ክርስቶስ ምን አለ ?


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


በዚህ Channel የሚለቀቁ
>Tanx for joining
>for any Comment @Ashezuker

Related channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter




Forward from: @ᴇʟɪᴀꜱ ʙᴇᴅᴀᴅᴀ
መልካም ወጣት 2013 የመሻገር ብስራት ዮናታን አክሊሉ በ Eliasbedada2 .መልካም ወጣት ምን አይደለም ?የማይቅም የማያጨስ ማለት አይደለም 1.ያለፈ ጉዳቱ እስረኛ አይደለም የትላንትና ጉዳት እስረኛ መሆን ማለት የነገን እርምጃ እነዳናረግ ያ ደርጋለል፡፡ሰዎች ያለፍ ጉዳታቸውን መተው ማይፈልጉትእየታዘነላቸው ለመኖርየገቢ ምንጫቸው ስለሆነ ነውያለፈ ጉዳት እስረኛ መሆን ማለት ጭቃ ውሰጥ እንዳለ እሾክ ማለት ነው የከፉብህ ሰዎች ሁሉ ጠላትክ አይደሉም አሁን ለደረስክበት ቦታ መሸጋገሪያ ድልድይ ናቸው እንጂበአለም ላይ በጣም አሳዛኝ ሰው ቢኖር ዳኛው ከበደሉ ነጻ እንዲሆን ፈቅዶለት ነጻ መሆን ያልቻለ ሰው ነው፡፡ ከገባበት እስር ቤት የማይወጣው እራሱን በራሱ ስላሰረ ነውይሄ እስረኛ እራሱን በራሱ ያሰረ እስረኛ ነው እራሱን በራሱ አስሮ ቁልፉን የዋጠ ወይም የደበቀ ነው፡፡በየትኛውም ሂሳብ ትላንት ከንገ አይበልጥም የትላንት ጭለማ የነገ ብርሃንን እንዲ,ያጠፋ አትፍቀድለት ያለፈ ጉዳትህን እሹሩሩ አትበለው፡፡በጥላቻ ውስጥ አትመላለስ ከትላንት ጉዳትህ ቀለም ተውሰህ ነገህን አትጻፈው 2.ያጉል ፍቅር እስረኛ አይደለም ያጉል ፍቅር እስረኛ ሰዎች መገለጫቸው በችግራቸው ይደሰታሉበደስታቸው ይሰቃያሉ የተገላቢጦሽ ኑሮ ይኖራሉየውርደታቸው ሰራተኛ ያስደስታቸዋልየሚኖሩት ለስሜታቸው ነውጊዜውን፤ገንዘቡን፤ጉልበቱን፤ክብሩን የሚተዉለት ጉዳይ አለው በምላሹ ግን የሚቀበለው ሀፍረት እና ውርደት ነው፡፡አጉል ፈቅር ሁል ጊዜ አይኑ ወደራሱ ነውስህተት እና ልክን አያቅም ያጉል ፍቅር እስረኛ መገለጫዎችከአቅም በታች ያደርጋል፤ውጪ ያሳቀህ ነገር ቤትህ ካስለቀሰህ ያጉል ፍቅር እስረኛ ነህ ፡ውጪ ያስደነሰህ ነገር ክላስህ ውስጥ ካሳቀቀህ ያጉል ፍቀር እስረኛ ነህ፡፡ውጪ ያስጨበጨበልክ ነገር እቤህ ካስለቀሰህ ያጉል ፍቅር እስረኛ ነህ፡፡3.የገንዘብ እስረኛ አይደለምመገለጫችውወንጀል አይፈሩምሃጢያት ፡አምላክን አይፈሩምገንዘቡን ለማምጣት በሚሄዱበት መንገድ ይበላሻሉ በገንዘቡ ይበላሻሉየትክክለኝነት መለኪያቸው ተሰርቆ በገንዘብ ነው ለነገሮች ያላቸውን አመለካከት ሚለኩትጥቅም አልባ ስራቸውቢጠቅምም ባይጠቅምም ይስርቃሉከሰው ላያ በቻ ሳይሆን ከራሳቸውም ላይ ይሰርቃሉእራሳቸውን በሱስ ይደብቃሉገንዘብን የስህተታቸው መሸፈኛ አርገው ይጠቀማሉእራሳቸውን አዋቂ አርገው ይቆጥራሉወዳጅ የላቸውም አምላካቸውን አያቁምየገንዘብ እስረኛ የሆኑ ሰዎች እንደጆተኒ ገንዘብ ካልተሰጣቸው አይሰሩም
.......4-6
@Eliasbedada


Forward from: የክርስቶስ ልብ-Mind Of Christ
1.ፍርሀት ማለት ? ሰይጣን በሰው መንፈስ ላይ የሚጭነው ሸክም ማለት ነው ።

2.የፈቃድህን ስሜት በሰይጣን ቁጥጥር ውስጥ ሲሆን የሚፈራህን መፍራት ትጀምራለህ።

3.ግጭትን የምናሸንፈው በስልጣን ሳይሆን በእውነት መንገድ ነው።

4.የገጠመንን ችግር ለመሰበር ሳይሆን ለመሰራት እንጠቀምበት

5.የእ/ር ን መንገድ የማይወድ ሰው በመንገዱ ላይ ያለውን በረከት አያገኝም።

6.መጀመሪያ ቁሳዊ ነገር ፈልገህ በኃላ እ/ር ን መፈለግ ማለት ? ጫማውን አስቀድመህ ካልሱን ከላይ ደርበህ ማረግ ማለት ነው።

7.እየሱስ የሰላም አለቃ እንጅ የገንዘብ አለቃ አልነበረም

8.ባቋራጭ ሂደህ ከምታገኘው ልምላሜ ይልቅ በምድረበዳ ሂደህ የምታገኘው የእ/ር እውነት ይበልጣል።

9.ሰይጣን እውነተኛውን ነገር ሳይሆን የሚሰጠን የሚመስል ነገር ነው።



https://t.me/joinchat/kE_nkI4OPBMyOGQ0


ሮሜ 5
⁶ ገና ደካሞች ሳለን ክርስቶስ ዘመኑ ሲደርስ ስለ ኃጢአተኞች ሞቶአልና።
⁷ ስለ ጻድቅ የሚሞት በጭንቅ ይገኛልና፤ ስለ ቸር ሰው ግን ሊሞት እንኳ የሚደፍር ምናልባት ይገኝ ይሆናል።
⁸ ነገር ግን ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ስለ እኛ ሞቶአልና እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን የራሱን ፍቅር ያስረዳል።
⁹ ይልቁንስ እንግዲህ አሁን በደሙ ከጸደቅን በእርሱ ከቍጣው እንድናለን።
¹⁰ ጠላቶች ሳለን ከእግዚአብሔር ጋር በልጁ ሞት ከታረቅን፥ ይልቁንም ከታረቅን በኋላ በሕይወቱ እንድናለን፤
¹¹ ይህም ብቻ አይደለም፥ ነገር ግን አሁን መታረቁን ባገኘንበት በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በእግዚአብሔር ደግሞ እንመካለን።

@Mkc1933
@Mkc1933


እርሱ ከሰማይ እዚህ ድረስ የመጣው
እኛ ከዚህ ሰማይ ድርስ እንድንሄድ ነው !
መሄድ ብቻ አይደለም ክርስቶስ ከሰማይ ወደ ምድር የመጣው ስለ እኛ ለመረገም ነው!
“በእንጨት የሚሰቀል ሁሉ የተረገመ ነው ተብሎ ተጽፎአልና ክርስቶስ ስለ እኛ እርግማን ሆኖ ከሕግ እርግማን ዋጀን፤” (ገላትያ 3፥13)
እኛም ሰማይ የሄድነው ለመባረክ ነው
“በክርስቶስ በሰማያዊ ስፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ።” (ኤፌሶን 1፥3)


ከእኔ አብ ይበልጣል

ብዙ አርዮሳውያን ሆነ ሙስሊም ወገኖቻችን ይህንን ጥቅስ መሠረት አድርገው ኢየሱስ ፍጡር ነው ከአብ ያንሳል ይሉናል። እስኪ እንቃኘው!

“የምትወዱኝስ ብትሆኑ ከእኔ አብ #ይበልጣልና ወደ አብ በመሄዴ ደስ ባላችሁ ነበር።”
— ዮሐንስ 14፥28

ክርስትና አንድ አምላክ ብቻ መኖሩን ቢያስተምርም ይህ አንዱ አምለክ ሦስት አካላት እንዳሉት ስለሚያስተምር በነዚህ አካላት መካከል የሥራ ድርሻ (function) ወይም የደረጃ (rank) ብልጫ ሊኖር ይችላል፡፡ ይህ በእግዚአብሔር በራሱ ሕላዌ ውስጥ የሚገኝ እንጂ ከእርሱ ውጪ የሚገኝ ባለመሆኑ በሥላሴነት ከሚኖረው ከአንዱ አምላክ ውጪ የሚገኝ አካል ብልጫ እንዳለው እስካልተነገረ ድረስ ምንም የሚፈጥረው ችግር የለም፡፡ በነዚህ ቦታዎች የተጠቀሰው μείζων(ሜይዞን) የሚለው የግሪክ ቃል ደረጃን እንጂ የግድ የባሕርይ ብልጫን የሚያመለክት አይደለም፡፡

ማሳያ አንድ፦ “እውነት እላችኋለሁ፤ ከሴት ከተወለዱት መካከል እንደ መጥምቁ ዮሐንስ ያለ አልተነሣም፤ ሆኖም በመንግሥተ ሰማያት ከሁሉ የሚያንሰው #ይበልጠዋልμείζων[ሜይዞን]።
— ማቴዎስ 11፥11
ይህ ማለት በመንግሥተ ሰማይ ያለው አካል በባሕርይ ይበልጠዋል ማለትም በመንግሥተ ሰማይ ያለው ፈጣሪ ዮሐንስ ፍጡር ነው ማለት ማለት አይደለም። ሁለቱም ፍጡሮች ናቸውና ነገር ግን በሥራ ድርሻ የደረጃ ብልጫን ነው የሚያሳየው።

ማሳያ ሁለት፦“እውነት እላችኋለሁ፤ በእኔ የሚያምን እኔ የማደርገውን ሥራ ይሠራል፤ እንዲያውም እኔ ወደ አብ ስለምሄድ፣ ከእነዚህም #የሚበልጥ ሜይዞን[μείζων] ያደርጋል።”
— ዮሐንስ 14፥12
ይህም ማለት እኛ በባሕሪያችን ከክርስቶስ እንበልጣለን ማለት አይደለም።

በአጭሩ አንድ አካል ከሌላው በሥራ ድርሻ፣ በሥልጣን ወይም በደረጃ ይበልጣል ማለት የባሕርይ ብልጫ አለው ማለት እንዳልሆነ ልብ ሊባል ይገባል፡፡ ለምሳሌ ያህል የአንድ አገር መሪ በሥራ ድርሻ፣ በሥልጣንም ሆነ በደረጃ በስሩ ከሚተዳደሩት ዜጎች ይበልጣል፡፡ ይህ ማለት ግን እንደ ሰው ያለው ዋጋ (Value) ከማንም ይበልጣል ማለት አይደለም፡፡ ባል የቤተሰብ ራስ እንደመሆኑ መጠን ከላይ በተጠቀሱት መንገዶች ከሚስቱ ሊበልጥ ይችላል ነገር ግን ወንድ እንደ ሰውነቱ ከሴት ይበልጣል ወይም ሴት ከወንድ ታንሳለች ማለት ግን አይደለም፡፡ የግሪክ አዲስ ኪዳን የባሕርይ ብልጫን ለማመልከት “ዲያፎሮስ”[διάφορος] የሚል ሌላ ቃል የሚጠቀም ሲሆን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በባሕርዩ ከመላእክት የላቀ መሆኑን ለማመልከት ዕብራውያን 1፡4 ላይ ጥቅም ላይ ውሏል፡፡

ከመላእክት ይልቅ እጅግ የሚበልጥ ስምን በወረሰ መጠን እንዲሁ ከእነርሱ አብዝቶ #ይበልጣል[διαφορώτερον]።
— ዕብራውያን 1፥4

በሥላሴ አካላት መካከል የሚገኘውን ግንኙነት ለማመልከት ግን ይህ ቃል ጥቅም ላይ ውሎ አናገኝም፡፡ ስለዚህ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አብ ከወልድ መብለጡ መነገሩ የመለኮታዊ ባሕርይ ብልጫን ሳይሆን የሥራ ክፍፍልን እና ወልድ ሥጋን በመልበስ መለኮታዊ ክብሩን ትቶ ወደ ምድር እንደመምጣቱ መጠን (ፈልጵስዩስ 2፡5-11) የደረጃ ብልጫን ብቻ የሚያመለክት በመሆኑ የኢየሱስን አምላካዊ ባሕርይ ከአብ የሚያሳንስ አይደለም፡፡
@mkc1933
@mkc1933


💡 የራሳችሁ አይደላችሁም 💡

" ወይስ ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን? በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ።
(1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6:19-20)

እኛ ክርስቲያኖች ዳግም ስንወለድ ከከንቱ የአባቶቻችን ኑሮ ክቡር እና ቅዱስ በሆነው #በክርስቶስ #ደም ተገዝተን ነው ስለዚህ እግዚአብሔር በጣም ትልቅ እና በአይምሮ በማይገመት ዋጋ አውጥቶ የራሱ አድርጎናል የራሱ ስለሆንንም የራሱ የመንፈስ ቅዱስ ማደሪያ አድርጎናል ስለዚህ እንደ ሌሎች በራሳችን ላይ የፈለግነውን የማድረግ #ስልጣን #የለንም ምክንያቱም #የራሳችን #አይደለንም የራሳችን ለመሆን ብንፈልግ እንኳ የተከፈለብንን ዋጋ መክፈል አለብን የክርስቶስን የደም ዋጋ የሚያክል ደግሞ አናገኝም
(❗️የኢየሱስ ደም የኢየሱስ ሕይወት ነው መጽሐፍ ሲናገር የሥጋ ሕይወቱ በደሙ ውስጥ ነው ይላል❗️)
ስለዚህ በራሳችን ላይ የምናደርጋቸው ውሳኔውች በሙሉ በእኛ የሚያድረውን እግዚአብሔርን ማክበር አለበት፡፡

እንደ ፈጥረታዊ ሰው በራስ አይምሮ ብቻ ከሚመራ ሕይወት መውጣት አለብን ይልቁን "በእግዚአብሔር መንፈስ የሚመሩ እነዚህ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉ" ቃሉ እንደሚል ለውሳኔዎቻችን በውስጣችን ያለውን የመንፈስ ቅዱስን ፍቃድ ማወቅ አለብን የድርጊቶቻችን ግብ እግዚአብሔርን ያከብራል ወይስ አያከብርም ነው መሆን ያለበት ምክንያት? አሁንም ደግሜ እላለው የራሳችን አይደለንም ስለዚህ? በሥጋችን እግዚአብሔርን እናክብር።

ስለዚህ እንደ እግዚአብሔር ፍቃድ ለመኖር የገዛንን የራሱ ያደረገንን እንዲሁ መቅደሱ አድርጎ በእኛ ያደረውን የሕያው እግዚአብሔር የመንፈስ ቅዱስን ፍቃድ እየተከተልን መኖር ነው እርሱ እንዲመራን ከፈቀድንለት እግዚአብሔር አብዝቶ ክብሩን እና ሕልውናውን የሚገልጥበት ቤተመቅደስ እንሆናለን።

#ጸሎት
እግዚአብሔር አባት ሆይ አመሰግንሃለሁ አንተ በልጅህ በኢየሱስ ደም ገዝተህ የራስህ አድርገኸኛል
የቅዱስ የመንፈስህም ማደሪያ ቤተመቅደስ አድርገኸኛል እኔ የራሴ አይደለሁም፡፡
ያንተ ሆኜ ሳለሁ በራሴ ሥጋ ፍቃድ አንተን በማያከብር ስለተጉዋዝኳቸው ጉዞዎቼ ይቅር በለኝ በደሌ በኢየሱስ ደም እጠበው ከእንግዲህ በመንፈስህ በመመራት ላንተ ክብር መኖር እፈልጋለው በውስጤ ያለው ቅዱሱ መንፈስህ ይምራኝ ልጅህን ኢየሱስንም በሕይወቴ ያክብረው አባት ሆይ ስለሰማኸኝ በውድ በልጅህ በኢየሱስ ስም አመሰግንናሃለው አሜን።

ተባረኩ!
@mkc1933
@mkc1933
@mkc1933
@mkc1933


. #አምሮን_ማንቃት
👇

የኢየሱስን ምሳሌ መማር
Jesus Model

- #ኢየሱስ የእግዚአብሔር ጥበብ ነበር 1ኛ ቆሮ 1፡24 
- #ኢየሱስ የእግዚአብሔርን ቃል ያውቃል  ሉቃ24፡27  
- #ኢየሱስ የተናገረውን ኖረ የሐን14፡28-31
- #ኢየሱስ የሁሉም አገልጋይ ነበር ፊልጵስዩስ 2: 5-8
- #ኢየሱስ ሕይወቱን ለሌሎች ለመሠዋት ፈቃደኛ ነበር የሐን 3፡16
- #ኢየሱስ እውነት ነበር እናም ለመናገር አልፈራም የሐን14፡6
-  #ኢየሱስ ለሰው ልጆች የማያቋርጥ ፍቅር ነበረው   የሐን17፡22-23  

@ashezuker

Channel @mkc1933


ሕይወት መንፈሳዊ ነዉ።/Life is spiritual./

....አስተውሉ ፊተኛው አዳምና ረዳቱ የነበረችው ሔዋን በእግዚአብሔር ኤደን በገን የነበሩበት ጊዜ በሕይወት የነበሩበት ጊዜ ነበር: ከጨርቅ ወይም ከቆዳ የተሰራ ልብስ አይለብሱም ነበር ነገር ግን እራቁትነት አይሰማቸውም ነበር፤ በዚያ ስራ ነበር ድካም ግን አልነበረም፤ ይመሽና ይነጋም ነበር ፍርሃት እና ሃዘን ግን አልነበረም! ምክንያቱም የሕይወት ምንጭ ከሆነው መንፈስ ጋር ተስማምተው የነበሩበት ጊዜ ስለነበር ነዉ። የእግዚአብሔርን ትዕዛዝ በተላለፉ ጊዜ ግን ወድያው እራቁቱነት፤ ፍርሃት፤ የበደለኝነት ስሜት በኃላም ድካም፤ ላብ፤ ስቃይ፤ ሕመም መጡባቸው! ምክንያቱም የሕይወት ምንጭ ከሆነው መንፈስ ባለመታዘዝ ስለተለያዩ እና ስለሞቱ ነው።

የሕይወት ምንጭ እግዚአብሔር ነዉ። እግዚአብሔር ደግሞ መንፈስ ነዉ። ከእግዚአብሔር የተለየ ሕይወትን እየኖረ አይደለም! በድካም በላብ እና በስቃይ ነው የሚኖረው: የሕይወት ምንጭ ከሆነው መንፈስ የተስማማ ግን በሕይወት ይኖራል። አያችሁ ሕይወት መንፈሳዊ ነዉ:እውነተኛ እረፍት፤ ሐሴት ፤ጤንነት ፤ ነጻነት፤ ስኬት ሁሉ መንፈሳዊ ነዉ። መንፈስ ቅዱስ ያልረዳው ስጋ ለባሽ ሕይወትን መኖር አይችልም: ምክንያቱም ሕይወት መንፈሳዊ ነዉ።

ሰው ሕይወትን መኖር የሚጀምረው ከእግዚአብሔር ጋር ሲሆን ነዉ።
ህይወት ትርጉም የምያገኘው በኢየሱስ ብቻ ነው፡፡

@mkc1933


#ኢየሱስ_ክርስቶስን የምትወደው ከሆነ ፤ #ኢየሱስ_ለአንተ መኪና ፣ ቤት ፣ አውሮፕላን ፣ መርከብ ወይም ባቡር አይደለም የሚገዛልህ ፤ #ኢየሱስ_ክርስቶስን ስቶደው ፥ #በእግዚአብሔር_አብ ትወደዳለህ ፥ #ኢየሱስ_ክርስቶስ እርሱ እራሱ ይወድሃል ፥ እራሱንም ይገልጥልሃል።

“የሚወደኝንም አባቴ ይወደዋል እኔም እወደዋለሁ ራሴንም እገልጥለታለሁ።”
— ዮሐንስ 14፥21

@mkc1933


📖 እግዚአብ#ሔር እንዲህ ይላል 📖


ማንም። #እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ #ወንድሙን_ቢጠላ ሐሰተኛ ነው፤ ያየውን ወንድሙን የማይወድ ያላየውን #እግዚአብሔርን_ሊወደው እንዴት ይችላል? እግዚአብሔርንም የሚወድ ወንድሙን ደግሞ እንዲወድ #ይህች_ትእዛዝ ከእርሱ አለችን።

#1ኛ የዮሐንስ መልእክት 4:20-21




Forward from: እውነታ TUBE
የዋይት ሀውስ ብሄራዊ የፀጥታ ምክር ቤት ያወጣውን መግለጫ ኢትዮጵያውያን እየተቃወሙ ነው

የዋይት ሀውስ ብሄራዊ የፀጥታ ምክር ቤት የህዳሴ ግድብን አስመልክቶ ያወጣውን መግለጫ ኢትዮጵያውያን እየተቃወሙ ነው፡፡

በመላው ዓለም የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የዋይት ሀውስ ብሄራዊ የፀጥታ ምክር ቤት የህዳሴ ግድብን አስመልክቶ ያወጣውን መግለጫ በመቃወም ላይ ይገኛሉ።

የዋይት ሀውስ ብሄራዊ የፀጥታ ምክር ቤት በትናንትናው እለት በትዊተር ገጹ፥ “257 ሚሊየን የምስራቅ አፍሪካ ህዝቦች የኢትዮጵያ ጠንካራ አመራርን ለማየት ይሻሉ፤ ይህም ማለት ፍትሃዊ ስምምነትን የሚጠይቅ ነው፤ በህዳሴ ግድብ ዙሪያ ያሉ የቴክኒክ ጉዳዮች መፍትሄ አግኝተዋል፤ አሁን ደግሞ የህዳሴ ግድብ ውሃ ሙሌት ከመጀመሩ በፊት ስምምነት ላይ የሚደረስበት ጊዜ ሊሆን ይገባል” ፅሁፍ አውጥቷል።

መልእክቱም ኢትዮጵያ በህዳሴ ግድብ ዙርያ ስምምነት ላይ ሳይደርስ ሙሌት እንዳትጀምር የሚል እንድምታ ያለው ሆኖም ተገኝቷል።

ታዲያ ምክር ቤቱ በትናንትናው እለት የህዳሴ ግድብን አስመልክቶ ያወጣውን መግለጫ በዓለም ዙሪያ የሚኖሩ በርካታ ኢትዮጵያውያንን ያስቆጣ ሲሆን፥ ኢትዮጵያውያኑ ተቃውሞዋቸውንም በተለያዩ ማህበራዊ ትስስር ገፆች በመግለፅ ላይ ይገኛሉ።

ኢትዮጵያውያኑ የዋይት ሀውስ ብሄራዊ የፀጥታ ምክር ቤት ያወጣው መግለጫ የሀገርን ሉዓላዊነት የሚጥስ መሆኑን በመግለፅ፤ “ምን ማድረግ እንዳለብን ማንም አይነግረንም፤ በድንበራችን ውስጥ ያለን ግድብ ውሃ ለመሙላት ማንንም አንጠይቅም” ብለዋል በሰጡት አስተያየት ።

100 በመቶ በኢትዮጵያውያን ወጪ የሚገነባን ግድብ ውሃ ሙሉ አትሙሉ ማለት የሚችል አካል የለም ያሉት ኢትዮጵያውያኑ፤ የግድቡ የመጀመሪያ ውሃ የመያዝ ሂደት ስምምነት ላይ ቢደረስም ባይደረሰም ግድባችን ይሞላል የሚል አስተያየት አስፍረዋል፤ በራሳችን ግድብ ለማንም ፈቃጅና ከልካይ ፍላጐት የምንተወው አይደለም በማለት።
ኢትዮጵያ ውሃውን በፍትሃዊነት ለመጠቀም ሲባል ከግብፅ ጋር ስምምነት ላይ ለመድረስ በጣም ረጅም ርቀት መጓዛንም አንስተዋል።

ኢትዮጵያ በፍትሃዊ ተጠቃሚነት ዙሪያ ይህን ያክል ርቀት የተጓዘችው በጋራ ጥቅም ስለምታምን መሆኑንም በመግለጽ፤ “ግብፅ በኢትዮጵያ በኩል የቀረበላትን ሁሉንም ወገን ተጠቃሚ የሚያደርግ መፍትሄን እድንትቀበል ምከሯት” ያሉም አሉ።

ግብፅ በእረግጥ የቸገራት ውሃ ሳይሆን የኢትዮጵያን ዘላቂ ጥቅም መጉዳት መሆኑን የጠቀሱ አስተያየት ሰጪዎች ደግሞ በግብፅ ያለውን እምቅ የከርሰ ምድር ውሃ፣ አባካኝ የውሃ አጠቃቀም ባህል እና ሌሎች ማስረጃዎችን በማጣቀስ የሀገሪቱን ሴራ ያጋለጡም ኢትዮጵያውያን አሉ።
(Ebc)
ሰኔ 11/2012 ዓ.ም
--------------------------------------------------
ክቡራን ቤተሰቦች ሀሳብ አስተያየታችሁን የዜና የመረጃ ጥቆማችሁን ከሰር ባለው ሊንክ አድርሱኝ:: አመሰግናለሁ


Forward from: እውነታ TUBE
ምክር
===
🤧 ሲያስሉ ወይም ሲያስነጥሱ ክርንን በማጠፍ ወይም በሶፍት መሸፈን

🧻 የተጠቀሙበትንም ሶፍት በቶሎ በቆሻሻ መጣያ ውስጥ መጣል

😷 በማስክ አፍና አፍናጫዎን መሸፈን፤

⛺ ለሌሎች እንዳያስተላልፉ ራስዎን መለየት

💊 ማስታገሻ መድኃኒት እና ፈሳሽ በደንብ መውሰድ



ቤት ውስጥ እርስዎን የሚነከባከቡ ሰዎች የሚከተሉትን ጥንቃቄዎች ያድርጉ
===
👐 ለታማሚው ፍቅር መስጠት እና መንከባከብ

⛺ ከተቻለ የራሱን ክፍል መለየት

🚪 በሩንም መዝጋት

👤 እንክብካቤው ጤናማ በሆነ አንድ ሰው ብቻ ይሰጥ

😷 ተንከባካቢው ማስክ እና ሌሎች ጥንቃቄዎችን ማድረግ አለበት

🍴 መገልገያ ቁሶችን መለየት

🤒 ታማሚው በቤት ውስጥ የሚያደርገውን እንቅስቃሴን መገደብ

💨 በጋራ የሚጠቀሙባቸውን ክፍሎች በደንብ ማናፈስ እና ማጽዳት

🧼 በተደጋጋሚ የሚነኩ ቁሶችን በቀን ቢያንስ ሁለት ጊዜ ማጽዳት

📲 የህመም ስሜትን በየቀኑ በዚህ መተግበሪያ መከታተል

የትንፋሽ ማጠር እና የህመም ስሜት መባባስ ካለ በታች በተዘረዘሩት ቁጥሮች ይደውሉ
☎️ አዲስ አበባ ከተማ: 8335 እና 952
☎️ ትግራይ ክልል: 6244
☎️ አፋር ክልል: 6220
☎️ አማራ ክልል: 6981
☎️ ኦሮሚያ ክልል: 6955
☎️ ሱማሌ ክልል: 6599
☎️ ቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል: 6016
☎️ የደቡብ ክልል: 6929
☎️ ሐረሪ ክልል: 6864
☎️ ጋምቤላ ክልል: 6194
☎️ ድሬደዋ ከተማ: 6407


Forward from: የአርቲስቶች ውሎ
የተወለዱበትን ወር ቶሎ ይምረጡ እና በ Zodiac ሳይንስ ስለራስዎ በደንብ  ይወቁ😍 የፍቅር ሁኔታዎንም ይጠቁማል
100% ትክክል የሆነ
የርሶን ይምረጡ






Forward from: እውነታ TUBE
ትምህርት ሚኒስቴር ቀጣዩን የትምህርት ዘመን እና የአሁኑን አንድ ላይ አጣምሮ ምን ለማድረግ እንዳሰበ ይፋ አድርጓል። ሙሉ መግለጫውን ለማንበብ JOIN👇

የትምህርት ሚኒስቴር ደደብዳቤ - http://t.me/joinchat/AAAAAFVTeavdxdhmT-y1YA


Forward from: እውነታ TUBE
ትምህርት ሚኒስቴር ቀጣዩን የትምህርት ዘመን እና የአሁኑን አንድ ላይ አጣምሮ ምን ለማድረግ እንዳሰበ ይፋ አድርጓል። ሙሉ መግለጫውን ለማንበብ JOIN👇

የትምህርት ሚኒስቴር ደደብዳቤ - http://t.me/joinchat/AAAAAFVTeavdxdhmT-y1YA


Forward from: እውነታ TUBE
​​#ሰበር_ዜና

ባለፉት 24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 5,709 የላብራቶሪ ምርመራ 245 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ተገኝቶባቸዋል

•ተጨማሪ 7 ሰዎች ህይወት አልፎል

20 last posts shown.

315

subscribers
Channel statistics