Zemedkun Bekele (ዘመዴ)


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


"ይህ የቴሌግራም ቻናሌ ግንቦት1/2011ዓም የተከፈተ ነው። የእኔን የስልክ ወጪ ጨምሮ አገልግሎቴን መደገፍ የምትፈቅዱ ጓደኞቼ በ
👉🏿 https://donorbox.org/zemedemedia እና
👉🏿 https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB በኩል ማገዝ ትችላላችሁ። በተረፈ ለቤተ ክርስቲያኔና ለኢትዮጵያ ሀገሬ የሚጠቅመውን ሁሉ አበረክት ዘንድ አብዝታችሁ ጸልዩልኝ።

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


167 ሰው ቀረኝ

"…ከ1ሺ$ እስከ 300$ 100$ ዶላር በመለገስ የዘመዴ ሚዲያን ለመቋቋም በገንዘባቸው ከእኔ ጎን በመቆም ሠራዊተ ጌዴዎንን ለመቀላቀል የቆረጡት ወዳጆቼ 133 ደርሰዋል። 133ኛ ወንድ አህመዲን ሱሌይማን ነው ከአሜሪካ።

"…አህመዲንንን እስከ አሁን በአካል አላየሁትም። ከሱሬና ከቀሲስ ያሬድ በቀር አንድም ሰው በፀረ ተሃድሶው ትግል ወቅት ከአጠገቤ ባልቆመበት በዚያ ዘመን ከእህቴ ሐረግ እና ከበረከት ወንድሜ ጋር በመሆን የስልክ ካርድ እየገዛ አይዞህ ተፋለም ዘመዴ። ይሄ የተሃድሶ እንቅስቃሴ በኦርቶዶክስ ብቻ የሚያቆም አይደለም። የእኛንም ቤት ይነቀንቃል ይለኝ የነበረ ወንድሜ ነው። እንዳለውም አለቀረ ተሃድሶው መጥቶ ሃጂ ሙፍቲን ገልብጦ በገሃድ ታየ። አህመዲን ዛሬም መጥቶ ዘመዴ መዝግበኝ እኔ አሁንም ከጎንህ ነኝ አለኝ። 🙏 

"…እስከአሁን አሜሪካ ያሉ ወገኖቼ ይመራሉ፣ ካናዳ የሚኖሩት ይከተላሉ፣ እንዲየውም በውስጥ ዘመዴ 1ሺ የካናዳ ዶላር ነው የምለግሰው ያለችኝ እና ቁጥር 001 ላይ የተመዘገበችው ከካናዳ ያለች እህቴ ናት። እንግሊዝና ጀርመንም ይከተላሉ።

"…ጎበዝ 300 ልንሞላ 167 ሰዎች ይቀሩናል። ጥንቅቅ አድርገን ነው የምንጀምረው። 300ውም ሰዎች መሥራች እንደ መሥራች ነው የሚቆጠሩት። የዘመዴ ሚዲያ ቤተሰቦችም ይሆናሉ። ለብቻችን የምንመክርበት የቴሌግራምና የኋትስአፕ ግሩፕም ይኖረናል። እንደዚያ ነው የምናደርገው።

"…አሁን ለቆጠራ፣ ለምዝገባ እንዲያመቸኝ ሌሎቻችሁ ዝም በሉ። ደስታችሁንም ተቆጣጠሩ። እናንት መዝግበኝ የምትሉ ወንድሞችና እህቶች ብቻ ስማችሁንና ያላችሁበትን ሀገር ጠቅሳችሁ ጻፉልኝ።

"…አሁን ብር አይደለም የሚፈለገው። አሁን ቅድሚያ ሰው ነው የሚፈለገው። 300 የጌዴዎን ሠራዊት ነው የሚፈለገው።

• እኔ እመዘግባለሁ እናንተ ስማችሁን ጻፉልኝ…✍✍✍

6.2k 1 5 54 333

"…200 ሰው ቀረኝ።

"…ተመልከቱልኝ የእግዚአብሔርን ድንቅ ሥራ። የአምላካችንን ተአምራት። ኮሚቴ የለ፣ ምን የለ፣ ራእዬንና ምኞቴን አደባባይ አውጥቼ ለገበያ አቀረብኩ።

"…የእኔ የሓሳብና የአቋም ምርት እንደ ማር፣ እንደ ስኳር እንደ አይስክሬምም አይጣፍጥም። እንደ ኮሶ፣ ሬት፣ መተሬ የሚመር፣ የሚጎመዝዝ፣ ለብዙዎችም የማይመች ነው። ሲያዩኝም፣ ሲሰሙኝም የማንገሸግሽ፣ የማንዘፈዝፍ ነኝ። ነጭ ነጯን፣ ሃቅ ሃቁን፣ እውነት እውነቱን፣ እንቅጯን ብቻ አምርቼ የምሸጥ ሰው ነኝ።

"…ዛሬ በአንዱ እውነት ደንበኛዬ፣ ቤተሰቤም የሆነ ሰው በማግሥቱ በሌላው የእውነት ምርቴ አይስማም፣ ሰድቦኝ፣ አብጠልጥሎኝ፣ አዋርዶኝ፣ አልያም ዝም ብሎ ጥሎኝ ይሄዳል። የሆነ ቀን ደግሞ ተመልሶ ይመጣል። ስለመጣም፣ ስለሄደም እኔ ግን የምቀይረው ምርት የለም። ከሚዛኔ ዝንፍ፣ ከደረጃዬም ውርድ፣ ከሥፍራዬም ንቅንቅ አልልም። ሲሄዱም፣ ሲመጡም እዚያው ነው የሚያገኙኝ።

"…የእኔ የሓሳብ ምርት እንደ ቃሪያ በሚጥሚጣ፣ ዳጣ ያለ ነው። ይለበልባል፣ ያቃጥላል፣ ያወራጫል። ለማብረጃ ወተት የለውም፣ እያቃጠለ እየለበለበህ የምትሸምተው ምርት ነው። ብዙዎች ኧረ ዘመዴ እንደ ሌሎቹ ተሞዳሞድ፣ አስመስል ይሉኛል። እኔ ግን ወይ ፍንክች።

"…አይችልም፣ መሃይም ነው፣ ጃል ቆቱ ወዲ አስገዶም ነው ይሉኛል። ማይምም ነው የሚሉኝ ብዙዎች ናቸው። አልተማረም፣ አያነብምም ይሉኛል። እብድ ነው፣ መራታ ተሳዳቢም ነው ይሉኛል። የተማርን ነን የሚሉት ግን ተሟግተው አይረቱኝም፣ ታግለው አያሸንፉኝም። እኔ ማይሙን ማሳፈርም አልተቻላቸውም።

"…እንግዲህ ተመልከት ብሮ… ያለ ፌስቡክ፣ ያለ ቲክቶክ፣ ያለ ተለቭዥን በቴሌግራም ብቻ በዚህች ደቂቃ ይሄን ሁሉ ሕዝብ ማግኘት ለሰው ይቻለዋልን…? 

• 101 ብዬ ልቀጥል ነኝ… 200 ሰው ነው የሚቀረኝ…✍✍✍

20.6k 1 7 357 1.3k

ወደ ሠራዊተ ጌዴዎን መረጣ ልገባ ነኝ።

"…ከዚያ በፊት ግን አንድ ነገር ልበል። ይኸውላችሁ ያለ እግዚአብሔር ፈቃድ በሺ ኮሚቴዎች ጋጋታ፣ በቢልዮን ብር በጀት፣ በዕለት ተዕለት በ24/7 የኮሚቴ ስብሰባ፣ በቲፎዞ፣ በሰውነት አቋም በጮሌነት በአቋራጭ መንገድም አይደለም ለሀገርና ለወገን የሚጠቅም ህልም ይቅርና የራስን የግል ምኞት እንኳ ለማሳካት አይቻልም።

"…እግዚአብሔር ከፈቀደ ግን አንበሳ ቢያገሳ፣ ማእበል ወጀብ ቢነሣ፣ ሰማይ ምድሩ ቢደባለቅ፣ ዲያብሎስ ምርጥና አለኝ የሚለውን የክፋትና የጥፋት ጦር በአየር በምድሩ በቀንና በሌሊት ቢያሰልፍ፣ የመሰናክል መዓት፣ ወጥመዶችን ሁሉ ከፊት ከኋላህ ቢያጠምድ፣ አይደለም ሩጦ የሚቀድምህ የሚደርስብህ፣ ታግሎ የሚጥልህ አይደለም የልብስህን ዘርፍ ጫፉን የሚነካም የለም። ብቻ ፈቃደ እግዚአብሔር ከአንተ ጋር ይሁን።

"…አሁን እኔ 300 ሰው ብቻ ነው የምፈልገው። 10ሺም 1ሺ፣ 500ም ሆነ 100 ዶላር ለሳታላይቱ ማስጀመሪያ፣ ለአስፈላጊ ቴክኒካል ወጪዎች የሚሆን ለሚዲያው የገንዘብ ድጋፍ ለማድረግ ፈቃደኛ የሆኑ ሰዎችን ነው የምፈልገው። ብሩን ሳይሆን ፈቃደኞችን ነው የምፈልገው። ሕልሜን የጋራ የሚያደርጉ ተመሳሳይ ሕልም ያላቸው ወዳጆቼን ነው የምፈልገው።

"…ሙሉ ስማችሁንና ያላችሁበትን ሀገር ብቻ ነው የምትጽፉልኝ። እኔ300 እስኪሞላ እመዘግባለሁ። ቅድሚያ ተመዝጋቢው ካለሁበት ሀገር ከሀገረ ጀርመን ቢጀምር ደስ ይለኝ ነበር። ከአውሮጳ ቢቀድም እወድ ነበር። ስሙ በአደባባይ የሚለጠፍ አይደለም። በስውር ነው። የራሱ ግሩፕም የሚኖረው ነው። ከጀርመንና ከአውሮጳ ካልተገኘም ዕጣው የሚወድቀው ያው የፈረደባችሁ እናንት አማሪካና ካናዳ ባላችሁት ላይ ነው። ያለቲክቶክ፣ ፌስቡክ፣ ዩቲዩብ፣ ያለግርግርም በቴሌግራም ብቻ እንዴት ሥራው እንደሚሠራም አብረን እናያለን።

• ጀምሩ✍✍✍

26.9k 1 9 453 1.5k

"…ኧረ ግሩም ነገር ነው። አዛኜን ከመደንገጤ የተነሣ ዲዳ ሆኜ ምን ብዬ እንደምጽፍ ሁላ ግራ ገብቶኝ እጄን በአፌ ላይ ጭኜ ቁጭ ብዬላችኋለሁ። እግዚአብሔር ይመስገን የሚለው ቃል ብቻውን አጠረብኝ አነሰብኝም።

"…ተረጋግቼ እመጣለሁ። በቀጣይ 300 ሠራዊተ ጌዴዎን ወደ መምረጡ እንገባለን። ገልአድ ከተራራው አጠገብ ቆመን የፈራ የደነገጠውን 21ሺ ሠራዊት ወደቤቱ እንመልሳለን። ፈሪ አይጸድቅም ገለባም እንክርዳድ ቢዘሩት አይበቅልምና ወደ ቤቱ እንመልሰዋለን። እያስመሰሉ፣ ወንድ ወንድ እየተጫወቱ ከጀግኖች ጋር ተደባልቆ፣ ተቀላቅሎ መጓዝ የለም። ፈሪ ወደ…

"…እዚያው ገልአድ ተራራው ጋር ቆመን የቀረውን 10ሺ ፈትነን ወደ መንደሩ እንመልሰዋለን። እንደ ውሻ ከሥነ ምግባር፣ ከባሕል፣ ከሃይማኖት ያፈነገጠውን 9,700 የውሻ ግብር ያለውን መንጋም ከሠራዊተ ጌዴዎን መካከል እንቀንሳለን። ያስነቀናል፣ ያሰድበናል፣ ያውከናልምና እንመልሰዋለን።

"…ከ32 ሺው ሠራዊት መካካል 31,700 መቶውን ወደ መንደሩ እንመልስና ጥርት ያሉትን 300 የጌዴዎን ሠራዊት ችቦ አስይዘን፣ ጨለማውን በእግዚአብሔር እውነት እየገፈፍን ወደፊት እንስፈነጠራለን። እናሸንፋለንም። ድሉ የእግዚአብሔርም ይሆናል።

"…እሁድ እሁድ ነጭ ነጯን ከዘመዴ ጋር ይቀጥላል። እንደ ዜጋ ስለ ሀገሬ እንደ አማኝ ደግሞ ስለ ሃይማኖቴ ሓሳብ መሸጤን እቀጥላለሁ። እኔን ከሚመስሉ ወንድም እህቶች ጋር ሁሉ ተያይዘን ከእግዚአብሔር ጋር ለለውጥ እንሠራለን።

"…እልሄን ነው የምወጣው። የፈረሱ ጥንታውያን ገዳማትን፣ አድባራትን፣ የአብነት መምህራንና ትምህርት ቤቶችን፣ የተረሱ፣ የተዘነጉ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያናትን ቢያንስ የመጨረሻ ዘመናቸውን ብሩህ አድርገን እንደ ሀገር መርቀውን እንዲያልፉ እናደርጋለን።

• ለ3መቶ ሠራዊት መረጣው ተመልሼ እመጣለሁ። አላችሁ አይደል?

29.6k 0 8 400 1.6k

“…ከፀሐይ መውጫ ጀምሮ እስከ መግቢያው ድረስ የእግዚአብሔር ስም ይመስገን።” መዝ 113፥3።”

"…እንደምን አደራችሁ?
"…እንደምን አረፈዳችሁ?
"…እንደምን ዋላችሁ?
"…እንደምን አመሻችሁ?

"…እግዚአብሔር ይመስገን ብቻ ‼

34.7k 0 10 1.9k 1.9k

• አላችሁ አይደል…?

"…24/7 ቀንም ሆነ ማታ ነጭ ነጯን ብቻ… ፀዓዳ ሃጫ በረዶ የመሰለ ሳይሆን የሆነ እውነት ብቻ የሚነገርበት፣ አራተኛ ሳይሆን ትይዩ መንግሥት የሆነ ዘመዴ ሚዲያ የተሰኘ ሀገርኛ ሚዲያ መንገድ ላይ ነው። እየመጣ ነው ስልህ።

"…ነገ በእለተ ቀዳሚት ሰንበት እኔ ጮቄ ተራራ ላይ ሆኜ እናንተ ባላችሁበት ሆናችሁ ከእኔ ከዘመዴ ጋር ይሄን ህልም የምታዋልዱ ወዳጅ ዘመዶቼን ስመዘግብ ነው የምውለው።

"…ከፌስቡክ ዘመን በፊት በመጽሔትና በአርማጌዶን ቪሲዲና ካሴት የምታውቁኝ፣ በእውነት መንገድ ላይ ስሮጥ ከግራና ከቀኝ ቆማችሁ ድንጋይም፣ አበባም ስትወረውሩብኝ የቆያችሁ በሙሉ ነገ እፈልጋችኋለሁ።

"…አዳዲስ መፍቻ፣ አዳዲስ ፋስና መዶሻ ይዤ የጠመመውን እነቅል ዘንድ፣ የላላውንም አጠብቅ ዘንድ የምትፈልጉ ወዳጆቼ በሙሉ ነገ አንዳንድ ነገር እናወጋልንና ለውይይት ተዘጋጅታችሁ ጠብቁኝ።

"…300 ጌዲዮናዊ ሠራዊት እፈልጋለሁ። የፈራ የደነገጠ ከገልአድ ተራራ እየመለስኩ፣ እንደ ውሻ በውሻ ጠባይ የሚመላለሰውን እየቀነስኩ 300 ጌድዮናዊ ሠራዊት ይዤ ወደፊት እገሰግሳለሁ። 300 ሰው ብቻ። አከተመ።

"…የኢትዮጵያን ትንሣኤ የምናበስርበት፣ የፈረሱ ገዳማትና አድባራትን መልሰን የምንገነባበት፣ ድንቅ ድንቅ ተግባራትን የምንፈጽምበት፣ ራሴ የምመራው የቴሌቭዥን ጣቢያ ለማዋለድ እንመክራለን። ነገርኳችሁ ከጀመርኩ ጀመርኩ ነው። ከነከስኩም ነከስኩ ነው ሳላደማ አልመለስም። አልፋታም። እየመጣን ነው።

"…ግራፊክ ዲዛይነሮች፣ የአይቲ ባለሙያዎች፣ ባለ ሀብቶች፣ መንፈሳዊያን፣ ጋዜጠኞች ሌሎቻችሁም ሁሉም ትፈለጋላችሁና ተዘጋጅታችሁ ጠብቁኝ።

• ዘመዴ ነኝ ከጮቄ ተራራ።

42k 1 18 173 2.3k

መልካም…

"…በዛሬው ርእሰ አንቀጼስ ጓ 😡 ብው ያሉት 3 ደርዘን ማለትም 36 ፍሬ ሰዎች ብቻ ናቸው። ሙንኡኖውኖ የቀነሱት? በሰላም ኖ…? …ቆይ እንዴኤኤ በኃይለኛው ነው እንዴ የገባሁላቸው…?

"…ለማንኛውም የእኔን ምልከታ ከጮቄ ከተራራው ላይ ሆኜ አቅርቤላችኋለሁ። አሁን ወደ ማረፊያ ጎጆዬ ልገባ ነኝ። ቀጥሎ የማደርገው የእናንተን በአስተያየት መስጫ ሰንዱቁ ላይ የምታሰፍሩት አስተያየት ቁጭ ብዬ አረቄ በጦስኜን እየጠጣሁ መኮምኮም ነው።

"…በእኔ ቤት የሓሳብ ነፃነት በሽ ነው። ብትናደዱ፣ ብትበሳጩብኝም ኋላ ተቀስፋችሁ ከምትቆጩብኝ ልክ እንደ ጥልምያኮስ አማኑኤል አብነት በጨዋ ደንብ የተቃውሞ ሓሳባችሁን ማንሸራሸር ነው። እሱ ነው የሚያዋጣችሁ። የሚያዛልቃችሁም።

• ዘመዴ ነኝ ከጮቄ…1…2…3…ጀምሩ…

44.3k 1 9 270 1.2k

👆⑤✍✍✍ "…ከመተኛቴ በፊት እስቲ ትንሽ ቆስቆስ ቆስቆስ መርፌም ወጋ ላድርጋቸው ብዬ የሆነች ቃሪያ በሚጥሚጣ የሆነች ፖስት ለጠፍኩ። በሚጥሚጣ መልክ እሳት ላይ በተን ስላደረግኩት የሚጥሚጣው ሽታ የትናየት ካናዳ ድረስ ሄዶ ጥልምያኮስ አማኑኤል አብነትን አጨናበሰው። ተጨነባብሶም አልቀረ አማኑኤል አብነት ኮመንት ሰንዱቄ ውስጥ ገብቶ እንዲህ አለኝ። "…እየተኛህ፣ ለነገሩ ሆድ አያስተኛ ብልፅግና ባላሰህ ልክ ተንፕስ! ሰርተህ ብላ! ስለአማራው ስለማይመለከትህ ከአንተ ጋ ንግግር የለንም ብለን ፋይል ዘጋን እኮ 😀 ላሽ እዛው! እዛው በጠበልሽ እንጅ ጆተኒ! አለኝ። እኔም አስቀድሜ ሰባት ጊዜ በማማተብ፣ አንድ አቡነ ዘበሰማያትና አንዲት ሰላምለኪ ጸሎተ ማርያም አድርሼ፣ ድርሳነ ሚካኤሌን አጠገቤ ካደርኩ በኋላ የእኔንና የእሱን ፎቶ በፔጄ ለጥፌ የነቆራ ደረጃዬንም ከፍ አድርጌ ለጨሰው ለአማኑ እንዲህ ብዬ ምላሽ ሰጠሁት። "… "…የእኔ ጥልሚያኮስ አማኑዬ… የኡጋንዳው ወዳጄ። ካናዳ ገብተህም አልቀላ ያልከው እንዴት ነህልኝ።

"…በቃ ተደብቆ መቀጥቀጥ አላስችል ብሎህ መሰስ ብለህ ከቤቴ መጣህ አይደል? አየህ እኔ ዘመዴ በጨዋ ደንብ ቀለል ያለ ስድብ እንደ ጆተኒ፣ ከረምቡላ ያለ ስድብ እየተሳደብክ እንኳ ቤቴ ክፍት ነው። 😂 …ስወድህ እኮ አንተው ራሱ ታውቃለህ አይደል? የጋሽ የበላይነህ ክንዴ ገንዘብ እንዴት እንዴት እያደረጋችሁ ነው ባክህ ጥልሜክስ? ካነሳችሁ እንዲጨምርላችሁ እነግረዋለሁ እሺ? አይዞኝ።

"…አማኑዬ ምነው ግን የዛሬውን የምዕራብ ጎጃሞ ልጆችን ሹመትና የሹመት ደብዳቤ በገጻችሁ መለጠፍ ችላ አላችሁ? …የሴራ ጓድህ ጥላሁን አበጀስ ምን ሆኖ ነው ሲጨሰ የዋለው? ደግሞ ቲክቶክም፣ ፌስቡክም ላይ ቀዘቀዛችሁብኝሳ። ተንቀሳቀሱ እንጂ።

"…በተረፈ አማኑ በሰኔ 15 ጉዳይ መድረሻ ሲጠፋህ፣ ምድር ስትጠብህ የነበረውን ሂደት አስታውስ። የጊዜ ጉዳይ ነው የእጅህን ታገኛታለህ። አስታወስክ አይደል ሽንቶ። ደግሞ ዘመዴ ምን አለ በለኝ እያየኸኝ ፀረ ዐማራ ፋኖ በጎጃም የሆነውን ሸንጎና የትግሬ ዲቃላ ሁላ ነቃቅዬ ባዶ ቀፎህን አስቀርቼህ ነው የምወጣው። ከጎጃም።

"…እናስይዝ ሰው ሁሉ ይፍረደን ለዐማራነት የእኔ መልክና የአንተ መልክ ለሕዝብ ይቅረብና ፍርድ ይሰጥብን። እኔ ጃልቆቱ ወዲ አስገዶም እና አንተን ሕዝብ ይዳኘን።

• ፍረዱን… 🙏🙏🙏 ብዬ ለጠፍኩ።  

"…አማኑም መተኛት አቅቶት የሆነች የንዴት ማስታገሻ ሞነጫጭሮ ለይኸነው የሸበሉ ይሰጠዋል። ሥጋ ቆራጩም እንደወረደ ይለጥፈዋል። ከዚያ ወዲያው አማኑኤል ከስር ለሸበሉ ኮመንት ላይክ ገጭቶ ሰጥቶ ራሱን በራሱ አርክቶ ተደስቶ እፎይ ይላል። ጠብደሉ ብአዴን ካድሬ ታመነ መኮንን ራሱ ከሊቱ 9 ሰዓት ሳይተኛ እዚሁ እኔን ሰይፍ አስይዘው ኡኡ ሲሉ ያደሩበት ልጥፍ ስር ሪአክት አድርጎ ታይቷል። የሚያስቀው ደግሞ በእኔ በዘመዴ የሴራው አባት፣ የሰኔ 15ቱ ወንጀለኛ አማኑኤል አብነት ስለተቀደመ ጨጓራው ጨሶም እንኳ ምንም እንዳልተፈጠረ በኢሞጂ ሲገለፍጥ ይውላል። ውስጡን እንተዋወቀለን። በቃ ተቀድሟል። ተቀድሟል ጎጄ ንቅትቅት ብሏል። ወግድ ብአዴን ብሎ እንደ ንሥር እየታደሰ ነው። ቪቫ ዘመዴ የብአዴን ለቅሶ ዕዳው ገብስ ነው። በእስክንድር ድራማ የሚታለፍ መስሎት ነበር ወይ ፍንክች ወደ ፍልሚያው ሜዳ በግዱ ገብቷል 😂። ብራቮ ዘመዴ፣ ወጥር ብሎኛል ጎጄ መለኛው። በጣም የሚገርመው ነገር 1 ወር ሙሉ ጃል ቆቱ ልኩ ተነግሮታል ይሉና በማግስቱም ዘመድኩን ብላ ብላ ደብዳቤ መለቅለቃቸውን ይቀጥላሉ። አንተ ዘመዴ ጃልቆቱ ወዲ አስገዶም በአገው ሸኔ በቅባቶች ቤት ልክህ ግን መቼ ነው የሚሞላው? ብዬ ራሴን እየጠየቅኩ ነው።

"…ሲጠቃለል… አሁን ጎራው እየለየ መጥቷል። ዘመነን ፈርተው የነበሩት የምዕራብ ጎጃምም፣ የምሥራቅ ጎጃምም፣ እንዲሁም የአገው ልጆችም ንቅትቅት ብለዋል። ስለዚህ ቅባቴ መናፍቆቹ እነ ጥላሁን አበጀና መዓረይ አዲስ ፕሮጀክት ፈጥረው በአዲስ አጀንዳ ሊመጡ ጨርሰዋል። ይሄንንም እዚያው ጮቄ ሆኜ ነው የምስማው። ቀጣዩ የእነ መዓረይ አጀንዳ እዚያው ጎጃም ውስጥ ተዋልዶ፣ ተዛምዶ፣ ተጋብቶ በፍቅር፣ በአንድነት፣ በሰላም የሚኖረውን ዐማራና አገው ማፋጀት ነው። አገውና ዐማራ የሚል እሳት በእነ አስረስ ቡድን ይለኮሳል። የብልጽግና አጀንዳ በአስረስ፣ ጥላሁን አበጀ፣ ማርሸት እና አበጀ በለው በኩል የጎጃምን ዐማራና አገው ደም የማቃባት ሴራ በራሳቸዉ በሴራው አከፋፋዮች በግልፅ ይጀመራል። ጠብቁ አልኳችሁ በቅርቡ ይጀምሩታል። እስከ አሁን ዐማራውን ሲገድሉት ዝም ስላለ አሁን አገው እየተመረጠ ይገደላል። ከዚያ ራሳቸው ገድለው ማሟረት፣ ማለቃቀስ ይጀምራሉ። አገውና ዐማሮች ይሄንንም በጥበብ እንደሚያልፉት በሙሉ ልቤ እርግጠኛ ሆኜ አፌን ሞልቼ እናገራለሁ። እመሰክራለሁ። የእኔ መዝሙር ቤት ደንበኞች የነበሩት የአገውና የዐማራ ልጆች ነበሩ። ዐማራና አገው ማለት የአንድ ሳንቲም ሁለት ገፅታ ሳይሆን የአንድ ሳንቲም አንድ ገፅታ ናቸው። መለያየት አይቻልም። ወያኔ ትግሬ አገው ሸንጎን በመመስረት፣ ኦሮሙማውም ያንኑ አገው ሸንጎን የኩሽ ሕዝብ ነህ በማለት ቀድሞ በማህበረ ቅዱሳን ሳለ ወዳጄ የነበረውን እነ ቀሲስ ስንታየሁ የእኔአባትን ናዝሬት ወስዶ በማሰልጠን፣ ከዐማራ ጋር ለማጋጨት በብዙ ተደክሟል። ነገር ግን ወፍ የለም።

• ማሳሰቢያ፦ እናንት ጎጃም ዐማራ እና አገው ፋኖዎች ሆይ! በፋይናንስ ሹመቱ ምክንያት ፀጉራቸውን ሲነጩ ያደሩትን የብአዴን ልጆች በንቃት ተከታትላችሁ ደም አፋሳሽ ሴራቸውን በተባበረ ክንድ ታፈርሱት ዘንድ በጀግናው በላይ ዘለቀ አጥንት እማፀናችኋለሁ።

• ዘመዴ ነኝ ከጮቄ ተራራ…

• እንግዲህ አንደዜ ነክሻለሁ። ከነከስኩ ደግሞ ነከስኩ ነው ሳላደማ እንደሁ አልመለሳትም። 

• ድል ለዐማራ ፋኖ…!
• ድል ለተገፋው ለዐማራ ሕዝብ…!

~ • ይደፈርሳል… ግን ደግሞ ይጠራል…✊

•••

ሻሎም…!  ሰላም…!

ዘመድኩን በቀለ ነኝ።
አሸበርቲው/አስነቀልቲው
ጥር 23/2017 ዓም
ከራየን ወንዝ ማዶ።


👆④✍✍✍ …በቴሌግራሜ የሚፈለጉትን ተመርማሪ የወርቅ እንቁላል ጣይ ዶሮዎቼን በመርፌ ጦማሬ ጠቅ እያደረግኩ ማስለፍለፌ አልቀረም። ይኸው ጉብኝቴ ድፍን አንድ ወር ሞላው። እነርሱ ግን 24 /7 ቴሌግራሜን መሳለም ግድ ሆኖባቸው እዬዬ እንዳሉ ነው። ምክንያቱ ደግሞ ነፍስና ሥጋቸው የተሰፋበትን ክር ስላገኘሁት ነው። ሕዝቡን ከዘመዴ ፔጅ ውጣ ይሉትና እነሱ ግን እኔ ቤት ተወዝፈው ዘጭ ናቸው። ሕዝቡን ዘመዴ ቤት ግቡና ተሳደቡ ይሉና ሕዝቡ እውነት መስሎት ገብቶ ሲሳደብ እኔ ዘመዴ ቀስፌ አባርረዋለሁ እነ አማኑኤል አብነት ግን ራሳቸውን ተቆጣጠረው በእኔ ቤት ሓሳባቸውን በነፃነት ያንሸራሽራሉ። የትናንት ምሽቱ የአማኑኤል በእኔ ቤት ማለቃቀስ ምስክር ነው።

"…አማኑኤልን እንቅልፍ የነሣው ምንድነው? ያልን እንደሆነ የሴራውን ህብለ ሰረሰር ስላገኘሁት፣ ስለነካሁት ብቻ ነው። እኔ ጎጃም ገብቼ መንጎማለሌ በደንብ የገባው ሴረኞቹን ነው። እነሱ ቁስላቸውን ስነካካው ወይ አላፈረጠው፣ ወይ አልተወን ብለው እየቃዡ እየተወራጩም ነው። ለምሳሌ ትናንት የሆነውን እናንሳ። ጥላሁን አበጀን መርህ አልባ ትግል ያስባለው። ኡፍፍ ስል ከአፌ እሳት ነው የሚወጣው የሚል የብስጭት፣ የጨጓራ መንደድ እና መቃጠል መልእክት እንዲያስተላለፍ ያደረገው ነገር ስለገጠመው ነው። ትናንት መቼም አገው ሸኔ ሲጨስ ነው የዋለው። አዝማሪዋማ ከማበዷ የተነሣ በሴራ የተገደለውን የአርበኛ ፋኖ ዮሐንስን ፎቶ ለጥፋ የጋለሞታ ልምዷን ተጠቅማ በአሽሙር "ብዙዎቹ አንተን መሆን ቀርቶ መምሰል አቅቷቸው በስልጣንና በጥቅም እሳት ሲተነፍሱ እያየን ነው😭

ጎበዝ ይምት ፈሪ ይኑር ባሻው
አተላ መሸከም ይችላል ትከሻው ❗
Yohannes Alemayehu Temesgen ❤❤😭 በማለት መስደብ የፈለገችውን አካል ሰድባ የአዞ እንባዋን ስታፈስ ነው የዋለችው። ይሄ ለሌላው አይገባውም። ይሄ የሚገባው እኔንና እኔን ለመሰሉት ብቻ ነው። ከዚህ በፊት ቀሚስ አልብሳ ፎቶውን ዘቅዝቃ የሰደበችውን ሰው አስታውሱ። ገባችሁ ኣ…? ኢንዴዣ ኖ።

"…ትናንት የዐማራ ፋኖ በጎጃም አዲስ ሹመት ይሰጣል። የፋይናንሱንም ሥልጣን ከሕጻን ደፋሪው ከማንቼ ነጥቆ ለምዕራብ ጎጃም ልጆች ይሰጣል ድርጅቱ። ወዲያው እኔ ከጮቄ ተራራ ላይ ሆኜ የምሥራቅ ጎጃሞቹ የሸበሏን ልጆች የፌስቡክና የቴሌግራም ገጾች ማየት ጀመርኩ። አስረስ መዓረይ ጭራሽ እብድ ብሎ ወደ አባይ ሸለቆ ወደ ዘመዱ ወደ ማስረሻ ሰጤ ቀጠና ሄዷል። የሆኑ ባዶ እጅ ወጣቶች ሰብስቦም ፎቶ እንደ አብይ የፎቶ ቦለጢቃ ሊለቅብን ተላልጧል። ሕዝቤስ? ሕዝቤ የሰጠውን ኮመንት ገብታችሁ እዩልኝማ። ልፋቴማ በከንቱ አልቀረም። መሬት ጠብ አላላም። አስረስ መዓረይ እንዲህ ያለኝን ትናንት ነው ያስታወስኩት።

• "ዘመዴ አንተ ግን ዋጋህን ታውቀዋለህ? እ
~ አላውቀውም
• አንተ ያለህ ዋጋ እንዲህ ነው ተብሎ አይገለፅም። አንዳንድ ሰዎች ዋጋቸውን አያውቁትም። አንተ በተለይ በመሬት ላይ ከገበሬ አንሥቶ እስከ ተማርኩ የሚለው 90 ምናምን ከመቶው ይቀበልሃል፣ ይሰማሃል፣ አንተ ተናገርክ ማለት አለቀ። እናም ዘመዴ "የፖለቲካ ካፒታሌን አደራ" ነበር ያለኝ። ቆይ ደግሜ እሰማዋለሁ። እናም የጎጃም ሕዝብ እንዳደመጠኝ ትናንት ገና ነው ያረጋገጥኩት።

"…የፋይናንስ ሹመቷ ጉዳይ ከፍተኛ ቀውስ ነው የፈጠረችው። እነ ይሄነው የሸበሉ ጭጭ፣ ዝም፣ ጮጋ፣ እነ አማኑኤል አብነት፣ እነ ከፍያለው ጌቱ፣ እነ እስማኤል ዳውድ፣ እነ ሰጣርጌ በሙሉ ጮጋ ነው ያሉት። ግንቦቴውና መሰሪው የዐማራ ፋኖ በጎጃምን ከአስረስ መዓረይ፣ ከአበጀ በለውና ከፓስተሮቹ ጋር አብሮ የቀበረው ይሁዳው ጥላሁን አበጀ፣ መጀመሪያ መርህ ይከበር ብሎ ጮኸ፣ እነ ዊክሊክ ራሳቸው ሲጮሁበት እኔም ያን ይዤ ቤንዚን ጨምሬ ክብሪት ስጭርበት ዊኪሊክ ቀውጢ ፈጠረ፣ እኔ ላይ ሲያላዝን እንዲውል አደረግኩት፣ ቆይቶ መልሶ ጥላሁን አበጀ ድሮ ኤርትራ በረሀ የብርሃኑ ነጋ ካልሲ አጣቢ ሳለና የዐማራ ልጆችን መከራ ሲያበላ፣ ሻአቢያም ፍየል ስታስጠብቀው የተነሣውን ጫጩት ፎቶ ለጥፎ ልክ አሁን ምዕራብ ጎጃም በጉስቁልና እንደሚታገል ሰው አክት ለማድረግ "…ኡፍፍፍ እሳት " ነው የምተፋው በማለት የጨጓራውን በቃጠሎ መሽተት በይፋ ገለጸልን። ይሄ ሁላ ግርግር ፋይናንሱ እንዴት ከእኔ ወጥቶ ለሌላ ይሰጣል ብሎ ነው የሚያብደው። ይሄ ነጋዴ። ፋይናንሱ ሲያዝ ነው ሁላቸውም የጨሱት።

"…ወዲያው ባህሌን ብማለት እዚሁ ጀርመን የሚኖረው ገምሻራው ታመነ መኮንን ብሮዬ ጎጠኛው ዓሰግድ በሚለው የብዕር ስሙ በሚጠቀምበት የፌስቡክ ገጹ እኔን ስሜን ጠቅሶ ጓ አለ። እንዲህም ብሎ ጻፈ። "…ዘመድሁንን ለማስደሰት የሚደረግ ሹም-ሽር እንደ ዘመድሁን በረንዳ ለማደርኳ እድል ላይሰጥ ስለሚችል ጥንቃቄ ያስፈልጋል!!! የደም ዋጋ ደም ያስከፍላል!!! ብሎ እሪ አለ። ይሄን የታሜን ልጥፍ ተከትሎ የሚመጣ ኮመንት እጠባበቅ ጀመር። ወዲያው የዘመነ ቀኝ እጅ፣ አስረስ ዘመዴ እሱን ከሰው ቆጥረኸው ያለኝ ግርማ አየለ ከች አለ። በእውነቱ ከሆነ ለመጀመሪያ ጊዜ እኔና ዘመነን ያስተዋወቀን እሱ ነው። ክሬዲቱን ልወስድበት አልፈልግም። በዚህ አመሰግነዋለሁ። በኋላ ላይ ነገሩ ሳይገባው ቢሰድበኝም "አባታችን ሁላ እያለ ያከብረኝ የነበረ ቅን ልጅ ነው። ዘመዴ ዘመነን አናግራው፣ ተገናኙ ያለኝ ግርምሽ ነው። እናም ግርምሽ ከች አለ። አለናም ታመነ ብአዴኑን ያፋጥጠው ጀመር።

• Girma ga ~ ምን ማለት ነው?
~ ጎጠኛ ዓሰግድ ~ Girma GA አይነበብም?
• Girma ga ~ ጎጠኛ ዓሰግድ ነገ የማትደግመውን ነገር ባትፅፍ ጥሩ ነው።
~ጎጠኛ ዓሰግድ ~ Girma GA ከሚገባው በላይ አወቅሁ ያልህ አልመሰለህም? …ተባብለው ተፋጠጡ። ግርምሽም ጭጭ አለ። ታሜም ስለ ዕቁብ ብር ማውራት ጀመረ። ብአዴንና የዐማራ ፋኖ በጎጃም ፋይናንሱ ላይ በኃይለኛው ተላለፉ። ታሜ አላስችለው ስላለ፣ ስለከነከነውም ቀጣዩን ፖስት ለጠፈ። "እንበልና የተሰበሰበ ብዙ የእድር ገንዘባችሁን የበላ ግለሰብ አዲስ የጀመራችሁት እቁብ ዋና ገንዘብ ያዥ ሆኖ ቢሾም ምን ይሰማችኋል??? ከምሬ ነው ስሜታችሁን አካፍሉኝ እስኪ🤔 ብሎ ኡኡ አለ። የፋይናንስ ሹመቷ አንጫጫቻቸው። ይሄነው የሸበሉም መናገር ፈርቶ ላይክ ይገጭ ጀመር። ኤታባሽ ሸንጎ፣ ኤት አባሽ ብአዴን። አልፋታሽ።👇④✍✍✍


👆③✍✍✍ "…እዚህጋ የማርሸትን በልበ ሙሉነት ሕዝቡ ይፍረድ የሚለውን ደጋግማችሁ አንሰላስሉት። መዓረይ ወንድሜ እንዲህ በልበ ሙሉነት ሲናገር ዳኛው የተጎዳው ሕዝብ ያነጻጽራል፣ የዐማራ ፋኖ በጎጃም ውስጥ ባሉት በእነ ፓስተር ዳዊት፣ በእነ ፓስተር ተሴ፣ በእነ ማዕረይ፣ በእነ አበጀ በለው፣ በእነ ጥላሁን አበጀ አማካኝነት ገደሉን፣ ከተሞቻችንን ጥለን እንድንወጣ ሜዳ እንድንቀር፣ ልጆቻችን እንዳይማሩ አደረጉብን፣ አስተማሪዎቻችንን ገደሉብን፣ መሪ ልጆቻችንን በልተው ጨረሱብን፣ አስራቡን፣ ማዳበሪያ አሳጡን ወዘተ በማለት ወደ ማነጻጸሩ ይሄዳል። በአንጻሩ ደግሞ እነ እስክንድር ከነዚህ ጠላቶች ጋር በመተባበር፣ በመደራደር፣ በመነጋገር፣ የሕዝቡን ችግር በመፍታት ማዳበሪያ ጭምር እንዲያቀርቡ አደርጎ አሳረፈን ብሎ ለማነፃፀር ይገደዳል። ማሬ ሆን ብሎ ነው የደነቀራት። የነ አሜሪካን የሴራ ስንዴም ለሕዝቡ ሲያደርስ፣ ሕዝቡ የነእስክንድር ቡድን በነፍሳችን ደረሰልን፣ ለራባችንም ስንዴና ዘይት ወዘተ ሰጠን ብሎ የዐማራ ፋኖ በጎጃምንም ሆነ ሌሎቹን ድጋፍ በመንሳት፣ በስተት እንዲያዳክም ነው የተናገራት የሚመስለኝ። ያኔ የሁሉም ግዛት ፋኖ በከፍተኛ ሁኔታ ይጎዳል። ወታደሩም ወደነ እስክንድር የሚሄድበት ዕድል ይመቻቻል። የሰላም ጥሪውን የተቀበሉና ያልተቀበሉ ተብሎ በክልሉ ውስጥ እርስ በእርስ ይጠዛጠዛሉ። ደረጀ በላይ ከእነ ሀብቴ፣ መከራው ከነ ደሳለኝ፣ ሙሀባው ከእነ ምሬ፣ ጎጃም ማስረሻ ከነ ዘመነ ሊታኮሱ ይችላሉ። በዚያ ላይ ሃይማኖት የሚጨመርበት ቦታም ይኖራል። አፈንጋጭ፣ ፀረ ሕዝብ ወዘተ ተባብለው ከላይ ከታች እሳት እንደ ገና ዳቦ ይነድባቸዋል። በዚህ ላይ እነ ህወሓት፣ እነ ሸኔ፣ የበአዴን ፋኖም በሰፊው ተዘጋጅተዋል። መከላከያው ከነ ድሮኑ አለ። ከነእስክንድር ጋር የተወያዩት ተመካክረው በነ እስክንድር በኩል ላፈነገጡት ማማለያ ማቅረባቸውና ኃይል ማጠናከራቸውም አይቀርም።

"…ፋኖ ማርሸት ይሄን ሳያውቅ፣ የሴራው ተካፋይ ሳይሆን በደመነፍስ የተናገረው ከሆነ ስህተቱን ማረሚያው መንገድ አንድና አንድ ብቻ ነው። እሱም የቀድሞውን ሕዝብ አሳታፊ የዐማራ ፋኖ በጎጃምን ሕዝባዊ እንቅስቃሴ መሬት ላይ ድጋሚ ማውረድና ጠንካራ ሥራ መሥራት። ከፎቶ ቦለጢቃ፣ ከሐሰት ፕሮፓጋንዳም ርቆ ሃቀኛ ትግል መሬት ላይ መፍጠር። በዐፋጎ ውስጥ ያሉትን ከጠላት ጋር ተዋግተው ጠላትን መግደል ኃጢአት ነው ብለው አመራር ላይ የተቀመጡትን የብልፅግና ወንጌል ሰዎች ከአመራርነት ጠራርጎ ማንሳት። ሌቦችን፣ ወንጀለኞችን፣ በሌላ ክፍለጦር ውስጥ ሰርቀው፣ ገድለው፣ መዝብረው ሲያበቁ፣ በዘመድ አዝማድነት፣ በእወቅልኝ ልወቅልህ፣ በጓደኝነት፣ በጎጥ፣ በሰፈር ልጅነት፣ በብአዴናዊ ጠባይ መልሰው የተሾሙትን ማውረድ። እንደገናም ሕዝቡን በተለያየ መንገድ መያዝ፣ መካስ፣ ማገዝ፣ የጎዱት፣ የበደሉት ነገር ካለ ሕዝቡን ይቅርታ ጠይቀው መካስ፣ ርዳታ ጭምር ቢመጣ ይቀበሉ ግን በሆዳቸው እንዳይታለሉ ሕዝቡን ማንቃት ብቻ ነው። ይሄ ነው ዳግም ነፍስ ሊዘራባቸው የሚችለው እንጂ እነ እስክንድር ቀጥሎ የሚመጡበት ማማለያ ዶላርን ጨምሮ ቀላል አይሆንም። ስለዚህ በአራቱም የፋኖ አደረጃጀት ውስጥ የሕዝቡን ከፍተኛ ሮሮና ችግር መፍታት፣ ሕዝቡ በጥቅም እንዳይታለል በማስተማር ከፍተኛ ሥራ መሥራት አማራጭ የሌለው ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር ነው የሚሆንባቸው። ያን ካላደረገ የጎጃም ፋኖ መጪው ጊዜ ቀላል አይሆንለትም።

"…እነ ማርሸት ምንም ምድር ላይ በሕዝቡ ላይ ግፍ ካልሰሩና ሚዲያ ላይ ብቻ ከሆነ ሴራው የተሠራው አሳሳቢ አይሆንም። ያለበለዚያ የሚያደርጉት በተቃራኒው ነው። እነ ማርሸት እነ እስክንድር ጥሩ እስኪሠሩ ይጠብቃሉ። ከዚያ በእነርሱ ተቃራኒ እነ መዓረይ ሕዝቡን ያማርራሉ። ከዚያ ለሕዝቡ በሰጡት የመፍረድ የዳኝነት ሥልጣን ሕዝቡ ፍርድ መስጠት ይጀምራል። ሕዝብ ሲፈርድ ደግሞ "የሰው ልጅ በእንጀራ ብቻ ተወስኖ አይኖርም በእግዚአብሔርም ቃል እንጂ" ብሎ ለማለት አቅም ያጣል። ያነዜ የዐማራ ፋኖ በጎጃም፣ በወሎ፣ በጎንደር እና በሸዋም ጭምር ሊዋጡ፣ በሕዝብ ፍርድ ሊዳኙ ይችላሉ። ከእንደገና ነገሮችን ለማስተካከል ሲጥሩ ድሮኗ እና ጀቶቹ የማይሠሩበት ግዜ አቢይ በፋኖ ሳይጠቃ ክረምቷን በሰላም ያልፍልና ከዚያ በጋው ሲመጣ "ሰማዩም የእኛ ነው" በማለት አራጅ አቢይም የሚተማመንበትን ድሮን ቆስቁሶ በታንክ ጭምር የዐማራን ሕዝብ ይጨርሳል። ለፋኖ ከክረምት የተሻለ ማጥቂያ ግዜ ይኖረዉ ይሆን? ስለዚህ የማርሸት ንግግር በኔ ግምት ሹፈት እንጂ ጤነኛ አይመስለኝም። ጉድ እኮ ነው። በአሁን ቁመና ሕዝቡ ይፍረድ የሚለው ያ ባሕርዳርን ከብቦ አየር መንገዱን የዘጋው የጎጃም ፋኖ ዛሬ አለ? ያ ባህርዳርን ከብቦ ብአዴንን አዲስ አበባ ያሰደደው አንድነቱን፣ ጀግንነቱ ያስፈራ የነበረው የአፋጎ ፋኖ አሁን አለ? አንድ ብንሆን ስንዝር ነበር የቀረን ሲል የነበረው ዐፋጎ ዛሬ ሌሎቹ ሲጠነክሩ ለምን እሱ ግንባር ቀደም ሳይሆን ለምን አፈገፈገ? ብሎ የሚጠይቅ አንድ ሁለት ሰው እንኳ እንደማይጠፋ ለምን አያስቡበትም? ስለዚህ የማርሸት ሕዝቡ ይፍረድ አባባል በራስ ላይ እንደ ማሟረት ነው የምቆጥረው። በፈረንሳይኛ እንዲህ ማለት ሕዝብ ሆይ ይኸው ስላማርነህ ፍረድብንና እነ አቢይና አሜሪካ ይሳካላቸው ማለትነው ባይ ነኝ። ግምቴ ትክክል ባይሆን እመርጣለሁ ከሆነ ግን ማርሸትም የተሳካለትና የተጨበጨበለት ሴረኛ ሆኖ ተልዕኮውን በጥበብ ተወጣ ማለት ነው።

"…የማርሸትን የኋላ ፋይል ወደ መመርመር ስትሄዱ ከጀርመን ድምጹ ጋዜጠኛ ከነጋሽ መሀመድ ጋር ያደረገውን ቃለ ምልልስ ማስታወሱ ሸጋ ነው። እዚያ ላይ ነው ማርሸት ጀግና ሆኖ ለሕዝብ የተገለጠው። ያን ቃለ መጠይቅ ማን እንዳመቻቸ ባይታወቅም ለሥራዬ ያመቸኝ ዘንድ እነ አስረስ መዓረይ ማርሸትን ቅጣቱን አንሥተው ወደ ቀደመ ቃል አቀባይነቱ ይመልሱት ዘንድ እኔ ዘመዴ አስረስ መዓረይን ጥያቄ ባቀረብኩለት ጊዜ "እንዲሁ እንደ አጋጣሚ ሜዳ ላይ እኔና እሱ አብረን ተቀምጠን እኮ ነው ተደውሎለት ኢንተርቪውን የሰጠው፣ ያውም ሳይዘጋጅበት እኮ ነው ያለኝን አልረሳውም። ስለዚህ ማርሸት ቀድሞውኑም የተዘጋጀ ነው ማለት ነው። ቀጥሎ የባልደራስ፣ የግምባሩና የዲሲ ግብረ ኃይሏ ወሮ ሕይወት የማርሸት አጎት ዶክተሩ ካቀራረቧት በኋላ በእነ ሀብታሙ አፍራሳ ምክር ጥያቄ ተሰጥቷት "በዐማራ ሕዝብ ላይ ጄኖሳይድ አልተፈጸመም" ብሎ የተናገረውን ስናስብ ማርሸት ተሳስቶ ነው ብሎ ለመፍረድ ይቸግረኛል። ማርሸት በዐማራው ትግል ብዙ ፋውል የሠራ ልጅ ነው። አንደበቱን የሚገራው ስለሌለ እንዳሻው፣ እንደልቡ ነው። የአረጋ ከበደን መኪና ማረክን ባለ ጊዜም ሞቅ ብሎት "አቢይ አሕመድ በሕርዳር ቢመጣ እንዲህ ነው የምናንቀው" ብሎ ተናግሮ አቢይ አሕመድ ባህርዳር መጥቶ ብሽክሊለት ሁላ ተጫውቶ የሄደውን ማሰብ ግድ ይላል። እናም ማሬ መዓረይ ማርሸት ፀሐዩ ምጥንቃቅ ቢገብርሎ ፅቡቕ ኢዩ።

"…በተረፈ በጎጃም ለውጦች እየታዩ ነው። ጎጃም ከገባሁ 1 ወር ቢሞላኝም፣ የእኔን ጎጃም መግባት ተከትለው ኡኡ ቁቁም ብለው ሀገር ይያዝ ብለው የነበሩት፣ ኋላም ዘመዴን አጠፋነው፣ ጎጃምን መንካት እንዲህ ዋጋ ያስከፍላል፣ ከመረጃ ቲቪ አስወርድነው ብለው ራሳቸውን በራሳቸው ሲያረኩ መክረማቸው ይታወቃል። ዘመድኩን እንኳን ከሳታላይት ቴሌቭዥን ላይ ወረደ እንጂ በቴሌግራሙ እና በቲክቶኩ ላይ የፈለገውን ይዳክር፣ ይሞንጭር፣ ከአሁን በኋላ እሱን ስሙን አናነሳውም ብለው ምለው ተገዝተው ለሕዝባቸው ቃል ቢገቡም እኔ ግን…👇③✍✍✍


👆② ✍✍✍ …ዛሬ ለነፃነት" ብሎ ድብልቅልቁን ያወጣው። መለስን ሌባ፣ ልደቱን ማንዴላ ብሎ ጨፈረ። ቆይቶም መለስን ማንዴላ፣ ልደቱን ዳውላ ያለውም ራሱ ይሄው ሕዝብ ነው። እናም እነ አማሪካና አቶ ታዬ አጽቀሥላሴ፣ እነ አገኘሁ ተሻገር ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋን እንደ ጃል ሰኚ የዐማራ ሙሴ አድርገው ከተፍ አድርገው ሊያመጡት ጨርሰዋል ማለት ነው።

"…ጮቄ ላይ ሆኜ ወደ ገመገምኳቸው ሌሎች ጉዳዮች እንሂድ። በእስክንድር የተቀደሙ የመሰላቸው የጎጃሞቹ እነ መዓረይ ማርሸት ፀሐዩን ወደ አንከር ሚዲያ ልከው መሳይ መኮንን ጋር ሲናኮሩ ነው የታዩት። እነ መሲና በቀደም ዕለት ከአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ጋር በነበረው ቆይታ የእስክንድርን የድርድር ወሬ ማንፀባረቅ በስጨት ያደረጋቸው መስለው የሠሩትን ፕሮግራም ደግማችሁ እዩትና የለጠፈውን ሓሳብ ተቃውሞ ሲበዛበት ጎመን በጤና በማለት በማንሣት የሚታወቀው መሳይ መኮንን ወዲያው እንዴት ፋፍሕዴንና አፋሕድን ለመስቀል፣ ለማግነን ሲላላጥ አይታችሁ ታዘቡ። መሳይ ማርሸትንና ደረጀ በላይን ሲጠይቅ የነ እስክንድርን ቡድን ከፍ ለማረግ ሲላላጥ ይታያል። ፋኖ ደረጀ ሁሉም የፋኖ አደረጃጀት ወደእኛ ካልመጣ አይሆንም ሲል ማርሸት ደግሞ "እነሱም ለአንድነቱ ጥሩ እየሠሩ ነው" ነው ብሎ ማኖ የነካው። የደረጀን ንግግር እንደቀላል ማየትም ዋጋ ያስከፍላል። ደረጀ በላይ እንደምንም ብሎ ጠንክሮ ያቺን ቃል በመናገሩ መሳይም ደረጄ በላይ የልቡን ስለተናገረለት "እግዜር ይስጥልኝ" በማለት ነበር የተሰናበተው። ማርሸትን ግን መሳይ ሲሰናበተው "አመሰግናለሁ" በማለት ነበር። በእነ ሀብታሙ አያሌው ተገፍቶ፣ ተሳድዶ፣ መድረሻ አጥቶ የነበረውን ውባንተ ብቸኛ በነበረ ሰዓት ቀርቦ ቃለመጠይቅ በማድረግ ዕውቅናና ተመልሶ የዐማራ ፋኖ ቦለጢቃን የመዘወር ዕድሉን ያገኘውና አጠገቡ በሴራ ቦለጢቃ ጥርሳቸውን ነቅለው የዳበረ ልምድ ባላቸው ጎምቱ ሰዎች የተከበበው መሲና የዐማራ ፋኖ መሪዎችን ከላይ ታች እንደ ጆተኒ ኳስ እያንቀረቀባቸው ነው።

"…ከምር ማርሸት ትናንት አሳዘነኝ። ቢጨንቀው "ሕዝቡ ይፍረድ ከኛና ከነ እስክንድር ማን እንደሚበጅ" እስከማለት ደረሰ። ይሄንንም ማርሸት ዝም ብሎ የተናገረው ነው ብዬ ላልፈው አልፈልግም። እንዴት ለለምትሉ የዓይን ሞራ ግርዶሽ ሞራችሁን ሰርጀሪ ሰርቼ ላሳያችሁማ። ማርሸት ያለው ነገር ከባድ ነው። መጥፎና ክፉ የሴራ ትብታብ ሆኖም ነው ለእኔ ለዘመዴ የታየኝ። የዐማራን ፋኖ የሚጎዳም ነጥብ አለው ብዬም እሰጋለሁ። ምክንያቱም ማርሸት ይሄን በድፍረት የሚናገረው ከምን ተነሥቶ ነው ብሎ ማየት ያስፈልጋል። ሲመስለኝ ይሄ ቃል የጎጃም ፋኖን አፈር ከደቼ የሚያስበላም ጭምር ነው። እነሱ አስቀድመው መከላከያና የብአዴን ፋኖዎች ተቀናጅተው በመናበብ የጎጃምን ሕዝብ በቀረጥ፣ በታክስ፣ በእገታ፣ በመድፈር፣ በመረሸን፣ በመጨፍጨፍ፣ በማገት፣ መምህራንን በመረሸን፣ ሀኪሞችን በመግደል፣ ነጋዴዎች ተማረው ሀገር እንዲለቁ በማድረግ፣ ካህናትን በመግደል የጎጃም ሕዝብ በዐማራ ፋኖ ላይ እንዲያማርር፣ እንዲያንጎራጉር ካደረጉት በኋላ ከጎጃም በሄደ ጠባቂ ብቻውን የቀረውን፣ በየትኛውም ዐውደ ውጊያ ተሳትፎ የማያውቀውን እስክንድርን "ሕዝብ ይዳኘን" ማለቱ ለእስክንድር አረንጓዴ የይለፍ መብራት እንደማብራት ነው የምቆጥረው። መጀመሪያም የነበረውን የዐማራ አንድነት "ዘመነ አቋርጦ ወጣ፣ ማርሸት በጠበጠ፣ አስረስ ለኃይለ ኢየሱስ ቀውሱ ሪከርድ እያደረገም፣ የዕለት የስብሰባ ውሎ ነገረ። ኃይሌ ጠሿም ለኤርሚያስ ዋቅጅራ እየነገረች አንድነቱን በጠበጡት። ማርሸት አሰግድን በልመና መለሰ፣ አሰግድም እስክንድር ካለ አልሰበሰም ብሎ ወጣ። ማርሸት ሲባረር የብሔራዊ ደኅንነቱ የጌታቸው አሰፋ ረዳት ከእስክንድር ጋር ጫካ የገባው፣ ግንቦት ሰባትንና ሻአቢያን በናይሮቢ ያገናኘው፣ ልደቱ አያሌውን ዱቄት ያደረገው መስፍኔ ተተክቶ እነ ኢያሱን አባረው፣ ማንም በሌለበት እስክንድርን መሪ አድርገው ብቅ አሉ። ይሄም ዜና በሰበር ዜና በስታሊን ገብረሥላሴ ዛራ ሚዲያ በድምፅ ሁላ ተዘጋጅቶ ቀረበ። እኔም ምኔ ሞኝ ነው በሰበር ዜና በመረጃ ቴቪ ገብቼ "ምርጫው ውሸት እንደሆነ" የድምጽ ቅጂ በመልቀቅ አፈር ከደቼ አበላሁት። ነገርየውንም ውኃ በላው። አሁንም የጎጃሙ አገው ሸኔና ቅባቴው ቡድን ከእስኬው እና ከስኳዱ ፋፍዴን ጋር ጥቅሴ እየተጫወተ ይመስለኛል። መርምሩት።

"…እንቅፋት የሆነው የሚመስለኝ አርበኛ ዘመነ ካሤ ነው። ፋፍዴኖችም፣ እስኳዶችም ዘመነ ካሤ ቢመራቸው፣ እስክንድርና ዘመነ ታርቀው ወደፊት ቢያመጧቸው ይወዱ ነበር። ነገር ግን ትልቅ እንቅፋት የሆነባቸው "ለዘመናት አገው ሸኔም፣ የጎንደር እስኳድና ፋሕፍዴን፣ ግንቦቴና ግንባሮቹ በዘመነ ካሤ ላይ ከሰኔ 15 ጋር ተያይዞ የጦስ ዶሮ አድርገውት ስለከረሙ፣ በዚህም ደም የመቃባት ያህል ቂም ስለተቆጣጠሩ አሁን ላይ ዘመነን መሪ ማድረግ ጣጣ እንደሚያመጣባቸው ዐውቀው እንጂ እንዲያ ቢያደርጉ በጣም ግልግል ይሆንላቸው ነበር። ባለፈው ረዳት ፍሮፌሰር ኢያሱ አባተ ከሰሎሞን አጣናው ጋር በስልክ ባደረጉት ውይይት ላይ የእስክንድርን ፈዛዛነት ጠቅሶ "ያ ወፍራሙ ወይፈኑ ቢሆን እኮ ይሄኔ በምላሱ ደረማምሶት የት በደረስን ነበር" እያለ የማልቀስ ያህል በቁጭት የሚናገረው እኮ ዘመነን ነው። ዘመነን ነው ወይፈኑ እያለ ይጠራው የነበረው። ፋፍህዴንም፣ አገው ሸንጎም በውስጥ እየተደራደሩ፣ እየተነጋገሩ ነው። የእነ ሀብቴ፣ ባዬ፣ ምሬ፣ ደሳለኝ ቡድን እንዳይቀድማቸው ነው የሚባዝኑት። እነ ፋፍዴን በጎንደርም፣ በወሎም፣ በሸዋም ነጥብ እየጣሉ ስለሆነ ያላቸው ተስፋ "እነ አስረስ መዓረይ ጎጃም አንድ ሆኖ ወደ ዐማራ አንድነት እንዳይመጣ ሽብልቅ ከትቶ ማደናቀፍ ነው" ይሄ በጣም ነው የተሳካው። ጎንደር፣ ወሎ፣ ሸዋም በሙሉ ተስማምተው፣ ዘመነ ካሤ መሪ እንዲሆን መርጠው፣ ጨርሰው አስረስ መዓረይ አይሆንም በማለት አንድነቱን እንዳይንቀሳቀስ ሽባ አድርጎላቸው እየጠበቃቸው ነው። ዘመነ ካሤንና ዝናቡ ልንገረውን አስወግደው ሲያበቁ አስረስን የዐፋጎ መሪ በማድረግ ወደፊት ሊያመጡት የነበረውንም እኔ ዕጢ ሆኜባቸው ከአፋቸው ላይ ላፍ አድርጌ አስቀርቼዋለሁ። አቤት እኔ እኮ በእነ ማዕረይ ጉዳይ ሲኦል የምገባ አይመስለኝም። ብሳል እንኳ ሲኦል የሚቀበለኝ አይመስለኝም።

"…የሰሞኗ ጨዋታ ምናልባትም ከቅርብ ቀን በኋላ እነ አጅሬ ብልጽግና፣ አማሪካ፣ የአፍሪካ ኅብረትና ወዘተ አንድ ላይ በመተባበር ወደፊት ሊያሰሙን የሚችሉት ነገር ይኖራል ብዬ እጠረጥራለሁ። የእስክንድር ቡድን ከዓለምአቀፉ አካል ጋር ያደረግነው ውይይት ነው እንጂ ድርድር አይደለም። ርዳታ ለማግኘት፣ መከላከያው ከክልሉ እንዲወጣ ለማድረግ ነው እንዳለ ሁሉ እነዚህም የውጭ ኃይሎች እና የእነ ታዬ አጽቀሥላሴው የስኳድ ቡድን የእነ እስክንድርን ቡድን ሓሳብ ደግፈው ለዐማራው ሕዝብ "በተስማማነው መሰረት" በማለት ማዳበሪያንም ጨምሮ ከፍተኛ ርዳታ ያቀርቡና ሕዝብን በደካማ ጎኑ በመያዝ እነ እስክንድር ምን ያህል ጠንካራና ዓለም አቀፍ ተሰሚነት ያላቸው እንደሆኑ በማሳየት፣ እንዲሁም የዐማራ ፋኖን ትግል ከሌላው ፊት ቀድመው እየመሩ ዐማራን በኦሮሙማ ለማስበላት፣ የምዕራባውያኑና የዓረቦቹን ዐማራውንና ኦርቶዶክሱን የማጥፋት ዕቅድ ይሳካ ይሳለጥ ዘንድ ከዚያም መጨረሻ ላይ እነሱ ክፍያቸውን ተቀብለው ለዐማራው የመከራ ዶፍ አሸክመው እነ እስኬው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግሥት ግምጃቤት ተቆጣጣሪ ዘበኛ አድርገው ሥልጣን አካፍልን ብለው ላጥ ይላሉ።👇②✍✍✍


"ርእሰ አንቀጽ"

"…ዛሬም እዚያው ጎጃም ጮቄ ተራራ ላይ ነኝ። ግራቀኙን፣ ከፊት ከኋላ የሚሆነውን እያየሁ ዘና ፈታ እያልኩ ነው። ጮቄ ተራራ ከፍ ያለ ሥፍራ ስለሆነ ባሻገር ጎንደር፣ ሸዋና ወሎም ይታዩኛል። ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ተፀንሶ ተወልዶ ወልቃይት በኮሎኔል ደመቀ መኮንን ጥበቃና የሰሊጥ ዘይት እየተጋተ በእንክብካቤ ያደገውንና በቀንጭራ በሽታ ተጠቅቶ ደቡብ ጎንደር የሚንከላወሰውን ፋፍዴንም ሲንደፋደፍ፣ በፓስተር ጸሎት ለመዳን፣ በአገኘሁ ተሻገርና በአዲስ ሞግዚቱ ታዬ አጽቀሥላሴ ድጋፍ በእስክንድር ነጋ በኩል አፈር ልሶ ከሞት ለመነሣት ሲዳክርም አየዋለሁ። አናቱን የተቀጠቀጠው ወልቃይቴው ፋፍሕዴን በእነ ፓስተር ምስጌና በብአዴናዊው በእነ አያል መንበሩ አማካኝነት አየር እየተሰጠው ሸዋን ሙጥኝ ብሎ ይዞ ጎጃምና ወሎን ጭምር ገዱ አንዳርጋቸው እንዳይቀድመን በሚል ሒሳብ ሲራወጡ እያየሁአቸው በሳቅ ፍርስ እላለሁ። አቤት የሰው ልጅ መከራ ግን ገራሚ ነው። እስክንድርን እንደ ኮን*ም ለመጠቀም ያለው ግርግር አስቂኝ ነው።

"…እነ አስረስ መዓረይ የጎጃሙ ሴራቸው ስለተባነነባቸው በድብቅ የነበረው የእስኳድና የፋፍዴን ግርድናቸው ፍንትው አድርገው አውጥተውታል። ድርድሩን በተመለከተ እስክንድር ላይ በድንገት የተነሣውን ሱናሚ ለመቀልበስ አሥረስ መዓረይና ማርሸት ፀሐዩ ተፍተፍ ቢሉም አልተሳክቶም። እነ ፓስተርም ቢጸልዩ፣ እነ ኦነግቲቲዋ ተብታባ ገመድ አፏ ሞገስ ዘውዱም፣ እነ ሀብትሽ አፍራሳም፣ ጣናና አበበ ዶላር በላውም ቢንጫጩ እስኬውን ማትረፍ አልተቻለም። መዓዚ ሞጆ ከተማ በፋኖ ቁጥጥር ስር ዋለ ብትል፣ አረጋ ከበደን አቢይ አሕመድ ጆሮውን ቆነጠጠው፣ ጄነራሉ ከሥራ ተባረሩ ቢባል ወይ ፍንክች። ሰዉ ጮቄ ላይ ፍጥጥ። ትግሬ በመቀሌ እየተፋለጠ ነው፣ እየተወጋገረ ነው ቢባል ለደንታው ብሎ ሕዝቤ ግግም። እስኬው ጃል ሀብታሙ በሻህ ቲክቶክ ላይ ወጥቶ ከእኛ እንደ አንዱ ቲክቶከራም ሆኖ ታብታብ አድርጉ ቢል፣ ጊፍት የሰጡትን አበባ እየቆጠረ ሀብትሽ ሂሳቡን ላክ ቢል፣ ሊና ቤት ገብቶ በትዊተር ስፔስ ኡኡ ድረሱልኝ ቢል ማን ይስማው? ሰዉ ከእኔ ጋር ጎጃም ገብቶ ጮቄ ላይ ግግም። በመጨረሻ የጦር መሪው፣ የዐማራ ፋኖ ሕዝባዊ ድርጅት ፕሬዘዳንቱ እስኬ ያራዳ ልጅ "በሉ ጅቡ መጣብኝ ከቂ* ስር" በማለት ስፔሱን ዘግቶ ነካው። በሳቅ😂

"…ጮቄ ለይ ሆኜ ነው ይሄን ሁሉ የማየው። እንደ ጉድ ነው የሚተራመሱት። እኔ ጎጃም ስለገባሁ ዘመዴ ከጎጃም ሳይወጣ በትበት እንበል ብለው አዳሜና ሔዋኔ ሲራኮቱም እያየሁ ሙድ እይዝባቸዋለሁ። ነገሩ ጦዟል። ሴራዎቹ በሴራ ፈጣሪ ሸማኔዎቹ እየተደወሩ፣ እየተሸመኑም ነው። እኔም ከሩቅ ሆኜ እያየሁ ብቅ ሲል ቂው አድርጌ ላፈራርሰው መዶሻዬንና ድጅኖዬን ይዤ በተጠንቀቅ ቆሜአለሁ። ወላ ሃንቲ ነገር ከቁጥጥር ውጪ አይደለም። ሸዋ በቱለማ ኦሮሞው በመከራው ማሞ በመጠለፉ (ቱለማ መሆኑን ጃል ሀብታሙ በሻህ ነው ያረጋገጠለን) አቅም አጣ እንጂ ጃል ሰኚን ሆኖ ከእስኬው ጋር በእርቅ ሰበብ ለመግባት ከጫፍ መድረሱ ነው የሚነገረው። እንዲያ ቢሆን ግልግል ነበር የሚሉ መተርጉማንም አሉ። ስኳድ እስኬውን እንደ አድራሽ ፈረስ፣ እንደ ህዳር አህያ እየጋለበና እየጫነው ቤዙን ወልቃይት አድርጎ ተፍተፍ እያለ ነው። እስኳድ ወልቃይት ቀይ መስመራችን ነው ሲል የጎጃሙም ሸንጎ በኦሮምቲቲዋ የመገርሳ የልጅ ልጅ በአልማዝ ባለጭራዋ በኩል ወልቃይት፣ መተከል፣ ራያና ሸዋን በተመለከተ በድንገት ተነሥታ "የአማራ እርስቱ ወልቃይት ራያ መተከል ሙሉ ሸዋ ነው!!" ብላ ነጠላ ዜማ እንድትለቅ ሲያስደርጓት እያየሁ አሁንም በሳቅ።😂

"…ፋፍዴንና አገው ሸኔ አንድ ላይ ገጥመው ላለመሞት የመጨረሻ ዕድላቸውን በመሞከር ላይ ይገኛሉ። ዓለምአቀፉም አካል ፍላጎቱን በስሱ እያሳየ ይገኛል። መጀመርታ እስክንድር እንዲናገር ተደረገ። ቀጥሎ የእስኬው የአምነስቲ ወዳጆቹ በአምነስቲ በኩል አቢይ ላይ ጫና እንዲፈጠርና ከዐማራ ክልል እንዲወጣ የሚል ቃና ያለው መግለጫ እንዲሰጥ ተደረገ። በዚህን ጊዜ የእስክንድር ድርድር ያስነሳውን አዋራ አይተው የእነ መሳይ መኮንን ቡድን ተበላን ብሎ ሩጫ ጀመረ። እነ አቢይ አሕመድ ኦሮሙማዎቹም በአማርኛ ተናጋሪ ከጎንደሬ አባቱና ከጉራጌ እናቱ በሚወለደው በጴንጤው ናቲ አንደግምም ወይ በኩል እስኬው ላይ የተነሣውን ማዕበል ለማስቆም በጂሰስ ስም ብለው ሄጵ ብለው ተነሡ። የጎንደር ጴንጤና ፓስተሮች በፓስተር ምስጌ አማካኝነት በልሳን ሁላ መናገር ጀመሩ። ፓራራሻምበረልራራ ቷ ጋገጭም አሉ። የልሣኑ ትርጉም የሚገባው የምረዳውም እኔ ብቻ ሆንኩኝ። አዳሜና ሔዋኔ ምን እየተካሄደ እንዳለ አይባንንም። ተራ ጦርነት፣ የቃላት ውርወራ መስሎት ከዳር ቆሞ አውቶቡስ ይጠብቃል። ሌባና ፎሊሶቹ ግን ተነቃቅተን ተፋጥጠናል።

"…በስሱ ስናየው የዚህ ሁሉ የድርድር ምንግርግር ጫጫታ ምክንያት ደግሞ አማሪካ፣ አይኤምኤፍና አምንስቲ ኢንተርናሽናል እጃቸውን ስላስገቡ በተፈጠረ ከፍተኛም ጫና ምክንያት ይመስላል። የእናት ጓዳ የተባለችው የአብይ አሕመድ የፈረንጅ ላሟ IMF ትናንት የሆነ ሚልዮን ወይ ቢልዮን ሊትር ወተት ልትሰጠወወ ቃል መግባቷም ተሰምቷል። በሌላ አገላለጽ ብድሩ ጸድቆለታል። ተፈጻሚ ለመሆን ግን ባለፈው የተለቀቀለትን የ1 ቢሊየን ዶላር የወተት ብድር ሪፖርት እንዲያቀርብ፣ እንዲሁም እስኬው በራሱና በአምነስቲ ፍሬንዶቹ በኩል ቀደም ብሎ አቀረበ የተባለው መከላከያን ከዐማራና ከኦሮሚያ ክልል አስወጥቶ ሠራዊቱን ወደ ካምፕ እንዲያስገባ፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ያደረሱትን ለፍርድ እንዲያቀርብ፣ ለተራቡት ዕርዳታ እንዲደርሳቸው እንዲፈቅድ ያሉትን እንደ ቅድመ ሁኔታ ቀርቦለታል። ስለዚህ አራዶቹ በመሃል ተጠቃቅሰው አቢቹም ጃልሰኚ እስኬው የጠየቀውን አሟላ ተብሎ የዐማራ ሕዝብ እስክንድርን እንደ ግል አዳኙ እንዲቀበለውና ድሮም ሌሎቹ የፋኖ አደረጃጀቶች አይረቡም ብሎ እንዲገፋቸውና ቅቡልነት እንዳይኖራቸው ለማድረግ ነው ቁማሩ እየተቆመረ የሚገኘው።

"…ሕዝቡም እውነት አለው በዚህ ጭንቅ ወቅት፣ በዚህ የራብ ወቅት፣ የድሮን ጭፍጨፋ፣ ቦንብና ልጆቹን የሚደፍር ሠራዊት ከክልሉ ሲወጣ፣ ስንዴና ዘይት፣ ዱቄትም ሲመጣለት፣ ይሄ ሁሉ የሆነው በእስኬው ምክንያት ነው እያለ ግልብጥ ማለቱ አይቀርም ተብሎ የተሠራ ሥራ፣ የተቆመረም ቁማር ነው። የሰው ልጅ ደግሞ ስሜቱን የሚከተል ነው። እሁድ ሆሳዕና በአርያም ያለው የኢየሩሳሌም ሕዝብ ነው ጌታ ለተቀመጠባት አህያ ሁላ ጨርቅ፣ ሸማ፣ ጋቢ ነጠላ ኮቱን አውልቆ አንጥፎ፣ ዘንባባ ዘንጥፎ፣ ላንቃው እስኪሰነጠቅ ጮሆ ሲያመሰግነው የዋለው ሕዝብ ነው ያው ሕዝብ አርብ ዕለት አደባባይ ወጥቶ "ስቀለው፣ ስቀለው፣ በርባን ወንቤዴውን፣ ገዳይ አስገዳዩን፣ ዘራፊውን፣ ቀማኛ ደፋሪውን ፍታልን፣ ይሄን ክርስቶስ ኢየሱስ የተባለ አዳኝ፣ መድኃኒት፣ እውር የሚያበራ፣ ሙት የሚያስነሣ፣ ለምጣም የሚያነጻ፣ ለህሙማነ ሥጋ ፈውስን፣ ለሕሙማነ ነፍስ ድኅነትን የሚያድለውን ጌታ ስቀለው ብለው የተቃውሞ ሰልፍ የወጡት። አቢይ አህመድ ሄሮድስ እስኪደነግጥ ድረስ ማለት ነው። ቅዳሜ ሚያዚያ 29/1997 ዓም እንዲሁ ነው የሆነው። መለስ ዜናዊ ነኣ ስሜቱን መቆጣጠር አቅቶት የሕዝብ ማዕበሉ ውስጥ ዘልዬ ካልገባሁ ሞቼ እገኛለሁ ብሎ ለገላጋይ እስኪያስቸግር ድረስ ነው ሕዝቡ ቅዳሜ ሚያዚያ 29 የንብ ቲሸርት ለብሶ እንደ ንብ መንጋ ተናዳፊ መስሎ የዋለው። መሸ ነጋ ሚያዚያ 30/1997 ዓም ሆነ። ያው የሸገር የአዱ ገነት አዲስ አበባ ሕዝብ ነው መልሶ "ትናንት ለቲሸርት…👇 ①✍✍✍


እኔምለው…

"…ርእሰ አንቀጹን ጨርሼዋለሁ። አጓጊ ነው። ራሴ ሳነበው መልሶ እየገረመኝ ነው። አሁን የመጣሁት ከመለጠፌ በፊት ላማክራችሁ ብዬ ነው።

"…ረጅም ነው። እንደ ሊማሊሞ፣ ግራካሱ ተራራ ጥምዝምዝም ነው። ይደክማችሁ ይሆን ብዬ ፈራሁ። እናም ይቀጥላል ብዬ ለማክሰኞ ቀሪውን ላቅርብላችሁ ወይስ ሙሉውን ዛሬውኑ አሁኑኑ ልለጥፍላችሁ? ትሁት አይደለሁ? ላስፈቅዳችሁ ብዬ ነው።

• የአንድ የመቶ ሰው ምላሽ ካገኘሁ ወዲያው እለጥፈዋለሁ። 😁🙏✍✍

• የእናንተው ዘመዴ ነኝ ከጮቄ…

38k 0 3 406 1.6k

"…ይቅርታ… ቆየሁባችሁ አይደል?

"…አዎ ይገባኛል። ነገር ግን ምን ላድርግ የማፈርሰው፣ የምነቅለው ሴራ ትንሽ ጠጠር ስለሚል፣ ደግሞ በዚያ ላይ የሚያግዘኝ የለ ብቻዬን ነኝ። ለሴራ ማፍረሻውም ኃይለኛ ድማሚት እና ዕፀ መሰውር የሆነ ቅጠል ከጮቄ ላይ ማዘጋጀት አለብኝ፣ እንዲያ ስለሆነ ነው የዘገየሁት። ከምር ስንት መፍቻ እና ፋስ፣ መዶሻም ሁላ ቀያየርኩ መሰላችሁ። ኧረ ባባጃሌው።

• ኡፍፍ እያላችሁና እሳት እየተፋችሁ በትእግስት ጠብቁኝ እሺ…! 😂

40.7k 1 5 225 1.5k

መልካም…

"…እዚያው ጎጃም ጮቄ ተራራ ላይ ነኝ። ተራራው ላይ ሆኜ ወልቃይት፣ ደቡብ ጎንደር፣ እዚያው ጎጃም፣ ደቡብ ወሎና ሰሜን ሸዋ፣ ኡጋንዳ፣ ጀርመንና አሜሪካ ርምስምስ የሚል ነገር ይታየኛል። 😂 እሱን ነው እየጻፍኩላችሁ ያለሁት። ከተራራው ላይ ባገኘሁት ቅጠላቅጠል ምን የመሰለ አፍራሽ፣ ያበጠውን አፈንድቶ ቁስሉን መዝምዞ መግሉን ውልቅ የሚያደረግ መድኃኒት ፈለሰምኩ መሰላችሁ።

"…ጮቄ ብርድ ቢሆንም ከጀርመን ብርድ አይበልጥምና እንደምንም ተቋቁሜው አረቄዬን እየላፍኩ ጉድ እያየሁ ነው። ምርምሬንም እየቀጠልኩ ነው። ፀረ ዐማሮቹ ለፍተው፣ ለፍተው፣ ስንት ደክመው የገነቡት የጥፋት ሴራ ልንደው ነኝ። ላፈርሰው ልነቅለውም ነኝ። የእኔ ጨዋታ አእምሮ ላይ ነው። በቴሌግራም ጦማር ደግሞ ዋይዋይ ላስብላቸው ነኝ።

• አላችሁ አይደል? እኔ ዘመዴ ጃል ቆቱ ወዲ አስገዶም ምን የመሰለ ዘለግ ያለ የሚያመራምር፣ የሚያተራምስም ግሩም የሆነች የዶሮ ወጥ በሉት፣ ክትፎ፣ ቁርጥ ነሽ ምላስና ሰንበር የሚያስንቅ ርእሰ አንቀጽ ልለቅላችሁ ነኝ። ✍✍✍

• ዘመዴ ነኝ ከጮቄ…😂

44.7k 0 13 384 1.9k

"…እነዚህም ሁሉ የምጥ ጣር መጀመሪያ ናቸው። ማቴ 24፥8

• እንደምን አደራችሁ?
• እንደምን አረፈዳችሁ?
• እንደምን ዋላችሁ?
• እንደምን አመሻችሁ?

• መልሱ እግዚአብሔር ይመስገን ብቻ ‼

46.4k 0 9 1.5k 1.5k

"…ነኝ ከጮቄ ተራራ ጎጃም…

"…በስኳዱም፣ በኦነግ ሸኔውም ቤት ዞርኩ። ምንኡነው ዝም ጭጭ አሉብኝሳ። አልሚዬ ባለጭራዋም ተንቀሳቀሽ፣ ጥልሚያኮስ አማኑኤል አብነትም ተንፍስ አንጂ፣ ብሮ እስማኤል ዳውድ፣ ሰጣርጌም እነ አበጀ በለውም ጭጭ፣ ጮጋ አላችሁሳ…?

"…ሰፈሩ እኮ ሬሳ የወጣበት መሰለ? ምን ጅብ በላቸው ጎበዝ? አጠቃላይ የብአዴን ኔትዎርኩ ተንገጫገጨሳ? የጀርመኑ ታሜ ብአዴኑ ብቻ አሽሙር ይለጥፋል ሌሎቹ ላይክ ይገጩታል 😂 ከምር ጎጃም እንደዚህ ጭር ብሎ አያውቅም። አላስለመዱንምም። ዐማራ ዛሬ፣ ስለሺ ኧረ ናፈቃችሁኝ።

"…ኧረ ተዉ በጥቂት ቀን አትፍረክረኩ። ገና ምኑንም ሳልጀምረው፣ እስከ እንቁጣጣሽ እቆያለሁ ብዬ የያዝኩትን የጎጃም ብሮግራሜን በአጭር አታስቀሩብኝ። አጫውቱኝ እባካችሁ። 😂

"…ታመነ መኮንን ጀርመን ያለኸው አንት ወፍራም ብአዴን አርበኛ ዘመነ ካሴ አንዲት ነገር ቢሆን አንተም፣ ላይክ ያደረጉልህ እነ ይኼነው የሸበሉም ሁሉ አልፋታችሁም። በቃ ከተነቃ ተነቃ ላሽ በል። ንካው አባ።

"…ግርማ አየለ እየባነንክ መጥተሃል። አንት ጨቅላ አዕምሮህን ማሠራት ጀምረሃል። ጅቦችን መለየት ከምረሃል። ወጥር፣ ጠይቅ። ጎጠኛ ዓሰግድን በደንብ ያዘው፣ ላይክ የገጩትን በሙሉ ተነልከታቸው።

"…ከዚህ በፊት ዘመነ ካሤ ሊታሰር ሲል ሁሉም የዘመነ ካሴን ፕሮፋይል ፒክቸር ገጭ አድርገው ነበር የተከሰቱት። ዛሬም ምን አስበው እንደሆነ እንጃ ያንኑ ጊዜ እያየሁ ነው።

"…ለሕዝቡ ባይታይም፣ ባይገለጽም እኔና እናንተ ተግባብተናል። ተስፋዬ ወልደ ሥላሴ ይኸው አደብ መያዝህ ነው የሚያዋጣህ፣ የሚሻልህም። ሮሐ ቲቪ ቀደዳ ቀንሺ፣ ባትቀንሺም ለደንታሽ ነው። ኧረ ተንፕሱ፣ ተናግራችሁ አናግሩኝ፣ የምን ዘም ጭጭ ነው። እኔ ግን የላላውን እያጠበቅኩ፣ ጠማማውን እየነቀልኩ ወደፊት እየነካሁት ነው።

• እርገጥ ዘመዴ…😁

50.2k 1 11 51 2.1k

መልካም…

"…ይሄን ከ21 ሺ ሰው በላይ ያነበበውን 49 ፍሬ ሰዎች ጓ 😡 ብው ያሉበትን የዛሬውን ርእሰ አንቀጽ ደግም እስቲ መላ በሉት።

•1…2…3…ጀምሩ ✍✍✍

49.4k 1 4 271 1.3k

👆③ ✍✍✍  "…ዘመዴ አንተም እወደዋለሁ፣ አከብረዋለሁ ማለቱን ተወውና አርበኘ ደረጀ በላይ እንደ ሌሎች ይመርመር፣ በመሳሪያ ንግድ ላይ ስሙ ይነሣል። ከጁንታው ጦርነት ጀምሮ በዚህ በኩል በአንደኛ ደረጃ ነው ስሙ የሚነሳው። በሰሊጥ ንግድ ቀረጥ ላይም እንደዚሁ። በዚህ ትግል አብረውት የተሰበሰቡትና ዙሪያውን የከበቡት ሁሉ የማፍያ ጠባይ ያላቸው ናቸው። የገዛ አብሮ አደግ ዘመዱን አሳፍኖ በመቶ ሺዎች የሚቆጠር ብር አስከፍሎ የለቀቀ ሰው ነው ብለውም የሚከሱት አሉ። ገበሬው በደረጀ ተማሯል። በፍጹም የዐማራ ጠባይም፣ ሥሪትም የለውም። የጎንደር አባቶችን የእነ ሻለቃ መሳፍንትን ቃል ሳይሰማ ብቻውን ከትግሬዎቹ ባሎች ከፓስተሮቹ ጋር ከቆመ፣ በአበበ በላው በእስክስም በልቅሜ ኪዳኑ ልጅም የሚመራ ከሆነ አርበኛ ደረጀ በላይ እርግጠኛ ነን ዐማራ አይደለም የሚሉ ተፈጥረዋል። ከዚያው ጎንደር ሰው ያልሰማው ጉድ አለ የሚሉም እየመጡ ነው። እኔ ደግሞ ፈርዶብኝ በአካል ሳላውቀው እንዲሁ እወደዋለሁ። አከብረዋለሁ። ምክንያቱን እንጃ እኔም አላውቀው። ግን የዐማራ ጉዳይ እስከሆነ ድረስ ምንም ብወደው፣ ባከብረውም ደረጀ በላይ ላይ ጨክኜ ፋይል ልከፍት ምርመራም ለመጀመር እገደዳለሁ። ከመሳይ መኮንን ጋር ገጥሞ የሚያውቀውን ተኩስ ትቶ የማያውቀውን ቦለጢቃ ልተንትን ካለ እንግዲህ ልገጥመው ነኝ። እስከዛሬ ስለደረጄ በላይ ሲነገረኝ፣ አላይም፣ አልሰማም ያልኩትን በራሴም ላይ ያወጣሁትን ሕግ በዛሬው ዕለት ሽሬዋለሁ። ከደሬ ጋር እየመረረኝም፣ እየቀፈፈኝም ቢሆን የጭቃ ዥራፌን አንሥቼ ልመዣረጥ ነኝ። አከተመ። ለደሬም ባለበት ንገሩልኝ። እነ ፓስተር ምስጋናውና የልቅሜ ኪዳኑ ልጅም፣ ፀረ ዐማራ ኃይሎችም አያዋጡህምም በሉልኝ።

"…ወደ ጎጃም ስንመለስ እነ አስረስ መዓረይ አሁን  መምህራንን መግደል፣ ማረድ፣ አግቶ ብር መቀበል፣ ብር የሌለውን መረሸን አቁመዋል። እነ አስረስ መዓረይ እና የጎጃም ፋኖ መሪ ፓስተሮች የኦርቶዶክስ ቄሶችን፣ ዲያቆናትን፣ የአብነት መምህራንን ከመከላከያው ጋር እየተፈራረቁ ምእመናንን መግደል፣ ማረድም አቁመዋል። አስረስ መዓረይ እና የጎጃም ፋኖ መሪ ፓስተሮች በውሸት፣ በሐሰት በሰበር ዜና የሕዝቡን አእምሮ በላም አለኝ በሰማይ ወተቷንም አላይ ጆካ ማጨናበር አቁመዋል። እነ አስረስ መዓረይ እና የጎጃም ፋኖ መሪ ፓስተሮቹ ከከተማ ዳር ወደ ወረዳና ዞን፣ ከዚያም ቀበሌ ሸሽተው አሁን በተራራና በበበረሃ ከትመዋል። ሽሽ፣ መከላከያ ሲመጣባችሁ አትተኩሱበት፣ አትንኩት እያሉ የጎጃም ፋኖን የበላይ ዘለቀን ልጆች ሽባ፣ ዱዳ አድርገው አስቀርተው እነሱም ጉድ ሆነዋል። አሁን እነ ጥላሁን አበጀም አደብ እየገዙ መጥተዋል። እንደ ፈለጉ መሆን እያቃታቸው መጥቷል። ከዳያስጶራ የሚጎርፈው የዶላር ምንጭም ድርቅ ብሏል። ድርቅ ነው የምላችሁ። ፍልሰት ወደ ኡጋንዳ ጨምሯል። ሕዝብ እረፍት እያገኘ መጥቷል። አሁን የሚያስፈልገው እነዚህን ወንጀሎች፣ የዐማራ ፋኖ በጎጃምን በወረቀት ላይ የሰፈረ ነብር አድርገው መሳቂያ መሳለቂያ ያደረጉትን አውርቶ አደር ፀረ ዐማራ መሪዎችን በፍጥነት መቀየር ነው። መቀየር ብቻ ሳይሆን በሕግ የሚጠየቁትን ለሕግ አቅርቦ እዚያው በፋኖ ደንብ መሠረት መዳኘት እና ፍትሕን ማረጋገጥ ነው። አሁን ወደፊት መስፈንጠር ያስፈልጋል። በዐፋጎ ውስጥ የከተመው የምሥራቅ ጎጃም ቅባቴ የብአዴን ኔትወርክ የሸኔ ሽንት ካልደረቀ በቀር የዐማራ ፋኖ በጎጃም በቅርቡ ከባድ አደጋ ይገጥመዋል። ጎጃም መፍጠን አለበት።

"…ጎጄ መለኞቹ ከእኔ ከዘመዴ ጋር መሳፈጥ፣ መሞላፈጡም ምንም አይረባላችሁም። ይልቅ እኔን መስደቡን ትታችሁ መሬት ላይ ወደ ቤተሰቦቻችሁ፣ ወደ ጓዶኞቻችሁ እየደወላችሁ ጠይቁ። የማኅበራዊ ሚዲያውን የፌክ፣ የውሸት ሰበር ዜና ናቅ፣ ተወት አድርጉና ወደ ቤተሰቦቻችሁ ደውሉ። ማዶና ማዶ ሆነው በዚህ መከላከያው፣ በዚያ ፋኖው መኪና አስቁመው ሳይተኳኮሱ፣ ሲጋራ እየተለኳኮሱ የሚግጡትን ሕዝብ ጠይቁ፣ ገበሬው መማረሩን ጠይቁ። መከላከያ ሲመጣ ለምን እንደሚፈረጥጡ፣ እንዋጋ የሚሉትን ፋኖዎች አምልጥ ዝም ብለህ እያሉ ለምን እንደሚያሸማቅቁ ጠይቁ። ጠይቁ መሬት ላይ እንዴት ታጋዩን ተስፋ እንዳስቆረጡት። ጠይቁ። እኔ ላይ ስታላዝን ውለህ ብታድር ምንም ፋይዳ የለውም። ፍጠኑ፣ ጠይቁ፣ ተወያዩ። እንደነ ተስፋዬ ያሉትን ከገንዘብ አካባቢ አርቁ። አዝማሪት አልማዝ ባለጭራዋ የምትመራው የጎጃም ፋኖ ስንዝር አይራመድም።

"…ጎጃም የምሁራን፣ የሊቃውንት፣ የጀግኖች ሀገር ነው። ጎጃም በኩታሮችና በአውርቶ አደሮች የሚወከል ሕዝብ አይደለም። ጎጃም እኮ የተንቀሳቃሽ ላይብረሪው ዐማራ የሆነ ሁሉ የሚኮራበት የወንድሜ የአቻምየለህ ታምሩ ሀገር ነው። ጎጃም በዚህ መጠን ስሙ በክፉዎች ሊነሣ የሚገባው አልነበረም። ጎጃም ዶሮ መግደል ኃጢአት ነው በሚሉ ፓስተር ጴንጤዎች ተመርቶ እንዴት ነው ጠላትን ገድሎ የሚያሸንፈው? ጎጃም ሲዋጋ የመከላከያ ወታደር ደስ የሚለው እኮ ተባራሪ ጥይት ካልመታው በቀር ጎጃምን አውድሞ ከተማረከ በኋላ የሚደረግለትን እንክብካቤ ስለሚያውቀው ነው። ለምን ያልን እንደሆነ የታረደ የበሬ ሥጋ እንጂ በሬ አርዶ መብላት ኃጢአት ነው በሚሉ ፓስተሮች ዐፋጎ ስለሚመራ ነው። ምከሩ ብያለሁ። መሳቂያ፣ መሳለቂያ ከመሆናችሁ በፊት አስቸኳይ የመዋቅር ለውጥ እንዲደረግ ወትውቱ። ተናግሬአለሁ። በየቀኑም እናገራለሁ። እስከ መስከረም ጎጃም ነኝ። ወይ ንቅንቅ።

"…ፓስተሮቹና እነ አስረስ መዓረይ ከጎንደር አንድነት፣ ከወሎ አንድነት፣ ከሸዋ አንድነት ጎጃምን ለይተውታል። ጎጃምን ወደ ኋላ አስቀርተውታል። በዚህም ምክንያት የዐማራ ትግል ተጎትቷል። ዘግይቷልም። ስለዚህ ጎጃም ጥያቄ ይጠይቅ። አርበኛ ዘመነ ካሤ ስካን በተደረገ ማኅተሙና ፊርማው ነው ሾመ፣ ሻረም የሚሉን እነ መዓረይ። ዘመነ ከሤ የት ነው? ይሄ ሁሉ ውጥንቅጥ ሲፈጠር የት ነው ያለው? ለምን መደበቅ፣ መሸሸግን መረጠ? ዘመነ የእነ አስረስ መዓረይ የቁም እስረኛ ነው ወይ? አስረስ መዓረይ የዘመነን ሥራ ተክቶ የሚሠራው ዘመነ ካሤ የት ሄዶ ነው? መደናበር ሳይበዛ ጥያቄ ይጠየቅ። ጎጄ መለኛ እንጂ ወሬኛ እኮ አይደለም። የአባቶቻችሁ ልጆች ተነሡ። ተነሡና ጠይቁ። መጠየቅ ያደርጋል ሊቅ ነው እኮ የሚባለው። ያልጠረጠረም ይመነጠራል። ብትሰደቡ ነው። በጋለሞታዋ አልማዝ ባለጭራዋ ብትዋረዱ ነው። ዐማራ ስላልሆነች ይሄ ደግሞ ሙያዋ መገለጫዋ ስለሆነ አትፍሩ። ጠይቁ።

• አንደዜ ነክሻለሁ። ከነከስኩ ደግሞ ነከስኩ ነው ሳላደማ እንደሁ አልመለሳትም። 

• ድል ለዐማራ ፋኖ…!
• ድል ለተገፋው ለዐማራ ሕዝብ…!

~ • ይደፈርሳል… ግን ደግሞ ይጠራል…✊

•••

ሻሎም…!  ሰላም…!

ዘመድኩን በቀለ ነኝ።
አሸበርቲው/አስነቀልቲው
ጥር 22/2017 ዓም
ከራየን ወንዝ ማዶ።


👆②✍✍✍ …ጠቅሶ ሊያቀሳስር የሞከረው አርበኛ ዘመነ ካሤን እና አርበኛ ሻለቃ ዝናቡ ልንገረውን ነው። ይሄ የሆነው በምክንያት ነው። ዝም ተብሎ እንደ ድንገት የተነገረ አይደለም። እነሱ ተጠቃቅሰው በፕላን ነው የሚንቀሳቀሱት።

"…የዐማራ ፋኖ በጎጃም ሕዝቡ ግዙፍ ከባድ ዋጋ ከፍሏል። ስንትና ስንት ተስፋ የነበራቸው ጀግኖች ተዋድቀዋል። ትግል ጠላፊዎቹ ሾተላዮች እነ አስረስ መዓረይ፣ እነ አበጀ ጥላሁን፣ እነ አበጀ በለው፣ እነ ፓስተር ዳዊት መጥተው አመራሩን ሥፍራ ይዘው እስኪጠልፉት ድረስ የዐማራ ፋኖ በጎጃም ተጋድሎው በተሪክ ተመዝግቦ የሚቀመጥ ነው። አስረስ መዓረይ መጥቶ እስኪያቀዘቅዘው፣ አፈር ደቼ እስኪያበላው ድረስ በግሩም መስመር ላይ እየተጓዘ ነበር። ተስፋ ሰጪም ነበር። ተስፋ ሰጪም ነው። አሁንም በጎጃም ያለው ኃይል አልተነካም። እንዳለ ነው ያለው። አመራሩን በዐማሮች ከተኩት የጎጃም ዐማራ ፋኖ አቅሙም፣ ወንድነትና ጀግንነቱም ሁሉ እንዳለ ነው። አልተነካም። ምንም አልተነካም። በጎጃም ዞር ዞር ስል የማየውም ይሄንኑ ነው። የዓድዋው ስርወ መንግሥት የመሰለው የጎጃምን ጀግኖች አንገት ያስደፋው የዐፋጎ አመራሮች ላይገድሉ መሪ የሆኑት የጴንጤ አመራሮች ሪፎርም ተደርጎ የጎጃም ዐማራ ፋኖ በወንዶቹ የበላይ ዘለቀ እና በእጅጉ ዘለቀ ልጆች ከተተኩ ሳምንት አይፈጅበትም ወደ ቀድሞው ሁናቴ ለመመለስ።

"…አሁን ላይ እኔ ዘመዴ በቶሎ ደረስኩ። የጎንደር ፋኖዎች የአርበኛ ባዬ ቀናው የመረጃ ልጆች ቀድመው ደርሰው አኮላሹት፣ አከሸፉት እንጂ በተለይ አርበኛ ሻለቃ ዝናቡን እና አርበኛ ዘመነ ካሤን ቀርጥፈው በአንድ ቀን፣ አንድ ላይ በልተዋቸው ነበር። አስረስ መዓረይ ሊነግሥ፣ የዐማራን ትግል አሳልፎ ሊሸጥ አኮብኩቦም ነበር። የሴራ የተንኮል ድሩን ነው ፈጣሪ የቆረጠበት። ብጥስጥስም ያደረገበት። ይኸው አሁን በጎጃም በየቀኑ የድሮን አደጋ ጠፋ እኮ። ዘመነ አንድ ነገር ቢሆን ከአስረስ መዓረይና ከጥላሁን አበጀ፣ ከፓስተሮቹ ራስ አንወርድም በማለቴ እና ድርቅ ክችች በማለቴ እኮ በሴራ ድሮን ተለይቶ የሚለቀም የጎጃም ጀግና አሁን ላይ ቀረ። አንድም ፋኖ በዚህ መንገድ ሞተ መባልን አልሰማንም እስከአሁን። በሌላ በኩል ግን ሊበሉት ያሰቧትን አሞራ ጅግራ ናት እያሉ አሁንም ጆፌ አሞሮቹ ሻለቃ ዝናቡ ልንገረውን እየዞሩት ነው የሚገኙት። በአስረስ መሰሪነት፣ በናትናኤል መኮንን አቀሳሳሪነት፣ በተስፋዬ ወልደ ሥላሴ አቃጣሪነት፣ በአበጀ በለው አዳኝነት ዝናቡን በደጋ ዳሞት ጉዳይ አጀንዳ አድርገው ከሰው ሊበሉት የተዘጋጁ ይመስለኛል። ዝናቡን የምትቀርቡት ካላችሁ ዘመዴ እንዲህ ብሎሃል በሉልኝ። "ከፈጣሪ ጋር ራስህን ጠብቅ" ብትሉልኝ የነፍስ ዋጋም ይሆናችኋል። ዘመነ እና ዝናቡ ተነክተው የሚተርፍ የዐማራ ፋኖ በጎጃም የተቋም መሪ የለም። ይሄን አስረግጬ ነው የምነግራችሁ። የናትናኤል መኮንን፣ የተስፋዬ ወልደሥላሴ፣ የአበጀ በለውን የጥቅሴ ኮድ ይዤ ስመረምር አስረስ መዓረይ ከእኔ ጋር የቃለመጠይቅ፣ ምርመራ ባደረግሁለት ወቅት የነበረውን ቃሉን ደጋግሜ እየሰማሁ አሁንም ለዝናቡ በጣም እሰጋለታለሁ። ከዝናቡ ቀጥሎም ለዘመነ ካሤም እሰጋለሁ። ዘመነ ካሴ በሙሉ አጠገቡ ያሉት በድሮን አልቀው አጠገቡ የቀረው ልጁ ብቻ ነው። ልጁ ነው አሁን የሚጠብቀው። እናም ለእሱም እሰጋለታለሁ።

"…በጎንደር የጎንደርን አንድነት ያፈራረሱት እነ አበበ በለው፣ እነ መሳይ መኮንን ጭምር ናቸው። የዐማራ ፋኖን አንድነት እንዲህች ብሎ የማይዘግበው ኦሮምቲቲው መሳይ መኮንን በዐማራ ፋኖ ውስጥ ሰተት ብሎ በመግባት የት ነህ? እንዴት ነህ? ወዘተ በማለት ትግሉን እንዳያድግ እየኮረኮመው ይገኛል። የዐማራ ፋኖ መሳይ መኮንን የሚባል ፀረ ዐማራ ኃይል አጠገብ ካልራቀ፣ ግኑኝነቱንም ካላቆመ ገና ብዙ ዋጋ ነው የሚከፍለው። የዐማራ ፋኖዎች ሚዲያ መምረጥ፣ ጋዜጠኛም መምረጥ እስካልቻሉ ድረስ ቀስ በቀስ እያዩት ይሾቃሉ። የጎንደርን አንድነት፣ የቀድሞውንም እርቅ ቢሆን ያልዘገቡት አበበ በለው እና መሳይ መኮንን ብቻ ናቸው። ለምን?  ሲባል እንጃ ፈጣሪ ይወቅ ተብሎ ብቻ ለፈጣሪ የሚተው ጉዳይ አይደለም። ይሄ ግልጽ ነው። ሁለቱም የዐማራ ጠላቶች ናቸው። መሳይም፣ አበበ በለውም ከፈጣሪ ዘንድ የእጃቸውን የሚያገኙበት ቀን ሩቅ አይደለም። በዐማራ ደም እንደቀለዱ አይቀሯትም። የዐማራ ቦለጢቃ እጅግ ከባዱን ጊዜ በጥበብ እያሳለፈ ነው። እየተሻገረውም ነው። መጪው ጊዜም ለዐማራው ብሩህ ነው። የነቁ፣ የባነኑ፣ እንደ ንስር በጥልቀት ነገሮችን የሚያዩ፣ የሚመራመሩ ልጆች ተፈጥረዋል። ጠያቂ ትውልድም ተፈጥሯል። ባይናገር፣ በአፉ ባይመሰክር እንኳ ተራው የእኔ ቢጤው ሕዝብ ሳይቀር የገባው የተረዳም ሆኗል። የሚፈለገውም ይሄ ነበር። ይሄ ተሳክቷል። መስተካከሉ የጊዜ ጉዳይ ነው። ነገ ይስተካከላል። ዋናው በጊዜ መንቃቱ ነው።

"…አሁን እነ መሳይ መኮንን ፊታቸውን ከጎጃም ወደ ጎንደር አዙረዋል። ከጎንደር የሚጋለብ ፈረስ፣ የሚጭኑት የህዳር አህያ እየመራረጡ ነው። ሳያገኙም የቀሩ አይመስለኝም። አዎ እኔ ከመሬት ተነሥቼ ዝም ብዬ የምወደውን፣ በዐማራ ፋኖ ትግል ሁለት ልጆቹን መስዋዕት አድርጎ ያቀረበውን አርበኛ ደረጀ በላይን መርጠው እየጋለቡት ነው። አርበኛ ደረጀ ለብቻው ወጥቶ ከፋፍዴኖች ጋር መግጠሙ፣ በሞተው የእስክንድር ድርጅት ውስጥ ግግም ብሎ በዚያው ካልቀረሁ ማለቱ ብዙዎቹን እያስቀየመ፣ እያስተቸውም ነው። ዘመዴ አንተ ዝም ብለህ እኮ ነው ደረጀ በላይን እወደዋለሁ የምትለው እንጂ ደረጄ በላይ መሬት ላይ ለጎንደር ገበሬ ዲዮቅልጥያኖስ ማለት ነው። ደረጄ የፖለቲካው ቅማንት የትግሬ ዲቃለው ስኳድ ሳይሆን አይቀርም የሚሉኝን ሁላ ነው ኧረ ተዉ ስል የኖርኩት። ዘመዴ አበበ በላው ደረጀን የሚነዳው እኮ ደረጀ ራሱ በግማሽ ጎን ወይ የተከዜ ማዶ ሰው ቢሆን ነው እንጂ በጤናው እንዲህ አላንቀዠቀዠውም የሚሉም አሉ። ደረጀ የደንቢያ ዐማራ ነው የሚሉም እንዳሉ ሁሉ አይደለም የደንቢያ ወረዳ የጭልጋ ወረዳ መገናኞ አካባቢ ያሉ የገጠር ቀበሌ ተወላጅ ቅማንት ይሆናል እንጂ ደረጀ በፍጹም ዐማራ አይደለም የሚሉም አሉ። እነ አበበ በላው ዐማራ ሳይሆኑ ዐማራንትን ጎንደር በመወለድ ተጠምቀው ያገኙት ነው እንጂ እንደ እንጃ ዐማራ አይደለም የሚሉት ብዙ ናቸው። የጠራው ዐማራ ልክ እንደ አርባኛ መሳፍንት ያለ መሪ ግን ዐማራነትን ማስመሰል እና መካድ አይወድም። የደረጀ በላይ ዓይነት ቅማንት፣ እንደ አስረስ ዓይነቱ የጎጃሙ ቅባት ግን ሃይማኖት እምነትን ስለማያውቁት ክህደት ይውዳሉ። እርግጠኛ ነኝ ደረጀ በላይ ዘሩ ቢቆጠር እንደ አገው ሸንጎ የቅማንት ሽኔ ፀረ ዐማራ ነው የሚሆነው ይላሉ። ዘመዴ ለልጆቹ ስንል ታግሰናል ከአሁን በኋላ ግን የጎንደር ፋኖም ሆነ እኛም ልኩን ልንነገረው ይገባል። ደረጀ በላይ ከአሁን በኋላ ልክ እንደ አስረስ መዓረይ ለዐማራ ትግል ፀር ነው የሚሆነው እንጂ ምንም አይጠቅምም። ልጆቹ ለከፈሉት መስዋእትነት ክብር እንሰጣለን፣ እናመሰግናለንም እንጂ በአበበ በለው ቅማንቴው የማይም ምክር እየተነዳ የዐማራ ትግል እንቅፋት እንዱሆን አንፈቅድም ነው የሚሉት መተርጉማኑ።…👇 ② ✍✍✍

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.