የፍቅር ታሪክ 🇪🇹


Channel's geo and language: Ethiopia, Amharic
Category: not specified


🌹የተለያዩ ታሪካችን ያገኛሉ 🌹

➴ ለአስተያየት➴ @Rominya_1
Since 2011 E.C.

Related channels  |  Similar channels

Channel's geo and language
Ethiopia, Amharic
Category
not specified
Statistics
Posts filter


♥️ ፅናት ♥️...!!!
           .
           .
           .
🥀..ክፍል 7..🥀
          .
          .
          .
እንዳፈቅር አፍቅሬም እንድሰጥ የሰጠከኝን ልብ ለእሱ ሰጥቼዋለውና ይህን ሰው የኔ አርገው ካላረከው ልቤን መክረክ መልሰው ልቤ ፈጣሪውን ይሰማልና። ውዴ ይህን ካልሽ ኋላ ልጁ ያንቺ ታማኝ አፍቃሪ ካልሆነ ፈጣሪ ጠራርጎ ከልብሽ አውጥቶ ያንቺን እጣ ፋንታ በልብሽ ያሰፍራል። የሰፈረውም ሰው በፍቅርሽ እኩል ፍቅር ሰቶሽ ያስደስትሻል"
    
ፅናት አንብባ ስትጨረስ ሊላኛውን ገልፅ ገለጠችው ሊላኛው ገልፅ ላይ ወንድ ሆይ አደራ ሴት ልጅን አትጉዳ ሴት ማለት በአለም ላይ ትልቁን ስቃይ ፤ ትልቁን መከራ ፤ምጥን ተቋቁማ በህይወት እንድትኖር ያረገችክ  የመኖርክ ትርጉም ናት። ምጥ ሲይዛት የሰውነት ክፍሏ ያለምንም ማደንዘዣ ተፈልቅቆ እና ተላቆ በባሊ ሙሉ ደም ከሰውነቷ ፈሶ ተቀድቶ ሰውነቷ በላብ ተጠምቆ በሞት እና በህይወት መካከል ሆና  የወለደችህ ናትና።
     
ትንሽ ነገር ሰውነትህን ሲቆርጥክ ምን ያህል ህመም ነው የሚሰማክ? በጣም ትልቅ አደል? እና እሷ ግን በምጥ ሰአት ሰውነቷ ለሁለት ሲሰነጠቅ አንተን በህይወት ተሰቃይታ ካኖረችክ ሆዷ ለማውጣት ለምትጥረው ጥረትስ? ስቃይስ? በሌላ መልኩ ያገባካት ሚስትክ አንተን አባት ለማድረግ ተመሳሳይ ስቃይ ነው ምትሰቃዬው አዳሜ ሄዋኔንን አትጉዳ" ይላል።
    
ፅናት አለቀሰች ስቅስቅ ብላ አለቀሰች በጣም አለቀስች አይኖቿ እንባን አዝለው መቆየት አልቻሉም እያነበበች ያለው ደብተር እና ፊቷ በእንባ እራሱ። ደብተሩን ከድና አስቀመጠችው። ነገር ግን ያዘነ ልቧን ከድና አለማዘን አልቻለችም። በህፃን አይምኖዋ ስንቱን አሰበችው!ሰው በኖረው ኑሮ እንጂ በኖረው እድሜ አስተሳሰቡ አይለካም።
     
ፅናት እሬሬሬሬ አለች አይታት ለማታውቀው እናቷ አለቀሰች። ተደፍታ ማንባት ጀመረች። እያለቀሰች ሊባኖስ መጣች። ፅናት ግን ልብ  አላለቻትም  ምክንያቱም ያኔ ለመጀመሪያ ጊዜ ስለ እናቷ አሟሟት  ስትሰማ የሰማቻቸው ቃላቶች በጆሮዋ እየተደጋገሙ ስለነበረ ነው።" አባትሽ ነው እናትሽን የገደላት!" የጎረቤታቸው ድምፅ "ፅናቴ አባታችን እናታችንን አንገቷ ላይ ቢላ ሰክቶ ነው የገደላት"። ፅናት እራሷን አጥብቃ በእጆቿ ያዘቻቸው።
      
ሊባኖስ ብትጠራትም ልሰማት አልቻለችም። ፅናት በእራሱዋ  አለም ውስጥ ያለ ሰው ሆናለች። ልክ እንደ ስሟ ፅናተኛ ብትሆንም ይህ ግን መቋቋም እጅግ ከበዳት ከተቀመጠችበት ተነስታ ቆመች። እጆቿ አሁንም ጭንቅላቷ ላይ ናቸው።ሊባኖስ ግራ ገባት "በደቂቃዎች ውስጥ ምን ሆና ነው?"ብላ ደነገጠች።  ሊባኖስ በድንጋጤ "ፅናት፤ ሚጢጢዋ ፤ደና ነሽ? ምነው ችግረ አለ?፤ እህትሽ ደና አደለችም  ፅናት መልስ አልስጠቻችም መንገዳገድ ጀመረች። ሊባኖስ ደገፈቻት። ፅናት ከዛን በኋላ እራሷን ሳተች ሊባኖስ እረዱኝኝኝኝኝ ብላ ጮከች።




  ፨የሊባኖስን ድምፅ የሰሙ ሁሉ ተሰበሰቡ ፅናትን ወደ ህክምና ክፍል ወሰዷት።
ሊባኖስ ደንግጣለች።"የፈጣሪ ያለ አሁን ደና አልነበረች እንዴ?" አለች ድምፅ አውጥታ ለእራስዋም አልገባትም ከዛም ወዲያውኑ "ለነገሩ ተረብሻ ነበር" አለች። ሊባኖስ  በራስዋ አለም ውስጥ ሆና ፅናትን ሊረዱዋት የሚረባረቡትን ሰዎች እረስታቸዋለች። አንድ ነርስ "ነይ እህቴ እዚህ ተቀመጪ እና ተረጋጊ ምኗ ነሽ?" አለቻት።

ሊባኖስ ምኔም ናት ማለት አልፈለገችም ፤ ግን ደሞ እህቴ ናትም ብላ መዋሸት አልፈለገች፤ ከዛም "እኔም ዛሬ ነው ያወኳት" አለች። ነርሷም "እሺ እንደዛ ከሆነ በቃ ተረጋጊ" አለችና ጥላት ሄደች። ሊባኖስ ደብተሯን ካስቀመጠችበት አግዳሚ ወንበር አምጥታ ገልፃ ከ ጉያዋ እራስ አውጥታ ለመፅፍ ጣቷቾን አዘጋጀች።

ደብተሩን ገለጠችው ስትገልጠው የፃፈችው ፅሁፋ ላይ የበሰበሰ ቦታ አየች የበሰበሰው ሉክ ከእስኪብረቶ ቀለም ጋር ሆኖ አንድ ፈዛዛ ነገር ሰረቷል። ሊባኖስ ይህንን ስታይ የፅናት እንባ ደብተሩን  እንዲህ እንዳረገው መገመት አልከበዳትም። "ይህቺ  ብላቴና ለምን በእዚህ ፅሁፋ አለቀስች? ለምንስ ነው ይህ ፅሁፍ የረበሻት?" አለች። ግን ይህንን ለማወቅ የግዴታ ፅናት ወደ እራስዋ እስክትመለስ መጠበቅ አለባት።
  
ሊባኖስ ስልኳን አውጥታ ደወለች።"ሄሎ" አለች። አንድ ሰው "አቤት" አላት። "በቃ እኔ ወደ ሰላማዊያን ልሄድ ነው" አለችው። "አሁን የት ነሽ?" ሲላት አሁንም "እዚሁ ነኝ ግን በቃ ልሄድ ደክሞኛል" አለችው።  ሰውየውም "አይ ሊባኖስ በቃ ስትረበሺ እና ማሰብ ስትፈልጊ እነሱ ጋረ ነው አደል የምትሄጂው?" አላት።
ሊባኖስም'' አዎ ልክ ነክ ዛሬ የሚመጣ ሰላማዊ  የለም?" አለች።  ሰውየውም "አለ ቦታ አለ እንዴ አንቺ ጋር" አላት። ሊባኖስም "አዎ 5 የተለቀቀ ቦታ አለ" አለችው። ሰውየውም "እሺ ጥሩ በቃ እዚህ 4 አሉ አመጣቸዋለው"። አለና ተሰናብቷት ስልኩን ዘጋው።ሊባኖስም ደብተሯን ይዛ ከሆስፒታሉ ውልቅ አለች።ወደ ሰላም የምታገኝበት ቦታ ሄደች...                                                  

   ከ 2 ወር ከ15 ቀናት በኋላ...

ሁሌም በእነዚህ የህክምና  ቀናት ውስጥ ፅናት ሲርባት የምታበላት ፤ሚስጥሯን ለምትነግራት ፤እና እራስዋን ያካፈለቻት ሴት ሊባኖስ ነበረች። ፅናት ለሊባኖስ ስለ እራስዋ እና ስላሉባት ችግሮች እንዲሁም ስለምትወዳት እህቷ ለምን ያንን ወረቀት ስታነብ እንደከፋት ሁሉንም ባለፉት ሀኪም ቤት በቆዩባቸው ጊዜ ነግራታለች።
    
ሊባኖስ ግን ለጭንቅላቷ ይከብዳታል በማለት ሙሉ ህይወቷን አላካፈለቻትም አልነገረቻትም ።
ሊባኖስ ለፅናት በህይወቷ ውስጥ የሚፈጠሩት  ነገሮች ሁሉ እሷ ምንም ያህል ብትታገል መሆናቸው እና መፈፀማቸው እንደማይቀር ብርታት ያለውን ቃል እየነገረቻት ውስጧ  እንዲቀረፅ አድርጋታለች። በተጨማሪም እራሷን  ስታ ከነቃች በኋላ በነጋታው መጥታ ብዙ ምክሮችን መክራት እና ከ ተሻላት በኋላ ሙሉ በሙሉ ትምርቷን እንድትማር ወላጅ በተባለ ቁጥረ እሷ እንደምትመጣላት አስረግጣ ነግራት ነበረ።  ያኔ ፅናትም መልሷ እሺ ነበር ምክንያቱም ፅናት ያኔ ለሊባኖስ በህይወቷ ስለተፈጠረው ነገር ስትነግራት ሊባኖስ ለፅናት  ብርታት ሆናታለች እንዲህ ነበረ ያለቻት "እየውልሽ ፅናትዬ እንዳልኩሽ ትምርትሽንም ቀጥይ በፍፁም ትምህርትሽን ማቋረጥ የለብሽም እህትሽ ደካማ መሆንሽን ብትሰማ በጭራሽ ደስ አይላትም ደስ የሚላት ጠንካራ ስትሆኚ  ነው እንጂ ደካማ ስትሆኚ አደለም እህትሽ በእሷ ምክያት ትምርትሽን እንዳቋረጥሽ ብታውቅ ይፀፅታታል" ነበረ ያለቻት።

ዛሬ ይህ ሁሉ አልፎ በፀሎት  ልትመጣ ነው። 2 ወር ከ15 ቀን ፅናት ትምህረት  ቤት ስትሄድ ሊባኖስ ሆስፒታል እህቷን እየተመላለሰች እየጠበቀችላት የ15ቀን ረፍቷ ሲያልቅ  ለ ወር ትምርቷን ሳታቋርጥ ቀጥላለች። ሊባኖስ ፅናት እንድታጠና እና የእሷን እና የእህቷን ህይወት ትልቅ ደረጃ ደርሳ እንድታሻሽል ብርታት ስለሆነቻት ትምህርቷን ጥሩ አድረጋ ይዛዋለች ። በፀሎትም ከህክምና ስትወጣ ከሊባኖስ ጋር ዶክተሩ አስተዋውቋታል "እህትሽ ጎን የነበረችው ሴት ናት"ብሎ።

ዛሬ የፌሽታ ቀን ነው በፀሎት ወደ ቤቷ ልትመጣ ነው ፅናትም ቤቱን በእሷ እና በቤቱ አቅም ፏፏ አድርጋዋለች። እህቷን ቤቷ እስክታያት በጣምምምምምም ጓጉታለች።
.
.
🥀..ክፍል 8 ቶሎ እዲለቀቅ አንብባቹ ስጨርሱ ላይክ ሼር አርጉ ..🥀
          .
          .


♥️ ፅናት ♥️...!!!
           .
           .
           .
🥀..ክፍል 6..🥀
          .
          .
          .
#Notice :- እውነተኛ ታሪክ ነው .!!
.
.

.
.
በደማቁ በእርሳስ በማያምር እና ምንጭርጭሩ በወጣ ፅሁፍ ወረድ ብሎ በተመሳሳይ ፅሁፍ...."ህይወት ብዙ አስመሳይ እና ከሀዲ እንዳሉዋት ግልፅ ነው። ሰው ሳያስመስል የሚኖረው ጥላቻን ፣ ውሸትን ፣ አጭበርባሪነትን፦ ብቻ ነው ጥቂት እውነተኛ ሰዎች አሉ። ግን እነሱን የምናገኛቸው አስመሳዮች ከጎዱን በኋላ ነው እኛም አናምናቸውም  ምክንያቱም አምነን ተጓድተናል እውነተኛ ሰዎችም ይከፋሉ  ምክንያቱም አስመሳዮች የሆነው ሆኖ ህይወት ቲያትር እኛ ደሞ ቲያትርኛ ነን ትወናችንን ስንጨርስ ደሞዛችንን ለመክፈል እንሄዳለን"። ፅናት ይህንን አንብባ ስትጨረስ ፈራችም ተፅናናችም ደብተሩን ልትገልፀው ስትል ከደረጃ የሚመጣ ኮቴ ሰማች ቋቋቋቋቋ ፅናት የያዘችውን ደብተር በድንጋጤ እና በፍጥነት ከደነችው።

፨የሰማችው የ ሊባኖስን ኮቴ ነበር። በፍጥነት ወደ እሷ ተጠግታ "ይህውልሽ ሻይ አምጥቼልሻለው ጠጪ" አለችና ሻይ የያዘውን እጇን ዘረጋችላት ፅናት እጇን በዝግታ ሰዳ ተቀበለቻት እና የሻዩን ብርጭቆ ጆሮ ይዛ ፈዛ ቀረች። ከመፈዘዟ ያነቃት የሊባኖስ "ጠጪ" የሚል ድምፅ ነበር።
 ፅናት "እሺ እሺ እጠጣለው" አለችና አንዴ ጎንጨት አረገች። ሊባኖስ ከለበሰችው ፎጣ ሸሽጋ የያዘችውን ፓስቲ(በዘይት የተጠበሰ ፍርኖ ዱቄት ብስኩት)  አውጥታ "እንኪ በሻዩ ብይ" አለቻት። ፅናት ፓስቲ በሻይ በጣምምም የምትወደው ምግብ ነው።  እሺ ብላ ተቀብላት ልትበላ ስትል ሊባኖስ ከፓስቲው ጋር የያዘችውን ዶቦ አውጥታ "እሱ ይደረቅብሻል በዳቦ ብይ ብዬ ነው ይህንን እኔ እበላዋለው" ብላ ከእጇ ወሰደችው።

ፅናት ዳቦ ጭራሽ የማትወደው ምግብ ነው በተለይ በሻይማ ጭራሽ አትበላም ሊባኖስን "ይህንን ምግብ ጭራሽ አልወደውም ፓስቲው ይሻለኛል" ማለትን ፈራች። እሺታዋን ገልፃ ከዳቦ በሻይ ጋር ውስጧ መታገል ጀመረ። ግባ አትግባ ፤ውጣ አትውጣ ሊባኖስ ሊባኖስን እያየች የግዷን እሩብ  ታክሏን በልታ ከዛ "በቃኝ" አለች። ሆዷ ቢርበውም ዳቦውን መብላት ግን አልቻለችም ፅናት ለመጨረሻ ጊዜ  ትናት ጠዋት ከ ትግስት ጋር ትግስት ማታ ማታ እያዞረች ከምትሸጠው የተረፈውን  ፓስቲ  በሻይ ነው።

ሊባኖስ ፅናትን አየት አድረጋ "ምነው ሚጢጢዋ? አልተመቸሽም እንዴ? አለቻት ። ፅናት በህይወቷ አንዴም ቢሆን አድረጋ ማታውቀው መዋሸትን ነውና በሚንቀጠቀጥ ድምፅ እጆቿን እያፋተገች "እእእ አአአ አዎ ዳቦ አልወድም" አለቻት። ሊባኖስ በግረምት እያየቻት "እና ለምን በላሽ?" አለቻት ቆጠት ብላ ፅናት በድጋሜ መዳፎቿን እያፋተገች በተቆራረጠ ድምፅ "ፈረቼሽ ነው" አለቻት። በሰቀቀን ቀና ብላ እያየቻት" ሊባኖስ የአግራሞት ፊት እያሳየች "ምን?እንዴት? ምኔ ያስፈራል? ምነው እንድትፈሪኝ ያረኩት ነገር አለ?" አለቻት። ፅናት አሁን የሊባኖስ ጥሩነት እየታያት የመጣ ይመስላል ፈገግ ብላ "አይ" አለች። ፍራቻዋ ለቀቅ ሲያረጋት እህቷ ትግስት ትዝ አለቻት። "ወይኔ እህቴ ብላ ብድግ" አለች። ሊባኖስ "አይዞሽ የት ናት ምን ሆና ነው እዚህ የገባችው?" አለቻት።ፅናት እየተርበተበተች የተፈጠረውን ሁሉ አንድም ሳታስቀረ   ለሊባኖስ  ነገረቻት።

ሊባኖስ ፅናት በነገረቻት የበፀሎት አወዳደቅ አዘነች። ፅናት አሳዘነቻት ውስጧ አቅፈሽ አፅናኛት አቅፈሽ አባብያት አላት። ከዛም ፅናትን በፍጥነት እና በቅልጥፍና ተጠመጠመችባት። ፅናት ደነገጠች ሊባኖስ ስታቅፋት ጠረኗ ይበልጥ ከ አፍንጮዋ ጋር ተገናኝቶ እንደጉድ ይሸታት ጀመር። ፅናት የሊባኖስ ጥሩነት እየታያት ቢመጣም ፍራቻዋ ግን ጭራሽ እየባሰባት መጥቶል። ሊባኖስ በድንገት ፅናትን ከእቅፏ አስወጥታ  ትክሻዋን ግጥም አርጋ በሁለት እጆቿ ያዘቻት። ከዛማ ወደ ፅናት ተጠጋች እና  አይን አይኗን ታያት ጀመረ። ፅናት አንገቷን ደፋች።

ሊባኖስ "ቀና በይና እኔን ፤ አይን አይኔን  እይኝ" አለቻት። ፅናት በሰቀቀን ቀና ብላ ሊባኖስን ማየት ጀመረች። ሊባኖስም ለፅናት "እኔ የምልሽን ሁሉ ትያለሽ ሰማሽኝ" አለቻት ፍጥጥ ብላ ። ፅናት በጉንጯ አዎታዋን ገለፀጭላት። በይ አይንሽን ጨፍኝ ስትላት ፅናት ደንግጣ "እ" አለቻት። "አልሰማሽኝም"? አለቻት። ፅናት "አይ ሰምቼሻለው እሺ ብላ አይኞቿን ከደነቻቸው  ከዛ ቃል በቃል እንዲህ አስባለቻት "እኔ ሁሌም የሚመጡብኝን ነገሮች ያለ ፍራቻ ያለ መደናገጥ ጠንክሬ አልፈዋለው። ፈጣሪ መቼም ቢሆን የማልችለውን ፈተና ሊጥለኝ አይሰጠኝም ውስጤ እና እምነቴ ጠንካራ ነው ፈጣሪ የመጥፎ ስሜቶች መሸጋገሪያ ድልድዬ ነው"።

ይንን አስብላት ስታበቃ "እሺ አሁን ውስጥሽን ምን ተሰማው?" አለቻት። ፅናት በረዥሙ ተንፍሳ "ነፃነት ሰላም እና ጥንካሬ" አለቻት። ሊባኖስም "በጣም በሳል ልጅ ነሽ በይ አሁን ተነሽና እህትሽ ስላለችበት የጤና ሁኔታ እንጠይቅ" አለችና የቀኝ እጇን ዘረጋችላት ፅናት አሁን ሊባኖስን ለምዳታለችና ፈገግ ብላ እጇን ያዘቻት እና ደግፋት እህቷን ቅድም ወዳስተኙበት ክፍል ሄዱ  በፀሎት ግንንንን የለችም።
ፅናት "እህቴ" አለችና ደነገጠች። ሊባኖስም "ተረጋጊ ሚጢጢዋ ኦፕራሲዮን ክፍል ነው ምትሆነው ኦፕራሲዮን ያረጓታል ብለሽኝ አደል እንዴ?" አለችና ጠቀሰቻት።ፅናት "ልክ ነሽ እሺ" አለቻት ከዛ እስቲ ነይ አረፍ በይ አለችና ወደ አንድ ብቸኛ ወንበረ ወሰደቻት። ፅናት በጣም የድካም እና የጭንቅ ስሜት እየተሰማት ነው ይህ የረሀብ እና የጭንቀቱ ምልክት ነው ሊባኖስም አውቀዋለች። "ስሚ ሚጢጢዋ አቅም አጥሮሻል እኮ ቆይ ምግብ ነገር ላምጣለሽ እዚሁ ጠብቂኝ እሺ ብላት" ሄደች።

ፅናት በጣም እርቧት ስለነበረ በፍጥነት ነው "እሺ ያለቻት። ከዛም ሊባኖስ እሮጥ እሮጥ ዱብ ዱብ እያለች ወደ ምግብ ቤቱ ሄደች። ሊባኖስ አሁንም ያንን ደብተረ ጥላው ነው የሄደችው ፅናት ሊባኖስ ከኮሊደሩ ወደ ደረጃው ስትወረድ ቀጣይ ገልፁን ለማንበብ ተጣደፈች።

እጇ በትንሹ ቢንቀጠቀጥም ከፈታ አየችው በጣም በትልልቅ ፅሁፍ ነው የተፅፈው ግን ይሄኛው የፊት ገልፁ ላይ እንደተጻፈው በሙንጭር ፅሁፍ አልተጻፈም ደብተሩን ብድግ አድረጋ ታፋዎቿ ላይ አስቀመጠችው እና አይኖቿን ወደ ደብተሩ ወረወረቻቸው።ፅሁፎቹ በጣም ተነባቢ ናቸው ነገር ግን አያምሩም ማንበብ ጀመረች።እንዲህ ይላል  ...

"ሄዋኔ የምነግርሽን አድምጪ በመጀመሪያ ሰው ተሰባሪ ነውና ሰውን ሳይሆን ዘላለማዊ የሆነውን አምላክሽን እመኚ።ለስላሳው  ልብሽን ለሸካራ ልብ ላለመስጠት የፈለግሽው አይነትን ሰው ከጎንሽ አድርገሽ ከእሱ ጋረ ትልቅ ህይወትን ለመመስረት እና ደስተኛ ለመሆን አምላክሽ ተማፃኝ ሁኚ ""

አቋምሽን ፣መልክሽን ፣አለባበስሽን በማየት የሚቀርብሽን አፍቃሪ ነኝ ባይ ሰው ቢመጣ ፈፅሞ ላለመሸወድ አሁንም ደግመሽ የፈጣሪሽ ለማኝ ሁኚ።  ውዴ እኛ ሴቶች ከወንዶች በተፈጥሮም በአስተሳሰብም እንበልጣለን ደካማ ጎናችን እምነታችን ነው። ክፉ ሲያጋጥመን ይቀየራል ማለታችን የሆነው ይሁን የቀረው ይቅር ያፈቀርሽውን ሳይሆን ያስፈቀረሽን ፈጣሪ እንዲ ብለሽ ለምኚው አምላኬ ይህ ሰው የልቤን መሻት የሚያሞላልኝ ሰው እንደሆነ ልቤ ምስክር ናት በሙሉ ልቤ እንጂ በሙሉ አይኔ አላየውትም።

.
.
🥀..ክፍል 7 ቶሎ እዲለቀቅ አንብባቹ ስጨርሱ ላይክ ሼር አርጉ ..🥀
          .
          .


♥️ ፅናት ♥️...!!!
.
.
🥀..ክፍል 5..🥀
.
.
ከ አልጋዋ እንድትነሳ እረድቷት ወደ እህቷ ወሰዳት።ደረጃውን እየወጡ ሳሉ ዶክተሩ  "እየውልሽ አንቺ በጣም ስለተጨነቅሽ ላሳይሽ ብዬ ነው እንጂ አይፈቀድም እህትሽን ከ ግማሽ ሰአት በኋላ ወደ ቀዶ ጥገና ክፍል እንወስዳታለን" አላት። ፅናት "ምን እህቴ አትሞትብኝም አደል? "አለችው። ዶክተሩ አዘነ ግን ፈገግ ብሎ "አታስቢ ምንም አትሆንም የህክምና ወጪዋንም የገፍታሪው ወላጆች ናቸው የሚችሉት" አላት። ፅናት እሺ ብቻ ብላው መሄድ ጀመረች ትንሽ ኮሊደሩን እንዳጋሙሱ ነይ እዚህ ነው አላት።
   
፨ክፍሉ ደረሱ በፀሎት  ያለችበት ፤ በፀሎት  የተኛችበት ፤በፀሎት የምታቃስትበት ክፍል  ዶክተሩ" ደረሰናል ይህኛው" ነው።  አላት ለፅናት እንድትገባ እየጠቆማት ፅናት ለመግባት ፈራች ክፍሉ ብትገባ የእሪሳ ሳጥን ውስጥ እህቷን የምታያት መሰላት። ውስጧ መግባትን ቢፈልግም እግሮቿ ግን ፍፅሞ አልቻሉም። ዶክተሩ ከትከሻዋ ገፋ ገደፍ አድጎ ሊያስገባት ሞከረ።

  ፨ ፅናት ግን  "አይ አይሆንም፤ በጭራሽ አይሆንም" አለች። ዶክተሩ ግራ ተጋባ "ምኑ" አላት።ፅናትም የዶክተሩን ሁለት እጆች ይዛ " እህቴ በህይወት አለች አደል?"፤ ምንም አልሆነችም አደል? "አለችው። ዶክተሩ "አዎ አታስቢ! ነይ ገብተሽ እያት" አላት። ፅናት እንደምንም እግሮቾን ጎትታ  ገባች።
    ፨ እህቷን ስታያት በጣም ደነገጠች። በደፈረሱ አይኖቿ ለእህቷ በድጋሜ፤ አለቀሰችላት ፤ አዘነችላትም። ዶክተሩ የፅናትን ፊት ሲያየው እሱም በጭራሽ ውስጡን አጀግኖ መቆየት አልቻለምና አለቀሰ እንባ አፈሰሰ። ፅናት ዶክተሩን አየችና "እንዴ  ለምን ታለቅሳለክ ስለማትድን ነው?" አለችና ዶክተሩ ፊት ላይ አፈጠጠች።

ዶክተሩ ውብ አይኖቿ አፈዝዘውት በአትኩሮት ያያት ጀመር።  ፅናት ግራ ገባት ዶክተሩ በመጨረሻ ወደ እራሱ ተመልሶ እራሱን ታዘበ በብላቴና እና በታናሽ ታናሹ አይን መማረኩን እሱንም አስገረሞታል። ደንገጥ ብሎ "አይ አይ እንደዛ አደለም አታስቢ ደና ትሆናለች" አለና ሁለት መዳፎቹን አይኖቹ ላይ አርጎ ሽቅብ አንገቱን አድረጎ "ኡፍፍፍፍፍ" አለ።
      ፨ፅናት ወደ እህቷ ተጠጋች መንካትም ፈራች እጇን ወደ በፀሎት ሰደደችው ግን መንካት አልቻለችም። እጆን መልሳ ፊቷን አዙራ በሩን ጓ አድርጋ ወጣች። ዶክተሩ ወደ በፀሎት ተጠጋ በፀሎት እግሯ ወደላይ በጅብሰን ታስሯል የወደቀችው የትምህርት ቤቱ መናፈሻ ሳር ላይ በመሆኑ እግሯን የፓርኩ አጥር ስለመታት እግሯ ተጎድቷል። ፊቷ ምንም አልሆነም ጭንቅላቷ ግን ተመቷል። ጭንቅላቷ ላይ የተጠመጠመው ፋሻ እንዳለ ሆኖ ፊቷ ግን ውብ ነው። ዶክተሩ "እነዚህ ልጆች ከምን ቢፈጠሩ ነው እንዲህ ውብ የሆኑት?" አለ ድምፅ አውጥቶ።
      ፨ከዛ ክፍሉን ለቆ ወጣ። ይህ ከሆነ ከግማሽ ሰአት በኋላ የሆስፒታሉ ዶክተር እና ነርሶች በፀሎትን ኣፕራሲዮን በማድረግ ላይ ናቸው። ፅናት ግን ተኝታለች ዶክተሩ። የእህቷ ኣፕራሲዮን ከ ግማሽ ሰአት በፊት እንደሆነ የነገራትን ዘንግታ ሳይሆን ሳታስበው ነው። የትግስት ኣፕራሲዮን ጊዜ 8 ሰአት የሚፈጅ በመሆኑ ግማሽ ሰአት ከፈጀ በኋላ ፅናት ከእንቅልፏ ባነነች ከ አልጋዋ ተነስታ ኮሊደሩን እየተደገፈች ፣ እየተጓዘች በድጋሜ እራሷን ስታ ወደቀች።
    
፨ያያት ሰው አልነበረም ከትንሽ ቆይታ በኋላ የአንድ ሴት ወደ ኮሊደሩ ስትመጣ አየቻት። ሴቲቷ አልጮከችም በቀስታ ወደ ፅናት ከሄደች በኋላ ፅናትን ተሸክማ አቅራቢዋ ወዳለው የአግዳሚ  መቀመጫ ወንበረ ላይ አስተኝታ  የፅናትን መንቃት መጠባበቅ ጀመረች። ፅናት ግማሽ ሰአት  አስቆጥራ ነቃች ስትነቃ የአንድ ሰው ታፋ ላይ ጋደም ብላለች። ቀስ ብላ ቀና ለማለት ስትሞክር አቅም አጥሮ አቃታት ። ሴቲቷ "ተኒ አዎ ተኒ መተኛት ፈረተሽ ነው አትፍሪ የአሁኑን መተኛት ከፈራሽ ለዘላለም መተኛትን እንዴት ልትቀበይው  ሚጢጢዋ" አለቻት ፀጉሯን እያሻሸች።
      ፨ ፅናት ደነገጠች ቀስ ብላ በድጋሜ ለመነሳት ስትሞክር ተሳካላትና ቀና አለች። ይህቺን ሴት ፅናት ታውቀዋለች  ይንን ፊት የት እንዳየችውም  በጭራሽ ልትዘነጋው አትችልም ይህቺን ሴት የምታውቃት የእናት እና የአባትዋን መቃብር ለማየት ከ እህቷ ጋረ ስትመጣ ሁሌም ባይሆን በብዛት ታያታለች። ሁሌም በእጆቿ አበባ ይዛ መቃብሮቹ ጋር ትበትናለች። ሽቶም ትነፋባቸዋለች ፅናት ይህቺን ሴት በጣም ትፈራታለች። ፊቷ ልክ እንደ ቆንጆ እንጀራ ምልክት አለው። ፀየም ያለች እና ፀጉሯን የተከረከመች ናት ሁሌም የምትለብሰው ልብስ ጥቁር ግን ፅዱ ነው ጠረኗ መቃብሮቹን የምትቀባው ሽቶ ነው። አቋሞ ቀጠን ያለች እና እጅና እግሮቿ እረጃጅም ናቸው።
       
  ፨ፅናት እና በፀሎት የሚፈሩት ሴት እሷን ሲያዩ ሞት ትዝ የሚላቸው ሁሌም ነው። ፅናት ፈራች የእህቷ በፀሎትን  የሞት መረዶ ልትነግራት የመጣች መሰላት። ከሴቲቱ ላይ ተፈጨረጭራ ተነስታ ወንበሩ ላይ ቁጭ ብላ አንገቷን ደፍች እጆቾን ቆላልፋ በታፋዎቾ መሀል አረገቻቸው ። ሴቲቱ እጆቿን ወደ ፅናት እጆች ሰዳ ከታፍዋ ፈልቅቃ ያዘቻቸው ፅናት ፈራች። ሴቲቱ የቀኝ እጃን ወደ ፅናት አገጭ ሰዳ ቀና ካረገቻት በኋላ "ምነው  ፈረተሽ ነው? አይዞሽ አትፍሪ! ያሰብሽውን እና ለእሱ የምትጨነቂለትን ሰው እንደማታጪ ተስፋ አደረጋለው" አለቻት።
   
    ፨ የሴቲቱ አይን ከ ፅናት አይኖች ጋር ተገጣጥመው ተፍጠጡ ፅናት አይኗን ስታየው ድንገት ደነገጠች ደርቃ ቀረች የልብ ምቷ ጨመረ ልቧ መታ እንደጉድ ድው ድው ድው ድውው። ሴቲቱ የፅናትን ድንጋጤ አስተውላለች "ምነው ለምን ደነገጥሽ?"  አለችና እጆን ከፅናት እጅ እና አገጭ አነሳች። ከዛም የቀኝ እጆን ወደ ፅናት ዘረግታ "እንተዋወቅ  ሚጢጢዋ ሊባኖስ እባላለው" አለቻት።

ፅናት የሊባኖስን እጅ በአይኗ አተኩራ አየቻቸው። "ያንቺ ስም ማነው?" አለቻት። ፅናት እረብትብት አለች። እጆቿን በቀስታ ወደ ሊባኖስ እጃች ወስዳ አጣመረቻቸው ከዛም የፅናት ትንፋሽ ተቆራረጠ "እኔ የእኔ የእኔ ስም ደሞ ፅፅፅፅፅፅፅናትትትትት ይባላል"። አለቻት ሊባኖስ "እሺ የተጨነቅሽ ትመስያለሽ ሚጢጢዋ ፅናት መጣው ውሀ ይዜልሽ" አለችና ሄደች።
    
  ፨ ሊባኖስ ከመቀመጫዋ ስትነሳ አንድ ደብተር ነበር። ሊባኖስ ከሄደች በኋላ ፅናት ጠጋ ብላ እጇእየተንቀጠቀጠ ደብተሩን አነሳችው። የደብተሩ የመጀመሪያ ገልፅ ላይ "በትልቁ ሞት ህይወት ነው! ህይወት ሞት ነው!?" ይላል


ይቀጥላል like. Share ቤተሰብ


♥️ ፅናት ♥️...!!!
.
.
🥀..ክፍል 4..🥀
.
.
፨ፅናት ከፍዘቷ ስትነቃ ጩከቷን አቀለጠችው ፤አለቀሰች ውስጧ በሀያሉ ታመመ። በአንድ ሲኮንዶች የተለያዩ አስቀያሚ ስሜቶችን  ውስጧ አስተናገደ "አንቺም ጥለሽኝ ልትሄጂ ነው በፀሎቴ፤ እህቴ አንቺም አንቺም አንቺም እንደ አባባ እና እማማ ጥለሽኝ ልትሄጂ ነው?፤ አይ አይሆንም እባክሽ" የሚሉ ቃላቶችን ከሲቃ ጋር አጓረፈቻቸው።
      ፨ የበፀሎት የጭንቅላት ደምም ለጉድ ጎረፈ አወይ ስቃይ! አወይ ሀዘን! በቃላት የማይገለፅ ሀዘን ፣የውስጥ ህመም ፣እረ ስንቱን በለጋ እድሜዋ አስተናገደች። አንፑላንስ መጣ፤ አንፑላንስ ጮከ ፤በፀሎትንን ይዘዋት በቃሪዛ ወደ ህክምና ጣቢያ ከነፉ ፅናትም እንድትገባ ባይፈቅዱላትም ታግላና አልቅሳ እንደምንም  ገባች።
   ፨ በስተመጨረሻ  ሆስፒታል ደረሱ ያኔ ፅናት ከመኪና ወረዳ የድረሱልኝ ጩከቷን ከ አንፖላንሱ ጋረ አቀለጠችው። ሆስፔታሉ በፅናት እና በአንፖላንሱ ድምፅ ታጀበ። ተጨማሪ ነረሶች መተው በፀሎትን ሆስፒታል አስገቧት ፅናት ውስጧ ተሸበረ ፈራች ውይይይ በቃ በጣም ጨነቃት። ምስኪኗ ትንሽየዋ ፅናት እራስዋን ሳተች።
    
  ፨ የነቃችው በነጋታው ጠዋት 1:30 ላይ ነበር። አይኗ ደብዘዝዝ አለባት ከዛም እይታዋ ተስተካከለ። 1:30 አለች። ስአቱን ያወቀችው ባለችበት ክፍል ውስጥ በተሰቀለ የግድግዳ ሰአት ነው።ስትነቃ መጀመሪያ የጠራችው የእህቷን ስም ነበር። "እህቴ በፂዬዬ፤ እህቴ በፀሎቴ " ሲቃ በተሞላበት  እና እንደ በረዶ በቀዘቀዘ ድምፅ ከዛ እንባ በድንቡሽብሽ እኛ በጥቂቱ ውረጭ በመታው ፊቷ ወረደ።
   
   ፨ያለችበት ክፍል በድንገት  ተከፍቶ አንድ ዶክተር እና ፖሊስ እህቷን ከገፈተራት ልጅ አባት ጋረ ገቡ። ፅናት ሰውየውን ስታየው ፊቷ ተቀያየረ እንባ እና ንዴት ተናነቃት አትችልም እንጂ ተነስታ ብታፈራረጠው እና የምትወዳትን እህቷን አስነስታ የገፈተራትን ልጅ እስከ አባቱ ከዛ ፎቅ ወረውራ ብትገላግላቸው ደስታዋ ነው። ፅናት የወረዋሪው ልጅ አባት ላይ አፈጠጠች። ፖሊሱ ወደ ፅናት ተጠግቶ የተፈጠረውን ነገር ለመናገር አሁን ዶክተሩ መልካም ጤንነት ላይ ናት ስላለ ቃልሽን ትስጫለሽ።" አላት።
      ፨ ፅናት አሁንም አይኗን ከ ወረዋሪው ወላጅ ላይ  አልነቀለችም የፓሊሱን ንግግረ ስምታ ይሆን?  ማንም አያውቅም አሁን አይኖን ዞርም ሳታረግ "ዶክተር እህቴ እንዴት ናት?" አለች። ዶክተሩ ፅናት የወረዋሪውን አባትን  እያየች እሱን መጠየቋ ግራ ቢያጋባውም "አታስቢ ደና ናት" አላት። ከዛም የገፍታሪው ልጅ አባት ሹክክ ብሎ ከ ክፍሉ ወጣ።
   
፨ዶክተሩ በፅናት ፊት ላይ የሚያየው እልህ እጅግ አስገረመው አስደነገጠውም ህፃንነቷን አይቶ ንግግሯን እና ሁኔታዋን ሲያይ ገረመው።ፓሊሉ ፅናት እንድትነሳ ክንዷን በመያዝ "ቀስ ብለሽ ተነሺና  ወደ ፓሊስ ጣቢያ እንሂድ" አላት። ዶክተሩ ፅናትን ሲያያት ሁኔታዋ ጥሩ ስላልነበረ "እዚህ መሆን አይችልም?" አለ። ፅናት ክንድ  ላይ ያረፈውም የፓሊሱን እጅ ያዝ አረጎ
ፖሊሱም አንዴ ፅናትን አንዴ ዶክተሩን እያየ እሺ ጥሩ ብሎ እጁን ከፅናት ክንድ ላይ አንስቷ ወደ ውጪ ወጣ።         ከቆይታ በኋላ ፖሊሱ ከመርማሪው ጋራ መጣ።
   
   ፨መግቢያ በሩ ላይ ያለውን ወንበር ይዞ ፅናት ከተኛችበት አልጋ አጠገብ ተቀመጠ። ዋና መረማሪ ፖሊሱ የፅናትን ሆዷ ላይ ያጣመረችውን  እጅ አንስቶ በእጁ ያዘው ፈገግ ለማለት እየሞከረ "እንደተጎዳሽ ይገባኛል ፤ስለ እዚህ ነገር አውርቼ ባረብሽሽም ምርጫዬ ነበር ግን በተቻለሽ አቅም የምጠይቅሽን ሁሉ መልሽልኝ አላት። እጅ እጇን እያየ ፅናት አገጯን በመነቅነት እሺታዋን ገለፀችለት።
   
፨ መረማሪው የድምፅ መቅጆዎን ካመቻቸ በኋላ ፅናትን አየት አረጎ  የድምፅ መቅጃውን ከማብራቴ በፊት ሁሉም እንዲወጡልሽ ከፈለግሽ ላስወጣልሽ እችላለው አላት። ፅናም "አይ አይሆንም በተለይ የአላዛር አባት እንዲኖረ እፍልጋለው ልጁ ያረገውን ነገር መስማት አለበት" አለች።መረማሪ  ፓሊሱ ወደ ፖሊሱ ዞሮ ሽቅብ እያየው "የአላዛረን አባት አስገባው" ብሎ ለፓሊሱ ትዛዝ አስተላለፈ ። ፓሊሱም "እሺ አለቃ እንዳልክ ይሁን "ብሎ ሊጠራው ከክፍሉ ወጣ።

፨ ፅናት "እሱ ሳይመጣ ምንም ማለት አልችልም አልፈልግምም" አለች። ዋና መረማሪ ፓሊሱም "እሺ ጥሩ እንዳልሽ ይሆናል" አለ። ከዛም ዝም ተባባሉ ፓሊሱ ግን ፅናትን በግረምት እያያት ነበረ። እሷም ጨረፍ አረጋ እያየችው ቆየች። ዶክተሩ በአትኩሮት ሁኔታውን ማየት ተያይዞታል ድንገት ፓሊሱ ከአፉ የሆነ ቃል ወጣ "ውብ ነሽ"  የሚል።
      ፨ ፅናት ደነገጠች በእረግጥ ይህ ቃል ለእሷ አዲስ አደለም ያያት ሁሉ የሚላት ነገር ነው። በድንገት በሩ ተከፈቶ የአላዛረ አባት እና ፓሊሱ መጡ። መረማሪው "እሺ አሁን መቀጠል እንችላለን የተፈጠረውን ሁሉ ንገሬኝ  ዝግጁ ነሽ አደል? " አላት። ፅናት የአላዛርን አባት በእልህ እያየች "አዎ በሚገባ" አለች።
    ፨ይህን ስትል አይኗ በሚጥሚጣ የተለወሰ እረጎ መስሎ ነበር። ልክ እንደ ውስጧ ደፍረሶ ነበር። መርማሪው የድምፅ መቅጃውን አበራው። ፅናት መናገር ጀመረች። "ትናት ትናት ትናንትትትት እህቴ ደና ነበረች።እኔም እንደዛው ሰረተፈኬት ተስቷኝ ከትምህርት ቤቱ አንደኛ እንደወጣው ሳውቅ ለእህቴ ላሳያት ፍለኩ በጣምምም ፈለኩ የመማሪያ ክፍላችን ፎቅ ስር ሆኔ ጠበኳት እስክትመጣ በጣም ጎጉቼ ነበረ። በጣም በጣም በጣም በመጨረሻ መጣች። እህቴ መጣችልኝ" አለችና ፈገግ አለች።
     ፨ ክፍሉ ውስጥ ያሉ ሁሉ እያለቀሱ እና በፅናት የቃላት አጠቃቀም ተገረመው ነበረ። ፅናት ስታወራ አፉዋን የድምፅ መቅጃው ላይ አይኗን ደሞ የአላዛር አባት ላይ አድረጋ ነበረ። ለተወሰነ ሲኮንድ ፀጥ ብላ በድጋሜ ወሬዋን ቀጠለች።  "ከዛማ እህቴ ስትመጣ የምስራቹን ነግሬያት ገና ፍገግ እንኳን ለማለት ሳይፈቅድላት አላዛር! አላዛር! አላዛር! የኔን እህት፣ የኔን ፋና፣ የእኔን ሁሉ ነገረ ከ 2ተኛ ፎቅ ወረወራት"።ብላ ተንሰቀሰቀች።
    
፨መረማሪው የድምፅ መቅጆውን አቋረጦ ፅናትን ሊያባብላት እጁን ወደ አንገቷ ሲያረገው ፅናት እጁን ይዛ "እንዳታባብለኝ በቃ ሁላችሁም ውጡ" አለች።በቃላቷቾ ክብደት ሁሉም ተገረመዋል። እድሜ ሳይሆን ኑሮ የሰውን ጭንቅላት  እንደሚያበስለውም ተረድተዋል። ሁሉም ተከታትለው ክፍሉን ለፅናት ትተውላት ወጡ።
    
፨ፅናትም ለብቻዋ ክፍልሉ ውስጥ በሀዘን ቁረምት ብላ ቀረች። አይኗን የግድግዶ ሰአቱ ላይ ተከለች የግድግዳ ሰአቱን ወደ ጊዜ ሰአት ቀይራ  ከዛም ተነስታ በጣቶቾ አዙራ መቀየረን ተመኘች። ይህን ጊዜ ወይ ወደ ኋላ መልሳ በእህቷ ፍንታ እሷ ለመሆን አልያም ደሞ አሳልፍ እህቷም ደና ሆና መኖርን አለመች። ፅናት ወደ እራስዋ ተመልሳ ፈገግ ብላ "የሞኝ ምኞት ሞኝ ነሽ ፅናት " አለች።
     ፨ እንዲህ ከእራሷ ጋር  የማይሆን ግን ቢሆን የሚያስደስታትን እያሰበች በማሰቧ እየተገረመች  እንቅልፍ ጥሏት  ሰአታት ነጎዱ።ከእንቅልፏ የነቃችው ዶክተሩ ስለ ጤንነቷ ሊያረጋግጥ ሲመጣ ነበረ። ዶክተሩ "እንዴት ነሽ አሁን" አላት። በውስጧ "ምን እንድመልስለት ጠብቆ ነው?አለችና ለእሱ ግን  "ደና ነኝ" አለችው።  ዶክተሩ "እሺ ጥሩ" ብሎ ሙቀቷን እየለካት ፅናት ዶክተሩን "ዶክተር" አለችው ልስስስ ባለ አንደበት።  "አቤት"  አላት እሱም ረጋ ባለ ድምፅ  "እህቴን ማየት እፍልጋለው" አለችው። ዶክተሩ አልተቃወማትም።" እሺ  ብቻ ነው ያላት"
.
.
ይቀጥላል
..

   ላይክ ሼር እዳረሱ...


..♥️ ፅናት ♥️...!!!
           .
           .
           .
🥀..ክፍል 3..🥀
.
.
#Notice :- እውነተኛ ታሪክ ነው .!!
.
.
አዘጋጅ እና አቅራቢ :-
#ከደራሲያን_አለም የቴሌግራም ቻናል✍
.
.
፨በሚኖሩበት አከባቢ ያሉ ስዎች እነ ፅናት ስፈራቸውን ሲቀላቀሉ  በስው ህይወት ገብቶ ማውራት ባይመቻቸውም የእነ ፅናት ነገረ ግን ስለሚገረማቸው ሁሌም ይንሾካሾካሉ ፤ያወራሉ "እንዴት ከአንድ ሞነክሴ ጋረ ሁለት ሙስሊም ይኖራል?" ብለው የመጀመሪያ ስሞን ያወሩ ነበረ። ከዛ በሳምንቱ ፅናት፣በፀሎት እና የእድሜ ባለፀጋዋ ሞነክሴ ቤተ ክረስቲያን ጠዋት ጠዋት ተሳልመው መምጣት ሲጀምሩ  የሰፈሩ ስው ዕርስ  ቀይረው "ቆይ ሙስሊም ካልሆኑ ለምን ይጠመጥማሉ?"ብለው ማውራት ጀመሩ ።
     ፨በእዚህ ወሬ የሰፈሩ ነዋሪ በጠቅላላ በእየግሉ ወሬ ተነበየ "ይህንን ሻረፕ የሚጠመጥሙት ቡዳ ስለሆኑ ነው"። ቤተ ክረስቲያንም የሚሄዱት ለታይታ ነው እንደው ፈጣሪን አይፈሩም? " አሉና  ወሬውን ነዙት። ከአመት በኋላ የእድሜ ባለፀጋዋ ህመማቸው ፀንቶባቸው የአልጋ ቁራኛ ሆኑ።በፀሎት እና ፅናት እኒን ሴት ሀኪም ቤት እንደምንም ደጋግፈው ወሰዶቸው። ከ15ቀናት በኋላ ኑ እና ውጤቱን ትስማላቹ ብሎ ዶክተሩ በስጣቸው ቃል መሰረት በ15ቀኑ ሄዱ። ዶክተሩ አዋቄ ሰው እንዲጠሩ ቢጠይቃቸውም በፀሎት ስላሉበት ነገር ምንም ሳይቀር ነግራው አሳመነችው።
  ፨ የሰሙት ዜና ልብ ሰባሪ ነበረ። ሴትየዋ ያለባቸው ችግረ ከደም ጋረ የተገናኘ በሽታ ነውና በሽታው በሙሉ በስውነታቸው ተሰራጭቶል  በህይወት ለትንሽ ጊዜም ቢሆን  ለመቆየት መዳኒት ያስፈልጋቸዋል። መዳኒቱን ለመግዛት ደሞ በሳምንት 10 ሺ ያስፈልጋል የሚል ዜና ነበረ። ይህንን መረዶ  ከሰሙ በኋላ ሁሉም ተረበሹ። በነጋታው በፀሎት ተነስታ ወዳከራዩት ቤት ሄደችና ቤቱን እንዲገዟት ጠየቀቻቸው።     መጀመሪያውም እንግዛው ሲሉ ስለነበረ ሳያቅማሙ እሺ አሉ።
     ፨ ተከራዮቹ ባልና ሚስት ናቸው  በቅረቡ ነው ከአሜሪካ የመጡት። ከዛም ባልየው ለበፀሎት አንድ ነገረ ጠየቃት  እሷ ህፃን ብትሆንም ግን በሳል ሀይምሮ ነው ያላት። "ቆይ እንዴት ነው የምትሽጭልን አንቺም ልጅ እህትሽም ልጅ" አላት።  በፀሎትም "አሁን በእራሳችን ስምምነት እንፈጠር እናንተ የቤቱን ብረ ስጡኝ እና ቤቱን ኑሩበት። እኔ 18 አመት ሲሞላኝ ደሞ በፊረማዬ አረጋግጥላችዋለው" አለች። ስውየው ይህ ቃል የወጣው ከብላቴና ልጅ ነው ለማለት ተቸገረ። የሆነ ሰው በይ ብሏት እንጂ በፀሎት ወሬዋን ቀጠለች ከእድሜ ባለፀጋዋ ጋር በተስማሙት መስረት እንግዲህ 500,000 ብር ነው ስትል ሰውየውም "ጥሩ የተስማማውት ስለማምንሽ ሳይሆን ብታጭበረብሪ እንደምይዝሽ እና እንደምገልሽ ስለማውቅ ነው" አላት። በፀሎትም "ማንም ባለጌ እና አጭበረባሪ አርጎ ስላላሳደገኝ አታስብ" አለችው። ስውየው በአነጋገሯ ከመገረም ጋር ተስማማ።
      ፨ ከዛ ስውየው በሶስተኛው ቀን 500,000 ብረ ስጣት። ከዛ ጊዜ ጀምሮ ለወራት በእዚህ ብረ ሴትየዋን ማስታመም ጀመረች። መዳኒቱን  ቢወስዱም ግን በሽታቸው ገፈቶ። ይህ በእንዲ እንዳለ ከ6 ወር በኋላ ለወረ የተገዛላቸውን እንኳን መዳኒት ሳይጨረሱ ነው ፅናትና በፀሎት  ከትምህርት ቤት ሲመጡ አልጋው ላይ አይናቸው ፈጦ ያገኟቸው። በሰአቱ በፀሎት  እና ፅናት ባዩት ነገር ተደናግጠው ሲጮሁ የሰፈሩ ሰው ተሰብስበው  መጥተው ሴትየዋን ገናዥ መጥቶ ከገነዛቸው በኋላ በፁሎት  ካስቀመጠችው የቤቱ ብረ ለገናዡ ከፈለች።ለንፍሮ እና ለሊሎች ነገሮች ከአስቀመጠችው ብረ እያወጣች ተጠቀመች። ብሩ  ከየት መጣ ብለው የስፈሩ ስው በፀሎትን  ቢጠይቆት እና ቢያንጓጥጧት ቤታችንን ሽጭኤ ነው አለቻቸው።
     ፨የሰፈሩ ነዋሪ ደሞ "አይ አይ በጥንቆላ ያጠራቀሙት ነው" ብሎ ፈረጀ።በፀሎት እና ፅናት ይህንን የሰፈር ወሬ ባልስማ እያለፉ ቆዩ። የሆነው ሆኖ የእድሜ ባለፀጋዋን ነገረ እና ሀሜት በተቀላቀለበት መልኩ ቀበሯቸው።
የአባታቸው እህት በለቅሶ ሳምንት መጥታ እንደ ማንኛውም ሰው ደረሳ ሄደች።የሰፈሩ ስው ከሰልስቱ በኋላ ቤታቸው ድረሽም አላሉ።እንደውም ይበልጥ ይሸሻቸው እና ያረቃቸው ጀመር።

፨በሳምንቱ "እናታቹ ለፅናት ክርስትና የተበደረችውን ብር መልሱልን እስካሁንም ዝም ያልኳቹ ብረ የላችሁም ብለዬ ነበረ። አሁን ግን ቤታችሁን ስለሸጣቹ መክፍል ትችላላቹ" አሉዋቸው።በፀሎት በጣም ተበሳጨች "እንዴት መጀመሪያ 'ፈጣሪ ያፅናቹ' ሳይሉ ስለ ብድረ ያወራሉ"አለች።አበዳሪውን እስከ አፍጫቸው ተናግራ የብረ መጠኑን ጠይቃ  ሰጠቻቸው። ከዛም የማታቃቸው ስዎች ሁሉ እየመጡ የአባታቹ እዳ አለባችሁ እያሉ ወሰዱ።
     
፨በፀሎት በተለይ የመጀመሪያው ሰውየው ከሆደ በኋላ ጨሰች። ተንገበገበች ፣ተቃጠለች ፣እረረረረ፣ ድብን አለች። በእዚህ ጊዜ ትንሾ ፅናት "ተረጋጊ እህቴ እንኳንም የሰውዎችን እዳ ከፈልን አሁን ነፃ ነን።ሁሉንም  ተረጃቸው እስካሁን ታግሰውናል ሊላ ሰው ቢሆን እንዲ ጊዜ አይሰጠንም ነበረ"።  አለቻት።  በፀሎት በፅናት ንግግር በጣም ተደመመች የማፅናኛ ቃላቶቾ ሁሌም እያስገረሙ ያፅናኗታል።በፀሎት  ፅናትን እቅፍፍፍ  አረጋ በሁለቱም በኩል ጉንጮቾን ሳመቻቸው።  "ውይይይይ የኔ ሚጢጢ እህቴ ስወድሽ እኮ ያልሽው እውነት ነው"  አለቻት እና ፈገግ ብላ  "ፈጣሪ ያውቃል ለእኛ ጥሎ የማይጥለን አምላክ አለ" አለች። "ልክ ነሽ፤ አንችም ልክ ነሽ" ተባብለው ተቃቀፉ።
    ፨ፅናት እና በፀሎት  እረዥም ደቂቃዎች ተቃቅፈው ከቆዩበት ፅናት ቀናብላ "እህቴ" አለቻት። በፀሎትም "ወዬ" አለች። ፅናት በድጋሜ ጥምጥም ብላ አቀፈቻት እና "ጭንቀትን ከሚያስረሱ ትልልቅ እና ዋና ከሚባሉት መካከል መተቃቀፈ እንደሆነ ታውቄያለሽ?"አለቻች።በፀሎትም  ግርም እያላት "አይ እህቴ ይህንን ደሞ ከየት ስማሽ" አለቻት። ፅናትም "ሬዲዮ ላይ ስምቼ ነው"። አለችት። በፀሎት "ውይይይይ የእኔ ውድ ምረጥ አኮ ነሽ"። አለችና አቅፋ ሳመቻት።
   ፨ ከሳምንት በኋላ  ሁለቱም ወደ ትምህረታቸው ተመለሱ። በፀሎት 10 ፅናት ደሞ 5ተኛ ክፍል ደረሰዋል።ጊዜ ሄደ ህይወትም ከነ ክብደቷ  በእራስዋ መንገድ ተመመች። ፅናት እና በፀሎት የሁለተኛ ሴሚስተረ ውሰጤታቸውን ለመቀበል ትምህረት ቤት ናቸው። ወረፋ ይዘዋል  ማንም እነሱን ወላጅ አምጡ አይላቸውም ምክንያቱም ችግራቸውም ስለሚያውቁ።

፨ፅናት ውጤቷን ተቀብላ ከፎቁ ወረዳ እታች እህቷን እየጠበቀቻት ነው። ወደ ፎቁ አይኗን ቀይሳ  ሰርተፊኬቷ ላይ የተፅፈውን እጅግ አስደማሚ ውጤቶን ልታሳያት። ከብዙ ጥበቃ ግን ከትንሽ ደቂቃ በኋላ በእስተመጨረሻ እህቷ በፀሎት ሁለተኛ ፎቅ ደረጃ እየወረጀች አየቻት። ከዛም ጠራቻት። በፀሎት ቁልቁል እህቷን ስታያት ፅናት ጮክ ብላ "እህቴ አንደኛ ወጣውልሽ" አለቻት።


    ፨በፀሎትም ፈገግ ብላ  ጓበዝ የእኔ ልዩ" ብላ ሊላ ልታወራው ያሰበችውን ሳጨረሽ አንድ ቀልዱ እንጨት እንጨት የሚል ልጅ ትግስትን ታግሎ ወደ ታች ወረወራት ፅናት ባየችው ነገረ ደረቃ ቀረች። ተማሪው ፣አስተማሪው ፣ብቻ ትምህረት ቤት የሚስሩ እና ያሉ ሁሉ በፀሎት ባወጣችው የጩከት ድምፅ ተደናግጠው ወጡ።
.
.
🥀..ከ 150 Like ቡሀላ ክፍል 4 ይቀጥላል ..🥀
         
         


❤️….. ፅናት…….❤️


🌹🌹🌹 ክፍል 2 🌹🌹🌹


https://t.me/+5IB6ndsrPnw3NzJk

.


.
          
..የሆነው ሆኖ ለፅናት ክረስትና ቀን ጠዋት የድግሱን ብረ ውሽማሽ ነው የስጠሽ ብሎ ለክፏት ወጣ።እናትየው ሁሌም መልስ አትሰጠውም የህይወቷን ምእራፍ በትንሿ ልጇ ፅናት ብላ ስይማዋለች።በእዚህ መሰረት የመጨረሻ ልጆ ስም ሴት ከሆነች ፅናት እላታለው ብላ አባ ስለነበር።ስትወልድ ሴት ልጅ ወለደች።ይህቺ ልጅ ለህይወቴ ፅናት ናት አንቺንም በህይወት አቆይቶኝ እንድወልድሽ ስለፀለይኩ ነው በፀሎት ያልኩሽ ብላ ለበፀሎት ይህንን የነገረቻት።ገና በእረግዝናዋ ስአት ነበር። በፀሎት በሳል ጭንቅላት ስላላት እናታቸው ሲከፈትም ስትደሰትም የምታማክራት ለበፀሎት ነው።የፅናት ክርስትና በአል አክብረው ጨረሱ።
  
   አመሻሽ ላይ በመጠጥ እራሱን የሳተው አባታቸው እናትየውን ይመጣና በተገረዳደፈ አንደበት በቆመበት እየተንገዳገደ"ስሚ አንቺ ቆይ እንዴት ተበድረሽ ትደግሻለሽ።ሀሀሀ ውይ ውይ ማለቴ ከውሽማሽ ተቀብለሽ ለነገሩ ለልጁ ያልሆነ ብር ይህቺም ደሞ ከእሱ ነው የወለድሻት አደል እሺ እሱስ ይሁን ይህንን ውበትሽን ለማውጣት ጥረሽ ተሳክቶልሽ ወንድን ማሽካርመምሽስ?"አለ።እናታቸው አለም ፀሀይ ምንም ትንፈሽ ሳታወጣ ጥበብ አብዝቶ የስጠው ስአሊ የሳለው  የሚመስል ውብ እና ትልልቅ አይኖቿን እያንከራተተች ታየው ጀመረ።
     ፨እናታቸው አለም ፀሀይ እንደ ስሟ ፀሀይ ናት። ውበቷን ማንም ሊክደው አይችልም ውበት ከደም ግባት ጋረ ያደላት ቁመተ መለሎ ስውነቷ ለመንካት የሚያሳሳ የእግረ እና የእጆ ውበት የፀጉሯ እረዝመት እና ጥቁረት ተዳፋቷ በራሱ ወንድን ለማማለል በቂ ነው።በዛ ላይ ፀባይዋ ትህትናዋ እና ድምፆ ውብ ነው።ነገረ ግን ከትዳሬ ውጪ ወደ ውጪ ያለች እመቤት ናት። አባትየው በጩከቱ መልስ ስላልስጠችው በመናደድ ጠረጴዛ ላይ ተቀምጦ በነበረውን ቢላ አንስቶ ፊት ለፊቱ በፋዘት ከምታየው ውቧ ሚስቱ አለም ፀሀይ ላይ ፤ የልጆቹ እናት ላይ የያዘውን ቢላ በረዥም እና ቀይ አንገቷ ላይ ሰካው።
     ፨ ይህንን ተደብቃ ስታይ የነበረችው በፀሎት  በህፃን አይምሮዋ ያለ አቅሟ ማየት የሊለባትን ያየችው በፀሎት  ጩከቷን አቀለጠችው። ጓረቤት ተስበሰበ አባታቸው እራሱንም ጎረቤቶቹ መጥተው ከመያዙ በፊት እራሱ አንገት ላይም ወግቶ እራሱን አጠፋ። ጎረቤቶች በሩን በረግደው ገብ ፅናት መኝታ ቤት ሆና ይህንን ክስተት አይታ የገባት ይመስል እሪሪሪ ማለቷን ቀጠለች። ግን ከበፀሎት ውጪ ማንም ልብ አላላትም በፀሎት ከተደበቀችበት ሶፋ ሮጣ ወደ እህቷ ሄደች።ከእህቷ ጋረ አልጋ ላይ ወጥታ ጭብጥ ብላ ተቀምጣ ማልቀስ ጀመረች።ፅናት አልቅሳ አቅሟን ስታጣ ዝም አለች።ትግስት ግን ተንቀጠቀጠች።
    ፨በእዚህ መልኩ ነበረ ወላጅ አልባ የሆኑት። ከዛማ በጎረቤት ጥሪ መሰረት ፖሊሶች መጡ።በነጋታው ፓሊሶች በፀሎትን ፓሊስ ጣቢያ ወስደው በህፆናት ሳይካትሪስት የተፈጠረውን እንድትናገረ አደረጉዋት።ያንን ቀን የተሰማትን ነገረ መግለፅም መረሳትም አትችልም ላይጠፋ በህሊናዋ ተቀረጿልና።
     ፨የእናታቸው  ሰልስት ካለፈ በኋላ የአባታቸው እህት ጓዟን ጠቅልላ ገባች። ይህቺ አክሰታቸው ባልም ሆነ ልጅ እንዲሁም ፈላጊ ወንድ የላትም ፀባይዋ በጣም አስቸጋሪ ስለሆነ።ቤታቸው ገብታ አብራቸው መኖረ ስትጀምረ የበፀሎት እና የፅናት ህይወት ሲኦል ሆነ።አባት እና እናታቸው ሙሉ ንብረታቸውን በልጇቻቸው ያረጉት ፅናት ከተወለደች ከሳምንት በኋላ ነው። ይህ ንብረት ልጆቻቸው 18 አመት ከሞላቸው ሙሉ ንብረቱን እንዲወረሱ የሚል ውል ነው። በእረግጥ ሀብታም አደሉም በስማቸው አንድ ቤት ብቻ ነው የነበረው አባታቸው ነው ይህንን ያረገው።
አክስታቸው እናት እና አባታቸው ያወረሷቸውን ውረስ አሳዳጊ ነኝ በማለት ልትወረስ ብትጥረም ችሎቱ ውሳኔዋን ውድቅ አረጎባታል የአክስታቸው ስም ድንቄ ይባላል።ፅናት ካደገች በኋላ ሁለቱንም ማሰቃየት ጀመረች።
  
  ፨ይህንን ያዩ ተከራይ የነበሩት የእድሜ ባለፀጋ አክስታቸውን ከሰው በፍረድ ቤት ክረክር ከእዛ ቤት አስወጧት።ይህን ሲያረጉ የሰፈሩ ሰውም ለምስክርነት ቀርበው ነበር። ያኔ በፀሎት10 ፅናት ደሞ 5 አመታቸው ነበረ።ከዛማ ከእኒ የእድሜ ባለፀጋ ጋረ መኖረ ጀመሩ።በፀሎትም አክስቷ ያስቆረጠቻትን ትምህረት አስቀጠሏት። ከ2 አመት በኋላም ፅናትን ከቆሎ ትምህረት ቤት አስወጥተው አንደኛ ክፍል ወስገቧት። ሁለቱም ትምህረታቸውን በሰረአቱ መማረ ጀመሩ።ከቀናት በኋላ የእድሜ ባለ ፀጋዋ ሴት በእረጅና እቤት መዋል ጀመሩ።የጡረታ ብራቸውም ምክንያቱ ባልታወቀ ጉዳይ ተቋረጠ።
    ፨ከዛም ሂሩት ከትምህረት ስትመለስ በዳቦ የሚሰሩ ምግችን እየሽጠች መተዳደር ጀመሩ።እንዲህ እየኖሩ እኒ የእድሜ ባለፀጋ በህመም አልጋ ላይ ዋሉ።እሳቸው ለማሳከም ቤታቸውን መሸጥ ቢፈልጉም 18 አመት ስላልሞላቸው መሽጥ አልቻሉም በእዛ ምክንያት እቃቸውን ጥቂት አስቀረተው ሸጡ ቤታቸውንም አከራይተው እነሱ የጭቃ ቤት ተከራዩ።

፨ እነ ፅናት ከእዛን ቀን ጀምሮ በጭቃ ቤታቸው ኑሮን ተያያዙት።የሚኖሩበትን ቤት ላየው ተመልካች ህፃናት ለጨዋታ ብለው እንደነገሩ የሰሩት የመጫወቻ ቤት ይመስላል።የፅናት ታላቅ  እህት በፀሎትም የእድሜ ባለፀጋዋን እና ፅናትን መንከባከብ ጀመረች። ከትምረህት ቤት  ከቤት ወደ ስራ ከስራ ወደ ጥናቷ እና እህቷን እና የእድሜ ባለፀጋዋን መንከባከብ የቀን ተቀን ስራዋ አደረገችው። የምትሰራው ስራ ቀለል ያሉ ምግቦችን በመዘፋዘፊያ ይዛ ዞራ መሽጥ ነው።
     ፨መኖሬያ ስፍራቸው  ሴተኛ አዳሪ፣ ዱረዬ እና የጎዳና ተዳዳሪ ይበዛበታል። በፀሎት እና ፅናት ሁልግዜም ፊታቸው ላይ ሻርፕ ሳይጠመጥሙ አይወጡም ካለ አይናቸው ምንም የሚታይ ገልፅ  የላቸውም። የሚለብሱት ልብስ በጣም የተንጓተተ ግን ደሞ የፀዳ ነው።ቤታቸውን አከራይተው እዚህ መረጋጋት ፣ ዝምታ እና  እራስን ማዳመጥ ከማይቻልበት  ሰፈረ ከገቡ በኋላ ነው መሸፋፈን የጀመሩት።

https://t.me/+5IB6ndsrPnw3NzJk

.
.
.
.
🥀. ሀሙስ ማታ 2:00 ክፍል 3 ይቀጥላል
………


❤️❤️ፅናት❤️❤️



🌹🌹 ክፍል 1 🌹🌹



   ፨" የከተማ ገጠር  ውስጥ መኖር እኮ ከባድ ነው"። አለች ፅናት እንደ ልማድዋ በእጅ የምትያዘዋን ሬዲዮ ለመስራት እየታገለች። እንዲ ስትል ዊልቸር ላይ የተቀመጠችው ማየት የተሳናት ታላቅ እህቷ በፀሎት  "እንዴ ፅናቴ አሁን የምንኖረው ከተማ አደል እንዴ ደሞ አነጋገረሽ ሁለት መልክ ያዘ" አለቻት። ፅናትም "አይ ፀሎትዬ ባክሽ አንዳንዴ የሌለ ነገረ ያናዝዘኛል መሰለኝ"። አለችና ሬዲዮኑን መታ አረገችው እሱም በዱላ ይሰራ ይመስል መስራቱን ቀጠለ።
       
  ፅናት  "ውይ ይሄ ፕሮግም አላመለጠኝም" አለችና ሬዲዩኑን ወደ ጆሮዋ አስጠጋችው። እንደው ወደ ጆሮዋ ማስጠጋት ልምድ ሆኖባት እንጂ የሬዲዮኗ ድምፅ ከእነሱ ቤት አልፎ ጎረቤት ይሰማል። ጓረቤት የላቸውም እንጂ ቢኖራቸው ኖሮ!..  ሬዲዮኑ ውስጥ አንድ ጓረናና ድምፅ ያለው ተወዳዳሪ የሊለው ደራሲ ስለ ድረሰቱ ምረቃት ለድረሰቱ ምረቃት በተዘጋጀው  መድረክ ላይ ቆሞ የሚናገረ ይመስላል።
      
የእነ ፅናት ቤት ሪዲዮኑ ውስጥ ከሚያወራው ሰው በቀር ምንም አይስማም ይህ ታዋቂ ደራሲ ከታዳሚዎች ጭብጨባ በኋላ ወሬውን ቀጠለ። "ሰላም ጤና ከአክብሮት ጋረ ይድረሳቹ። ስለ መፅሀፌ ከማውራቴ በፊት ስለ ድረሰት አንዳንድ ነገረ ልበላቹ። ሁላችንም እዚህ አለም ላይ ስንኖር የፈጠረን አምላክ አለ ብለን በማሰብ ነው። እና ለምሳሌ አውሮፕላን የስራው ስው ከወፍ ነው የአሰራር ብልሀቱን የተማረው ፤መኪና የስራው ስው ከስው ውስጣዊ ሆድ እቃ አካል ተነስቶ ነው መኪናን የስራው፤ኧኧኧኧ ሊሎችም እንደዛው ደራሲም ከህይወት በመነሳትና  እና ፈጠረን ካለው ፈጣሪ ህይወትን በመውሰድ ነው የሚደረሰው።
  
ልዩነቱ ፈጣሪ የፈጠረቻው ፍጥረታት በእውን አሉ እኛ የፈጠረኛቸው ደሞ በምናብ አሉ። እኒን ምናባችን ውስጥ ያሉትን ስዎች በአካል ማምጣት በጭራሽ አንችልም።ኧኧኧኧ ለምሳሌ እኔ በምፅፈው ድረሰት ውስጥ 3ሜትረ ቁመት ያላት እምምምም ፤ ፀጉሯ እስከ እግረ ጥፍሯ የሚደረስ እእእእ፤ አፈንጮዋ በጣም ትንሽ፤ አይኗ በጣም ትልልቅ፤ እጅ እና እግሯ የአራስ ህፆን መጠን ያላቸው፤ እእእእእ ስትሄድ አንካሳ ሴት በምናቤ ፈጥሬ መፃፍ መብቴ ነው።
       ፨ታዲያ እኔ መብቱ የግሌ ነውና  ብገላትም ፣ባኖራትም፣ ባሳምማትም፣ ባድናትም ፣ባስቆዝማትም፣ ክፉ ባረጋትም፣ ደግ ባረጋትም ፣መብቴ ነው። በተቃራኒው ቁመቷንም አጭረ አረጌ ፁጉሯን ረዥም ማረግ መብቴ ነው ብዙ አፈቃሪ ወንድ ወይም ወንድ የማይጠጋት ማረግም የእኔ ውሳኔ ነው። በእረግጠኝነት ይህቺ የነገረኮችሁን ሴት በምናባቹ አስባችዋታል ግን በአካል የለችም።
      ፨እኔ በምናቤ የሳልኳትን ስው እንኳን እሷኑ አምጣ ብትሉኝ አላመጣም። ግን በሀሳባቹ አኑሬያታለው ምክንያቱም የእኛ ስልጣን እዚህ ድረስ ስለሆነ ነው። ፈጣሪ ግን ካሻው አሁን በእዚህ ስአት ከሁለት ቁመት አብዝቶ ከነሳቸው ስዎች መጀመሪያ የገለፅኩላችሁን 3ሜትረ ቁመት ያላትን እንስት ፈጠሮ እና ህይወት ስጥቶ ማኖረ ይችላል።እኔም የሆነ ደራጃ ድረሰ መሄድ እችላለው። ፈጣሪ በአንድ እንስት መሀፀን ውስጥ ይህቺን ሴት ሲፀንሰሰ እኔ በሀሳቤ ይህቺን ሴት ፀነስኩ ይባል። ታዲና ይህቺ ሴት ፈጣሪ በውልደት ወደ እዚህ አለም ሲያመጣት እኔ የእሱ ተፈጣሪ ደሪሲ ደሞ ይህቺን ሴት በምናቤ አረግዤ በብእሬ እወልዳታለው።
     ፨ እኔም ሀሳቤን እሷም  በእኩል ህመም እናስተናግዳለን። ይህንን ካልኩ ዘንዳ ስለ ድረስቴ አንዳንድ ነገረ ልበላቹ ያው ይህ መፅሀፈ በእውነቱ ብዙ ዋጋ አስከፈሎኛል። ውስጡ ያለውን  ሀሳብ ትወዱታላቹ ብዬ አስባለው አመስግናለው"። ሲል የታዳሚ ጭብጨባ አጀበው።
    ፨ በመሀል የሙዚቃ መሳሪያ ድምፅ ገባና የፕሮግራሙ አቅራቢ ሰው አመስግኖ ተባባሪ አቅራቢውም "አብራችሁን እንድትቆዩ በአክብሮት እንጋብዛለን" አለች። ወዲያው  የሙዚቃ ክላክሲካል ተስማ። እረዥም ደቂቃዎች ካስቆጠረ በኋላ የፕሮግራሙ መሪ ድምፅ ተሰማ "ተመልሰናል አድማጭ ተመልካቾቻችን አሁን በመቀጠል የደራሲ መሀመድ ሳላዲን ባለቤት የሆነችው ወይዘሮ ከድጃ ኢብራሂም  ንግግረ እንድታረግልን በማክበር እንጋብዛታለን" አለ ወንዱ አቅራቢ። ከዛ ጭብጨቦ ተከተለ መድረግ ላይ  እንድትወጣ አበረታቶት። ጨብ ጨብ.......... ጨብ ጨብብብብብብብብብብ የደራሲ መሀመድ ሳላዲን ሚስት በሙዚቃ እና በጭብጨባ ታጅባ ወደ መድረክ እየሄደች ይመስላል።ከደቂቃዎች በኋላ መድረክ ላይ ወጥታ ወደ ማይኩ ተጠጋች
         " ሰላም እንዴት ቆያቹ"
        አለች። ከዛን በኋላ ጭብጨባ አጀባት። እሷም "በመጀመሪያ ፣በመሀል  እና በመጨረሻም ጥሉ ለማይጥለን አምላክ አልሃምዱሊላህ እኔ ምን ማለት እንዳለብኝ አላውቅም ማሚዬ ሁሌም ጥሩ ስራ ለመስራት እንደጣረ ነው። እሱ ለእኔም ለልጆቹም እንዲሁም በዙሪያው ላሉ ስዎች ሁሉ ጥሩ ሰው ነው።ይህ የፆፈው መፅሀፍም በህይወታቸው ተስፋ ለቆረጡ ስዎች የህሊና ብረታት ይሆናል። ይህ መፅሀፈ በቃ አንብባቹ ተረዱት ምንም ማለት አልችልም አመስግናለው" አለች።
      ሁሉም አጨበጨብ ሴቷ የፕሮግራም አቅራቢም "እናመስግናለን ወይዘሮ ከድጃ ፣ተመልካቾቻን እና አድማጮቻችን ፍቅረን እና ስላምን እንዲሁም ደስታን እንዲሰጣቹ እየተመኘን ፕሮግራማችንን በእዚሁ እንደዘጋለን" አለች። ወንድ አቅራቢውም "መልካም ጊዜ ስናይ እለታትን እንድታሳልፉ እንመኝላችዋለን" አለ። እና ፕሮግራሙ አበቃ።
   
፨ፅናት "ውይይይ ደስ አይሉም በፀሎቴ እንዲህ አይነት ፍቅረ ሲኖረ አለ እንጂ የእኛ አባት" አለችና አንገቷን አቀረቀረች። ፅናት አባት እና እናቷን በፎቶ እንጂ በአካል ያየቻቸው ማስታወስ በማችልበት የጨቅላ እድሜዋ ላይ ነው በፀሎት ግን በትንሹ ታስታውሳቸዋለች። እሷም "እውነትሽን ነው ፅናቴ የእኛ አባት እኮ በጭራሽ ሰው አይደለም" አለች። ሁለቱም አይምሮ ውስጥ የአባታቸው እረኩስት ታወሳቸው።
  ፅናት እህቷ በፀሎት  በነገረቻት መሰረት በፀሎት ደሞ አይኗ ባየው መሰረት አስታውሰው ፊታቸው ጭር አለ።በፀሎት በሀሳብ ጭልጥ አለች።ያሰብት ስለ እናታቸው የሙት ቀን ስለሚወዶት እናታቸው አስቃቂ ግድያ እና ስለ ገዳዩ አባታቸው ነበር።
     ፨ጊዜው 11 አመታትን አስቆጥሯል።እናታቸው ያኔ ፅናትን ወልዶ አራስነቷን ጨረሳ የፅናት ክረስትና በአል የተከበረበት ጊዜ።በፀሎት ያን ጊዜ 5 አመቷ ነበረ። በጊዜው የፅናት የክረስትና ቀን ስለሆነ ሁሉም ደስተኞች ነበሩ።እናታቸው ከስፈራቸው ባለ ሀብት ገንዘብ ተበድራ በደመቀ መልኩ አክብራው ነበረ።  አባታቸው ለድግሱ አልገኝም ብሎ ወደ እህቱ ቤት ሄደ። የአባታቸው እህት የስይጣን አለቃ ባህሪ ያላት ሴት ናት። አባታቸው እናታቸውን ካገባ በኋላ "ሚስትክን ከሊላ ወንድ ጋረ አየዋት እሷ  በጭራሽ ላንተ ፍቅር የላትም" በማለት በመከረችው መስረት በፀሎት ሆዷ ውስጥ እያለች ልጅቷ የኔ አደለችም በማለት ይነዘንዛት እና ይጨቃጨቃት ነበረ።
.
.
🥀..ከ
150 ላይክ በሗላ ክፍል 2 ይቀጥላል ……..
          .
          .

𝗝𝗼𝗶𝗻 𝘂𝘀
@Yefkrtarik
@Yefkrtarik

3.9k 0 30 3 127

❤️❤️ ፅናት ❤️❤️

አዲስ ልብ አንጠልጣይ ልብ ወለድ..❤️

እንጀምራለን 👍
SHARE እያረጋቹ ♥️ 100 Like በሗላ
                 .
                 .
                 .
🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹
                 .
                 .
                 .
ከፍቅር ታሪክ የቴሌግራም ቻናል 𝐉𝐨𝐢𝐧 በማለት ራሶን በጣፋጭ ትረካዎች ዘና ያድርጉ ..♥️✨
                 .
                 .
                 .
..............................................................
..............................................................
..............................................................
                 .
                 .
                 .
             𝗝𝗼𝗶𝗻 𝘂𝘀
╔═══❖•🌺🌸•❖═══╗
  ♥️♥️ተቀላቀሉን ♥️♥️
https://t.me/Yefkrtarik
https://t.me/Yefkrtarik
╚═══❖•🌺🌸•❖═══╝


Forward from: Hibtu store
AYESS Türkiye 🇹🇷 brand ካልሲ / socks 🧦
Specially for DM patients or ለስኳር ህምተኞች የተሰራ ምቹ ካልሲ
Price - 400

Telegram- @hibtuuu
Phone- 0913285784


❤️ተማሪዋ❤️



🌹…………ክፍል 50 ………..🌹

የመጨረሻ ክፍል

" ምን እያልሽ እንደሆነ እንኳን ለኔ ለራስሽም የሚገባሽ አይመስለኝም ቃልዬ ፣  ዛሬም ዛኪን እንደምታፈቅሪው  ብቻ ነው የገባኝ አሁን ያልሽኝን ልረዳውም ላምንሽም አልችልም ።

መቼም እንዳላምንሽ አርገሽ ልቤን ሰብረሽዋል አሁን የምፈልገው ከዚህ በላይ ምንም ክፍ ቃል ካፌ ሳይወጣ እንድትሄጅልኝ ብቻ ነው" አልኳት።  ቀና ብዬ ቃልዬ ስትሄድ ላለማየት እንዳቀረቀርኩ።
ረጅም ደቂቃ እያለቀሰች ቆየች። ከዝምታ ውጪ ምንም አላልኩም።
"ኤፍዬ ይቅርታ እሺ" ብላኝ እያለቀሰች ቤቱን ለቃ ወጣች።

እኔም ወጣሁ። ታምሜ ተኛሁ።

አስር ቀን ሙሉ ምን እንወሆነ በማይታወቅ በሽታ  ታመምኩ  ስራ አልሰራሁም ። የቃልዬ ምርቃት ቀን እንደምንም ተነስቼ ቀደም ብዬ የገዛሁላትን ስጦታ እና አበባ ይዤ ወደ ግቢ ሄድኩ።
ከቤተሰቦቿ መሀል ሆና ከግቢ እንደወጡ ከጀርባ ጠጋ አልኩና
"ቃልዬ" ብዬ ጠራኋት።
ዘወር ብላ እንዳየችኝ ከቆመችበት አልተንቀሳቀሰችም ። ቤተሰቦቿ ወደፉት እየሄዱ ነው። ቃልዬ እዛው ቆማ እያየችኝ በዝግታ እየተራመድኩ አጠገቧ ስደርስ እነዛ አይኖቿ ላይ ያቀረረው እንባ በጉንጯ ላይ ቀልቀል ወረደ።
ስጦታዋን ሰጠኋት። ተቀበለችኝ። አመሰግናለሁ ሳይሆን  ምናልባትም ለአስረኛ ግዜ•••
"ኤፉዬ ይቅርታ እሺ" ነበር ያለችኝ።
ፉቴን መልሼ ካጠገቧ ሄድኩ። ምናልባት ቃልዬም ከአንድ ከሁለት ቀን በሁዋላ ከቤተሰቦቿ ጋር ወደ አዲስ አበባ ትሄዳለች።
ህይወት ፣ ምኞት፣ ደስታ ፣ ስራ፣ ተስፋ ሁሉ ፣ እራሱ መኖር  ትርጉሙ አልገባህ አለኝ። ለምን እንደምኖር እራሴን ስጠይቅ ለመኖር የሚያስገድደኝ አንድ ምክንያት ብቻ ነበር ያገኘሁት።
እሷም እህቴ ነች።
የምኖረው ልኔ ብዙ ለደከመችው ለእህቴ ስል ብቻ ነበር።
የናትና ያባቴ ምትክ እህቴ እኔን ብታጣ ምን እንደምትሆን ማሰብ አልችልም። ለሷ ስል እኖራለሁ። ሂወት ቀጠለ።
ለወራት የክቡር ዶክተር አርቲስ ጥላሁን ገሰሰን  ሳላስብ ትተሽኝ የሚለውን ሙዚቃ ሳላዳምጥ ተኝቼ አላውቅም።
ከስምንት ወር በሁዋላ አይቼው የማላውቀውን የፌስቡክ አካውንቴን ከፍቼ ስመለከት መጀመሪያ ላይ የመጣው ፎቶ ቃልዬ ከሁለት ቀን በፊት የለጠፈችው ቀለበት ስታስር የተነሳችው ፎቶ ነበር። ቀለበት ያሰረችው ግን ከዛኪ ሳይሆን ከሌላ ወንድ ጋር ነው።
"ቃልዬ ከተመረቅን በሁውላ ከዛኪ ጋር አብረን እንደማንቀጥል እርግጠኛ ነኝ " ያለችው እውነት ነበር ማለት ነው አልኩ። ስልኬን ወርውሬ ግርግዳው ላይ ለጠፍኩት ፣ ብትንትኑ ወጣ።
ከተበታተነው የስልኬ ስብርባሪ መሀል ግን የቃልዬ የቀለበት ፎቶ ቅዳጅ አልነበረም።
ዳግም ህመም ዳግም ግርሻት ፣ ዳግም ስቃይ። አወይ ፍቅር ግርሻቱም አይጣል ነው ለካ።
ስልኬን ከሰበርኩት ከአንድ ወር በሁዋላ እህቴ ከወራት በፉት  በገዛችልኝ ሚኒባስ ውስጥ ቁጭ ብዬ ሰው እስኪሞላ መሪው ላይ ተደፍቼ  እየጠበኩ ነው።
መኪና ውስጥ የሚለጠፉ ጥቅሶችን እያዞረ የሚሸጥ አንድ እድሜው ከአስራ አራት የማይበልጥ  ልጅ እግር  በጋቢናው በኩል መጥቶ ምርጥ ምርጥ ጥቅሶች በቅናሽ ዋጋ እያለ የያዛቸውን ጥቅሶች ተራ በተራ እያነበበ ነው ።  አራት ጥቅሶችን አንብቦ አምስተኛው ላይ ሲደርስ እንደመባነን ብዬ ከመሪው ላይ በፍጥነት ቀና አልኩና•••
"እስቲ ቆይ ቆይ አሁን ያልከውን ድገመው !" አልኩት። ደገመው ከጠየቀኝ ሂሳብ በላይ እጥፉን ከፍዬ ጥቅሱን ገዛሁትና መኪናዬ ዳሽ ቦርድ ላይ ለጠፍኩት።

ወረቀቱ ላይ የተፃፈው  ••••
"ባልንጀራህን እንደራስህ አድርገህ ውደድ ቢልም ፣ ለባልጀራህ ሁሉን ሚስጥርህን ንገረው ግን አይልም"
የሚል ጥቅስ ነበር ። መታሰቢያነቱ ለኪያ።           .
                      .
                      .
                      .
      •••••••ተፈፀመ ••••••••
                      .
                      .
                      .
                      .
ለነበረን ቆይታ ከልብ አመሰግናለሁ ❤❤


.

.
ቤተሰቦቼ በሌላ ልብ ወለድ እንገናኛለን። በአጠቃላይ በታሪኩ ላይ ጠቅለል ያለ ሀሳብ አስተያየታችሁን ፣ ወደፊት ቢስተካከል የምትሉትን ነገር ሁሉ በኮሜንት መስጫው ስር እንደምታስቀምጡ ተስፋ እናደርጋለን 🙏🏻

https://vm.tiktok.com/ZMkkFephM/

8.5k 0 24 36 183

❤️ ተማሪዋ ❤️


❤️….. ክፍል 49 …….❤️


"ምን እሚሉት ጥያቄ ነው እስከዛሬ ምን ያህል እንደማፈቅርህ አታውቅም እና ነው ቆይ ምንድን ነው የሆንከው ፊትህ እኮ ልክ አይደለም?"
"ፉቴ ብቻ አይደለም ሁሉ ነገሬ ልክ አይደለም ቃል እባክሽ ለምጠይቅሽ ጥያቄ ብቻ መልስ ስጪኝ አንቺ ምንም ነገር አትጠይቂኝ"
"እሺ"
"ታፈቅሪኛለሽ ቃል"
"አዎ ኤፍዬ አፈቅርሀለሁ"
"ዛኪንስ ታፈቅሪዋለሽ ቃል?" ስላት ፊቷ ላይ ያየሁት ድንጋጤ እኔኑ አስደነገጠኝ።
ያ ድንጋጤዋ ነበር  የመጨረሻውን መርዶ ያረዳኝ። በቃ የቃልዬን መልስ  ድንጋጤዋ ውስጥ አየሁት።
ቃልዬ ብዬ ጠራሁዋት አይን አኗን እየተመለከትኩ።
ወዬ ማለት አልቻለችም። በቃ አቃታት። የኔም የሷም አይኖች እኩል እንባ አቀረሩ።
" ቃልዬ!" ብዬ ደግሜ ጠራኋት።
አይን አይኔን ከማየት ውጪ አቤትም ወዬም ማለት ተሳናት ቃል አፏ ተለጎመ።  የስረኛው ከንፈሯ  ይንቀጠቀጥ ጀመር።
ጣቴቻን በጣቶቿ እያፍተለተለች ተለጎመች የኔ ቃል።
ሁሉን ነገር እንደደረስኩበት ውስጧ ነግሯታል።
ይህን  ሳስብ አመመኝ ።
ቃልዬ ሁኔታዋ አንጀት ይበላል።
የሚታዘንልኝ እኔ ሆኜ ሳለሁ ቃልዬ በዛ ልክ ጭንቅ ጥብብ ሲላት ሳይ አሳዘነችኝ።
ያን ሲተናነቀኝ የነበረውን እውነት መናገር ጀመርኩ•••
ቃልዬ አውቃለሁ ሁሉን አውቃለሁ።  ከቀናት በፊት ሀረር እስከሄዳችሁባት አስቀያሚ ቀን ድረስ ይቺ ቅፅበት በኔና ባንቺ መሀል እንዳትፈጠር ስሸሻት ኖሪያለሁ።
ነገር ግን እውነትን መሸሽ ከሞት እንደማያድነኝ ተረዳሁ። አዎ ቃልዬ አንቺን ከማጣ ሞቴን እመርጣለሁ፣ መሞት አልፈልግምና አንቺን ማጣት እፈራለሁ።
እኔ ስለፈራሁት  እኔ ስለሸሸሁት የሚቀር ነገር የለም።
ሁሌም አፈቅርሻለሁ። ምንም ብትበድይኝ ምንም ብትጎጂኝ አንቺን አለማፍቀር እስክችል ድረስ አፈቅርሻለሁና  ዛሬም ቢሆን አንቺን  ክፉ የምናገርበት አንደበት የለኝም።
ክፉ ይናገረኛል አልያም ይጎዳኛል ብለሽ እንዳታስቢ እሺ? ፣ እኔ አንቺን የማፈቅርሽ የእውነት ነው ፣ የማፈቅርሽ ግን የኔ ስለሆንሽ ብቻ አይደለም።
ዛሬም የማልፈልገው አንቺን አለማፍቀር ሳይሆን እየታመምኩ፣ እየተረበሽኩ፣ እንቅልፍ እያጣሁ፣ የተበዳይነት፣ የተገፊነት ስሜት እያንገላታኝ ማፍቀርን ነው።

ነገ ከነገ ወድያ ላጣሽ ልትለይኝ እንደምትችይ እያሰብኩ ማፍቀር ደከመኝ ቃልዬ።
አብሬሽ ሆኜ የተሰቃየሁት ስቃይ አጥቼሽ ከምሰቃየው ጠናብኝ ቃልዬ ።
ሀለቱም ለኔ ህመም ቢሆንም ከእውነት ጋር መታመም ይሻላል እውነትን ሸሽቼ የማላመልጥበት ደረጃ ላይ ደርሻለሁና የምደበቅበት የምሸሽበት የለኝም እውነቱን ልጋፈጠው የተገደድኩት ሁሉ ነገ ካቅሜ በላይ እስከሚሆን ታግሼ ነውና በውሳኔሽም በውሳኔዬም እንደማልፀፀት ተስፋ አደርጋለሁ።
አንድም ቀን በዚህ ልክ ትጎጂኛለሽ ብዬ አስቤ አላውቅም ነበር ቃልዬ።
ዛሬ እውነቱን ካንቺ አንደበት ሰምቼ ሀቁን ልጋፈጠው ወስኛለሁ። ስለትናንት አልወቅስሽም፣  ስለነገም አላውቅም አሁን የምፈልገው በራስሽ አንደበት እውነቱን እንድትነግሪኝ ብቻ ነው ቃልዬ።
" ዛኪን ታፈቅሪዋለሽ አደል ቃል?"
"እ ቃል እባክሽ ንገሪኝ ዛኪን ታፈቅሪዋለሽ አደል?"
ቃልዬ መልሷ ማልቀስ ብቻ ሆነ። ከጎኔ ቁጭ ብላ ስታለቅስ ሰውነቴ መንቀጥቀጥ ጀመረ። እራሴን ፈራሁት። ስሜታዊ ሆኜ ቃልዬ ላይ እጄን እንደማልሰነዝር ባውቀውም እራሴን ፈራሁት ከአጠገቧ ተነስቼ  በመራቅ  ፊት ለፉቷ ተቀመጥኩ።
አቀርቅራ ስታለቅስ ቆየችና ድንገት ቀና ብላ
"ኤፍዬ ይቅርታ!" አለችኝ። ሰማይ ተደፋብኝ። ቤቱ የሚሽከረከር መሰለኝ። ከተቀመጥከበት እንዳልወድቅ አይኔን ጨፍኜ ግርግዳውን ተደገፍኩ።
"ኤፍዬ ይቅርታ !" አለች በድጋሚ። መልስ አልሰጠኋትም።
ቃልዬ ቀጠለች ••••

"እኔና ዛኪ እዚህ ግቢ ትምህርት እንደጀመርኩ የዛሬ ሶስት አመት ነው በፍቅር አብረን የሆነው ፣ " ስትል ገና ከግር ጥፍሬ ጀምሮ ሁለመናዬን ወረረኝ። እያየኋት ልሰማት አቅም አጣሁ። ጭንቅላቴን ጉልበቶቼ መሀል ደፍቼ አቀረቀርኩ ። ቃልዬ ቀጠለች...

"ፍቅር ጀምረን ወራት ያህል እንደቆየን ስለሱ ብዙ ነገር እሰማ ጀመር ከብዙ ሴት ጋር እንደሚቀራረብ ባውቅም አምነው ነበር። ሁሉንም ነገር የምሰማው በውሬ ነው። ስጠይቀው ይክደኛል ። ያን ቀን አንተና እኔ በተገናኘንበት ምሽት አንዷ ሴት ጋደኛዬ ዛኪ ከሌላ የግቢ  ሴት ጋር  የለበትን ሆቴል ነግራኝ ነበር ሳንቲም እንኳን ሳልይዝ አለ ወደተባለበት በርሬ የሄድኩት።
ግን አጣሁት መመለሻ ሳንቲም እንኳን ልነበረኝም ። ዛኪን ከዛ በኋላ አብሬው ላልቀጥል ወስኜ ነበር። ለምን በዛ ሰአት እዛ ሆቴል በር ላይ እንደቆምኩ አንተ  ስጠይቀኝ ሌላ ግዜ እነግርሀለሁ ነበር ያልኩህ። ዛኪን አየሁት ብላ የደወለችልኝ ሴት ያንን አጋጣሚ ተጠቅማ አብረዋት  ከነበሩ ሁለት ወንዶች መሀል ከአንደኛው ጋር ልታቀራርበኝ ስትሞክር ተናግሪያት ወጣሁ። በዛ ሰአት ነበር አንተ መጥተህ ፊት ለፉቴ የቆመከው ። ይህንን ደሞ በመጠኑም ቢሆን ነግሬሀለሁ። ኤፍዬ የኔና ያንተ ነገር  ከተዋወቅንባት ምሽት ጀምሮ መቀራረባችን እና ወደ ፍቅር መግባታችን እንዴት እንዴት እንደፈጠነ ታውቃለህ።
እኔና አንተ ወደፍቅር በገባንባት ሁለት ወር ውስጥ  ከዛኪ ጋር ተኮራርፈን ነበር ።ድጋሚ የምታረቀውም አልመሰለኝም ነበር።
ነገር ግን ልጅቷ ሆን ብላ እኔን ለሌላ ወንድ ለማጣበስ ስለሱ መጥፎ እያወራች እንዳጣላችን በየቀኑ እየመጣ ይነግረኝ ነበር።  መውጫ መግቢ መቆሚያ መቀመጫ አሳጣኝ። ካንተ ጋር ሆኜ እንኳን ስንቴ እንደሚደውልና ስንቴ ተነስቼ ካጠገብህ እየሄድኩ እንደማዋራው ታስታውሳለህ።
በቃ ታረቅን።  እኔና እሱ ስንታረቅ በጣም ተጨነቅኩ።  ዛኪን የታረቅኩት ትምህርቴን ተረጋግቼ ለመጨረስ ብቻ ነበር።
አንተን ልጎዳ ብዬ ያደረኩት ምንም ነገር የለም ። ከዛኪ ጋር እዛ ግቢ ውስጥ እስካለሁ ድረስ መውጫ መግቢያ ስለሚያሳጣኝ መለያየት ከባድ ቢሆንም አብረን እንደማንዘልቅና ከተመረቅን በኋላ እንደምንለያይ እርግጠኛ ነኝ። አንተን •••ብላ ልትቀጥል ስትል መስማት አቅለሸለሸኝ።

የመጨረሻ ክፍል ረቡዕ ማታ 2:00 ላይ ❤️🙏🏻

https://www.instagram.com/reel/DD6fkUSu_mv/?igsh=MWRkNjA2dWFvMzg1eg==

6.9k 0 14 24 216

❤️❤️ተማሪዋ❤️❤️
.

🌹🌹…….ክፍል 48 ……🌹🌹

.

አላወቅኩም ቆይ እስቲ ጥበቃውን ልጠይቅልሽ " ብያት ወደ ጥበቃው ስመለስ አሁንም እማርኛ እና የነጮቹን አፍ እየቀላቀለች ስላስቸገርኩህ ይቅርታ አይነት ነገር አለች ። መልስ ሳልሰጣት ሄጄ ጥበቃውን...

"አባባ የሚላላከው ልጅ አለ እንዴ ? ዲያስቦራዋ ፈልጋው ነበር?'' አልኳቸው።

"ውይ ፈለገችው እሱማ መሄጃ ሰአቱ ደርሶ ወጣኮ ምሽት ሁለት ሰአት ወደ ቤቱ ሄደ። ምን ፈልጋ ይሆን ?" እያሉ አብረውኝ ተመለሱና ልጁ እንደለለ ነገሯት።

እዛው ቆም ብዬ እኔ ከወጣሁ በኋላ የተያዙና መብራት የበራባቸውን ክፍሎች ገልመጥ ገልመጥ እያልኩ ስቃኝ። ዲያስቦራዋ ልጁን የፈለገችው ቢራ ከውጪ ገዝቶ እንዲያመጣላት እንደነበር ስትነግራቸው ጥበቃው አንዴ እሷን

አንዴ እኔን አንዴ በሩን በየተራ እየተመለከቱ።

"አይይይ ግድ ከሆነና ካስፈለገሽ እኔው ሄጄ ላምጣልሽ ይሆን የኔ ልጅ?••• ልጁማ ሰአቱ ደርሶ ወጣኮ ቀደም ብትይ ደግ ነበር?'' አሏት። አሳዘኑኝ። ለሷ ሳይሆን ለሳቸው ስል አንዳፍታ ገዝቼ ላቀብላትና ገብቼ ልተኛ አሰብኩና

"ችግር የለውም አባቴ እርሶ ከሚሄዱ እኔ አመጣላታለሁ"

ስላቸው ገና መርቀውኝ ሳይጨርሱ ለሳቸው ጉርሻ መቶ ብር ጨምራ የቢራ መግዣውን ብር ሰጠቻቸው ።

የሳቸውን ለሳቸው ሰጥቼ ቢራውን ልገዛላት ስንቀሳቀስ ከዳግም ምርቃታቸው አስከትለው ቆይ የኔ ልጅ ጠርሙስ ካልያዝክ ማስያዣ ይጠይቁሀል ጠብቀኝ ጠርሙስ ላምጣ ብለውኝ ግቢ ውስጥ ወዳለ አንድ ክፍል አምርተው አራት የቢራ ጠርሙስ ይዘውልኝ መጡ።

ተቀብያቸው ልወጣ በሩን ከከፈትኩ በኃላ እዛ አከባቢ በግራም በቀኝም ሆቴል አለማየቴን አሰብ አድርጌ••••

"እታች ወርጄ ነው የምገዛው አደል አባባ እዚህ አከባቢ በቅርብ ሆቴል የለም አደል?" ስላቸው •

"ውይ የኔ ነገር የምትገዛበትን ሳላመላክትህ ሰደድኩህ አደል የኔ ልጅ ፣ ለካ አታውቀውም እያሉ ከግቢ ወጡና ካለንበት በቀኝ በኩል ትንሽ ሄደት ብዩ ወደ ግራ ቁልቁል የምትወስድ ቀጭን

መንገድ እንዳለችና ገባ እንዳልኩ ሆቴል እንደማገኝ ነገሩኝ። ከዚህ በፊት አላውቀውም ሆቴሉን ምናልባት በቅርብ የተከፈተ ይሆናል እያልኩ ወደ ሆቴሉ አቅንቼ ግቢ ውስጥ ስገባ ግቢው ጭር ያለ ነው ። ወደ ሆቴሉ ከሩቅ ሳማትር አለፍ አለፍ ብለው ወንበር ይዘው በተከፈተው ለስላሳ ሙዚቃ የሚዝናኑ ውስን ሰዎች ይታያሉ።

ራመድ ራመድ እያልኩ ወደሆቴሉ ዘው ብዬ እንደገባሁ ፊት ለፊት ባየሁት ነገር ልቤ ስንጥቅ አለች። ወይኔ አምላኬ ምንድን

ነው የማየው ? ጭራሽ እኔ የገዛሁላትን አዲሷን ልብስ••• እያልኩ በሁለቱም እጆቼ ሁለት ሁለት ባዶ የቢራ ጠርሙዝ እንዳንጠለጠልኩ ድንጋጤዬ አብረክርኮት አልራመድ ያለኝን እግሬን በግድ እየጎተትኩ በቀስታ ወደ ተቀመጡበት ወንበር ተጠጋሁ በሆቴሉ ውስጥ  ጭልም ደሞ ብርት የሚሉ ሲበሩም ደብዛዛ ብርሀን የሚፈነጥቁ ጌጣማ አንፖሎች እዛም እዛም ተሰቅለዋል ፣
ቀረብ ስል ግራ ገባኽ አብሯት ያለው ወንድ ፊቱ በደንብ ታየኝ። ዛኪ አይደለም።ገዘፍ ያለ ነው። አስተያየቱ  ደሞ ያስፈራል። ገልመጥመጥ ሲያደርገኝ እነሱን እያየሁ በቀጥታ ወደነሱ መሄዴን ቀየር አደረኩና እንደማለፍ ብዬ አየት ሳደርግ ልጅቷም ቃልዬ አይደለችም። ቀሚሱዋም ዲዛይኗ የቃልዬ አይነት ቢሆንም ' ከለሯ 'በተወሰነ መልኩ ይለያል።
የስራሽን ይስጥሽ ቃልዬ፣ ግራ የገባኝ ደግሞ ተከትያት ሀረር ከመጣሁ በሁዋላ የተጠናወተኝ በቅርብ ርቀት ያየኋት ሴት ሁሉ ቃልዬን የምትመስለኝ በሽታ ነው ፣ ይሄ መታመም ካልሆነ ምን ይሆናል ? እያልኩ ቢራውን ገዝቼ ተመለስኩ።
የግቢው ጥበቃ የቀራቸውን ምርቃት ሁሉ አሟጠው መረቁኝ።
"የእኔን እድሜ ያድለህ ፣ ጧሪ አያሰጣህ፣ የማታ እንጀራ ይስጥህ፣ የልጅ ልጅ ያሳይህ•••••" ሌላም ሌላም ብዙ ምርቃቶች።
"አባባ " አልኳቸው እንደጨረሱ።
"ወዬ የኔ ልጅ"
"ፍቅር ይዝለቅልህ!" ብለው ይመርቁኝ አልኳቸው እንባ እየተናነቀኝ።
"ፍቅር ይዝለቅልህ ፣ የወድድካትን ያፈቀርከትን ክፉ አይይብህ ፣ ትዳርህን ይባርክልህ !
" አሜን አሜን አሜን አባቴ" አልኳቸው ዋናው እሱ ነው ። እኔ የልጅ ልጅ ማየት የምፈልገው ከቃልዬ ነው። ከቃልዬ ከነጠለኝ በሁዋላ ረጅም እድሜ ምን ሊጠቅመኝ። እያልኩ ቢራውን ሰጥቻት ወደ ክፍሌ ገባሁ።

ቃልዬ ከዛኪ ጋር ማደሯን ማሰብ አስፈሪ እንደሆነብኝ ድካምና ረሀቡ ነው መሰለኝ የወደቅኩበትን ሳላውቅ ነጋ።
ጥዋት ወደ ድሬ ዳዋ ስመለስ ቃልዬ እራሷ እስክትደውል ላልደውልላት በናቴ ማልኩ።
ሳትደዉል መሸ፣ ሳትደውል ነጋ ፣ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ቀንም እንደዛው ልደውል ስልኬን ካወጣሁ በሁዋላ በናቴ መማሌ ትዝ ሲለኝ  ስልኬን ወደ ኪሴ እመልሰዋለሁ።
በአራተኛው ቀን ደወለች ።
"ይቅርታ ኤፍዬ በዚህ ምርቃት ሰበብ ተዋክቤ፣ ቻርጀሬ ጠፍቶ ፣ ባትሪ ዘግቶ••••"   ብዙ ብዙ  አለች ፣ ለመጥፋቷ  ብዙ ምክንያት ብዙ ሰበብ  ተናገረች ቃል። ዝም ብዬ ሰማኋት።
ስትጨርስ አንድ ነገር ብቻ ተናገርኩ ።   አንድና አንድ  ነገር ብቻ አልኳት።
"ችግር የለውም ቃልዬ በጣም ላገኝሽ እፈልጋለሁ መች ይመችሻል?" የሚል ጥያቄ ብቻ ሰነዘርኩላት። ድምፄ መሰባበሩ ለኔ ቢታወቀኝም ለሷ አላታወቃትም አልያም አላስተዋለችውም።
"ኤፍዬ አብረን ለመዋል ከሆነ ነገ ፣ ለማደር ከሆነ ግን ከነገ ወድያ"
"አይ ችግር የለውም አብረን ውለን ትሄጃለሽ"
"በቃ ነገ ከሰአት ደውልልኝ "
የቃልን ስልክ እንደዘጋሁ ጌትነት ስልክ ላይ ደወልኩ።
እቤቱን ለአንድ ቀን እንደምፈልገው ነገርኩት።
"ችግር የለውም ኤፍዬ ማደርም ትችላለህ እኔ ጀለሶቼ ጋር እሄዳለሁ" አለኝ።
ቃልዬን ላመጣት ስሄድ ለጌትነት ደውዬ  ልመጣ ነውና ቁልፉን አስቀምጠህልኝ ሂድ አልኩት።

ደረስኩ ተገናኘን ። ስማኝ ከጀርባ ገባች። ደንዝዣለሁ። ምንም አላወራም ቃልዬ ግን ምን ያህል እንደናፈቅኳት ፣ ስለሰሞኑ የምርቃታቸው ወከባ ምን ያህል ግዜ እንዳሳጣት እያወራችልኝ የማውራት እድል ሳትሰጠኝ  እነ ጌትነት ቤት ደረስን።የማውራት እድል ብትሰጠኝ ምን እንደማውራ አላውቅም።
ገብተን ትንሽ እንደቆየን ከምን እንደምጀምር ምን እንደምላት ጨነቀኝ።
ካንድም ሁለት ሶስቴ ልጀምር እልና የሆነ የሚረብሽ ስሜት እየተናነቀኝ አቋርጠዋለሁ። ተነስቼ ወደ መታጠቢያ ቤት እሄድና በቀዝቃዛ ውሃ ፊቴን ታጥቤ እመለሳለሁ።
ቃልዬ ቡና ለማፍላት እየተንጎዳጎደች ሁኔታዬን ማስተዋል አልቻለችም።
አቦሉን እንደጠጣን •••
"በቃ ሁለተኛውን አታፍይ ይቅር " አልኳት።
"ለምን ኤፍዬ?" አለችኝ ፊት ፊቴን እያየች።ፊቴ ልክ እንዳልሆነ ያስተዋለችው ያኔ ነበር። መጥታ አጠገቤ ተቀመጠች።
"ምን ሆነሃል ኤፍዬ ችግር አለ?" አለችኝ አገጬን ይዛ ወደግራም ወደቀኝም ገልበጥ ገልበጥ እያደረችኝ።
"አዎ ችግር አለ ቃል"አልኳት አገጬ ላይ ያለውን እጇን ይዤ ከአገጬ ላይ እያወረድኩት።
"ምንድን ነው እሱ?" አለችኝ ልቧን በግራ እጇ ደገፍ አድርጋ እየተመለከተችኝ። ልቧ ነገራት ብዬ በውስጤ እያሰብኩ  ዝም አልኩ።
"ኤፊዬ!" ብላ ተጣራች።
"ወዬ ቃል"
"ምን ሆነሀል ?" ምን ሆንኩ እንደምላት ቸገረኝ።
"ቃልዬ" አልኳት።
"ውዬ"
"ታፈቅሪኛለሽ?"
.
.
ክፍል 49 ከ150 ላይክ ቡሀላ ይቀጥላል



https://t.me/saloda_trading

6.2k 0 15 14 232

❤️ ተማሪዋ ❤️

🌹………ክፍል 47 …………🌹
.
.
.
.
ሊጠናቅ 3 ክፍሎች ብቻ ቀሩት 🫶ሼር ይደረግ


ጅቦቹ ቢኖሩም እነቃልዬ እዛም የሉም። የት ይሆኑ? እኔና እሷ ያደርንበት ሆቴል ይዛው ትሄድ ይሆን? እሱም ለሀረር አዲስ ከሆነ ሁለቱም ሀረርን በደንብ ስለማያውቋት ወደምታውቀው ወደዛው እኔና እሷ ወደነበርንበት ነው ይዛው የምትሄደው በርግጠኝነት ሌላ ቦታማ አያድሩም።

ደሞ ፀጥታውን ወድጄዋለሁ ስትል አልነበር እዛ ነው የሚሄዱት።

እኔና ቃልዬ ያደርንበት ፔንስዬን በር ላይ ስደርስ ከምሽቱ ሶስት ሆኖ ነበር።

ገባሁ... ጥበቃውን ሰላም ስላቸው አላስታወሱኝም። ቀጥታ ወደሚከፈልበት ክፍል ገብቼ ከፈልኩና ቁልፍ ወስጄ ቁልፉ ላይ ባለው ቁጥር መሰረት ወደ ክፍሌ አመራሁ። ቃልዬ እዛው ግቢ ውስጥ ብትሆን እና ብታየኝ ደንታ አልነበረኝም። እሷ አየኝ አላየኝ ብላ ትፍራ እንጁ እኔ ምን አስፈራኝ እያልኩ ከክፍሌ ወጥቼ የግቢው ጥበቃ ወደሆኑት ሰው ሄድኩና ሰላም ብያቸው እዛው እሳቸው ካሉበት በስተግራ የግንብ አጥሩ ስር ባለች አንዲት ጠፍጣፋ ድንጋይ ላይ እየተቀመጥኩ...

"ስገባ አላወቁኝም አደል አባባ? እኔም እገሌ ነኝ ሳልሎት ገባሁ እንጂ እንዳላወቁኝ አውቁያለሁ?" አልኳቸው።

"ኧረ አለየሁህም የኔ ልጅ ይቅር በለኝ የኔ ልጅ"

"ችግር የለውም የዛሬ ሶስት ወር አከባቢ ከሴት ጓደኛዬ ጋር መጥተን ነበር"

"አይ የኔ ልጅ እዚህ ስንቱ በየእለቱ እየመጣ ይሄዳል ማንን ከማን ለይቼ አውቃለሁ ብለህ ነው?"

"በርግጥ ልክ ኖት ከባድ ነው፣ ያኔ ግን ልንሄድ ተሰናብተናት ከወጣን በሁዋላ ተመልሰን መጥተን ነበር ፣ እንደውም ደግ አደረጋችሁ እንኳን ተመለሳችሁ የማታ ጉዞ ጥሩ አይደለም ብለውን ነበር አያስታውሱም?"

ውይ ውይ ውይ አስታወስኩ ጥዋት ስትሄዱ ቁርስ ይብሉበት አባቴ ብላ ብር የሰጠችኝ ልጅ ከሷ ጋር የነበርከው አንተ ነህ አደል ይቅር በለኝ የኔ ልጅ ታድያ እሷን የት ጥለሀት መጣህ ደና ነች??

እሷ ጣለችኝ እንጂ እኔማ ቃልዬን ጥዬ የት እሄዳለሁ አልኩና ለራሴ ለሳቸው...

"አይ እኔ አልተመቸኝም ነበርና እሷ ከወንድሟ ጋር ቀድማኝ ነው የመጣችው፣ ደሞ ክፋቱ ስልኬን እቤት ረስቼው መምጣቴ ነው፣ እዚሁ አልጋ እንደሚይዙ ነበር ከመምጣታቸው በፊት ያወራነው

ምናልባት በአንዱ ክፍል ከሆኑ ብዬኮነው ወደዚህ አልመጡም አደል አባቴ ?"

"ኧረ አልመጡም የኔ ልጅ ይሄው እንግዲህ አዳሬም ውሎዬም እዚሁ ነው ። ዛሬ በግቢው ሶስት ክፍል ብቻ ነው የተያዘው ሁለቱ ጠና ጠና ያሉ ሰዎች ናቸው።

አንደኛዋ እንኳን እዚሁ ነው የከረመችው እዛ አንተ አሁን ገብተህ ከወጣህበት ጎን በስተግራ ነው ያለችው ። ዲያቦራ ነው ምን አላችሁት ስማቸውን ብቻ ከውጪ ነው የመጣችው "

"ዲያስቦራ”አልኳቸው

" አዋ እንደዛ ነች ቀን ቀን ዘመዶቿ ዘንድ እየዋለች አዳሯ እዚህ መሆኑን ነው የሰማሁት " ከነሱ ውጪ ማንም የለም እንግዲህ ምናልባት ከተማ አምሽተው ሊመጡ ይሆን የኔ ልጅ ? " አሉኝ። "ይሆናላ አባቴ" እስቲ መጣሁ ከሌላ ሰውም ቢሆን ስልክ ለምኜ ልደውልላት። ብያቸው ልወጣ ስል

"እህ ና ከዚሁ መደወል ትችላለህ የኔ ልጅ ና ግባና ሂሳብ ክፍሏን አስደውይኝ በላት" አሉኝ ፡፡

"ችግር የለውም አባቴ ስልክ አላጣም" ብያቸው ወጣሁ። ስልክ መች አጣሁ የጠፋችብኝው ቃልዬ ነች እንጂ እያልኩ ። ስልኬን ከኪሴ አወጣሁና ቃልዬ ስልክ ላይ ደወልኩ።

"የደወሉላቸው ደንበኛ ከአገልግሎት መስጫ ክልል ውጪ ናቸው ትላለች ፣ ቃልዬ እኔን ከገልግሎት መስጫ ክልል ውጪ አደረገችኝ እንጂ እሷማ እዚሁ ነች።" እያልኩ ሁለተኛ ዙር ፍለጋዬን ጀመርኩ እኔና ቃልዬ የሄድንበትንም ያልሄድንበትንም ቦታ ሁሉ እየገባሁ ፈለኳት የለችም። የሚወስድ ይውሰደውና የት እንደወሰዳት ግራ ረባኝ።

ምናልባትም ቃልዬ ያን ግዜ መጨፈር እየፈለገች በግድ ይዣት ስለወጣሁ እስኪወጣላት ልትጨፍር ወደዛ ጭፈራ ቤት ቆይተውም ቢሆን መምጣታቸው አይቀርም በሚል ተስፋ ወደዛው ሄድኩና ጥጌን ይዤ መጠጣት ጀመርኩ። በባዶ ሆዴ ስለነበር የምጠጣው ወድያው ነበር አናቴ ላይ የወጣው። እነ ቃልዬ ሳይመጡ የቃልዬ ዘፈን መጣ፣ ያ ከወጣን በሁዋላ ገብተን ካልደነስንበት ያለችኝ ዘፈን••• የብሶት ስሜት ከደረቴ ስር

ሲፈነቀል የተሰማኝ ገና ክላሲካሉ ላይ ነበር ።

ዘፈነ ፀሀዬ...

ጥንድ ጥንድ ሆነው ሲሄዱ ባይ ሳጣሽ የኔን ሲሳይ ፣ ቀናሁ በሰዎች ላይ ዛሬም ሳላይሽ ላድር ነው ወይ እባክሽ ነይ ዝርያዬን ባስስ ባስስ አንቺ እንደሁ የለሽም

ባንጋጥጥ ወደሰማይ••••

ቃልዬን በአይነ ህሊናዬ ፊት ለፊት እያየኃት አብሬው ዘፈንኩ። ቃልዬ ሳትመጣ ዘፈኑ አለቀ።

በር በሩን እያየሁ እኩለ ለሊት አለፈ። ከብዙ ግራ የገባቸው ዘፈኖች በኋላ የመጣው አንድ ዘፈን የብሶት ሰንኮፌን ሁሉ አጥቦ አወጣው።

በቃልዬ ፍቅር የመጨረሻውን ብሶት እና ምሬት ፣ የመጨረሻውን ሀዘን እና መከፋት የማስተናግድበት የመጨረሻው ሰአት እስኪመስለኝ ዘፈኑንን እየሰማሁ አብሬው ስዘፍን እስከዛሬ ለማንም አልቅሼ የማላውቀው እኔ ኤፍሬም ለቃልዬ አነባሁላት። ዘፈኑ ሲያልቅ ወደ ዲጄው ሄድኩና በፍቅር አምላክ ይሁንብህ ይሄን ዘፈን ድገመው አልኩት።

"ኧረ ጣጣ የለውም ከፈለክ በመሀል በመሀል ሌላ ዘፈን እያስገባሀ አምስቴ እደግምልሀለሁ አያሳስብህ!"

"አይ በመሀል ሌላ ዘፈን ሳታስገባ አሁኑኑ ድገመው እባክህ" አልኩት ደገመው...

ሳላስብ ትተሽኝ ቢጠፋኝ ሚስጥሩ በንባ ተጥለቅልቀው አይኖቼም ታወሩ አንቺ አለሽኝ ብዬ ለሁሉም ሳወራ ብቸኛ አረግሽኝ ለንባዬ ቦይ ልስራ ትዝ አይልሽም ወይ አቅፌሽ አቅፈሽኝ...

ያ. ጫወታና ሳቅ እየደባበሽኝ በዛ ደስታ ምትክ እንባ ፈረድሽበት ኧረ ምን ተሰማሽ ምን ይላል ያንቺ አንጀት....ዘፈኑ ሲያልቅ ውስጤ የነበረው መጥፎ ስሜት ሁሉ በንባ ተጠርጎ የወጣ ያህል ቅልል አለኝ። ከዛ በሁዋላ እዛ ቤት መቆየትም ሌላ ዘፈን መስማትም ቃልዬን መፈለግም አልፈለኩም። አልጋ ወደ ያዝኩበት ክፍል አመራሁ። የግቢው ጥበቃ በሩን እንደከፈቱልኝ

"አላገኘሀቸውም የኔ ልጅ?" አሉኝ።

"አዋ አባባ " ብያቸው ብቻ ገባሁ።

ወደክፍሌ ሳመራ ዲያስቦራ የተባለችው ከኔ ክፍል ጎን ያለችው ሴት የክፍሏን መስኮት ከፍታ በለሊት ልብስ እንደቆመች ፀጉሯን እየነካካች ወደ ግቢው ታማትራለች። እድሜዋ ከሰላሰ ብዙ አይርቅም። ስታየኝ አየኋት። ምን ታፈጣለች እሷም እንደኔ የጠፋባትን ፍቅረኛዋን ፍለጋ ነው እንዴ የመጣችው እያልኩ ወደ ክፍሌ እየሄድኩ ደግሜ አየት ሳደርጋት አሁንም እያየችኝ ነው። አስተያየቷ የሆነ ነገር ልትጠይቀኝ የፈለገች ትመስላለች ። ፊቴን መልሼ ወደ ክፍሌ ራመድ ስል••..

"ይቅርታ ወንድም ኢዝ ዜር ኖ ሆስት?" አለችኝ። ወይ ጣጣ ለራሴ ሂወት ተደበላልቆብኛል የምን ድብልቅልቁ የወጣ ነገር ነው የምትናገረው ይቺ ደሞ አልኩና ለራሴ ። ግቢው ውስጥ አልጋ ለያዙ ሰዎች የሚያስፈልጋቸውን ከውጪ ገዝቶ የሚያቀርበውን አስተናጋጁን ፈልጋ እንደጠየቀችኝ ቢገባኝም

"ምን አልሽኝ?" አልኳት እሷን።

"ሰው የለም ግቢ ውስጥ መልክት መላክ ፈልጌ ነበር" አለችኝ ያው እንግሊዘኛውን እንግሊዘኛውን በሚል አነጋገር። እና ከውጪ ቆልፈውብሽ ነው እንዴ የሄዱት ወጥተሽ አጠይቂም እያልኩ በሆዴ...
.
.

https://vm.tiktok.com/ZMk8WD6kN/

8.7k 0 18 56 273

ቀጣይ ክፍል 46 ማታ 2 ሰአት ይለቀቃል


❤️ተማሪዋ❤️
.

.

🌹…….. ክፍል 45…….🌹
.
.
ልክ እሩብ ጉዳይ ለሰባት ላይ ዛኪ በርሳ ጀርባው ላይ ጣል አድርጎ ከግቢ ብቅ ሲል አየሁት።ቃልዬ ተከተለችው ፣ ዘንጣለች። ቀድመው ደወለው ነው መሰል ባጃጅ በር ላይ ነበር የጠበቃቸው።

ተከታትለው ገቡ፣ ከሀለቱ ውጪ ሌላ ሰው ወደባጃጇ አልገባም።

ባጃጇ ተነስታ መሄድ እንደጀመረች ብዙም ሳትርቅ ተከተልኳት።

ቀጥታ ወደ መነሀሪያ ነው እየሄዱ ያሉት። የምይዝ

የምጨብጠው ግራ ገባኝ።

ልክ ሼል ደርሰው ወደ መናሀሪያ ከመዞራቸው በፉት አንዲት ሚኒባስ ስትክለፈለፍ መጣች። ሀረር ሁለት ሰው አለ ረዳቱ

አንገቱን ብቅ አድርጎ።

እነቃልዬን የጫነው ባለባጃጅ ለሚኑባስ ረዳት በእጁ ምልክት አሳየው ሚኒባሷ ቆመች ። እነቃልዬ ከባጃጇ ላይ ወርደው ሚኒባሷ ውስጥ ገቡ። ወደ ሀረር ነጎዱ።

የሰው ባጃጅ መሪ በቡጢ እየመታሁ እዛው በቅርቤ ወዳለው ማደያ አስጠጋሁና አቆምኳት፣ ቀልፉን እኔም ጋደኛዬም ለምናውቀው ነዳጅ ቀጂ ሰጥቼው ለጋደኛዬ ደውዬ ነገርኩትና ወደ ሀረር ለመሳፈር ወደመናሀሪያ ሮጥኩ።የገባሁበት ሚኒባስ አልሞላም። ተቁነጠነጥኩ።

እንደምንም ሞላ እነቀልዬ ወደሀረር ጉዞ ከጀመሩ ከሀያ አምስት ደቂቃ በኃላ የተሳፈርኩባት ሚኒባስ ወደ ሀረር ጉዞ ጀመረች ከፊት ለፊት ሚኒባስ ባየሁ ቁጥር ይሄ እነቃልዬ ያሉበት ይሆን?

እያልኩ። እነሱን ተከትዬ ወደሀረር እየተጓዝኩ ነው ። ከቃልዬ ጋር ስንሄድ አምስት ደቂቃ የተጓዝኩት ያልመሰለኝ መንገድ አምስት ቀን የተጓዝኩ ያህል ቢረዝምብኝም ሀረር ደረስኩ....

ሀረር እንደደረስኩ ለምን እንደመጣሁ፣ ምን እንደማደርግ፣ ወዴት እንደምሄድ ግራ ግብት አለኝ። ምግብ ትናንት ምሳ ሰአት ላይ እንደበላሁ ነኝ። የት እንደማገኛቸውም ፣ ባገኛቸው ምን እንደምላቸውም የማውቀው ነገር አልነበረም።

የሆነ ቦታ ተቀምጠው አልያም ከተማ ውስጥ እኔ ያስጎበኘኋትን የጀጎል በሮች ልታስጎበኘው ዘወር ዘወር እያሉ ፊት ለፊት ብንገጣጠም ፣ ምን እንደሚሰማኝ፣ ምን እንደማደርግ፣ ምን እንወምትል፣ እና ምን እንደምላት አላውቅም ። ይህን ሳላውቅ ነው እንግዲህ ቅናት የሚባል ዛር እያንዘረዘረኝ ተከትያቸው የመጣሁት። ግን ይሄ ቅናት ነው እንዴ? የምን ቅናት ቅናት እማ አይደለም። ይሄ መከዳት፣ መበደል፣ መገፋት፣ የወለደው መጥፎ ስሜት እንጂ ተራ ቅናት ሊሆንማ አይችልም። ይህን አይቶ እና ሰምቶ ፍቅረኛው ጋር ያለውን እውነት ለማወቅ ተከትሎ የማይመጣ ወንድ አለ እንዴ? ኧረ የለም። ቀናተኛ ነህ፣ ትጠረጥረኛለህ፣ አታምነኝም ስለዚህ በድብቅ ትከታተለኛለህ ትነዛነዛለህ ፣ ትጨቃጨቃለህ ላለመባል ብዙ ታግሻለሁ ይህንን ግን ልታገስና አይቼ እንዳላየሁ ላልፈው አልችልም። ባልፈውም ሰላም አላገኝም ፣ ሰላም ፍለጋ ሰላሜን አጣሁ፣ ፍቅርን ፍለጋ ፍቅሬን እስከማጣ መታገስ ምን ፋይዳ አለው? ምንም። ፍለጋዬን ልጀምርና እውነቱን ልጋፈጥ ብዬ ፍላጋዬን ከመጀመሬ እሷ ሳታየኝ እኔ ቀድሜ ባያቸው እንዳያዩኝ የምደበቅ መስሎ ተሰማኝ።

" እንዴ ቆይ ለምንድን ነው የምደበቀው ?" አልኩት የራሴ ስሜት እኔኑ አስደንግጦኝ።

እሺ ምን ታደርጋለህ አለኝ ያ ለብዙ ወራት ድምፁን አጥፍቶ የነበረውና ቃልዬ ውስጤ ያስቀመጠችው ጠበቃዋ እስኪመስለኝ ድረስ እኔና ቃልዬ ፍቅር በጀመርን ሰሞን ሲሞግተኝ የነበረው የራሴ ሀሰብ።

በርግጥ አሁን ላይ ምን እንደምላና ምን እንደማደርግ አላውቅም ፣ በቃ ልክ ሳያት የሚሰማኝን፣ ውስጤ በል በል የሚለኝን እላለሁ። ልክ ሳያት ተደበቅ ተደበቅ የሚል ነገር ከተሰማኝም የምደበቀው መጨረሻቸውን ለማየት ነው። ተደብቄ ለመከታተልና እዚሁ አብረው አንድ ክፍል ውስጥ እንደሚያድሩ ለማረጋገጥ እንጂ ለመሸሽ አይደለም። እንዴ ለምን እሸሻለሁ? እኔ ምን አጠፋሁና እሸሻለሁ? ከዚህ በላይ እውነቱን ላለመጋፈጥ ብሸሽሽስ ሸሽቼ የት እደርሳለሁ? ፣ ብቻ ላግኛት እንጂ ልክ ስንተያይ እሷ እራሷ የምታሳየኝ ስሜትና የምትለኝ ነገር ምን ማድረግ ምን ማለት እንዳለብኝ ያመላክተኝ የለ እንዴ ። ባገኛት ምንድን ነው የምላት እያለኩ ምን ያስጨንቀኛል?" ብዬ ለራሴም ለቃልዬ ጠበቃ ለሆነው የውስጤ ስሜትም ምላሽ እንደሰጠሁ ፣ ••••ቆይ አንተ ሳታያት እሷ ብታይህስ የሚል የላኪ አድራሻ የለለው ጥያቄ አቃጨለብኝ።

ይህንን ነው መፍራት፣ ድንገት ቀድማ ከሩቅ ብታየኝ እንኳን እንዳትለየኝ ምን ላድርግ? የሆነ እራሴን የምደብቅበት ኮፍያ ነገር መግዛት አለብኝ ። ኮፍያ ብቻ ሳይሆን ማክስም ማድረግ አለብኝ።ዘወር ዘወር አልኩና ዙርያዬን ቃኘሁ። ከሚርመሰመሰው የከተማው ሰው መሀል ማክስ ያደረገ አንድም ሰው አልታየህ አለኝ። አይኑራ ታድያ እኔ ባደርግ ምን ችግር አለው። ያየኝም በውስጡ የሚለውን ከማለት ባለፈ ቀርቦ ለምን ማክስ አደረክ የሚለኝ የለ። ይልቅ ኮፍያና ማክሴን ልግዛና የት ሊሆኑ የት ሊሄዱ እንደሚችሉ ማሰብና ፍለጋዬን መጀመር ነው ያለብኝ። መነፀርም ልግዛ እንዴ? አይ አይ መነፀሩስ ቢቀር ይሻላል ፣ ኮፍያና ማክስ አድርጌ በዛ ላይ መነፀርም ጨምሬበት ከተማ ውስጥ ወደዚህ ወደዛ ስል ፖሊስ እራሱ ቢያየኝ ዝም ብሎ የሚያልፈኝ አይመስለኝም። እራሴን ለመደበቅ የምሞክር ወንጀለኛ ልመስላቸው ሁላ ችላለሁ።

አይ መነፀሩ ይቅርና ማክስና ኮፍያውን ብቻ ልግዛ ብዬ ወሰንኩና ገዝቼ በኮፍያና በማክሱ እራሴን በመጠኑም ቢሆን ለመደበቅ ሞክሬ ፍለጋዬን ለመጀመር ተሰናዳሁ። ከሱሪዬ በስተቀር ከላይ የለበስኩትም ከዚህ ቀደም ለብሼው አይታኝ ስለማታውቅ ቃልዬ ቀረብ ብላ ካላየችኝ በስተቀር ከሩቅ ብታየኝ እንኳን ቁመናው እና አካሄዱ ኤፍሬምን ይመስላል ብላ ትጠራጠር ይሆናል እንጂ እርግጠኛ መሆን እንደማትችል እርግጠኛ ነበርኩ።

ፍለጋ ጀመርኩ በአንድ ድፍን ከተማ ውስጥ ሁለት ሰው መፈለግ መጃጃል መስሎ ቢታየኝም ሊሄዱ ይችላሉ ብዬ የማስባባቸውን ቦታዎች ብቻ ኢላማ አድርጌ ስለምፈልጋቸው አላገኛቸውም የሚል ተስፋ መቁረጥ ውስጥ ሳልገባ እየፈለኩ በየመሀሉ ግን ሴትና ወንድ ሆነው ተቃቅፈው አልያም ጎን ለጎን ሆነው የሚሄዱ ጥንዶችን ባየሁ ቁጥር ምንም እንኳን ቃልዬና ዛኪ ከግቢ ሲወጡ የለበሱትን ልብስ ያየሁና ያን አለባበሳቸውን እንኳንስ በዛች ቀን ወደፊትም እድሜ ልኬን የማልረሳው ቢሆንም ምናልባት እዚህ ደርሰው ቀይረው ቢሆንስ እያልኩ ጥንዶች ባየሁ ቁጥር ልቤ እየደለቀ ጥንዶቹ ወዳየሁበት አቅጣጫ ስገሰግስ፣ አንዳንዶቹን ቀርቤ እነቃልዬ እንዳልሆኑ ሳረገግጥ አንዳንዶቹ እኔ አጠገባቸው ከመድረሱ በፊት ታክሲ

ይዘው ሲፈተለኩ ቀልቤ አብሯቸው ሲፈተለክ እነቃልዬን ሳላገኛቸው መፈለግ ደከመኝ።

ቀኑ ደንገዝገዝ አለ። እንዴ ስንት ሰአት ሆኖ ነው ብዬ ሰአት ስመለከት አስራ ሁለት ሰአት አልፏል። ሳይታወቀኝ ምን ያህል ሰአት እነሱን ፍለጋ ከተማው ውስጥ እንደባዘንኩ አሰብኩና ለራሴ አዘንኩ።

የከተማ ውስጥ ፍለጋዬን ገትቼ ካንዱ ሆቴል ወደ ሌላ ሆቴል ስገላበጥ እነቃልዬን የበላ ጅብ ሳይጮህ ከምሽቱ ሁለት ሰአት ሆነ።

ነገሩ የሀረር ጅብ ምን በወጣው እሱ መች ሰው ይበላና ቃልዬን የበላትማ ዛኪ የተባለ ...•ብዬ ያሰብኩትን ተናግሬ ሳልጨርሰው ተውኩትና ፣ ምናልባት የሀረርን ለማዳ ጅቦች ልታሳየው ይሄዱ ይሆን? እሷ ባለፈውም መጠጋት ፈርታ ነበር ምናልባት ለሱ ለማሳየት ስትል ይዛው ትሄድ ይሆናል እያልኩ ወደዛው አቀናሁ።
.
.

ከ 200 ላይክ በኃላ ክፍል 46 ይለቀቃል❤️

6.8k 0 16 8 191

❤️ ተማሪዋ ❤️

🌹…….. ክፍል 44 ………..🌹

.
.
.
.
.

.
እኔማ ግዜ እውነቱን ያውጣው ብዬ ትቼው ነበር እድሜ ለኪያ የቃልዬን እና የዛኪን ዱካ እየተከታተለ አልፈልግም ብለውም በግድ ወሬ እያቀበለኝ ወዳሉበት ሁሉ ይልከኛል። ካየሁዋቸው ደግሞ መረበሼ አይቀርም። ምንሽ ነው አልላት ነግራኛለች ። ለምን ከሱ ጋር እንዲህ ትሆኛለሽ እንዳልላት የምከታተላት፣ የማላምናት፣ የምጠረጥራት ይመስላታል ትጣላኛለች ብዬ እፈራለሀ። የጨነቀ ነገር ሆኖብኝ እንጂ የምቀየረው እሄስ ባህሪ የኔ አልነበረም።

አቦሉን እንደጠጣን..

"ኤፍዬ"

"ወዬ ቃል"

"እስቲ ስለኔም እናውራ" ስትለኝ ደነገጥኩ።

ስላንቺ ምን ቃሌ?"

"አንተስ የምትወድልኝን እና የምትጠላብኝን ባህሪ አትነግረኝም?"

"ቃልዬ የምወድልሽን ነገር መናገር ብጀምር እየደለም እሄ ምሽት ነገ ቀኑም ቢጨመር መሽቶ እስኪነጋ አውርቼ የምጨርስ የሚበቃኝ ይመስልሻል?"

"እሺ በቃ የምትጠላብኝን ባህሪ ንገረኝ"

"ቃሌ የምጠላው ሳይሆን ብትሆኝልኝ ወይ ብትለምጂልኝ ብዬ የምመኘውን አንድ ሁለት ነገር ልንገርሽ አንደኛው ቃልዬ ውሎ እንዴት ነበር ? የሚባል ነገር አለማወቋ ያበሽቀኛል" ስላት "ማለት?" አለችኝ።

"ማለትማ በፍቅር ሂወት መሀል አንዱ ወሳኝ ነገር ውሎ እንዴት ነበር ብሎ ማውራት ነዋ፣ አንቺ ደሞ አልፈጠረብሽም "

"አልገባኝም ኤፍዬ"

"እኔ ስንገናኝ ከመገናኘታችን በፊት ባሳለፍነው ቀን የነበርንበትን ሁኔታ ብናወራ ደስ ይለኛል ፣ አንቺ ግን እንኳንስ ሳልጠይቅሽ ልትነግሪኝ ስጠይቅሽም ደምሽ ይፈላል" ስላት ትን እስኪላት ሳቀች።

"ወይ ኤፍዬ እና አንተ እምትፈልገው ልክ ስንገናኝ ዛሬ ጥዋት ልክ አስራ ሁለት ሰአት ከአርባ አምስት ደቂቃ ላይ ከእንቅልፌ ነቃሁ፣ ሁለት ተኩል ላይ ቁርስ በላሁ፣ አራት ሰአት ክላስ ገባሁ፣ ስድስት ሰአት ከክላስ ወጣሁ፣ መንገድ ላይ አንድ ለከፈኝ፣ ግቢ ውስጥ አንዱ ወደድኩሽ አለኝ፣ ከግቢ ውጪ አንዱ ሰደበኝ እያልኩ ሪፖርት እንዳቀርብልህ ነው ኪኪኪ"

"አትሳቂ ቃልዬ ኮተታ ኮተቱን ሁሉ እንድታወሪልኝ ሳይሆን በጥቅሉ ያለውን ነገር እና ወጣ ያለ ፕሮግራም ምናምን ሲኖርሽ መናገሩ ጥሩ ነው ፣ ደስ ይላል እኮ፣ ደስ ስለሚል ብቻ ሳይሆን አብረን ባልሆንበትም ሰአት አብረን እንዳለን ያህል እንዲሰማን ያደርጋል፣ ግልፅነትን እና መተማመንን ያጠነክራል፣ብዙ ጥቅም አለው ቃሌ"

"ኦ. ማይ. ጋድ. ግን በጣም አሰልቺ አይሆንም ኤፍዬ እሺ ሌላስ?"

"ሌላውም ያው የዚሁ ግልባጭ ነው ። ስለነገ ማውራትም አትወድን ቃልዬ። ይሄም ግን አስፈላጊ ነው። ስለነገ ስልሽ ሰለነገ ሳይሆን ስለወደፊት እንዲሆን እምትፈልጊውን እንዲሁም ለማድረግ ያሰብሽውን ነገር ማውራት ደስ ይላል ለምሳሌ እኔ ሁሌም ሀሳብ የሚሆንብኝ ቃልዬ ከተመረቀች በሁዋላ የት ነው ተቀጥራ ስራ መስራት የምትፈልገው ድሬ ነው ወይስ አዲስ አበባ የሚለው ነገር በጣም ያሳስበኛል። እንኳን ስለወወፊቱ ስለዛሬም ስጠይቅሽ ጭቅጭቅ ስለሚመስልሽና ቶሎ ስለሚሰለችሽ ግን ጠይቄሽ አላውቅም ።"ስላት በስስት እያየችኝ ከተቀመጠችበት ተነስታ ወደኔ መጣችና አቀፈችኝ። ኤፍዬ ሙት አንጀቴን አላወስከው። እንደተመረቅኩ ያው ቤተሰቦቼ ለምርቃቴ መምጣታቸው ስለማይቀር አብሪያቸው ሄዳለሁ ትንሽ ቆይቼ ወደዚህ ተመልሼ ነው ስራ መፈለግ የምጀምው ከፈለክ አንተ ወደ አዲስ አበባ ትመጣና ወደዚህ አብረን እንመለሳለን ፣ይሄንን ቀደም ብዬ ሳስብት ነበር ኤፍዬ አፈቅርሀለሁ እሺ" ስትለኝ ያለንበት ቤት ብቻ አይደለም ምድር የጠበበችኝ እስኪመስለኝ በደስታ ተጥለቀለቅኩ። እንቅፋት የገጠመው የመሰለኝ ፍቅራችን በዚች በቃልዬ ንግግር እንቅልፋቱ ሁሉ ሲጠራረግ ታየኝ። ተስፋዬን አለመለመችው። በዚች ምሽት ቃልዬ ልትመረቅ ሁለት ወር ነበር የቀራት። መድረሱ ያስፈራኝ የቃልዬ ምርቃት ቀን ናፈቀኝ። እህቴ እገዛልሀለሁ ያለችኝ ሚኒባስ ደግሞ ሶስት ወር ነው የቀረው። እያንዳንዷ ቀን መሽታ በነጋች ቁጥር የምመኘውን ሂወት ወደምጀምርበት ቀን የምታወጣኝን መሰላል እየወጣሁ ያጋመስኩ ያገባደድኳት መስሎ ይሰማኝ ነበር።

ቃክዬ መመረቂያ ግዜዋ እየደረሰ ነው አንድ ወር አከባቢ ሲቀረው የመመረቂያ ፅሁፍ ገለመሌ እያለች በጣም ትዋከብ ነበር።ልክ ቃልዬ ልትመረቅ ሁለት ሳምንት ሲቀራት ስራ ላይ እያለሁ፣ በአንድ ቀን አመሻሹ ላይ ከምሽቱ ሁለት ሰአት አከበቢ ባጃጄ ውስጥ ቁጭ ብዬ ሞባይሌን እየነካካሁ ቴሌግራም አካውንቴ ላይ መልዕክት ገባ። ቴሌግራሜን ከፍቼ ስመለከተው መልዕክቱ የተላከው ደግሞ ከዛ ከማላውቀው ቁጥር ነው። ቃልዬ ጭፈራ ቤት ከዛኪ ጋር ያመሸች ቀን የጭፈራ ቤቱ ስም ተፅፎ የተላከበትን ቁጥር የማይታወቅ ብዬ ይዤው ነበር።
ቴሌግራም ላይ የተላከው መልክት በዛ ቁጥር ነው፣ የተላከው መልክት ፎቶ ነው።ጫን ብዬ ካልከፈትኩት ምንነቱ የማይታወቅ ፎቶ መልክቱን ከፍቼ ማየት ፈራሁ። ሳመነታ ቆየሁ፣ በመጨረሻም ከፈትኩት ። ፎቶው የሰው ፎቶ አይደለም፣ ሁለት ሰዎች የተላላኩትን መልክት 'እስክሪን ሹት' አድርገው ነው የላኩልኝ። የመልክት ልውውጡ እንዲህ ይላል•••

"ዛኪ ነገ የት ነህ አንገናኝም?"

"ነገ ግቢ የለሁም ባክህ?"

-"የት ልትሄድ ነው?"

" ከችኳ ጋር ሀረር ልንሄድ ነው"

"ኧረ ባክህ ደስ ይላል ፈታ ልትሉ ነዋ ፣ ስንት ሰአት ነው የምትሄዱት በጥዋት ነው ያቺን መፃፍ ፈልጌ ነበር?''

"አይ በጥዋት አይደለም ከምሳ ሰአት በኋላ የምንሄድ ይመስለኛል እስከስድስት ሰአት አለሁ ናና ውሰድ ወይ እኔ እራሴ አቀብልሀለሁ"

"በቃ ለማንኛውም ጥዋት እንደዋወል"

የሚል ነበር ። ዛኪ ከአንድ ግቢ ካለ ወንድ ጋደኛው ጋር የተለዋወጠው መልክት መሆኑ ግልፅ ነው።

ያንን ፎቶ አንስተው የላኩልኝ ዛኪ ሀረር የሚሄደው ከቃል ኪዳን ጋር እንደሆነ ሊነግሩኝ መሆኑን ሳስበው በተቀመጥኩበት ቢዥዥዥ አለብኝ። አዞረኝ። ባጃጄ ውስጥ የነበረውን ኮዳ አነሳሁና ውስጡ ያለውን ውሃ አናቴ ላይ አፈሰስኩት። በውሃ የሚቀዘቅዝ መች ሆነና። ምን እንደማስብ ምን እንደማደርግ ግራ ገባኝ። ከባጃጄ ላይ ወርጄ ጭለማ ቦታ መርጬ ድንጋይ ላይ ቁጭ አልኩ።

ለብዙ ደቂቃዎች ምናልባትም ለአንድ ሰአት ያህል ቁጭ አልኩ። ትንሽ ስረጋጋ ወደ ቃልዬ ስልክ ደወልኩ።,በቃ ነገ እፈልግሻለሁ እላታለሁ፣ አይመቸኝም ካለች የማይመቻት ከዛኪ ጋር ሀረር ለመሄድ እንደሆነ በግልፅ እነግራታለሁ። እኔ ብሸሸውም እየተከተለ ስቃዬን ያበላኝን እውነት አፍርጬው የምትለውን እሰማታለሁ ። ብዬ ከወሰንኩ በኋላ ነበር ወደ ቃልዬ ስልክ የደወልኩት።ስልኩን አንስታ.. "እንዴት ነህ ኤፍዬ?" ስትለኝ ደፍሬ ያንን ልበላት አልበላት ግን እርግጠኛ ልነበርኩም ። ብቻ ደውልኩ ። የቃልዬ ስልክ ጥሪ አይቀበልም።ከደረሰኝ መልክት በላይ የቃልዬ ስልክ ዝግ መሆኑ ቅስሜን ሰበረው። በሩጫ ግቢያቸው ድረስ ሂድና ስሟን እየጠራህ ጩህ ጨህ አለኝ ። ነገርግን ከተቀመጥኩባት ድንጋይ ላይ አልተነሳሁም። ሶስት ግዜ እየቆየሁ እየቆየሁ ብሞክርላትም ስልኳ ጥሪ አይቀበልም፡፡ ሀሳቤን ቀየርኩ ቃልዬ ስልክ ላይ መደወሌን ትቼ ፍፁም ወደሚባል እንደኔው ባጃጅ ያለው ጋደኛዬ ጋር ደወልኩ ለነገ ባጃጁን እንዲያውሰኝ እና ከፈለገ የኔን ባጃጅ መጠቀም እንደሚችል ስነግረው ።
እኔ ነገ ስራ አልወጣም ናና ውሰድ አለኝ። ምንም ሳልተኛ አደርኩ። ጥዋት ሶስት ሰአት ላይ የሱን ባጃጅ ይዤ እነቃልዬ ዩንቨርስቲ መግቢያ አከባቢ አደፈጥኩ።
.
.

https://vm.tiktok.com/ZMk1XrBAJ/
TikTok · salodatrading
Check out salodatrading’s post.

8.2k 0 17 16 190

❤️ ተማሪዋ ❤️
.
.

🌹🌹 ክፍል 43 🌹🌹


.

አለች እንጂ የኔዋ ያፈር ገንፎ የመሰለች ወድጄ መሰለህ እንዴ እንዲህ አፈር የመስልኩት። እቺ እኮ ጣፋጭ ጠረኗ ሁሉ እስካሁን እስካሁን ባጃጁ ውስጥ አለ ። አለች እንጂ የኔዋ የላብ ገንቦ ወድጄ መሰለህ እንዴ አፍንጫዬ ላይ ማድያት ያወጠሁት።
ያንተ እኮ ሀፒታይዘር በላት ሽንኩርት የሆነች ልጅ አለች እንጂ የኔ ዘጊ ምግብ ስነላ ፊቴ ተቀምጣ ካፈጠጠች ምግቡ ይዘጋኛል ወድጄ መሰለህ እንዴ እንዲህ ባጥንቴ የቀረሁት።"

ወድጄ መሰለህ እያለ ሁሉንም የሱን እንከን በሚስቱ ላይ ሲለድፍ ግራ ገብቶኝ ከሳቄ መልስ ..ቆይ ጠልፋህ ነው እንዴ ያገባሀት?" አልኩት
"እንዴት?
"ፈልገህ አደል እንዴ ያገባሀት?" አልኩት።
"መጀመሪያ እማ ያገባሁዋት ላባቷ አንድ ልጅ ነች ብቸኛ ወራሽ እሷ ነች ብዬ ነበር።
አባቷ ሲሞት ለካ በየቀበሌው ሁለት ሁለት ወልዷል ተጠራርተው ስምንት ሆነው መጡ ከኔዋ ጉድ ጋር ዘጠኝ አትልም አንዷን ውርስ ለዘጠኝ በጣጥሰው ሲካፈሏት ክው አልኩ። ለሚስቴ የደረሳት ብር አመትም አልቆየ አለቀ፣  ከዛ በሀላ በሰላም ውለንም አድረንም አናውቅም ጭራሽ ያባቷን ፈለግ ተከትላ ስምንት ልጅ በየቀበሌው ልትወልድ ነው መሰለኝ አርፋ አትቀመጥም ወድጄ መሰለህ እንዴ እንዲህ የምጠጣው ?"  ብሎኝ ወረደ።

የቃልዬ ዳንስ አይኔ ላይ እየተርገበገበ፣ የኪያ ንግግር ጆሮዬ ላይ እያቃጨለ አልጠፋ አለኝ። ለሶስት ቀን ያህል ከገባሁበት ድባቴ አልወጣሁም። ከቃልዬ ጋር በስልክ እንደነገሩ ከማውራት ውጩ ሶስቱንም ቀን አልተገናኘንም።ቃልዬ በደወልኩም በደወለችም ቁጥር ምን ያህል እንደምታፈቅረኝ ሳትነግረኝ ስልኩን አትዘጋም።
ናፍቆት ፀናብኝ። የቃልዬ ናፍቆት ዳንሱንም ከአይኔ ላይ የኪያን ንግግርም ከጆሮዬ ላይ ጠራርጎ ድራሹን አጠፋው። ሶስት ቀን ያላየኋት  ቃልዬ በብርቱ ናፈቀችኝ።
ንዴቴም ፣ ብሶቴም፣ ኩርፊያዬም በቃልዬ ናፍቆት ታጥቦ ገደል ገባ። እሷን ከማግኘት ረሀብ ውጪ የሚሰማኝም የሚታየኝም ነገር ጠፋ። በሶስተኛው ቀን ማታ ወደቃልዬ ስልክ ደወል።
"ሄሎ" አለኝ የወንድ ድምፅ ነው ። ክፉኛ ደንግጬ ስልኩን ከጆሮዬ ላይ አወናጭፌ አወረድኩትና አፈጠጥኩበት ። አልተሳሳትኩም ቃልዬ ላይ ነው የደወልኩት ..ሄሎ ....አልኩ ደግሜ ካሁን አሁን ዛኪ ነው መቸስ ስልኳን ያነሳሁ ማነህ አንተ ቢለኝ ማነኝ እንደምለው እያሰብኩ ሄሎ አልኩ። ቃልዬ ''ኤርሚያስ ምነካህ የሰው ስልክ አይነሳም እሺ ብልግና ነው " እያለች ስልኩን ስትቀበለው ተሰማኝ።
"ሄሎ ቃልዬ!" አልኩ በልቤ አወይ ጣጣዬ ኤርሚያስ ደሞ ማን ይሆን እያልኩ።
"ሄሎ ኤፍዬ ይቅርታ እሺ አንዱ የክላስ ልጅ ነው መመረቂያ ፅሁፉን በግሩፕ ስለምናዘጋጅ አንድ ግሩፕ ነን እና ዶክመንት ልላክ ብሎ ተቀብሎኝ ስልኬ እሱ ጋር ነበር ይቅርታ እሺ?"አለችኝ። "ችግር የለውም ቃልዬ ናፍቀሽኛል ቃሌ ነገ ላገኝሽ እፈልጋለሁ" አልኳት። እኔም ንፍፍፍቅ ነው ያልከኝ" አለችኝ። በቃ ምንም እንዳልተፈጠረ በንጋታው ምሳ ሰአት ላይ ቃልዬን እስካገኛት ጓጓሁ።

በንጋታው ምሳ ሰአት ደረሰ አልደረሰ እያልኩ አራት ሰአት ላይ ጌትነት ስልኬ ላይ ደወለ። የደወለው ማን እንደሆነ እንዳየሁ ነበር ገና ስልኩን አንስቼ ሳላናግረው የኔና የቃልዬ የምሳ ቀጠሮ ወደ አዳር እንደሚቀየር እርግጠኛ የሆንኩት። "ሄሎ ጌትሽ አማን ነው ?" ወዬ ኤፍዬ እንዴት ነህ ? አቦ ድንገት ለሆነ ጉዳይ ተደወለልኝ እና ከድሬ ልወጣ ነው ፣ እቤት እንድታድርልኝ ላስቸግርህ ነው ጋደኛዬ" ኧረ ጣጣ የለውም አባቴ ገና ስትደውል ነው ባየር ላይ የምሳ ቀጠሮዬን ወደ እራት የቀየርኩት" ካካካ ያው እራት ማለት ደሞ አዳር ነው በለኛ"
''እሱ ግልፅ ነው መጠየቁስ" ሀዬ ኤፍዬ በቃ ቁልፉን የተለመደው ቦታ ሱቋ ውስጥ አስቀምጬ ሄዳለሁ"

"እሺ ጌት ሰላም ግባ"

ወድያው ለቃልዬ ደውዬ የምሳ ቀጦሮኣችን ወደ አዳር መቀየሩን ከነ ምክንያቱ ስነግራት እሺ ኤፍዬ ልትወስደኝ ስትመጣ ደውልልኝ" አለችኝ። እስከ ምሽቱ አስራ ሁለት ሰአት ስሰራ አመሸሁና ቃልዬን ይዣት ወደዛው አመራን።
"ዛሬ እራት ምርጥ ጥብስ ነው የምሰራልህ ስጋ ገዝተን እንግባ ኤፍዬ" ጥሬ አይሻልም ቃል?" "ጥሬማ ምን ስራ ያስፈልገዋል? እኔ ግን ጥብስ ሰርቼ ባብላህ ነው ደስ የሚለኝ ቡናም እናፈላለን " አለችኝ። አልገባትም ቃልዬ። ጥሬ አይሻልም ስላት የሀረሩ ትዝ ብሏት ትስቃለች ብዬ ጠብቄ ነበር። ገብተን እየተጋገዝን እራት ሰርተን እየተጎራረስን በልተን እንዳበቃን ቡና እየጠጣን "ቃልዬ ቅድም ጥሬ ምናምን ስልሽ ምንም ትዝ አላለሽም እኔ ታስታውሽዋለሽ ብዬ ጠብቄ ንበር" ምኑን ኤፍዬ?"

"ትገርሚያለሽ የሀረሩን ቆይታችንን ረስተሽዋል ማለት ነው"

"ኦኬ. ካካካካ የእውነት ግን ጥሬ ስትለኝ አልመጣልኝም እንጂ የሀረሩን ቆይታችንን አንድም ቀን ሳላስታውሰው አድሬ አላውቅም ሁሌ ነው ስተኛ ስተኛ ትዝ የሚለኝ" "እህ ለምንድን ነው ስተኚ ስተኚ ትዝ የሚልሽ ቀንስ?"

"ያው ቀን በተለያየ ነገር ማለት በትምህርት፣ በጥናት፣ ባንተ ሀሳብ፣ በቃ በብዙ ነገር ቢዚ ሆኜ ስለምውል ነዋ ። ጋደም እንዳልኩም ስላንተ አስባለሁ ያኔ ለመጀመሪያ ግዜ አብረን ያደርንበት ሀረር ትዝ ትለኛለች ። ከዛ ያንተ ወሬ ፣ ጥሬ ስጋው ዳንሱን ሁሉ በየተራ አስታውሰዋለሁ"

''ለመጀመሪያ ግዜ አብረን ያደርነው ሀረር ነው እንዴ ቃል" ሂድ ወደዛ እና በተገናኘን በዛው ምሽት ያደርነውን አዳር እንደአዳር ላስታውሰው እንዴ?" ለምንድን ነው የምታስታውሽው ያኛው በደረቁ ስለሆነ ነው"

"ኪኪኪኪ አቦ ያድርቅህ ወደዛ ሞዛዛ" አለችኝ። ቃልዬ አፈረች።

"እኔማ ሀረርን የረሳሻት መስሎኝ ገርሞኝ ነበር"

"እንዴት ይረሳል ኤፍዬ ያኔ ስታወራ የነበረውን ወሬ ባስታወስኩት ቁጥር እስቃለሁ አይ ኤፍዬ ግልፅነትህ እኮ ደስ ይላል!! ስትለኝ ሀረር እያለን ከግልፅነቴ ውጪ የምትወጁልኝ ምንድን ነው ስላት ሌላ ግዜ ነግርሀለሁ ያለችኝ ትዝ አለኝ። ጠየኳት።

" ኤፍዬ ሙት ሁሉ ነገርህን እወድልሀለሁ ብቻ አንዳንዴ•••'' ብላ እያየችኝ ዝም ብላ ቆየችና

"በቃ አሁን ቡናውን እንጠጣ አታስለፍልፈኝ " አለች፡፡

"ቃልዬ ደሞ አንዴ ጀመርነው እኮ ቆይ ከኔ ባህሪ የማይመችሽ ወይ የማትወጂው አለ ? እሱን ንገሪኝ እስቲ"

"ኤፍዬ ሙት ብዙ የለም ብቻ አንዳንዴ ድንገት የሚቀይርህ ነገር አለ ዝም ብሎ የሚከፋህ ነገር ያኔ እጨነቃለሁ"

"ሌላስ?"..

"ሌላው ደሞ ቶሎ ግንፍል የምትለው ነገር ያስፈራል ኤፍዬ እኔ ላይ አይደለም ግን በቀደም ያንን ሰካራም ሰውዬ ልታንቀው ስትንደረደር ላየህ ሁኔታህ በጣም ያስፈራ ነበር እኔ እራሴ ፈራሁህ። እንዴ ኤፍዬ እንዲህ አይነትም ባህሪ አለው እንዴ ነው ያልኩት። ሀረር እያለንም እየደንነስን አንዱ ሳያውቅ ገፋ አድርጎኝ እንዴት እንዳሽቀነጠርከው ትዝ ይልሀል ? ደስ አይልም ቶሎ ወደ ፀብ የምትገባ ሰው እንድትሆን አልፈልግም"

"እሺ ቃልዬ አስተካክላለሁ" አልኳት።

ቃልዬ እንዳለችው ቶሎ ወደ ፀብ የመግባት ድክመቴን አምኜ እቀበላለሁ። በርግጥ ከድሮው አንፃር አሁን እሻላለሁ። ቃልዬ ድሮ ብታውቀኝ ደንብራ ካጠገቤ ትጠፋ ነበር አልኩ በውስጤ። ድንገት የሚቀይር ድንገት የሚከፋህ ያለችው ነገር ግን በሷና በዛኪ ድፍንፍን ባለ ግኑኝነት ምክንያት የመጣብኝ አዲስ ህመም ነው።

ምን ላድርግ ተናግሬም የማይወጣልኝ ትቼም የማልተወው ህመም ሆነብኝ።
.
.

https://vm.tiktok.com/ZMhTas2wC/

9k 0 18 20 210

❤️ተማሪዋ ❤️

.

🌹…………ክፍል 42 ……….. 🌹
.
በአይነ ህሊናዬ ታየኝ ፣ ከዚህ ጭለማ በላይ የኔ ሂወት ሲጨልም ታየኝ  እውን የሆነ ያህል ደንግጬ •••
"ኧረ ቃልዬ!" አልኩ ሳይታወቀኝ በደመነፍስ ።
"ምንድን ነው የምትለኝ ኤፍዬ ግባና ንዳ እንጂ ቀስ እያልክ ንዳ ማለት ይህን ያህል ያናድዳል?" ስትለኝ ከሄድኩበት የሀሳብ አለም ባንኜ።
"ምናልኩሽ?" አልኳት ደንግጬ።
ግባና ንዳ እራስሽ ንጂው አልነዳም እየተባባልን ስንጨቃጨቅ አንድ ስካር ጢንቢራውን ያጠናገረው ሰካራም ከየት እንደመጣ እንጃ ጎንበስ ቀና እያለ መጣና ድንገት ባጃጇ ውስጥ ጥልቅ አለ።
"ወይኔ ኤፍዬ ድረስ !!" ብላ ጮኸች ቃልዬ ደንግጣ። ዛኪዬ ድረስ አለማለቷም ተመስገን ነው።
"እሰይ  እኔን እብድ ስትይ የለየለት መጣልሽ " አልኩ በውስጤ ሰውየውን እያየሁት።
"የየየየየ የምን ኤፍዬ ነው ? የኔ ስም ገረመው ነው ቆንጅት ኤፍዬ ትያለሽ እንዴ ገረመውብለሽ ጥሪኝ ህቅ•••እስቲ ገረመው በይ?" አላት ። ከመስከሩ የተነሳ ቁጭብ ሎም መሸከም ያቃተው ጭንቅላቱ ብቻውን ይንገዳገዳል።
"አሁን ትወርዳለህ አትወርድም ገረመው እኔ ሰው አልጭንም " አልኩት።
"ምናልክ ሹፌሩ ሰው አልጭንም እና ኩንታል ልትጭን ነው እንዴ የቆምከው በባጃጅ ኩንታል ወግ ነው ሲዳሩ ማልቀስ አቅምን አውቆ መኖር ጥሩ ነው የሚለውን ዘፈን ጨርሰህ ዝፈነው እሺ ያኔ አቅምህን ታውቃለህ። እኔ እዚህ ጨለማ ውስጥ ባጃጅ ጥበቃ ስንት ሰአት እንደቆምኩ ታውቃለህ  ሰው አልጭንም ይላል እንዴ እና ይቺ ከጎኔ የተቀመጠችው ኩንታል ነች እንዴ ? እሄው በደንብ አየኃት አይደለችም " እያለ ወደ ፉቷ ጠጋ ብሎ ሲመለከታት ቃልዬ ሽምቅቅ ብላ  ባጇጇ ላይ ተጣበቀች።
"አይዞሽ የኔ ቆንጆ አስደነገጥኩሽ አደል ይቅርታ አንቺኮ  በጭለማ ውስጥ ያለሽ   የ-የ-የ-የ የብርሀን ጭላንጭል ነሽ ።
አይገርምሽም ታምሪያለሽ አይገልፅሽም።
  አለች እንጂ የኔ ሚስት በጨለማ አትታይ በፀሀይ አትታይ ምኗን አይቼ  እንዳገባሁዋት  ግራ ገብቶኛል።
ወድጄ መሰለሽ የምጠጣው ምናልባት ምኗን አይቼ እንደወደድኳት ስጠጣ ቢገለጥልኝ ብዬኮነው።
ሴት መሰለችሽ ሰላቢ በያት እሄው እሷን ስከታተል ስንት አመት ሆነኝ እሳን እጅ ከፍንጅ እይዛለሁ ብዬ  ስከተላት  ስንት ቦታ ፈንጅ ረገጥኩ መሰለሽ።
እኔና ሚስቴኮ አብረን እየኖርን የተፋቷን ብቸኛ ባለትዳሮች ነን ።
አብረን እየኖርን አብረን እያደርን ነው አሁንም ድረስ ግን ተፋተናል።
ብዙ ወሬ ሰማሁ ወሬ ሰምቼ ከምወስን በገዛ አይኔ አይቼ ቢለያኝ ይሻላል ብዬ ምንም እንዳልሰማ ባል ሆኜ በድብቅ እከታተላት ጀመር እኔ እሷን ተደብቄ ልከታተል እሷው ተደብቃ እኔን ትከታተለኝ እስከሚምታታብኝ ድረስ እንኳንስ በማታ በቀንም ላገኛት አልቻልኩም ቀን ከስራ እቤት መጥቼ የለሽም የት ነበርሽ ስላት አጠገብህ ትለኛለች ። በቃ ሁሌ ያለሁበት ቦታ ሁሉ ያለች ይመስለኛል ወድጄ መሰለሽ ድምፄን ቀንሼ የማወራው የምትሰማኝ እየመሰለኝ እኮ ነው ።
" ባጃጁን ያቆምኩት ላንተ አይደለምና ውረድ!" አልኩት በንዴት!።
"ስማ ሹፌሩ አንተም ወንድ ነህ ነገ ማግባትህ መውለድህ አይቀርም የጀመርኩትን ወሬ ልጨርስበት አታቋርጠኝ ምን ይመስላል በሚስቴ ሞት።
ለኔማ ነው ያቆምከው!  ለሌላ የቆምክ መስሎህ ነው እንዴ?
እኔን  እኮ ነኝ  እዛ ጋር ቆሜ ያየከኝ።  ሌላ ሰው ቢኖር ለምን እስካሁን አልመጣም?  ይልቅ አንተ ስራህን ስራ ከልጅቷ ጋር ላውራበት" ሲል ቃልዬ ሳቀች። አንገቱን ከኔ ላይ መንጭቆ  በፍጥነት ወደሷ ዞረና•••
"ምን ምን ምን ምን እስቲ በናትሽ ሳቅሽን ድገሚው  የተኮረኮረ ህፃን ልጅ እኮ ነው የምትመስይው !
ግን ግን በናትሽ ካላስቸገርኩሽ ያሁኑን ሳቅ አንዴ ድገሚልኝ !" አላት ። ተበሳጨሁ።
"ስማ ሰውዬ  የሷ ሳቅ ስትጋት ያመሸከው ጠጅ መሰለህ እንዴ የሚደገመው  አሁን የምትወርድ ከሆነ በፀባይ ውረድልኝ? አልኩት።

"ጠጅ አልጠጣሁም አረቄ ነው ጠጅ ስጠጣ አይተሀል? ነበርክ? እኔ ጠጅ አልጠጣሁም  አረቄ ነው ነው የጠጣሀት ዝም ብለህ በመላ ምት ጠጅ ትላለህ እንዴ?
ደሞ ሳቅ እንጂ ሌላ ነገር ድገሚኝ አላልኳት ምን አቃጠለክ ኪኪኪኪ " ብሎ ሳቀና ደሞ ወደሷ ዞሮ
"እኔኮ ተሳፋሪ መስለሽኛል  ! ፍቅረኛሽ ነው እንዴ ለካ! በቅናት አንገበገብኩልሻ  አንበሳ ነኝ አደል አንበሳ••••" እያለ ሳቁን ቀጠለው።
ትግስቴ አለቀ።  አንቄ ላወርደው ገና ያዝ ሳደርገው•••
"ኤፍዬ ኤፍዬ ለኔ ስትል ስሞትልህ ኤፍዬ ልቀቀው እራሱ ይወርዳል!" አለች ቃል ግብግብ ብላ።
" አፌ ቁርጥ ይበልልሽ  አንቺ ባትኖሪ ምን  ይውጠኝ ነበር  ሆሆሆሆ ሊበላኝ ነው እንዴ?
እራሱ ድብን ይበል አንቺ ለምን ብለሽ ነው የምትሞችው?  እውነቴን ነው  እድሜ ለሴቶች እንበል  እናንተ ባትኖሩ እኮ እኛ ወንዶች እሄን ግዜ እንደ ዳይኖሰር እርስ በርስ ተበላልተን ከምድረገፅ በጠፋን ነበር! ምኑ ዳይኖሰር ነገር ነው በሚስቴ ሞት ተከመረብኝ እኮ"
"እሺ አሁን ትወርዳለህ አትወርድም?"  አልኩት ወደሱ እየተጠጋሁ..

"እራስህ እኮ ነህ አቁመህ የጫንከኝ !"
"ላንተ አልቆምኩም አልኩህ እኮ!
"ታድያ ለማን ነው የቆምከው?"
"ለሷ!"
"ለሷ ካካካ እሷኮ አብራህ ነው የመጣችው አሃሃሃ  ልታወርዳት ነበር እንዴ የቆምከው ገባኝ !
ታድያ ምን አጣደፈህ ቀስ ብለህ አትቆምም  ብቻሽንማ አትወርጂም ነይ በይ እንውረድ!"
ሲላት•••
ሳላውቀው  በንዴት ውስጥ ሆኜ  ሳቄ መጣብኝ እንደምንም ላለመሳቅ እየታገልኩ ኮሌታውን ይዤ ጎትቼ ላወርደው ስል•••
"እባክህ  ተወው እንደዛ አታድርግ ! ቆይ የት ነው መሄድ እምትፈልገው አንተ ?!" አለችው።
"ብዙ አርቅም እኮ እሄኛው  መጠጥ ቤት ስለተዘጋብኝ  እቅዴ ደሞ አዳሬን መጠጣት ስለሆነ ቤት ልቀይር ነው እዛች ጋ ያለችው ግሮሰሪ ልጠጣ እየሄድኩ ነው ።
ያቺ ግሮሰሪ  አትዘጋም።  ሙች እውነቴን ነው  ያቺ ግሮሰሪ  ካልታሸገች በስተቀር  አትዘጋም
ወደዛ ነው እምሄደው. ዝግ ከሆነች ወደ ከተማ እመለሰላሁ"ሲላት
"በናትህ ኤፍዬ ጣል አርገነው እንለፍ ?" እለችኝ ባይኗ እያባበለችኝ።
ብስጭት እንዳልኩ ባጃጇን አስነስቼ ከነፍኩ።
"ምን አርጊ ነው እምትላት እነጨርሳለን እንጫረሳለን እያልክ ታስፈራራለህ እንዴ?" አለ

እስቲ ዝምበል ስለው ጭራሽ ባሰበት•••
"ዝም አልልም እንደውም እሱን ተይው አንቺ ብቻ  እሺ በይኝ ?"
"ምን ?"
"አንዴ ብቻ የቅድሟን ሳቅ ድገሚልኝ " አላት ቃልዬስ ሳቂልኝ የሚላት  አግኝታ ነው ለቀቀችው። ደስ አለው።
በናትሽ ይህን ሹፌር እናቃጥለው አሁንም ድገሚው ሲላት እኔ እራሴ ሳልፈልግ ሳቄ መጣ።
"ግን ምን ሆነሽ ነው ከዚህ ባለ አስፈሪ ፊት ሹፌር ጋር በጭለማ ብቻሽን የምትሄጂው ?" ሲላት አልቻልኩም። ሳቄን ለቀቅኩት።
"ግሮሰሪዋ ዝግ ነች ምን ይሻልሀል?"
" ዉ ይ ዝግ ነው እንደውም ባንተ ባጃጅ መሄድ አልፈልግን እዛው የጫንከኝ ቦታ መልሰኝ "
"ምን ?" አልኩት እያቆምኩ።
"ኪኪኪኪ ኤፍዬ በናትህ በቃ አድርሰኸኝ ስትመለስ ጣል አድርገው"
"አንቺ ደሞ አበዛሽው!"
ቃልዬን ግቢ በር ላይ አድርሻት እንደወረደች ።
"ኬት ጠብ አደረካት ይቺን የመሰለች ልጅ እባክህ አንባሳ ነህ አባቴ ይሙት ኮራሁብህ ጀግና " ሲለኝ አሁን ገላጋይ የለም ብሎ እያባበለኝ መሆኑ ገባኝና ፈገግ አልኩ።

https://vm.tiktok.com/ZMh7Q9na4/

9.5k 0 25 11 224

❤️….. ተማሪዋ ……❤️

🌹🌹ክፍል 41 🌹🌹

አልኳት አዎ አውቀዋለሁ " አለችኝ ፀጉሯን በጣቶቿ እየነካካች።
"ስንቴ መጥተሻል?"
"አንድ ሁለቴ"
"ከማን ጋር?"
"ከግቢ ልጆች ጋር ነዋ ብቻዬን አልመጣ ምነው ኤፍዬ?"
"አይ ምንም መች ነበር የመጣሽው?"
"እህህህ ኤፍዬ ምንድን ነው፣ መጥቻለሁ ከግቢ ልጆች ጋር አልኩህ ፣ የግድ ቀንና ሰአቱን ማስታወስ አለብኝ  የወንጀል ምርመራ ጥያቄ አስመሰልከው እኮ"
"በይው"
"በ. ይ. ው. ምኑን ነው እምለው ኤፍዬ. መነታረክ ትተን ነበር ደሞ ሊጀምርህ ነው?" ስትለኝ ሀሞቴ ፍስስ አለ። በቃ እኔ የምጠላው ነገር በቃልዬ መፈረጅ ነው። ቃልዬ ጨቅጫቃ፣ ነትራካ፣ ተጠራጣሪ፣ የሚቀና ወንድ አድርጋ ስታስበኝ ያመኛል ። ምንም ነገር መጠየቅም መስማትም ያስጠላኛል።  መነታረክ ትተህ ነበር ሊጀምርህ ነው ስትለኝ ገና እራስ ምታቱ ጀመረኝ።ዝምምም አልኩ።
" በቃ እንሂድ " አለችኝ።
"ለምን ቃል?" አልኳት በደከመ ድምፅ ። የራሴ ሁኔታ እኔኑ አሳዘነኝ።
"ብዙ አልቆይም ስለናፈቅከኝ አግኝቼህ ልመለስ ብዬህ አደል የመጣሁትአለች። መግባት አለብኝ " አለች።
ብዙ ግዜ ብዙ አልቆይም አየት አድርጌህ ልመለስ ብላኝ መጥታ አብረን አድረናል። አሁን ለምን ጥያቄ አበዛብኝ ብላ እንጂ ሌላ የምትሄድበት በቂ ምክንያት ቢኖራት ትነግረኝ ነበር። ። እንድትቆይ ላግባባት አልችልም ውስጤ በሚያስጠላ ስሜት እየተተራመሰ ነው ፣ መበሳጨቴን መደበቅ አልቻልኩም።
ቃልዬን ክፉ ነገር ከምናገራት ብሸኛት እንደሚሻል  አሰብኩና
"እኔም እራሴን እያመመኝ ነው ልክ አይደለሁም ነይ በቃ ላድርስሽ"  ብያት ወጣን ።
የራስ ምታቴ ምክንያት ምን እንደሆነ መች ይገባታል። ምን ሸቶህ ነው ፣ ጉንፋን ሊይዝህ ይሆን ለምን ከፋርማሲ መድሀኒት አንገዛም እያለች ስትወተውተኝ
"ተይኝ ቃልዬ እፈልገዋለሁ!"አልኳት።
" ምኑን?" አለች ግራ ገብቷት።
"በሽታውን እራስ ምታቱን "
"ኤፍዬ ምን ሆነሀል ዛሬ?"
"እራሴን አሞኛል አልኩሽ አይደል ቃሌ"
"እሱን እማ ፈልገዋለሁ ተመችቶኛል እያልክ አይደል እንዴ"
"አንዳንዴ ቢያሳምሙሽም  አብረውሽ እንዲሆኑ እምትፈልጊያቸው ነገሮች አሉኮ
"በናትህ ኤፍዬ አታላግጥ ይልቅ መድሀኒቱን እንግዛ"
"አልገዛም መታመሙን እፈልገዋለሁ አልኩሽ እኮ"
ተናዳ ዝም አለች። እኔም ዝም አልኩ። ከግማሽ መንገድ በላይ በፀጥታ ከሄድን በኋላ
"ኧረ ቀስ ብለህ ንዳ  ኤፍዬ ! እንዴ እንዴት እንዴት ነው የምትነዳው ? ያስፈራል " አለችኝ።
ባጇጇን ቀጥ አደረኩና " ሰአቱ ሄደ መሸብኝ እቤት ይቆጡኛል ገለመሌ ብለሽ ያጣደፍሽኝ አንቺው አይደለሽ እንዴ? ነይ ንጂዋ እንግዲህ እስቲ ንጂውና እንዴት እንዴት መሄድ እንዳለብኝ አሳይኝ!" ስላት እሷ ገና እቤት ይቆጡኛል የሚለው ንግግሬ ጋር መሳቅ ስለጀመረች ከዛ በኋላ የተናገርኩትን የሰማችኝ አልመሰለኝም።
እኔ በብስጭት የምይዝ የምጨብጠው ጠፍቶኛል እሷ ትስቃለች።
"እና አሁን ለምንድን ነው እዚህ ጭለማ ውስጥ የቆምከው"
"በቃኣ አነዳድህ አልተመቸኝም እያልሽ አይደል ነይና ንጂዋ"
"ሆሆሆ እብድ" አለችኝ። ካበድኩ ስለቆየሁ ስድብ ሳይሆን ስሜ መሰለኝ።ጭራሽ ከባጇጇ ወርጄ በቀኝ በኩል በመቆም " ውረጂና ንጂ እኔ ከጀርባ እቀመጣለሁ ያለበለዚያ እዝቹ ባጃጅ ውስጥ እናድራታለን እንጂ አልነዳም አልኳት።
"አሪፍ ነዋ እንደውን ወደፉት እያስታወስነው የምንስቅበት ጥሩ ትዝታ ይሆነናል " ስትለኝ ደሞ በረድ አልኩ።
በአንዲት ቃል ስታቀዘቅዘኝ እራሴን ታዘብኩት " ምን ይሻልሀል ኤፍሬም በቃ ቃልዬ ስትፈልግ የምታነድህ ስትፈልግ በአንዲት ንግግር ብቻ የምታበርድህ የኤሌትሪክ ምድጃ ሆነህ አረፍከው የኤሌትሪክ ምድጃ እንኳን በጣም ከጋለ በኃላ ሶኬቱ ቢነቀልም ለመቀዝቀዝ ግዜ ይወስድበታልኮ!" አልኩት እራሴን ።
ለወደፊቱ እያስታወስን የምንስቅበት ጥሩ ትዝታ ይሆነናላ ስትለኝ ቃልዬ ከኔ ጋር እስከመጨረሻው መዝለቋን ያረጋገጠችልኝ ያህል በንዴት ውስጥም ሆኜ ደስ ስሊኝ ገርሞኝ።
በርግጥ ለወደፊት በፍቅር በትዳር አብሮ ስለመዝለቅ ከቃልዬ አንደበት ሲወራ ሰምቼ አላውቅምና ይህ ንግግሯ ብርቅ ቢሆንብኝ በኔ አይፈረድም። ቢሆንም ባጃጁን አለመንዳትና ቃልዬን ማበሳጨት የኔን ንዴት ያበርደው ይመስል ባለመንዳት አቋሜ ፀናሁ።
ንዳ አልነዳም ስንነታረክ ለምን ትናንት እዛ ጭፈራ ቤት ኮንትራት የፈለገ ሰው ደውሎልኝ ስመጣ አየሁሽ ብያት አልገላገልም በውስጤ ይዤው ከምብሰከሰክ እንደዛ ብያት ብገላገልስ አልኩ።
ያው መልሷ የታወቀ ነው መቸስ ።
"ትናንት የዛሬው ጭፈራ ቤት አየሁሽ ልበላት እንዴ?"
ጭንቅላቴ ከመፈንዳቱ በፊት ተንፍሸው ልገላገል የምትለውን ትበል።
በቃ ለኔ ሁለቱም ያው ነው ፣ እኔ በጭንቀት ከመፈንዳቴ በፊት ጭንቀቴን ተንፍሸው ያበጠው ይፈንዳ።
ምን ብዬ ልጠይቃት•••
"ቃልዬ ከአንድ ቀን በፊት ዛሬ የሄድንበት ጭፈራ ቤት አየሁሽ ልበል?" ስላት
ቃልዬ  ብስጭት ንጭንጭ እያለች
" አዎን እኔና ጓደኞቼ  እና የአክስቴ ልጅ  ሆነን ወጣ ብለን ነበር "
"ኡፍፍፍ••• እና ያክስትሽ ልጅ ከሆነ  ከሱ ጋር እንደዛ እየተሻሹ መደነሱ ለምን አስፈለገ?"

ምን ? ምናልክ እንኳንም በግዜ አወቅኩህ ለካ እንደዚህ አይነት ሰው ነህ?"
"እንዴት"
"ኦኦኦ ተደብቀህ እኔን መከታተል ጀመርክ ገና ፍቅረኛህ ሆኜ እንዲህ እየተደበቅክ የምትከታተለኝ ብታገባኝማ እቤት ውስጥ ቆልፈህብኝ ነው የምትወጣው እንኳንም በግዛ አወቅኩህ ። እንኳንም ወደፊት ምን አይነት የቅናት ዛር የሚያንዘረዝርህ ቅናታም ባል እንደምትሆን በግዜ እንድነቃ አደረከኝ።  ከዚህ ቀደም ዛኪ ማነው አልከኝ፣ ማንነቱን በግልፅ ነገርኩህ ፣ ከዚህ በላይ ምን ፈለክ ?  ተሻሸሽ ይላል እንዴ እንኳን ተሻሸሁ ደግ አደረኩ በራሴ ገላ ምን አገባህ።  ሆ•••• አንሶላ ስጋፈፍ የያዘኝ አይመስልም በጌታ፣ ምን ውስጥ ነው የገባሁ ትገርማለህ ግን ከማንም ጋር ያሻኝን የመሆን መብት አለኝ እሺ፣ ምንም ነገር የማደርገውም የማላደርገውን አንተን ፈርቼ ከመሰለህ
ለራስህ የሰጠኸው ቦታ የተሳሳተ መሆኑን እወቀው። ሰማንያ ቆርጠህ፣ ሽማግሌ ልከህ ፣ ደግሰህ ያገባኸኝ መሰለህ እንዴ?
ያኔማ  በየመንገዱ ምንድን ነው ለሰውየው ፈገግ አልሽለት እንዴ ? ለምንድን ነው ትኩር ብሎ ያየሽ ? ታውቂዋለሽ እንዴ? እና ካላወቅሽው በየመንገዱ ምን ያስገለፍጥሻል? እያልክ መሳቅ ስፈልግ በናትህ ሳቅ አፈነኝ ልሳቅ እንዴ ኤፍዬ እያልኩ እንዳስፈቅድህ ሳታስገድደኝ አትቀርም።
ተሻሸሽ ይለኛል እንዴ እንኳን ተሻሸሁ ፣ ታድያ አሁንስ ከኔ ጋር ምን ታደርጋለህ አንተም አንዷን ፈልገህ አትተሸሽም?።
ይሄው አንድ አመት ሊሞላን ነው ካንተ ያተረፍኩት ነገር ቢኖር ጭቅጭቅ ብቻ ነው። እኔ ነፃነቴን እፈልገዋለሁ። ቤት ገባት ቤት ወጣሽ ? ማንን አገኘሽ? ከማን ነሽ? እሚለኝ ፍቅረኛ አይደለም እንዲኖረኝ በጭራሽ አልፈልግም!። ካሁን በሁዋላ እንዳትደርስብኝ አልደርስብህም። ድርሽ እንዳትልብኝ። ዞርበልልኝ አትጠጋኝ ኤፍሬም ። እንዳትጠጋኝ እኔ ጮኻለሁ ኤፍሬም!"
እያለች ኤፍዬ ስትለኝ እንዳልነበር ስሜን ከነአሰስ ገሰሱ እየጠራች ፣ እንደአብድ እያደረጋት ፣ ንፋስ ላይ እንደተሰጠ ጨርቅ እየተወናጨፈች ሜዳ ላይ ገትራኝ ስትሄድ....
.
.
ከ 150 ላይክ በኃላ ክፍል 42 ይለቀቃል

https://vm.tiktok.com/ZMhYMxcmU/

9.5k 0 20 22 221

❤️ ተማሪዋ ❤️
.
.

🌹…… ክፍል 40……..🌹

ኢትዮጲያ ውስጥ የትም ቦታ የትኛዋም ሴት ከአክስቷ ልጅ ጋር እንደዚህ የምትደንስ አይመስለኝም ።ለቃልዬ ባክስት ልጅ እና በኔ መካከል ያለው ልዩነት ምንድን ነው ።  ጭፈራ ቤቱ ጥግ ላይ እንደግርግዳ ቋሚ ተለጥፌ እነቃልዬን እያየሁ ስንጨረጨር ስልኬ ጮኸች። ከጭፈራ ቤቱ እየወጣሁ ስልኬን ስመለከታት ያ መልክት የተላከበት የማይታወቅ ስልክ ነው። አነሳሁት።ሄሎ ስል የሚያስጠላ የሴት ልጅ ሳቅ። ፈጣሪዬ ሆይ እኔ አላብድ ያልኳቸው ሰዎች በዙርያዬ አሉ እንዴ ? ደሞ ይሄንን ሳቅ አውቀዋለሁ። መቼ እና የት እንደሆነ ባላውቅም ይህንን ሳቅ የሆነ ቦታ አውቀዋለሁ። ለማስታወስ ሞከርኩ። የመክሊት ሳቅ ነው ። አዎ እራሷ ነች ። በገንኩ ። እንደእብድ አደረገኝ ። አይ ኪያ የቶማስ ሳያንሰው ለመክሊትም አሳልፎ ሰጠኝ ። ደግማ ከሳቀች ለማረጋገጥ ደወልኩ አይነሳም ።
ይሄ ልጅማ ከኔ ጋር የከረረ ፀብ ፈልጓል ፣ጭራሽ ለመክሊት ፣ ወይኔ ኤፍሬም እኔና ኪያ የሚለይልን ዛሬ ነው።
ወደ ጭፈራ ቤቱ መመለስ ይኑርብኝ ወደኪያ መሄድ መወሰን አቅቶኝ ጭለማው ላይ እንዳፈጠጥኩ ደቂቃዎች አለፉ። ኪያን ምን እንደበደልኩት ለማስታወስ ሞከርኩ። ምንም ትዝ አይለኝም ። አንድ ሰፈር ተወልደን አንድ ላይ ተምረን እንደየፍላጎታችን በምንፈልገው የስራ ዘርፍ ተሰማርተን ሂወትን ለማሸነፍ መፍጨርጨር እስከጀመርንበት ድረስ የከረረ ፀብ እንኳን ተጣልተን አናውቅም እንደማንኛውም ያንድ ሰፈር ልጆች በተለያየ ግዜ በተለያየ ጉዳይ ከመከራገር ከመበሻሸቅ፣ከመኮራረፍ እና መልሶ አስታራቂ መሀላችን ሳይገባ በጫወታ ሞቅታ ከመታረቅ ያለፈ ክፉ ነገር በመሀላችን ተፈጥሮ አያውቅም።
ቢያውቅም የዛሬን ያህል በኪያ የተከፋሁበት ቀን የለም የማትነካውን እየነካብኝ ነው ኪያ በማይመጣው እየመጣብኝ ነቅ ኪያ ማንንም ልታገስ በማልችልበት ደካማ ጎኔ እየመጣብኝ ነው። ኪያ ሁሉ ነገሬ ከራሴም በላይ በማፈቅራት በቃልዬ ከመጣብኝ አብሮ ማደግ፣ አብሮ መማር፣  ጓደኝነት፣ወንድምነ ሁሉ ለኔ ቦታ አይኖራቸውም ምክንያቱም ቃልዬ እንኳንስ ከኪያ ከራሴም በላይ አፈቅራታለሁ። እሷ ካጣሁ እኔ እራሴ የታለሁና ቃልዬ እኮ ነች እጅ ላይ በሚጠለቅ ቀለበት ሳይሆን በፍቅሯ ልቤ ላይ ቃልኪዳን ያሰረች የኔ ፍቅር ቃልኪዳን ነች ድጋሚ ወደ ጭፈራ ቤቱ ብገባና ቃልዬን በዛ መልኩ ከልጁ ገር ስትጨፍር ባያት  ያስችለኝ ይሆን በጭራሽ ።
መሀላቸው ገብቼ ቃልዬን ከዛኪ ላይ መንጭቄ እየጎተትኳት ስወጣና ማንው ደሞ ይሄ ጥጋበኛ እያለ ስከተለኝ በደምፍላት ዞሬ አፍንጫውን ብዬ ደሙን ሳንዥቀዥቀው ታየኝ። ከዛ ቡሀላስ በኔና በቃልዬ ማሀል ምን ይፈጠራል?
ሁሉም ነገር  ድብልቅልቁ  ሲወጣ ታየኝ። ስልኳ ላይ ሞከርኩ አሁንም ጥሪ አይቀበልም። የማደርግ የምሆነው ነገር ግራ ገባኝ።
የቃልዬ አደናነስ ፉቴ ላይ ይውለበለባል ተቃጠልኩ።  በኪያ ተንኮልና ወሬ ቃልዬ ላይ መናደድ የሱን ሀሳብ ማሳካት መስሎ ቢታየኝም አለመናደድ አልቻልኩም። እኔኮ የቃልዬን ገላ አይደለም የቃልዬን ቀሚስ ንፋስ እንኳን ሲገልበው እቀናለሁ። ታድያ  እንደዛ ተጠብቃበት ስትጨፍር እያየኃት እንዴት ብዬ ነው አለመናደድ የምችለው።

ስለኔና ስለቃልዬ ለኪያ ያወራሁባትን ቀን ያቺን አርብ ምሽት ክፉኛ ጠላኋት ፣ከአያቴም ከእናቴም የሰማሁትን እርግማኖች ሁሉ ረገምኳት።
ግን ቀኗ ምን ታድርገኝ ። በግድ አፌን ፈልቅቃ አላስወራችኝ። እራሴው ነኝ የግል ሚስጥሬን  ሳልጠየቅ የለፈለፍኩት ሊያውም ለኪያ ። እሄ የተረገመ ልጅ አሁን የት ነው ያለው? በሱ ወሬ ከቃልዬ ጋር ሳይሆን ከሱ ጋር እንደምጣላ ከዚህ ቀደም ነግሬዋለሁ ። ዛሬ በተግባር አሳየዋለሁ እያልኩ ባጃጄን አስነስቼ ከነፍኩ።
እንዴት እና በምን ፍጥነት እቤት እንደደረስኩ አላውቅም። ኪያ እቤት ውስጥ የለም። ገራዡ ዝግ ነው። ገኒ ጋርም ፈለኩት እዛም የለም።
ጭለማ ውስጥ ባጃጄን ተደግፌ እንደቆምኩ እንድ ጥያቄ ውልብ አለብኝ። አዋ እንዴት ግን ቅድም ልክ ጭፈራ ቤቱ በር ላይ ስደርስ ጠብቀው "አትወጣም" ብለው መልክት ላኩልኝ? ያ ማለት እኮ ስገባ እያዩኝ ነበር ማለት ነው። በቃ ኪያ ከመክሊት ጋር እዛው ጭፈራ ቤት አልያም እዛው አከባቢ ነው ያለው። እሄን ሁሉ ነገር የሚያደርገው መክሉትን ለማስደሰት እንደሆነ ግልፅ ነው ። እሱ መክሊትን ለማስደሰት ቶማስን ከዛኪ ጋር እንዲተዋወቅና የት ምሳ እንደሚበሉ የት እንደሚያመሹ መረጃ እንዲያቀብለው አደረገ።  ከዚህ የከፋ ነገር አለመሸረቡንስ ማን ያውቃል እስቲ እንተያያለና እንግዲህ ። ድጋሚ ወደ ጭፈራ ቤቱ ገሰገስኩ።
እነቃልዬ ጭፈራ ቤቱ ውስጥ የሉም ሄደዋል። ኪያንም በዛው ጭፈራቤትና በአከባቢው ባሉ ሆቴሎች ፈልጌ አጣሁት። ቃልዬ ስልክ ላይ ሞከርኩ አሁንም ዝግ ነው። ወደቤት ስመለስ ኪያ አልገባም። ጭራሽ ሳይመጣ አደረ። እንቅልፍ ባይኔ ዝር ሳይል አስቀያሚና ረጅሙ ለሊት እንደምንም ነጋ። እንደተነሳሁ ቀጥታ ወደ ገራዥ አመራሁ። ከኪያ ጋር ክፉኛ ተጣላን። የገራዡ ሰራተኞች  መሀላችን ገብተው ባይገላግሉን ከሱ ጋር ከመነጋገር መደባደቡ ይሻለኝ ነበር።
በዛ ተምዘግዛጊ ምላሱ ከአስር ግዜ በላይ  •••" ኤፍሬም ይልቅ አይንህን ግለጥ !" ይለኛል። ጭፍኜ ስሄድ የት እንዳየኝ እሱ ነው እሚያውቀው ስለኔ እንደማይመለከተው ደጋግሜ ስነግረው እየደጋገመ
"ኤፍሬም ይልቅ አይንህን ግለጥ ከኔ ጋር በመጣላት የምታተርፈው ነገር የለም ትርፉ መቀያየም ነው ። አንተን እና ቃልኪዳንን የማውቃችሁ እኔ ብቻ ነኝ እንዴ? ድሬ ዳዋ ዩንቨርስቲ የሚማረው የድሬ ዳዋ ልጅስ ቶማስ ብቻ ነው እንዴ? ብዙ ተድሬ ልጆች እኮ እዛ ይማራሉ። እሷን ስታደርስ እና ስትመልስ የሚያይህ ብዙ ነው ። ከኔ ላይ አይንህን አንሳና ዙርያህን ተመልከት ፣ እውነቱን በመሸሽ ወይም ከኔ ጋር በመጣላት ፍቅርህን ማትረፍ የምትችል መሰለህ እንዴ? ና ምታኝ ምታኝ ችግር የለውም ፣ እኔን በመምታት ንዴትህ የሚወጣልህ፣ ቃል ኪዳንም ታማኝ የምትሆንልህ ከመሰለህ ምታኝና ደስ ይበልህ!" ሲለኝ እራሴን አቅቶኝ ዘልዬ አንገቱን አነቅኩት። ምታኝ ምታኝ ከማለት ውጪ ለመሰንዘር አልሞከረም ። የገራዥ ልጄች እንዳላቀቁን ምንም ማለት ምንም መናገር አልቻልኩም ወወቤት ገብቼ ተኛሁ።

አመሻሹ ላይ እህቴ ጋር ሄጄ እራት በልቼ ስመለስ ኪያ የራሱን ልብስና መኝታ ይዞ አብረን ከምኖርበት ቤት ለቋል።
እራስ ምታት እያጣደፈኝ ነው የዋለው ። ማታም አለቀቀኝም። ለቃልዬ አልወልኩም እሷም አልደወለችም ።
በሁለተኛው ቀን አመሻሹ ላይ ደወልኩላት። እንዳነሳችው ገና  ለምን ስልክሽን ዘጋሽ  ብዬ ሳልጠይቃት ቀድማ ከትናንት ወድያ ቻርጅ ዘግቶባት እንደነበርና ቻርጅ ስታደርገው ብዙ ግዜ መደወሌን መልክት እንደደረሳት መደወል ፈርታ እስክደውል እየጠበቀችኝ እንደነበር ፣ እንደናፈቅኳትና አሁን ለአጭር ሰአትም ቢሆን ልታገኘኝ እንደምትፈልግ፣  ከቻልኩ ወደ ግቢ ሄጄ እንድወስዳት ነገረችኝ ።
መጣሁ እየወጣሽ ጠብቂኝ ከማለት ውጪ ምንም አላልኳትም።
ግቢ ስደርስ ቆማ እየጠበቀችኝ ነበር።  ምንም ሳልናገር ቀጥታ ከአንድ ቀን በፊት ከዛኪ ጋር ወደጨፈረችበት ጭፈራ ቤት ይዣት ሄድኩ።

በሩ ላይ ስንደርስ "እንዴ ኤፍዬ ዛሬ እዚህ ነው የምናመሸው?" አለችኝ።
"አዎ" ብያት ገብተን ትንሽ እንደቆየን
"ምነው ቃል ቤቱ አልተመቸሽም እንዴ ? ይሄን ቤት ከዚህ በፊት ታውቂዋለሽ?"
.

ከ150 ላይክ በኃላ ክፍል 41 ይለቀቃል 🌹

https://t.me/saloda_trading

7.9k 0 21 19 258
20 last posts shown.