Фильтр публикаций


#MoH

የጤና ባለሙያዎች የብቃት ምዘና ፈተና በመጋቢት 2017 ዓ.ም ይሰጣል።

ፈተናውን የምትወስዱ ተፈታኞች ምዝገባ ከዛሬ የካቲት 24/2017 ዓ.ም እስከ መጋቢት 7/2017 ዓ.ም ይከናወናል።

ፈተናውን የምትወስዱ የመንግሥትም ሆነ የግል ተቋማት ተመዛኞች በኦንላይን http://hple.moh.gov.et/hple ላይ በመግባት ምዝገባ ማድረግ ትችላላችሁ ተብሏል።

በተጠቀሱት ቀናት እንድትመዘገቡና ሲስተሙ የሚሰጣችሁን የፈተና መለያ ቁጥር (Registration No.) የያዘ ስሊፕ Print አድርጋችሁ መያዝ ይኖርባችኋል።

ለተጨማሪ መረጃ፦
0115186275 / 0115186276

እያንዳንዱ የፈተና ጣቢያ በየሙያ መስኩ ማስተናገድ በሚችለው ከፍተኛ የተመዛኝ ቁጥር ልክ ገደብ ስለተቀመጠለት፥ ተመዛኞች ምዝገባውን ቀድማችሁ በማጠናቀቅ ተጠቃሚ መሆን የምትችሉ መሆኑ ተገልጿል።

Note:
በጥር 30/2017 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስቴር የተሰጠውን የመውጫ ፈተና ተፈትናቹ ያለፍችሁና በዚህ የብቃት ምዘና ፈተና ለመቀመጥ የተዘጋጃችሁ ነገር ግን ቴምፖራሪ ዲግሪ ከተቋማችሁ ያልደረሰላችሁ ተመዛኞች ከትምህርት ሚኒስቴር ይህ ጉዳይ ቀጥታ ከሚመለከተው የሥራ ክፍል የትብብር ደብዳቤ ማያያዝ ይጠበቅባችኋል ተብሏል።

@tikvahuniversity

28.8k 0 547 52 120

#ASTU

አዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የተለያዩ ፕሮጀክቶችን አስመርቋል።

የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ ትምህርት ቤት፣ ቅድመ-መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ መጀመሪያ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት፣ የአካሚክ ሠረተኞች መኖሪያ ህንጻ፣ ባለ አራት ወለል የታደሰ የንግድ ማዕከል ህንጻ እና የሠረተኞች መዝናኛ ላውንጅ የተመረቁ ፕሮጀክቶች መሆናቸው ተገልጿል።

ዕድሳት ተደርጎባቸውና ተገንብተው የተመረቁት ፕሮጀክቶች፥ የትምህርት ጥራትን ለማምጣት እንዲሁም የተቋሙን ሠራተኞች እርካታ ለማምጣት ያግዛሉ ተብሏል።

ዩኒቨርሲቲው የዳታ ማዕከል፣ የምርምር ፓርክ እና ዘርፈ-ብዙ አገልግሎት የሚሰጥ አዳራሽ ግንባታዎች እያከናወነ መሆኑ ተጠቁሟል።

@tikvahuniversity

29k 0 23 23 112

#ጥቆማ

የእንግሊዘኛ ቋንቋ ምዘና ፈተና (IELTS Test) በድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ይሰጣል!

ብሪቲሽ ካውንስል ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር የ'IELTS' ፈተና የካቲት 29/2017 ዓ.ም ይውሰዱ!

ዩኒቨርሲቲው ፈተናውን መውሰድ የሚፈልጉ አመልካቾች የኦንላይን ምዝገባ በማድረግ ላይ ይገኛል።

ኦንላይን ይመዝገቡ 👇
https://forms.gle/LxdEGVCMDZaPpACV7

ለበለጠ መረጃ፦
☎️ 0923032129

@tikvahuniversity


Репост из: TEST Channel Biruk
21ኛ፣ 22ኛ እና 23ኛ ዙር ሙሉ የሒሳብ መዝገብ አያያዝ (Modern Accountancy) ስልጠና ሰኞ መጋቢት 01/2017 ዓ.ም በፒያሣ እና በመገናኛ ካምፓስ በቀን እና በማታ መርሐግብር ይጀመራል!

👉 ተግባርን ከንድፈ ሀሳብ ያስተሳሰረ ስልጠና
👉 መሠረታዊ አካውንቲንግ እና ኦዲት አሰራር፣ ሙሉ የአካውንቲንግ ሒሳብ አሰራር በፒስቺሪ ተደግፎ እና የግብር አያያዝ ትምህርቶችን አካቶ የሚሰጥ
👉 የሥራ ላይ ስልጠና (Internship) የተመቻቸለት

☎️ 0906777799 / 0906777755
አድራሻ
ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ
ቁ.2፡ መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ

Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute


#MoE

በሰኔ 2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ዕጩ ተመራቂዎች የፋይዳ መታወቂያ ሊያወጡ ይገባል። - ትምህርት ሚኒስቴር

የካቲት 21/2017 ዓ.ም በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ተፈርሞ ለሁሉም የመንግሥት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተላከ ሰርኩላር፤ ብሔራዊ ዲጂታል መታወቂያ (ፋይዳ) የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተማሪ እና የሠራተኞችን መረጃ በተደራጀ መልኩ ለመያዝ ጠቀሜታ እንዳለው ይገልጻል።

የሀገር አቀፍ ፈተናዎችን ደህንነት ለማስጠበቅ አስፈላጊ መሆኑንም ያትታል።

በዚህም በሰኔ 2017 ዓ.ም የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና የሚወስዱ ዕጩ ተመራቂዎች ፈተናውን ለመውሰድ የፋይዳ መታወቂያ ሊያወጡ እንደሚገባ አሳስቧል።

@tikvahuniversity

66.9k 0 722 143 548

እንኳን ለ፻፳፱ ኛው የዓድዋ ድል መታሰቢያ እና የጥቁር ሕዝቦች የድል በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

የበለጠ ይጠብቁ ...
ሴጅ ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት

Congratulations on the 129th Anniversary of Adwa Victory Day!

Expect More ...
Sage Training Institute

Telegram: https://t.me/sagetraininginstitute
TikTok: https://www.tiktok.com/@sage_training_institute
LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/sage-training-institute

☎️   0906777799 / 0906777755
አድራሻ
ቁ.1: ፒያሣ ቸርችል ጎዳና ኤልያና ሆቴል 2ኛ ፎቅ
ቁ.2: መገናኛ ታሜጋስ ህንፃ 2ኛ ፎቅ


ዶ/ር ኤልሳቤት አርአያ 👏

ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ህክምና ትምህርት ቤት 3.93 CGPA በማምጣት የወርቅ ሜዳልያ ተሸላሚ

የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም ያሰለጠናቸውን 179 ተማሪዎች ዛሬ ማስመረቁ ይታወቃል።

@tikvahuniversity

55.5k 0 149 248 1.6k

#AAUCHS

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ በቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም ያሰለጠናቸውን 179 ተማሪዎች አስመርቋል።

153 ተማሪዎች በሜዲካል ዶክትሬት፣ 21 ተማሪዎች በጥርስ ህክምና እና 23 ተማሪዎች ደግሞ በአኔስቴዥያ የመጀመሪያ ዲግሪ ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ ናቸው።

ከአጠቃላይ ተመራቂዎቹ መካከል 165 ተማሪዎች የላቀ ውጤት በማስመዘገቡ የተመረቁ መሆናቸው ዩኒቨርሲቲው ገልጿል።

@tikvahuniversity

47k 0 21 129 176

#Update

የጤና ተመራቂዎች የሙያ ብቃት ምዘና (COC) አመልካቾች ምዝገባ ከነገ የካቲት 22/2017 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ቀናት ክፍት እንደሚሆን ይጠበቃል።

የሙያ ብቃት ምዘና ለመውሰድ እየጠበቁ የሚገኙ የጤና ተመራቂዎች ምዝገባ በየካቲት መጀመሪያ ለማከናወን ዕቅድ ተይዞ የነበረ ቢሆንም በተለያዩ ምክንያቶች መዘግየት አጋጥሟል።

አሁን ላይ አጋጥመው የነበሩ ችግሮች መፍትሔ በማግኘታቸው ከነገ ቅዳሜ የካቲት 22/2017 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ጥቂት ቀናት የአመልካቾች ምዝገባ (በድጋሜ ተፈታኞችን ጨምሮ) እንደሚደረግ ከጤና ሚኒስቴር ያገኘነው መረጃ ያሳያል።

@tikvahuniversity

69k 0 944 104 249

በነፃ ብር በመላክ የM-PESAን ነፃ አገልግሎት እናጣጥም! ከM-PESA ወደ የትኛውም የሳፋሪኮም ስልክ በነፃ እንላክ!

#MPESASafaricom #MPESAEthiopia


በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ለመውሰድ ከ600 ሺህ በላይ ተማሪዎች ተመዝግበዋል፡፡ - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት

ለዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የተማሪዎች ምዝገባ ከታህሳስ 6 እስከ ጥር 6 ቀን 2017 ዓ.ም መከናወኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) አስታውሰዋል፡፡

በዚህም ከ608 ሺህ በላይ የተፈጥሮ ሳይንስ እና የማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች መመዝገባቸውን ገልፀዋል።

ሀገር አቀፍ ፈተናው በወረቀት እና በበይነ መረብ የሚሰጥ ሲሆን፤ ክልሎች በኦንላይን እና በወረቀት የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና የሚወስዱ ተማሪዎችን መረጃ እስከ የካቲት 25/2017 ዓ.ም ድረስ ለይተው እንዲያሳውቁ ይጠበቃል፡፡

የፈተና ዝግጅቱ ከኢኮኖሚክስ በስተቀር ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያሉ የትምህርት አይነቶችን ያካተተ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ኢኮኖሚክስ በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት የገባ በመሆኑ ለዚህ ዓመት ከ12ኛ ክፍል ብቻ እየተዘጋጀ መሆኑን አንስተዋል። #ENA

@tikvahuniversity

53.1k 0 89 33 159

በኦሮሚያ ክልል በ2017 ዓ.ም ከ212 ሺህ በላይ ተማሪዎች ሀገር አቀፍ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ይወስዳሉ፡፡ - የኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቢሮ

በኦሮሚያ ክልል በ2017 ዓ.ም ከ212 ሺህ በላይ ተማሪዎች ሀገር አቀፍ ፈተና የሚወስዱ ሲሆን፤ 59 በመቶ የሚሆኑት የተፈጥሮ ሳይንስ ቀሪዎቹ ደግሞ የማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ መሆናቸውን የክልሉ ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ቶላ በሪሶ (ዶ/ር) ለፋና ዲጂታል ተናግረዋል፡፡

ሀገር አቀፍ ፈተና በወረቀት እና በኦንላይን ይሰጣል ያሉት ኃላፊው፤ ከ50 ሺህ በላይ የሚሆኑ ተማሪዎች ፈተናውን በኦንላይን የሚወስዱበት ሁኔታ እየተመቻቸ ነው ብለዋል፡፡ ተማሪዎች ፈተናውን በኦንላይን የሚወስዱባቸው ማዕከላት እየተለዩ እንደሆነ ጠቁመዋል። #FMC

@tikvahuniversity


#ጥቆማ

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለደረጃ አንድ የቻይንኛ ቋንቋ ሰርተፊኬት ፕሮግራም ምዝገባ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡

150 ተመዝጋቢዎች በፕሮግራሙ ይሳተፋሉ ተብሏል፡፡

ለደረጃ ሁለት የቻይንኛ ቋንቋ ሰርተፊኬት ፕሮግራም ምዝገባ ያደረጉ አመልካቾች ትምህርት ነገ የካቲት 22/2017 ዓ.ም ይጀመራል፡፡

የምዝገባ ቦታ፦
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኮንፊሽየስ ኢንስቲትዩት ቢሮ፥ 6 ኪሎ ዋና ግቢ፣ ፎረም ህንጻ፣ 8ኛ ፍሉር ጠዋት ከ3፡00-5፡00 ሰዓት

የስልጠናው ቦታ፦
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ 6 ኪሎ ካምፓስ

@tikvahuniversity


ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ በንግድ ሀሳብ ፈጠራ ውድድር አሸናፊ ለሆኑ ተወዳዳሪዎች ሽልማት ሰጠ።

የዩኒቨርሲቲው የኢንተርፕርነርሺፕና ቴክኖሎጂ ማበልጸጊያ ዳይሬክቶሬት ባዘጋጀው የንግድ ፈጠራ ውድድር ላይ በባለሙያዎች ድጋፍና ክትትል የተደረገላቸው 23 የፈጠራና ንግድ ሀሳቦች ቀርበዋል።

በውድድሩ ከቀረቡ ሀሳቦች መካከል ከ1-3ኛ ደረጃ ላገኙ ተወዳዳሪዎች፥ ፈጠራቸውን ወደ ተግባር ለመለወጥ የሚያስችል የገንዘብ ሽልማት ተሰጥቷል።

አንደኛ ደረጃ ለወጣ የመነሻ ካፒታል ብር 200,000፣ በሁለተኛነት ለተመረጠ ብር 150,000 እንዲሁም በሦስተኛነት ለተመረጠው ብር 100,000 ሽልማት ተበርክቷል።

በውድድሩ ቀርበው አሸናፊ የሆኑት የፈጠራ ሀሳቦች የአካባቢውን ችግር ፈቺ መሆናቸው ተገልጿል። የቀረቡት የፈጠራ ሀሳቦች ምንድን ናቸው?

➦ የማይድኑ ነገር ግን በዘላቂነት መድኃኒት የሚሰጣቸው ታማሚዎቹ ባሉበት ሆነው የባለሙያ ድጋፍ እንዲያገኙ በቴሌ ሜዲሲን የሚታገዝ የፈጠራ ሀሳብ፣

➦ በአባቢያችን የሚገኙ ደረቅና ፍሳሽ ቆሻሻዎችን በመጠቀም የሚሰራ የተፈጥሮ ማዳበሪያ፣

➦ ተማሪዎችን ሊያግዝ የሚችል ሰው ሰራሽ አስተውሎትን የሚጠቀም መተግበሪያ። #ሀዩ

@tikvahuniversity

56.3k 0 27 44 230

የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ፕሬዝዳንት ተመድቦለታል።

ንጉሥ ታደሰ (ዶ/ር) ከየካቲት 18 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ሆነው ተሹመዋል።

ፍቅሬ ደሳለኝ (ፕ/ር) ከ2009 ዓ.ም ጀምሮ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት በመሆን ሲያገለግሉ ቆይተዋል።

ዩኒቨርሲቲው ራስ ገዝ ለመሆን የተለያዩ ፖሊሲዎችና መመሪያዎች ዝግጅት በመጠናቀቅ ላይ መሆናቸው በሥራ ርክክብ ወቅት ተገልጿል።

@tikvahuniversity


#DillaUniversityAlumniForum

ዲላ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ የተቋሙ ምሩቃን የሚገናኙበት መድረክ አዘጋጅቷል፡፡

ወደ ድሞው የእውቀት ቤታችሁ ለመሔድ በተከታዩ ሊንክ ይመዝገቡ 👇
https://forms.office.com/r/EXc4rmXFYB

@tikvahuniversity


⛺🗺 ሃይኪንግ ላይ ሆናችሁ ዳታ መጠቀም ፈልጋችሁ ታውቃላችሁ? እነሆ አዲስ ቅመም!

💨⚡ የትም ይዛችሁት መሄድ የሚያስችላችሁ እስከ 6 ሰዓት የሚቆይ የባትሪ አቅም ያለውና አዳዲስ የቴክኖሎጂ ትሩፋቶችን ይዞ በአንዴ እስከ 8 ሰው ድረስ የሚያስጠቅመውን ልዩ ቅመም MIFIን ገዝተን ፈጣን 4G ኢንተርኔት እንጠቀም! ለ30 ቀን ከሚቆይ ነጻ 30ጊባ ዳታ ጉርሻ ጋር 😋

ከሳፋሪኮም ጋር አንድ ወደፊት⚡
  
🔗 የM-PESA ሳፋሪኮም መተግበሪያ በዚህ ሊንክ እናውርድ፦ https://play.google.com/store/apps/details?id=et.safaricom.mpesa.lifestyle

#MPESASafaricom #SafaricomEthiopia #1Wedefit #Furtheraheadtogether


አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የ2017 አጋማሽ ዓመት የተማሪዎች የምርቃት ስነ-ስርዓት በሳምንቱ መጨረሻ ያካሒዳል።

በዚህም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የጤና ሳይንስ ኮሌጅ ተማሪዎች የምረቃ ስነ-ስርዓት ቅዳሜ የካቲት 22/2017 ዓ.ም እንደሚካሔድ ተገልጿል።

@tikvahuniversity

54.1k 0 39 34 169

#UoGAlumni

70ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን ማክበር ላይ የሚገኘው ጎንደር ዩኒቨርሲቲ፤ የተቋሙን የቀድሞ ምሩቃን መመዝገብ ጀምሯል።

ይህም የቀድሞ የዩኒቨርሲቲው ተመራቂዎችን አብረዋቸው ከተማሩ ጋር ለማገናኘት እና ዩኒቨርሲቲው በሚያከናውናቸው ተግባራት አበርክቶ ለማድረግ ያስችላል ተብሏል።

ተከታዩን ሊንክ በመጫን ይመዝገቡ 👇
https://alumni.uog.edu.et

@tikvahuniversity


#ጥቆማ

አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአድዋ ድል መታሰቢያ በዓልን ምክንያት በማድረግ ልዩ የተማሪዎች ሴሚናር አዘጋጅቷል።

ሴሚናሩ "ኢትዮጵያዊነት እና አፍሪካዊነት በእኔ ትውልድ" በሚል ጭብጥ ላይ ይመክራል።

ሴሚናሩ አርብ የካቲት 21/2017 ዓ.ም ጠዋት 3:00 ሰዓት በዋናው ግቢ ራስ መኮንን አዳራሽ ይካሔዳል።

@tikvahuniversity

Показано 20 последних публикаций.