ግጥም ለኢየሱስ ️️️📖✍


Channel's geo and language: Ethiopia, English
Category: Other


እንኳን ወደ ግጥም ቤታችሁ በደህና መጣችሁ ይህ የገጣሚ #አማኑኤል ነጋሽ እና የለሎች ገጣሚያን ግጥም የሚቀርብበት ነው
አዘጋጅ✍️AMANUEL NEGASH(Abu)
ግጥሜን ለኢየሱስ
10,000 members 🏃🏃‍♂️
ለአስተያየት👇
@AbuGitimBot
@abu_ND8
🛑YOUTUBE🛑
https://www.youtube.com/@gitim_alem
Telegram
@gitim_alem

Related channels

Channel's geo and language
Ethiopia, English
Category
Other
Statistics
Posts filter




🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶🎶
ይህን ምሽት ብርክ ብላቹ እንድታሳልፉ በማሰብ
ድንቅ መዝሙሮችን ልንጋብዛቹ ነው

⚫️ታዲያ የድሮ መዝሙሮችን📀
ወይስ
⚪️አዳዲስ መዝሙሮችን💿
እንጋብዛቹ🎁
📛ምረጡ
ቀጥሎም የሚመጣላቹን ቻናል በመቀላቀል በዝማሬዎቹ ተባረኩ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇


መልካም አዳር🥰


ይሄ ክፉ ዓለም ምኑ ይመቻል
በሥጋ በደም የትኛው ሲቻል🥺
በየማለዳው አዲስ በሆነው
በምህረቱ ነው ያልጠፋነው 🙏
እንደ እኔ ቢሆን እንደድካሜ😭
ዛሬም በፊቱ ባልታየሁ ቆሜ 🚶
በዐይኔ እያየሁት አለፈ ስንቱ
የያዘኝ አምላክ እግዚአብሔር ብርቱ💪

ሰቆ. 3
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²² ሔት። ያልጠፋነው ከእግዚአብሔር ምሕረት የተነሣ ነው፤ ርኅራኄው አያልቅምና።
²³ ማለዳ ማለዳ አዲስ ነው፤ ታማኝነትህ ብዙ ነው።

መልካም ቀንይ ይሁንላችሀ
@gitim_alem


ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ

#ሁለት ሰይፍ
ክፍል አምስት(ሜርሲ✍️)


"ይሀውልሽ ሱዚያና አሁን ላይ የጣልኩትን ነገር የማነሳበት ሰዓት አይደለም::የድሮው ናቲ ሞቷል::ሕይወትሽን ኑሪ::"
"እርዳታህን የምጠይቀው እኮ ማንም ሰው እዛ ስለሌለኝ ነው::እማዬ ብቻዋን ከቤተሰብ ተነጥላ እንዳሳደገችኝ ታውቃለህ::ማንንም አምኘ ያንን ዕቃ ልሰጠው አልችልም::እባክህን.. እንደ አንድ እርዳታን እንደሚጠይቅህ ሰው ብቻ አድርገህ ቁጠረኝ እና ተበባረኝ::"
ዝም ብሎ ይቆያል::
"ህ.. ናቲ..."
"እሺ::ድጋሚ ግን ባትደውይልኝ ደስ ይለኛል::"
"አመሰግናለሁ ናቲዬ::እባክህን ለእናቴ ዕቃው ባልኩህ ሰዓት ሊደርስላት ይገባል::"
"እሺ አልኩሽ እኮ::ቻው::" ስልኩን ዘግቶ ሶፋው ላይ ወርወር ያደርጋል::
ድምፅ የሰማ ስለመሰለው ወደ ውጭ ሲወጣ ዮሃና ወደ ውጭ በር እየተጣደፈች ስታመራ ይመለከታታል::
"ዮሃና ተመለሺ::በዚህ ለሊት የት ልትሄጂ ነው!?" አለች ሳራ ከበሩ ቆማ::ናትናኤል ወደ ሳራ ይዞራል::
"የትም ልህዲ አያገባሽም::" በሩን ልትከፍተው ስትል በቁልፍ እንደተዘጋ ትመለከት እና በቁጣ ወደ ሳራ ትመለከት እና ትመለሳለች::
"ቁልፉን ስጪኝ::"እጇን እየዘረጋች::
"እባክሽ እንደ ሕፃን አትሁኚ::ወደ ቤት ግቢ!"
"እሱን አንቺ አትነግሪኝም... ቁልፉን ስጪኝ::"
"ዮሃና::" ሁለቱም ወደ ናትናኤል ይዞራሉ::
"ነገሩ ምንም ይሁን ምን በዚህ ሰዓት ብትወጪ ተጎጂዋ አንቺ ነሽ::ሲነገ ብታወሩ አይሻልም::ለእሱም ስትይ::"
ዮሃና ከበሩ በባዶ እግሩ የቆመውን ማክቤልን ትመለከተው እና ወደ ሳራ ትመለከታለች::
"ነገ አዘጋጅተሽ ጠብቂኝ::" በትከሻዋ ገፋ አድርጋት የማክቤልን ግንባር ስማ ትገባለች::
"ማክ ግባ እመጣለሁ::"
"አንቺ ጋር ዛሬ ማተኛት እችላለሁ?"
"አዎ የኔ ጣፋጭ::"
እሱ ሲገባ ወደ ናትናኤል ትዞራለች::
"ይቅርታ ናትናኤል ይሄን ክፍል ማከራየት ያልፈለግኩት ለዚህ ነበር::በየቀኑ ባህሪዋ ይቀያየራል::"
"ኢ ት ኢዝ ኦኬይ... ስልክ ተደውሎልኝ ነቅቼ ነበር::"
"እምም... እሺ..." ፊቷን አዙራ ስትገባ ይመለከታታል::

*                               *                               *
ሳራ እንደለመደችው በጠዋት ተነስታ ቁርሳቸውን ከሰራራች በኋላ እያቀራረበች እያለ ዮሃና ዩኒፎርሟን ለብሳ ትወርዳለች::
ሳራ ቀና ብላ አይታት :-"ቁርስ ቀርቧል..."
ቦርሳዋን ከትከሻዋ ታወርድ እና በእጇ አንጠልጥላው በተሰላቸ ስሜት ትመለከታታለች::
"ማታ ያልኩሽን ገንዘብ አዘጋጀሽልኝ?"
"የምለፋው.... አንቺ ፓርቲ ለፓርቲ እየዞርሽ እንድትበትኚው አይደለም::"
"ልበትን.. ሁ ኬርስ.... አባዬ ያስቀመጠልኝን ገንዘብ ነው የጠየኩሽ::"
"አስራ ስምንት ዓመት አልሞላሽም...."
"አሃ.... ጥሩ...."ወደ በሩ በፍጥነት ታመራ እና በሩን በርግዳ ትወጣለች::
"እህቴ.... ቁልፌን አስተካኪይልኝ::"አላት ማክቤል::ዞራ በስስት ትመለከተዋለች::

*                             *                              *

አቤነዘር እና ናትናኤል ፀጥታ ከሰፈነበት ካፌ ተቀምጠው ከፊታቸው ቡና ተቀምጦ ያወራሉ::
"እምም... የተወሰነ አውቃለሁ::እናት እና አባታቸውን ካጡ በኋላ ቦታ ተቀያየሩ ማለት ይቻላል::ሳራ ወደ እራሷ ስትመለስ ደህና የነበረችው ዮሃና ደግሞ ፍፁም ነው የተለወጠችው::ምን እንደተፈጠረ መረዳት አልቻልኩም::ምን አሰብክ ታዲያ::ቤት ትቀይራለህ?"
"አይ በፍፁም::እስኪ ትንሽ ልያቸው::"
"አዎ ልክ ነህ::እግዚአብሔር ያለምክንያት እዛ ቤት እንድትገባ ፍቃዱ አይሆንም::እርግጠኛ ሆኘ የምነግርህ ሶስቱም በጣም ንፁህ ልብ ያላቸው ልጆች ናቸው::የገጠማቸው ችግር ነው::"
"አይ ሲ..." ደገፍ ይል እና ይተነፍሳል::
"የሆነ የማደርሰው ዕቃ አለኝ::ነገ እንገናኛለን::" ተሰናብቶት ሂሳብ ሊከፍል ሲል አቤነዘር አሻፈረኝ ሲለው ቅር እያለውም ቢሆን ተሰናብቶት ወጥቶ ወደ መኪናው ያመራል::

*                           *                             *

መኪና እየነዳ እያለ ስልኩ ሲጠራ መኪናውን ከዳር አቁሞ ያነሳል::
"ሄለው..."
"እንዴት ነህ ናትናኤል::ሳራ ነኝ..."
"ኦውው ሳራ.. እንዴት ነሽ?"
"ደህና ነኝ::እባክህን አንድ ነገር ላስቸግርህ ነበር::"
"ችግር የለውም... ምን ነበር?"
"ወደ ሃያት ሄድኩኝ እና መንገድ ተዘጋጋብኝ::ሹፌሩ ደግሞ ስልኩ አይሰራም::ሥራ ካልያዝክ ማክቤልን ፒክ ታደርግልኛለህ?... በጣም ከይቅርታ ጋር::"
"እምም... ችግር የለውም::የት ነበር የሚማረው?"
መኪናውን ያዞራል::

*                              *                             *

ሰዓቱን ሲመለከት ለአንድ ሩብ ጉዳይ ይላል::መኪናውን ከኩርባው ላይ ሲያደርስ ግርግር እና ጩሀት ይመለከታል::መንገዱ በሰዎች ስለተሞላ መኪናውን እዛው ያቆም እና ኮፈኑን ከፍቶ ከሱዚያና የተላከውን እና ከፍቶት ያላየውን ቦርሳ በእጁ ይዞ ኮፈኑን በመዝጋት ቀና ብሎ ሲያስተውል ግርግሩ እና ጩሀቱ ያለው ከሱዚያና እናት ቤት መሆኑን ይመለከት እና ደንገጥ ብሎ ከጎኑ ወዳሉት ሁለት ሴት ወጣቶች ጠጋ ብሎ:-
"ምን ተፈጥሮ ነው?"
አንዷ ዘወር ብላ አስተውላው ከተመለከተችው በኋላ:-
"ያቺ ካናዳ ልጅ ያለቻት እናት አርፈው ነው አሉ::"
"የሱዚያና እናት!?"ድምፁን ከፍ አድርጎ::
"አው.. ሱዚያና... ምስኪን እናት.. እንደው ምን አጣው ብለው ነው በፈጣሪ ሥራ የገቡት::በገመድ ተንጠልጥለው ነው የተገኙት አሉ...."
"በኢየሱስ ስም.."ቦርሳውን ከመሬቱ በድንጋጤ ይጥላል::

   
Like🥰 Comment📩 Share💫
ቀጣዩ  እንድለቀቅ

ይቀጥላል...

ግጥሜን  ለኢየሱስ
   💙እወዳችኋለሁ 💙
---------------------------------------------------------
SHARE
| @GITIM_ALEM |
| @GITIM_ALEM |
--------------------------------------------------------
SHARE
   Contact me  @abu_ND8


ከሙሴ መና ትበልጣለህ


አባቶቻችን በልተው መናን ምድረ በዳ
አንተን ሳያገኙ ካንተ እንደ እዳ
አንተ የሌለህበትን መብልና ሙሃ
ሁሉም ሰው በላና ቀረ በበረሃ

መቼ ግን ገባቸው አንተ እንደምትበልጥ
ከሰጠሃቸው ነገር ከመብል እና መጠጥ
መብሉን ተውና እሱን ግን እውቁ
ብሎ ብመክራቸውም ባርያህን ግን ናቁ

ለ'ተቀን ህልማቸው መብሉ ሆነና
አንተን ግን ቀየሩ ባበላሃቸው መና
የሚረዱት አንተን በምግቡ ሆነና
ሁሉም እዛዉ ቀረ በተስፋው ገዳና

የኔም ሲጋት ያለው እዚህ ጋር ነው ኣባ
እንዳልሆን ደካማ ፍቅርህ የማይገባ
እንደበሉት በመና አንተን እንዳጠበቡ
እነም እንዳልለካህ በቁስ እጄ በምገቡ

አንተ መች ትለካለህ ለኔ በምትሰጠው
በሀብትና ገንዘብ ከቤቴ ውስጥ ካለው
ከፍትፍትህ ፊትህን እንዳውቅ አስቀድሜ
እርዳኝ እልሃለሁ አልችልም በአቅሜ

✍️Amanuel Negash(abu)

ግጥሜን  ለኢየሱስ
   💙እወዳችኋለሁ 💙
---------------------------------------------------------
SHARE
| @GITIM_ALEM |
| @GITIM_ALEM |
--------------------------------------------------------
SHARE
   Contact me  @abu_ND8


እና Guys ለቀጣይ Please ግጥም ሲለቀቅ like🥰 አድርጉ Comment 💬 አስቀምጡ አለ ኣ በቃ ቢያንስ #በርታ በሉኝ #motive የሚባል ነገር አለ።

እወዳችኋለሁ ደህና እደሩ🥰


ግን ግጥሙን like🥰 የማታረጉት በሰላም ነው😞
እኔ እየፈራሁ ነው🥹
እንደ like🥰 አድርጉ እንጂ አብረን እንጓዝ እየገጠምን🤨


እንዳልገኝ ተኝቼ

የመምጣትህን ዳግመኛ ተስፋ
እየጠበቅኩኝ ይሄው ቀናቱ ተገፋ
ልቤም ተዘናግቶ ይሄው እየከፋ
ቃልህን እረስቶ ስምህን አክፋፋ

ጠብቅ ባልከኝ ቦታ ድካሜ በዛና
በመጠበቂያዬ ሆኜ ረክሼ አለሁና
የማንቂያውን ደወል የመምጣትህን ወሬ
በእንቅልፌ ሲሰማ እንዳልቀር ከስሬ

በትጋት ነው እንጅ አንተን መጠበቁ
ከድካምና እንቅልፍ ዘወትር እየነቁ
ጠላትን ሊዋጉ ለጽድቅ ሲታጠቁ
ዳግም ምጻትህን ለተ'ቀን እያወቁ

እኔ ደካማ ነኝ በእጅጉ ሰነፍ
የተናገርከኝን ቃሎችን የማጥፍ
መጠበቅያዬ ቦታን የማደርግ ለእንቅልፍ
ሲበዛ ደካማ ለጽድቅ የማልሰለፍ

አደራ ጌታ ሆይ ይህን ቃሌን አደራ
ከቤት ውስጥ ሆኜ እንዳልሆን ክስራ
አንተ በምትመጣበት ቀን ፊትህን ፈርቼ
ከውጭ እንዳልቀር እንዳልገኝ ተኝቼ


ጠብቅ ካልከኝ ቦታ
እርቄ የማታ የማታ
ዳግም ስትመጣ
ስዖል አይሆን የኔ እጣ

Guys እንንቃ የምር🥰

✍️Amanuel Negash(abu)

ግጥሜን  ለኢየሱስ
   💙እወዳችኋለሁ 💙
---------------------------------------------------------
SHARE
| @GITIM_ALEM |
| @GITIM_ALEM |
--------------------------------------------------------
SHARE
   Contact me  @abu_ND8


ዮሐንስ 14 : 15-16፤
ብትወዱኝ ትእዛዜን ጠብቁ።

ኢየሱስን መውደዳችን የሚታወቀው ትዕዛዙን በመጠበቃችን ነው።
ካልታዘዝንለት አንወደውም ነው በቃ !!

እንድወድህ አንተ ታውቃለህ🙄
እንድወድህ እርዳኝ ጌታ ሆይ🤲


ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ

#ሁለት_ሰይፍ
ክፍል አራት (ሜርሲ✍️)

ናትናኤል የእራሴ የሚላቸውን ዕቃዎች በስርአት ከሰደረ በኋላ ከበሩ ጋር ሆኖ ቤቱን ይመለከታል::
"ናትናኤል::" ወደ ውጭ ይወጣል::ሳራ ሙሉ ቱታ ለብሳ በእጇ የመኪና ቁልፍ አንጠልጥላ ከእሱ እራቅ ብላ ቆማለች::
"ቤቱ አማረልህ?"
ፈገግ ብሎ:-
"ቀድሞም ያማረ ቤት ላይ እኮ ነው የገባሁት::"
እሷም ፈገግ ትል እና:-
"ቆንጆ ቆይታ እንዲኖርህ ነው የምመኘው::እምም... የሚያስቸግርህ ወይም የምትፈልገው ነገር ካለ ደውልልኝ::ማክቤልን ከክላስ የማመጣበት ሰዓት ደርሷል::"
"እሺ.." ፊቷን አዙራ ወደ በሩ ትሄዳለች::
"ሳራ.."
ቆም ብላ ትዞራለች::
"ስልክሽን አልሰጠሽኝም::"
"ኦውው.. ያ... ያዘው::"
ቁጥሯን ተቀብሏት ስትወጣ በዓይኑ ሸኝቷት ወደ ቤቱ ሲገባ እጁ ላይ የያዘው ስልክ ይጠራል::አቤነዘር መሆኑን ሲያይ ተቻኩሎ በማንሳት ወደ ጆሮው ያደርጋል::
"እንዴት ነው አዲሱ ቤትህ... እየተለመደ ነው::"
"ይለመዳል ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ::" ከሶፋው ተቀምጦ ከአጠገቡ ሪሞቱን በማንሳት ከፊቱ ስታንዱ ላይ ያለውን ቲቪ ይከፍታል::
"ምን አሉህ?... ቅድም እኮ አልተደማመጥንም::"
"እምም... እንግዶችህ ጋር ነበርክ::እንደጠበቅኩት ነው::አላሳመንኳቸውም::"
"የምር.."
"ይሃ.... አባዬ በተለይ..."
"አንድ ልጃቸው እኮ ነህ::"
"ይገባኛል አቤኒ::ግን አንዳንዴ ውስጥህ የሚነግርህን ማዳመጥ አለብህ::"
"ልክ ነህ::ለልብህ የሚነግርህን መንፈስ ቅዱስ ማዳመጥ አለብህ::"
"መንፈስ ቅዱስ..."
"አዎ.. ምነው..."
"አይ ምንም...."
"ዛሬ የወጣቶች ፕሮግራም አለ::አስራ አንድ ሰዓት ለምን ብቅ አትልም::"
"ኦውው.. አቤኒ... በዛ ሰዓት ኦንላይን የምሰራው ሥራ አለኝ::በኋላ እንደዋወል በቃ::"
እያቅማማ:-"እሺ እንዳልክ::ደሕና ሁን::"
"ባይ.."ስልኩን ዘግቶ ከጎኖ በማስቀመጥ ወደ ቲቪው እየተመለከተ በእረጅሙ ተነፈሰ::
"ግራ የገባሽ ዓለም..."

*                         *                                   *

ሳራ መገናኛ ከሚገኘው ከሰፊው ዳቦ እና ኬክ መጋገሪያ እና መሸጫቸው ላይ ተሰይማ ከውስጥ ከሚሰራው ጀምሮ እስከ መሸጫው ድረስ ጥራታቸውን ሁኔታውን ካየች በኋላ ማኔጀሩ የቀን የሽያጭ ሁኔታውን ካብራራላላት በኋላ የሚያደርገውን አዛው ከእሱ ከተለያየች በኋላ ተሰናብታቸው በመውጣት ከመኪናዋ በመግባት ሰሚት ወዳለው ሌላኛው ቅርንጫፍ ታመራለች::

*                          *                             *

ናትናኤል ከበሩ ሲወጣ ማክቤል ከበረንዳው ጫፍ ላይ ተቀምጦ ኳሱን በእጁ እያመላለሰ ከበሩ ላይ ዓይኑን ተክሎ ሲያገኘው እሱም የዓይኑን አቅጣጫ ተከትሎ ወደ በሩ ይመለከታል::
ምንም የሚታይ ነገር ሲያጣ ዓይኑን ወደ ማክቤል ይመልሳል::
"ደሕና ነህ ማክቤል... ማክቤል.."
ማክቤል ደንገጥ ብሎ ይመለከተዋል::
"ደሕና ነህ..."
"አዎ..."
"እምም... ኳስ አብረን መጫወት እንችላለን::"
የማክቤል ፊት ይፈካል::
"እንዴ ትጫወታለህ::" ኳሱን እንደያዘ ይነሳል::
ናትናኤል ወደ መሃል እየሄደ:-
"ኩመካ ላይ እንዴት ነህ?"
"ማንም አይችለኝም::"
ናትናኤል እየሳቀ:-
"ታዲያ እኔ ልሞክርሃ::" እየተጫወቱ እያለ ሳራ ስትገባ ማክቤል የመታው ኳስ ከፊቷ ሲያርፍ ፊቷን ይዛ ዝቅ ትላለች::ማክቤል እና ናትናኤል በድንጋጤ ይመለከቷታል::
"ሳ... ደሕና ነሽ.." ቀና ብላ ትመለከተዋለች::
"ማክ አሁን ግባ::" ትላለች በተቆጣ ድምፀት::ማክቤል ፊቱን አዙሮ ወደ ውስጥ ይገባል::
"ደሕና ነሽ.."
"አዎ... አስቸገረህ አይደል?" ጉንቿን እያሻሸች::
"አይ እኔ ነኝ እንጫወት ያልኩት::"
ፊቷን አዙራ ትልቁን በር በመክፈት ከውጭ የቆመውን መኪናዋን ወደ ግቢ ታስገባ እና መልሳ ስትቆልፍ ወደ በሩ ጋር ይመለከታታል::ከመኪናው ነጭ ኬክ እና ዳቦ የያዘ ሁለት ፔስታል ይዛ በመውረድ ወደ እሱ ቀረብ ብላ አንዱን ፔስታል እያቃበለችው:-
"እስኪ ይሄን ቅመሰው::"
እየተቀበላት:-
"ኦውው... አመሰግናለሁ::"
"እናቴ እያለች ተከራዮችዋን የመጀመሪያ ቀን ቡና አፍልታ ኦልሞስት ደግሳ ነበር የምትቀበለው::ትንሽ ቢዚ ሆንኩኝ::"
"ዚ ስምን ኤሎት::አመሰግናለሁ በጣም::"
"ደሕና እደር::"
"ደሕና እደሪ::"
ገብቶ በሩን ከኋላው በመዝጋት አንድ ሶፍት ያወጣ እና ከፔስታሉ ውስጥ አንድ ተቆራሽ አንስቶ አንዴ ሲገምጠው አይኑ ይፈካል::
"ኦ ማይ ጋድ.. ይሄ ይለያል::" ድጋሚ ይገምጠዋል::

*                        *                                *

ስልኩ ሲጠራ ብድግ ይላል::ላፕቶፑ እንደተከፈተ ከጠረጴዛው ላይ ተቀምጧል::
"አምላኬ::መቼ ነው እንቅልፍ የወሰደኝ::"ቀና ብሎ የግድጊዳውን ሰዓት ሲመለከት ለሰባት ይቆጥራል::
"ማነው በዚህ ለሊት.." እግሩን ከሶፋው ላይ በማውረድ ስልኩን ከጠረጴዛው ላይ አንስቶ ደዋዩን ሲመለከት ደንገጥ ይላል ካቅማማ በኋላ አንስቶ ጆሮው ላይ ያደርጋል::
"ሱዚያና..."
"ይቅርታ የኔ ውድ ከመሸ ደወልኩብህ.... የሆነ ነገር ተፈጥሮ::"
"እባክሽን..."
"ይገባኛል... ብዙ እንደተጎዳህ... ግን አንዴ ብቻ ስማኝ.."
በእረጅሙ ይተነፍስና:-
"ምንድነው እሺ..."

   Like🥰 Comment📩 Share💫
ቀጣዩ  እንድለቀቅ

ይቀጥላል...

ግጥሜን  ለኢየሱስ
   💙እወዳችኋለሁ 💙
---------------------------------------------------------
SHARE
| @GITIM_ALEM |
| @GITIM_ALEM |
--------------------------------------------------------
SHARE
   Contact me  @abu_ND8


ሁለት ሰይፍ
ልብወለድ ዛሬ ማታም ይለቀቃል አንብቡት


ክርስትና ማለት መስቀል መሸከም ነው
ክርስቶስን መልስሎ በህይወት መኖር ነው
ቃሉን መተግበር ነው

ህይወት ይናገር እስት !


የዘላለም ፈጣሪ

እግዚአብሔር በይሁዳ የታወቅህ
ድንኳንህ በሳሌም ማደሪያህ በጽዮን
አንተ ብርሃን ተላብሰህ ደምቀህ
ግርማዊነትህ ከዘለዓለም ተራሮች ሁሉ ይልቃል

ልበ ሙሉ የሆኑት ሁሉ አለቁ
ከተግጻጽህ የተነሳ ፈረስና ፈረሰኛው
ጭልጥ ድብን ብለው ተኙ
የያዕቆብ አምላክ ሆይ
በአንተ ፊት ማንስ መቆም ይችላል (2x)

መፈራት ያለብህ አንተ ብቻ
መወደስ ያለብህ አንተ ብቻ
እልሃለው ዛሬም እኔም ቆሜ
አንተው በሰጠኸኝ ዘመንና ቅኔ

ልዑል ሆይ ማደሪያህ ይባረክ
ቅዱስ ሥምህ ይባረክ
ልዑል ሆይ ማደሪያህ ይባረክ (4x)

ከኃያላኑ በፊት ኃያል
ከብርቱዎቹ በፊት ብርቱ የነበርህ
አንተ ነህ የምትኖር
አንተ ነህ ፈጣሪያቸው
አንተ ነህ ገዢያቸው
አንተ ነህ እግዚአብሔር
አንተ ነህ አንተ ነህ

እነዚያ ዘመናቸው አልቆ ተራቱ
እንደ ቀልድ አባሩ አለፉ ተረሱ
ሲራቡ ሌላን ነገር ማየት
ባሉበት መዘግየት ከመሞት መሰንበት

አልቻሉም አልቻሉም
አለመሞት አልቻሉም
ነገን ማየት አልቻሉም
አልቻሉም አልቻሉም

ዝቅ ብዬ ሳይ ከአፈሩ
አልኩኝ አወይ አቤት አቤት
ስንት ጀግና ስንት ጐበዝ
ስንት አይደፈር ኖሯል በታች
ከምረግጠው መሬት

አሻቅቤ ሳይ ወደላይ ወደላይኛው ሠማዪ
አየሁ የዘምን ልክ የዘምን ቁጥር
የዘመኑ ባለቤት የቁጥሩም ባለቤት
የሁሉን በላይ ሞትን የማይ

መወደስ ያለበት እርሱ ብቻ
መመለክ ያለበት እርሱ ብቻ
እልሃለው እኔም ዛሬም እኔም ቆሜ
አንተው በሰጠኸኝ ዘመንና ቅኔ

ልዑል ሆይ ማደሪያህ ይባረክ
ቅዱስ ሥምህ ይባረክ
ማደሪያህ ይባረክ
ልዑል ሆይ ተባረክ

ዘለዓለምም ቢሆን የእርሱ ልክ አይደለም
መች በዚህ ይለካል የሠማይ የምድሩ የሁሉ ፈጣሪ
ኧረ እርሱ እንዲህ ነው ዘለዓለምን ፈጥሮ ወዶ በፈቃዱ
ዘለዓለምን ዘለዓለም ያኖረዋል እንጂ
ጭራሽ አይለካም እግዜሩ ክብሩ አይመዘንም
ክብሩ ለብቻው ነው ዝናው ለብቻው ነው

እስኪ አለኝ ይበለኝ አንድ ሥጋ ለባሽ
እንደ እግዚአብሔር ያለ እስኪ የትኛው ነው
የዘለዓለም ነዋሪ የዘለዓለም ፈጣሪ
የሁሉ በላይ ሞትን የማያዪ

መወደስ ያለበት እርሱ ብቻ
መከበር ያለበት እርሱ ብቻ
እልሃለው እኔም ዛሬም እኔም ቆሜ
አንተው በሰጠኸኝ ዘመንና ቅኔ

ልዑል ሆይ ማደሪያህ ይባረክ
ቅዱስ ሥምህ ይባረክ
ልዑል ሆይ ተባረክ (2x)

@gitim_alem
@gitim_alem


Track Title ፦ 02 የዘላለም ፈጣሪ
Volume(ቁጥር)፦ 2
Album Title፦ የዘላለም ፈጣሪ
Singer Name ፦ሃና ተክሌ

@gitim_alem
@gitim_alem


ከእንቅልፍ የምትነሡበት ሰዓት አሁን እንደ ደረሰ ዘመኑን እወቁ፤ ካመንንበት ጊዜ ይልቅ መዳናችን ዛሬ ወደ እኛ ቀርቦአልና።
      ሮሜ 13:11

ጊዜው ደርሷል ንቁ...


  ትንሹም ትልቁም ሴትም ሆነ ወንዱ
  በውነት ልንገራችሁ ሳይመጣብን ፍርዱ
  እባካችሁ ሰዋች ሳትባክን ደቂቃ
  ከጣኦቶች ሸሽተን ለወንጌል እንንቃ
  ጣኦት የሆነብን ምንድነው ካላችሁ
  እኔ አለው ምሳሌ እኔ ልንገራችሁ
  ከጌታ ያራቀኝ ከቤቱ ሚያስቀረኝ
  ቅዱስ መጽሐፉን እንዳላይ ያረገኝ
  እረ እንዳውም ተውት ጊዜዬን የቀማኝ
ይህ ነው ጣኦቴ በጄ ያለው ስልኬ
ጊዜዬን የቀማኝ በልጦብኝ ከአምላኬ
ጣኦታችሁ ማነው እህቴ ወንድሜ
እራሳችሁ እዩት ጥያቄ ነው የኔ
ብዙ ነገር አለ ጣኦት ካልንማ
ግን ምን ዋጋ አለው ሒወት አይሆንማ
በቶሎ እንንቃ ሳንል ውዴ ጓዴ
ጣኦት የሆነብንን እንጣለው ዛሬ
ምክንያቱም ብትሉኝ ብትጠይቁኝማ
ጌታ በደጅ ነው ይመጣል አባባ
  እሱን እያወቅን እሱን እያሰብን
  የተኛን እንንቃ ጠላታችን ይፈር
  አይጠቅምም አይረባም ብለን ጣኦታችን
  ካንቀላፋንበት እንንቃ ሁላችን
  ጊዜ እየበረረ ሳይታጠፍ ክንፉ      
   እኛ  በቁማችን ምንድነው እንቅልፉ
   ወንድማለም ንቃ እህታለም ንቂ
   እንቺ ተሰናድተሽ ትውልድሽን አንቂ
   የአለም ነገር ይብቃ ጣኦት ማምለክ ይብቃ
   አንተ ተሰናድተህ ትውልድህን አንቃ

✍️በ ብላቴናው ታዴ

ተወዳችኋል🥰

---------------------------------------------------------
SHARE
| @GITIM_ALEM |
| @GITIM_ALEM |
--------------------------------------------------------
SHARE
   Contact me  @abu_ND8


ወደ ቦታውም ሲደርሱ ፊታውራሪ ዶግሶም ገና መድረሳቸውም ነበረና (አባባ ዋንዳሮ ጢሙን ተላጭቶ በሆድና በጀርባው አርባ አርባ እንዲገረፍ ወስነው ነበር) ፊታውራሪውም በሉ ያንን ደበኛ ያዙት ብለው ወደ ዋንዳሮ በርቀት እያመላከቱ ሳለ ይቀመጡበት ዘንድ ባርጩማ አቀረቡላቸውና ወፍረምም ሰው ስለነበሩ ገና ከወገባቸው ዝቅ ሲያደርጉ ሆዳቸው ፈንድቶ አንጀታቸው ተዘርግፎ እዚያው ሞቱ። እቀጣለሁ ያለው በእግዚአብሔር እጅ ተቀጣ። አባባ ዋንዳሮን ሊያስገርፉት የቆሙ ፊታውራሪ ዶግሶ የራሳቸው ቀብር ተፈጸመ።

በጣሊያን ወረራ ወቅት ከወንጌል ስብከት ጋር በተያያዘ ከወላይታ አከባቢ ከተለቃቀሙ ወንጌላዊያን ጋር አባባ ዋንዳሮም በሶዶ ሸክላ ወኅኒ ቤት ታስረው ነበር ።በዛም ቦታ ሁሉም በአንድ ቦታ መሰብሰባቸው ለጋራ መዝሙርና ጸሎት ተመቻቸው። አባባ ዋንዳሮንም ይኼን ሁሉ የሚታደርገው አንተ ነህ ብለው ለይተው ጢማቸውን እየነጩት አርፌህ ትቀመጣለህ ወይስ ትገደላለህ? ይሉት ነበር ።
አባባ ዋንዳሮም ስቃያቸው በበዛበት ደቂቃ ላይ ያመንሁበት ጌታዬ ኢየሱስ አሁን ይመጣልኛል ብለው ሲያበቁ ፍም የሚመስል እሳት ከሰማይ እየታየ መጥቶ በወህኒ ቤት አናት ላይ ወረደ። በዚያው ላይ ሀይለኛ አውሎ ነፋስን ተቀላቅሎ ይመጣበትና የሸክላው ወህኒ ቤት በእሳት ተቀጣጠለ። ድብልቅልቅ ወጥቶ መነዋወጥ ሆነና የዚህ ሰውዬ ጦስ ያስፈጀናልኮ ብለው ፈተው ለቀቁት።

አንድ ቅዳሜም ከታላቅ ሴት ልጃቸው(ሞልሴ) ጋር በአንድ ቤተክርስቲያን የጌታ እራትን ለመስጠት ሲሄዱ መንገድ ላይ መሸባቸው፤ ነገር ግን የግድ እዛው ቤተክርስቲያን ደርሰው ለነገው የጌታ እራት መጸለይ ነበረባቸው። በመሃል ግን በጨለማው እየተረመዱ ከሁለት እግረቸው መሃል መብራት በራና መንገዱን ያሳያቸው ጀመረ ። እየሄዱ እያሉም ሽፍታዎች ከፊት ለፊታቸው ሲመጡ ከመንገዱ ገሸሽ ብለው ወደ ዛፍ ውስጥ ገቡ ያንጊዜ መብራቱ ጠፋ፤ ሽፍታዎቹ ካለፉ በኋላ መንገዳቸውን ሲቀጥሉ መብራቱ እንደገና በራ እና እስከ ቤተክርስቲያን ግቢ ድረስም ሸኛቸው።
አባባ ዋንዳሮ በብዙ ፕሮግራሞች ላይ ደም እየፈሰሰባቸው ያገለገሉ እንደነበር ታርካቸው ያወራል።
ዕብራውያን 12 (Hebrews)
1-2፤ እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና።

ይህ የወንጌል አርበኛው የአባባ ወንዳሮ ታርክ ነው

ተወዳችኋል🥰

---------------------------------------------------------
SHARE
| @GITIM_ALEM |
| @GITIM_ALEM |
--------------------------------------------------------
SHARE
   Contact me  @abu_ND8


የወንጌል አርበኛው አባባ ዋንዳሮ

ወንጌላዊ ዋንዳሮ ዳባሮ (አባባ ዋንዳሮንታ) ....
ስለ አባባ ዋንዳሮ ታሪክ ከብዙ በጥቅቱ ለማስፈር ሞክርያለሁና ብታነቡትት የወንጌል ሀይል የመንፈስ ቅዱስ እሳት ያገኛችኃል ።
አባባ ዋንዳሮ ከወላይታ ሶዶ ወደ ደቡብ አቅጣጫ 20km ርቀት ያላት ሁምቦ በሚትባል ወረዳ በ1906 ዓ.ም ተወደዋል ።

እንደ አባቱም ጭሰኛ ገበሬ እና ሽማኔ ሥራን ይሰራ ነበር ።
በወጣትነቱም ለሐይማኖታዊ ነገሮች ንቁ ስለነበር ከ 1915-1920 ዓ.ም ደረስም "የነብዩን" እሳ ላሌን ትምህርት ለመተግበር ይሞክር ነበር ። የ"ነብዩም" ትምህርትም "ለሰይጣን የሚያደርጉትን አምልኮ ትተው ለእውነተኛው አምላክ አምልኮን ቢያቀርቡ በደስታ እና ተድላ እርስ በርስ እንደሚኖሩ ያስተምር ነበር።"
ይኼንንም ትምህርት አባባ ዋንዳሮ በልቡ "ለእንጨት ማምለክ እና እንስሳትን መሰዋዕት ማቅረብ ለሰይጣን ስለሆነ መተው አለብኝ" ብሎ አሰበ ።
አንድ ቀን አባባ ዋንዳሮ ወደ ሁምቦ ሲመለስ በግፍ ፊታውራሪ ዶግሶ በሬውን ቀምቶ ነበር ፤ ስለ በሬውም ፊታውራሪውን በሁምቦ ፍርድ ቤት ከሶ'ት ነበርና ነገር ግን ፍትሕ በዛም ተጣመመና አባባ ዋንዳሮም እንዲህም አሉ " እኔ ወደ እግዚአብሔር ብቻ አለቅሳለሁ እኔስ ምንም ማድረግ አልችልም።" ብሎ ተወው። በኋላም ደጀዝማች መኮንን በ1932 ለወላይታ ተሾመ ። አባባ ዋንዳሮም ከአባ ጮራሞም ደጃዝማች መኮንን በእውነት እንደሚፈርድ ሰማ ፤ ከፊታውራሪ በቀለም አረጋገጠ ፤ ነገር ግን አባባ ዋንዶሮ ወደ ሶዶ ሲመጣ ደጃዝማች መኮንን ለአማራ ጦርነት ዘምቶ ነበርና በቦታው ማንም አልነበረም ። አባባ ዋንዳሮ በሐዘኔታ ለእረፍት ወደ ቤታቸው ተመለሱ ።

አባባ ዋንዳሮም ያለውን ብቸኛ ንብረቱን ከማጣቱ የተነሳ ለእርዳታ በኦቶና ያሉ ሚሽኔሪዎችን ፈለገ እና ወዳሉበት ሄደ ፤ ሄዶም ቀያይ ፊቶችንም አይቶ " በርግጥም በነዚህ ሰዎች ውስጥ እግዚአብሔር አለ ፍትህም ይኖራል" አለ ።
አባባ ዋንዳሮም ከጥቅት ሳምንታትን በኋላ እንደገና ተመልሶ ከሁምቦ ወደ ሚኔሪዎች ጣቢያ መጣ ፤ በዛም ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ጠያቃቸው በወቅቱ እነዚህ የአሜሪካ ሚሽኔሪዎች አላማ እርዳታ ብቻ ሳይሆን ወንጌልን ለፍጥረታት መስበክ ነበርና አንድ ጠይቆ የሚሰማ ሰው ማግኘታቸው ደስም አላቸው ። Earl Lewis የሚባል ሚሽኔሪ የወላይታን ባሕላዊ የደም መሰዋዕት ባሕልን በደንብ ስለሚያውቅ "ኢየሱስ ብቻ የዓለምን ኃጢአት የሚያስወግድ የእግዚአብሔር በግ" መሆኑንና ይህ ኢየሱስ ከዚህ ጭንቀት መከራ ሲቃይ እርግማን ጭንጋፋ በነፃ እንደሚያድን በደንብ አድርጎ መሰከረለት አባባ ዋንዳሮም ለሶስተኛ ጊዜ ወንጌልን ስለሚሰማ አመነበት ።

በቀጣይ ሳምንት እሁድ ግን አባባ ዋንዳሮ ወደ ሚሽኔሪዎች ጣቢያ ሲመጣ ከ20 የሚበልጡ ሰዎችን ይዞ መጣ ፤ (ያኔ ኢየሱስ ክርስቶስን አምኖ ወደ ሁምቦ ሲመለስ የ2:00 ሰዓት መንገድ ወንጌልን ስመሰክር 3 ቀን ነበር የፈጀበት ) በጭንጋፋ እና በረሃብ በስቃይና በርግማን የሚሰቃዩ የተገለሉ ወገኖች ልክ እንደሱ በደል የደረሰባቸው ይህንን የሚያሳርፍ ኢየሱስን ለመቀበልና በሱ ምክንያት የሚመጣውን መከራ ለመጋፈጥ ምንም አላመነቱም ።
በጨንቻ ከተማ ያለችሁ የSIM nurse የነበረችሁ ሩት ብረይ እንደ አዲስ በተከፈተው ክሊኒክ ስለኢየሱስ ስትመሰክር ሰዎቹ " ይኼን ሁሉ እኛ እዛ በሁምቦ ገበያ ሰምተናል " ይሏት ነበር፤ ለካ እዛ በገበያ ቦታ የሰበከው አባባ ዋንዳሮ ነበር ። ከጥቅት ወራትም በ ኋላ በኦቶና [ ኦቶና ማለት ሚሽኔሪዎች በወቅቱ ለህክምና እና ለወንጌል አገልግሎት የመሰረቱት ትልቁ ሆስፕታል ነው ከሁሉም ኢትዮጵያ ሰዎች ይጎርፉ ነበር ] በሚደረገው ስብሰባ ከመቶ በላይ ሰዎች እንደተሳተፉ የወቅቱ የSIM ዳይረክተር የሆኑት ዶክተር ቶማስ ላ ምቤ መስክረዋል ።

አባባ ዋንዳሮ በሁምቦ የመኖርያ ቀበሌአቸው የሠሩትን የፕሮቴስታንት ተከታዮች ጎጆ የጸሎት ቤት ከኢትዮጵያ መንግሥታዊና ከኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ጥንታዊ ሐይማኖት ውጭ የሆነውን የሚቃረነውን አዲሰን መጤ እና ጴንጤ እምነት ተከታዮች ጸሎት ቤት ነው የሚባለውን አሠርተዋል ።
ይህንንም እምነት አጋግሎ እያራመደ ነው፤ አባሎቻችንን ሰብኮ ከአንገታቸው ክር እያስበጠሰ አጥምቆ ወደ መጤና ጴንጤ ሃይማኖት እያስገባብን ነው በተዋሕዶ ሐይማኖታችን ላይም ደባ እየፈጸመ ነው፤ ይህ ደበኛ ይቀጣልን፤ ጸሎት ቤት ነው ብሎ የሰራውንም ያፍርስልን ሲሉ በጊዜው በሙሉ ሥልጣን ለነበሩት ፊታውራሪ መጠሎ ዶግሶ አመለከቱ።
ፊታውራሪ ዶግሶም አባባ ዋንዳሮን አስጠርተው አንተና ጭፍሮችህ የምታደርጉትን ደባ ሰምችያለሁ። ከጭፍሮችህ ጋር አብረህ በቤተክርስቲያንነት የሰራኸውን ጎጆ ቤተን በአስቸኳይ አሁኑኑ ጭፍሮችህን ሰብስበህ አፍርሱትና ያፈረሳችሁትን ይዛችሁ ሶዶ ወስዳችሁ ለኦርቶዶክሱ የግዮርጊስ ቤተክርስቲያን የዙርያ አጥር ሥራ እዚያ ለሚገኙት ቀሳውስት አስረክቡ ብለው አዘዙአቸው።
አባባ ዋንዳሮም "እሽ የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሁን" ብለው የጸሎት ቤቱን አፍርሰው የቤተክርስቲያኒቱ አባላት ሁሉም ራሳቸው ተሸክመው የሚገርም መዝሙር እየዘመሩ ("ኢ ያና! ዛሩዋካ ኢማና"= እሱ[ኢየሱስ] ይመጣል መልስንም ይሰጣል) የሚለውን መዝሙር እየዘመሩ ከሁምቦ ዶግሶ ወንገላ ከሚባለው ቦታ እስከ ሶዶ ኦርቶዶክስ ግዮርጊስ ቤተክርስቲያን ድረስ ወስደው ለቀሳውስቱ አስረክበው ተመለሱ በደስታ አሁን እየዘመሩ እየፀለዩ እየመሰከሩ ተመለሱ ።

ከዚያም በኋላ አማኞች በግለሰብ ቤት እና በየእንጨት ጥላ ሥር እየተደበቁ እግዚአብሔርን ያመልኩ ነበር። ይኼንንም አቶ ጠቀሮ የተባለ ሰው ለፊታውራሪው ጠቆመ። ፊታውራሪውም አባባ ዋንዳሮን የመጨረሻ ከፍተኛ ቅጣት ለመቅጣት ለአርብ ቀጠረ። ይኼም ቀጠሮ ለአባባ ዋንዳሮ ደረሰው፤ አባባ ዋንዳሮም እንዲህ አሉ ለመልዕክተኛው"ከአርብና ከዶግሶ መኻል እግዚአብሔር አለ!"
አርበም ሲደርስ አባባ ዋንዳሮ በቀጠሮ ቦታ ለመገኘት ስወጡ ብዙ አማኞችም ተከተሉት፤ አባባ ዋንዳሮም አማኞችን እንዲህ አላቸው"የጌታዬን የኢየሱስን አካል ከመቃብር ያስነሳውን ያንን ታላቅ ኃይል ተጠራጥራችሁ ነው ልትከተሉኝ የመጣችሁት?" አሏቸው።( አማኞቹም ምናልባት በሞት ከተቀጣ አስክሬናቸውን ለማምጣት ነው ተመካክረው ነው የተከተሉአቸው።)አማኞችም "አንጠራጠረውም" ብለው መለሱለት።
አባባ ዋንዳሮም "ኢ ያና " "ዶግሶ ከምድር ሲመጣ አምላኬ ከላይ በአየር ቀድሞት ይደርስልኛል" እያሉ ጉዟቸውን ቀጠሉ።


ተከታታይ መንፈሳዊ ልብወለድ

#ሁለት_ሰይፍ
ክፍል ሶስት (ሜርሲ✍️)


"ኦውው... የአቤነዘር ጓደኛ...ማታ መልእክት ልኮልኝ ነበር እመልሰዋለሁ እያልኩ ተዘናጋሁ::"
"ያ.. አብሮኝ እንዳይመጣ ፕሮግራም ገጠመው::አቅጣጫውን እያጠያየኩ ነበር የደረስኩት::"
"ኦውው.. አስለፋሁህ ይቅርታ::የሚከራየው ቤት ከዚህ ቤት ሶስተኛ ላይ ያለው ነበር::እምም... ቀደም ብትል ጥሩ ነበር::አንድ ሶስት ቀን አለፈው ሰው ከገባባት::"
"እርሊይ..."
"ይቅርታ በጣም::"
ዮሃና መጥታ ከአጠገቧ ትቆማለች::
"እንዴ ናቲ..."
ዞራ አየቻት:-
"ታውቂዋለሽ::"
"እኛ ቸርች ሆኖ እሱን የማያውቀው አለ::ልክ እኛ እዛ ቸርች እንኳን ደህና መጣችሁ የተባለን ቀን ነው እርሱ የተሸኘው::የወጣቶች መሪ ነበር::አንቺ አልነበርሽም ነበር::"
"ኦውው... አንድ ቀን አይተሽኝ ነው ያልረሳሽኝ::"
"መርሳት የማልፈልገውን ሰው አልረሳም::ምን እግርህ ጣለህ እኛ ቤት?"
"እምም... የሚከራይ ቤት አለ ተብዬ ነበር::ተከራይቷል::"
"ኦውው... ብቻህን አንድ ግቢ ነው የምትፈልገው ማለት ነው?"
"አይ እንደዛ እንኳ ሳይሆን.. ሥራዬን ከቤት ሆኘ ስለሆነ የምሰራው..."
"ገባኝ::ግን እዚህ ማንም ነፃነትህን የሚነሳ የለም::ግራውንድ ላይ ከተመቸህ ክፍሎች አሉ::እኛ አንጠቀምበትም::"
"ዮሂ..."
"እህቴ ደግሞ::ለሚታመን ሰው ነው የማከራየው ስትይ አልነበር::"
"አይ... ፍቃድሽ ካልሆነ ችግር የለውም ሌላ ቦታ እከራያለሁ::"
"አይ እንደዛ ሳይሆን::ልንረብሽህ እንችላለን ብዬ ነው::"
"እነማናቸው የሚረብሹት?.. አረ እህቴ... ይሀውልህ ናቲአታስብ::አንድ አንዴ እኔ ብረብሽህ ነው... እባክህን ክፍሉን ልታየው ትችላለህ?..."

*                          *                           *

"ዕቃ ከመግዛት ነው የተረፍኩት::ሙሉ ዕቃ የተሟላለት ቤት ነው::ሳሎን መኝታ ሻወር አለው ሌላ ምን እፈልጋለሁ::"
"አይ ጥሩ አድርገሃል::እዛ መግባትህ የእግዚአብሔር ፍቃድ ይሆናል::አሁን እንዴት እንደምታሳምናቸው አስብ::"
"እምም... እሱም አለ ለካ... አይፈቅዱልኝም በእርግጥ::አሳውቅሃለሁ ለማንኛውም::"
"እንደዋወል.." ስልኩን ከዘጋ በኋላ ወደ ጎን አይኑን ከትራፊኩ ላይ ይጥላል::የፈራው አልቀረም የፊሺካ ድምፅ ይሰማል::
"ፈጣሪዬ... ናቲ መንጃ ፍቃድ ይዣለሁ በለኝ::"መኪናውን ከዳር አቁሞ ሊፈልግ ዝቅ ይላል::

*                            *                            *

"በዛ ላይ ቆንጆ ነው..."
"ምን አልሽ!?"
"ቀልዴን ነው አረ::"እጇን ከፍ እያደረገች::
"ለቀልድም ቢሆን..."
"አረ አምላኬ መች ነው እንደዚህ አንባገነን የሆንሽው::"
"ዶክተሩ ያለውን በደምብ ሰምተሻል::በፍፁም መጠጥ አጠገብ መድረስ የለብሽም::ጨጓራሽ በጣም ተጎድቷል::"
"እሺ... እሞክራለሁ::"
"እሞክራለሁ አይደለም ታደርጊዋለሽ!" ትላለች ድምፁአን ከፍ አድርጋ::
"እህቴ እየጮህሽ ነው::"
"ልጩህ::ጮኬም በገባሽ::"
"እህቴ ከአይንሽ እንባ እየፈሰሰ ነው እያለቀስሽ ነው?"
ፊቷን ወደ አስፓልቱ አድርጋ በእጇ እንባዋን ትጠርጋለች::
"መች ነው እራስሽን መበቀል የምታቆሚው?... ቆይ እንዳጣሽ ትፈልጊያለሽ?... እናታችን እጄን ይዛ ነው ቃል ያስገባችኝ::"
"እህቴ.. ይቅርታ::" ስታቅፋት ሳራም ታቅፋታለች::
ድምፅ ሰምታ ዘወር ስትል ማክቤል ከመኪናው ውጭ ሆኖ መስታወቱን እያንኳኳ አይታ ፈገግ ትላለች::
"ማክ... " ዮሀና ዘወር ብላ ታየው እና ትስቃለች::
"በሩን ክፈቺለት::" ከኋላ ሲገባ ቦርሳውን አስቀምጦ በየተራ ይስማቸዋል::
"ክላስ ቆንጆ ነበር ማክ.."
"አዎ... ተሻለሽ አንቺ?"
"አንተም ሰምተህ ነበር!?"
"ባትሄጂ ማታ ጥሩ እራት ትበይ ነበር::አያምሽም ነበር::"
"የእኔ ነብስ::ሁለተኛ አልሄድም ጥያችሁ::አሁን ቤት ሄደን ቆንጆ እራት እንሰራለን::"
"እንዴ... ዛሬ ፒዛ አልጋበዝም?"
"ትጋበዛለህ አረ... እሱ ግን መክሰስ ነው::እራት እኔ ነኝ ቆንጆ አድርጌ የምሰራው::"
"ምን... እራት ላይ እንቁላል ልታበይን?"አለች ሳራ::
"እየተሰደብኩ ነው!?"
ማክቤል እና ሳራ ተያይተው ይሳሳቃሉ::

*                         *                                *

ናትናኤል ከእናቱ ሕይወት እና አባቱ ኪሮስ ጋር እራት በአንድ ጠረጴዛ እየተመገበ በየመሃሉ ቀና እያለ ይመለከታቸዋል::
ኪሮስ አስተውሎት ኖሮ ከወንበሩ ደገፍ ብሎ ይመለከተዋል::
"የሆነ ነገር ልትነግረን ፈልገሃል አይደል?"
ደንገጥ ብሎ ቀና ብሎ ይመለከተዋል::ሕይወትም መመገቧን አቁማ ታየዋለች::ከዚህ በላይ እንደማያስኬደው ስላወቀ ለመናገር ይወስናል::
"ምን መሰላችሁ አባዬ.... አድጌባችሁ አይደለም::እናንተ ላይ ማደግ አልፈልግም::ይሄን ስወስን ሁለት ዓመት እርቄያችሁ ቆይቼ እንደገና ልርቃችሁ ፈልጌ ሳይሆን...."
"ናቲ... ምንድነው ዋናው ጉዳይ?" አለ ኪሮስ ቆጣ እንዳለ::
"ቤት ተከራይቻለሁ::" ፊታቸው ሲለዋወጥ አስተዋለ::

   Like🥰 Comment📩 Share💫
ቀጣዩ  እንድለቀቅ

ይቀጥላል...

ግጥሜን  ለኢየሱስ
   💙እወዳችኋለሁ 💙
---------------------------------------------------------
SHARE
| @GITIM_ALEM |
| @GITIM_ALEM |
--------------------------------------------------------
SHARE
   Contact me  @abu_ND8


ያዕቆብ 4 ፥14፤ ሕይወታችሁ ምንድር ነው? ጥቂት ጊዜ ታይቶ ኋላ እንደሚጠፋ እንፍዋለት ናችሁና።

20 last posts shown.