የሰለፍያ ደዕዋ በቻግኒالدعوة السلفية فى مدينة الشاغنى


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


ወደ ቻናሉ👇 ለመቀላቀል 👇ከፈለጉ👇
t.me/selefiyadawabechagni
አስተያየታችሁን 👇ወይም 👇እርማታችሁን👇
t.me/selefiyadawabechagnibot
ይፃፉልን። ይላኩልን።

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


የ ሸይኽ ሙሐመድ ሀያት ቻናል dan repost
ይዩልኝ ማለት ምን ማለት ነው ?

➷➴➷
https://t.me/SheikMohmmedHyatHara


የ ሸይኽ ሙሐመድ ሀያት ቻናል dan repost
✍قال الشيخ الفوزان حفظه الله

📌من تمسك بالسنة سيلقى عنتا وتعبا
واحتقارا وازدراء أو تهديدا من الناس لكن
عليه أن يصبر ولا يتضعضع عن الحق

📓( شرح السنة ( 306 )


➷➴➷
https://t.me/SheikMohmmedHyatHara


Muhammed Mekonn dan repost
Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
ይሰማል አይደል?
◈◈◈◈◈◈◈

💬 ከዚህ በፊት ሸይኽ ሀሰን ገላው ታስረው ዳዕዋው አልቆመም። ሸይኻችንም ምንም አልሆኑም። ዛሬም ሸይኽ ሙሐመድ ሀያት ታስረው ዳዕዋው አይቆምም ይቀጥላል ሸይኻችንም ምንም አይሆኑም።

🏝 የሚያሳዝነው ንፁሃንን እያንገላታ ከጌታውም ከህዝቡም የሚጋጨው ሚስኪን የመጅሊስ ስልጣን ይዞ የሚረብሸው ሁሉ ነው።

◉ አላህ ልብ ይስጣቸው!

◈ 💬◉ 💬 ◉💬 👇👇
https://t.me/AbuImranAselefy/10567


Muhammed Mekonn dan repost
📈 ታላቁ የየመን ሙሀዲስ አል ኢማም ሙቅቢል ብን ሀዲ አልዋዲዒ رحمه الله تعالى ስለ ሂዝብዮች /ቡድንተኞች/ ሲናገሩ እንዲህ ይላሉ ፦
"أركان الحزبية ثلاثة : -
١ التلبيس
٢ الكذب
٣ الخداع

📚 رحلات دعوية ص ١٤١

🫳 "የቡድንተኞች/ሙብተዲዖች/ መሰረቶች ሶዎስት ናቸው። እነሱም፦
1 ሀቅ እና ባጢልን ማቀላቀል
2 ውሸት
3 ሽወዳ"


📚 ሪሳላ ደዐዊያ ገፅ 141

https://t.me/Abujaefermuhamedamin
https://t.me/Abujaefermuhamedamin
https://t.me/Abujaefermuhamedamin


Semir Jemal dan repost


Semir Jemal dan repost
(☝️⚡️)
"ከሰለፊዮች እና ከኢኽዋኖች ልዩነት መካከል በጥቂቱ..."
"""""""""""
⚡️ከሰለፊዮች መገለጫዎች በጥቂቱ:

↪️ ሰለፊዮች ጥርት ወዳለው ወደ ተውሒድ ይጥ'ጣራሉ፣

↪️ ሰለፊዮች ቁርኣንና ሱንናን በሰለፎች ግንዛቤ (አረዳድ) ነው የሚከተሉት፣

↪️ የሰለፊዮች ዐቂዳ ግልፅ ነው፣

↪️ ሰለፊዮች ስልጣንን ከመፈለጋቸው በፊት ኡማውም ወደ-ማጥራት ነው ሚቻኮሉት (ሚጥ'ጣሩት)፣

↪️  ሰለፊዮች ከቢድ'ዐ እና ከሙብተዲኦች ያስጠነቅቃሉ፣

↪️ ሰለፊዮች የታነፁት ወይም ሌሎችን ሚያንፁት፡ "በእውቀት፣በትዕግሥትና በተርቢያ...ነው"

↪️ ሰለፊዮች: "ዲሞክራሲና ሰው ሰራሽ ሕጎችን" አበክረው ይቃወማሉ፣

↪️ ሰለፊዮች የመስሊም አስተዳደር ሆነው የተሾሙትን በወንጀል አስካላዘዙ ድረስ፣ለነሱ መታዘዝ እንዳለብን ያዛሉ፣

↪️ የመንሐጅ መሰረቱ እውቀት ሲሆን፣ይህ እውቀት ደግሞ በትክክለኛ በሰለፎች አረዳድ አካሄድ በሚሄዱ በዑለማዎች የታነፀ ነው፣

↪️ በዘመናችን ካሉ ስመጥር የሆኑ ዑለማዎች መካከል፡ቢን ባዝ፣አል-አልባኒ፣ አብኑ ዑሰይሚን...(ረሂመሁሙሏህ) ይገኙበታል፣

🚫 ከኢኽዋኖች መገለጫዎች መካከል በጥቂቱ፡


↪️  ኢኽዋኖች ምንም አይነት ዐቂዳ ሳይለዩ "አንድነት" የሚል "መፈክርና መሪ-ቃል" አራማጆች ናቸው፣

↪️ ቁርኣንን ከዘመናዊ ርዕዮተዓለም ጋር ነው የሚያራምዱት፣

↪️ ኢኽዋኖች ሕዝብን በመሰብሰብ ላይ ነው የተጠመዱት፣ እንዲሁም ግልፀኝነት የላቸውም፣

↪️ ኢኽዋኖች የመጀመሪያው ዓላማቸው ስልጣንን መቆናጠጥ ነው፣

↪️ ኢኽዋኖች፡ "ከሱፊዮች፣ከ'ዐሽዓሪዎች እንዲሁም ከሺዓዎች ጋር ተደባልቀዋል፣

↪️ ኢኽዋኖች የታነፁት በእውቀት ሳይሆን በአክቲቪስትነት፣በሚዲያ እንዲሁም በስሜታዊነት...ነው የታነፁት፣

↪️ ኢኽዋኖች ኢስላማዊ ዲሞክራሲ አለ ብለው ያምናሉ፣

↪️ ኢኽዋኖች፡ አመፀኞችን፣ ሁከቶችን፣ ሰልፎችን ያበረታታሉ፣

↪️ የኢኽዋኖች መንሐጅ የታነፀው በአክቲስቶች (በአንቂዎች) እና በፀሐፊዎች ነው፣

↪️ የኢኽዋኖች ዋናዎቹ (መሪዎች) የሚባሉት፡ "እንደነ ሐሰኑል በንና፣ሰዪድ ቁጥብ፣ዩሱፍ አል-ቀረዷዊ...ተጠቃሾች ናቸው።

📝 Translated by: Abu Hafsah
     
@semirEnglish


Bahiru Teka dan repost
👉 የስህተት ማስተካከያ

በመጀመሪያ ጫፍ የወጣ የመብት ረገጣ የሚለው ፁሑፍ ዝም ብሎ በችኮላ ወይም ስም ለማጥፋት ተፈልጎ የተፃፈ ሳይሆን ችግሩ ከተከሰተበት ጊዜ ጀምሮ 11 የሚሆኑ ወንድሞች በሓራ ከተማ ፖሊስ ጣቤያ እንደታሰሩና እነሸይኽ ሙሐመድ ሓያት ደግሞ በቀጥታ ወደ ወልዲያ ማረሚያ ቤት እንደ ተወሰዱ ከምናምናቸው ወንድሞች የተነገረን ሲሆን በማግስቱ ደግሞ ሊጠይቋቸው በሄዱ ሰዎች አማካይነት ተሰማ በተባለው መረጃ ጉዳያቸው ከ10 ቀን በኋላ ይታያል እንደተባሉ ነበር ።
ይህ መረጃ እስከዛሬው ሚያዚያ 17/2017 ጫፍ የወጣ የመብት ረገጣ የሚለው ፁሑፍ ከመፃፌ በፊት ለማረጋገጥ እስከ ጠየቅሁበት ድረስ የነበረ ነው ። ይሁን እንጂ ወደ ማምሻ አካባቢ ይኸው መረጃ ባደረሱኝ ወንድሞች ተቃራኒ የሆነ ነገር ደረሰኝ ። ይኸውም እነሸይኽ ሙሐመድ ሓያት መጀመሪያ ሓራ ፖሊስ ጣቢያ እንደገቡና ወዲያው ፖሊስ ፍ/ቤት አቅርቧቸው ለምርመራ ተጨማሪ ጊዜ ጠይቆ ፍ/ቤቱ 10 ቀን እንደሰጠና ጣቢያ ቦታ ስለሌለ በሚል ማረሚያ ቤት ተወሰዱ የሚል ነው ።
የመጀመሪያው መረጃና ሁለተኛው መረጃ ፍፁም የተለያዩ ሲሆኑ የመጀመሪያው የተሳሳተ ነበር ማለት ነው ። በመሆኑም በፁሑፉ ላይ የተላለፈው መልእክት የተሳሳተ ነበር ። ለዚህ የተሳሳተ መረጃ በራሴና መረጃውን ባደረሱኝ ወንድሞች ስም ልባዊ ይቅርታ እጠይቃለሁ ። መሳሳት የሰው ልጅ ባህሪ ሲሆን የሚጠላው በስህተት መቀጠል ነው ። ተሳስቶ ከስህተት መመለስ ውርደት ሳይሆን እውቀት መሆኑን ማወቅ ጥሩ ነው ።
የተፈጠረው ስህተት መሆኑን ከገለፅኩኝ በኋላ ፁሑፉን አጥፍቼዋለሁ ። መልእክቱን ያጋራችሁ በሙሉ እንድታጠፉትና እርማቱን እንድታጋሩ በአላህ ስም እጠይቃለሁ ።
በመቀጠል ራሴንና ወንድሞቼን ማስታወስ የምወደው መረጃ መስጠት ምስክርነት ስለሆነ የምንሰጠው መረጃ ውሸት ሆነ ማለት የውሸት ምስክርነት ነው ማለት ነው የሰጠነው ።‼
የውሸት ምስክርነት በኢስላም ያለው ቦታ በነብዩ ምላስ በጣም አስፈሪ በሆነ ሁኔታ ተነግሮናል ። በመሆኑም አንድ መረጃ ከመስጠታችን በፊት በጣም እርግጠኛ መሆን እንዳለብንና ባልሆነው ነገር በፍፁም መረጃ መስጠት እንደሌለብን ሳስታውስ የተሳሳተ መረጃ ለነብዩ ደርሷቸው በንፁሃን ላይ ጦር ማዝመታቸውን ለሚያውቅ ሰው የተሳሳተ መረጃ አደጋ ምን ያክል እንደሆነና ለመዋሸት የማይፈልግ ሰውም የተሳሳተ መረጃ ሊሰጥና እሱን አምኖ ሌሎችም ሊሳሳቱ እንደሚችሉ ማወቅ አይከብደውም ።
አሁንም በድጋሚ ለተፈጠረው ስህተት ልባዊ ይቅርታ እጠይቃለሁ ።

https://t.me/bahruteka


አህባሹ ኡመር ኩምቦልቻ.m4a

⚠️ አህባሾች በዝህ ልክ ደረታቸውን ነፍተው ባደባባይ ወሃቢያ የሙስልም ጠላት ነው እያሉ ይደነፋሉ

✖️እነ አቶ እኽዋኒና ሙመይዓ ግን ተደምረናል ብለው ይርመጠመጣሉ ለአህባሽ ነፃነት ሰተው በሰለፊዮች ላይ ያሴራሉ ፣ የሰለፊዮችን መድረሳ ይበትናሉ ፣ የሰለፊያ መሻይኾችን ያስራሉ ፣ ሰለፊዮች ለኡማው ተውሒድን እንዳያደርሱ በየ ቦታው በጀት መድበው ደእዋ እንዳይሰሩ ፖሊስ ይሊካሉ …
የቻላቹትን በሙሉ አድርጉ ነገር ግን መንሀጀ አል_ሰለፊያን አለህ ነው ሚጠቢቃት

عن ثوبان، قال: قال رسول الله صلى الله عليه وسلم: ((لا تزال طائفة من أمتي ظاهرين على الحق، لا يضرهم من خذلهم، حتى يأتي أمر الله وهم كذلك))
رواه مسلم، رقم: 1920.
ከሰውባን በተዘገበ ሐዲስ ረሱል ﷺ እንድህ ብሏል፦
ከኔ ሕዝቦች መካከል ኣንዲት ቡዱን በሐቅ የበላይ ከመሆን አትወገድም። ያዋረዳቸው አይጎዳቸውም የአለህ ትዛዝ እስከሚመጣ ድረስ የበላይ ከመሆን አይወገዱም።
(ሙስልም 1920 ላይ ዘግቦታል)

✍ lbn_jemal

የተለያዩ ት/ቶችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችን ⤵️ #join በማለት ይቀላቀሉ

https://t.me/lbn_jemal
https://t.me/lbn_jemal


Abu abdurahman dan repost
ጥብቅ ማስጠንቀቂያ‼️
በምስሉ በምትመለከቱት መልኩ በቴሌግራም እና ዋትሳፕ የውስጥ መልእክት በምታውቁት ሰው ስም መስለው የሚመጡላችሁን ሊንኮች ከመክፈት ተጠንቀቁ!!
🔸እንደሚታወቀው ሃከሮች በተለያየ ጊዜ ዘዴዎችን ቀያይረው የሰዎችን የማህበራዊ ሚዲያ ትስስሮችን ይጠልፋሉ፣ አሁን ደግሞ በዚህ መልኩ የአንድን ሰው ከጠለፉ በኋላ የሱን ጓደኞች ደግሞ በተጠለፈው ሰው ስም አድርገው ሊንክ እየላኩ በቀላል መንገድ የብዙዎችን የማህበራዊ ሚዲያ ትስስሮችን መጥለፍና የፈለጉትን ማድረግ ይችላሉ።
"ሊንኩን ተጭናችሁ ፎቶዋችሁን ተመልከቱ…" እያሉም በስልካችሁ የከፈታችሁትን አካውንት ከመጥለፍ ባሻገር የብልግና ምስሎችን እያሰራጩ ይገኛሉ፣ በምንም ተኣምር በዚህ መልኩ በምታውቁት ሰው ስም የተላኩ ምንነታቸው ግልፅ ያልሆኑ ሊንኮችን ከመክፈት ተጠንቀቁ!! ብዙዎች ቴሌግራማቸው እየተጠለፈ ስለሆነ ለሌሎችም ሸር በማድረግ አዳርሱ!!
#join ⤵️ ቴሌግራም ቻናል
https://telegram.me/IbnShifa
https://telegram.me/IbnShifa


" ዓብዱረህማን ዑመር" dan repost
የኢኽዋንና የሰይጣን ውለታ መላሽነት¡

ባለፈው ፍትሃዊ ሆንኩ ብየ ስለ የበፊቱና የአሁኑ መጅሊስ እንዲህ 👉 t.me/Abdurhman_oumer/9296
ፅፌ ነበር።
እነ አጅሬም ብዙም ሳይቆዩ፦ ለካ በመጥፎ ብቻ ነው ውለታ መመለስ የሚችሉበት! ሰሞኑን ያያችሁትን የፅንፈኝነት ጥግ ፈፅመዋል።

አላህ ይጠብቃቸው ሸይኽ ሱለይማን አርሩሃይሊ፦
ኢኽዋን አል ሙፍሊሱን ምንም ያህል ብታደርግላቸው ከሸራቸውና ከተንጎላቸው አትድንም። ከእባብ የባሱ ናቸው። ይላሉ።

የኢኽዋንን ውለታ ሳስታውስ አንድ ታሪክ ትዝ ይለኛል። ታሪኩ እንዲህ ይወራል፦ ሰዎች መስጅድ ውስጥ በተሰባሰቡበት “አዑዙ ቢላህ በሉ” ተባሉ አሉ። አንዱ ሰው እኔ ከማነም መጣላት አልፈልግም ከሰይጣንም ቢሆን መጣላት አልፈልግም “አዑዙ ቢላህ!” አልልም ይላል። ቢሉት ቢያደርጉት “አዑዙ ቢላህ” አልልም ከማነም መጣላት አልፈልግም። ብሎ ግድድ ይላል። ከቤቱ መጥቶ ባለቤቱ ጋር እንቅልፍ ላይ ባለበት አጅሬ (ሰይጣን) በህልሙ ይመጣና ዛሬ የዋልክልኝ ውለታ በምንም የሚከፈል አይደለም አዝየህ ነው የምዞረው አለው። እንዳለውም አዝሎት ሲዞር ከቆየ በኋላ ሰውየው እንዲህ አለ፦ አውርደኝና ሽንት ቤት መጠቀም ፈልጌያለሁ አለው። ሰይጣንም አረ በፍፁም ያንተ ውለታ በምንም የሚከፈል አይደለም እንዳዘልኩህ በላየ ላይ ልቀቀው አለው። ሚስኪኑ ሰውየም የሱን ወሬ ሰምቶ በተኛበት ተረክ ሲያደርገው ወይዘሪት ሚስት የለለ ደንግጣ አረ ምን ጉድ ነው ትላለች? ባልም አንቺው ተይው የእጀን ነው ያገኘሁት መስጅድ ውስጥ “አዑዙ ቢላህ” በል ተብየ ማነንም አላስቀይምም ከማነም ጋር አልጣላም ብየ አሁን ውለታውን እየከፈለኝ ነው አለ። ውለታውን ሲከፍል እንዲህ ነው።

ኢኽዋን ዘንድ የፈለገ ፍትሕን ብታስቀምጥ ሙሉ በሙሉ እንደነሱ ካልተበላሸህ ደስታ አያገኙም ሴራቸውንም አይተውም።


አቡ ዐብዲላህ ሰዕድ ዐብዱለጢፍ dan repost
Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
✨ ይህን ዲን አሰራጩ!!

🎙 አሸይኽ ፈውዛን ሀፊዘሁላህ!


𝓳𝓸𝓲𝓷 ! ⇣⇣⇣📲⇣⇣⇣ 𝓼𝓱𝓪𝓻𝓮 !!

             👇👇

https://t.me/sead429


Muhammed Mekonn dan repost
✅ አዲስ የተጠናቀቀ ደርስ

📚 شرح مسائل الجاهلية
📚 ሸርህ መሳኢሉል ጂሂሊያህ

📝 لشيخ الإسلام المجدد الشيخ محمد بن عبدالوهاب رحمه الله
📝 በሸይኹል ኢስላም ሙሐመድ ብን አብዱልወሃብ አላህ ይዘንላቸው!

📝 شارح: فضيلة الشيخ صالح بن فوزان بن عبد الله الفوزان حفظه الله

ከክፍል አንድ ጀምሮ ↙️ ↙️
https://t.me/bahirutekadurus/746


🔸 ወቅታዊ ምክር (ማበረታቻ)

🔊  " የሃራ ወንድሞቻችንን ልብ መጠገኛ"

🎙በሸይኽ ዐብዱል ሐሚድ ያሲን አል_ለተሚይ!


https://t.me/abdulham/2429
https://t.me/abdulham/2429
https://t.me/abdulham/2429


Abdusomed Muhamed dan repost
📌የአህባሹን ዘመን አስታዎሰኝ

ያኔ ቻግኒ መተከል ሸይኽ ከማል አፍሬ
(هداه الله وسدده) ላይ ቂረአት ስንቀራ በአህባሾች ሴራ ደረሶች ተበተኑ።

ሴራው እንዲህ ነበር ከደረሶች አምስት ደረሶች ገደማን አሳሰሩ ከታሰሩትም መካከል አቡል አባስ የኢብኑ ሙነወር ወዳጅ ይገኝበታል።

የሚገርመኝና የሚያዛዝነኝ ነገር  እነ ኢብኑ ሙነወር ያን ጠንካራ አቋም ቀይረው ዛሬ የመጅሊስ አጋፋሪ መሆናቸው ነው።

ያኔ የአህባሹ መጅሊስ ግን ሸይኹን አላሰረም ነበር ዛሬ ግን....።

በዚያ ምክኒያት ከደርስ የተቋረጡ ተስፋ የቆረጡ ብዙ ደረሶች ነበሩ።

ዛሬ ላይ የኢኽዋኑ ጥምር መጅሊስ አካሄድ ከአህባሹ ግዜ እጅጉን የከፋ እረምጃዎችን እየተራመደ ይገኛል።

ለምሳሌ፦ በየሀገሩ ለተውሂድ ዳዕዋ ደፋ ቀና የሚሉትን ወንድሞች፣ኡስታዞችንና መሻይኾችን ማሸማቀቅ፣ ማሳደድና ማሳሰርን ተያይዞታል። ሁሉም ያልፋል ትዝታም ይሆናል።

✒️አቡ ፊርደውስ

https://t.me/abdu_somed
https://t.me/abdu_somed


Abdusomed Muhamed dan repost
የአሁኑ መጅሊሶች ከአህባሹ መጅሊስ በምን ተለያቹህ???

ጥምር መጅሊሱ ለኢስላም የማይሰራ መሆኑን ግልፅ አድርጎ የሚያሳይ ድርጌት ነው። ለኢስላም የሚሰራን ሸይኽ ማሰር እንዲሁ ኢስላምን ለመማር የተሰማሩ ደረሶችን መበተን እጅጉን አስቀያሚ ተግባር ነው።


" ዓብዱረህማን ዑመር" dan repost
ከውጭ ጠላትም ከውስጥ ጠላትም ክፋት አላህ ይጠብቀን።

የሀራ ወንድሞቻችን እንደ ፍልስጤም ትልቅ  ዱዓ አስፈልጓቸዋል። በአሁኑ ሰዓት በአረመኔዎች ከባድ መከራ እየደረሰባቸው ይገኛል።
   በየ ሀገሩ የተሰባሰቡ በሱና ፈለግ የታሸ ዒልም ሲቀስሙ የነበሩ ደረሶች ከመበተን የከፋ መከራ ምን ይመጣል። ይሄን ከምሰማ  ቦታው ላይ ሆኘ አንገቴን ተቀልቼ በሞትኩ ተመኘሁ።
ፅንፈኛው መንጋ የኢኽዋንና የሙመይዓ ጥምር መጅሊስ በመንግስት ጣልቃ ገብነት “በሱና ሰዎች" ላይ እኩይ ተግባሩን ቀጥሏል። በአሁኑ ሰዓትም እነዛ ሁሉ በርካታ ደረሶች ተጠርገው እንድወጡ ተደርጓል።
  ቦታው ላይ ካሉ ወንድሞቻችን በደረሰኝ መረጃ መሰረት ሸይኽ ሙሐመድ ሀያትን ጨምሮ ዋና ዋና የሚባሉ ወንድሞቻችንን ወስደዋቸዋል። ለማመን በሚከብድ መልኩ አህባሾችን ጫታቸውን እየቃሙ ጋብዘዋቸው እየዶለቱ ነው።
    የሙብተዲዖችን ክፋት ለማወቅ ሌላው ቀርቶ ይሄን እኩይ ስራቸውን መመልከት በቂ ነው።
     የአላህ ባሮች ሆይ ልክ ካፊሮችን በሚያደርሱብን አደጋ ከምንታገለው ባልተናነሰ የቢድዓ ባለቤቶች የሚያደርሱት ቀላል የሚባል አይደለምና ኢኽዋንና ሙመይዓዎችም ነፍጠኛ ሙብተዲዖች መሆናቸውን በማረጋገጥ ከዲናችን ጎን እንቁም።
  በዋናነትም አላህ ከፅንፈኞች ተንኮል ጠብቆን ድልን እንድያጎናፅፈን በቅድሚያ በአላህ በኩል ካጓደልናቸው ነገሮች (ከወንጀሎቻችን) እንመለስ ከዛ በመቀጠል በዱዓእ ላይ እንበራታ። የሀራ ሰለፍዮች አላህ ከእናንተ ጋር ይሁን ድልን ያጎናፅፋችሁ። እሱ በሁሉ ነገር ላይ ቻይ ነው።

t.me/Abdurhman_oumer


Bahiru Teka dan repost
✅ የሐራ ሰለፍዮች የድሉን ጉዞ ጀምራችኋል ቀጥሉ

በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል ያላችሁ ሰለፍዮች ከኢኽዋኖች ጋር በሚደረገው ትግል አሸናፊ የምትሆኑት በትእግስትና በሰላማዊ መንገድ ነው ። የሰላም አካሄድ ለሰለፍዮች የድል መቀዳጃና ትርፋማ ነው ። ለኢኽዋን ደግሞ ሽንፈትና ኪሳራ ነው ። ምክንያቱም ኢኽዋኖች ሰለፍዮችን እናሸንፋለን ብለው የሚያስቡት በሚሰሩት ድራማ ማኖ እንዲነኩላቸው በማድረግ ነው ። ሰለፍዮች ይህን ቀመራቸውን ተረድተው የሚለኩሱትን እሳት ሳያራግቡት ሲተውት ይጠፋል ። የዚህን ጊዜ ኢኽዋኖች ይከስራሉም ይሸነፋሉም ።
አሁንም ሓራ ላይ የተሞከረው ይኸው ነበር ። ሁኔታውን ወንድሞች ሲነግሩን ኢኽዋኖች የሓራ ሶፋ መስጂድ ጀማዓ ( ሰለፍዮች) የሓራ ሳይሆን የሀገር ስጋት እንደሆነና መስጂድ ሳይሆን የጦር መሳሪያ ማከማቻ እንደሆነ ፣ ሸይኽ ሙሐመድና ባልደረቦቻቸው ኪታብ የሚያስቀሩ የሸሪዓ እውቀት ባልተቤቶች ሳይሆኑ የጦር ጄኔራሎችና በኪታብ ማስቀራት ሺፋን ሽብርተኛን የሚያሰለጥኑ እንደሆኑና በፍጥነት ካልተወገዱ ሀገርን ስጋት ላይ የሚጥሉ ተደርጎ ተስሎላቸው ነው የሚመስለው ይላሉ ። ምክንያቱም ኪታብ የሚያስቀራ ሸይኽና ኪታብ የሚቀራ ደረሳና ኪታብ እንጂ የሌለበት መስጂድ በመከላከያ ሊከበብ አይችልምና ።
ሁከት እንኳን ቢነሳ ሶስት አራት ፖሊስ በቀላሉ ሁኔታውን መቆጣጠር ስለሚችል ። ነገር ግን የኢኽዋኖች ይህ አካሄድ ወጣቱን ስሜታዊ አድርጎ አላስፈላጊ እንቅስቃሴ ውስጥ እንዲገባ ስለሚያደርገው የዛን ጊዜ አሸናፊና አትራፊ እንሆናለን የሚል ስሌት ተሰልቶበት የነበረ ለመሆኑ ብዙ ማሳያዎች ነበሩ ።
ነገር ግን የሓራው የሰላም አምባሳደር ሸይኽ ሙሐመድ ሐያት ከሱስና ከአጓጉል ልምድ እንዲሁም ከባእድ አምልኮ አውጥተው በተውሒድና ሱና አንፀው ከሁከትና ብጥብጥ ኪሳራ እንጂ ትርፍ እንደለሌ አስርፀው ይህ ደግሞ የሰለፍዮች ሳይሆን የኢኽዋኖች አካሄድ መሆኑን አስተምረው ኮትኩተውና ተንከባክበው ያሳደጉት ወጣት ምንነቱን አሁን አሳይቷል ።
የሓራ መስጂድ ጀማዓ ከሩቅ እንደሚሳለው ሳይሆን የሰላም ተምሳሌትነቱን በማስመስከሩ የሀገር ትልቅ ሀላፊነት ያለበት መከላከያ ሰራዊት ታዝቦ ትቷቸው ሄዷል ።
በሸይኽ ሙሐመድ ሐያት ተርቢያ የታነፀው ወጣት መልከጥፉን በስም ይደግፉ እንደሚሉት ሰላማዊ ሰልፍ በሚሉት የጥፋት ሰልፍ የማይሳተፍ ፣ ከሱስና ከአጉል ልማድ የራቀ ፣ በሀገር ልማት ላይ ከማንም በፊት ቀድሞ የሚገኝ ፣ ቁጭ ብሎ በምኞት ድህነትን ሳይሆን በመስራት መክበርን መርጦ ታታሪ ለመሆኑ ከወዳጅ በፊት ጠላት ይመሰክርለታል ። ይህ እውነታ ዛሬ ኢኽዋኖች በኡኡታ የጠሩዋቸው የመንግስት አካላት በአካል አይተውታል ።
በመሆኑም የሓራ ሰለፍዮች የጀመራችሁት በሰላም የማሸነፍ ጉዞ ቀጥሉበት ። መሻኢኾችን በማሳሰርና ደረሶችን በመበተን ተውሒድና ሱናን እንገታለን ብሎ ማሰብ ቂልነት ነው ። ተውሒድና ሱና እንኳን ሸይኽ ሙሐመድ ሐያት ታስረው አይደለም ነብዩም ሞተው አልተገታም ። አሁንም ድሉ የሰለፍዮች ነው ። ሰለፍዮች ቢታሰሩም ፣ ቢገረፉም ፣ ቢገደሉም አትራፊና አሸናፊዮች ናቸው ። ምክንያቱም ሐቅ ላይ ስለሆኑና ሐቅ ደግሞ ሁሌም አሸናፊ ስለሆነ ነው ።
ኢኽዋኖች ድካማችሁ ከንቱ ነው በቁጭታችሁ ሙቱ !!! ሰለፍዮች ድሉ የናንተ ነው በርቱ !!! ።

https://telegram.me/bahruteka


" ዓብዱረህማን ዑመር" dan repost
ያ ታላቅ “ ነብይ! ﷺ ”

እስኪ ትንሽ ልበል - ሰለዛ ታላቅ ሠው፣
ትንሽ ቢሆን አቅሜ - ቦታው ባይመጥነው፣
ብቻ ላመላክት - ጥቂት በምችለው!
/
እሳቸውን መግለፅ - አልችልም በእውነት፣
ትክክል የሚያትት - የት ይገኛል ቃላት፣
እርሰዎን የሚገልፅ - የት ተገኝቶ አንደበት፣
ትልቅ ያረጋቸው - አላህ ሲፈጥረዎት፣
ፍፁም የተላኩ - ለአለማት እዝነት!
   
የአላህ መልዕክተኛ ﷺ - ታላቅ ባለ ፀባይ፣
መልእክት የመጣቸው - ከሰማያት በላይ፣
መቋጫ የሆኑ - መደምደሚያው ነብይ!
  
በጨለማ ጉዞ - ይህ ዓለም ሲዋልል፣
የሰው ልጅ ሲሰምጥ - በክህደት ማዕበል፣
ሰይጣን አላማውን - ሲበትን ሲያታልል፣
ይሄን ለመታደግ - ለማምከን ያን ተንኮል፣
ምድርን ለማብራት - ከአላህ ተልከዋል!
     
የፊት ነብያቶች - ጉዟቸው ተረስቶ፣
መመሪያቸው ሁሉ - ተበርዞ ጠፍቶ፣
የሠው ልጅ እምነቱ - ጠፍቶት ተበላሽቶ፣
መጥፎ ልማድ ባህል - እጅግ ተበራክቶ፣

በሕይወቷ እያለች - ሴት ልጅ ስትቀበር፣
ሲተገበርባት - ብዙ ዘግናኝ ተግባር፣
ከብዙ ባሎች ጋር ፣ አንድት ሴት ስታድር፣
በኑሮዋ ሁሉ - በጣም ስትቸገር፣
ድንቁርና ህይወት - በሰፈነበት ወቅት፣
ነብያችን ﷺ መጡ - በዛ ጭንቅ ሰዓት፣
በጥሩ ስነ-ምግባር - ያን ትውልድ አነፁት፣
በተውሒድ ብርሃን - ያን ጨለማ አበሩት፣
ከምድር አጠፉ - ያን ባዓድ አምልኮት፣
መጥፎ አስተሳሰብን - ከስሩ አመክኑት!
           
ወደ ንጹሕ እምነት - ሠዎችን ተጣሩ፣
በቁርኣን መመሪያ - ሁሉን አሰተማሩ፣
በእውነት ለአማኞች - ጀነት አበሰሩ፣
ደግሞ ካሀዳንን - በእሳት አሰፈራሩ!

እሺ ያላቸውን - ጀነት አስከትለው፣
እምቢ ያላቸውን - እሳት እንዳይባላው፣
አስጠንቅቅ አበስር - የሚል ትዛዝ ይዘው፣
ትልቅ ሀላፊነት - አቅፈው ተሸክመው፣
ለሠው ልጅ የሚደርስ - መልእክት አስይዟቸው፣
እኝህ ታላቅ ነብይ ﷺ - ከፍ ያለ ሚና,ቸው፣
አሸናፊው ጌታ - አላህ የላካቸው!

ከሠው ዘር ሁሉ ምርጥ - ልዩ ድንቅ ፍጥረት፣
ደረጃቸው በላጭ - ከሁሉም ነብያት፣
እድሜያቸውን ሁሉ - ባሳለፉት ሕይወት፣
የሰይጣንን መንገድ - የጣዖትን እምነት፣
ድራሹን ያጠፉ - በጣም ያሳደዱት፣

እንኳን ትልቅ ሆነው - መጥቶላቸው መልእክት፣
ጅስማቸው ሳይጠና - ገና ከልጅነት፣
ተዓምር ነበሩ - አስገራሚ ትንግርት፣
እኩይ መጥፎ ድርጊት ጸያፍን ተግባራት፣
ዝክትልትል ቅርፃቅርፅ - አማልክት ጣኦት፣
ይፀየፉ ነበር - ገና በለጋነት!

ታላቅ ሞዴላችን - በሶብር በትእግስት፣
ለዚህ ለኢስላም ሲሉ - ለተፈጥሮው እምነት፣
ያነ ሁሉ ችግር - ፍዳ ሲያሳዎት፣
ከአፀያፊ ትቺት - እስከ ከባድ ጥቃት፣
ያልደረሰ የለም - ያልወረደ መዓት፣
ይቅር በለው ሲያልፉ - ግፉን ሲቋቋሙት፣
ታግሰው ግብ መቱ - በጠንካራ ፅናት!

ለሀቅ ጥላቱ - ብዙ ነው በፊትም፣
የበፊት ነብያት - ተፋልመዋል ሁሉም፣
ይሄን ጥሪ ይዘው - ሲመጡ እሳቸውም፣
የሰይጣን ሰራዊቶች- ሆነባቸው ህመም፣
አመፀኛው ሁሉ - ተነሳ ሊቃወም፣
ስም ማጥፋት ጀመሩ - ማንቋሸሽ ማጣመም!!

ምን የቀረ አለና - ያልተፈጠረ ጉድ፣
ለመግደል ሙከራ - ከሀገር ማሳደደድ፣
ብዙ ጫና ቢደርስ - ብዙ ጉድ ማስገደድ፣
ተራምደው አለፉት - ፍቅርን በማስለመድ!

ነብዩን ﷺ በመስደብ - ከሀቅ ለመከልከል፣
እውነት ለመሸፈን - የሚጣጣር አካል፣
አላማው ግልፅ ነው - በጀመርባው መርዝ አዝሏል፣
የሰይጣን ስራ አስኬያጅ - ክህደት ለማስቀጠል፣
ከአላህ ከመጣው - ከሀቁ ለማግለል፣
ቅጥፈት ቢደማመር - መች እውነት ይሆናል፣
ነቢን ﷺ ታላቁን ሰው - በመጥፎ የሚስል፣
እርሰዎን የሚሰድብ - እውነት ያ ሠው ታሟል፣
ውቂያኖስ በቁንጥር - እንደት ይቆሽሻል፣
የፀሀይ ብርሃን - መች በእጅ ይሸፈናል፣
አንጋጠው ቢተፉ - መልሶ አፍ ላይ ያርፋል!

✍ አብዱረህማን ዑመር
t.me/Abdurhman_oumer/9400


Bahiru Teka dan repost
👉 ለሽርክና ቢዳዓ እውቅና ለተውሒድና ሱና ንፍግና

የመጅሊሱን ስልጣን እንያዝ ብቻ ከዛ በኋላ ሽርክና ቢዳዓን እናጠፋለን ተውሒድና ሱናን የበላይ እናደርጋለን የሚል ዲስኩር እየለፈፉ ወጣቱን ሲያደነቁሩ የነበሩ ኢኽዋኖች የመጅሊስ ወንበር ላይ ሲወጡ ተገለበጡ ። የቀድመዎቹ ኢኽዋኖችና አዲሶቹ ( ነሲሓዎች ) በአሁኑ ጊዜ ትልቁ ስራቸው የተውሒድና ሱናን ዳዕዋ ማጨናገፍ አድርገዋል ።
ለሽርክና ቢዳዓ እውቅና የሚሰጡት የመጅሊስ አመራሮች ለተውሒድና ሱና እንዴት ተደርጎ እያሉ ነው ። ወንድና ሴት ተደባልቆ የሽርክ አይነትና ቢዳዓ እንዲሁም የተለያዩ ወንጀሎች የሚሰሩበትን መውሊድ የፈለገ ያክብር ይላሉ ። ይህ የመጅሊሱ መርህ ነው ብለው እያወጁ ሰዎች ከተለያየ ክ/ሀገር ወደ ሚፈልገው ቀብር አምልኮ እየሄደ ሞቶ አፈር የሆነን የሙታን መንፈስ እያመለከ አፈር በጥብጦ የሚጠጣበትን ፣ በቀብሩ ዙሪያ ጠዋፍ የሚያደርግበትን ፣ ጭንቁን ለበሰበሰው ሰጋና አጥንት የሚነግርበትን ፣ ሴቷ ዘር ፍለጋ ብላ ሄዳ እርሶ ጋር መጥቼ ምን አጣሁ ብላ የምታለቅስበትን ፣ አብዛኛው ሙስሊም ማህበረሰብ ጭንቁን ፣ መከራውን ፣ ማጣቱን ፣ መራብ መጠማቱን ተንበርክኮ እየተንሰቀሰቀ ለሙታኖች የሚነግርበትን የኩፍርና ሽርክ ተግባርን እያበረታቱ ተውሒድና ሱናን መዋጋቱ እንደ ድል እየቆጠሩት ነው ።
በተለያዩ ቦታዎች የሚዘጋጁ የተውሒድና ሱናን ዳዕዋ ለማስቆም አብዛኛዎች የመጅሊስ አመራሮች የሌላ እምነት ተከታይ ፖሊሶችን ይልካሉ ። ከሚላኩት ፖሊሶች እንደሰማነው በጣም ነው የሚሰማን ግን ምን እናድርግ ከናንተው የመጅሊስ አመራሮች ለሀላፊዮቻችን መመሪያ ተሰጥቶ ተልከን ነው ይላሉ ። ተመልከቱ ይህ የመጅሊስ አመራሮች ተግባር በሌላ እምነት ተከታይ የፀጥታ ሰዎች ዘንድ እንኳን ትዝብትን አትርፏል ።
ሄዳችሁ እንዲህ የሚባል ቦታ ላይ መስጂድ ውስጥ ተሰባስበው ቁርኣንና ሐዲስን የሚሰሙትን በትኑ አስተባባሪዮችን እሰሩ እያሉ መመሪያ ይሰጣሉ ። አብዛኞቻቸው መጀመሪያውኑ ጥላቻ ስለሚኖርባቸው አጋጣሚውን ቂማቸውን ለመወጣት ይጠቀሙበታል ። ጤነኛ አመለካከት ያላቸውና አካሄዱ ኢህገመንግስታዊ ነው ብለው የሚያምኑት ደግሞ በነገሩ ይበሽቃሉ ። እኛ ምንም ማድረግ አንችልም ታዘን ነው እባካችሁን ተረዱን ይላሉ ። በጣም ጥቂት የሆኑ የተጣለባቸውን የህዝብ አደራና ህገመንግስቱ ለዜጎች የሰጠው የእምነት ነፃነትን እንደመመሪያ አድርገው የሚያዩ ሀላፊዮች ደግሞ የመጅሊስ አመራሮችን ትእዛዝ ከልኩ ያለፈና ገደቡን የጣሰ በማለት ውድቅ አድርገው ሙስሊሙ ማህበረሰብ እምነቱ የሚያስተምረውን በነፃነት እንዲከታተል ያደርጋሉ ። ለዚህ አይነቱ አስገራሚ አቋም እንደምሳሌ የአሊቾ ወረዳና የሌራ ወረዳ የፀጥታ ሀላፊዮች እንደምሳሌ ይጠቀሳሉ ።
ከላይ ሆነው በድል አድራጊነት የልብሳቸውን ቁልፍ እየከፈቱ የሚንጠራሩት የኢኽዋንና ነሲሓ ጥምር የመጅሊስ አመራሮች ግን ነገ አላህ ፊት ራቁት ቆሞ መመርመር እንዳለ የሰሙ አይመስሉም ። በአላህ ቤቶች ላይ የአላህ ስም ከፍ ተደርጎ እንዳይወሳ ከመከልከል የበለጠ ምን በደል አለ ።
« وَمَنْ أَظْلَمُ مِمَّن مَّنَعَ مَسَاجِدَ اللَّهِ أَن يُذْكَرَ فِيهَا اسْمُهُ وَسَعَىٰ فِي خَرَابِهَا ۚ أُولَٰئِكَ مَا كَانَ لَهُمْ أَن يَدْخُلُوهَا إِلَّا خَائِفِينَ ۚ لَهُمْ فِي الدُّنْيَا خِزْيٌ وَلَهُمْ فِي الْآخِرَةِ عَذَابٌ عَظِيمٌ »
البقرة ( 114)
" የአላህንም መስጊዶች በውስጣቸው ስሙ እንዳይወሳ ከከለከለና እርሷንም በማበላሸት ከሮጠ ሰው ይበልጥ በዳይ ማነው? እነዚያ ፈሪዎች ኾነው እንጂ ለእነርሱ በቅርቢቱ ዓለም ውርደት አላቸው ፡፡ ለነርሱም በመጨረሻይቱ አገር ታላቅ ቅጣት አላቸው " ፡፡

እነዚህ ተውሒድና ሱናን የሚዋጉት የመጅሊስ አመራሮች በየክ/ሀገሩ ያሉ ሰዎችን አላህን ከማምለክ አውጥተው ራሳቸውን ወደ ማምለክ የሚጠሩትን ህገመንግስቱ የሰውን ገንዘብ ያለአግባብ መብላትና በሰዎች ላይ ፍርሃትና ሽብር መንዛት ስለሆነ ወንጀል ነው ብሎ የወንጀለኛ መቅጫ ህግ ያስቀመጠለትን የጠንቋዮች ተግባርን ጭምር እውቅና የሚሰጡና ማንም ተሰብስቦ የፈለገውን ቢያደርግ የማይከለክሉ ናቸው ። ‼
በጣም የሚያሳፍረውና መልስ ያልተገኘለት ሀገሪቷ የምትመራው በመጅሊሶች መተደዳደሪያ ደንብ ነው ወይስ በህገ መንግስቱ የሚለው ነው ። በኢሀዲግ ዘመን የመጅሊስ አመራሮች እኛ ኢሀዲግ ነው ያስቀመጠን እሱ ያዘዘንን ነው የምናስፈፅመው ይሉ ነበር ። አሁን ደግሞ አብዛኛዎች በትላልቅ የስልጣን ደረጃ ላይ ያሉ የመንግስት አመራሮች ህገመንግስቱ ለዜጎች ያረጋገጠውን የዜግነት መብት ሲጠየቁ መጅሊሱ እንዳትፈቅዱ ብሎናል አንሰማም ይላሉ ። !!! አንሰማም ማለት ብቻ አይደለም ፍትህ በጎደለው የመጅሊስ አመራሮች በሚያስተላልፉላቸው ትእዛዝ ዜጎችን ያንገላታሉ ያስፈራራሉ ያስራሉ ። የዚህ አይነቱ እየተስፋፋ የመጣው የመብት ጥሰት ሀገሪቷ ወጥ የሆነ መንግስታዊ መመሪያ የሌላት እያስመሰላትና ሁሉም ለየክልሉ ለየዞኑና ወረዳው ያሻውን መመሪያ በማውጣት የበላይ የሌለበት መንግስት የሆነ እያስመሰለው ነው ።
አሁንም ለማስታወስ የምፈልገው የዶ/ር አብይ አስገራሚና ነገር ግን እየተናፈቀ የቀረ ንግግርን ነው ። ዶ/ር አብይ ከወልቂጤ ማህበረሰብ ጋር ውይይት ባደረጉበት ጊዜ አንድ አባት የኔ ስጋት እርሶ እላይ ኖት ታች የሚሰራውን እንዴት ያውቃሉ የሚለው ነው ሲሏቸው
" የመጣሁት ከታች ስለሆነ የማላውቀው ነገር አይኖርም ስጋት አይግባዎት " የሚል ነበር ። ታዲያ ዛሬ ዶ/ር አብይ እየመሩት ያለው የብልፅግና አመራር ከላይ እስከታች ምን እየሰራ እንዳለ ያውቁ ይሆን የሚለው የብዙዎች ጥያቄ ነው ።
ከመጅሊስ አመራሮች ጋር መሰረታዊ ልዩነት አለን እያልን ሰሚ ልናጣ አይገባም ። የመጅሊስ አመራሮች የሙስሊሞች የሆነውን ተቋም በቁርኣንና ሐዲስ በሰለፎች ግንዛቤ ከመሩት አንድ እንሆናለን ካልሆ ግን ልዩነታችን አንተም ተው አንተም ተው የሚባልበት አይደለም መሰረታዊ ነው ። የኛ ጥያቄ መጅሊሱን እኛ እንምራው አይደለም ። እናንተም በመንገዳችሁ እኛም በመንገዳችን በመብታችን አትግቡ ነው ። እንደሀገር በህገ መንግስቱ እንደሙስሊም በቁርኣንና ሐዲስ በቀደምት ደጋጎች ግንዛቤ ነው የምንመራው ። ይህን መብታችንን የሚረግጥ የትኛውንም አካል አንቀበልም ።
ስለዚህ ዜጎችን በእኩልነት ልታገለግሉ በየደረጃው የተቀመጣችሁ የመንግስት ተቋም ሀላፊዮች የተጣለባችሁን አደራ ተወጡ ስልጣንን ለግልና ለቡድን አመለካከት ማስፈፀሚያ አታድርጉ እንላለን ።

https://telegram.me/bahruteka


Bahiru Teka dan repost
👉 የሓራ ሰለፍዮች በሶብር ታገዙ

የአሕባሽና ኢኽዋኑ ጥምር የመጅሊስ አመራር የተዋጣለት ድራማ ሰርቶ የሐራ ሶፋ መስጂድ ኢማም ሸይኽ ሙሐመድ ሓያትን ጨምሮ ኮሚቴዎችን እንዳሳሰረና ደረሶችን እንዳስጫነ ሰምተናል ። የዚህ ድራማ አካሄድ የወረዳው መጅሊስ ሰብሳቢ ለሶፋ መስጂድ ኻዲሞች ሮብ ተገኝታችሁ መስጂዱንና የመስጂዱን ንብረት እንድታስረክቡ የሚል ደብዳቤ በመሀተምና ፊርማ አስደግፎ ፅፎ ለቀበሌው መጅሊስ ሰብሳቢ ልኮ ደብዳቤው የደረሰው ሰብሳቢ ይመለከታቸዋል ለሚላቸው በማህበራዊ ገፃቸው እንደላከና ከሳአታት በኋላ ተመቷል የሚል ወሬ የተሰማ መሆኑ ነው ።
በዚህን ጊዜ የመንግስ የፀታ ሀይል ገብቶ ሸይኽ ሙሐመድንና ኻዲሞችን በቁጥጥር ስር አውሎ ደረሶችን እንዳስወጣ ነው የሰማነው ።
በመሆኑም የሐራ ሰለፍዮች ከስሜታዊነት በመውጣት በሶብር መታገዝ ግድ ይላችኋል ። ከዚህ በኋላም የሚወሰዱ እርምጃዎች ሊኖሩ ይችላሉ ። ምክንያቱም የኢኽዋኖችን አካሄድ እናውቀዋለን ። ስሙን ለሰው አወረሰው እንደሚሉት የእነርሱን ማንነት በሰለፍዮች ላይ በመለጠፍ ለመንግስት ሰለፍዮች የሀገር ስጋት እንደሆኑ አድርገው ስለሚያቀርቡና የመንግስት አካላት ከሰላምና ፀጥታ አንፃር ስለሚያዩት በተለይ ደግሞ አሁን ያለው የሰሜኑ ክፍል ሁኔታ ለሌሎች የስጋት ሀይሎች በር እንዳይከፍት ለጊዜው ስጋቱን ለመቅረፍ መፍትሄ የሚሉትን እርምጃ ሊወስዱ ይችላሉ ። ከዚህ ውስጥ አሁን የወሰዱት እርምጃ አይነት ። በዚህን ጊዜ ኢኽዋኖች ባዘጋጁት ወጥመድ ዘሎ መግባት ሳይሆን ነገሮችን በሰከነ ሁኔታ ማየትና ማሳለፍ ያስፈልጋል ።
እውነትና ንጋት እያደር ግልፅ ይሆናልና አብሽሩ ተረጋጉ በማንኛውም እንቅስቃሴ የእውቀት ባልተቤት የሆኑ ዑለሞችን አማክሩ ። የኢኽዋንን ተልእኮ ለማስፈፀም በመካከላችሁ ሰርጎ ገብቶ ለሰለፍያና ሰለፍዮች ያሰበ መስሎ ወደ ሌላ አቅጣጫ እንድትሄዱ የሚያደርግን ነቅታችሁ ጠብቁ ።
አላህ ሐቅንና የሐቅ ባልተቤቶችን ይረዳል ።

https://telegram.me/bahruteka

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.