Zemedkun Bekele (ዘመዴ)


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


"ይህ የቴሌግራም ቻናሌ ግንቦት1/2011ዓም የተከፈተ ነው። የእኔን የስልክ ወጪ ጨምሮ አገልግሎቴን መደገፍ የምትፈቅዱ ጓደኞቼ በ
👉🏿 https://donorbox.org/zemedemedia እና
👉🏿 https://www.paypal.com/paypalme/ZemedkunB በኩል ማገዝ ትችላላችሁ። በተረፈ ለቤተ ክርስቲያኔና ለኢትዮጵያ ሀገሬ የሚጠቅመውን ሁሉ አበረክት ዘንድ አብዝታችሁ ጸልዩልኝ።

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


"…ከውሾች ተጠበቁ፥ ከክፉዎችም ሠራተኞች ተጠበቁ፥ ከሐሰተኛም መገረዝ ተጠበቁ። ብዙዎች ለክርስቶስ መስቀል ጠላቶቹ ሆነው ይመላለሳሉና፤ ብዙ ጊዜ ስለ እነርሱ አልኋችሁ፥ አሁንም እንኳ እያለቀስሁ እላለሁ። መጨረሻቸው ጥፋት ነው፥ ሆዳቸው አምላካቸው ነው፥ ክብራቸው በነውራቸው ነው፥ አሳባቸው ምድራዊ ነው። ፊሊ 3፥ 16-19

"…እንደምን አደራችሁ?
"…እንደምን አረፈዳችሁ?
"…እንደምን ዋላችሁ?
"…እንደምን አመሻችሁ?

"… መልሱ እግዚአብሔር ይመስገን ብቻ ‼

22k 0 2 1.5k 1.2k

8 ሰው ብቻ ቀረን

"…እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በሚቀጥለው ሳምንት የዘመድ ሚዲያ የሳታላይት መርሀ ግብር ስርጭቱን ይጀምራል ብለን ተስፋ እንዳረጋለን። ሁሉም ነገር እጅግ ደስ በሚያሰኝ ሁኔታ ተሳክቷል። እግዚአብሔር ይመስገን።

• 318 ቱ ሠራዊተ ጌዴዎኖችን አመስግኑልኝ። ተረባረቡ አይገልጸውም።

• 318 ቱን የሚያግዙ 120 ቤተሰብ እፈልጋለሁ ብዬም ነበር። በጥሪው መሠረት 112 ሰዎች የዘመድ ሚዲያ ቤተሰብ ለመሆን ተመዝግበዋል።

• አሁን የሚቀረን 8 ሰው ብቻ ነው።

~ ኑ የዘመድ ሚዲያ ቤተሰብ ይሁኑ።


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
"…የዘመኑ የእግዚአብሔር ፍርድ ከዓይን ጥቅሻ በእጅጉ የፈጠነ ነው። እንደ ድሮው በልጅ ልጅህ ይደርሳል ብለህ አትጠብቅ።

• ፈጣን ፍርድ ⚖⚖⚖

38k 1 71 172 1.4k

ጊዜ ቂጣው…

"…ይሄ የምታዩት ትዕይንት እዚያው በኢትዮጵያ በአዲስ አበባ የካቲት 23/2017 ዓም በዕለተ እሑድ ሰንበት የታላቁ የዓድዋ የድል በዓል በሚከበርበት ዕለት የተፈጸመ ነው።

• ጊዜ የሰጠው ቅል…

"…ባለ ጊዜ ምኒሊካውያንን በየሱስ ስም አስሮ፣ በር ዘግቶ የፓስተር ዮናታንን ፎቶ በጨርቅ አሠርቶ አይደለም በምሽት በቀን በብርሃን የማይቻል፣ የማይሞከረውን ሰልፍ በምሽት…

"…ጣልያን በገዛን ኖሮ አላለም ልጁ። ትውልድ እንዲሆን የተፈለገው እኮ እንዲህ ነው። ተስፋ እንድትቆርጥ፣ ፈጣሪስ የታለ እንድትል፣ ነፃነት የሚኖርህ ጴንጤ ስትሆን ነው ብለው እያሳዩህ ነው። አባቴ ጽና… ጽና አልኩህ… ጊዜ ቂጣ ነው።

40.9k 1 35 94 1.6k

ከዓድዋ ድል በኋላ…

"…ከታላቁ የዓድዋ ድል በኋላ በግልጽ፣ እንዲረክሱ፣ በሀገሬው ሕዝብም እንዲጠሉ ጠላት በብርቱ የደከመባቸው።

ሀ፦ራሱ ዓድዋ የሚለው ስም
ሁ፦እምዬ ምኒልክ
ሂ፦የዐማራ ነገድ
ሃ፦የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን
ሄ፦ሰማእቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ
ህ፦ታቦት እና ማርያም
ሆ፦ሰንደቅ ዓላማ እና ሀበሻ

• ሀ፦ጠላት ኢትዮጵያን የሚያደሙ ባንዳዎችን በሙሉ ከዓድዋ ከተማ መረጠ። መለስ ዜናዊ፣ ስብሃት ነጋ፣ ቅዱሳን ነጋ፣ ወዘተ ከከዓድዋ ብቻ ተመረጡ። ከሌላኛው የትግሬ ክፍል እምብዛም ነው። ዓድዋ በእነሱ ምክንያት ተጠላ። ሁ፦በዓድዋ የጦር መሪ በእምዬ ምኒልክ ላይማ የሚዘንበው የጥላቻ ዶፍ ምኑ ይነገራል? ሂ፦ ጦርነቱን የመራው ነገደ ዐማራው ነውና በሚል ይኸው መቶ ዓመት ሙሉ ፍዳውን እያየ ነው።

• ሃ፦ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ያን ዋነኛዋ ጠላት ተደርጋ የምትሰቃየውም ለዚሁ ነው። ከመሃል አዲስ አበባ ዓድዋ ድረስ የዘመተው ታቦተ ጊዮርጊስንማ በደንብ ነው የተበቀሉት። ቢራ አድርገው ቅዱስ ሥዕሉ ተረገጠ፣ ሽንት ተሸናበት፣ ተረገጠ፣ ተዋረደ፣ ቄሶቹ ራሱ ጠጥተው እንዲሰክሩበት ተደረገ። ታቦት ቅርስ ነው እንዲል ብርሃኑ አድማስ፣ ለሦሰተኛው መቅደስ ታቦተ ጽዮን ትመለስ ዘንድ ኢትዮጵያውያን ታቦት እንዲጠሉ በሰፊው ተሠራ። ምኒልክ ማርያምን ብለው በመማላቸው ምክንያት ማርያም የሚለው ስምም ከምኒልክ በላይ በኢትዮጵያውያን ዘንድ ይጠላ ዘንድ በሰፊው ተሠራ። ሆ፦ የቀረው ሰንደቅ ዓላማዋና ሀበሻ ነበር። ሰንደቅ ዓለማው በዓድዋው ሾተላዮች ረከሰ፣ በኦሮሞ የወያኔ ገረዶች ተዋረደ፣ ተቃጠለም። ሀበሻ የሚለው ክቡር ስምም ነበር እሱም ቢራ አድርገው አመጡት። አሁን ላይ እሱም እንደ ቅዱስ ጊዮርጊስ በየቦታው ይረገጣል። ሽንት ይሸናበታል። ቆሻሻም ተደረገ።

• አይገርምላችሁም?

• የረሳሁት፣ ያስቀረሁት ካለም ጨምሩበት…

39k 1 36 46 1.3k

"…ያልጠፋነው ከእግዚአብሔር ምሕረት የተነሣ ነው፤ ርኅራኄው አያልቅምና። ማለዳ ማለዳ አዲስ ነው፤ ታማኝነትህ ብዙ ነው። ሰቆ ኤር 3፥ 22-23። “…እግዚአብሔርን ማመስገን መልካም ነው። መዝ 92፥1። እናም ተወዳጆች ሆይ “…ከማመስገን ጋር በጸሎት እየነቃችሁ ለእርሱ ትጉ፤” ቆላ 4፥2።

"…እንደምን አደራችሁ?
"…እንደምን አረፈዳችሁ?
"…እንደምን ዋላችሁ?
"…እንደምን አመሻችሁ?

"… መልሱ እግዚአብሔር ይመስገን ብቻ ‼

44k 0 11 1.6k 1.6k

"…ገብተናል ገባ ገባ በሉማ…

http://tiktok.com/@zemedkun.b


"…በቲክቶክ መንደራችን ሞቅ፣ ደመቅ፣ ሸብረቅ፣ የባንዳንና የባንዳ ልጆችን ወሽመጥ ቆረጥ፣ ጉምድ፣ ጉምድምድ እያደረግን እኛም ኮራ ጀነን፣ ቀብረር እያልን የታላቁን የዓድዋ የድል በዓላችንን ብናከብርስ ምን ይላችኋል…?

• ዘራፍ አካኪ ዘራፍ እያልኩ ልመጣ ነኝ…

47k 0 5 140 1.3k

• አትገቡም… አትወጡም…!

"…ዛሬ የካቲት 23/2017 ዓም የወሄጴኑ የኦሮሙማው አገዛዝ መሃል ፒያሳ በሚገኘው በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ሠራዊቱን ልኮ በደቡብ በር በምኒልክ አደባባይ በኩል የቤተ ክርስቲያኑን በር በዚህ መልኩ በውስጥም፣ በውጪም ጥርቅም አድርጎ ዘግቶ ውሏል። 😂

"…ወደ ገነተ ጽጌ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ለማስቀደስ ለመግባት ከሰሜን ሆቴል፣ ከአፍንጮ በር፣ ከሀብተ ጊዮርጊስ ድልድይ፣ ከቸርቸር ማለፍ አይቻልም ነበር አሉኝ። ፍተሻው ለጉድ ነበር፣ ነጠላ ያልለበሰ ሰውም ማለፍ አይችልም ነበር አሉኝ።

"…የሀገረ ስብከቱ ሊቀጳጳስ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ ኦሮሞ ናቸው ያውም የወለጋ ኦሮሞ፣ ዋና ሥራ አስኪያጁ የማነ ዘመንፈስ ትግሬ ነው። ዓድዋ ደግሞ… 😂😂 ኧረ ላሽ…

"…ቤተ ክህነቱ ዝም፣ ጭጭ፣ ነገ ቅዳሴ መግባት አትችሉም ቢላቸውም የሚተነፍሱም አይመስልም። አይ ኦሮሞ አለ አቢይ…!

"…በኮሪደር ልማት ሰበብ ያጸዱትና እንጨቆረር የከተቱት ምእመን አይመጣም፣ ቤተ ክርስቲያንን ያለ ምእመናን አስቀርተናል ብለው ቢያስቡም ሰዉ ከእንጨቆረርም ቢሆን በገፍ መምጣቱን አልተወም። ይሄም ለወሄጴኑ የእግር እሳት ነው።

"…በደብረ ዘይት የቅድስት ሥላሴን ካቴድራል አፍርሰው የሕዝቡን ሙቀት ለክተዋል። ዝም ጭጭ ነው ያለው ሕዝቡ፣ አሁን ተክለሃይማኖት መርካቶ፣ በዓታ፣ ግቢ ገብርኤል፣ አራዳ ጊዮርጊስ፣ ቅድስተ ማርያም፣ ቅዱስ እስጢፋኖስን በቀጣይ ቢያፈርሱት እንኳ ቅዱስ ሲኖዶሱ አይተነፍስም።

• እየመዘገባችሁ… ይብላኝ ነገ አኬሩ የተገለበጠ ጊዜ…

41.8k 1 31 50 1.5k

Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
~ የዘንድሮው የዘመነ ኦሮሙማው የ2017 ዓም የዓድዋ በዓል አከባበር… 😂😂😂 ጭው፣ ጭር፣ ዝም… ጮጋ…

"…ወዳጄ ጊዜ ቂጣ ነው… ይገለባበጣል…! እንዲህ እንደሆነ አይቀርም። እንደመሸም አይቀርም። ለዛሬ ግን እነ ወሄጴን መጣም፣ መጣም ደስ ብሏቸዋል። እምዬ ምኒልክን በአካል አግኝተው የተበቀሉ ያህል ነው የተሰማቸው አይገልጠውም።

• ከምር ጥልያን ራሷ ሳትደነግጥ አትቀርም። 😂

43.7k 1 29 72 1.2k

ድሮ ድሮ…

"…የታላቁ የዓድዋ የድል በዓል በሀገረ ኢትዮጵያ በዋና ከተማዋ በአዲስ አበባ በምኒልክ አደባባይ እንዲህ ባለ ከፍ ባለ ክብር ይከበር ነበር። ድሮ ነው ድሮ ከዛሬ ሁለት ሦስት ዓመት በፊት።

• የዘንድሮውን ደግሞ ቆይተን እናየዋለን።

42.3k 1 11 40 1.1k

• ቪቫ ምኒልክ…✊

"…የነፃነት ያይደለ የድል፣ የአሸናፊነት በዓላችንንና የድሉ መሪን የእምዬ ምኒልክን፣ የአርበኞቻችንን በዓል ሞቅ ደመቅ አድርገን እያከበርን ነው።

ከይቅርታ ጋር…

"…ይሄ የድል በዓል፣ የጠላት ባሪያ፣ አሽከር፣ ገረድ የሆናችሁ ጥቂት የትግሬ እና የኦሮሞም ስም የያዛችሁ፣ የምኒልክ ስም ሲነሳ የሚያስጓራችሁ፣ የሚነስራችሁም የባንዳና የባንዳ የልጅ ልጆች እንቁላል ቀቃይ መንገድ መሪ የአቃጣሪ ልጆችን፣ እንዲሁም የምኒልክ ኦርቶዶክስ መሆን የሚያበግናችሁ የዓረብ ገረድ የወሃቢይ እስላም እና ጆሌ ሚሽኖታን አይመለከትም።

• ዓለም በሦስት አቢዮቶች ተቀይራለች።

፩፦ በእሳት
፪፦ በኢንዱስትሪ
፫፦ በዓድዋ

"…እነዙህ ሦስት ክስተቶች የዓለምን ቋሚ ሥርዓት፣ የሰው ልጅን አኗኗር የለወጡ ናቸው። ከእነዚህ ውጪ የዓለምን ሥርዓት የለወጠ የለም። ወያኔም ኦነግም፣ ጴንጤም፣ የወሃቢ እስላሞችም ጊዜ ሰጠን ብለው ጊዜ የሰጠው ድንጋይ ሰባሪ ቅል መስለው ዊኒጥ ዊኒጥ ሊሉ ይችሉ ይሆናል እንጂ ታላቁን የዓድዋን ድል መቅበር አይቻላቸውምም።

"…ብዙ የትግሬዎችን እና የኦሮሞ ጴንጤ፣ የኦሮሞ የወሃቢይ እስላሞችን ገፆች ካየሁ በኋላ ነው ደስ ደስ እያለኝ ይሄን የጻፍኩት።

• ምኒልክ ለምን ማርያምን ብሎ ማለ? ይልልኛላ ወሄጰኑ… 😂

44.2k 1 18 115 1.7k

• የት ሀገር ነው አበባ ያስቀመጡት…? 😂

"…አቤት እግዚኦ… የምኒልክ ስሙ ለባንዳ፣ ለባንዳ የልጅ ልጅ፣ ለእንቁላል ቀቃይ፣ ለጠላት መንገድ መሪ ልጆች እኮ እሳት ነው። ፈጃቸው፣ ለበለባቸው፣ አቃጠላቸው። ትኩስ ድንች ነው የሆነባቸው። ጣልያንን ለማስደሰት ይህን ያህል መገረድ ለጉድ ነው። ራሷ ጣሊያን የኦሮሞን እንዲህ መገረድ አይታ ሽምቅቅ ሳትል የምትቀር አይመሰለኝም። ማርያምን አሽከር፣ ገረድ፣ ባርያማ አይንገስ። ባርያ አይንገስ፣ ገረድ…

• ቪ ቫ ምኒልክ…✌️

43.6k 1 10 103 1.6k

እንኳን አደረሰን

"…የዛሬ 129 ዓመት ልክ በዛሬው ዕለት የካቲት 23/1888 ዓም በዕለተ እሑድ በዓድዋ ሥላሴ ግብጻዊው ሊቀጳጳስ አቡነ ማቴዎስ በመሩት ሥርዓተ ቅዳሴ ላይ ንጉሠ ነግሥት ዳግማዊ ዐፄ ምንልክ እና ንግሥቲቱ እቴጌ ጣይቱ በተገኙበት ከሥርዓተ ከቅዳሴው ፍጻሜ በኋላ ተአምረ ማርያም ተነብቦ፣ የሊቀ ጳጳሱ ቡራኬና ቃለ ምዕዳን ተሰምቶ፣ በጦርነቱ ላይ የሚሰዉ ኢትዮጵያውያን ጀግኖችም እግዚአብሔር ይፍታህ ተብለው፣ ቁጥራቸውም ከሰማእታት ወገን እንደሆነ ተነግሮአቸው፣ በሁዳዴ በዐቢይ ጾም እህል እንኳ በአፋቸው ሳይቀምሱ ነው በቀጥታ በባዶ አንጀታቸው ወደ ጦርነቱ ሥፍራ ሄደው በግማሽ ቀን ያን ግዙፍ የአውሮጳ ጦር ድል ያደረጉት።

"…በዚህ ድል ዓለም በሙሉ ይደመማል፣ ይኮራልም። በዚህ ድል የማይኮሩት የእንቁላል ቀቃይ ልጅ የጠላት አድራሽ ፈረስ እስከ አምባላጄ ድረስ መንገድ መሪ የነበሩ ፀረ ኢትዮጵያ ባንዳ የባንዳ የልጅ ልጆች ብቻ ናቸው።

"…ዓድዋ ፀሐይ ነው። ፀሐይ የምትጋረደው ለጥቂት ጊዜ በደመና ብቻ ነው። ደመና ደግሞ ስስ ነው። ሲያዩት ተራራ፣ ባዘቶ ጥጥ ይመስላል እንጂ ይተንናል። ይበንናል። ፀሐይን የሚጋርድ፣ የሚደብቅ ምድራዊ ኃይል የለም። ወደፊትም አይኖርም። የክረምት ደመና ጥቂት ጊዜ ዊኒጥ ዊኒጥ ይላል ፀሐይን ለመጋረድ። በክረምት የደመናን ፀሐይን መጋረድ ያየ ሰው ፀሐይ መቼም የምትወጣ ላይመስለው ይችል ይሆናል። የክረምት ደመና የፀሐይን ሙቀት እንጂ ብርሃኗን መጋረድ አይቻለውም። ፀሐይ አዲስ አበባ ላይ ብትጋረድ ሌላ ቦታ አለች። መንጋቱ፣ ቀን መሆኑን ከደመናው ጀርባ በማትታየው ፀሐይ ብርሃን ይታወቃል።

"…ዓድዋም ፀሐይ ነው። ለጊዜው መቀሌና ሸገር፣ ትግራይና ኦሮሚያ እንደ ፀሐይ ደምቆ ላይገለጥ ይችላል። ደመና ወያኔ፣ ደመና ኦነግ ኦህዴድ ሲተንኑ ፀሐይ ዓድዋ በድምቀት ይከበራል።

43.8k 0 28 120 1.7k

“…ፈረስ ለጦርነት ቀን ይዘጋጃል፤ ድል ግን ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው።” ምሳ 21፥31 “…ጻድቃን ድል ባደረጉ ጊዜ ብዙ ክብር አለ፤ ኀጥኣን ከፍ ከፍ ባሉ ጊዜ ግን ሰው ይሸሸጋል።” ምሳ 28፥12

"…እንደምን አደራችሁ?
"…እንደምን አረፈዳችሁ?
"…እንደምን ዋላችሁ?
"…እንደምን አመሻችሁ?

"…እግዚአብሔር ይመስገን ብቻ ‼

46.2k 0 16 1.5k 1.9k

መረጃ አምስት

"…አርበኛ ዘመነ ካሤ ከሰባታሚት እስር ቤት ትፈታለህ ዕቃህን አዘጋጅ ይለዋል ፖሊስ። ዘመነም ተዘጋጅቶ እየጠበቀ ሳለ የእስር ቤት ጓደኞቹ እነ ኮሎኔል ታደሰ እሸቴም ወደ ዘመነ በመቅረብ እንኳን እግዚአብሔር ረዳህ። ሰላም ሁን። እንግዲህ ተመላልሰህ ባትጠይቀን እንኳ አንዳንዴ አትርሳን ይሉታል። ዘመነም ጠጋ ብሎ "ኮሎኔል አይዟችሁ፣ በቅርቡ ይሄን እስር ቤት ሰብረነው ነፃ ትወጣላችሁ! ብሏቸው ተሰነባበቱ።

"…የሆነ ቀን ላይ ዘመነ እዚያው እስር ቤት ደውሎ እነ ኮሎኔል ለመውጣት እንዲዘጋጁ ይነገሯቸዋል። ማንችሎት ወደ እስርቤቱ ኃይል እንዲያስጠጋ ሲጠየቅ "ኋላ በሕግ ብጠየቅስ?" ብሎ አንገራግሮ የነበረ ቢሆንም ኃይል ተጨምሮ ዘመነ ካሤም ቃሉን ጠብቆ እነ ኮሎኔል ታዴም ከሰባታሚት ወጡ።

"…ኮሎኔሉ መልካም ሰው ነበር። እነ ፓስተር ምስጋናው፣ እስክንድር ነጋና ፋፍህዴን፣ እነ ሀብታሙ ዘፍራሳ፣ አቤ እስክስ ናቸው ኮሎኔሉን የጠለፉአቸው። በሽምግልናው ወቅትም ከእነ ባዬ ጋር ነበሩ። ኋላ ላይ የዐማራ ፋኖ በጎንደር ውክልና ሳይሰጣቸው ዘመነ መመረጥ የለበትም ብለው እስክንድርን መረጡ። ዘመነም አዘነባቸው። ብዙም አልቆዩ ኮሎኔሉ በውጊያ ላይ በጥይት ተመተው ቆሰሉ። ቆስለውም ተኙ። እንግዲህ እኚህ ለሀገራቸው ብዙ ሠርተው መጨረሻ ላይ ቆስለው ሕክምና እንኳን አጥተው በስቃይ ላይ የነበሩ ኮሎኔል ናቸው የሚደርስላቸው አጋዥ ኃይል አጥተው በኦሮሙማው ጦር በግፍ የተሰዉት።

"…ለእኔም ወዳጄ ነበሩ። በሽምግልናውም ወቅት ክፋት አላየሁባቸውም። ልብ በሉ የዐማራ ፋኖ አንድ ባለመሆኑ ምክንያት ጭራቅ ቡልጉ ጅቡ ኦሮሙማ ተራ በተራ እየበላቸው ነው። የዐማራ ፋኖ አንድ እንዳይሆን የሠራችሁ እግዚአብሔር ይፍረድባችሁ። በተለይ አስረስ መዓረይ ግን እግዚአብሔር ይይልህ። ሌላ ምንም አልልም።

• ነፍስ ይማር ወዳጄ…

48.9k 1 20 107 2.2k

መረጃ አራት…

አዲስ አበባ ገርጂ አካባቢ የሚገኘው የኢትዮ ፓረንትስ ት/ቤት ተማሪዎች 129ኛውን የዓድዋን በዓል ለማክበር በተዘጋጁበት ወቅት የአብይ አህመድ ፖሊሶች ትምህርት ቤቱን ከበው በዓሉ እንዳይከበር አስተጓጉለው የትምህርት ቤቱን ዳይሬክተር፣ ሠራተኞችና የተወሰኑ ተማሪዎችን በፓትሮል ጭነው ወስደዋቸው እንደነበር ሰማነ። ወደ ዘብጥያ የተወሰዱት የትምህርት ቤቱ ዳይሬክተር፣ ተወሰኑ የአስተዳደር ሠራተኞችና ተማሪዎች የዚያኑ ዕለት ማታ ከብዙ ስድብ፣ ጉሸማና ማዋረድ በኋላ ሁለተኛ አይለምደንም ብለው በወረቀት ላይ አስፈርመው እንደለቀቋቸውም ሰማነነ።

"…ኢትዮጵያኑ የዓድዋ በዓል አክባሪዎች በፈረሙት ወረቀትም ላይ "የፅንፈኛው መጠቀሚያ፣ የፅንፈኛው አጀንዳ ተቀባይ፣ የፅንፈኛው ዓላማ ምናምን የሚል በግሳግንስ የተሞላ የካድሬ ጽሑፍ ላይ እንደሆነና ሁለተኛ እንዲህ ዓይነት በዓል እናከብራለን ብላችሁ ብትሞክሩ በትምህርት ቤቱ ላይ ለሚፈጠሩና ለሚደርሱ ነገሮች ሁሉ ሓላፊነት እንደሚወስዱ አስገድደው አስፈርመው እንደለቀቋቸውና በተጨማሪም ተማሪዎች ወደ ቤት ሲሄዱም የሀበሻ ነጭ ልብስ ለብሰው ከታዩ እንደሚታሰሩ የኦሮሙማው ፎሊሶች እየዛቱ ሲናገሩ የትምህርት ቤቱ ተማሪዎች የደህና ቤተሰብ ልጆች ስለሆኑ እንዲህ ያለ ነገር ዓይተው ስለማያውቁ በጣም ተጨናንቀው እንደ ነበርም ሰማነ።

"…እውነት ከሆነ ግን በቃ ዕድሜ ለአስረስ መዓረይ በዓድዋና በምኒልክ ላይ ኦሮሙማው አምርሯል ማለት ነው።

• ወይ ባልቻ አባ ነፍሶ ተብሎ ይሞከር ይሆን እንዴ?

45.6k 1 32 36 1.3k

መረጃ ሦስት

• የስም ቅያሬ ከምኒልክ አደባባይ ወደ ዓድዋ ዜሮ ዜሮ ሙዚየም

"…የአብይ አሕመድ ብልፅግና መለስ ዜናዊ የጀመረውን ግድብ፣ ኃይማርያም ደሳለኝ መሠረት የጣለውን ድልድይ፣ የአርባ ምንጭ ገበሬዎች የተከሉትን ሙዝ፣ የከፋ ገበሬዎች ያለሙትን የቡና ችግኝ በዐቢይ አሕመድ ሓሳብ አመንጪነት እያስባለ ስሙን ተነቅሰን እንድንዞር የሚወተውተን ባርቲ እንደምንም ብሎ አለማምዶ፣ አለማምዶን የዓድዋን በዓል ዜሮ አስገብቶት አረፈው።

"…መጀመሪያ ዓድዋ ዜሮ፣ ዜሮ አሉት። በእሱ ትችት ሲበዛባቸው የዓድዋ ሙዚየም አሉት። የምኒልክ ሓውልትን ሸፈኑት፣ ስሙንም ደመሰሱት። ዓድዋ ሙዚየም አሉት። ምኒልክ አደባባይ ቀረ። ተረሳ።

"…አይሆንም እንዳትሉ። በቅርቡ ኦሮሙማው የምኒልክ ሃውልትን አፍርስልን ካሉት ልክ እንደራስመኮንን ሃውልት ያፈርሰዋል። ሙዚየሙን ከለከለን ብሎም ሊያነሣው ይችላል። እንደ መሬት መንቀጥቀጡ ሕዝቤ ይቀልዳል እነሱ ሥራ ላይ ናቸው። ሰሞኑን ቤተ ክርስቲያኑ ረብሾኛል ያለው ብልጽግና ቤተ ክርስቲያኑን እንደናደው፣ እንዳፈረሰው ሰምቻለሁ።

"…እነ ጃዋር በፍጥነት ሲሉ፣ አቢይ አሕመድ አይደለም ቀስ፣ በቀስ በዝግመት ነው የሚለው።

• ዓድዋ ሙዝየም ግን የት ነው?

49k 1 17 61 1.4k
18 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.