገ ሲሆን በዚህ ዝርዝር ውስጥ ኢትዮጵያም ተካታለች።

🎯የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ከውጭ ድጋፍ በመላቀቅ በራስ አቅም የልማት ሥራዎችን መደገፍ የሚያስችል እንቅስቃሴ እያደረጉ መሆናቸውን ገልፀዋል።

🎯የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ በተከናወኑ የአቅም ማሳደግና የማዘመን ሥራዎች ተጨማሪ 310 ሜጋ ዋት ኃይል ማግኘት መቻሉን አስታውቋል፡፡

🎯የትራፊክ አደጋ መረጃ ማሰባሰቢያ ሥርዓት የሚያዘምን ሶፍትዌር ከስድስት ወራት የሙከራ ጊዜ በኋላ ወደ ሙሉ ትግበራ መግባቱ ተገልጿል፡፡

ዜና አዲስ ነገር ነው! አዲስ ነገርም ዜና ነው!"
የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ


#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


⚽️ፈረንሳዊው አማካይ ፖል ፖግባ ከአበረታች መድሃኒት ጋር በተያያዘ ተጥሎበት የነበረውን ቅጣት በዛሬው ዕለት አጠናቋል፡፡

⚽️ላለፉት ሁለት የውድድር ዘመናት አበረታች መድሃኒት መውሰዱ መረጋገጡን ተከትሎ ከእግር ኳስ ርቆ የሰነበተው የቀድሞ የማንችስተር ዩናይትድ አማካይ ቅጣቱን ፈፅሟል፡፡

⚽️ይህንን ተከትሎም ተጫዋቹ ከዛሬ ጀምሮ እግር ኳስን መጫወት የሚችል ሲሆን ከፈለገው ክለብ ጋርም ተደራድሮ ወደ አዲስ ቡድን ማምራት ይችላል፡፡

⚽️የአለም ዋንጫ አሸናፊው ያለፉት 18 ወራቶችን በቅጣት ያሳለፈ ሲሆን ከጁቬንቱስ ጋርም በስምምነት ተለያይቷል፡፡

⚽️የ31 አመቱ ፈረንሳዊ አሁን ላይ ስሙ ከኦሎምፒክ ደማርሴ እና ከሳውዲ አረቢያ እና ሜጀር ሶከር ሊግ ክለቦች ጋር እየተነሳ ይገኛል፡፡

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


👉የትራፊክ አደጋ መረጃ ማሰባሰቢያ ሥርዓት የሚያዘምን ሶፍትዌር ከስድስት ወራት የሙከራ ጊዜ በኋላ ወደ ሙሉ ትግበራ መግባቱ ተገልጿል፡፡

👉ሶፍትዌሩ የትራፊክ አደጋ የመረጃ ሥርዓትን ለማዘመን ለሁለት ዓመታት ያክል ሲዘጋጅ መቆየቱን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ፤ የመንገድ ደኅንነትና መድህን ፈንድ አገልግሎት የገለጹ ሲሆን ከዚህ በፊት የነበረው ማንዋል የመረጃ አያያዝ ሥርዓት ወደ ዲጂታል ሶፍትዌር ተቀይሮ ከሰው እጅ ንክኪ ነጻ የሆነ የተሟላ መረጃ በቀጥታ አደጋ ከደረሰበት ቦታ እስከ ኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ ሰርቨር እንደሚያደርስ ተናግረዋል፡፡

👉ከዚህ በኋላ ሁሉም ክልሎች የሚጠቀሙበት ዘመናዊ የትራፊክ አደጋ መቆጣጠሪያ እና መረጃ ማሰባሰቢያ ሥርዓት መዘርጋቱንም ተቋማቱ ገልፀዋል፡፡

👉የዲጂታል ሶፍትዌሩ መረጃ ከትራፊክ አደጋ ጋር የተያያዙ ችግሮችን ህብረተሰቡ በትክክል እንዲረዳ ለማስተማሪያነት ጭምር እንደሚውልም ነዉ በመግለጫቸው ያስታወቁት።

መረጃዉን ያገኘነዉ ከኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ነዉ፡፡

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


👉አገልግሎቱ ለጊዜው በሀያት፣ ጦርሀይሎች፣ ዳግማዊ ሚኒሊክና ቃሊቲ ጣቢያዎች እንዲሁም በስታዲየም እንደሚጀመር ነው የተነገረው።

👉የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር ትራንስፖርት አገልግሎት ድርጅት ባለፉት 10 ዓመታት በ39 የትኬት መቁረጫ ጣቢያዎች የወረቀት ትኬት በመሸጥ የቀላል ባቡሩ አገልግሎቱን ሲሰጥ መቆየቱን አስታውሶ አሁን ግን ዘመኑ ባፈራው ቴክኖሎጂ በመጠቀም ደንበኞች ካሉበት ሆነው ትኬቱን መቁረጥ የሚችሉበትን አሰራር መዘርጋቱን አሳውቋል።

👉የክፍያ ሥርዓቱ በቴሌ ሱፐር አፕና በሌሎች የክፍያ መተገበሪያዎች አማካኝነት መቁረጥ እንደሚቻል ሲገለፅ ይህም ደንበኞች የትኛውንም አይነት ስልክ በመጠቀም አገልግሎቱን ማግኘት የሚያስችላቸው ነው የተባለው።

👉በዚህም ድርጅቱ የወረቀት ትኬት ሽያጩን ሙሉ ለሙሉ በማስቀረት ወደ ዲጂታል የክፍያ ሥርዓት ለመሸጋገር ለሚያደርገው ጉዞ መደላድል የሚፈጥር እንደሆነ ከአዲስ አበባ ትራንስፖርት ቢሮ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


👉የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ሃሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት አንዱ የሌላውን ሃይማኖት ለመስደብና ለማዋረድ ጥቅም ላይ ሊውል አይገባውም ብሏል፡፡

👉ጉባኤው ይህን ያለው ወቅታዊ ጉዳይን አስመልክቶ በሰጠው መግለጫላይ ሲሆን፤ከሰሞኑ በሁለት ታላላቅ ሃይማኖቶች የተቀደሰ የጾምና የጸሎት ወቅት ከመንፈሳዊና ሃይማኖታዊ እሴቶች ጋር በማይሄድ መልኩ በማህበራዊ ሚዲያው እየተሰራጨ ያለው ያለውን ሃሳብ አወግዛለሁም ብሏል፡፡

👉በተለይ አንዳንድ የኦርቶዶክስ ክርስትና አማኝ ነኝ የሚሉ ግለሰቦች የእስልምና ሃይማኖት ነብይ በሆኑትና በነብዩ መሃመድ ላይ ድፍረት የተሞላበት ክብረነክና ጸያፍ ንግግር ሲያደርጉ ታይተዋል ያለው ተቋሙ ይህም ሙስሊሙን ማህበረሰብ ብቻ ሳይሆን ሰላም ወዳዱን ህዝብ ያሳዘነ ነው ብሏል፡፡

👉ጉባኤው ይህ አይነቱ ኢ ስነምግባራዊና ተግባር የትኛውንም ሃይማኖት የማይወክል መሆኑን ገልጾ፤ድርጊቱም ሊወገዝ የሚገባው ነው ሲል አክሏል፡፡

👉ከዚሁ ጋር ተያይዞም አንዳንድ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ነን የሚሉ ግለሰቦች ይህንን ህገወጥ ተግባር ተቋማዊ ለማድረግ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ እንዲያጤኑና ግለሰብን ከተቋም እንዲለዩ አሳስቧል፡፡

👉በተመሳሳይ አንዳንድ የሙስሊም እምነት ተከታይ ነን የሚሉ ግለሰቦችም ተደፈርን በሚል ስሜት የክርስትና አስተምህሮና የእየሱስ ክርስቶስ ክብርን የሚነቅፍና የሚያጠለሽ እንዲሁም መላው ክርስቲያንንም በሚያዋርድ መልኩ ምላሽ ሲሰጡና ድርጊቱን በፈጸመው ግለሰብም ላይ የደቦ ፍርድ ሲያስተላልፉ ይታያሉ ብሏል፡፡

👉ይህም ድርጊት በወንጀል የሚያስጠይቅ በመሆኑ የሚመለከታቸው አካላት እርምጃ እንዲወስዱ ጠይቋል፡፡

ዘገባው የሃና አብደታ ነው

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


👉የአሜሪካ መንግስት ለጉዞ አደገኛ ናቸው ሲል 23 አገራትን ይፋ ያደረገ ሲሆን በዚህ ዝርዝር ውስጥ ኢትዮጵያም ተካታለች።

👉ለጉዞ አስተማማኝ አይደሉም የተባሉት አገራት በአብዛኛው የደቡብ አሜሪካና የአፍሪካ አገራት ሲሆኑ ከአፍሪካ አገራት እንደ ኢትዮጵያ፣ ግብፅና ናይጄሪያ ያሉ አገራትም ይገኛሉ።

👉የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ በየጊዜው የአገራት ጉዞ ማስጠንቀቂያ የሚያወጣ ሲሆን ይህም አገራቱ በወቅቱ ባሉበት ተጨባጭ ሁኔታ ላይ የተመሰረተ ነው ተብሏል።

👉አሁን አራት ደረጃ በወጣለት ማስጠንቀቂያ መንገደኞች ወደእነዚህ አገራት ከመጓዛቸው በፊት በውል ሊያጠኗቸው የሚገቡ ጉዳዮች አሉ በሚል ነው ኢትዮጵያ የተካተተችበትን ዝርዝር ያወጣው።

👉የአሜሪካ መንግስት እንዲህ ዝርዝር ሲያወጣ በዝርዝሩ የተካተቱ አገራት ምክሩን ያልተገባ ሲሉ አብዝተው ይቃወሙታል።

የየአገሮቻቸውን ቱሪዝም የሚጎዳና ኃላፊነት የማይሰማው ሪፖርት ነው ሲሉ ያጣጥሉታል።

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


የመጋቢት 02/2017 ዓ.ም የረፋድ ዓበይት የዓለም ዜናዎች

🎯መነሻውን ዩክሬን ያደረገ የሳይበር ጥቃት በኤክስ የማህበራዊ የትስስር ገፅ ላይ መፈፀሙን ቢሊየነሩ ኤሎን መስክ ተናገሩ።

🎯የንግድ ጦርነት ከቻይና ጋር እያካሄዱ ያሉት የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቀጣይ ወር በቻይና ጉብኝት ሊያደርጉ እንደሚችሉ ተነገረ።

🎯ሩሲያ በመዲናዋ ሞስኮ ጥቃት የፈፀሙ 69 የዩክሬን የሰው አልባ አውሮፕላኖችን መትታ መጣሏን የሀገሪቱ ባለስልጣናት ተናገሩ።

🎯ብሪታንያ በአሜሪካ አደራዳሪነት የተጀመረውን የዩክሬን የሰላም ጥረት ለማደናቀፍ እንደምትፈልግ የሩሲያ የደህንነት ባለስልጣናት ተናገሩ።

🎯የአሜሪካና የዩክሬን ተደራዳሪዎች የዩክሬንን ጦርነት ለማቆም ያስችላል የተባለውን ወሳኝ ድርድር ዛሬ በሳዑዲ አረቢያ መዲና ሪያድ ይጀምራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ የመጋቢት 1 2017 ዓ.ም የምሽት 1፡ 00 ሰዓት የሀገር ውስጥ ዋና ዋና ዜናዎች፦

🎯መንግስት በቀጣይ 3 አመታት የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔትን ለመተግበር 45 ቢሊየን ብር መመደቡን የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስትሯ ጫልቱ ሳኒ ተናግረዋል፡፡

🎯ታንዛኒያ ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ሃይል ግዢ ለመፈፀም የወሰነችው በሃገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል ያለውንና በተደጋጋሚ በሚከሰቱ የሃይል መቆራረጦች በአመት 32 ቢሊየን ሽልንግ እያከሰራት ያለውን ችግር ለመቅረፍ መሆኑን አስታውቃለች፡፡

🎯የመጋቢት ወርን "መጋቢት የደም ልገሳ ወር " በሚል የደም ልገሳ የንቅናቄ ስራ ላይ ህብረተሰቡ ከዛሬ ጀምሮ ተሳትፎ እንዲያደርግ ጥሪ ቀረበ።

🎯በማዕከላዊ ኢትዮጲያ ክልል ጉራጌ ዞን ባለፉት 6 ወራት ከ70 ሺ በላይ ሰዎች በወባ በሽታ መያዛቸዉን የዞኑ ጤና መምሪያ አስታውቋል።

🎯በየዓመቱ ህይወታቸው ከሚያልፍ 12ሺህ እናቶች ውስጥ 8 ሺህ የሚሆነው በደም መፍሰስ ይከሰታል ተባለ፡፡

🎯 የለሚ ናሽናል ሲሚንቶ ፋብሪካ ሰባት ሚሊዮን ኩንታል ሲሚንቶ ለገበያ አቅርቢያለሁ አለ፡፡

ዜና አዲስ ነገር ነው! አዲስ ነገርም ዜና ነው!"
የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ


#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


👉ታንዛኒያ ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ሃይል ግዢ ለመፈፀም የወሰነችው በሃገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል ያለውንና በተደጋጋሚ በሚከሰቱ የሃይል መቆራረጦች በአመት 32 ቢሊየን ሽልንግ እያከሰራት ያለውን ችግር ለመቅረፍ መሆኑን አስታውቃለች፡፡

👉የሃገሪቱ ፕሬዝዳንት ሳሚያ ሱሉ በኪሊማንጃሮ ተራራ አካባቢ የተገነባ የውሃ ፕሮጀክትን ባስመረቁበት ወቅተ መንግስታቸው ይህን ውሳኔ የወሰነው ቴክኒካዊና ኢኮኖሚያዊ ምክኛቶችን ከፈተሸ በኋላ መሆኑን ሲናገሩ ከደቡብ ምስራቅ እስከ ስሜናዊ የአገሪቱ ክፍል ያለው የኤሌክትሪክ መስመር ከፍተኛ ኪሳራን እያስከተለ ነው ብለዋል፡፡

👉እናም ይህን መስመር ከኢትዮጵያ በሚመጣ ሃይል ለመሸፈን መወሰንዋን ያሳወቀችው ታንዛኒያ ከኢትዮጵያ የምትገዛው 100 ሜጋ ዋት ለማቅረብ ሃይል በአገር ውስጥ ለማመንጨት ከምታወጣው ወጪ ያነሰ እንደሚያስወጣት ያሳውቀች ሲሆን ኢትዮጵያም ከዚ ግብይት በአመት በዓመት ከ200 ሚሊዮን ዶላር ልታገኝ እንደምትችል ተነግሮ ነበር፡፡
መረጃው የታንዛኒያው ዘ ሲቲዝን ነው፡፡

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


👉በትምህርት፣ በጤና፣ በኢኮኖሚ ጉዳዮችና በሌሎች አምራች ዘርፎች ያሏችሁን ጥያቄዎች እና ማብራሪያ የሚሹ ጉዳዮችን ላይ ጥያቄያችሁን እንድታቀርቡ የጠቅላይ ሚንስትር ጽሕፈት ቤት ጥሪ አቅርቧል፡፡

👉በዚሁ መሠረት ሕብረተሰቡ እስከ ነገ ድረስ በጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የማኅበራዊ ትሥሥር ገጾች አማካኝነት ጥያቄዎቹን መላክ እንደሚችል የተገለጸ ሲሆን የሚመለከታቸው የሥራ ኃላፊዎች ተገኝተው ምላሽና ማብራሪያ እንደሚሰጡም ጽሕፈት ቤት በማህበራዊ የትሥሥር ገጹ አሳውቋል።

👉ጥያቄዎቹን https://web.facebook.com/share/p/15st5pyP38/ በዚህ ማስፈንጠሪያ ተጠቅመው መጠየቅ እንደሚችሉ ተገልጿል፡፡

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews


👉የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማርኮ ሩቢዮ የአሜሪካው የተራድዖ ድርጅት ዩ.ኤስ.ኤይድ ፕሮግራሞችን የመከለስ ስራ መጠናቀቁን ጠቁመው 83 በመቶ የሚሆኑት የኤጀንሲው የቀድሞ ፕሮግራሞች ከዚህ በኋላ እንደማይቀጥሉ ገልጸዋል፡፡

👉ኤጀንሲው ከነበሩት 6 ሺህ 200 ፕሮግራሞች መካከል 5 ሺህ 200 የሚሆኑት ፕሮግራሞች ሙሉ በሙሉ በይፋ መሰረዛቸው ነው የተገለጸው፡፡

👉የትራምፕ አስተዳደር በዚህ 60 ዓመት በሞላው ኤጄንሲ ፕሮግራሞች ላይ 6 ሳምንታት የፈጀ ግምገማ ማካሄዱን የጠቆሙት ሩቢዮ በግምገማው 18 በመቶ የኤጀንሲው ፕሮግራሞች እንዲቀጥሉ መወሰኑን ተናግረዋል፡፡

👉እነዚህ 18 በመቶ የሚሆኑት የእርዳታ እና የልማት ፕሮግራሞችም የሚቀጥሉት በአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ስር ብቻ መሆኑ ነው የተገለጸው፡፡

👉ሩቢዮ በኤክስ የማህበራዊ ትስስር ገፃቸው በለጠፉት መልዕክት ኤሎን መስክ የሚመሩት የዶጅ ቢሮ ሰራተኞች ለረጅም ሰዓታት የኤጀንሲውን ፕሮግራሞች በመገምገም ለዚህ ታሪካዊ ለውጥ ስላበቁዋቸው ምስጋና አቅርበዋል፡፡

#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews

Показано 20 последних публикаций.