የኢቢኤስ አዲስ ነገር ዲጂታል ሚዲያ የጥር 29 ቀን 2017 ዓ.ም የምሽት 1፡00 ሰዓት የሀገር ውስጥ ዋና ዋና ዜናዎች፡_
🇪🇹▶️የሕዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት ባካሄደው 18ኛ መደበኛ ስብሰባ የፌዴራል የፍትህና የህግ ኢንስቲትዩት እንዲሁም የሲቪል እና የቤተሰብ ምዝገባ ስርዓት አዋጆችን መርምሮ አጸደቀ፡፡
📱📱የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ኤሌክትሮኒክ መገበያያ የሆነው "ኤምፔሳ" አገልግሎት ተጠቃሚዎቹ ቁጥር ባለፈው አንድ አመት ብቻ ከ3.1 ወደ 10.8 ሚሊዮን መግባቱ ቢዝነስ ዴይሊ አፍሪካ ዘግቧል፡፡
🪪🪪የኢትዮጵያ ብሄራዊ የመታወቂያ ፕሮግራም ጽ/ቤት በተያዘው የፈረንጆቹ 2025 ብቻ ለ70 ሚሊዮን ኢትዮጵያዊያን የዲጂታል መታወቅያ ተደራሽ ለማድረግ ማቀዱን አስታወቀ፡፡
🇺🇸🧪አሜሪካ በዩኤስኤይድ በኩል የምታደርገው እርዳታ በድንገት መቋረጥ ለገዳዩ የወባ በሽታ መስፋፋት አስተዋጽዖ ሊኖረው እንደሚችል እየተነገረ ነው።
🏦🏦በኤሌክትሮኒክ የነዳጅ ግዥ ስርአት ውስጥ ሁሉም ባንኮች ሊካተቱ መሆኑ ተነገረ፡፡
🏚🏠በኢትዮጵያ በከተሞች ያለውን የቤት አቅርቦት ችግር ለመፍታት በዓመት በአማካኝ 471 ሺህ ቤቶችን መገንባት ይጠይቃል ሲል የፖሊሲ ጥናት ኢንስቲትዩቱ አስታወቀ።
🚅🚄የኢትዮ- ጂቡቲ የባቡር መስመር የገቢና ወጪ ጭነቶችን የማጓጓዝ አቅሙን እያጎለበተ እንደሚገኝ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ታከለ ኡማ ተናገሩ፡፡
ዜና አዲስ ነገር ነው! አዲስ ነገርም ዜና ነው!"
ያማረ ምሽት ተመኘንላችሁ !
#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews