🇵🇸ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: не указана


ይህ ቻናል ቁርኣን እና ሐዲስ መሰረት በማድረግ የመልካም ቀደምቶቻችን ፋና በመከተል ስለ እስልምናችን የምንማማርበት እና የምንመካከርበት ቻናል ነው።
✍እስልምና አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው‼
👇🏾👇🏾👇🏾
@hamdquante
አስተያየትዎ ይበልጥ ይገነባናል
👉🏿 @hamdquante_bot👈🏿

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
не указана
Статистика
Фильтр публикаций



በመስጂድ, በመድረሳ, በየትኛውም ዐይነት የዳዕዋ ዘርፍ እየተንቀሳቀስክ እንደሆነ ካወቀህ ገና ሲያይህ በስስት በሽታ የገረጣ ፊቱ የሚቀያይርብህ በኺል በሞላበት;

"ዳዕዋው የእኔም የአንተም አደራ ነው!! አብሽር በምችለው ከጎናችሁ ነኝ!!"
በሚሉ የኢማን ሽቶ ግንባራቸው ላይ በሚያበራ ወንድሞች ላይ የአላህ ሰላምታ ይስፈን!!



ዲን ላይ መተጋገዝ የነብያቶች አካሄድ ነው፦
📖 {…سَنَشُدُّ عَضُدَكَ بِأَخِيكَ …}
{…ጡንቻህን በወንድምህ እናጠነክራለን…}





https://t.me/hamdquante



    የሸመገሉ አባቶች "ሸይኽ" እያሉ ማክበር ኢስላማዊ ስርዓት ነው!!

📖{قَالَ مَا خَطْبُكُمَا ۖ قَالَتَا لَا نَسْقِى حَتَّىٰ يُصْدِرَ ٱلرِّعَآءُ ۖ وَأَبُونَا شَيْخٌۭ كَبِيرٌۭ}
{……"ጉዳያችሁ ምንድን ነው?" አላቸው፡፡ "እረኞቹ ሁሉ (መንጋዎቻቸውን) እስከሚመልሱ አናጠጣም፡ አባታችንም ትልቅ ሸይኽ (ሽማግሌ) ነው» አሉት፡፡}

         [አል_ቀሰስ:²³]



📖{قَالُوا۟ يَٰٓأَيُّهَا ٱلْعَزِيزُ إِنَّ لَهُۥٓ أَبًۭا شَيْخًۭا كَبِيرًۭا فَخُذْ أَحَدَنَا مَكَانَهُۥٓ ۖ إِنَّا نَرَىٰكَ مِنَ ٱلْمُحْسِنِينَ}
{የተከበርከው ሆይ! "ለእርሱ ትልቅ ሸይኽ (ሽማግሌ) አባት አለው፡፡ ስለዚህ በእርሱ ስፍራ አንደኛችንን ያዝ፡፡ እኛ ከመልካም ሠሪዎች ሆነህ እናይሃለን" አሉት፡፡}

        [ዩሱፍ:⁷⁸]



📖{قَالَتْ يَٰوَيْلَتَىٰٓ ءَأَلِدُ وَأَنَا۠ عَجُوزٌۭ وَهَٰذَا بَعْلِى شَيْخًا ۖ إِنَّ هَٰذَا لَشَىْءٌ عَجِيبٌۭ}
{"ዋልኝ! እኔ አሮጊት ይህም ባሌ ሸይኽ (ሽማግሌ) ሆኖ ሳለ እወልዳለሁን? ይህ በእርግጥ አስደናቂ ነገር ነው" አለች፡፡}

          [ሁድ:⁷²]



🤝ለስላሳ: ትሁት እና ገር ባሪያ ሁን!!
https://t.me/hamdquante



    ነብዩﷺ  አላህ መልእክተኛ አድርጎ የላካቸው ትልቁ ዐላማ ሽርክን ገርስሶ ተውሒድ ለማስፈን ነው።

   እንደሚታወቀው ብዙኃን ሙሽሪኮች አላህ ላይ የሚያጋሯቸው ነብያቶች እና በሆነ ዘመን የነበሩ ደጋግ ሰዎችን ነው። ስለሆነም ነብዩ ነብያቶችን ለአላህ አጋር አድርጎ ከመያዝ አጥብቀው ያወግዛሉ።

  ሌሎች ነብያቶች እንዳይመለኩ ከሚያወግዙት በበለጠ ራሳቸው እንዳይመለኩ አስጠንቅቀው ያስተምራሉ። ቀብራቸው እንዳይመለክ ጌታቸውን ይማፀናሉ። ከፊል ሰዎች ቀላል የሚመስላቸው ነገር ላይ ራሱ "አላህ እና አንተ ከፈለክ" ሲባሉ በቁጣ «ለአላህ ቢጤ እያደረከኝ ነው??» ብለው ያወግዛሉ። ይህ የሲራጠል ሙስተቂም መንገድ ነው!!


እናም ወዳጄ………
  አንድ ሸይኽ ወይም አንድ ኡስታዝ ሰዎችን በጭፍን ከመከተል እያወገዘ የሚያስተምር ከሆነ: ራሱ በሚያስተምረው ትምህርት መሰረት እሱንም ቢሆን ተማሪዎቹ በጭፍን መከተል እንደሌለባቸው እሱና አድማጮቹ ሊገነዘቡ ይገባቸዋል።


  የኢስላም ፈርጥ የሆኑ ቀደምት ዑለማዎች ከመሃላቸው አንዱን ነጥሎ ተቅሊድ ማድረግ የማይቻል ነገር ሆኖ: የአንተን ሸይኽ መከተል ግን የምታግራራ ከሆነ ገና መታጠብ ያለበት ነገር ለመኖሩ ማሳያ ነው።




https://t.me/hamdquante



እርሶ የቱጋ ኖት??

የመጀመሪያ ሚስት………
የላጤ አስተዳደር ላይ የሚደረግ አመፅ ተደርጋ ትታያለች፣።

ሁለተኛዋ ሚስት………
የመጀመሪያ ትግል ላይ የተፈፀሙ ስህተቶች የሚታረሙበት ሂደት ተደርጋ ትታያለች።

ሦሥተኛዋ ሚስት…………
ጠንካራ የሆነ ግዛት እንደ መመስረት ተደርጋ ትታያለች።

አራተኛዋ ሚስት………
ደህንነቱ የተጠበቀ ህዝብ እና ጠንካራ መከላከያ ያለው መንግስት ለመመስረትህ ማረጋገጫ ናት።




ባረከላሁ ፊክ!!
ካነበብከው በኋላ ለግዛት ሰላም ስትል ከስልክህ ላይ ደልተው።





https://t.me/hamdquante


🤳
ሌላው ይደረስበታል…………

ቀጣይ ግን ልክ ከኤርፖርት ሲወርዱ ጀምሮ GPS መግጠም ሳያስፈልግ አይቀርም!!



   ሕይወት በድመት እና በአይጥ መሃል እንዳለ ውድድር ናት። ብዙ ጊዜ አይጧ ታሸንፋለች።

ምክንያቱም፦
  ድመቷ ለምግብ ስትሮጥ፤
  አይጧ ግን ለሕይወት ነው የምትሮጠው።


የምልህ ከገባህ ......
  👌ሁል ጊዜ ከፍላጎትህ; አላማህን አስቀድም!!




https://t.me/hamdquante



“እየሱስ ይወድሃል” ይለዋል
"አዎን! ሁሉም ሙስሊም ሙስሊም ወንድሙ ይወዳል።" አለው


እኛም ሙስሊም ወንድማችን ስለ ሆነ እንወደዋለን!!




https://t.me/hamdquante



    እስልምና የትላልቆቹ ትልቁ ምኞት!!

🌙ነብዩ ኢብራሂምﷺ አባታቸው ሙስሊም እንዲሆንላቸው ተመኙ;
  ግን አልሆነላቸውም።

🌙ነብዩ ኑሕﷺ ልጃቸው ሙስሊም እንዲሆንላቸው ተመኙ፤
  ግን አልሆነላቸውም።

🌙ነብዩ ሙሐመድﷺ አጎታቸው ሙስሊም እንዲሆንላቸው ተመኙ፤
  ግን አልሆነላቸውም።

  እኔና አንተ ግን አላህ ከራሱ በሆነ ቱሩፋት ይህንን የትላልቆቹ ምኞት የሆነው ትልቁ እስልምና ወፍቆናል። ምን ያህል እንሰራበታለን??

📖{إِنَّ اللَّهَ لَذُو فَضْلٍ عَلَى النَّاسِ وَلَكِنَّ أَكْثَرَ النَّاسِ لَا يَشْكُرُونَ}
{አላህ በሰዎች ላይ ባለ ችሮታ ነው፤ ግን አብዛኞቹ ሰዎች አያመሰግኑም።}






                   https://t.me/hamdquante



ቀልብ ከደረቀ ለካስ……………


ሱዳኒ ነው። በሲጋራ ሱስ የተለከፈ። እንደው ዘመናዊ ምድጃ ብትሉት ማጋነን አይሆንም። አንዱ ነሲሀ ሊያደርግለት መጣና………

"ወንድሜ! ይህ ሲጋራ ይቅርብህ: ቀስ እያለ ወደ ሞት ነው የሚወስድህ" ይለዋል

"ታድያ እኔስ መች ፈጥኜ መሞት ፈለኩኝ??"




https://t.me/hamdquante



    አላህ ሁሉም ነብያቶች ጠርቶ ሲያናግራቸውም ይሁን ስለ እነርሱ ሲናገር በስማቸው ይጠቅሳቸዋል; ነብዩ ሙሐመድ ሲቀር።

  ለነብዩ ሙሐመድ  ግን ሲጠራቸውም ይሁን ስለ እሳቸው ሲናገር ቀጥታ በስማቸው ሳይሆን በክብር ስማቸው {ነብዩ ሆይ} {መልእክተኛው ሆይ} እያለ ይጠራቸዋል።

አንድ ጥያቄ ሊነሳ ይችላል፦
  "አላህ ነብዩን በስማቸው ካልጠቀሳቸው እሱ የላካቸው ነብይ እሳቸው መሆናቸው በምን እናውቃለን?" የሚል
  በእርግጥም አላህ ነብዩን ቀጥታ በስማቸው ውስን ቦታ ላይ ጠቅሷቸዋል፤ እነዚህ ስማቸው የጠቀሰበት ቦታ ላይም ነብይነታቸው በሚገልፅ መልኩ ነው አያይዞ የሚገልፃቸው እንጂ ስማቸውን ብቻ ጠቅሶ አያልፍም።


ለምሳሌ፦
📖{وَمَا مُحَمَّدٌ إِلَّا رَسُولٌ قَدْ خَلَتْ مِن قَبْلِهِ الرُّسُلُ…}
{ሙሐመድ ከእሱ በፊት እንዳለፉት መልእክተኞች መልእክተኛ እንጂ ሌላ አይደለም።…}

       [አል_ዒምራን:¹⁴⁴]


📖{مَّا كَانَ مُحَمَّدٌ أَبَآ أَحَدٍۢ مِّن رِّجَالِكُمْ وَلَٰكِن رَّسُولَ ٱللَّهِ وَخَاتَمَ ٱلنَّبِيِّۦنَ ۗ …}
{ሙሐመድ ከወንዶቻችሁ የአንድም ሰው አባት አይደለም፡፡ ግን የአላህ መልክተኛና የነቢዮች መደምደሚያ ነው፡፡ …}

           [አል_አህዛብ:⁴⁴]


📖{مُّحَمَّدٌ رَّسُولُ اللَّهِ……}
{ሙሐመድ የአላህ መልእክተኛ ነው።……}

           [አል_ፈትሕ:²⁹]





https://t.me/hamdquante



የስስት ክፋቱ……………

"መቅበራው ሊታጠር መዋጮ እየሰበሰብን ነው የአቅምህን ስጠን" ሲሉት
:
:
:
"በሕይወቴ አንድም ቀን ሬሳ ሲያመልጥ አይቼ አላቅም; ባይታጠርስ?"





https://t.me/hamdquante



     ለነብዩﷺ አላህ ከሰጣቸው ብልጫ እና ክብር አንዱ ነው።

  አላህ በቁርኣኑ ለነብዩ ሙሐመድ ባልደረቦቻቸው በስማቸው እየጠሩ እንዳያናግሯቸው ከልክሏቸዋል። ይህ ክብር የተሰጠው ለእሳቸው ብቻ ሲሆን ከእሳቸው በፊት ለነበሩ ነብያቶቾች ግን ህዝቦቻቸው በስማቸው እየጠሩ ያናግሯቸው እንደ ነበር አላህ በቁርኣኑ ጠቅሶታል።


ለምሳሌ………
📖{… قَالَ يَا مُوسَى إِنَّ الْمَلَأَ يَأْتَمِرُونَ بِكَ …}

📖{وَلَمَّا وَقَعَ عَلَيْهِمُ الرِّجْزُ قَالُوا يَا مُوسَى ادْعُ لَنَا رَبَّكَ …}

📖 {… يَا عِيسَى ابْنَ مَرْيَمَ هَلْ يَسْتَطِيعُ رَبُّكَ أَن يُنَزِّلَ عَلَيْنَا مَائِدَةً مِّنَ السَّمَاءِ…}

📖{… وَقَالُوا يَا صَالِحُ ائْتِنَا بِمَا تَعِدُنَا إِن كُنتَ مِنَ الْمُرْسَلِينَ}

📖{قَالُوا يَا هُودُ مَا جِئْتَنَا بِبَيِّنَةٍ …}

📖{قَالُوا يَا نُوحُ قَدْ جَادَلْتَنَا فَأَكْثَرْتَ جِدَالَنَا…}



ለነብዩ  ግን………
📖 {لَّا تَجْعَلُوا۟ دُعَآءَ ٱلرَّسُولِ بَيْنَكُمْ كَدُعَآءِ بَعْضِكُم بَعْضًۭا …}
{በመካከላችሁ የመልክተኛውን ጥሪ ከፊላችሁ ከፊሉን እንደ መጥራት አታድርጉት።…}






https://t.me/hamdquante



"ሰባራው እግርህን እየጎተትክ ሂድ እንጂ
የእጅህ አሻራ የማንም ትከሻ ላይ አታሳርፍ"
ይላሉ




https://t.me/hamdquante



የደፈረሰውን   ሳይጠራ አይጠጣም
የደከረተውም   ሳይነጣ አይሰጣም


ይህ ነው እኔም ያልኩት  ሳይጠራ አልጠጣም
    ያልነጣውም ለብሼ    ገበያ አልወጣም


እንዲህ ነኝ ሲፈጥረኝ   ፊጥራ አይለወጥም
   ለመወደድ ብዬ    ማስመሰል አልችልም





https://t.me/hamdquante


💳
    ATM ማሽን ላይ ብሩን ሳንወስድ ካርዱ የሚመልስልን ለምንድን ነው?
ብሎ ሲጠይቅ

  የዘመኑ ሰው ብር ካየ ሁሉም ነገር ስለሚረሳ ካርዱን ትቶ እንዳይሄድ በሚል ነው!!





https://t.me/hamdquante


💪
     ወጣትነት የመፈንዳት ሳይሆን የዒባዳ እድሜ ነው!!


  እነዝያ ሙሽሪክ ከነበሩ ህዝቦቻቸው ተገንጥለው ተውሒድን በመያዝ ከሦሥት መቶ ዓመታት በላይ ውሻቸውን ይዘው ጉድጓድ ውስጥ የኖሩት አስሃቡል ካህፎች ሽማግሌዎች ሳይሆኑ ወጣቶች ነበሩ።

📖{نَّحْنُ نَقُصُّ عَلَيْكَ نَبَأَهُم بِٱلْحَقِّ ۚ إِنَّهُمْ فِتْيَةٌ ءَامَنُوا۟ بِرَبِّهِمْ وَزِدْنَٰهُمْ هُدًۭى}
{እኛ ታሪካቸውን በአንተ ላይ በእውነት እንተርካለን፡፡ እነሱ በጌታቸው ያመኑ ወጣቶች ናቸው፡፡ መመራትንም ጨመርንላቸው፡፡}

    [አል_ካህፍ: ¹³]


  ኢብራሂም ዐለይሂ ሰላት ወሰላም ተውሒድን አንግሶ ሽርክን ለመደምሰስ ጣዖቶች ሰባብሮ ሙሽሪክ ከነበሩ ህዝቦቹ ጋ ትግል ሲጀምር ሽማግሌ ሳይሆን ወጣት ነበር።

📖{قَالُوا۟ مَن فَعَلَ هَٰذَا بِـَٔالِهَتِنَآ إِنَّهُۥ لَمِنَ ٱلظَّٰلِمِينَ}
{በአማልክቶቻችን ላይ ይህንን የሠራ ማነው? እርሱ በእርግጥ ከበደለኞች ነው» አሉ፡፡}
{قَالُوا۟ سَمِعْنَا فَتًۭى يَذْكُرُهُمْ يُقَالُ لَهُۥٓ إِبْرَٰهِيمُ}
{ኢብራሂም የሚባል ወጣት (በመጥፎ) ሲያወሳቸው ሰምተናል» ተባባሉ፡፡}

      [አል_አንቢያ: ⁶⁰]



  ፀሀይ የስንዝር ያህል በምትቀርብበት: ከአላህ ጥላ በቀር ምንም ዐይነት ጥላ በሌለበት የቂያማ ዕለት አላህ ሱብሀነሁ ወተዓላ ከጥላው ስር ከሚያደርጋቸው ሰባት ዐይነት ዕንቁ ሰዎች አንደኛው ወጣት ነው።
«وشاب نشأ في عبادة الله»
  «በአላህ አምልኮ ያደገ ወጣት»



ወጣትነትህ በምን እያለፈ ነው??
   ቲክቶክ ላይ ተጥደህ የጅል ሳቅ በማየት?
  በጫት እና በመሰል አደንዛዥ ሱሶች በመደንዘዝ?
የእንግሊዝ የስፔን እያልክ የፈረንጅ እርግጫ በመከታተል?

ወይስ…………
  አላህ በቂያ ቀን ከሚያጠልላቸው ወጣቶች ተርታ ለመገኘት ስሜትህን ረግጠህ ዒባዳ ላይ የፀናህ ነህ??








https://t.me/hamdquante


👆
👉ሁለት ሰዎች ነበሩ። አንደኛው ማር ሻጭ ሲሆን ሌላኛው ሬት ይሸጣል። ሬት የሚሸጠው ገበያው በደንበኞች የተጨናነቀ ነው። ማር ሻጩ ግን በተቃራኒው ገበያው ቀኑን ሙሉ እንደ ቀዘቀዘ ነው።

  ማር ሻጩን እየሆነ ባለው ነገር በጣም ተገርሞ ለባልደረባው ጠየቀው;
  "አንተ መራራ የሆነው ሬት እየሸጥክ ብዙ ሰው ይገዛሃል፤ እኔ ግን ጣፋጩን ማር ይዤ የሚገዙኝ በጣም ጥቂቶቹ ናቸው" አለው።

ያኛው ሲመልስ
   "አንተ ማር የምትሸጠው ሬት በሆነ ምላስ ነው: እኔ ግን ማር በሆነ ምላስ ነው ሬት የምሸጠው።"





https://t.me/hamdquante



አነጋገርህ ከተበላሸ: የያዝከው እውነታ ያደበዝዘዋል!!


ንጉሱ ህልም ያይና ወደ አስፈቺ ይሄዳል።
መጀመሪያ ላገኘው ህልም ፈቺ………
  "እንቅልፌ በተኛሁ ጊዜ እንዲህ ዐይነት ህልም አየሁኝ: ሁሉም ጥርሶቼ ረግፈው ወደቁ: ደንግጬ ስነቃ ግን ምንም የሆንኩት ነገር የለም"

ህልም ፈቺው፦
  "ሁሉም ቤተሰቦችህ እያየኻቸው ሊሞቱ ነው።" አለው።
   ንጉሱ በጣም ተናዶ ለወታደሮቹ  "ይህ ሟርተኛ በፍጥነት ወደ እስር ቤቱ አስገቡልኝ" አላቸው።


ወደ ሌላ ህልም ፈቺ ሄደ………
  "ማታ ማታ ስተኛ ሁሉም ጥርሶቼ ከድዴ ረግፈው እየወደቁ ይታየኛል። ፍቺው ምንድን ነው?" አለው

ህልም ፈቺው…………
   "ሁሉም ቤተሰቦችህ ዐይንህ እያየ ሊሞቱብህ ነው" አለው።
ንጉሱ "ይህንንም ከቅድሙ ጋ ቀላቅሉልኝ" አላቸው።
  

ንጉሱ ህልሙ በጥሩ እንዲፈታለት ስለፈለገ አሁንም ወደ ሌላ ህልም ፈቺ ሄደ……
  "በህልሜ ሁሉም ጥርሶቼ እየረገፉ ይታየኛል: ፍቺው ምንድን ነው?" አለ

ህልም ፈቺው…………
  "ማሻ አላህ!! ትልቅ የሆነ ብስራት ላበስርህ ነው" አለው።
ንጉሱ በጣም ጓጉቶ እና ተደስቶ………
  "በምንድን ነው የምታበስረኝ?" አለው።

ህልም ፈቺው…………
   "ከሁሉም ቤተሰቦችህ ረዥም እድሜ የሚኖረው አንተ ነህ!!" አለው።

  ንጉሱ በጣም ደስስስ ብሎት ለዚህ ህልም ፈቺ ውድ የሆነ ስጦታ ሰጥቶ ህዝቡ ዘንድ ዕውቅና እንዲያገኝ አደረገው።


የሦሥቱም ህልም ፈቺዎች ንግግር ተመሳሳይ ትርጉም ያለው ነው; አነጋገራቸው እና የቃላት አመራረጣቸው የፈጠረው ልዩነት እና ተቀባይነት ግን እጅግ በጣም የተራራቀ ነበር።

ወዳጄ!!
  ንግግርህ, እምነትህ, መንሓጅህ ትክክል ሊሆን ይችላል፤ ምላስህ ላይ መርዛማነት ካለ ግን እውነት እያወራህ እንኳ ሰዎች ይሸሹሃል: አጋዥም ይሁን አጋር ታጣለህ።






https://t.me/hamdquante



    ቆዳህ ተኮማትሮ  ፀጉርህ ከሸበተ
ጉልበትህ ተዳክሞ  መሮጥ ከሰሰተ

ምኞት አብቅታለች  ሳታልቅ አቁማለች
ተሰናብታህ ልቴድ  ከፈኗ ለብሳለች!!


ብቻህ መሄድህ ነው  ትተህ ዘመድ ወዳጅ
ለማይቀረው ጉዞ   በ ቀ ረ ው ተዘጋጅ!!





🖊አቡ ሙስሊም
https://t.me/hamdquante


🤲

Показано 20 последних публикаций.