⚽️የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ሁለተኛ ዙር ጨዋታዎች ዛሬ ምሽት ሲከናወኑ ሊቨርፑል ፓሪሴንት ጀርሜይንን ባየር ሊቨርኩሰን ባየር ሙኒክን የሚያስተናግዱባቸው ጨዋታዎች ተጠባቂ ሆነዋል፡፡
⚽️27 ሙከራዎችን ቢያስተናግድም በፓርክ ደፕሪንስ ፓሪሴንት ጀርሜይንን 1-0 አሸንፎ የተመለሰው ሊቨርፑል በአንፊልድ ሮድ የመልሱን ጨዋታ ምሽት 5 ሰዓት ላይ ያደርጋል፡፡
⚽️ሊቨርፑል የመጀመሪያውን ዙር ጨዋታዎች ባሸነፋቸው ያለፉት 14 የሻምፒየንስ ሊግ መርሃ ግብሮች ወደ ተከታዩ ዙር ማለፍ ችሏል፡፡
⚽️ሌላኛው የምሽቱ ጨዋታ ደግሞ ባየር ሊቨርኩሰን እና ባየር ሙኒክን በባይ አሬና ምሽት 5 ሰዓት ያገናኛል፡፡
⚽️በሁለቱ ቡድኖች የመጀመሪያ ጨዋታ ባየር ሙኒክ 3-0 አሸንፏል፡፡ የሻምፒየንስ ሊጉ አድማቂ ባየር ሙኒክ ከዚህ ቀደም ለ34 ያህል ጊዚ በሩብ ፍጻሜው ተገኝቷል፡፡
⚽️ አንድ ተጫዋች በቀይ ካርድ ወጥቶበት በስታዲዮ ዳሉዝ ቤኒፍካን 1-0 አሸንፎ የተመለሰው ባርሴሎና በስታዲዮ ኦሎምፒኮ የመልስ ጨዋታውን ምሽት 2፡45 ላይ ያደርጋል፡፡
⚽️በአውሮፓ የክለቦች ውድድር ታሪክ ባርሴሎና ቤኒፍካን 10 ጊዚ የገጠመ ሲሆን አንድ ሽንፈት ብቻም በፖርቱጋሉ ክለብ አስተናግዷል፡፡
⚽️ሌላኛው ምሽት 5 ሰዓት የሚደረገው ጨዋታ ደግሞ ኢንተር ሚላን እና ፌይኖርድን ያገናኛል፡፡ ኢንተር ሚላን ከሜዳው ውጭ 2-0 አሸንፎ መመለሱን ተከትሎ ወደ ተከታዩ ዙር ለማለፍ እድሉን አስፍቷል፡፡
#EBS
#EBSTVNEWS
#EBSTVSPORT
#_7696_WN
https://t.me/ebstvnews