በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት ፶ አዳዲስ አማኞች በጥምቀት ከብረው የሥላሴ ልጅነት አገኙ።
የካቲት ፪/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት በአናሌሞ ወረዳ ቤተ ክህነት በወጎ ወጌላ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ፶ ኢ አማንያን በብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ የሀዲያና ስልጤ ፤ የደቡብና ምዕራብ አፍሪካ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በዛሬው ዕለት ተጠምቀው የሥላሴን ልጅነት አግኝተዋል ።
በዕለቱም ብፁዕነታቸውን ጨምሮ የሀገረ ስብከቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ መልአከ ሕይወት ንጉሤ ባወቀ ፣ የሀገረ ስብከቱ የሥራ ክፍል ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
©
ብሕንሳ ሚዲያ