የኑር መስጂድ ደርሶች


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


📮 ይህ አዲስ አበባ {ፉሪ} በሚገኘው በታላቁ ኑር መስጂድ የሚዘጋጁ የተለያዩ የአቂዳ የፊቂህ የነህው የሶርፍ እና ሌሎችም ኢስላማዊ ትምህርቶችን በማስራጨት ላይ ትኩረት ያደረገ ቻናል ነው።
🎁 ለሌሎችም ይህን ኸይር ስራ በማሰራጨት የምንዳው ተቋዳሽ ይሁኑ።
🔗 https://telegram.me/nurders

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


🎁 የጁመአ የቁርአን ግብዣ ተጋበዙልን

⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️
https://t.me/nurders/7617


« ረመዷን ከሌሎች ወራቶች የተለየበት ምክንያት»

📌 በሚል ርዕስ የተዘጋጀ መደመጥ ያለበት ገሳጭ ወቅታዊ እና መካሪ የሆነ ሙሃደራ።

ሙሀደራው ላይ ከተወሱ ነጥቦች⤵️⤵️

👉የመጨረሻው ረመዷናችን ሊሆን ስለ ሚችል መጠንከር እንዳለብን፤
👉ከአሉባልታ ወሬ ርቀን በዒባዳ መሽጉል መሆን እንዳለብን፤
👉በዚህ ወር ከእሳት ነፃ የሚሆንበት ወቅት በመኖሩ በዒባዳ በመጠንከር ነፃ መውጣት እንዳለብን፤
👉በዚህ ወር ከቁርዐን ጋር ያለን ግንኙነት ማጠናከር እንዳለብንና ሌሎችም ነጥቦች ተዳሰውበታል።

🎙በታላቁና በተወዳጁ ወንድማችን አቡ የህያ ኢልያስ ቢን አወል  አላህ ይጠብቀው።

🕌በታላቁ ፉርቃን መስጂድ አለም ባንክ ስልጤ ሰፈር

🗓 24/07/2015 EC

https://t.me/Al_Furqan_Islamic_Studio/15676
⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️
https://t.me/Abu_Yehya_ilyas_Awel/6141


🌙ስለ ረመዷን አዲስ ደርስ ለሴቶች

📗ደርስ ቁጥር (9)

📘مختصر الكلام في أحكام الصيام

🖌أبوبكر بن عبده بن عبدالله الحمادي حفظه الله تعالى ورعاه


📘ደርሱ የሚያስተምረው

🎙በታላቁና በተወዳጁ ወንድማችን አቡ አብደላ አብድልቃድር الله  ይጠብቀው

⌚️እሮብ ከአስር ሰላት በኋላ

🕌በመስጂደል ኑር ፉሪ الله ይጠብቃት

👇👇👇👇👇
https://t.me/nurders/7615


👉🥀የትዳር ገዳይ ወረርሽኞች🌹

👉 ስንፍና ትዳርን ይገድላል ።

👉 አጉል ጥርጣሬ ትዳርን ይገድላል።

👉 አለመከባበር ትዳርን ይገድላል።

👉 አላስፈላጊ ክርክርና ጭቅጭቅ ትዳርን
        ይገድላል።

👉 ሚስጥር መደባበቅ ትዳርን ይገድላል።  

👉በገንዘብ፣ በስሜት፣ በስነ-ልቦና፣ በቁሳቁስ የሚደረግ ጭቆና ትዳርን ይገድላል።

👉ደካማ የሆነ ተግባቦት ትዳርን ይገድላል።

👉 ከትዳር አጋር ይልቅ ከቤተሰብ ከጓደኛና ከዘመድ አዝማድ ጋር ጊዜን ማሳለፍ ትዳርን ይገድላል።

👉 የትዳር አጋርን ማንጓጠጥ፣ ማዋረድና መዝለፍ ትዳርን ይገድላል።

👉 ወሬ ማብዛትና ጥንቃቄ የጎደለው ንግግር ትዳርን ይገድላል።

👉 ለትዳር አጋርና ለትዳሩም ጭምር በቂ ጊዜ አለመስጠት ትዳርን ይገድላል።   

👉ወጪ ማብዛት፣ ድግስ ቸበርቻቻ፣ ከአቅም በላይ ወጪ የሚያስወጡ መኀበራዊ ግንኙነቶች ትዳርን ይገድላሉ።

👉 ለቤተሰብና ለዘመድ የትዳር አጋርን ድክመት መናገር ትዳርን ይገድላል።

👉 ፈጣሪን አለመፍራት፣ ከሃይማኖትም ከዕምነትም ህግጋት ውጭ መሆን ትዳርን ይገድላል።

👉 ከስህተት አለመማርና ጥፋትን ለማረም አለመሞከር ትዳርን ይገድላል።

👉 ጋባዥ ያልሆነ፣ ደባሪ ሙድና ፈገግታ የተለየው ፊትን ለትዳር አጋር አዘውትሮ ማሳዬት ትዳርን ይገድላል።

👉በትዳር ውስጥ ያለንን ኃላፊነትና ድርሻ አለመወጣት ትዳርን ይገድላል።

👉ቁጣንና ብስጭትን መቆጣጠር አለመቻል ትዳርን ይገድላል።........

🌺..እነዚህን ምክሮች ትዳራችንን በመልካም ለመምራት ይረዳናልና አላህ ለሁላችንም ሁሌም ያማረ የተዋበ መልካም ትዳር ያድርግልን🤲

👇👇👇👆👆👆
https://t.me/nurders/7614


👉ለማስታወስ ያህል ነገ ሀሙስ ነው ነሸጥ በሉስ


بسم الله الرحمن الرحيم
ይደመጥ

👉ደርስ ቁጥር ( 266)

⚡️ማክሰኞሰኞከመግሪብ በኋላ

👉ሀዲስ ቁ 1146__1147

📚اللؤلؤ والمرجان

✍محمد فؤاد عبدالباقي

🎙በኡስታዝ አቡ የህያ ኤልያስ አወል حفظه الله

🕌በኑር መስጂድ ፉሪ الله ይጠብቃት
⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️
https://t.me/nurders/7612




📸 ስለ ሱራ ሀራምነትና 🖥የቲቪ ያለው ፈሳድ
በደንብ የተብራራበት ለሁሉም ተደራሽ በማድረግ ሙስሊሞች ካሉበት ፈሳድ በማውጣት ሰበብ እንሁን ያለብንን ሀላፊነትም እንወጣ


🎙በታላቁና በተወዳጁ ወንድማችን አቡ ሂባን አብድሰሚዕ ኢብኑ በድሩ الله ይጠብቀው

📘ከላሚያ ኢብኑ ወርዲ ደርስ የተወሰደ

🕌በመስጂደል ኑር ፉሪ الله ይጠብቃት
⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️
https://t.me/nurders/7610
⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️
https://t.me/Abu_Hiban_Abdsemi


🌙ስለ ረመዷን አዲስ ደርስ ለሴቶች

📗ደርስ ቁጥር (8)

📘مختصر الكلام في أحكام الصيام

🖌أبوبكر بن عبده بن عبدالله الحمادي حفظه الله تعالى ورعاه


📘ደርሱ የሚያስተምረው

🎙በታላቁና በተወዳጁ ወንድማችን አቡ አብደላ አብድልቃድር الله  ይጠብቀው

⌚️የዛሬ ማክሰኞ ከአስር ሰላት በኋላ

🕌በመስጂደል ኑር ፉሪ الله ይጠብቃት

👇👇👇👇👇
https://t.me/nurders/7609


👉♻️ሚስት በባልዋ ላይ ያላት ተጽእኖ!

🤌ሀሰን አል-በስሪ እንዲህ አሉ፡ "በመካ አንድ የጨርቅ ነጋዴ ጋር ቆሜ ልብስ ልገዛው ነበር። እሱም ሸቀጡን ለማራመድ እንዲሸጥለት ሲል ማሞገስና መማል ጀመረ። ስለዚህ እሱን ትቼ ከሌላ ገዛሁ። ከሁለት ዓመት በኋላ ተመልሼ ሳገኘው ሲያሞግስም ሲምልም አልሰማሁትም!

እኔም፡ "ከዓመታት በፊት እዚህ ቆሜ የማውቅህ ሰው አይደለህም እንዴ?" አልኩት።
እሱም፡ "አዎ" አለ።

እኔም፡ "ምን አገኘህና እንደዚህ ሆንክ? ስታሞግስና ስትምል አላይህም!" አልኩት።

እሱም፡ "ሚስት ነበረችኝ። ትንሽ ነገር ይዤ ብመጣ ትንቃለች [ይኸውም ታቃልለች]፣ ብዙ ነገር ይዤ ብመጣ ደግሞ ታሳንሳለች። አላህም ወደ እኔ ተመልክቶ አስወገዳት። ከዛም ሌላ ሴት አገባሁ፣ ወደ ገበያ ልሄድ ስል ልብሴን ትይዝና

"እገሌ ሆይ! አላህን ፍራ! ጥሩ ነገር እንጂ አታብላን። ትንሽ ይዘህ ብትመጣልን እናሳምረዋለን፣ ምንም ይዘህ ባትመጣልን ደግሞ ባለን ነገር እንብቃቃለን" ትለኛለች።
[አል-ሙጃላሳ ወጀዋሂር አል-ዒልም (ገጽ 141)]

ከዚህ ታሪክ የምንረዳው ሚስት በባሏ ላይ ያላትን ተጽእኖ ያሳያል። አንዲት ሚስት ባሏን በመደገፍና በማበረታታት ቀጥተኛና ታማኝ እንዲሆን ልትረዳው ትችላለች። በተቃራኒው ደግሞ ባሏን በማንቋሸሽና በማሳነስ አሉታዊ ተጽእኖ ልታሳድርበት ትችላለች። ስለዚህ ሚስቶች ባሎቻቸውን መደገፍና ማበረታታት፣ ባሎችም ሚስቶቻቸውን ማክበርና ማድነቅ አለባቸው።

                                           🤝መልካም አዳር
👇👇👇👆👆👆
https://t.me/nurders/7608


👉♻️በቀደምት ደጋጎች ዘመን አንድ ሰው  ተቸግሮ ወደ ወዳጁ ቤት ሂዶ መቸገሩን ነገረው :: ወዳጁን ለቸገረው ወንድሙ ያለውን ሰጥቶ ከሸኘው በኋላ አለቀሰ :: ሚስቱም "ለምን ታለቅሳለህ ?  ከሰጠኸው በኋላ በመስጠትህ ተፀፀተህ  ከሆነ ለምን ሰጠህ ? " አለችው :: እሱም ያስለቀሰኝ መስጠቴ ሳይሆን ወንድሜ ቸግሮት እኔ ጋር እስከመምጣት መድረሱ  መቸገሩን  ራሴው ተረድቼ ሳልደርስለት በመቅረቴ ነው አለ :: " የኛ ነገር ከዚያም የባሰ ሆነ ::

ያገኘነውም አላህ የሰጠንን በኛ ላይ ሲያየው ይወዳል በሚል ራሳችንን ሸንግለን  በምቾት እየተንደላቀቅን ጎረቤቱ ተርቦ ጠግቦ ያደረ...የሚለውን ሀዲስ ረሳን !

ሱረቱ ተካሱር

أَلْهَىٰكُمُ ٱلتَّكَاثُرُ
: በብዛት መፎካከር (ጌታችሁን ከመገዛት) አዘነጋችሁ፡፡
በሚል የጀመረው ሱረቱ ተካሱር ቁርዓን አንቀፅ መቋጫውን እንዲህ አለ

ثُمَّ لَتُسْـَٔلُنَّ يَوْمَئِذٍ عَنِ ٱلنَّعِيمِ

: ከዚያም ከድሎታችሁ ሁሉ በዚያ ቀን ትጠየቃላችሁ፡፡

ብቻ አላህ ይድረስልን !

የዚያኔ ስለዚህ ፀጋ ትጠየቃላችሁ
ድሆች ከቆሻሻ ላይ ምግብን እየለቀሙ ይበላሉ። ባለሀብቶች ከዓይነት ዓይነቱ ማዕድን ያማርጣሉ።የተቸገረን እንርዳ ለማለት ነው ባረከላሁ ፊኩም

 👇👇👇👆👆👆
https://t.me/nurders/7607


🌙ስለ ረመዷን አዲስ ደርስ ለሴቶች

📗ደርስ ቁጥር (7)

📘مختصر الكلام في أحكام الصيام

🖌أبوبكر بن عبده بن عبدالله الحمادي حفظه الله تعالى ورعاه


📘ደርሱ የሚያስተምረው

🎙በታላቁና በተወዳጁ ወንድማችን አቡ አብደላ አብድልቃድር الله  ይጠብቀው

⌚️ሰኞ ከአስር ሰላት በኋላ

🕌በመስጂደል ኑር ፉሪ الله ይጠብቃት

👇👇👇👇👇
https://t.me/nurders/7606


🌱ከካፊር ጋር ተጣልቼ ነበር ከዛ ሰው ጋር መታረቅ አልፈለኩም ሳልታረቅ ብፆም ፆሜ እንዴት ይታያል

🎙በታላቁና በተወዳጁ ወንድማችን አቡ የህያ ኤልያስ አወል حفظه الله تعالى
⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️
https://t.me/nurders/7605
⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️
http://t.me/Abu_Yehya_ilyas_Awel


👉♻️አስለቃሽ ታሪክ እዉነተኛ የእዉነተኛዉ ልጅ የሆነችዉ የአይሻ ቢንት አቡበከር ታሪክ


🤌የእናታችን አይሻ ቢንት አቡበከር ረዲየላሁ አንዐ ሙናፊቆች በዝሙት ስሟን ያጠፉበት ታሪክ በአጭሩ እንዲህ ዳሠነዋል ።

ነቢያችን ሙሀመድ ( ሠለላሁ አለይሂ ወሠለም)  ጉዞ ለመዉጣት ሲያስቡ በባለቤታቸዉ መሀከል እጣ ይጥሉ ነበር እጣ የወጣላትን ባለቤታቸዉ ይዘዉ ይሄዱ ነበር የዚያን ቀን ለእናታችን አይሻ እጣ ወጣላትና ከነቢዩ ሙሀመድ ( ሰለላሁ አለይሂ ወሠለም )  ጋር ጉዞ ወጣች ።

በዚያን ጊዜ ሴቶች ጉዞ ሲወጡ መንገዱ ከመርዘሙ ጋር ጸሐይ እንዳይጏዳቸዉና ከወንዶች እይታ ተሠዉረዉ ኒቃባቸዉን አዉልቀዉ እንዲጏዙ ከግመል በላይ ጎጆቤት የሚመስል አይነት ሀዉደጅ የተባለ መጠለያ ይሠራቸዉን ዉስጡ ገብተዉ ይጏዙ ነበር ። ሴቶች በአንድ ሠፍ ሆነዉ በመሪዎች እየተመሩ በመጏዝ ላይ ነበሩ ከአንድ አከባቢ ሲደርሱ የአሏህ መልዕክተኛ ጦሩ እንዲያርፍ አዘዙ ሴቶች  የነበሩበትን ግመሎች ካንበረከኩላቸዉ በኃላ ከግመሎቹ ላይ የነበረዉን አዉደጅ አወረዱላቸዉ እናታችን አይሻ አሏህ ይዉደድላት ከጏደኞቿ ጋር ለመጸዳዳት ራቅ ወዳለ ቦታ ሄደች ።

ሲመለሡ ነብያችን ሙሀመድ ( ሠለላሁ አለይሂ ወሠለም ) ጦሩ እንዲንቀሳቀስ ትዕዛዝ አስተላልፎ ስለ ነበር ጎጆዋቸዉ ከግመላቸዉ ላይ ተጭኖ ነበር እናታችን አይሻ የአነገቷን ሀብል ለመጸዳጃ በሄደችበት ቦታ ጥላዉ መጥታ ስለ ነበር አጣችዉ ሀብሏን ለማምጣት ለብቻዋ ተመለሠች ማንም አላስተዋላትም ነበር እናታችን አይሻ ሀብሏን አምጥታ ስትመለስ ጦሩ በሙሉ ሄዶዋል ።

ከአዋቂነቷ የተነሳ ሴት ልጅ ለብቻዋ እንደማትሄድ ስለምታቅ ባለችበት ቦታ ረጋች ሲያጡኝ መጥተዉ ይወስዱኛል ብላ በቦታዋ ላይ ቁጭ እንዳለች እንቅልፍ ይዟት ሄደ ነቢያችን ሙሀመድ ( ሠለላሁ አለይሂ ወሠለም ) ከጦሩ በረጂም ርቀት ከኃላ እየተከተለ የሚመጣ የወደቁ እቃዎች ካሉ እየሠበሠበ እንዲመጣ ሰፈዋን የሚባልን ሠሀቢይ መድበዉ ነበር ። ሰፍዋን አይሻ በተኛችበት ፊቱዋ ተገልጦ ስለ ነበር ይመለከታታል በጣም ደንግጦ ላሀዉለ ወላ ቁወተ ኢላ ቢላህ ኢናሊላሂ ወኢና ኢለይሂ ራጂኡን ሲል እናታችን አይሻ ትሠማዋለች ።

በአሏህ ይሁንብኝ ከነዚህ ቃላት ዉጪ ሌላ ቃላትን አልተናገረም ትላለች አይሻ ግመሉን አንበረከከልኝ ዉጪ እንኻን አላለኝም እራሴ ወጣሁኝ ያለምንም እረፍት ረጂም ሰዓት ተጎዞ ጦሩ ጋር ሲደርሱ ከሡ ግመል ወርዳ ወደ ግመሏ ስትሄድ የሙናፊቆች አለቃ አብዱሏህ ኢብኑ ሰሉል ተመለከታት ወላሂ እሱ ከእሷ አልጸዳም እሷም ከእርሡ አልጸዳችም ዝሙት ሠርተዋል ብሎ ወሬ ማናፈስ ጀመረ ።

ነብያችን ሙሀመድ ( ሠለላሁ አለይሂ ወሠለም ) መዲና በደረሡ ግዜ ሙሉ መዲና ከተማ ዉስጥ ሙናፊቆች የዉሸት ወሬዉን ማናፈስ ጀመሩ እናታችን አይሻ ከመንገድ ስለ ገባች ትንሽ አመማትና ተኛች እስካሁን ድረስ ምንም የደረሳት ወሬ የለም ። አንዴ ገላዋን ለመታጠብ ከኡሙ ሚስጣ ጋር ወጣች ኡሙ ሚስጣ እንቅፋት ሲያደናቅፋት ልጇን ሚስጣ ረገመችዉ አይሻ በሰማች ግዜ አሏህን ፍሪ የበድር ጦርነት ላይ የተሳተፈን ሰዉ ትረግሚያለሽ አለቻት ኡሙ ሚስጣም ለጄ ሚስጣ ምን እያለ እንዳወራብሽ አልሠማሽም አለቻት ምን አለ አለቻት እየተወራ ያለዉን ነገር ሁሉ ነገረቻት ።

ይህ ወሬ ነብያችን ሙሀመድ ( ሠለላሁ አለይሂ ወሠለም ) ጋር ደረሠ አለቻት አዎ ደርሶዋል አለቻት ወደ ቤት ተመልሳ ነቢያችን ሙሀመድ ( ሠለላሁ አለይሂ ወሠለምን ) አስፈቅዳ ወደ ወላጆቿ ቤት ሄደች ኡሚ ሠዎች እንዲህ እያወሩብኝ ለምን አልነገርሽኝም አለች ። ልጄ ተረጋጊ ብላ ልታረጋጋት ሞከረች ተንሠቅስቃ እያለቀሠች ወደ አባቷ አቡበከር ሲዲቅ (ረዲየሏሁ አንሁ ) ሄደች ።

አባቴ ሰዎች የሚያወሩብኝን ነገር ለምን አልነገርከኝም አለችዉ እንደ እናቷ ሊያረጋጋት ሞከሩ ተንሠቅስቃ ማልቀስ ጀመረች ቤተሠቦቿ በለቅሶ ብዛት ትሞታለች ብለዉ እስኪፈሩ ድረስ ቀንና ማታ ማልቀስ ጀመረች የአሏህ መልዕክተኛ አኮረፏት ሌላ ቀን ከሳቸዉ የምታገኘዉን ፍቅር አጣች በሀዘን ላይ ሀዘን በረታበታ ። አንድ ወር ሙሉ ጅብሪል ለነቢያችን ሙሀመድ ( ሠለላሁ አለይሂ ወሠለም ) ዋህይ ይዞ ይወርዳል ስለ ሷ ግን ምንም አይነት ዋህይ አልወረደም አልነገራቸዉም ።

ነብያችን ሙሀመድ (ሠለላሁ አለይሂ ወሠለም) ከሙናፊቆች በሚደርሳቸዉ አዛ በጅጉ ልባቸዉ ይሠበር ያዝኑ ነበር ። ኻዲማቸዉን አነስ ኢብኑ ማሊክ ጠርተዉት ያአነስ አንድ ቀን እንኳ ከአይሻ የሚያጠረጥርህን ነገር አይታሀል አሉት ያረሡሉሏህ ከቤተሠቦችህ ኸይርን እንጂ አይቼ አላቅም አላቸዉ ።

ኡሳማን ጠየቁት እሱም የአነስ አይነት ምላሽ ከመለሠላቸዉ በኃላ የአይሻን ኳዳሚ በሪራን ይጠይቋት እሷ እዉነቷን ትነግሮታለች አለች በሪራን ጠየቋት ያበሪራ ከአይሻ ጋር ስትኖሪ የሚያጠራጥርሽን ነገር አይተሽባት ታዉቂያለሽ አሏት ያረሡለሏህ ከእሷ መልካምን እንጂ አላየሁባትም አለች ።

ነቢያችን ሙሀመድ ( ሠለላሁ አለይሂ ወሠለም ) የሙናፊቆች አዛ መቆሚያና መቀመጫ ሲያሳጣቸዉ ሚንበር ላይ ወጡና እናንተ ሰዎች ሆይ የዚን ሙናፊቅ ሸር የሚይዝልኝ ማነዉ አሉ ዘዉትር አዛ ያደርገኛል አሁን ደሞ በኔና በባልተቤቴ ሂወት ገባ ሲሉ የአዉስ መሪ የሆነዉ ሳዐድ ቢን ሙዐዝ ተነሳና ያረሡለሏህ ይህ ሠዉ አብዱሏህ ኢብኑ ሰሉል ከኔ ጎሳዎች ከሆነ በአሏህ ይሁንብኝ አሁኑኑ አንገቱን ቀነጥስልሀለዉ ነገር ግን ከወንድሞቻችን ኸዝረጅ ከሆነ ያንተን ትዕዛዝ እሻለሁኝ ከፈለክ አንገቱን እቆርጥልሀለዉ አላቸዉ ። የኸዝረጅ ጎሳ መሪ የሆነዉ ሠዐድ ኢብኑ ኡባዳ ትክክለኛ ሙስሊም ቢሆንም የሆነ ወኔ ያዘዉና ለሰዐድ እኔ ቁጭ ብዬ ከጉሳዬ ሰዉ ትገላለህ በአሏህ ይሁንብኝ አትገለዉም አለ ኡሠይድ የተባለዉ ሰሀቢ ተነሳ አንተ ሙናፊቅ ለሙናፊቅ ትከራከራለህ አለዉ ።

መስጂድ ዉስጥ ቃላት ይለዋወጡ ጀመር ነቢያች ሙሀመድ (ሠለላሁ አለይሂ ወሠለም) አረጋጏቸዉና ከሚንበራቸዉ ላይ ወርደዉ ከወር በኃላ ለመጀመሪያ ግዜ ወደ እናታችን አይሻ ቤት ሄዱ ከተኛችበት ፍራሽ ጎን ቁጭ አሉ አይሻ ወንጀልን ሰርተሽ ከሆን ተዉበት አድርጊና ወደ አሏህ ተመለሺ አሏህ ይምርሻል ንጹህ ከሆንሽ አሏህ ንጽህናሽን ይመሠክርልሻል አሏት ወደ አባቷ ዞረች አባቴ የአሏህ መልዕክተኛን ስለኔ መልስ ስጣቸዉ አለቻቸዉ ምን ብዬ እንደ ምመልስ አላዉቅም አሏት ወደ እናቷ ዞረች እናቴ ለአሏህ መልዕክተኛ ስለኔ መልስ ስጪ እናቷም ለአሏህ መልክተኛ ምን እንደምመልስ አላዉቅም አለች አይሻም ወላሂ ወንጀል ሰርቼያለሁኝ ብላችሁ ታምኑኛላችሁ ግን አልሠራሁም አልሠራሁም ንጹህ ነኝ ብላችሁ አታምኑኝም አሏህ ምስክሬ ነዉ እኔ ንጹህ ነኝ ዩሱፍ አባት እንዳለዉ ፈሰብሩን ጀሚል ከማለት ዉጪ ሌላ ምንም አልልም አለችና ተከናንባ ተኛችና ።

መንሠቅሠቅ ጀመረች ነቢያችን ሙሀመድ ( ሠለላሁ አለይሂ ወሠለም ) ከቦታቸዉ ሳይነሡ ንጹህነቷን የሚያረጋግጥ የቁርኣን አያ ጅብሪል ይዞ ወረደላቸዉ አብሽሪ የአይሻ ከሠባት ሠማይ በላይ የሆነዉ አሏህ ንጽህናሽን መስክሮልሻል አሏት አባትና እናቷ ተነሺ የአሏህን መልዕክተኛ አመስግኝ አሏት ወላሂ ከአሏህ ዉጪ ማንንም አላመሠግንም ንጹህ እንደሆንኩ ነብያችን ሙሀመድ ( ሰ,ዐ,ወ) ህልም ያያሉ ብዬ እንጂ አንድም ቀን በኔ ሠበብ ቁርዐን ይወርዳል ብዬ ጠብቄ አላዉቅም ነበር ትላለች ሡረቱ ኑር ዉስጥ ስለ  ንጽህናዋ አሏህ ተባረከ ወተዐላ 9 አንቀጾችን በማዉረድ መሠከረላት ።


📘የላሚያ ኢብኑ ወርዲ የግጥሙ ደርስ


📮ይደመጥ ይደመጥ 👂

👉📘አዲስ ደርስ ቁጥር (29)

👉እሁድ ከመግሪብ እስከ ኢሻ
📚شرح لامية ابن الوردي

✍فضيلة الشيخ العلامة يحي بن علي الحجوري حفظه الله

ኪታቡ የሚያስቀራው

👇👇👇👇
በታላቁና በተወዳጁ ወንድማችን አቡ ሂባን አብዱሰሚዕ ቢን በድሩحفظه الله تعالى

🕌በመስጂደል ኑር ፉሪ الله ይጠብቃት
https://t.me/nurders/7081

📘የኪታቡ pdf ለማግኘት📘
https://t.me/nurders/7066
https://t.me/nurders/7602


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
https://t.me/nurders/7601




📮 ረመዷንን እንዴት እናሳልፈው⁉️

📌 በሚል ርዕስ የተዘጋጀ መደመጥ ያለበት ገሳጭ እና መካሪ የሆነ ሙሓደራ።

🎙️ በኡስታዝ አቡ የህያ ኢልያስ ቢን አወል አላህ ይጠብቀው።

📅 እሁድ 25/07/2014E.C
🕌 በፉርቃን መስጂድ {አለም ባንክ}
ـــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــــ
📲 አጠቃላይ ፕሮግራሞቻን በሶሻል ሚዲያ ለመከታተል:-

🖥️ በ Telegram~Channel
📎 https://telegram.me/Al_Furqan_Islamic_Studio/8182
⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️
https://t.me/Abu_Yehya_ilyas_Awel/6138


⌚️ሀሙስከኢሻ ሰላት በኃላ ለተማሪዎች የሚሰጥ ደርስ

📚ደርስ ቁ35)
👉የኪታቡም ስም
📚📚 التفسير الميسر

🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌱🌿🌿

👉ኪታቡ የሚያስቀራው
👇👇👇👇👇👇👇

🎙በታላቁና በተወዳጁ በኡስታዝ  አቡየህያኢሊያስ አወልحفظه الله تعالى

🕌በመስጂደል ኑር ፉሪ الله ይጠብቃት
⤵️⤵️⤵️⤵️
https://t.me/nurders/7598


👉⌚️ከኢሻ ሰላት በኃላ ለተማሪዎች የሚሰጥ


📚ደርስ ቁ(47)



👉የኪታቡም ስም
📚📚 القواعدالفقهية

✍الشيخ العلامة عبدالرحمن بن ناصرالسعدي

👉ኪታቡ የሚያስቀራው
👇👇👇👇👇👇👇

🎙በታላቁና በተወዳጁ ወንድማችን አቡ አብድል ሀሊም ሸምሱ حفظه الله تعالى

🕌በመስጂደል ኑር ፉሪ الله ይጠብቃት
⤵️⤵️⤵️⤵️
https://t.me/nurders/7597

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.