🟢
የእሳት ሰንሰለት♨️በሰሞነኛው የሁለቱ የኢኽዋን ክንፎች ጥምር ትእይንት አዲሶቹ ሙመይዓዎች ከመጠቆር አልተረፋም:: መርከዝ ኢብኑ መስዑዶች ላይ ረድ ሲሰጥና አቋም ሲያዝባቸው ጊዜ ሽንጣቸውን ገትረው ጥብቅና ቆመዋል። ይህን ሀቅ የሚክድ ከራሱ ጋር ይጣላል።
"ለመስለሃ ነው ፣ ድንበር ታለፈባቸው ፣ የረድ ጉረኞች ፣ የተብዲዕ ጥማት ያለባቸው ፣ ወዘተ" እያሉ ሰለፊዮችን ሲጋፈጡና ሲያንቋሽሹ ከርመዋል:: እነዚህ በሳል መሳይ መሃል ሰፋሪዎች ከእሳቱ ሰንሰለት እስከ ዛሬም በግልፅ ተውበት አላደረጉም::
ከቢድዓ አራማጆች ጋር የሚተሳሰርና የሚተባበር በአደገኛ የእሳት ሰንሰለት እንደተጠለፈ ቁርጡን ይወቅ። የሀገራችንም የሙብተዲዖች ሰንሰለት አለማቀፍ ከሁኑት ዋና ዋና አጥማሚዎች ጋር በቀጥታም ይሁን በእጅ አዙር የተሳሰረ መሆኑን ልብ ይሏል።
ለምሳሌ:
1️⃣ መውሊድን በጀት መድቦ በድምቀት የሚያከብር
መጅሊስ ተባብረውና ደግፈው የቆሙ ሁሉ ለብዙ ቢድዓዎች ግልፅ እገዛ አድርገዋል። እንዲያውም አባል ናቸው።
2️⃣ ኢኽዋናዊ አደረጃጀት ከላይ እስከታች የተሳሰረ ነው:: ከሀገራችን
የኢኽዋን መንሀጅ አራማጆች ጋር የተለጠፉ አካላት አለም አቀፍ ከሆኑት የአንጃው መሪዎች ፣ ሚዲያዎችና ድርጅቶች ጋር በትብብር እየሰሩ እንደሆነ ይወቁት። “ኢኽዋን አይደለንም “ ቢሉም ተግባራቸው ግልፅ ምስክር ነው። ተዋህደዋል።
3️⃣ከመቃወምና ጥፋታቸውን ከማስጠንቀቅ ይልቅ ለጥመትና ለጥፋት አራማጆች
ጥብቅና የቆሙ ፍትሃዊ መሳይ የሀሰት ደጋፊዎች ከእነርሱ አይደለንም ቢሉም ተሳስረዋል። አንዱ ያጠፋል ሌላ እንዳይነከ ይከላከልለታል።
وفي الديث الذي رواه مسلم في صحيحه (1978) من حديث علي بن أبي طالب رضي الله عنه عن النبي صلى الله عليه وسلم ، قال :
… وَلَعَنَ اللهُ مَنْ آوَى مُحْدِثًا…
ነቢዩ (ﷺ)አሉ:
የአላህ እርግማን ወንጀለኛን ወይም ሙብተዲዕን በሸሸገና ባገዘ ላይ ሁሉ።
قال الشيخ العثيمين "ظاهر الحديث : ولو كان أمراً يسيراً…" شرح كتاب التوحيد
አሸይኽ አልኡሰይሚን አሉ:
ሀዲሱ በግልፅ የሚጠቁመው በትንሽም ጉዳይ ብትሆን ከደገፈው የተረገመ ነው።
👉ለቢድዓም ሆነ ለሌላ የወንጀል እንቅስቃሴ የገንዘብ ፣ የጉልበትና የሞራል ድጋፍ የምታደርጉ ሁሉ ከዚህ የእሳት ሰንሰለት ፈጥናችሁ ውጡ።
በግፍ የተሞላ ጥቁር ታሪክ እያስመዘገቡላችሁ ነው::
✍በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ አጋዦች ፣ አድናቂዎች እና አጋሮች ሆነው ሲያበቁ መሰል የሁለቱን የኢኽዋን ክንፎች ጥፋቶችና ጉዶችን "እኛ አልሰራነውም" የሚሉ አይጠፋም:: በጋራ የገነባችሁት መንሃጅ መሆኑን አትርሱ::
የሞተው ወንድምሽ
የገደለው ባልሽ
ሀዘንሽ ቅጥ አጣ
ከቤትሽም አልወጣ
✍ ሸምሱ ጉልታ (አቡ ሀመዊያ)
http://t.me/Abuhemewiya