"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Религия


🌹«ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን
/አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ።♥ https://t.me/Orthodoxtewahdoc

ሐምሌ 3 በ2014 ዓ°ም ተከፈተ።
📌እግዚአብሔር ቢፈቅድ የቅዱሳኑን ታሪክ እንመማርበታለን ብለን ከፈትነው ቅዱስ እግዚአብሔር ይፍቀድልን አሜን‼
❤የእመ ብርሃን ልጅ🤗

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Религия
Статистика
Фильтр публикаций


✝እንኳን አደረሳችሁ!

"" ነጻነትን ሰበከላቸው! "" (፩ኛ ጴጥ. ፫:፲፱)

"የበዓለ ትንሣዔ ትምህርት"

(ሚያዝያ 12 - 2017)

https://t.me/zikirekdusn


የብርሃን እናቱ ሆይ ካንቺ በነሳው ስጋ እኛነታችንን አከበረ፡፡መዐዛሽ ስቦት አንችን በወደደ ጊዜ ድህነታችን ተሰራ፡፡ድንግል ሆይ እውነተኛው የህይወት እንጀራ : ጣፋጩን የነፍስ መጠጥ አማናዊው የፅድቅ ብርሀን የፈነጠቀብሽ ነሽና ከትውልድ መሀል ብፅዕናሽን እንናገራለን፡፡ጥማችንን የቆረጠ ጥዑም ወይን፡ረሀባችንን ያጠፋ እውነተኛው መብል ካንቺ ወጥቶልናልና እንወድሻለን፡፡ምስራቃዊት በራችን ሆይ ከሴቶች አንችን የሚመስል የለም፡፡ባንቺ ላይ ስለተደረገልን ታላቅ ነገር ዛሬም ለዘላለምም ስምሽን እናገናለን፡፡

ዝምተኛይቱ ድንግል ሆይ አንቺ አንገታቸውን እንደሚያገዝፉ የአይሁድ ሴቶች አይደለሽም።በትሕትና ተልመሽ በንፅሕና አጊጠሽ የባህርያችንን መመኪያ ያስገኘሽልን የፅድቅ በራችን ነሽ። አንችን ማመስገን የነፍስ ምግብ የህሊና እርካታ ነው።ስናመሰግንሽ እናርፋለን ስናርፍ እናመሰግንሻለን።ክብርሽ ከሰማይ ምስጋናሽም ከአርያም ነውና አንችን ለማመስገን ልቦናችን ይብራ አሜን።🌷


ከሴቶች ሁሉ ተለይተሽ የተመረጥሽ #እመቤታችን_ሆይ! አንቺን አናመልክም ነገር ግን ከሁሉ በበለጠ እጅግ በላቀ ምስጋና ክብርሽን እንገልጣለን።

#የተመረጥሽ_ድንግል_እመቤቴ_ማርያም ሆይ ሁልግዜ #በዓይን_ልቦናዬ አይሻለሁ . . . በሃሳቤም በየስፍራው ሁሉ አገኝሻለሁ ልጅሽም የዓለም መድሀኒት ነው ። በተኛሁም ጊዜ እኔን ለመጠበቅ የነቃሽ ነሽ ፣ከመኝታዬም ስነቃ እኔን ለማንሳት የተዘጋጀሽ ነሽ ስቀመጥም እኔን #ለመምከር ትደረሻለሽ ፣ በቆምሁም ጊዜ በቀኜ ትቆሚያለሽ ፣ በተናገርሁም ጊዜ አንደቤቴን ለማጣፈጥ ታከናውኛለሽ ፣ በዝምታዬም ጊዜ ለመጠበቄ ማሞገሻ ነሽ ፣ ሀሴትም ባደረግሁ ጊዜ ተድላ ደስታዬ ነሽ
በእውነት ምን ብዬ እንዴት ልገልጥሽ ይቻለኛል።
ዝክርሽን ዘክሬ በበረከትሽ እንድጎበኝ ፈጣሪ ይርዳኝ።
የእናታችን የኪዳነ ምህረት ረድኤት በረከት ፍቅር አይለየን አሜን ።🤲

፲፮❤️ እናቴ ቅድስት ኪዳነ ምህረት ሆይ በዕለተ ቀንሽ ከክፉ ሁሉ ሰውሪን ሀገራችንን ሰላም አድርጊልን ወቶ ከመቅረት ካልታሰበ አደጋ ከመከራ ስጋ ከመከራ ነፍስ  ሰውሪን።

🌷አሜን በእውነት።🙏

"ላመነባት ለተማፀናት ኪዳነ ምህረት አምባ መጠጊያ ናት🙏


https://t.me/Orthodoxtewahdoc


#"የቃል ኪዳኗ እመቤት ሆይ ለጽድቅ የሚያበቃ በጎ ምግባር ባይኖረኝም እንኳ የገሃነምን ደጅ "እንዳታሳይኝ" እማልድሻለሁ ቃል ኪዳንሽ እንዲሁ በከንቱ አይደለምና፡፡

🌹አሜን በእውነት🙏

❤       ኪዳነ ምህረት እናቴ     ❤


ስምሽ ይጣፍጣል ማር ነው ለአንደበቴ፣
ትውልድ የሚወድሽ ብፅዕት እመቤቴ።
በእጆችሽ የታቀፍሽ የዓለምን ዳኛ፣
ኪዳነ ምህረት የልቤ መፅናኛ❤


 
             🥀 አለው ትበለን 🤲

886 0 12 1 24

Репост из: "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
🌷መልክአ ቅድስት ኪዳነ ምህረት☦

ቅድስት ኪዳነ ምህረት ሆይ በክፉ ሰዎች እጅ ከመውደቅ ከመከራ ስጋ ከመከራ ነፍስ ካልታሰበ አደጋ ሰውሪን።🤲


✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
✍️"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"📖ምሳ 1፥33☦📚
        
✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥
📗ስንክሳር ዘወርኃ ሚያዝያ 16

https://t.me/Orthodoxtewahdoc
🌹የያዕቆብ ሌሊት ይሁንልን🕊




✝✝✝ እንኩዋን ለዕለተ አዳም ዓመታዊ የመታሠቢያ በዓል በሰላም አደረሳችሁ ✝✝✝

+*" ዕለተ አዳም "*+

=>ከትንሳኤ በሁዋላ ያሉ ሰባቱ ዕለታት ስያሜ እንዳላቸው: ሰኞ ማዕዶት: ማክሰኞ ቶማስ/አብርሃም: ረቡዕ ደግሞ አልዓዛር እንደሚባሉ ተመልክተናል::

+ሐሙስ ደግሞ አዳም (የአዳም ሐሙስ) በመባል ይታወቃል:: በዚህ ዕለት መድኃኔ ዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ አዳምን ለማዳን መጸነሱ: መወለዱ: መሰቀሉ: መነሳቱና ማረጉ ይነገራል:: በዕለቱ ሕጻናቱ "ስለ አዳም" የሚል ባሕላዊ ዜማ እያዜሙ በዓሉን ያዘክራሉ::

=>አባታችን አዳም:- የመጀመሪያው ፍጥረት (በኩረ ፍጥረት) ነው::

=>አባታችን አዳም
*በኩረ ነቢያት
*በኩረ ካኅናት
*በኩረ ነገሥትም ነው::

+በርሱ ስሕተት ዓለም ወደ መከራ ቢገባም ወልድን ከዙፋኑ የሳበው የአዳም ንስሃና ፍቅር ነው:: አባታችን ለ100 ዓመታት የንስሃ ለቅሶን አልቅሷል:: ስለዚህ አባታችን አዳም ቅዱስ ነው:: ከሌሎቹ ቅዱሳን ቢበልጥ እንጂ አያንስም::

=>ለአዳም አባታችን የተናገርነው ሁሉ ደግሞ ለእናታችን ሔዋን ገንዘቧ ነውና አብረን እናስባታለን:: እናከብራታለን::

=>አምላከ አዳም ወሔዋን ጸጋ ክብራቸውን : ረድኤት በረከታቸውን ያሳድርብን::

=>+"+ በክርስቶስ በሰማያዊ ሥፍራ በመንፈሳዊ በረከት ሁሉ የባረከን የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አባት ይባረክ:: ዓለም ሳይፈጠር በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን በፍቅር እንሆን ዘንድ በክርስቶስ መረጠን:: +"+ (ኤፌ. 1:3)

   >


ጌታ ሆይ... በቢታንያ አልዓዛር የተባለ ወዳጅህን ከአራት ቀን በኋላ ከሞት እንዳስነሳኸው በወንጌልህ ተጽፎ አንብቤያለሁ። ታዲያ በሥጋ ሐሳብ ከሞትኩ ዘመናት ያለፈኝ እኔንስ የምታስነሳኝ መቼ ነው? ጌታዬ ሆይ ወደ አልዓዛር እንደሄድክ ወደ እኔም ና፥ 'ተነስ' ብለህ  አስነሣኝ። 'ውጣ'ም ብለህ ካለሁበት የኃጢአት ዓለም አውጣኝ። ጌታ ሆይ ለእኔም እዘንልኝ፥ ለእኔም ራራልኝ 🙏አሜን።


"ነገ ሚያዝያ 16 እናታችን ቅድስት ኪዳነ ምህረት  የኪዳን ቀኗ ነው እንኳን አደረሳችሁ።

ወቶ ከመቅረት ካልታሰበ አደጋ ከክፉ ነገር ሁሉ ትሰውረን።🙏


Репост из: "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
††† እንኳን ለቅዱስ አንቲቦስ ሐዋርያ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ቅዱስ አንቲቦስ †††

††† በዚህ ቀን ታላቁ ሐዋርያና ሰማዕት ቅዱስ አንቲቦስ ይታሰባል:: ቅዱሱ በአርማ በምትባል ሐገር በእረኝነት (ጵጵስና) ያገለገለ የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ደቀ መዝሙር ነው::

ቅዱሱ ስለ ክርስቶስ መንጋ ብዙ መከራን ተቀብሏል:: በእሥር ቤት ሳለም ከቅዱስ ዮሐንስ ነባቤ መለኮት (ወንጌላዊ) ክታብ (መልእክት) ደርሶታል:: በክታቡም ከሐዋርያትና ሰማዕታት መቆጠሩን ነግሮታል:: ጊዜው 1ኛው ክ/ዘ ሲሆን ክታቧ ከእኛ አልደረሰችም::

ከቅዱስ ዮሐንስ እግር ቁጭ ብሎ በመማሩ እንደ መምሕሩ የንጽሕና ሰው ነበር:: ከብዙ ዓመታት አገልግሎት በኋላ ስለ ፍቅረ ክርስቶስ በዚሕች ቀን በሰማዕትነት አልፏል::

በታላቁ ቅዱስ መጽሐፍ ደግሞ የዚህ ቅዱስ ስም መጠቀሱን ምስራቅ ኦርቶዶክሶች ያምናሉ:: በዮሐንስ ራዕይ 2:12 ላይ የእኛው (ግዕዙ) "ጻድቅየ መሃይምን" ሲለው የግሪኩ ግን በቀጥታ በስሙ "አንቲጳስ (አንቲቦስ) ብሎ ይጠራዋል፡፡ እርሱም በታናሽ እስያ ከነበሩት 7 አብያተ ክርስቲያናት የአንዱ (የጴርጋሞን) አለቃ የነበረ ሲሆን ሰማዕት መሆኑም በዚሁ ምዕራፍ ላይ ተጠቅሷል ፡፡

"በጴርጋሞንም ወዳለው ወደ ቤተ ክርስቲያን መልአክ እንዲህ ብለህ ጻፍ:: በሁለት ወገን የተሳለ ስለታም ሰይፍ ያለው እንዲህ ይላል:: የሰይጣን ዙፋን ባለበት የምትኖርበትን አውቃለሁ፤ ስሜንም ትጠብቃለህ፥ ሰይጣንም በሚኖርበት፥ በእናንተ ዘንድ የተገደለው የታመነው ምስክሬ አንቲጳስ በነበረበት ዘመን እንኳ ሃይማኖቴን አልካድህም:: ዳሩ ግን ለጣዖት የታረደውን እንዲበሉና እንዲሴስኑ በእስራኤል ልጆች ፊት ማሰናከያን ሊያኖርባቸው ባላቅን ያስተማረ የበልዓምን ትምህርት የሚጠብቁ በዚያ ከአንተ ጋር ስላሉ፥ የምነቅፍብህ ጥቂት ነገር አለኝ:: እንዲሁ የኒቆላውያንን ትምህርት እንደ እነዚህ የሚጠብቁ ሰዎች ከአንተ ጋር ደግሞ አሉ:: እንግዲህ ንስሐ ግባ፤ አለዚያ ፈጥኜ እመጣብሃለሁ፥ በአፌም ሰይፍ እዋጋቸዋለሁ:: መንፈስ ለአብያተ ክርስቲያናት የሚለውን ጆሮ
ያለው ይስማ:: ድል ለነሣው ከተሰወረ መና እሰጠዋለሁ፥ ነጭ ድንጋይንም እሰጠዋለሁ፥ በድንጋዩም ላይ ከተቀበለው በቀር አንድ ስንኳ የሚያውቀው የሌለ አዲስ ስም ተጽፎአል::
(ራዕይ 2:12-17)

††† አምላካችን ከቅዱስ አንቲቦስ በረከትን ያሳትፈን::

††† ሚያዝያ 16 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅዱስ አንቲቦስ ዘሃገረ በአርማ (ሐዋርያዊ ጳጳስና ሰማዕት)
2.ቅዱስ ሳባ ሰማዕት

††† ወርኀዊ በዓላት
1.ኪዳነ ምሕረት (የሰባቱ ኪዳናት ማሕተም)
2.ቅድስት ኤልሳቤጥ (የመጥምቁ ዮሐንስ እናት)
3.ቅዱስ ገብረ ማርያም ጻድቅ ንጉሠ ኢትዮጵያ (የቅዱስ ላሊበላ ወንድም)
4.ቅዱስ አኖሬዎስ ንጉሥ ጻድቅ
5.አባ አቡናፍር ገዳማዊ
6.አባ ዮሐንስ ወንጌሉ ዘወርቅ
7.አባ ዳንኤል ጻድቅ

††† "የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሯችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ:: የኑሯቸውንም ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነት ምሰሏቸው:: ኢየሱስ ክርስቶስ ትናንትና ዛሬ: እስከ ዘለዓለምም ያው ነው:: ልዩ ልዩ ዓይነት በሆነ በእንግዳ ትምሕርት አትወሰዱ:: ልባችሁ በጸጋ ቢጸና መልካም ነው እንጂ በመብል አይደለም:: በዚህ የሚሠሩባት አልተጠቀሙምና::" †††
(ዕብ. ፲፫፥፯)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††

https://t.me/zikirekdusn




Репост из: "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
#ኪዳነ_ምህረት ፲፮

❤️☞︎︎ኪዳነ ምህረት ማለት የምህረት መሐላ ማለት ነው፡ ከ33ቱ በዓላተ እግዝእትነ ድንግል ማርያም አንዱ ነው፡፡ እመቤታችንም ከጌታችን መቃብር እየሄደች በምትለምንበት ጊዜ አይሁድ ለምቀኝነት አያርፉምና ምን ልታመጣብን ነው በማለት ሊጣሏት ሲመጡ ጌታችንም ከዓይናቸው ሰውሯታል አይሁድም ጠባቂ ቢያቆሙ እመቤታችን ዕለት ዕለት መሄዷን አላቋረጠችም እመቤታችንም እንዲህ ብላ ስትጸልይ ልጄ ወዳጄዘንድ ሆይ ከስጋዬ ስጋ ከነፍሴ ነፍስ ነስተህ ሰው በመሆንህ ዘጠኝ ወር ከ5 ቀን በቻለችህ ማሕጸኔ ከአንተ ጋር ሀገር ለሀገር ስለ መሰደዴ መትተህ ልምናዬን ትሰማኝ  እለምንሃለሁ አለች በዚህ ጊዜ ንውጽውጽውታ ሆነ መቃብራት ተሰነጣጠቀ ጌታችንም እልፍ ከእልፍ መላዕክቱ ጋር መጥቶ ሰላም ለኪ ማርያም ምን እንዳደርግልሽ ትለሚኚኛለሽ አላት፡፡ እርሷም መታሰቢያዬን ያደረገውን ስለ ስሜ ለችግረኛ የሚራራውን በስሜ ቤተ ክርስቲያን ያነጸውን መባዕ የሰጠውን ከሃይማኖት ከፍቅር ጽናት ልጁን በስሜ የጠራውን ሁሉ ማርልኝ ከሞተ ስጋ ከሞተ ነፍስ አድንልኝ አለችው፡፡ ጌታችንም ይህን ሁለ እንዳደርግልሽ መሐልኩ ለኪ በርእስየ ወበ አቡየ ሕያው ወበመንፈስ ቅዱስ ብሎ ቃል ገብቶላት አርጓል፡፡
•••
ሌላው በላዔ ሰብ በአማርኛ ሰው በላ ማለት ነው ፤ ትክክለኛ ስሙ ግን ስምዖን ይባላል ቅምር በሚባል አገር የሚኖር
ሌላው በላዔ ሰብ በአማርኛ ሰው በላ ማለት ነው ፤ ትክክለኛ ስሙ ግን ስምዖን ይባላል ቅምር በሚባል አገር የሚኖር እጅግ ባለጸጋ ነበር ፤ እንደ አብርሃም እንግዶችን እየተቀበለ ድሆችን እየመገበ የሚኖር ጻድቅ ነበር ፤ ሰይጣን በዚህ ስራው ቀናበት ሊፈትነውም በሦስት አረጋዊ ሽማግሌዎች ሥላሴ ነን ብሎ ተገለጠለት ልክ እንደ አብርሃም ፤ ሐዋርያው ጳውሎስ ሰይጣን የብርሃን መልአክ መስሎ ይመጣል እንዳለ ፤ እርሱም ሥላሴ መስለውት ተቀበላቸው ተንከባከባቸውም ፤ ምግብ አቀረበላቸው ምግብ አንበላም የምንጠይቅህን ግን ትፈጽምልን ዘንድ ቃል ግባልን አሉት ቃል ገባላቸው እንግዲያውስ የምትወደን ከሆነ አንድያ ልጅህን ሰዋልን አሉት ፤ መጀመሪያ ደነገጠ ኃላ አብርሃም ልጁን ሊሰዋ አልነበረምን እኔንም ሊፈትኑኝ ይሆናል ብሎ ለማረድ ተዘጋጀ፤ ተው የሚለው ድምጽ አልሰማም ፤ አረደው አወራረደው ይዞላቸው ቀረበ ፤ መጀመሪያ ቅመስልን አሉት ቀመሰው ወዲያው እነዚያ ሰዎች ተሰወሩበት እርሱም አህምሮውን ሳተ ተቅበዘበዘ ከዚያ በኃላ ምግብ አላሰኘውም የሰው ስጋ እንጂ መጀመሪያ ቤተሰቦቹን በላ ከዚያም ጓደኞቹን ጦርና የውኃ መንቀል ይዞ ከቤቱ ወጣ ያገኘውን ሰው እየገደለ ይበላል የበላቸው ሰው ቁጥር 78 ደረሰ ፤ በመንገድ ተቀምጦ የሚለምን በደዌ የተመታ አንድ ደሃ አገኘ ሊበላው ወደ እርሱ ተጠጋ ግን ቁስሉን አይቶ ተጸየፈው ፤
•••
ደሃውም “ ስለ እግዚአብሔር ከያዝከው ውኃ አጠጣኝ ” አለው “ዝም በል ደ ሃ ” ብሎት አለፈ ፤ “ አረ በውኃ ጥም ልሞት ነው ስለ ጻድቃን ስለ ቅዱሳን ” አለው አሁንም ዝም ብሎት ሄደ ለሦስተኛ ጊዜ “ ስለ አዛኝቷ ስለ ድንግል ማርያም ” አለው ፤ ሰውነቱን አንዳች ነገር ወረረው “ አሁን የጠራከውን ስም እስኪ ድገመው ስለ ማን አልከኝ ” አለው ፤ ስለ አዛኝቷ ስለ እመቤቴ ማርያም አለው ፤ ይህቺስ ደግ እንደሆነች በምልጃዋም ከሲኦል እንደምታወጣ ህጻን እያለው እናትና አባቴ ይነግሩኝ ነበር ፤ በል እንካ አለው እጁን ዘረጋለት ጥርኝ ውኃ ጠብ አደረገለት ወደ ጉሮሮው አልወረደም የተሰነጠቀ እጁ ውስጥ ገባ እንጂ ፤ በለዔ ሰብ ከዚያች ደቂቃ በኃላ አዕምሮው ተመለሰለት እንዲህም አለ “ በአንድ ዋሻ ውስጥ ገብቼ ስለ ኃጢያቴ አለቅሳለሁ ስጋዬ ከአጥንቴ እስኪጣበቅ እጾማለሁ ወዮሊኝ ወዮታም አለብኝ አለ ፤ ወደ ዋሻ ገባ ምግብ ሳይበላ ውኃም ሳይጠጣ 21 ቀን ኖሮ በርሃብ ሞተ ይላል ተአምረ ማርያም። ጨለማ የለበሱ ሰይጣናት እያስፈራሩ እያስደነገጡ ነፍሱን ወደ ሲኦል ሊወስዷት መጡ ፤ እመቤታችን ፈጥና በመካከላቸው ተገኘች ፤ ልጄ ወዳጄ ይህችን ነፍስ ማርሊኝ አለችው እናቴ ሆይ 78 ነፍሳትን የበላ እንዴት ይማራል አላት ፤ የካቲት 16 ቀን በጎልጎታ የገባህልኝ ቃል ኪዳን አስብ ስምሽን የጠራ መታሰቢያሽን ያደረገን እምርልሻለው ብለኸኝ የለምን አለችው ፤ እርሱም እስኪ ይህቺን ነፍስ በሚዛን አስቀምጧት አለ ቢያስቀምጧት ጥርኝ ውኃው መዝኖ ተገኘ ፤ ስላንቺ ስል ምሬታለው ሰባት ቀን ሲኦልን አስጎብኝታችሁ ወደ ገነት አግቧት አላቸው። ቦታሽ እዚህ ነበር እያሉ ሲኦልን አስጎብኝተው ወደ ገነት አገቧት።
•••
ልመናዋ ክብሯ የልጇም ቸርነት ከሁላችን ጋር ይሁን።

•••https://t.me/Orthodoxtewahdoc ጆይን እያላችሁ ግቡ




Репост из: "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒
♨ወር በገባ በ16 የቅዱስ አቡናፍር ወርኃዊ በዓሉ ነው ።🌹

#ገዳማዊ አቡነ አቡናፍር 🎚+

❖ ይኸውም ቅዱስ አቡናፍር ጥቂት የሰሌን ፍሬዎችን ብቻ እየተመገበ በበረሃ ውስጥ 60 ዓመት የኖረ ታላቅ ጻድቅ ነው፡፡
❖ በእነዚህ ድፍን 60 ዓመታት ውስጥ ከቶ የሰውን ፊት አላየም፤ ዛሬ ከምስር ከተማ ውጪ የተሠራች ቤተክርስቲያኑ የከበረችበት ዕለት ነው፡፡

❖ አቡነ አቡናፍር መልካም ሽምግልና ያለው ስም አጠራሩ የከበረ በገዳም የሚኖርና በገድል የተጠመደ አባት ነው፤ ከላይኛውግብፅ የተገኘ ሲሆን ታሪኩን የተናገረለት ጻዲቁ አባ በፍኑትዮስ ነው፡፡

❖ ይኸውም አባ በፍኑትዮስ ወደ በረሃ ውስጥ በገባ ጊዜ አንዲት የውኃ ምንጭና አንዲት የሰሌን ምንጣፍ አግኝቶ በዚያ እየተጋደለ ብዙ ዘመን የኖረ ነው፡፡
❖ በአንዲት ዕለት አባ በፍኑትዮስ ወደ እርሱ ሲመጣ አባ አቡናፍር አየው፤ አባ በፍኑትዮስም የሰይጣንን ምትሐት የሚያይ መስሎት ደነገጠ፡፡

❖ አባ አቡናፍር ፀጉሩና ጽሕሙ ሰውነቱን ሁሉ ሸፍኖታል እንጂ በላዩ ላይ ልብስ አልነበረውም፤ አባ በፍኑትዮስንም በመስቀል ምልክት ባርኮ አጽናናው፡፡

❖ አቡነ ዘበሰማያትንም ከጸለየ በኋላ ‹‹አባ በፍኑትዮስ ሆይ ወደዚህ መምጣትህ መልካም ነው›› ብሎ በስሙ ከጠራው በኋላ ፍርሃቱን አራቀለት፡፡

❖ ከዚህም በኋላ ሁለቱም በጋራ ጸልየው የእግዚአብሔርን ገናናነት እየተነጋገሩ ተቀመጡ፤ አባ በፍኑትዮስም አኗኗሩንና እንዴት ወደዚህ በረሃ እንደመጣ ታሪኩን ይነግረው ዘንድ አባ አቡናፍርን ለመነው፡፡
✍‹እኔ ደጋጎች እውነተኞች መነኮሳት በሚኖሩበት ገዳም ውስጥ እኖር ነበር፤ የገዳማውያንን ልዕልናቸውን ሲናገሩ ሲያመሰግኗቸውም ሰማሁ፤ እኔም ‹ከእናንተ የሚሻሉ አሉን› ብዬ ጠየኳቸው፡፡

❖ እነርሱም ‹አዎን እነርሱ በበረሃ የሚኖሩ በእግዚአብሔር ዘንድ የከበሩ ናቸው፤ እኛ ለዓለም የቀረብን ስለሆንን ብንተክዝና ብናዝን የሚያረጋጋን እናገኛለን ብንታመም የሚጠይቀንና የፈለግነውን ሁሉ እናገኛለን፣ በበረሃ የሚኖሩ ግን ከዚህ ሁሉ የራቁ ናቸው› አሉኝ፤ ይህንንም ስሰማ ልቤ እንደ እሳት ነደደና ወደ ፈቀደው መንገድ ይመራኝ ዘንድ በእኩለ ሌሊት ተነሥቼ ጸለይኩ፡፡

❖ ከዚህም በኋላ ተነሥቼ ወጥቼ ስጓዝ አንድ አባት አገኘሁና የገዳማውያንን ገድላቸውን እያስተማረኝ ከእርሱ ጋር ተቀመጥኩኝ፡፡
ያዘጋጀልኝን ይህችን ሰሌን አገኘኋት፤ በየዓመቱ 12 ዘለላ ታፈራለች፤ ለየወሩም የምመገበው አንዱ ዘለላ ይበቃኛል ውኃም ከዚህች ምንጭ እጠጣለሁ፡፡

❖ በዚህችም በረሃ እስከዛሬ 60 ዓመት ኖርኩ፤ ከአንተም በቀር የሰው ፊት ከቶ አይቼ አላውቅም›› ብሎ አቡነ አቡናፍር ጣፋጭ ታሪኩን በዝርዝር ነገረው፡፡

❖ ይህንንም ሲነጋገሩ የታዘዘ መልአክ መጥቶ የጌታችንን ሥጋና ደም አምጥቶ አቆረባቸው፤ ቀጥለውም ጥቂት የሰሌን ፍሬ ተመገቡ፤ ወዲያውም የአቡነ አቡናፍር መልኩ ተለወጠ፤ እንደ እሳትም ሆነ፤ ወደ እግዚአብሔርም በተመስጦ እየጸለየ ሳለ ቅድስት ነፍሱ ከሥጋው ተለየች፤ አቡነ በፍኑትዮስም በፀጉር ልብሱ በክብር ገንዞ ቀበረው፡፡

❖ ከዚህም በኋላ አባ በፍኑትዮስ በዚያች ቦታ ይኖር ዘንድ ወደደ ነገር ግን ያቺ የሰሌን ዛፍ ወደቀች፤ የውኃዋም ምንጭ ደረቀች፡፡
በረከታቸው ረድኤታቸው ይደርብን፤ በጸሎታቸው ይማረን

አርኬ
✍️ሰላም ለቅዳሴ ቤትከ በአፍኣ ሀገር ዘምስር። እንተ ሐነፅዋ ኬነውት ወጠበብተ ምክር። አቡናፍር አቡየ ሠውረኒ አመ ዕለተ ፍዳ ወፃዕር። በዘከደነከ እምሐሩር ወቊር። እምነ ርእስከ ወጽሕምከ ዘወረደ ጸጒር።

https://t.me/Orthodoxtewahdoc






እንደተናገረ ተነስቷል
             
Size:-35.5MB
Length:-38:20

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
http://t.me/abagebrekidan
http://t.me/abagebrekidan


✍️..ስለ እውነት አንገቱን የተቆረጠ ታላቅ ቅዱስ ሰመዓት መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ "ሚያዝያ 15 ቀን ፀአተ ነፍሱ ለዮሐንስ መጥምቅ"💚💛♥️

✅በዚህች ታላቅ ዕለት የቅዱስ ዮሐንስ ራሰ ለ15 ዓመት ስታስተምር  ከኖረች በኋላ በ45 ዓ/ም በሃገረ ዐረቢያ ነፍሱ ከራሱ ተለይታ ከበድኑ ጋር ተቀብራለች።

❤በረከቱ ይደርብን!!!🤲


ረቡዕ‼

☞ ከትንሳኤ በኃላ ያለው 3ኛው ቀን አልዓዛር ተብሎ ተሰይሞል፡፡
☞አልዓዛር በዚህ ዕለት የማርያምና የማርታ ወንድም የሆነው አልዓዛር ከሞተ አራት ቀን ሆኖት ሳለ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሞት አስነሥቶታል፡፡
☞ለትንሣኤ ክርስቶስ ምሳሌ ነው፡፡
☞ለአይሁድ የአልዓዛር መነሣት ቅናት ፈጥሮባቸዋል፡፡እርሱ ሁሉ ትንሣኤና
ሕይወት መሆኑን ገልጦ ይህንን ቀን ለአልዓዛር መታሰቢያ ይሆን ዘንድ
አልዓዛር
ተብሎ ተሰይሞ ተስቦ ይውላል፡፡(ዮሐ ፲፩፥1-፵፬)

ቴሌግራማችንን ይቀላቀሉ
https://t.me/Orthodoxtewahdoc

Показано 20 последних публикаций.