ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍት እና ጽሑፎች Tsegaye kiflu


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


በዚህ ቻናል ላይ አበው ያስረከቡንን መጻሕፍትን እንዲሁም መንፈሳዊያት ጽሁፎችን ለምዕመናን ተደራሽ ማድረግ ነው።
https://linktw.in/mejQ6H
ሰብስክራይብ ያድርጉ

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


ለኅብረተሰቡ የሕክምና አገልግሎት እንሰጣለን በማለት የሃይማኖት ተኮር እንቅስቃሴዎች እየተደረጉ መሆኑን ምእመናን ገለጹ !

መጋቢት ፫/፳፻፲፯ ዓ/ም የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ

በአሪ ዞን በባካ ዳውላ ወረዳ ለኅብረተሰቡ የሕክምና አገልግሎት እንሰጣለን ፣ መነጽር እናድላለን በማለት ምእመኑን ስብከት ለመስበክ እና ለማደናገር ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑን በአካባቢው የሚገኙ ምእመናን ጠቁመዋል።

ሕክምና እንሰጣለን በማለት ከእስራኤል ሀገር በመጡ የሕክምና ባለሙያዎች "ጉዞን ከመሲሁ ጋር መጀመር" የሚሉ ወረቀቶችን በመበተን ምእመኑን የማወዛገብ ሥራ እየተሠራ መሆኑን ለተዋሕዶ ሚዱያ ማዕከል አስረድተዋል።

ተሚማ የመረጃውን እውነተኛነት ለማጠናከር ባደረገው ጥረት የሀገረ ስብከቱ የሥራ ኃላፊዎችን በስልክ በማነጋገር ስለጉዳዩ ባደረገው ማጣራት የሕክምና ባለሙያዎቹ እንደገቡና ሕክምና እየሰጡ እንደሆነ በመግለጽ ከአንዳንድ ምእመናን ግን በደረሰን መረጃ በአዳራሽ አስገብቶ የመስበክ ሁኔታዎች መኖራቸውን ፣ በተለይም ወቅቱ የዐቢይ ጾም በመሆኑ ሁሉም አባቶች በሥርዓተ ቅዳሴ አገልግሎት ስለሚያሳልፉ ምእመናኑ ከእንደዚህ ዓይነት ድርጊት ራሳቸውን እና ቤተሰቦቻቸውን እንዲጠብቁ አሳስበዋል።

በሕክምና እንዲሁም በሌሎች ሃይማኖት ነክ ባልሆኑ ሥራዎች ገብቶ እንደዚህ ዓይነቱን የሃይማኖት ተግባር ማከናወን በሕግም የሚያስጠይቅ መሆኑ የሚታወቅ ነው።

ዘገባው የዋሕዶ ሚዲያ ማእከል ነው።


እፎይ እና ጰልድዮስ እውነት አላቸው dan repost
አሁንም ደግመን ደጋግመን የምነግራቹ ነገር ቢኖር
እፎይ ያለመረጃ አያወራም።!!
የክርስቶስ ቤተሰቦች በሙሉ ደረታቹን ነፍታቹ እፎይ ያለመረጃ አያወራም ብላቹ።የእነሱ ኡስታዞች ግን ያለመረጃ እንደሚያሰድቡ እውነቱን ግለጡ።

እፎይ እና ወንድም እህቶቹ ለተናገሩት ነገር በመረጃ ጠይቁን ኢስላማዊ ቁብልነት ባለው ማስረጃ ትላትም ዛሬም ነገም ሁሌም እንደምናረጋግጥ በተደጋጋሚ አረጋግጠናልም እናረጋግጣለንም።

እነሱስ ለተሳደቡት ስድብ መፅሀፍቅዱሳዊ እና ክርስቲያናዊ መረጃ ማቅረብ አይችሉም።

ይህ ደሞ ንቀት ስድብ ወንጀል ነው።

በወንጀል ይጠየቁልን
በወንጀል ይጠየቁልን
በወንጀል ይጠየቁልን
በወንጀል ይጠየቁልን




ወንጀል ከሆነ የመጀመሪያው ወንጀለኛ ይህ ነው፡፡
======================
ይህ አቡሃይደር የሚባል ነው፡፡ ታዲያ አቡሃይደር መጽሃፍ ቅዱስን በመተቸትና ክርስቶስን በመስደብ ነው የጀመረው፡፡ ስድብ ማለት ያልሆነው ሆነ ማለት ነው፡፡ ክርስቶስ አምላክ አይደለም ማት በራሱ ስድብ ነው፡፡አይሁዶች ክርስቶስ በከሰሱ ጊዜ ስለ ስድብህ ሰው ሆነህ ሳለ አምላክ ነኝ ስለማለትህ ነው ብለው ነበር፡፡ስድብ ማለት ውሸት መናገር ነው፡፡
በዚህ መልኩ አቡሃይደር እጁን መጽሃፍ ቅዱስ ውስጥ መስደድ የጀመረው ጉዳይ ነው፡፡ ሁለት የወሎ አካባቢ ሰዎች ነን ከኦርቶዶክስ ወደ እስልምና መጣን በማለት ኦርቶዶክስን ስላሴን ሲያበሻቅጡ ሁላችንንም እናስታውሳለን፡፡ ከዚያ ኦርቶዶክሶች መልስ መስጠት ጀመሩ፡፡ የኦርቶዶክሶች ተግባር ግብረመልስ ነው እንጂ ጀማሪዎች አይደሉም፡፡መጀመሪያ መምህር ምህረተአብ መልስ ሰጠ፡፡ መምህር ምህረተአብ መልስ በመጽሃፍ ቅዱስ ላይ የተመሰረተ ነበር፡፡
በኋላ ዲያቆን ቢኒያም ፍሬው፡፡ የሙስሊሞችን ቁርዓኖችና ሀዲሳትን በማጣቀስ እስልምናን በመግለጥ ግንባር ቀደምት ነው ማለት ይቻላል፡፡ ዲያቆን ቢኒያም ያረገው ኡስታዝ አቡሃይደር በክርስትያን እና በመጽሃፍ ቅዱስ ላይ ላደረገው የሰጠው መልስ ነው፡፡ ይሄን ዛሬ ወንጀል የሚባለውን ተግባር የጀመረው አቡሃይደር እንደፈለገ ሲፏልል፣ ለዚያውም ቢለ*ዋ አዘጋጁ ለጅ*ሃድ ተዘጋጁ እያለ፣ ዲያቆን ቢንያም ዛሬ ጫካ ለጫካ ከቤተሰቦቹ ከልጆቹ ተለይቶ ይንከራተታል፡፡ዲያቆን ቢንያም ወንጀል ሰርቶ አይደለም፣ሙስሊሞች የሚያፍሩበትን የእስልምናን እውነት ስለገለጣ ብቻ ነው፡፡
አቡሃይደር በተገኘበት ቦታ ሁላ ያለ ፍርሃት በክርስትና ላይ ሲዝት ፣ በክርስትና ላይ ሲቀጥፍ፣ሌሎችም የሙስሊም ኡስታዞች በአደባባይ ተመሳይ ተግባር ሲፈጽሙ፣ ሲሳደቡ፣ ይታሰሩ ያልተባሉት፣ ኦርቶዶክሶች ሀቁን ከቁርዓን እና ሀዲሳት እንዲሁም ሱናዎች ላይ ተመስርተው እውነቱን ስለገለጡ እንገደል፣ ይታሰሩ የሚለው ለምንድን ነው፡፡ እውነት እፎይ እና ዲ/ቆን ቢኒያም የሰሩት ወንጀል ከሆነ የመጀመሪያ ዎንጀለኞች የሙስሊም ዎሃቢ ኡስታዞች ናቸው፡፡ክርስቶስን በብልግና የሚሳደቡ፣ አምላክን በብልግና የተሳደቡ የዎሃቢ ኡስታዞች በክርስቶስ ላይ ስለተናገሩት አንዳች ክርስትያናዊ ማስረጃ ሳይኖር ቀጠፉት መጀመሪያ ለፍርድ ይቅረቡ፡፡
ፓፓሳት አባቶች ድሆች ከሚበሉት ቀንሰው በሚሰጡት አስራት ሆዳቸውን አንዘርጠው ከመሄድ ይልቅ ለራሳቸውም ሲሉ ኦርቶዶክስን መከላከል አለባቸው፡፡ ለነፍሳቸው መኖሩን ስለተዉት፣ ለሆዳቸው የሚባሉትንም እንደያጡ፡፡
ለፍርድ ይቅረቡ ከተባለም ሙስሊሞቹም ኦርቶዶክሶቹም ይቅረቡና ለተናገሩት ነገሮች ማስረጃ ያቅርቡ፣ ችሎቱም ክፍት ይን ህዝብ ይስማው፡፡ እውነት ፍትህ ካለ፡፡ እያንዳንዱ ቪዲዮ ለፍርድቤትና ለህዝብ በህዝብ ሚዲያ ይፋ ይሁን፡፡
ሲኖዶስ እንደው አምላክ ልብ ይስጣቸውና፣ማስረጃዎች ከወዲሁ ማዘጋጀት፣የህግ ጠበቆችን ማደራጀት፣እስካሁን በኦርቶዶክሶች ላይ ከጂማ፣አርሲ፣ባሌ፣ስልጤ ጀምሮ የደረሰው ማውጣት፣ የሙስሊም ኡስታዞች በክርስትና ላይ የቀጠፉት ማስረጃዎችን ማደረጀት ማሰባሰብ፣ በሰነድ አለባት፡፡
ሁሉም ኦርቶዶክሳዊ አጠቃላይ ክርስትያን በአንድነት መቆም አለብን፡፡ በአንድነት የምንቆመው ለእኩልነት ሀሳብን በነጻነት ስለመግለጽ መብት እና ስለ ሀይማኖት መብት ነው፡፡ በናይጂያ በተመሳሳይ የዎሃቢያ እሳቤ እየተገደሉ ያሉት ክርስትያች ኦርቶዶክሶች አይደሉም፡፡
የጊዜ ጉዳይ ነው፡፡ ዋቄፈታዎች እንዲያውም ይስባቸዋል፣ ጊዜ እየተጠበቀላቸው ነው፡፡እንዲየውም ዋቄፈታዎችን ክርስትያኖችን እንዲያዳክሙላቸው እየተጠቀሙኣቸው ነው፡፡መጨረሻ ግን እንሱም አይቀርላቸውም፡፡ሀይማኖትን መተቸት መብት ነው፡፡




ይህ በሶሪያ የሚኖር ሰው የመስቀል አንገቱን ማንጠልጠያ ለማውለቅም ሆነ በክርስቶስ ያለውን እምነት ለመካድ ፈቃደኛ አልሆነም። በእስላማዊ አክራሪዎች አንገቱ ተቀልቷል።


እፎይ እና ጰልድዮስ እውነት አላቸው dan repost
† እኛም በአምላካችን ድርድር አናውቅም †

★ እነዚህም በአስቸኳይ ለፍርድ ይቅረቡ !! ★

እኛ ክርስቲያኖች አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ከነፍሳችን በላይ እንወደዋለን።የሕይወታችን መመሪያ የሆነውን መጽሐፍ ቅዱስንም ከምንም ነገር በላይ እናከብረዋልን።

እነዚህ ከታች የምንመለከታቸው ሙስሊሞች በአምላካችን ላይ የዘለፋ፣የንቀት፣ የጥላቻና ክብሩን የሚያቃልል ርካሽ ቃላት ተናግረዋል። የሕይወታችን መመሪያ የሆነውን መጽሐፍ ቅዱስንም አራክሰዋል፣አቃለዋል ተሳድበዋል። እነዚህ አጉራ ዘለል ሰዎች በተለያየ ጊዜ ሲያሰራጩ ለኖሩት የጥላቻ ንግግርና ፀባ ጫሪ ትንኮሳዎች ከነገዛሬ ይስተካከላሉ ብለን በትዕግሥት ዝምብለን ብንቀመጥም መንግሥትም ሆነ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ አንዳቸውንም ሥርዐት እንዲይዙ ሲገስጹ አልታዩም። የእስልምና ጉዳዮች ምክር ቤትም መደዴ የሆኑ ሙስሊም ወጣቶች እየተነሱ በክርስቲያኖች ላይ ጸያፍ ቃላትን ሲሰነዝሩና ሕገ ወጥ ተግባራትን ሲፈጽሙ አንድም ቀን መሪዎቻቸው ስህተት ነው ብለው ሲቃወሙ አልታየም ይልቁንም በየመስኪዱ በኡላማዎችና በኡስታዞች ተመሳሳይ ድርጊቶች ሲፈጸሙ ቆይተዋል።ዛሬ ላይ ነቢያችን ተነካ ብላችሁ እንደተነሳችሁት እኛም ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ላይ ነውረኛ ቃላት ሲናገሩ የኖሩት ሁሉ በአስቸኳይ ለፍርድ ይቅረቡ ዘንድ አጥብቀን እንጠይቃለን።

ከታች ያሉት ኡስታዞችና የሙስሊም አክቲቪስቶች ለፍርድ ይቅረቡ !!

ሼር በማድረግ ክርስቲያኖች ሁለ ተባበሩ

1ኛ.አቡ ሃይደር ወይም ሳዲቅ መሐመድ

አድራሻ= አዲስ አበባ

2ኛ አህመዲን ጀበል

3ኛ =ኢምራን
አድራሻ=የሚኖረው አዲስ አበባ ነው

4ኛ =ሳላህ
አድራሻ=አዳማ

5ኛ =ኦሳማ ጁሄር
አድራሻ=

6ኛ=አስረስ
አድራሻ=ስልጤ

7ኛ =ሙሐመድ ከድር
አድራሻ=አዲስ አበባ

ሌሎቹንም በዝርዝር እንቀጥላለን

እኛም በአምላካችን ድርድር አናውቅም ለህግ ይቅረቡ ።




የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የጥቃት ዓላማ ያደረጉ የጥላቻ ንግግሮች እንዲቆሙ ምእመናን ጠየቁ !

በተለያዩ የማኅበራዊ ሚዲያ አማራጮች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ዒላማ ያደረጉ የጥላቻ ንግግሮች እና መልእክቶች በአፋጣኝ እንዲቆሙ እና መንግስትም ሕጋዊ እርምጃ እንዲወስድ ቲኤምሲ ያነጋገራቸው ምእመናን ገልጸዋል።

ማናቸውም ቤተ እምነቶች መብቶቻቸው እንዲከበር እንደሚፈልጉትና የሃይማኖታቸውን አስተምህሮ በነጻነት ማስተላለፍ ሕገ መንግስታዊ መብታቸው እንደሆነ የጠቆሙት አስተያየት ሰጪ ምእመናኑ በተመሳሳይም ሁሉም ቤተ እምነቶች የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን እምነት እና አስተምህሮ ባከበረ መልኩ ሊንቀሳቀሱ እንደሚገባ ገልጸዋል።

ሁሉም ኢትዮጵያውያን የሃይማኖት ነጻነታቸውን ተጠቅመው በማናቸውም መልኩ ሃይማኖታቸውን ማራመድ ሕገ መኖግስታዊ መብታቸው ቢሆንም የሌላውን እምነት ማንቋሸሽ፣ ማኮሰስ እና ማጥላላት ፈጽሞ ተቀባይነት የሌለው እና ግጭት ቀስቃሽና ጸረ ሰላም እንቅስቃሴ መሆኑ ነው የተገለጸው።

ባለፉት ጊዜያት ከአንዳንድ ቤተ እምነት ተከታዮች ስለ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፣ ስለ ቅዱሳን፣ ስለ ንዋያተ ቅድሳት ብሎም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት በምታስተምቸው ትምህርቶች ላይ ትኩረት ያደረጉ የጥላቻ ንግግሮች ሲተላለፉ መቆየታቸው የሚታወስ ነው።

በተለይም መዋቅራዊ ድጋፍ እየተሰጠው በሚመስል መልኩ የጥላቻ ንግግሮች ተባብሰው መቀጠላቸው እና ይኸው ጥላቻም በኤሌክትሮኒክስ ሚዲያ ብቻ ሳይሆን በሜንስትሪም እና በመጽሐፍትም ጭምር ሲካሄድ መቆየቱ እና እየተካሄደ መሆኑ በርካታ ምእመናንን ያሳዘነና ያስቆጣ መሆኑ ተመላክቶአል።

መንግስት እነዚህን የጥላቻ አራማጆች እና ጸረ ሃይማኖት ግለሰቦችን በሕግ አግባብ እንዲጠይቅም ምእመናን ጥሪ አቅርበዋል።

@ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል


ስለ ሰሞኑ ጉዳይ ...
***
1. ያለሕግ ፍርድ የግድያ ቅስቀሳ ማድረግ ወንጀል ነው። እስከምናውቀው ድረስ ኢትዮጵያ ለሃይማኖት የማይወግን (secular) ሕገ መንግሥት ያላት ሀገር እንጂ በሸሪዓ የምትተዳደር ሀገር አይደለችም። በመሆኑም የሚያስቆጣ ነገር ሲኖር ወደ ሕግ መውሰድ እንጅ በደቦ ለመግደል መነሣት ትልቅ ስሕተት ነው። ሰው ሁሉ ፍርድን በእጁ አድርጎ መገዳደል ከጀመረ የሚነደው እሳት መጥፊያው ጭንቅ ይሆናል።
2. የሃይማኖት ውይይት (ክርክር) መደረጉ አስፈላጊ እና የማይቆም ነገር ነው። ሁሉም ሃይማኖቶች ዕቅበተ እምነት የመሥራት እና ሌላውን ወደራስ የማምጣት ኃላፊነት አለባቸውና።
3. በውይይቶች ምን ዓይነት መንገድ እንከተል? የሚለው ወሳኝ ነገር ነው። Double standard አያስኬድም። "እኔ እንደ ልቤ ልናገር። ሌሎች ግን እኔ እስከፈቀድኩት ልክ ብቻ ይናገሩ" ማለት ፍትሕ አይሆንም። ዘላለማዊ እውነትን ከሚፈልግ ሃይማኖተኛ የሚጠበቀው ለራስም ለሌሎችም አንድ አይነት መሥፈርት ማውጣት ነው። በመሆኑም አንዳንድ ጠንከር ያሉ የእቅበተ እምነት አካሄዶችን የሚያወግዝ ሰው በሁለቱም በኩል ያለውን ቢያወግዝ ቢያንስ ፍትሐዊ ይሆናል።
4. ከሰሞንኛው ችግር ተነሥተን የክርስትና-እስልምና ተዋሥኦ እንዴት ይሠራ? እኛ ላለንበት ሁኔታ ትክክለኛው ተግባራዊ አካሄድ የትኛው ነው? በሚሉ ጉዳዮች ላይ ውይይቶች ቢደረጉ ጥሩ ይመስለኛል።

ዲያቆን በረከት አዝመራው እንደጻፈው


አይ ኢቲቪ ስብከት ማስተላለፉ ሳያንስ ጭራሽ ለአፅዕኖተ ነገር እንዲሆን ቆርጦ በድጋሚ “የፍራንክሊን ግራሃም ስብከት” ብሎ ጫነ።

በነገራችን ላይ እንዲህ ያለ መድረክ ቀርቶ በዓመት በሚታወቁና በካሌንደር በሚዘጉ ሃይማኖታዊ በዓላት አከባበር በሚኖር የቀጥታ ሥርጭት የetv ኤድቶሪያል ፖሊሲ ጥቅል ሃሳብ ይህ ነው።

ማንኛውም የሃይማኖት በዓል የቀጥታ ሥርጭት ላይ ስብከት ወይንም ሃይማኖታዊ ትምህርቶች አይተላለፉም። ይህ ግን መልእክቶችንና ክዋኔዎችን አይመለከትም።

ለዚህም ነው ካያችሁ መስቀል ወይ ጥምቀት አከባበር በቀጥታ ሲሰራጭ ስብከት መርሐ ግብር ላይ ጋዜጠኞቹ ተሳታፊ እንግዳ በማስገባት ተሯሩጠው ሚያቋርጡት።

ዛሬ እንደመንፈሳዊ ጣቢያ የእገሌ ስብከት ቢል የቀድሞ ቤቴ ምን አገኘው ብዬ ነው እንጂ ለማን አማው ነበር?

ደግሞም አምቼውም አላውቅ!

ጋዜጠኛ መስከረም ጌታቸው እንደጻፈችው


DNE Africa በምንጮች መሠረት የኢትዮጵያ ወታደሮች በመምህርነት የሚያገለግሉትን መሪጌታ ገብረመድህን የተባሉ ዓይነ ስውር ካህን እና ከ10 እስከ 14 ዓመት የሆናቸው ሰባት ተማሪዎችን በኢትዮጵያ የአማራ ክልል ራያ ዓላማጣ አካባቢ ገድለዋል።






................የአክሊል ጉዳይ "..............

መፍትኄ ብትሆን ብየ ነው። አስተምህሮ ከሚለጠጥ

ከላይ የምንሰማው አንድ ድምጽ የለንም?

ስለ ወንድማችን አክሊል ቲክቶከሩም ፤ ዩትዩበሩም ልጁ ያለውንም ያላለውንም እየጨመረ እያውራ ሰዎች ከሚጨነቁ ፤ አስተምህሮዎችም በሆነ ባልሆነው ከሚንገላቱ አጭር መፍትኄ የለንም እንዴ ? አንዳንዴ የገበያ ግር ግር ለቀጣፊ ይመቻል እንዳይሆን እና ምናልባት ጉዳዩን አዠንዳ አድርጎ የሰጠን ይኖር ይሆን?ብሎ ቆም ብሎ ማሰብም ተገቢ ይመስለኛል ።

1ኛ የሊቃውንት ጉባኤ ውስጥ የሚሰሩ አባቶቻችን ልጁን ቀን ሰጥተው ፤ በፍቅር ጠርተው እርሱም ተዘጋጅቶ ፦ ከጉባኤ መምህራንም ፤ ከቲኦሎጅ መምህራንም ፤ በማኅበረ ቅዱሳን ውስጥ ከሚያገለግሉ ከምናውቃቸው ታላላቅ መምህራንም በቅርቡ ያሉ
አንድ ስድስት መምህራን ተጠርተው ሀሳቡን አቅርቦ በመጽሐፍ ቅዱስ ፤ በአበው አስተምህሮ ታይቶ ተመርምሮ
ባቋጭስ? ምክንያቱም እርሱም ለመታረም ዝግጁ ነኝ ያለ መስሎኛል ። ከአካሄዱ ጀምሮ የሚታረመውን አርሞ ፦ ልክ የሆነውን ልክ ነው ብሎ ፦ ልክ ያልሆነውን ሕዝቡ ሲሰማው ስለቆየ እርሱም እራሱ በራሱ ምክንያት አንድ ሰው ቢሰናከልበት ስለሚያስጠይቀው ፈቃደኛ ሁኖ ተወያይቶ ቢዘጋ ምን ችግር አለው ?

የሊቃውንት ጉባኤ አባላት አባቶቻችን ጉዳዩ ከሆነች ጎጆ ውስጥ ያሉ ሰዎች ጩኸት ብቻ አይደለም። ከሀገር ውስጥ እስከ ሀገር ውጭ ደርሷል። ይህንን አዠንዳ ማስተካከል እንዴት ተሳነው? ለልጁም ለቤተ ክርስቲያኗም እረፍት ነው። ሁሌም ከኔ ጀምሮ በያንዳንዱ አፍ ሲባረክ ሲረገም ከሚውል " እራሱ በተገኘበት ውይይቱ ሲጠናቀቅ ራሱም በዚህ ሀሳብ ልክ አይደለሁም እንዲል። ልክ የሆነበት ሀሳብ ደግሞ ይሄ ሰዎች እያጣመሙበት ወይም ያለ መረዳዳት ችግር እንጅ ልክ ነው ቢባል ምናለ?

↗️ ለቤ/ክርስቲያኗም ለምእመንም እኮ እረፍት ነበር ።እኔ ምድያ ላይ ተወያይቶ ከወደታች የኮሜንት በረዶ እየወረደ ምድያ ላይ ችግርን ማረምም ሆነ ማስተካከል የሚቻል አይመስለኝም ። የሀሳቡን ልብም ማግኘት አይቻልም። ምድያ ላይ የተሰራጨን ሁሉ በዚያው በምድያ ማስተካከል ጥሩ ነው። ነገር ግን ለማስተካከል ይ
የምንጓዝበትን ጉዞ ሁሉ በምድያ ማድረጉ አግባብ ውጤታማ አይመስለኝም። መፍትኄው ከተገኘ እና ከመረዳዳት በኋላ ከጅግሩ እስከ መፍትኄው በምድያ ማቅረብ የበለጠ ነው።ችግሩን ለይቶ ለማወቅም ለማሳወቅም ከዚያው ምድያ ላይ ከሆነ ግን ችግርን ጨምሮ ያርፋርል እንጅ ችግርን አይፈታም ።

↗️ በአጭሩ የሚቋጭ ቢሆን የእስከ ዛሬው የመምህራኑ ጥረት በቂ ነበርና። ለሁሉም ይህ ሁሉ ክርክር ለምን መጣ? ብላችሁ የምትደነግጡ ? የምትሸበሩ ምእመናን ትኖሩ ይሆን? ይህ የሆነው ሃይማኖታችሁ ድንቅ እጹብ ቢሆን ነው። የማርያም ነገር እንዲህ ነው ።መላእክት እንኳን ተጨምረው ቢያስቡት በእርሷ የተከናወነው ምሥጢር ክቡድ ነው። ሃይማኖታችሁ እንዲህ ነው።የማርያም ነገር ዛፎች ተሰብስበው ስለ እርሷ ቢያጨበጭቡ!! ተራሮች ተከማችተው ስለ ክብሯ ቢዘምሩ" የራሳችን ጠጒሮች አንድ ሁነው ቢያሸበሽቡ የማርያም ነገር የድንቅ ድንቅ ነው። ሃይማኖታችሁ ተራ ተረት ተረት አይደለም። ከሕሊና በላይ ነው።የማርያም ነገርም እንዲሁ ነው። ወላዕለ ኲሉ ሕሊና አይደለች። ማርያም ታማልዳለች አታማልድም ማለት ብቻ ሳይሆን በነገረ ድኅነት ያላት ድንቅ ሱታፌም እንደ ፋና ሲያበራ ይታያል።

አንድ ሊቅ ባለፈው በየ ዘመኑ በጥባጭ ጸሐፊ በጥባጭ ሊቅ መነሳት አለባት ያሉት ትዝ አለኝ። በጥባጭ መናፍቅ አይነሳ እንጅ በጥባጭ ሊቅማ ይነሳ። እንዲህ ያነቃቃልና። በስንፍና የረጋውን ሁከት መንፈሳዊ ሰጥቶ ይቀሰቅሰዋልና።

መምህር ጽጌ አስተርአየ እንደጻፉት


.....
በዚህ ጊዳይ ላይ ተመልሼ እመጣለሁ፤ ነገር ለጊዜው አክሊል ማብራሪያ ውስጥ ያለው ችግር መዋቲነትንና መለወጥን (mortalility and corruptibility) ጌታ ስለተዋሐደው ሥጋ ስንናገር የኀጢአት ውጤት የሆነ ሞትና ጉስቁልና አድርጎ ማቅረቡ ይታያል። ይህ የኔ እይታ ብቻ ከሆነና ራሱም ሆነ ሌላ ሰው እይታየን እንዳስተካክል ከረዳኝ አርማለሁ። የአክሊል መልእክት በሚዲያ የተላለፈ ስለሆነ እንጂ ጉዳዩን በሚዲያ ማንሣት ያለውን ጣጣ እረዳለሁ። በፍቅርና በእውነት ቤተ ክርስቲያንን ማእከል አድርገን ደግሞም ራሳችንንና የሚሰሙን ለማነጽ ከተነጋገርን ችግር አያመጣምና በዚህ መንፈስ እዩልኝ።

ሰላም ለሁላችን ይሁን!

መጋቤ ብሉይ አዕመረ አሸብር እንደጻፉት


የአክሊል ችግር ምንጩ ምንድነው?
...
ወንድማችን አክሊል ወደ አገልግሎት መመለሱ መልካም ነው፤ እግዚአብሔር የሰጠውን ጸጋ ለመጠቀምና ለቤተ ክርስቲያን ተልእኮ መሳካት ለማዋል ማበረታታት አለብን። እኔ በትጋቱና በብዙ መንገድ ምእመናንን እየጠቀመ ላለው አገልግሎቱ አድናቆት አለኝ። አድናቆቴን ከምገልጥባቸው መንገዶች አንዱ ስሕተት ሳይ እንዲያስተካክል መምከር እንቢ ካለም የሚሰሙት እንዳይሳሳቱ ማስተማር ነው።
....
በትጋት ሲያገለግል ምርቃትና ድጋፍ እንደሚሰጠው ሁሉ ስሕተት ሲሠራም ለመታረም ፈቃደኛ እንደሆነ እገምታለሁ፤ ለመታረም ፈቃደኛ ነኝ ብሎ ሲናገርም ስለሰማሁት ስሕተት የማይሠራና የማይታረም አድርጎ ራሱን አይቆጥርም ብየ አምናለሁ።
...
ከዚህ ቀደም ያሉኝን ልዩነቶች አገልግሎታችንን በማይጎዳና ፍቅርን መሠረት ባደረገ መንገድ አስተያየት ሰጥቻለሁ። አስተያየቶቼ ይዘትንም አካሄድንም የሚመለከቱ ነበሩ፤ በዚህ ጽሑፍ ግን መታረም አለመታረማቸውን መገምገም አልፈልግም።
....
አክሊል በቅርቡ በቪዲዮ ያስተላለፈውን መልእክት ሁለት ጊዜ ሰማሁት፤ አንድ ጊዜ የሰማሁት ሌሊት ከ9:30-10:35 ነው። ይህ ጊዜ ጸጥታ የሰፈነበት ስለሆነ በትክክል ሰምቼዋለሁ። ስሕተት ነው ብየ ያመንሁትን ነጥብ የለየሁት በዚህ ጊዜ ነበር። ተመልሼ ስሰማው ማስታወሻ ይዤ ቪዲዮ በየስፍራው እያቆምሁና መልሼ እያዳመጥሁ ነበር።
...
"ያልነሣውን አላዳነውም" የሚለው ርእስ የታወቀና የታመነ ንባብ ነው፤ የነሣውን በትክክል ዐውቀን በትክክል እየገለጥነው ነው ወይ? የሚል ጥያቄ ግን አለኝ።
...
ጥቅሱን ተገቢ ባልሆነ መንገድ እንደተረዳውና እንደተጠቀመው ተረድቻለሁ። እንደ አቻዎቹ ያለ ሥጋን ይዟል እያለ ደጋግሞ ይናገራል። የአክሊል እንደ አቻዎቹ ያለ ሥጋ ማለት ምን ማለት ነው? የአቻዎቹ ማለት የሁላችንም ሰዎች ሥጋ ማለት ነው። ክርስቶስ ገንዘብ ያደረገው ሥጋችንን ወይም ባሕርያችንን ነው። ባሕርያችን በተፈጥሮ አንድ ነው። የእኛ ሥጋ ኀጢአተኛ ሥጋ/ባሕርይ ግን መሆኑን አክሊልም አይክድም። የጌታ ሥጋም እንደ አቻዎቹ ያለ ሥጋ ከሆነ ኀጢአተኛ ሥጋ (ባሕርይ) ነው ማለት ነው? ይህን እያለ ከሆነ ስሕተት ነው። ቢያንስ ይህን አጥርቶ መናገርና ሰሚን ከማደናገር መታቀብ አለበት። የጌታ ሥጋ እንደ ሁላችንም የሰው ልጆች ሥጋ ነው። ይህም ማለት ሞት የሚስማማው ሥጋ ነው ማለት ነው። መዋቲነት፣ መታመም፣ መራብና መጠማት፣ መድከም እነዚህ ሁሉ የሥጋ (የሰው ባሕርይ) ገንዘቦች ናቸው እንጂ በኀጢአት ምክንያት በኋላ የመጡ አይደሉም።
....
የሳዊሮስና የአትናቴዎስን ትምህርት በትክክል ካነበበ መዋቲነት የሰው ተፈጥሮ ገንዘብ እንጂ የኀጢአት ውጤት አይደለም። ዲያቆን ያረጋል በተረጎመው የቅዱስ አትናቴዎስ መጽሐፍ ገጽ 160 ላይ
"ሕጉን መተላለፍ ሲጀምር ሰውን በባሕርዩ የነበረ መዋቲነትና መለወጥ (moryality and corruptibility) ገንዘቡ አድርጎ ወርሶታል" ይላል። በቅዱስ ሳዊሮስና በቅዱስ አትናቴዎስ ትምህርት መሠረት ሞት እንጂ መዋቲነት የኀጢአት ውጤት አይደለም። መዋቲነትና መለወጥ (mortality and coruptibility) የሰው የባሕርይ ገንዘቦች ናቸው። ኢመዋቲነትና አለመለወጥ ( immortality and incorruptinility) ደግሞ የእግዚአብሔር ብቻ የባሕርይ ገንዘቦች ናቸው። እግዚአብሔር ሰውን ኢመዋቲ ሊያደርገው ፈቃድም ችሎታም አለው እንጂ ኢመዋቲ አድርጎ አልረጠረውም።
....
አክሊል በሁሉም ንግግሩ ውስጥ ደጋግሞ ስለጌታ መዋቲነት ሲናገር በኀጢአት ምክንያት በሰው መዋቲነት እንደመጣበትና ጌታም ያን ገንዘብ እንዳረገ አስመስሎ ይናራል። ይህን ነጥብ ለብዙ ትምህርቱ ምንጭ አድርጎ እየተጠቀመው ስለሆነ አጥርቶ መረዳትና ማረም አለበት።
.....
ጌታ ሥጋን ገንዘብ ያደረገው ፦ በተፈጥሮው መዋቲ ከሆነ፣ በኋላም በኀጢአት ወድቆ ሞት ከሰለጠነበት ሥጋ ከፍሎ በሥጋዌ ምሥጢር በግብረ መንፈስ ቅዱስ በዐዲስ መልክ በድንግል ማርያም ማኀፀን የተፈጠረ ሥጋን እንጂ ሞት የሰለጠነበትን ባሕርይ ከሞት ነጻ ሳያወጣ አይደለም። በፈቃዱ ለሌሎች ቤዛ ሆኖ ከመሞት በቀር በጌታ የግድ ሞት የሌለበት በተፈጥሮው መዋቲነት ገንዘቡ የሆነ እንጂ ሞት በኀጢአት ምክንያት ያልሰለጠነበት ሥጋን ገንዘቡ በማድረጉ ነው።
...
የእኛ ሥጋ በተፈጥሮው ከጌታ ሥጋ ጋር አንድ ብቻ አይደለም። በኀጢአተኛነቱና ሞት የሰለጠነበት በመሆኑም የተለየ ነው። የጌታ ሥጋ መዳንን የማይፈልግና ከቃል ጋር በመዋሐዱም አዳኝ ነው። ይህን ነጥብ አክሊልም በስሱ አንሥቶታል። ነገር ግን በጉሕህ መነሣት ያለበት ይህ ልዩነትም እንጂ ባሕርያዊ አንድነቱ ብቻ አይደለም። የጌታ ሥጋ እንደ እኛ ነው ብለን በደፈናው ብንሰብክማ ሞት ችግር ያመጣል። ጌታ ሥጋችንን ሲዋሐድ የሰውን ባሕርይ ከኀጢአት በፊት ወደ ነበረው ክብር ብቻ ሳይሆን ወደማይነገር ታላቅ ክብር ያወጣው መሆኑን አክሊል ከተናገረውም ይገኛል።
....
ሳዊሮስና ዩልያኖስ የተለያዩበት ነጥብ ሰው ከኀጢአት በፊት መዋቲ ነው/አይደለም የሚል ነበር። ዩልያኖስ መዋቲ አልነበረም። ኢመዋቲ ነው ብሎ አስተማረ። ሰው ኀጢአት ሲሠራ መዋቲ ሆነ አለ። ስለዚህም ጌታ የለበሰው ሥጋ አዳም ከመበደሉ በፊት የነበረው ሥጋ ነው። ሞት አይስማማውም። የሞተውም በፈቃዱ ነው እንጂ የሚስማማው ሥጋ ስላለው አይደለም አለ። መዋቲነት የኀጢአት ውጤት ነው ብሎ ማመኑ ጌታ መዋቲ ሥጋን ሊዋሐድ አይችልም እንዲል አደረገው። ሳዊሮስ ግን መዋቲነት የሰው ተፈጥሮ ገንዘብ እንጂ የኀጢአት ውጤት አይደለም። የኀጢአት ውጤት ሞት እንጂ መዋቲነት አይደለም አለ። ልዩነቱ ካልገባን ቀጣይ አጽፋለሁ።
...
ጌታ ሰው ሲሆን መዋቲ ሥጋን ገንዘብ ማድረጉ የሰውን ተፈጥሮ መዋሐዱ ነው። ነገር ግን የአዳም ባሕርይ መዋቲነቱ ኢመዋቲ የመሆን እድል ነበረው። ይህን እድል በበደለ ጊዜ አጣ። በቅዱስ አትናቴዎስ አገላለጽ ኀጢአት የነበረውን እድል ማጥፋትዋ ብቻ ሳይሆን ሰውን ወደ አለመኖር እንዲመለስ ጉዞ አስጀምራው ነበር። ኀጢአት የሰውን ክብርና እድል ብቻ ሳይሆን ህልውናውን ለማጥፋት ጉዞ አስጀምራው ነበር። ነገር ግን የፈጠረን እግዚአብሔር ራራልንና ከጥፋት መንገድ መለሰን።
...
ጌታ መዋቲነትን በተዋሕዶ ጊዜ ያላጠፋው ስለማይችል ሳይሆን እንዲያድንበት ፈልጎ እንዳይጠፋ ስለፈቀደ ነው። ሞትን በፈቃዱ ለመቀበልና በእርሱ ሥጋ ለማጥፋት መዋቲነቱ መቆየት ነበረበት። መዋቲነቱን በተዋሕዶ ጊዜ ከራሱ ሥጋ ላይ ካጠፋው እርሱ ኢመዋቲ ይሆናልና ሞቶ ቤዛ ሊሆነን አይችልም። "በሞቱ ለሞት ደምሰሶ" እንዳለው ሞትን አግኝቶ ሊውጠው ወይም ሊያጠፋው አይችልም። ሞት ጌታን መያዝና ማጥፋት አይችልም። እርሱ ንጹሕ ነውና በፈቃዱ ካልሆነ ሊይዘው አይችልም። በፈቃዱ ሊይይዘው የቻለው ደግሞ ሞትን ለማጥፋት ራሱ ስለፈለገ ነው እንጂ ሊሞት ስለተገደደ አይደለም። ይህ ነጥብ በአባቶች ትምህርት በዝርዝር የተገለጠ ነው። አትናቴዎስና ሳዊሮስ ደግሞ ይበልጥ አብራርተውታል።


ጥቅስን ማንም አንባቢ ይጠቅሰዋል፡፡ በልኩና በዐውዱ መረዳት ግን ለኹሉም አይደለም፡፡ ዐይነ ልብ ላላቸው ብቻ ነው፡፡
ስለ አንዱ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ዐለም መግባባት ያልቻለው ኹሉም እንደ ፍላጎቱ መጽሐፍ ቅዱስን ስለሚጠመዝዘው ነው፡፡
መጻሕፍት ሲነበቡ ቢያንስ ከ Textual Analyisis; comparativ Study; Historical Context አንጻር ማየትግዴታ ነው፡፡ ዐውቀንም ይኹን ሳናውቅ በእኛ ዘንድ Eisegetical reading/ንባብን በራስ ፍላጎት ብቻ መቆልመም ከተለመደ፥
ቅድስት ቤተክርስቲያን ነገ በእጅጉ ትፈተናለች፡፡
በሰሞነኛው ውርክብ ዙርያ ይኽን የወንድማችንን መጽሐፍ ማንበብ፥ መደበኛውን ኦርቶዶክሳዊ ትምህርት ለማወቅ ያግዛል፡፡

ሊቀ ሊቃውንት ስሙር አላምረው


1) የሞተችው ለመበስበስ ሳይኾን የትንሣኤን አካል ገንዘብ ለማድረግ ነው። ይኸውም ኢመዋቲ አካልን ገንዘብ ለማድረግ እንጂ ለመበስበስ አይደለም። ይህ ዮሐንስ ዘደማስቆ በመደነቅ የገለጸው ነው። ሰውነቷ እንዲበሰብስ ልጇ አለመፍቀዱን ሞታ መበስበስ ሳያገኛት ከልጇ ትንሣኤ በኋላ በልጇ ሥልጣን በሦስተኛው ቀን መነሣቷን ብዙዎቹ ቅዱሳን ሊቃውንት የገለጹት እና እኛም የምናምነው ነው።

2) የሞተችው ሰው ስለ ኾነች ነው። አምላክ በመውለዷ ምክንያት በሕሊናቸው ሰው አይደለችም የሚሉ ሰዎች እንዳይኖሩና በእርሷ ሰው የመኾን ጉዳይ ጥርጣሬ እንዳይፈጠር ሞትን ትቀምስ ዘንድ ልጇ ፈቅዷል። ይህ እነ አብሮኮሮስ በአጽንዖት ያስረዱት ነው። ይህ ምክንያት ቃል ሰው አልኾነም የሚለውን ክሕደትናና እርሷም ሰው አይደለችም የሚለው ስሕተት የሚያርም ነው።

3) ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ እንዳለው ያረፈችው የልጇን የሞት ጽዋ ለመቅመስ ነው። ይህም እንዲኾን የእርሱ ፈቃድ ነው።

4) ሞቷ የመሸነፍ ሳይኾን የክብር እና የድል እንደ ኾነ እንድናውቅ ነው። ይህን ለመረዳት የሞቷን ዜና ከልጇ ዘንድ የተላከው ቅዱስ ገብርኤል ሊያበሥራት ሲመጣ የድል ምልክት የኾነውን የዘንባባ ዝንጣፊ ይዞ መምጣቱን እነ ማክሲሞስ ተናዛዚው የቀደሙ ትውፊቶችን ማዕከል አድርገው "The Life of The Virgin" በሚለው መጽሐፍ ዘግበዋልና።

5) ሞቷ ተራ ሞት ሳይኾን በመደነቅና በመገረም የሚናገሩት ሞት ነው። ቅዱስ ያሬድ "ማትሰ ለመዋቲ ይደሉ ሞታ ለማርያም የአጽብ ለኲሉ" - ሞትማ ለሚሞት ይገባል የማርያም ሞት ግን ለኹሉ ያስደንቃል" የሚለው ለዚህ ነው። እንደ በሥጋና በደም ኾነን በድፍረት ከመናገር ልንቆጠብና ልናደንቅ ይገባል።

ዲያቆን ዮሐንስ ጌታቸው እንደጻፈው


የጎሠቆለ ባሕርይ (Fallen Nature)

ይህን ጉዳይ ትንሽ ዘርዘር አድርጎ ለመረዳት አዲሱን "ዐይነ ልቡና" የሚለውን መጽሐፌን ይመልከቱ። አምስት ኪሎ "ሰርዲኖስ የመጻሕፍት መደብር" ዋና አከፋፋይ ኾኖ በሌሎችም የመጻሕፍት መደብር ታገኙታላችሁና። ዛሬ በአጭሪ ላቀርብ ወዳሰብኹት ጉዳይ ልግባ።

የጎሠቆለ ባሕርይ የሚባለው በዋነኛነት አዳም ከበደለ በኋላ የኾነው ነው። አዳም ከውድቀቱ በኋላ የሰውነት ባሕርዩ አልተለወጠም። ከውድቀት በፊት ኾነ ከውድቀት በኋላ በሰውነት ለውጥ የለምና። ነገር ግን ከውድቀት በፊት በንጹሕ ባሕርይ መልክአ እግዚአብሔሩ ሳይደክም፤ የጸጋ ልብስን ለብሶ በፍጥረት ላይ የገዥነትን ሥልጣን ተጎናጽፎ በክብር ይኖር ነበረ። ሕገ እግዚአብሔርን ተላልፎ በወደቀ ጊዜ ግን የባሕርይ ውድቀት (ሕማም) ወይም ንዴተ ህላዌ (የባሕርይ ድህነት) ገጠመው።

- Fallen Nature በዋነኛነት የመልክአ እግዚአብሔር መድከምን፦ አዳም የተፈጠረው በእግዚአብሔር መልክ ነው። ያን በተፈጥሮ የተሰጠውን መልክአ እግዚአብሔር ሙሉ በሙሉ ባያጣውም በሕግ መተላለፉ ምክንያት አደከመው። አንዱና ዋነኛው የጎሠቆለ ባሕርይ ምልክት ይህ ነው። ኹለተኛው የጎሠቆለ ባሕርይ የሚባለው ከጸጋ እግዚአብሔር የተራቆተ፦ ማለትም እግዚአብሔር አልብሶት የነበረውን የብርሃን ልብስ ያወለቀ፥ የእግዚአብሔር ልጅነትን ያጣ ባሕርይ ነው። ሦስተኛ ከባሕርዩ መጎሥቆል የተነሣ ለኃጢአት የሚያዘነብል መኾን ነው። አራተኛ ጉሥቁል ባሕርይ ያለው ሰውነት ርግማንን ተሸክሟል። ይኸውም መርገመ ሥጋ መርገመ ነፍስ ነው። በሥጋው ወደ መቃብር ገብቶ መበስበስ (ሞተ ሥጋ)፤ በነፍሱ ወደ ሲኦል መግባት ነው (ሞተ ነፍስ) ዋናው ሞተ ነፍስ ከእግዚአብሔር መለየት ገጥሟቸዋል። ስለ ርግማን ሞት ስናነሣ በዋነኛነት የነፍስ ከሥጋ መለየትን ብቻ ሳይኾን የሥጋን ወደ መቃብር ገብቶ መበስበስ፣ የነፍስን ከእግዚአብሔር መለየት (ሞታ ለነፍስ ርሒቅ እም እግዚአብሔር እንዲል ሊቁ ቅዱስ ያሬድ) ይህን ይመለከታል። የሐዲስ ኪዳንን ሞት ለመረዳት "ዐይነ ልቡና" የምትለውን መጽሐፌን ይመልከቱ። እነዚህ በመሠረታዊነት ሰውነትን የጎዱና ያደከሙ ናቸው።

-በባሕርዩ መጎሥቆል ምክንያት የመጡ ጎጂ ያልኾኑ ኹኔታዎች ወይም ሕማማት ዘአልቦቱ ኃጢአት (blemeless Passions) ኃጢአት አልባ ሕማማትን መቀበል ግን በአምላካችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስለኛ ተብሎ በፈቃዱ ለቤዛነት ብሎ የተቀበላቸው ናቸው፤ እመቤታችን ደግሞ ሰው እንደ መኾኗ ያን እንድትቀበል ልጇ ወዳጇ ኢየሱስ ክርስቶስ ፈቅዷል። ስለዚህም ተርባለች፣ አዝናለች፣ ተሠቃይታለች፣ ሞታለች። እነዚህ ኹኔታዎች በራሳቸው ኃጢአቶች አይደሉም። እንደ ነውርና ርኲሰትም አይቆጠሩም። ጌታችንም እነዚህን ስለኛ ብሎ የተቀበለው በዚህ ምክንያትና ስለኛ ቤዛ ሊኾነን ነው። ይሄን የተቀበለው ደግሞ ሥግው ቃል እንደ መኾኑ ነው። ስለኛ መራቡን፣ መጠማቱን፣ መገረፉን፣ የእሾህ አክሊል መቀዳጀቱን፣ መራራ ሆምጣጤ መጠጣቱን፣ በመስቀል ላይ ዕርቃኑን መሰቀሉን፣ መሞቱን በእውነት የተቀበላቸው ቤዛ ሊኾነን እንጂ ያን በመቀበሉ ምክንያት የጎሠቆለ ባሕርይን ለብሷል ለመሰኘት አይደለም። ቃል ከሥጋ ከተዋሐደ በኋላ ሥግው እንደ መኾኑ ለቤዛነት የተቀበላቸውን ነገሮች የማዳን ሥራ (Economy of Salvation) እንላለን እንጂ በሌላ መንፈስ እንዲታይ ፈጽሞ አናደርግም።

እነዚህን ነገሮች ሥግው ቃል በፈቃዱ ያደረጋቸው ናቸው። ብዙ ቅዱሳን ሊቃውንትም ቅዱስ ቄርሎስ፣ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ፣ ቅዱስ ያሬድ፣ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ... "ኅሥሩ" -"ጉሥቁል" ሥጋን ነሣ ሲሉ በአንድ በኩል ከደካማው አዳም ሰውነት የተከፈለውን ሰውነት መንሣቱን ለማሳየት ሲኾን በሌላ በኩል በፈቃዱ ሕማም፣ መከራና ሞት የሚስማማውን ሰውነት ገንዘብ ማድረጉን ለማመልከት ነው። ከዚህ ውጭ ከላይ በዋነኛነት የወደቀ ባሕርይን የሚገልጡ ነገሮች ያሉበትን ሰውነት ለበሰ ለማለት አይደለም። ለዝርዝሩ "ዐይነ ልቡናን" ይመልከቱ። በነገራችን ላይ አኹን እንኳን እኛ ኦርቶዶክሳውያን አምነን፣ ተጠምቀን በቅብዐ ሜሮን ከብረን ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀብለን የክርስቶስ አካል ከኾን በኋላ blemeless passions የሚባሉት ያልቀሩልን በራሳቸው ክፉዎች ስላልኾኑ ነው። እነዚህ ነገሮች አዲስ ሰውነትን ገንዘብ አለማድረግን የሚያመለክቱ አይደሉም። ይኸውም ማለት በጥምቀት ከአሮጌ ማንነት ወጥተን ክርስቶስን ለብሰን አዲስ የምንኾን መኾናችንን የሚያስቀሩ አይደሉምና። ከአሮጌ ማንነት በጥምቀት ከተላቀቅን በኋላ መልሰን ባረጀ ሰውነት ውስጥ እንዳለን አድርገን አንናገርም። በትንሣኤ አኹን ከለበስነው የበለጠ የከበረ ኢመዋቲ ኢድኩም ወኢሕሙም የኾነ ሰውነትን መልሳችንን ፍጽሙ ድኅነት ከትንሣኤ በኋላ መኾኑን የሚያረጋግጥ እንጂ አኹን ብትጠመቁም አሮጌ ማንነት ውስጥ ነው ያላችሁ የሚያስብል አይደለም። ሌላው ቀርቶ ያን አዳም በገነት እያለ ያወለቀውን የብርሃን ልብስ ስንጠመቅ እንለብሰዋለን (በተለይ ቅዱስ ኤፍሬምና ቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ በትኩረት ይህን ያስተምራሉና) ነገር ግን ለኛ ለዐይነ መጭማጮች ከተጠመቅንም በኋላ ያን የብርሃን ልብስ መልበሳችን አለመታየቱ ያለመልበሳችን ማረጋገጫ ሊኾን አይችልም። ነገር ግን በግልጽ አኹን ያን ልብስ መልበሳችንን ማየት ባንችልም ከትንሣኤ በኋላ ተገልጦ እናየዋለን። ያኔ የሚገለጠው ግን ላልተጠመቁ ሳይኾን በጥምቀት ለከበሩት ክርስቶስን ለለበሱ ነው። ይህን ልብ ማለት ይገባል።

- አካላዊ ቃል የተዋሐደው ሥጋ ንጹሕ ሥጋ ነው። ምንም ዓይነት ነውርና ነቀፋ የለበትም። መንሣትና መዋሐድ ያለመቀዳደም የኾነ ስለ ኾነ ከእመቤታችን የነሣው ሰውነት ንጹሕና ነውር ነቀፋ የሌለበት ነው። የኃጢአት ጠባሳም አላገኘውም። ጸጋን የተመላ፣ መልክአ እግዚአብሔሩ ያልደከመ፣ ኃጢአት ያልገዛው፣ መርገም ያላረፈበት ንጹሕ ሰውነት ነው። ቅድስት ድንግል ማርያም የተጠበቀችው የጉሥቁልና ውጤት ከኾነው ከጸጋ መራቆት፣ ከመልክአ እግዚአብሔር መድከም፣ ለኃጢአት ከማዘንበል፣ ከመርገመ ሥጋ ወነፍስ፣ ከልማደ አንስት በወሊድ ጊዜ ከሚመጣ ምጥ ኹሉ ነው። ይህ ከእርሷ በቀር ከሰው ወገን ለማንም ቀድሞ የተደረገ አይደለም። ስለዚህም ምክንያት በዋነኛው የውድቀት ምልክት አንጻር አድርገን ስናይ እርሷ የወደቀ ሰውነትን ገንዘብ እንዳታደርግ ልጇ ጠብቋታል እንላለን። የእርሷን ሕይወት በልዩ ኹኔታዎች እንዲመላ ያደረገው እርሱ አምላኳ ነውና። የጎሠቆለ ሰውነትን አልለበሰችም ስንል ሕማም፣ ኀዘን፣ መከራ፣ ሞት የማይስማማውን ሰውነት ገንዘብ አድርጋለች ማለታችን አይደለም። ይህን የሚልም አይኖርም ይልቅስ ከላይ እንዳልኹት ከዋነኛው የጒሥቁልና ውጤት መጠበቋን ማዕከል በማድረግ የወደቀ ሰውነትን አልለበሰችም እንላለን። አበውም ያስተማሩት በዚህ አግባብ ነው። በዝርዝር የእርሷን ጉዳይ ለመረዳት "ዐይነ ልቡና" ይነበብ። ልጇ በፈቃዱ ስለኛ የሞተው በማስመሰል ሳይኾን በአማን ነው። ሞትንም በፈቃዱ የተቀበለው ያ ሥጋ የዕሩቅ ብእሲ ሥጋ ሳይኾን የሥግው ቃል ሥጋ ነውና። ሞትን ስለኛ የተቀበለው ሥጋ ራሱ ለኛ ሕይወትን የሚያድል ነው። የሞተውም ሊበሰብስ ሳይኾን ሞትን በሞቱ ገድሎ ሞት የወረሰውን ሰውነት ሕይወት ሊያለብሰው ነው። ይህ የቅዱስ አትናቴዎስና የቅዱስ ቄርሎስ የትምህርት ማዕከል ነው።

እመቤታችን ለምን ሞተች? መልሱ በአጭሩ፦

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.