እውን መረጃ


Гео и язык канала: Эфиопия, Амхарский
Категория: Музыка


📌#ቀዳሚ_ምርጫዎ ➠ ፈጣን እና ተዐማኒ መረጃ ➠ወቅታዊ መረጃዎች ➠ልዩ ልዩ ዘገባዎች የምታገኙበት ቻናል
📌ጥቆማ ለመስጠት
👉 @ewun_mereja_bot
#እውነተኛ እና #ትኩስ #መረጃዎች
#እውንነት

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Гео и язык канала
Эфиопия, Амхарский
Категория
Музыка
Статистика
Фильтр публикаций


ሰበር ❗️

ህወሓት መቀሌን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጠረ!


በመቀሌ ከተማ ያለው ሁኔታ ከቁጥጥር ውጭ ሆኗል። ህወሓት በከባድ መሳሪያ የታገዘ ኃይል በመጠቀም ከተማዋን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥሯል። የከተማው ነዋሪዎች ከፍተኛ ድንጋጤ ውስጥ የገቡ ሲሆን፣ ከቤታቸው ለመውጣት እንኳን እየተሳቀቁ ነው።

የደብረጽዮን ገብረሚካኤል ደጋፊዎች በስፋት በማህበራዊ ሚዲያ ላይ "ህወሓት ማለት የትግራይ ህዝብ ነው፣ የትግራይ ህዝብ ማለት ህወሓት ነው" የሚሉ መፈክሮችን እያስተጋቡ ነው። ይህ ሁኔታ በከተማው ውስጥ ያለውን ውጥረት የበለጠ አባብሶታል።

በተጨማሪም፣ የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ የፌዴራል መንግሥቱ በአስቸኳይ ጣልቃ እንዲገባ እና አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርግላቸው ጥሪ አቅርበዋል። ይሁን እንጂ፣ የፌዴራል መንግሥቱ እስካሁን ድረስ በጉዳዩ ላይ ይፋዊ ምላሽ አልሰጠም።

በመቀሌ ያለው ሁኔታ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ የደረሰ ሲሆን፣ ዓለም አቀፉ ማህበረሰብ በአስቸኳይ ትኩረት እንዲሰጥበት ጥሪ ቀርቧል። የከተማው ነዋሪዎች ለከፍተኛ የሰብዓዊ ቀውስ ተጋልጠዋል።(ዜና Ethiopia)

@Ewun_Mereja
@Ewun_Mereja


ብሄራዊ ክህደት ተፈፅሞብናል-ህወሃት‼️

"በትግራይ የጸጥታ ሃይሎች የተጀመረው ህገ መንግስታዊ እና የህግ የበላይነት የማስከበር ንቅናቄ የፕሪቶሪያን የሰላም ሂደት ያከብራል እንጂ የሚጥስ አይደለም።

ሰራዊቱ እና አመራሩ የፕሪቶሪያን ስምምነት በከፈሉት መስዋዕትነት ያመጡ ሲሆን አሁንም ለተግባራዊነቱ እየታገሉ ነው። ህወሓት፣ የትግራይ ህዝብና ሰራዊት፣ ጊዜያዊ አስተዳደሩ ተልእኮውን ለመወጣት እንዲችል በአዲስ መልክ ሊዋቀር ይገባል በማለት ወስኗል።

ስለዚህ የብሄራዊ ክህደት ቡድኑ [የጌታቸው ረዳን ቡድን ነው] በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በትግራይ ላይ የሶስተኛ ወገን/የፌደራል መንግሥቱ/ ጣልቃ እንዲገባ ያቀረበው ጥሪ፣ ግልፅ ብሄራዊ ክህደት እና የፕሪቶሪያውን ስምምነት አደጋ ላይ የሚጥል በመሆኑ በፍጹም ተቀባይነት የለውም።"
በደብረጽዮን የሚመራው ሕወሓት ዛሬ ካወጣው መግለጫ

@Ewun_Mereja
@Ewun_Mereja


የሰሞኑ የንግድ ባንክ ክስተት❗️

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንድ ግለሰብ ሁለት ሰዎችን ገድሎ ራሱን እንዳጠፋ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ተነግሯል።

በአዲስ አበባ ልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ ስድስት ካርል አደባባይ አካባቢ በሚገኝ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ቅርንጫፍ አንድ ግለሰብ ሁለት ሰዎችን ገድሎ ራሱን እንዳጠፋ ከአዲስ አበባ ፖሊስ ተነግሯል።

ክስተቱ ያጋጠመው ትናንት ማክሰኞ መጋቢት 02/2017 ዓ.ም. ሲሆን፤ ለሦስት ሰዎች ሞት ምክንያት የሆነው ሁኔታ የተፈጠረው 'የፍቅር ጥያቄዬ ምላሽ አላገኘም' በሚል ምክንያት መሆኑን ፖሊስ ገልጿል።

አቶ ሽፈራው ረጋሳ የተባለ የባንኩ የጥበቃ ሠራተኛ ለሥራ ባልደረባው የፍቅር ጥያቄ አቅርቦላት ምላሽ ባለማግኘቱ ግለሰቧን እና ከግለሰቧ ጋር የፍቅር ግንኙነት አለው በሚል የጠረጠረውን ሌላ ባልደረባውን በመግደል ራሱን እንዳጠፋ አዲስ አበባ ፖሊስ አስታውቋል።

ግለሰቡ የፍቅር ጥያቄ ያቀረበላት ወይዘሪት ሃና ተስፋዬ የተባለች 32 ዓመት ወጣት እና አቶ ንጉሤ ብርሃኑ የተባለ የሥራ ባልደረቦቹን በጥይት ተኩሶ የገደለው።

የአዲስ አበባ ፖሊስ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ እንደገለጹት ወንጀሉን የፈፀመው የጥበቃ ሠራተኛ ካልተራው ሌላ ሠራተኛን ተክቶ በመግባት እና ከምሽት የጥበቃ ሠራተኞች የጦር መሳሪያ በመቀበል ግድያውን ፈፅሟል።

ግለሰቡ ግድያውን የፈጸመው ተጠርጣሪው ወደ ዕለታዊ ሥራቸው እስኪገቡ ድረስ በመጠበቅ መጀመሪያ አቶ ንጉሤ ብርሃኑ የተባለውን ግለሰብ በሁለት ጥይት መትቶ መግደሉን ኮማንደር ማርቆስ ገልጸዋል።

ግድያው ማክሰኞ መጋቢት 2/2017 ዓ.ም. ጠዋት ከአንድ ሰዓት ተኩል እስከ ለሁለት ሰዓት ሩብ ጉዳይ ድረስ ባላው ጊዜ ውስጥ መፈፀሙን የተናገሩት የአዲስ አበባ ፖሊስ ቃል አቀባይ፤ በሁለቱ ግድያዎች መካከል እስከ 15 ደቂቃ የሚሆን የጊዜ ክፍተት እንደነበረ አመለክተዋል።

ግድያውን የፈጸመው ግለሰብ ባልደረባውን ተኩሶ ከገደ በኋላ ሌላኛዋን የጥቃቱ ሰለባን ከመግደሉ በፊት ከድርጊቱ እንዲቆጠብ መጠየቁን ነገር ግን ፈቃደኛ እንዳልነበረ ተገልጿል።

ግለሰቡ መሳሪያውን እንዲያስቀምጥ እና እጁን እንዲሰጥ በተደጋጋሚ በተደጋጋሚ ጥያቄ ቀርቦለት የነበረ ሲሆን፣ በዚህ መካከልም ወደ ባንኩ አንደኛ ፎቅ በማምራት የፍቅር ጥያቄውን አልተቀበለችም ያላትን በተመሳሳይ ሁኔታ በጥይት መትቶ መግደሉን ፖሊስ ገልጿል።

ግለሰቡ ሁለቱን ባልደረቦቹን ከገደለ በኋላ በያዘው መሳሪያ የእራሱንም ሕይወት እንዳጠፋ የአዲስ አበባ ፖሊስ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ለቢቢሲ ገልጸው በክስተቱ በአጠቃላይ የሦስት ሰዎች ሕይወት ጠፍቷል።

ሁለቱ ሟቾች ወ/ሪት ሃና ተስፋዬ እና አቶ ንጉሤ ብርሃኑ የፍቅር ግንኙነት እንደነበራቸው የሚጠቁም ፎቶግራፎች መገኘታቸውን የጠቆሙት ኃላፊው፤ ፖሊስ በምርመራው ስለግንኙነታቸው እንደሚያጣራ ገልፀዋል።

ከዚሁ ክስተት ጋር በተያያዘ ፖሊስ እያካሄደ ያለውን የምርመራ ሂደት እንደሚቀጥል አስታውቋል።

ቢቢሲ ስለ ግድያው ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ኃላፊዎችን ለማነጋገር ያደረገው ጥረት አልተሳካም።

Via: ቢቢሲ

@Ewun_Mereja
@Ewun_Mereja


የወጣቷ ሥርዓተ ቀብር ተፈፀመ

ሰኞ መጋቢት 1 ቀን ህይወቷ ያለፈው ሞዴል እና የማስታወቂያ ባለሙያ ቀነኒ አዱኛ የቀብር ሥነ ሥርዓት ዛሬ መጋቢት 03/ 2017 ዓ.ም ተፈጽሟል።

በዛሬው ዕለት በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተክርስቲያን ቤተሰቦቿ እና ወዳጅ ዘመዶቿ በተገኙበት በ9:00 ሰዓት ሥርዓተ ቀብሯ ተፈጽሟል።

@Ewun_Mereja
@Ewun_Mereja


ተጠንቀቁ❗️

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን "ታኪሎ ኢንቨስትመንት ባንክ" ሕገ-ወጥ ነዉ ሲል አስጠነቀቀ

የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለስልጣን "ታኪሎ ኢንቨስትመንት ባንክ" በሚል ስም የሚንቀሳቀስ አካል ያለ ምንም ህጋዊ ፈቃድ የኢንቨስትመንት አገልግሎት መስጠት መጀመሩን አሳውቋል።

ባለስልጣኑ ይህ አካል የመጀመሪያው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ባንክ ነኝ ብሎ ድረ-ገጽ ከፍቶ ማስተዋወቁን ገልጿል።

ባለስልጣኑ ባወጣው መግለጫ መሰረት ታኪሎ ኢንቨስትመንት ባንክ በካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች ፈቃድ አሰጣጥና ቁጥጥር መመሪያ ቁጥር 980/2016 መሰረት ፈቃድ ሳያገኝ አገልግሎት እየሰጠ ነው። በዚህም ምክንያት በኢትዮጵያ ውስጥ የካፒታል ገበያ አገልግሎት እንዲሰጥ ያልተፈቀደለት አካል መሆኑን አሳስቧል።

በተጨማሪም ባለስልጣኑ የካፒታል ገበያ አገልግሎት መስጠት የሚችሉት በህጋዊ መንገድ የተመዘገቡና ፈቃድ ያላቸው አካላት ብቻ መሆናቸውን አስገንዝቧል። ግለሰቦች እና ድርጅቶች ከዚህ አካል ወይም ከሌሎች ፈቃድ ከሌላቸው "የካፒታል ገበያ አገልግሎት ሰጪዎች" ጋር ማንኛውም አይነት የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ እንዳያደርጉ አሳስቧል።

@Ewun_Mereja
@Ewun_Mereja


የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር የፌደራል መንግስትን እርዳታ ጠየቀ።

የትግራይ ጊዝያዊ አስተዳደር በትግራይ ክልል ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ በማስመልከት ዛሬ ረፋድ መግለጫ አውጥቷል።

አስተዳደሩ የትግራይ ጦር አዛዦች ከተልኮ ወጭ የአንድ ጠባብ ቡድን የስልጣን ጥም ለማርካት በማለት ግልፅ መፈንቅለ መንግስት ለማድረግ እየተንቀሳቀሱ ቆይተዋል ያለ ሲሆን በዚህ ሳምንትም በተመሳሳይ በሰሜን ምስራቅና በደቡብ ግንባር አዛዦች እንቅስቃሴው በከፋ ሁኔታ ተባብሶ ቀጥሏል ማለቱን በመግለጫው ተመላክቷል።

አስተዳደሩ በመግለጫው ይህንን አደገኛ እንቅስቃሴ እንዲያስቆም ለአጠቃላይ ጦር አዛዡ ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ ትእዛዝ ቢሰጥም የጥፋት ድርጊቱ ማስቆም እንዳልቻለ አስታውቋል።

የጥፋት ድርጊቶቹ ተባብሰው በቀጠሉበት በአሁኑ ሰዓት በስቪሎች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እየተፈፀመ መሆኑንና ከላይ እስከታች ያለውን የመንግስት መዋቅር የማፍረስ እንቅስቃሴዎች ቀጥለዋል ማለቱንም ዳጉ ጆርናል ሰምቷል።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ በመግለጫው የትግራይ ጦር የበላይ አዛዦች የኃላ ቀሩን ቡዱን ፍላጎት ለማሟላት ሲሉ መንግስት እንዲፈርስ እንዲሁም የፕሪቶርያ ስምምነት በይፋ እንዲጣስ በማድረግ የትግራይን ህዝብ ዳግም ወደ ጦርነት እያስገቡት ነውም ብሏል።

አስተዳደሩ በመጨረሻም " የፌደራል መንግስት በትግራይ የፀጥታ ሀይል ስም የሚንቀሳቀሱት አዛዦች የአንድ ኃላቀርና ወንጀለኛ ቡዱን ተላላኪዎች እንጂ የትግራይ ህዝብና ጊዜያዊ አስተዳደሩን እንደማይወክሉ በመረዳት አስፈላጊ እርዳት ማድረግ አለበት" ብሏል። ከዚህ ባሻገር የፕሪቶርያ ስምምነት እንዲ በይፋ ሲፈርስና የትግራይ ህዝብ ዳግም ወደ እልቂት ሲገባ ዝም ብሎ ሊመለከት አይገባም ሲል የትግራይ ጊዝያዊ አስተዳደር ዛሬ ረፋድ ባወጣው መግለጫ አስታዉቋል።

@Ewun_Mereja
@Ewun_Mereja


አባይ ባንክ ለመቄዶንያ የ10 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረገ

የባንኩ ፕረዜዳንት አቶ የኃላ እንደተናገሩ ባንኩ እንደ ባንክ ላለፉት ዓመታት ከመቄዶንያ ጎን አልጠፋም ዛሬም ይህንን እርዳታ ለማድረግ ስናስብ ሰራተኛውንም እናሳታፍ በማለት ከሰራተኛው 3 ሚሊዮን ብር ባንኩ 7 ሚሊዮን ብር በአጠቃላይ 10 ሚሊዮን ብር ድጋፍ ተደርጓል ብለዋል።

ድጋፉንም የተረከቡት ክቡር ዶክተር ቢንያም በለጠ፣ አርቲስትና ጋዜጠኛ ሰይፉ ፋንታሁን እና አርቲስት ይገረም ደጀኔ ናቸዉ።

የክቡር ዶክተር ቢንያም በለጠ ሌሎችም ተቋማት መሳተፍ እንዳለባቸው መልዕክት አስተላልፈዋል።

@Ewun_Mereja
@Ewun_Mereja


⚠️ይህ በምስሉ ላይ የምትመለከቱትን እና መሰለ አደገኛ ሊንኮች ከማንም ቢላክላቹህ በፍፁም እንዳትነኳቸው

በስህተት ላለመንካት ከላኪው ብታጠፉት ይመከራል።

በከፍተኛ ፍጥነት እየተሰራጨ ያለ አደገኛ ሊንክ ሲሆን አካውንታችሁንና የግል መረጃዎቻችሁን ያሳጣቹሃል።

@Ewun_Mereja
@Ewun_Mereja


የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር የሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሀላፊውን ከሀላፊነቱ አነሳ

ግዚያዊ አስተዳደሩ ህግና ስርዐትን አክብረው በማይንቀሳቀሱና በይፉ አመፅ ውስጥ በተሰማሩ ከፍተኛ አመራሮችና ሀላፊወች ላይ የሚወስደውን ዕርምጃ አጠናክሮ ቀጥሏል።

በዚህም የግዚያዊ አስተዳደሩን ትዕዛዝ ተቀብሎ ተፈፃሚ ለማድረግ ፍቃደኛ ያልሆነውን የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ ሀላፊ ከሀላፊነት ማንሳቱን በደብዳቤው አሳዉቋል።

@Ewun_Mereja
@Ewun_Mereja


ዩክሬን ከሩሲያ ጋር የ30 ቀን የተኩስ አቁም ስምምነትን ለመቀበል ዝግጁ መሆኗ ተሰማ

በሳውዲ አረቢያ ከአንድ ቀን የዩናይትድ ስቴትስ እና የዩክሬን ውይይት በኋላ በአሜሪካ የቀረበውን የ30 ቀን የተኩስ አቁም ስምምነት ዩክሬን ለመቀበል ዝግጁ መሆኗን ተናግራለች። የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ዋና ፀሀፊ ማርኮ ሩቢዮ ይህንኑ ሀሳብ ለሩሲያ እንደሚያቀርቡ እና " አሁን ኳሱ በእጃቸው ውስጥ ነው" ሲሉ ተደምጠዋል።የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዶሚር ዘለንስኪ እንዳሉት ሩሲያ በ"አዎንታዊ" ሀሳብ እንድትስማማ የማሳመን ድርሻ የዩናይትድ ስቴትስ ብቻ ነው ብለዋል።

የማክሰኞው የጄዳ ንግግር በዜለንስኪ እና በአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሞላላው የዋይት ሀውስ ቢሮ ውስጥ ከተፈጠረው ያልተለመደ ግጭት በኋላ በሁለቱ ሀገራት መካከል የመጀመሪያው ይፋዊ ውይይት ነው።በጋራ የሁለቱ ሀገራት ተወካዮች በሰጡት መግለጫ፣ ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ መልኩ የትራምፕ እና የዜለንስኪን ግጭት ተከትሎ ዋሽንግተን ያቋረጠችውን ለዩክሬን የስለላ መረጃ ልውውጥ እና የደህንነት ድጋፍ ወዲያውኑ እንደገና እንደሚጀምር ተናግራለች። የአሜሪካ እና ዩክሬን መግለጫ እንደሚያሳየው “ሁለቱም ልዑካን ቡድን ተደራዳሪ ቡድኖቻቸውን ለመሰየም መስማማታቸውን እና ዘላቂ ሰላም ለማምጣት የዩክሬን ደህንነትን ለማስፈን ድርድር ይጀምራሉ” ይላል።

ሩቢዮ ማክሰኞ ማምሻውን በጄዳህ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ሩሲያ ሃሳቡን እንደምትቀበል ተስፋ አደርጋለው ብለዋል። ዩክሬን " ተኩስ ለማቆም እና ለመነጋገር ዝግጁ ነች" ሲሉ አክለዋል። ሩሲያ የተኩስ አቁም ስምምነቱን ውድቅ ካደረገች " በሚያሳዝን ሁኔታ ሰላም ለማምጣት እንቅፋት የሆነው ማን እንደሆነ እናውቃለን" ብለዋል። "ዛሬ ዩክሬናውያን የተቀበሉትን ሀሳብ አቅርበናል ይህም የተኩስ ማቆም እና አፋጣኝ ድርድር ለማድረግ ነው።"፤ "ይህንኑ ለሩሲያውያን እናቀርባለን እናም ለሰላም አዎ እንደሚሉ ተስፋ እናደርጋለን፤ ኳሱ አሁን በእነሱ ግቢ ውስጥ ነው" ሲሉ ተደምጠዋል።

@Ewun_Mereja
@Ewun_Mereja


የኤርትራ መንግሥት፣ የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ምክትል ፕሬዝዳንት ሌትናንት ጀኔራል ጻድቃን ገብረተንሳይ የጦርነት ሰባቂነት አጀንዳ አቀንቃኝ ናቸው በማለት በቃል አቀባዩ የማነ ገብረመስቀል በኩል ከሷል።

ጀኔራል ጻድቃን ሁለቱ አገሮች ጦርነት ውስጥ ለመግባት የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሰዋል ማለታቸው፣ የጦርነት አጀንዳ አራማጅነታቸውን ያሳያል በማለት የማነ ወንጅለዋል። ጀኔራል ጻድቃን ኢትዮጵያ አሰብ ወደብን በኃይል መያዝ አለባት የሚል አቋም ከድሮ ጀምሮ በማንጸባረቅ ይታወቁ ነበር ያሉት የማነ፣ አኹን ግን የሰላም አቀንቃኝ መስለው መታየት ይፈልጋሉ በማለት ተችተዋል። የማነ ይህን ትችት የሠነዘሩት፣ ጀኔራል ጻድቃን በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ጦርነት መቀስቀሱ አይቀሬ መኾኑን ሰሞኑን በጻፉት ጽሁፍ ካስጠነቀቁ በኋላ ነው።

@Ewun_Mereja
@Ewun_Mereja


Видео недоступно для предпросмотра
Смотреть в Telegram
ተኩስ ዓዲ ጉዶም❗️

ትግራይ ክልል ድጋሜ ወደ አስፈሪ ቀውስ እንዳይገባ ብዙዎችን አስግቷል።

ቪዲዬ:- ከመቀሌ 35 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው አዲጉደም ከተማ አሁን ከመሸ ተኩስ መከፈቱ ተሰመቷል።ተኩስ የከፈቱት የእነደብረጺዮን ታጣቂዎች መሆናቸው ተነግሯል።

በእነ ደብረፅዮን የሚመራው የህወሓት ቡዱን የመንግስት ስልጣን ከጊዜያዊ አስተዳደሩ ለመቀማት ከሞከረባቸው አከባቢዎች መካከል አንደኛዋ ነች ዓዲ ጉዶም።በከተማዋ ዛሬ መጋቢት 2 ቀን 2017 ዓ/ም በተኩስ ድምፅ ስትናወጥ ማምሸቷን ተከትሎ "የዛሬው ድርጊታቸው በስልጣናቸው ለመጣ ምንም ርህራሄ እንደሌላቸው ማሳያ ነው" ሲሉ ድርጊቱን ያዩ ብለዋል።

ሌላው ዛሬ ማለዳ የአዲግራት ከተማ አስተዳደር ፅህፈት ቤት "በጉልበት" የተቆጣጠረው በእነ ደብረፅዮን የሚመራው ህወሓት በአዲግራት ያደረገውን በሌሎች የትግራይ ከተሞች ለመድገም እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ያስረዳል ተብሏል።

@Ewun_Mereja
@Ewun_Mereja


የወረባቦ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ፈንታው ከበደ በተተኮሰባቸው ጥይት ተገደሉ‼

ከአስተዳዳሪው አቶ ፈንታው ከበደ በተጨማሪ የወረዳው ፖሊስ ምርመራ ኃላፊ ዋና ኢንስፔክተር አዲስ ዘመን ፍስሃ የአምፑላንስ ሾፌሩ አቶ ከበደ ዛሬ ረፋድ 3:00 ከቢስቲማ ወደ ቦቀቅሳ ሲጓዙ አባና ገንዳ በተባለ ቦታ በጥይት መገደላቸውን ምንጮቼ አረጋግጠውልኛል።የዋና አስተዳዳሪውና ሾፌሩ ስርዓተ ቀብር እየተፈፀመ ሲሆን የዋና እንስፔክተሩ አስክሬን ወደ ደሴ ቤተሰብ ጋር ተልኳል።

ጥይት ሲተኮስ ከኋላ አጅበዋቸው የነበሩት የፀጥታ ኃይሎች በመሸሻቸው ጥቃቱ እንደተፈፀመባቸው የደረሰኝ ጥቆማ ያመለክታል።

ወረባቦ አማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን ከሐይቅ ከተማ በስተምስራቅ የሚገኝ ወረዳ ነው።

@Ewun_Mereja
@Ewun_Mereja


አንጋፋው የማሲንቆና በገና ተጫዋች አለማየሁ ፋንታ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

አንጋፋው የማሲንቆና በገና ተጫዋች፣ ድምጻዊና በያሬድ ትምህርት የሙዚቃ ኮሌጅ የባህላዊ ሙዚቃ መሳዊያዎች መምህር ጋሽ አለማየሁ ፋንታ ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

የጋሽ አለማየሁን ነፍስ በአጸደ ገነት ያኑርልን

@Ewun_Mereja
@Ewun_Mereja


የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት አቶ ጌታቸው ረዳን ትእዛዝ “ አልቀበልም አልፈፅምም “ አለ የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ።

የትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት ፤ “ በቢሮው ስም የቀረበው መግለጫ የአንድ የጊዚያዊ አስተዳደሩ አካል ሳይሆን የአንዱ ቡድን ወታደራዊ ክንፍ መሆኑ በግልፅ የሚያሳብቅና የተፈጠረውን ችግር የሚያባብስ ነው “ ብሎታል።

ትናንት መጋቢት 1/2017 ዓ.ም ፕሬዜዳንት ጌታቸው ረዳ በሦስት ከፍተኛ የሰራዊት አመራሮች የጣሉት ጊዚያዊ እግድ ተከትሎ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል (ዶ/ር) የሚመሩት ህወሓት “ እገዳው መሰረተ ቢስ እና የማይተገበር “ በማለት ውድቅ ለማድረግ ጊዜ አልወሰደበትም።

ዛሬ ማክሰኞ ጠዋት ደግሞ የክልሉ ሰላምና ፀጥታ ቢሮ የጊዚያዊ አስተዳደሩ ፕሬዜዳንት ጊዚያዊ እግድ ሙሉ በሙሉ በመፃረር ባወጣው መግለጫ ፤ በግልባጭ የተፃፈለትን ትእዘዛዝ እንደማይቀበል በመግለፅ “ የህግ ማስከበር እርምጃው “ ይቀጥላል ብሏል።

@Ewun_Mereja
@Ewun_Mereja


ለገዢው ፓርቲ ማጠናከሪያ በመንግስት ተቋማት የሚደረጉ የገንዘብ ማሰባሰቢያዎች “በአስቸኳይ እንዲቆሙ” ኢዜማ ጠየቀ!

የኢትዮጵያ ዜጎች ለማህበራዊ ፍትህ (ኢዜማ) ከመንግስት ተቋማት አገልግሎት ጋር በተያያዘ ለገዢው ብልጽግና ፓርቲ ማጠናከሪያ የሚደረግ የገንዘብ ማሰባሰቢያ “በአስቸኳይ ያስቆም” ዘንድ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ጥያቄ አቀረበ። ምርጫ ቦርድ በገዢው ፓርቲ ላይ የሚወስደውን የወሰደውን “የእርምት እርምጃ” ለህዝብ “በግልጽ እንዲያሳውቅም” ፓርቲው ጠይቋል።

ኢዜማ ዛሬ ማክሰኞ መጋቢት 2፤ 2017 ባወጣው መግለጫ፤ ብልጽግና ፓርቲ ባለፈው ጥር ወር መጨረሻ ባካሄደው ጠቅላላ ጉባኤ ካሳለፋቸው ውሳኔዎች አንዱ “ፓርቲውን ማጠናከር” እንደነበር አስታውሷል።ይህን ተከትሎም ዜጎች “በውድም ሆነ በግድ የፓርቲ ማጠናከሪያ እንዲያዋጡ እየተደረገ” መሆኑን ኢዜማ “ባሰባሰባቸው ማስረጃዎች” ለማወቅ መቻሉን ገልጿል።

በማንኛውም ፓርቲ ያልታቀዱ ግለሰቦች፤ ብልጽግና ፓርቲን ጨምሮ “ለየትኛውም ድርጅት እና በፈቃደኝት የፈለጉትን ድጋፍ የማድረግ መብት እንዳላቸው” እንደሚገነዘብ ኢዜማ አመልክቷል። ሆኖም ለገዢው ፓርቲ የማጠናከሪያ ገንዘብ እንዲያወጡ እየተገደዱ ያሉት ዜጎች “በተለያዩ የመንግስት ተቋማት ጉዳዮችን ለማስፈጸም በሚንቀሳቀሱበት” ወቅት እንደሆነ ኢዜማ በመግለጫው አብራርቷል።

“ዜጎች አገልግሎት ለማግኘት በሚሄዱባቸው የመንግስታዊ ተቋማት ይህን ተግባር መፈጸም በፍጹም ህገወጥ ተግባር ነው” ሲልም ተቃዋሚ ፓርቲው ነቅፏል።ብልጽግና ፓርቲ አባላቱ ካልሆኑ ዜጎች “ከመንግሥት ተቋማት አገልግሎት ጋር አያይዞ መዋጮ ማሰባሰብ ምንም ዓይነት የህግም ሆነ የሞራል መሰረት የለውም” ሲልም ተችቷል።

Via: Ethiopia Insider

@Ewun_Mereja
@Ewun_Mereja


አዲግራት ከተማ

በትግራይ ክልል ያለው የፀጥታ ኹኔታ ከቁጥጥር እየወጣ ይመስላል። በዶ/ር ደብረፂዮን የሚመራው ቡድን በአሁኑ ሰዓት የአዲግራት ከተማ አሥተዳደርን በኋይል መቆጣጠሩ እየተነገረ ሲኾን፣ በአካባቢው ካሉ ወጣቶች ጋር ወደ ግጭት መግባታቸውም ተሰምቷል።

ትላንት የክልሉን እና ቀጠናውን ወቅታዊ ትኩሳት አስመልክቶ ጽሑፋቸውን ያስነበቡት ጀነራል ፃድቃን፣ በትግራይ ያለው ፖለቲካዊ መካረር ለሻእቢያ በር እንደከፈተና ከኢሳይያስ ጋር መሥራት የሚፈልጉ የትግራይ ኃይሎች እንዳሉ ጠቅሰው፣ በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ድንገት ጦርነት የመጀመሩ ነገር አይቀሬነትን አስረግጠዋል።

@Ewun_Mereja
@Ewun_Mereja


"በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል በማንኛውም ቅፅበት ጦርነት ሊነሳ ይችላል"
- ሌተናንት ጄኔራል ፃድቃን ገብረትንሳይ

ጄኔራል ፃድቃን ገብረትንሳይ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል "በማንኛውም ቅፅበት ጦርነት ሊነሳ ይችላል" በማለት አስጠነቀቁ።

የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳም "በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል በግልጽ የሚታይ መቃቃር አለ። የእኔ ስጋት ይህ ከቃላት አልፎ ወደ ጦርነት እንዳያድግ ነው" ብለዋል።

ጦርነቱ ለቀጠናውም ዳፋ እንደሚሆንም ጄኔራል ፃድቃን በእንግሊዘኛ ባስነበቡት ጽሑፍ አስታውቀዋል።

በሁለቱ አገራት መካከል የሚደረግ ጦርነት በሁለቱም ወገኖች እንደሚባለው "አጭርና ወሳኝ" እንደማይሆን የገለጹት ጄኔራል ፃድቃን ለቀጠናው አውዳሚ እንደሚሆን ጠቅሰዋል።

"ጦርነቱ ሲያከትም አሁን የምናውቀው የአገራቱ ጂኦግራፊ ይለወጣል። በአፍሪካ ቀንድና ከቀይ ባሕር አሻግሮም ጉልህ የፖለቲካ አሰላለፍ ለውጥ ያስከትላል" ብለዋል።

በትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ውስጥ በምክትል ፕሬዝዳንት ማዕረግ ያልተማከለ አስተዳደር እና ዴሞክራታይዜሽን ካቢኔ ሴክሬተሪያት ኃላፊ የሆኑት ሌተናንት ጄኔራል ጻድቃን ገ/ትንሳይ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል የሚቀሰቀሰው ጦርነት "የሱዳንና የቀይ ባሕር ደኅንነት ላይ በቀጥታ ተጽዕኖ ያሳድራል" ብለዋል።

"በጦርነቱ ማዕከላዊ የምትሆነው በደንብ የሠለጠነና ልምድ ያካበተ ከፍተኛ የወታደር ቁጥር ያላት ትግራይ ናት" ሲሉም አክለዋል።

Via:BBC

@Ewun_Mereja
@Ewun_Mereja


የትግራይ ክልል ጊዚያዊ አስተዳደር ፕረዚደንት አቶ ጌታቸው ረዳ ማምሻቸዉን ሶስት የህወሃት የጦር አዛዦችን ከስራ አግደዋቸዋል።

ጄኔራሎቹ ከስራ የታገዱት መፈንቅለ መንግሥት ለማድረግ የግጭት እንቅስቃሴ መጀመራቸውን ተከትሎ ነው ተብሏል።
የታገዱት ጄኔራሎች:-
1. ብ/ጄኔራል ምግበይ ሀይሌ
2. ሜ/ጄኔራል ዮሃንስ ወልደጊዮርጊስ
3. ሜ/ጄኔራል ማሾ በየነ ናቸው።
እነዚህ የታገዱት ጄኔራሎች በሰሜኑ ጦርነት ወቅት ዋና የጦር አዛዥ የነበሩ ናቸው።

@Ewun_Mereja
@Ewun_Mereja


የሶማሊያ ጦር ባካሄደው የአየር ጥቃት ከፍተኛ የአልሻባብ አዛዥ ተገደለ

ዩሱፍ ዴግናስ በመካከለኛው ሸበሌ ክልል በኤል-ባድ አቅራቢያ እንደተገደለ ተገልጿል። በአካባቢው በመንግሥት ኃይሎች እና ታጣቂዎች መካከል ለቀናት የቆየ ከፍተኛ ግጭት ሲካሄድ ነበር ተበሏል። የመንግሥት ሚዲያዎች እንደዘገቡት ዴግናስ በመካከለኛው ሸበሌ የአልሻባብ* ዘመቻዎችን ያቀነባብር ነበር። የአዛዡ ግድያ ቡድኑ በክልሉ ውስጥ የሚያደርገውን እንቅስቃሴ እንደሚያሰናክል ተነግሯል፡፡

የሶማሊያ ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ ሞሐሙድ በአካባቢ ሚሊሻዎች ከሚታገዘው ብሄራዊ ጦር እና ከአፍሪካ ሕብረት ኃይሎች ጋር በመሆን በቅርቡ በአልሻባብ ላይ “መጠነ ሰፊ ጦርነት” ለማወጅ ቃል መግባታቸው ይታወሳል።

@Ewun_Mereja
@Ewun_Mereja

Показано 20 последних публикаций.