የወሃቢያዎች ሚስጥራዊ ጥመት በመርጃ ሲጋለጥ "


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


#አክራሪ ጽንፈኛ ውሐብያ ድብቅ ሴራዎቻቸውን እናጋልጥ** ።
አክራሪ ፖለቲከኛ እና የሽብር ተላላኪ የውሐብይ ISIS ቡድንን ለማስቆም ሁለችንም በሀላፊነት መታገል ግደታ ይሆንብናል!
#فَضَائِحْ_الْوَهَابِيَة
#የወሃቢያን_ግድፈቶች_ግልፅ_ማድረግ
**የውሐብያ ሚስጥራዊ ጥመት በመርጃ ሲጋለጥ**
https://t.me/stop_wahababizm
@Stop_wahabizm_bot

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций


ላለፉት 14 ክፍለ ዘመናት የኖሩ ዑለሞቻችን ለሰይድ ዑመር የ20 ረከዐ ተራዊህ ይህን ያህል ክብደት የሰጡትና ከርሱ መጨመርን ወይም መቀነስን በግልጽ ባይከለክሉም በጥርጣሬ ዓይን እንዲያዩ ያደረጋቸዉ ስለኹለፋኡ ራሽዲን ባጠቃላይና ስለሰይድ ዑመር በተለይ የተነገሩ የሀዲስ ዘገባዎች፣ሀሳባቸዉ ከአላህ ፍላጎት ጋር አብዝቶ መግጠሙ፣እንዲሁም የሶሀቦች ስምምነት በሸሪዐዉ ያለዉ ክብደት እንደሆነ ዕሙን ነዉ፡፡ ይኸዉም፡-

1. የአላህ መልዕክተኛ ﷺ በአንድ ሀዲሳቸዉ የሚከተለዉን ትእዛዝ አስተላልፈዋል፡-

فَعَليْكُمْ بسُنَّتِي وسُنَّةِ الخُلَفاءِ الرَّاشِدِينَ المَهْدِيِيِّنَ عَضُّوا عَلَيْهَا بالنَّواجِذِ

‹‹አደራችሁን፣የኔንና ቅኑን ጎዳና የተከተሉትን ቅን ኸሊፋዎች (ኹለፋኡ ራሽዲን) ሱናዎች ተከተሉ፤አጥብቃችሁም ያዟቸዉ፤››[i]

ኹለፋኡ ራሽዲን የሚባሉት በዋነኛነት አቡበክር፣ዑመር፣ዑስማንና ዐሊ መሆናቸዉ ይታወቃል፡፡[ii] ይህ ሀዲስ ሶሂህ ነዉ፤ ስለትርጉሙ ከተሰጡ ማብራሪያዎች፡-

إن سنة الخلفاء والطريقة المسلوكة عنهم أيضاً سنة وليس ببدعة ، وقيل : إن سنة الخلفاء في الواقع سنة النبي - صَلَّى اللهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ - وإنما ظهرت على أيديهم

‹‹የኹለፋኡ ራሽዲን ሱናና የአስተሳሰብ /የትግበራ/ መንገድም እንደዚሁ ሱና እንጅ ቢድዐ አይደለም፤‹በነርሱ እጅ ይፋ ስለሆነ እንጅ የነብዩ የራሳቸዉሱና ነዉ› ተብሏልም፤››[iii]

በሙሀመዳዊዉ ድንቅ ዩኒቨርሲቲ ዉስጥ ከታላቁ መምህር ﷺ ሥር ለዓመታት ተኮትኩተዉ ለፍሬ ከበቁት አራቱ ኸሊፋዎች በላይ የሸሪዐዉን ይዘትና መንፈስ ሊረዳ ሚችል ሌላ ሰዉ እንደሌለ ዕሙን ነዉ፡፡ ከላይ የሰፈሩ የወለላዉ ነቢ ﷺ ምስክርነት ይህንኑ ያረጋግጣል፡፡ ለሀዲሱ የተሰጠዉ ማብራሪያ ደግሞ የኹለፋኡራሽዲን ሱና በእርግጠኝነት በነርሱ እጅ የተገለጸ ወይም በአንደበታቸዉ የተነገረ የነብዩ ﷺ ሱና መሆኑን ያስረግጣል፡፡ ነብዩ ‹ሱናቸዉን ተከተሉ› ሲሉ ‹ቃላቸዉ ቃሌ፣ተግባራቸዉ ተግባሬ ነዉ› በማለት በነርሱ ላይ ያላቸዉን መተማመን እየገለጹ ነዉ፡፡ ስለዚህ የሰይድ ዑመርን ትዕዛዝ መተግበር የነብዩን ﷺ ትዕዛዝ ከመተግበር አይተናነስም። በዚህ ትንታኔ አግባብ የተራዊህ 20 ረከዐ በሰይድ ዑመር የተገለጸ የነብዩ ﷺ ሱና ነዉ ማለት ይቻላል፡፡ የሶሀቦች ሙሉ ስምምነት (ኢጅማዕ) ይህን ፍሬ ነገር ከመረዳት የመነጨ ይመስላል፡፡ የተራዊህ 20 ረከዐ አሀዝ በዑለሞች እንዲህ ክብደት ተችሮት አራቱም መዝሀቦች የጸናዉም ለዚሁ ነዉ፡፡ የያዝነዉን ርዕሰ ጉዳይ በስምምነት ለመዝጋት ይህ ሀዲስ ብቻ በቂ ቢሆንም ሌሎች ተጨማሪ ዘገባዎችን አነሆ፤

2. በሊቃዉንት የሀሰን ደረጃ የተሰጠዉ ተከታዩ ሀዲስም የላይኛዉን ሀሳብ ያጸናል፡-

اقتدوا باللذين من بعدي أبي بكر وعمر

‹‹እኔን የሚተኩትን አቡበክርንና ዑመርን ተከተሉ፤››[iv]

ይህ ሀዲስ ከኹለፋኡ ራሺዲን መካከል የሰይድ አቡበክርንና የሰይድ ዑመርን ፈለግ በተለየ ሁኔታ መከተልን ያሰምርበታል፡፡ 20 ረከዐ ተራዊህ በሰይድ ዑመር አማካይነት የተገለጸ ሱና መሆኑ በዚህ ሀዲስ ብርሀን የበለጠ ክብደት እንድንቸረዉ ያደርገናል፡፡

3. ሰይድ ዑመር ‹‹አልፋሩቅ›› በሚል ቅጽል ስም ይታወቃሉ- ዕዉነትን ከሀሰት የሚለዩ ማለት ነዉ፡፡ በእስልምና ወሳኝ የታሪክ እርከን ላይ አላህ እርሳቸዉን በማስለም ዕዉነትን ከሀሰት ለይቷል፡፡ ሲሰልሙ አርባኛ ሙስሊም ነበሩ፡፡ በስድስተኛዉ ዓመተ ‹ሪሳላ› መሆኑ ነዉ፡፡ ከርሳቸዉ መስለም በፊት ሙስሊሞች ጥቃት እንዳይበረታባቸዉ ለመጠንቀቅ ሲባል ሀይማኖታቸዉን በድብቅ ለማከናወን ተገደዉ ነበር፡፡ ሰይድ ዑመር ሲሰልሙ ግን ይህ ሁኔታ በቅጽበት ተቀየረ፡፡ ሙስሊሞች ከፍተኛ ጉልበት አገኙ፡፡ ይፋ ለመዉጣትም ተደፋፈሩ፡፡ የአላህ መልዕክተኛም ﷺ በሶሂህ ሀዲስ ስለሰይድ ዑመር እንዲህ መስክረዋል፡-

إِنَّ الله تَعَالَى جَعَلَ الْحَقَّ عَلَى لِسَانِ عُمَرَ وَقَلْبِهُ

‹‹አላህ በዑመር አንደበትና ልቦና ላይ ዕዉነትን አኑሯለወ፤››[v]

ከባድ ምስክርነት ነዉ፤ሰይዱል በሸር ﷺ በኒህ ተማሪያቸዉ ቃልና ተግባር ብቻ ሳይሆን በቀልባቸዉ በሚያስቡት ነገር ሳይቀር ምን ያህል ይተማመኑ እንደነበር ያሳያል፡፡ ‹ዑመር የሚናገሩትና የሚያስቡት ሁሉ ሀቅ ስለሆነ ተቀበሉት›› ማለት መሆኑን ልብ ይሏል፡፡ ስለዚህ የተራዊህ ረከዐዎች ቁጥር 20 መሆኑ ዕዉነት እንጅ ሌላ ከማይናገር አንደበት፣ዕዉነት እንጅ ሌላ ከማይቋጥር ልቦና የመነጨ ስለሆነ ዕዉነትነቱ ከጥያቄ ዉስጥ የሚገባ አይደለም።

4. ሰይድ ዑመር ‹‹ሙልሀም›› /አላህ ፍላጎቱን ከልቦናቸዉ ዉስጥ ከሚያሳድርላቸዉ ሰዎች መካከል አንዱ/ መሆናቸዉ በዓለማት ዕዝነት ﷺ አንደበት ተመስክሮላቸዋልበ፡-

لَقَدْ كَانَ فِيمَنْ قَبْلَكُمْ مِنَ الأُمَمِ مُحَدَّثُونَ – أَيْ مُلْهَمُونَ – فَإِنْ يَكُنْ فِي أُمَّتِي أَحَدٌ فَإِنَّهُ عُمَرُ

‹‹ከናንተ በፊት ከነበሩ ሕዝቦች ዉስጥ ‹ሙልሀም› ስብእናዎች ነበሩ፤በኔ ኡመት ዉስጥ ‹ሙልሀም› ስብዕና ካለ ያ ስብዕና ሊሆን የሚችለዉ ዑመር ነዉ፤››[vi]

5. ሰይድ ዑመር እንዲህ ዓይነት የታደሉ ስብዕና ስለነበሩ ቁርአን ለበርካታ ጊዜ የርሳቸዉን ሀሳብ ደግፎ ወርዷል፡፡ አል-ፋሩቅ ራሳቸዉ የተወሰኑ አጋጣሚዎችን እንዲህ ተርከዉልናል፡-

وافقتُ ربِّي في ثلاث: في مقام إبراهيم، وفي الحجاب، وفي أَساري بدر، قلت: يارسول الله، لو اتخذنا من مقام إبراهيم مصلَّى؟ فنزلت: "وَاتَّخِذُوا مِنْ مَقَامِ إِبْرَاهِيمَ مُصَلَّى". وقلت: يارسول الله، إن نساءك يدخل عليهنَّ البرُّ والفاجرُ، فلو أَمرتَهُنَّ أَن يَحَتَجِبْن؟ فنزلت الآية الحجاب: "وَإِذَا سَأَلْتُمُوهُنَّ مَتَاعاً فَاسْأَلُوهُنَّ مِنْ وَرَاءِ حِجَاب". واجتمع نساء النبي r عليه في الغَيْرة، فقلت: " عسى ربُّه إن طلقكنَّ أَن يبدله أَزواجاً خيراً منكن" فنزلت كذلك

‹‹በሶስት ጉዳዮች ሀሳቦቼ ከጌታየ ፍላጎቶች ጋር ተገጣጥመዋል፤በመቃመ ኢብራሂም፣በሂጃብና በበድር ምርኮኞች ጉዳይ፡፡ ‹የአላህ መልዕክተኛ ሆይ፣መቃመ ኢብራሂምን የመስገጃ ቦታ አድርገዉ ለምን አይዙም?› በማለት ጠየቅኳቸዉ፤ ወዲያዉኑ ‹መቃመ ኢብራሂምን የመስገጃ ቦታ አድርጋችሁ ያዙ› የሚል የቁርአን አንቀጽ ወረደ፡፡[vii] ‹የአላህ መልዕክተኛ ሆይ፣ደግም ክፉም ሰዎች ባለቤቶችዎ ወዳሉባቸዉ ጓዳዎች ስለሚገቡ መከለያ ግርዶ (ሂጃብ) እንዲያደርጉ ቢያዟቸዉስ?› በማለት ጠየቅኩ፤ወዲያዉኑ ‹‹አንዳች ነገር ስትጠይቁ ከመጋረጃ ጀርባ ጠይቋቸዉ› የምትለዉ ሂጃብን ግድ የምታደርገዉ የቁርአን አንቀጽ ወረደች፡፡[viii] ባለቤቶቻቸዉ ባደሙባቸዉ ጊዜ ‹እርሳቸዉ ከፈቷችሁ አምላካቸዉ ከናንተ የተሸሉ ሚስቶችን ይተካላቸዋል› በማለት ገሰጽኳቸዉ፡፡ እንደዚሁ የምትል የቁርአን አንቀጽ[ix] ወረደች፡፡››[x]

ቲርሚዚ ‹ሀሰን› በሆነ ሰነድ እንደዘገቡት ዐብደላህ እብን ዑመር እንዲህ ብለዋል፡-




👉 ሰሞኑን ኡስታዝ ሀሰን ታጁ ስለ ተራዊህ ሰላት በተከታታይ ያስነበቡት ፅሁፍ ሰለፎችን በመከተል ስም ሰለፎችን የሚቃወሙትን ሰለፊይ ነን ባይ ወገኖችን አለቅጥ እያስጮሀ ይገኛል ፤ የሀበሻ ወሀቢ በምላሽ ምናምን ብዙም ያልተነካ ድንግል ስለሆነ ጩሀቱ የሚጠበቅ ነው ።

❇️ ከዚህ ጋር ተያይዞ ራሳቸውን ሚዛናዊ አድርገው ለማቅረብ የሚዳክሩ ቅሉ ግን ወሀቢዝምን ጭልጥ አድርገው የጠጡ ፈጣጦች “ ሁሉም የቻልነውን ይስገድ ፤ ምንም የሚያጣላ ነገር የለም “ ብለው ለወሀቢዮች ስህተት ሽፋን ሲሰጡ ተመልክተናል ።

❇️ የሚያጣላው ሁሉም የቻለውን መስገዱ ሳይሆን ከሰሀባ በላይ የምትከተሉት ሸይኻችሁ አልባኒ በሰሀቦች ስምምነት እስካሁን ሲሰገድ የቆየውን “ ሀያ ረከዐ “ ከሱና የሚቃረንና አዲስ መጤ ተግባር መሆኑን መናገሩና ይህን የሚተገብሩ ሙስሊሞችን የቢድዐ ሰዎች ብሎ መፈረጁ ነው ።

ከላይ ያለው የድምፅ ቅጂ ላይ አልባኒ እንዲህ ይላል :-

“ እነዚህ ሙብተዲዖች ተራዊህ ላይ ሀያ ረከዐ በመስገድ ላይ ችክ የሚሉበት ተግባራቸው ላይ ማስረጃ የላቸውም “ ።

በሌላ ቅጂ ደግሞ : -
“ ጥንት ተራዊህ ሰላት ላይ ሀያ ረከዐን የፈበረኩ ሰዎች “ እያለ ይናገራል ።


እፎይ በተባለው ግለሰብ ዙሪያ የጻፍኩትን ጽሁፍ አስመልክቶ ከደረሱኝ መልዕክቶች መሀል፦ "ከናንተ ወገንም እኮ ክርስትናን የሚያንቋሽሹ መምህራን ይገኛሉ፤ የክርስቲያን ባለጌን ብቻ ለይቶ መውቀስ አድሏዊነት ነው" የሚል ይዘት ያላቸው በብዛት ይገኙበታል። የልጁ ጉዳይ በአጋጣሚ አጀንዳ ስለሆነ እንጅ በየትኛውም ማህበረሰብ ውስጥ አጥፊ መኖሩ አይታበልም። ስድብና ብልግና ከየትኛውም ወገን ቢሆን ሊወገዝ እንጅ ሊደገፍ አይገባውም። አንድን ማህበረሰብ መቶ በመቶ ከእንዲህ ዓይነት ድኩማን የጸዳ ነው ብሎ ዋስትና መስጠት የሚቻል አይመስለኝም። መጠኑ ይለያይ እንጅ ከግራም ከቀኝም እኩያን ይኖራሉ። የአብዛኛዎቹ አማኞች ባህሪ ግን ጨዋነት ነው። ሁሉም ወገን የራሱን ባለጌዎች ዎች እንዲቆነጥጥ በቀረቡ ሀሳቦችና በተሰጡ አስተያየቶች የማይስማማ ያለ አይመስለኝም። የብዙሀኑ ጨዋነት በጥቂቶች ጋጠወጥነት መሸፈን የለበትም። ሆኖም መረጃን መሠረት ባደረገ መልኩ በጨዋ ደንብ መወያየትንና መማማርን ወይም እምነትን መግለጽን ከስድብ መለየት ተገቢ ነው።

በጥቅሉ ግን ሀይማኖት እጅግ ስስ አጀንዳ ከመሆኑ አኳያ የተለየ ጥንቃቄ የሚሻ ጉዳይ ነው። በርሱ በኩል የሚቀጣጠል እሳት መጥፊያ የለውም።

በኑሮ ውድነትና በሌሎች አጣዳፊ አጀንዳዎች በአራቱም አቅጣጫ ተሰቅዞ የተያዘው ማህበረሰብ ሌላ ሸክም ለመሸከም የሚችል ትከሻ የለውም። ምናልባትም ሁለቱን ሀይማኖቶች በማጋጨትና በተለያዩ አጀንዳዎች የተቆራረሰን ህዝብ የበለጠ በመበታተን ማትረፍ የሚሻ ወገን እንዳይኖር መጠንቀቁ አይከፋም። ስለዚህ ተጨማሪ ጥፋቶችን ከወዲሁ ለዘለቄታው ለመከላከል የሁለቱ ሀይማኖቶች ሊቃውንት ምክክርና ከምክክሩ የሚመነጭ የጋራ ጥብቅ የስነምግባር ደንብ፣ደንቡን በጽናት ማስፈጸምና አፈንጋጮችን በጋራ ማውገዝና ማስቀጣት ያስፈልጋል። የኢትዮጵያ ሀይማኖቶች ተቋማት የጋራ ጉባኤ ይህን ጉዳይ በሀላፊነት ማስፈጸም አለበት ባይ ነኝ። እስካሁን ሀላፊነቱ እየተወጣ ስለመሆኑ እርግጠኛ አይደለሁም።

ለተጨማሪ መረጃ የቴሌግራም ቻነሌን ይከታተሉ።

https://t.me/hassentaju




የዚህን ልጅ የቲክቶክ መልዕክቶችን ለሰከንድ ችሎ ማድመጥ ይከብዳል። አሳዳጊ የበደለው ባለጌ ነው። በዚህ ልክ ጋጠወጥ ለመሆን የተለየ ችሎታ ይጠይቃል።

አንዳንድ ድኩማኖች ሌላ የሚታወቁበት ዕውቀትም ሆነ መልካም ምግባር ሳይኖራቸው ሲቀር በብልግናም ቢሆን ለመታወቅ ራሳቸውን በእጅጉ ያዋርዳሉ። ከሶስት አስርት ዓመታት በፊት ሰልማን ሩሽዲ የተባለ እንግሊዛዊ satanic verses የተሰኘ በነብያችን ﷺ እና በቤተሰቦቻቸው ዙሪያ የሚያጠነጥን ልብ ወለድ ጽፎ ነበር። መጽሀፉ እዚህ ግባ የማይባል ቢሆንም ነብዬን ﷺ ስላንቋሸሸ ብቻ ዓለም አቀፍ ዕውቅና ተጎናጽፏል። የተለያዩ አካላትም ሽልማት ሰጥተውታል። በተቃራኒው ከብሪታንያ የቀኝና የግራ ክንፍ ፖለቲከኞች ድርጊቱን በማውገዝ ከሰውየው ነውር ራሳቸውን ያራቁ ነበሩ። ከፍተኛ የተቃውሞ ሰልፍም በለንደን አድርገዋል። ከኛም ዘንድ በግለሰብ ደረጃ የዚህን ባለጌ ነውር የተቃወሙ እንዳሉ አይተናል። በተቋም ደረጃ ግን የተለየ ነገር እስካሁን አላየሁም።

አሜሪካ ውስጥም በአባላት ድርቅ የተመታች አንዲት ቤተክርስቲያን ሀላፊ ቁርአንን በሜዲያ ፊት በማቃጠል አንድ ሰሞን ዝነኛ ሆኖ ነበር። በዚህ ብልግናው ያገኘውን ዝነኝነት ቤተክርስትያኑን ለማስተዋወቅ ተጠቅሞበታል።

እንዲህ ዓይነት እብዶች በሚያገጥሙን ሰአት የሚከተሉትን ጥንቃቄዎች ማድረግ ያስፈልጋል፦

1- ብልግናን በብልግና አለመመለስ፣

2- ግለሰቡን ብቻ ነጥሎ መተቸች፤ ከሀይማኖት ወይም ብሄር ጅምላ ፍረጃ መጠንቀቅ፣

3- ጉዳዩን ወደህግ መውሰድ፣ ሂደቱን ሳይሰለቹ በመከታተልና ለውጤት በማብቃት ለሌሎች አስተማሪ የሆነ ቅጣት እንዲያገኝ መስራት፤

3- ብልግና የሚረጭባቸውን ሜዲያዎች ተረባርቦ በማዘጋት በጋጠወጥነት ሊሸምተው የፈለገውን ዝናና ገንዘብ ማሳጣት፤

4- የተነሱ ብዥታዎች ካሉ በዕውቀት ብርሀን ማምከን፣

5- የዕምነት ወገኖቹ ይህን ብልግና በግልጽ በማውገዝና ባለጌ ልጃቸውን ከራሳቸው በመነጠል ከነውሩ ራሳቸውን ማጽዳት ይጠበቅባቸዋል።

ከዚህ ውጭ ሙስሊሞችን በማበሳጨት ዝነኛ መሆን ለሚሹ አካላት ፍላጎት ማሳኪያ ግብአት ላለመሆን መጠንቀቅ ያሻል።

በመጨረሻም ዕውነትን በሀሰትና በስድብ መሸፈን አይቻልም። ከአሁን በፊት እነአቡጀህል ሞክረው ከስረውበታል። ብዙዎች ተፍጨርጭረው ወድቀውበታል። የጸሀይን ብርሀን በሰፌድ ለመካተር መሞከር ከንቱ ድካም ነው። ወደላይ የተፋ አክታው ተመልሶ የሚያቆሽሸው ራሱን ነው። 'ኢነሻኒአከ ሁወል አብተር!!!'

ለተጨማሪ መልዕክት የቴሌግራም ቻነሌን ይከታተሉ።

https://t.me/hassentaju




ተራዊህ በ20 ረከዐዎች አሀዝ የተጀመረዉ በሰይድ ዑመር ዘመን መሆኑ ይታወቃል፡፡ በሰይድ ዑስማን ዘመንም ይኸዉ ልምድ አልተቋረጠም፡፡ ያን ጊዜ ተራዊህ የማሰገዱ ኃላፊነት በአብዛኛዉ የሰይድ ዐሊ እብን አቢጣሊብ እንደነበር የሚያመለክቱ ዘገባዎች ተላልፈዋል፡፡ በሰይድ ዐሊ ዘመንም የተለየ ነገር አልተዘገበም፡፡ ሰይድ ዐሊ እንዲህ ማለታቸዉ ተዘግቧል፡-

نوَّر اللهُ على عمر قبره، كما نوَّر علينا مساجدنا

‹‹ዑመር መስጊዶቻችንን እንዳበሩልን አላህ ቀብራቸዉን ያብራላቸዉ፤››[i]

ስለዚህ በሰይድ ዑስማንና በሰይድ ዐሊ ዘመን የሰይድ ዑመርን የ20 ረከዐዎች አሀዝ የሚቀይር እርምጃ መወሰዱን የሚያሳይ ሁነኛ ዘገባ ስለሌለ ሁኔታዎች በነበሩበት መልኩ እንደቀጠሉ መረዳት ይቻላል፡፡ የኢማም ቲርሚዚ (209-279 ሂ) ተከታዩ ማጠቃለያ የዚህን ድምዳሜ ትክክለኛነት ያጸናል፡-

أَكثرُ أَهل العلم على ما رُويَ عن عمر، وعليٍّ، وغيرهما من أَصحاب النبي r :عشرين ركعة وهو قول سفيان الثوري، وابن المبارك، والشافعي، وقال الشافعي: وهكذا أَدركت ببلدنا بمكة يصلُّون عشرين ركعة

‹‹ብዙሀን ዑለሞች ከዑመር፣ከዐሊና ከሌሎች ሶሀቦች ተገኘዉን 20 ረከአ የመረጡ ሲሆን፣ይህ የሱፍያነ ሰዉሪ፣የእብን ሙባረክና የሻዒም ምርጫ ነዉ፡፡ ሻፊዒ፡- ‹በሀገራችን መካ 20 ረከዐዎችን ሲሰግዱ ነዉ ያገኘኋቸዉ› ብለዋል፤››[ii]

እስካሁን የተሰጠዉ ማብራሪያ የሰይድ ዑመር ተራዊህን በአንድ ኢማም ስር በጀማዐ የማሰገድ ጥረት በአሀዝ ረገድ በ20 ረከዐዎች ተራዊህና በ3 ረከዐዎች ዊትር፣በድምሩ በ23 ረከዐዎች እንደጸና በማያሻማ ሁኔታ ግልጽ አድርጓል፡፡ ይህ አሀዝ በኹለፋኡ ራሽዲንና በሌሎች ሶሀቦች ሙሉ ስምምነት፣ያለተቃዉሞ እንደፀናም ግልጽ ሆኗል፡፡ ከላይ የተዘረዘሩት መረጃዎችና የዑለሞች ገለጻዎች 20 ረከዐ የተራዊህ ሶላት አሀዝ በብዙሀን ሶሀቦች የጸደቀ መሆኑን የሚያረጋግጡ ናቸዉ፡፡ የኢማም አህመድ እብን ሀንበልን መዝሀብ በማደራጀቱ ረገድ ጉልህ ድርሻ ያላቸዉ ኢማም እብን ቁዳማህ ‹‹አል ሙግኒ›› በተሰኘ ኪታባቸዉ ጁ፣2 ገጽ 167 ይህ አሀዝ ለ‹‹ኢጅማዕ›› ቀረብ ያለ መሆኑን አስረግጠዉ ጽፈዋል፡፡ መራቂል ፈላህ ከተሰኘዉ የሀነፍይ መዝሀብ ኪታብ ዉስጥም ተመሳሳይ ሀሳብ ሰፍሮ እናገኛለን፡-

وهي عشرون ركعة ) بإجماع الصحابة رضي الله عنهم ( بعشر تسليمات ) كما هو المتوارث

‹‹የተራዊህ ሶላት 20 ረከዐዎች መሆኗና በአስር መሰላመቶች እንደምትጠናቀቅ በሶሀቦች ኢጅማዕ የጸደቀና ከጥንት ይዞ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ አተገባበር ነዉ፤››[iii]

አልካሳኒ (አስከ 587 ሂ) ተመሳሳይ ሀሳብ አስፍረዋል፡-

جَمَعَ عُمَرُ أَصْحَابَ رَسُول اللَّهِ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ فِي شَهْرِ رَمَضَانَ عَلَى أُبَيِّ بْنِ كَعْبٍ - رَضِيَ اللَّهُ تَعَالَى عَنْهُ - فَصَلَّى بِهِمْ عِشْرِينَ رَكْعَةً ، وَلَمْ يُنْكِرْ عَلَيْهِ أَحَدٌ فَيَكُونُ إِجْمَاعًا مِنْهُمْ عَلَى ذَلِكَ

‹‹ዑመር የአላህን መልዕክተኛ ሶሀቦች በወርሀ ረመዳን በኡበይ እብን ከዕብ ኢማምነት ሥር ሰብስበዉ 20 ረከዐዎችን አሰግደዋል፤ ከሶሀቦች መካከል አንዳቸዉም የዑመርን ድርጊት አለመንቀፋቸዉ ስለተረጋገጠ ይህ አሀዝ በኢጅማዕ የጸና ሆኗል፡፡››[iv]

የሀንበሊ መዝሀብ ሊቅ የሆኑት አል በሁቲ (1000-1051 ሂ) እንዲህ ደምድመዋል፡-

وهي ( عشرون ركعة في رمضان ) لما روى مالك عن يزيد بن رومان قال كان الناس يقومون في زمن عمر في رمضان بثلاث وعشرين ركعة والسر فيه أن الراتبة عشر فضوعفت في رمضان لأنه وقت جد وهذا في مظنة الشهرة بحضرة الصحابة فكان إجماعا

‹‹ተራዊህ በረመዳን ወር ዉስጥ የምትሰገድ 20 ረከዐዎች ሶላት ናት፤ ሰዎች በዑመር ዘመን በረመዳን ዉስጥ 23 ረከዐዎችን ይሰግዱ እንደነበር የዚድ እብን ሩማን መናገራቸዉን ማሊክ ዘግበዋል፤ይህ ዘገባ የአሀዙ መነሻ ነዉ፤ ተራዊህ 20 ረከዐዎች የተደረገችበት ሚስጥሩ ረዋቲብ ሱናዎች አስር ስለሆኑ የነርሱ እጥፍ ለማድረግ ታልሞ ነዉ፡፡ ምክንያቱም ረመዳን የበለጠ ትጋት ይፈልጋልና፡፡ ይህ አሀዝ ሶሀቦች በተገኙበት በአደባባይ የጸደቀ ስለሆነ በኢጅማዕ የጸና ሆኗል፤››[v]

ከሶሀቦች በኋለም ይህ የስምምነት መንፈስ ተጠብቆ መቆየቱን ሊቃዉንት ይገልጻሉ፡-

كَانَ عَلَيْهِ عَمَل الصَّحَابَةِ وَالتَّابِعِينَ

‹‹የሶሀቦችና የታቢዖች ትግበራ ይኸዉ ነበር፤››[vi]

عَلَيْهِ عَمَل النَّاسِ شَرْقًا وَغَرْبًا

‹‹ከምስራቅም እስከምዕራብ የሰዎች ትግበራ በዚሁ አሀዝ ላይ የጸና ነዉ፤››[vii]

هُوَ الَّذِي عَلَيْهِ عَمَل النَّاسِ وَاسْتَمَرَّ إِلَى زَمَانِنَا فِي سَائِرِ الأْمْصَارِ

‹‹በሌሎች ከተሞችም ዉስጥ እስካለንበት ዘመን ድረስ የጸና የሰዎች ትግበራ ነዉ፤››[viii]

የአራቱ የፊቅህ መዝሀቦች ዕይታ የሶሀቦችን ኢጅማዕ ያከበረ ነዉ፡፡ይህን የጋራ ስምምነት መድፈር የተጀመረዉ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መሆኑን ልብ ይሏል፡፡

ለተጨማሪ መልዕክቶች የቴሌግራም ቻነሌን ይከታተሉ፤


https://t.me/hassentaju

[i] እብን ቁዳማህ፣አል ሙግኒ ፊፊቅሂል ሀንበሊ 2/167

[ii] ሱነን ቲርሚዚ

[iii] መራቂል ፈላህ ሸርህ ኑረል ኢዳህ፣ገጽ 183

[iv] በዳኢዑ ሶናኢዕ 1/288

[v] ከሻፉል ቀናዕ 1/425

[vi]ሀሽየቱ ዱሱቂ 1/315

[vii] እብን ዐቢዲን፣ረዱል ሙህታር 1/474

[viii] ሰንሁሪ፣ሸርሁ ዘርቃኒ 1/284




https://www.facebook.com/share/1DCL8GmRrU/?mibextid=wwXIfr
እኛ ብንሆን መጅሊሱ የሽአን እምነት ሊያስገባ መሆኑ ተደረሰበት የሚል ዜና ይሰራ ነበር #############################################################
እንግዲህ እነ ኢብራሂም ቱፋ ከኢራኑ የሽአ እመነት መሪ ጋር በኢራን ኤምባሲ አማካኝነት ተደጋጋሚ ግንኙነት እያደረጉ መጎኑ ይታወቃል።ይህ ግንኙነት በሱፍይ መጅሊስ መሪወች ቢሆን ኖሮ ፌስቡክ ላይና ቲክተክ ላይ ያሉ የፈጠራ ኡስታዝ ነን ባዮች ምን ዜና ሊሰሩ እንደሚችሉ መቸም መገመት አያቅታቹህም።"መጅሊሱ የሽአ እምነትን ሊያስገባ ንግግር ጀመረ" ብለው በምሽት ዜናቸው እንደሚያደነቁሩን ግልጽ ነው።ከአሁን በፊት መጅሊሱ አህባሽ የሚባል እምነት አስገባብን እያሉ ከ2002-2006 ድረስ እነ ኡስታዝ አወሊያ ላይ የፈጠሯት  ፈጠራ ዛሬም ድረስ አቡበክርን፣አህመዲንንም ሆነ ተራ ጯሂ ሳኡዲ የሄዱ አማተር የፌስቡክ ጸሀፊያንን ዛሬ ላይ በመንግስት የህዝብ ተቋም ሰብረው ገብተው እንደፈለጉ እንዲፈነጩ አድርጓቸዋል።

እኛ ማስመሰልም ሆነ መዋሸት እምነታችን አይፈቅደውምና ማጋለጥ ላይ ብቻ ትኩረት እናደርጋለን።"ዘንድሮ ሀጅ አይወጅብም" ያለው ሆዳም በሙፍቲ ጊዜ ትንሽ ብር ተጨመረ ብሎ ዛሬ ላይ ህዝቡ 625000 ብር ከፍሎ ሀጅ እንዲሄድ የሚቀሰቅሰው አህመዲን ጀበል የስልጣን ጉዳይ ስለሆነበት ብቻ መሆኑንም ሳንረሳ እናስታውሳለን።

SHARE  SHARE  SHARE ያድርጉ
LIKE LIKE LIKE LIKE በማድረግ የእርስወን ድርሻ ለሌሎች በማዳረስ ይወጡ
#የፌስቡክ #ገጻችንን #የዲን #ወታደር #የሚለዉን #ይህንን👇🏿
https://m.facebook.com/yedinwetader
በመንካት ገብተዉ  #LIKE #ያድርጉ

በቴሌግራም ይከታተሉን
https://t.me/joinchat/AAAAAFlZ0HCkBTtYs5KqDA
#እኔ_ኡለሞቸን_ተቋሜን_መስጅዴን_የምጠብቀው_ጀግናው_የሙፍቲ_ትውልድ_ነኝ




#ዳና
በሀገራች ኢትዮጵያ 1400 አመታት በላይ ያስቆጠረው ነአህሉ ሱነህ ወልጀማዓ (ሱፍይ) መስመር ለማስቀጠል እንዲሁም ተቋማቱን (መጅሊስ ፣መሳጂድና ሀሪማዎች) ለመጠበቅ ዓላማ አንግቦ ዳና አህሉ ሱነህ ወልጀማዓ ዑለማ ማህበር ከ5 ዓመት በፊት ተቋቁሟል። በከተማችን ኮምቦልቻ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ከከፈተ ደግሞ ሁለት አመት ሊሆነው ነው።

ይሁንና ከተለያዩ አካላት በሚደርስበት ከፍተኛ ጫና በሚጠበቅበት ልክ መንቀሳቀስ አልቻለም ነበር። ከጥቂት ቀናት በፊት ለቀጣይ 5 ዓመታት መንቀሳቀስ የሚያስችል ፍቃድ ከሚመለከተው የመንግስት አካል ስላገኘን ማህበራችንን ለማጠናከር እየተንቀሳቀስን እንገኛለን። ስለሆነም እንደ አንድ የሱፍዮች ወዳጅ ለማህበራችንን አስፈላጊውን ትብብር በማድረግ የማህበራችንን ዓላማ እንድናሳካ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

https://t.me/stop_wahababizm
https://t.me/stop_wahababizm


🛑 በዲፕሎማሲያዊ አካሄድ ያልተሸፋፈነውን ትክክለኛውን የወሀቢዮችን አቋም ለማወቅ ከፈለግክ ከላይ ያለውን የወሀቢ ፅሁፍ ተመልከት

❇️ እነ ኢማም አንነወዊን ፣ አቡ ሀሚድ አልገዛሊን ፣ ኢዝ ቢን አብዱሰላምን ፣ ኢብኑ ሀጀር አል ዐስቀላኒን ወዘተ በኩፍር የሚፈርጀው የወሀቢያ ቡድን ሱፊይና አሽዐሪያ በመሆኔ አያከፍረኝም ብለህ ራስህን የምታታልል ከሆነ ከእንቅልፍህ ስትነቃ እንገናኝ ቻው ቻው

❇️ ሙስሊም ሆነን ሳለ እንዴት በረመዷን ደማችንን ያፈሳሉ ⁉️ አሏህን አይፈሩም እንዴ⁉️ ብለህ አትወዛገብ ፤ እነርሱ እኛ ዘንድ ሙስሊም ናቸው እንጂ እኛ እነርሱ ዘንድ ከነ አቡለሀብ የበለጠ ሙሽሪኮች ነን ፤ እኛን መግደል ፣ ደማችን ማፍሰስ እነርሱ ዘንድ አጅር የሚያስገኝ ተግባር ነው


♦️ለመሆኑ ይህ ጥሪ ማንን ነው የሚመለከተው?

በየትኛውም ተቋም ላይ ችግሮች ይፈጠራሉ። እንዲህ ዓይነት ችግሮች ሲከሰቱ ችግሩ የሚፈታበት መንገድ ግልፅና የማያሻማ ሁኖ ሳለ በዐሊይ መስጂድ ላይ የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት መጅሊሱ ጥሪ ያስተላለፈበት መንገድ ግን ለምን ዓላማ እንደተፈለገ ግልፅ አይደለም።

ለመሆኑ ይህ ጥሪ ለማን የተላለፈ ነው?

ለየትኛው ጀመዓ ?
ከሁለቱም ወገን ጀመዓ አለ ጥሪው ማንን ነው የሚወክለው
ሁለቱም ቅሬታ አለው እና ጥሪው ለየትኛው ባለ ቅሬታ ነው?

ችግርን መፍታት የፈለገ አካል ወይም ተቋም እንዲህ ያለ #የተድበሰበሰ ጥሪን ማስተላለፍ ለምን ፈለገ ለየቱ ዓላማ?

ጥሪን አስተላልፈን ነበር መገኘት አልቻላችሁም ለማለት ወይስ ከሁለቱም ወገን አቤት ብሎ የሄደን ጀመዓ አንተን አልጠራንም ብሎ እነሱ ያልፈለጉትን ለመመለስና ለማሸማቀቅ?

ጀመዓ ማለት የአካባቢ ማህበረሰብን : በዛ መስጂድ ውስጥ ተጠቃሚን : መስጂዱን ያስገነባ ማህበረሰብን : የአካባቢ ኗሪን እንዲሁም ሌሎችን ሊወክል ይችላል።
ይህ ጥሪ ችግሮቹን ለመፍታት ያለመ አለመሆኑ ከጥሪው ጀምሮ የተለጠፈበት ሰዓት እና ወጪ የሆነበትን ቀን ለሚዲያ አድርገን ነበር ከማለት ውጪ ሌላን የማያስይዝ መሆኑን ትረዳላችሁ

ተጠሪው ማን እንደሆነ ባለየበት ሁኔታ ምን ዓይነት ውይይት ምንስ ዓይነት መፍትሄ ይኖራል?
ይህንን ችግር ከሥሩ ለመፍታት የተፈለገ ቢሆን

ጥሪው ሊሆን የሚገባ የነበረው

1. ሕዝብ ለመረጠው ኮሚቴ
2. ለመስጂዱ ወጣት ጀመዓዎች
3. ከአካባቢው ለተውጣጡ ተወካይ ማህበረሰቦች
እንዲሁም በዚህ ጉዳይ ለሚመለከታቸው ወኪሎች እደግመዋለሁ #ወኪሎች ነበር

ደም መፋሰሱን እርስ በርስ መጋ*ደ*ሉን የፈለገ በሚመስል ሁኔታ ተራ የመንደር ዓይነት ጥሪን ጠርቶ ብለን ነበር የሚል የሚዲያ መግለጫ ለመስጠት የቋመጠም ይመስላል✨


በዛሬዉ ምሽት በአዲስ ከተማ አሊ መስጂድ የተነሳዉን ፀብ ያስጀመረው ይህ ልጅ ነዉ። በአዲስ ከተማ በተበጠበጡ መስጂዶች ከፊት አይጠፋም ። የአሊ መስጂድ ጀማአ አይደለም ይሁን እንጂ በአሊ መስጂድ ፀብ ለመፍጠር ከመጡት ዉስጥ አንዱ ነዉ ።በየቦታዉ እንደፈለገ የሚሆነዉ የመጅሊሱ ከለላ ስላለው እንደሆነ ይናገራል ።

ይህ ዋና የመስጂዳችን በጥባጭ ፌደራል ሲመጣ ፖሊስ በፍጥነት ከለቀቁት ዉስጥ ነዉ ።የሚመለከተው ገለልተኛ የፀጥታ አካል ይህንን ልጅ ለህግ እንዲያቀርብልን እንጠይቃለን !!


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram


https://www.facebook.com/share/v/1BFBkoKoSp/?mibextid=wwXIfr
በአዲስ-አበባ በፖሊሶችና ጎረምሶች ድብደባ በረመዳን የወጣቶችን አይን አጠፋ!!!😭

ትላንት የአድዋ ቀን ምሽት 23/6/2017 በአዲስአበባ ሎሚ ሜዳ አሊ መስጅድ ሱልጣን አማን የተባለ ግለሰብ አደራጅቶ የሚልካቸው ጎረምሶች መስጅድ ውስጥ ሊሰግዱ የገቡትን ወጣቶች" ለምን የተራዊህ ዚክር" ይባል አላቹህ ብለው ቀድመው ገብተው ቁሳቁስ ይዘው ሲደበድቡ ከመስጅዱ በር ላይ ያሉ ፖሊሶች ደግሞ ኮማንደር ዳንኤል ለተባለና የአጣና ተራ ፖሊስ ጣቢያ አዛዥ ጥቅመኛ ሲባል ለግልግል የሄዱ ሰወችን ሁሉ "ተመለስ" በማለት አካል ሲያጎድሉና፣ኢ-ሰብአዊ በሆነ መልኩ ሴቶችን በየ ቤቱ እየገቡ ዘግናኝ በሆነ መልኩ ሲደበድቡና ሲቀጠቀጥጡ ና የግለስብን ህገወጥ ፍላጎት ለማሳካት ህግ ላይ ሲቀለድ አምሽቷል።

ሁሉም ይህንን አስነዋሪና ሰቅጣጭ አደጋን ለአለም ህዝብ፣ለከተማው ፖሊስ እና ለፌደራል ፖሊስ ጉዳዩን በማሳወቅ ይህንን ግፍ ተዝናንተው ሲፈጽሙ ያመሹ አክራሪና ቅልብተኛ ጎረምሶችን፣ሙሰኛ ፖሊሶችን ለህግ እንዲቀርቡ እንዲደረግ እየጠየቅን፣መስጅዶች የህዝብ እንጅ በህገ-ወጥ መልኩ ስልጣኑን የያዘውና እንደፈለገ የፖሊስ አዛዥ ጋር ሆኖ የሚዘውረው የሱልጣን አማን እና የጓደኞቹ የሚፈነጩበት እንዳልሆነ ማስረዳትና የሚመለከተው አካልም ሁሉንም ጉዳይ ከአካባቢው ማህበረሰብ መረጃ በመውሰድ በህገ-ወጥ መልኩ የተቋቋመውን ኮሚቴ በማስወገድ ለህዝብ እንዲመልስ በጥብቅ ማሳወቅ እንወዳለን።

SHARE  SHARE  SHARE ያድርጉ
LIKE LIKE LIKE LIKE በማድረግ የእርስወን ድርሻ ለሌሎች በማዳረስ ይወጡ
#የፌስቡክ #ገጻችንን #የዲን #ወታደር #የሚለዉን #ይህንን👇🏿
https://m.facebook.com/yedinwetader
በመንካት ገብተዉ  #LIKE #ያድርጉ

በቴሌግራም ይከታተሉን
https://t.me/joinchat/AAAAAFlZ0HCkBTtYs5KqDA
#እኔ_ኡለሞቸን_ተቋሜን_መስጅዴን_የምጠብቀው_ጀግናው_የሙፍቲ_ትውልድ_ነኝ


መስጂዶች የጸብ ሜዳ ሲሆኑ ዝም ብለህ የምትቀመጥ ምእመን ነገ ልጅህ መስጂድ አይሄድም እንዴ? ፓኪስታን, ሊቢያ, ሶሪያ, ሶማሊያ ወዘተ መስጂድ ውስጥ የሚሞቱት እኮ ምንም የማይመለከታቸው ንጹሓን ናቸው:: እዚህም prospected ሟች ያንተው የኔው ልጅ እንዳይሆን ዛሬውኑ ተከላከል:: እንከላከል:: ይህንን የምልህ ሌሎች ሀገሮች ላይ ከሚያደርጉት በመነሳት ነው:: የጠቀስኳቸው ሀገራት ላይ አንዱ ባንዱ ጣት እየተቀሳሰረ ነው ሀገራቸውና መስጂዳቸውን ያጡት:: አንዱ አላሁ አክበር ብሎ ይገ^ድላል:: ሟች ላኢላሃ ኢለላህ እያለ ይሞታል:: ያሳዝናል::

(ፎቶ: አዲስ አበባ ሎሚ ሜዳ ዐሊ መስጂድ ረመዷን ጾመው ውለው ማታ ሊሰግዱ በገቡ ምእመናን ላይ ኢማም ካልተገለበጠ ብሎ መጅሊሱ ያስፈጸመው ተግባር ነው)::


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ወሀብያ ገዳይ ካልሆነ ማነው ገዳይ እሺ?


በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ወ ሀ ብ ያዎችን ሽፋን እየሰጠ ወደ መስጂዶቻችን ፥ ወደ ሀድራዎቻችን ለሚያስገባና መግቢያ ቀዳዳ ለሚያበጅላቸው ሰው የትላንትናው የዓሊ መስጂድ አይነቱ ድርጊት ሊያስተምረው ይገባ ነበር:: ባለፉት አመታቶች ውስጥ ሀገራችን ውስጥ እጅግ ብዙ ተመሳሳይ የሆኑ ክስተቶች ተፈጥረዋል::

ያንን ያየ ሰው በምንም አይነት ሁኔታ እነዚህን ሰዎች ወደ ሀድራዎቻችንም ሆነ መስጂዶቻችን ሊያቀርባቸው ባልተገባ ነበር:: በሚያሳዝን ሁኔታ አንዳንዶቻችን በተደጋጋሚ ተመሳሳይ የሆነ ስህተት ስንፈፅም ይስተዋላል:: ተመሳስለውና ተለሳልሰው ገብተው ከተመቻቹ በሁዋላ በተለያየ አይነት ሸ ር ያዳክሙናል ፥ ያሳስሩናል ፥ ያስደበድቡናል ፥ ያፈራርሱናል:: ከዛም መሳጂዶቻችንን ይቀሙናል::

Показано 20 последних публикаций.